Risalah

Risalah Islamic Affairs , Islamic Knowledge , Muslim , Entertainment

የ60 ሚሊዮን ብር መኪና ስጦታ ተበረከተላቸው‼=================================✍ በአሁኑ ወቅት በሃገረ ሳዑዲ የሚገኙት እውቁ ባለሃብትና ኢትዮጵያዊው ቢሊዬነር ሸይኽ ሙሐመ...
16/06/2022

የ60 ሚሊዮን ብር መኪና ስጦታ ተበረከተላቸው‼
=================================
✍ በአሁኑ ወቅት በሃገረ ሳዑዲ የሚገኙት እውቁ ባለሃብትና ኢትዮጵያዊው ቢሊዬነር ሸይኽ ሙሐመድ ሑሴን አል-አሙዲ አዲስ ለተተኩት የመጅሊሱ አመራሮች እና ዑለማዎች ዘመናዊ መኪናዎችን በስጦታነት አበርክተዋል።

አል-አሙዲ ከ60 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ ከሃገረ ጃፓን ያዛዟቸውን እያንዳንዳቸው ከ20, 000, 000 ብር በላይ የሚሆኑ ③ የ2022 ሞዴል NISSAN መኪኖች አዲስ ለተመረጡት የመጅሊሱ ፕሬዝዳንት ለሸይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ፣ ለቀድሞ የመጅሊስ ዋና ፕሬዝዳንት ለ"ሐጂ" ዑመር ኢድሪስ እና ለቀድሞ ምክትል ፕሬዝዳንታቸው ለዶ/ር ጄይላን ኸዽር በስጦታ አበርክተዋል። የቀድሞ የመጅሊሱ ፕሬዝዳንት ስጦታው ከተሰጣቸው ዋል አደር ብሏል።

ስጦታው የተበረከተላቸው የህዝበ ሙስሊሙን አንድነት በማስጠበቅ ለህዝበ ሙስሊሙ እየለፉ ያለውን ጥረት ለማበረታት መሆኑ ታውቋል።

ስጦታውንም የሚድሮክ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ጀማልን ጨምሮ በርካታ ኡስታዞች፣ የፌደራል መጅሊሱ የሥራ አመራር አባላት በተገኙበት በመጅሊሱ ጊዜያዊ ፕሬዝዳንት ሸይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ መኖሪያ ቤት በመገኘት አበርክተዋል።

ስጦታው ከተበረከተላቸው አካላት መካከል አንዱ የሆኑት የቀድሞው የመጅሊስ ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ጀይላን ኸድር በዚህ ፕሮግራም ላይ እንዲህ ማለታቸው ተነግሯል፦
«እኔ ለሙስሊሙ አንድነት ስል ያለምንም ቅሬታ ከቦታዬ እንደተነሳሁት ሁሉ፣ እንዲሁም የቀድሞ መጅሊስ ፕሬዝዳንት ሸይኽ ሙሐመድ አሚን ለሰላም ሲሉ ይህንኑ እንዳደረጉት ሁሉ፣ "ሐጂ" ዑመር ኢድሪስ የሙስሊሙን አንድነት ለማስጠበቅ ሲሉ ለአዲሱ አመራር ስልጣናቸውን በሰላም እንዲያስረክቡ ጥሪዬን አስተላልፋለሁኝ።»

[ዶ/ር ጀይላን ኸዽር ዛሬ በሸይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ የዚያራ ፕሮግራም ላይ ከተናገሩት]

ማሻ አላህ ብለናል። የተጣለባቸውን አማና በአግባቡ እንዲወጡ አደራ እንላለን። አላህ ይገዛቸው። የህዝብ ንብረት ከመዝረፍ ወይ ሠርቶ ወይ ተሰጥቶ ማግኘት ይበልጣል።
||
t.me/MuradTadesse
twitter.com/MuradTadesse

ስሟ በጦርነትና በረሃብ፣ በችግር በመከራ ብቻ ሲጠራ የኖረችው አገር ዛሬ ኢንተርናሽናል የቁርአን ሂፍዝ ወድድ ጠርታ በሰላም አጠናቃለች። ሰላም ወዳዱ የኢትዮጵያ ህዝብ ይህ ፕርግራም በሰላም ተ...
13/06/2022

ስሟ በጦርነትና በረሃብ፣ በችግር በመከራ ብቻ ሲጠራ የኖረችው አገር ዛሬ ኢንተርናሽናል የቁርአን ሂፍዝ ወድድ ጠርታ በሰላም አጠናቃለች። ሰላም ወዳዱ የኢትዮጵያ ህዝብ ይህ ፕርግራም በሰላም ተጠናቆ የሰላም ስማችን ከፍ ብሎ እንዲታይ በማድረግህ ምስጋና ይገባሀል።

የመጡት እንግዶች ነገ ወደ አገራቸው ሲሄዱ በቴሌቪዥን ጣቢያቸው ላይ ቀርበው ስለኢትዮጵያ ህዝብ ሰላምና ፍቅር አንድነት ሲናገሩ እናያቸዋለን።

ሀይማኖታችንን አምነን ለአገራዊ ግንባታና ለሰላም ከተጠቀምነው ሁላችንም የአገራችን አምባሳደር ነን ማለት ነው።
አንድ አገር ስንከባበር አንድ ስንሆን አንዳችን የሌላውን ስናከብር አልፈንም ስናስከብር ሁላችንም ተጠቃሚወች ነን።

ሱሌማን አብደላ

የደስታ እንባበዛሬው የስታዲየሙ የአለም አቀፉ የቁርዓን ውድድር ላይ እውቁ የሀገራችን አሊም ሼይኽ ሰዒድ አህመድ ሙስጠፋ በምስሉ ላይ እንደምትመለከቱት የደስታ እንባ ሲያነቡ ይታያል::በዛሬው ...
13/06/2022

የደስታ እንባ

በዛሬው የስታዲየሙ የአለም አቀፉ የቁርዓን ውድድር ላይ እውቁ የሀገራችን አሊም ሼይኽ ሰዒድ አህመድ ሙስጠፋ በምስሉ ላይ እንደምትመለከቱት የደስታ እንባ ሲያነቡ ይታያል::

በዛሬው ታሪካዊ ፕሮግራም ስኬት ሁላችንም ተደሰተናል፣ የደስታ እንባ አንብተናል::

የሀበሾች ክብር በሌሎች አንደበት ሲነገር ውስጥ ድረስ ይነዝር ነበር:: ማንባትም ሲያንስ ነበር

አቡዳውድ

13/06/2022

በሀገራችን የመጀመሪያው አለም አቀፉ የቁርዓን እና የአዛን ውድድር እንዲህ ውብ እና ስኬታማ በመሆን ፍፃሜውን ማግኘት ችሏል!አልሐምዱሊላህ
13/06/2022

በሀገራችን የመጀመሪያው አለም አቀፉ የቁርዓን እና የአዛን ውድድር እንዲህ ውብ እና ስኬታማ በመሆን ፍፃሜውን ማግኘት ችሏል!

አልሐምዱሊላህ

በአዲስ አበባ ስታዲየም ለሚካሄደው የአለም አቀፍ የቁርዓን ውድድር ፕሮግራም ላይ ለመካፈል ህዝበ ሙስሊሙ ወደአዲስ አበባ ስታዲየም እየተመመ ይገኛል።Akkas kunoo ummanni dorgomm...
13/06/2022

በአዲስ አበባ ስታዲየም ለሚካሄደው የአለም አቀፍ የቁርዓን ውድድር ፕሮግራም ላይ ለመካፈል ህዝበ ሙስሊሙ ወደአዲስ አበባ ስታዲየም እየተመመ ይገኛል።

Akkas kunoo ummanni dorgommii Qur'aanaa irratti argamuuf ganamarraa hiriira galee jira

ሃላባ
13/06/2022

ሃላባ

በኢትዮጵያ የመጀመሪያው አለም አቀፉ የቁርዓን ውድድርበአዲስ አበባ ስታድየምህዝበ ሙስሊሙ ከጠዋት ጀምሮ የአላህ ቃል የሆነውን ቁርዓን ለማላቅ እና ውድድሩን ለመታደም ወደ ስታዲየም እየተመመ ይ...
13/06/2022

በኢትዮጵያ የመጀመሪያው አለም አቀፉ የቁርዓን ውድድር
በአዲስ አበባ ስታድየም

ህዝበ ሙስሊሙ ከጠዋት ጀምሮ የአላህ ቃል የሆነውን ቁርዓን ለማላቅ እና ውድድሩን ለመታደም ወደ ስታዲየም እየተመመ ይገኛል::

የመግቢያ ትኬት አልያዝኩም በሚል ማንም ሰው መቅረት የለበትም::

Address

Bole
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Risalah posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share