Christian Independent/ክርስቲያን ኢንዲፔንደንት

Christian Independent/ክርስቲያን ኢንዲፔንደንት ክርስቲያን ኢንዲፔንደንት ክርስቲያናዊ ገለልተኛ ሚዲያ ሲሆን በአማኞች ፤ በቤተክርስቲያን እንዲሁም በመንፈሳዊ ጉዳዮች የሚያተኩር የመረጃ ምንጭ ነው፡፡

ክርስቲያናዊ ዜናዎች፣ ዝማሬዎች፣ ስብከቶች፣መፅሐፍ ቅዱስን መሰረት ያደረጉ ፅሁፎች እንዲሁም ምስክርነቶች የሚቀርቡበት ገፅ ነው።

 ።የኬንያ ፕሬዚዳንት ዊልያም ሩቶ ናይሮቢ በሚገኘው ቤተ መንግሥታቸው ትልቅ ቤተ ክርስቲያን ሊገነቡ እንደሆነ አሳወቁ።ሩቶ ለቤተ ክርስቲያኑ ግንባታ ራሳቸው ወጪያቸውን እንደሚሸፍኑ ገልጸው የማ...
05/07/2025


የኬንያ ፕሬዚዳንት ዊልያም ሩቶ ናይሮቢ በሚገኘው ቤተ መንግሥታቸው ትልቅ ቤተ ክርስቲያን ሊገነቡ እንደሆነ አሳወቁ።

ሩቶ ለቤተ ክርስቲያኑ ግንባታ ራሳቸው ወጪያቸውን እንደሚሸፍኑ ገልጸው የማንም ፈቃድ እንደማያስፈልጋቸው አጽንኦት ሰጥተዋል።

"ቤተክርስቲያን ለመገንባት የማንም ይሁንታ አያስፈልገኝም። ሰይጣንን ሊያበሳጨው ይችላል እናም የፈለገውን ማድረግ ይችላል" ሲሉ ሩቶ አርብ ዕለት ተናግረዋል።

የፕሬዚዳንቱ ንግግር በሳቸው አመራር የቤተ ክርስቲያንን እና የመንግሥት በጽኑ መጣመር ቀድሞውኑ የሚተቹት ኬንያውያንን አበሳጭቷል።

ቢቢሲ የኬንያ መንግሥትን አስተያየት እንዲሰጠው ጠይቋል።

ለተጨማሪ መረጃ የፌስቡክ ገፃችንን ይከታተሉ
https://www.facebook.com/CInewsethiopia

እውቁ የወንጌል አገልጋይ ጂሚ ስዋጋርት በ90 ዓመታቸው አረፉ። ጂሚ ስዋጋርት ሚኒስትሪ በፌስቡክ ገጹ ይፋ እንዳደረገው ዛሬ ማክሰኞ ጠዋት አገልጋዩ ጂሚ ስዋጋርት ወዳገለገለው ጌታ ተሰብስቧል ...
01/07/2025

እውቁ የወንጌል አገልጋይ ጂሚ ስዋጋርት በ90 ዓመታቸው አረፉ።

ጂሚ ስዋጋርት ሚኒስትሪ በፌስቡክ ገጹ ይፋ እንዳደረገው ዛሬ ማክሰኞ ጠዋት አገልጋዩ ጂሚ ስዋጋርት ወዳገለገለው ጌታ ተሰብስቧል ሲል ገልጿል።

ባለፈው ወር ጁን 15 በልብ ህመም ሆስፒታል የገባ ሲሆን ዛሬ ማለዳ ወዳገለገለው ጌታ መሄዱን ሚኒስትሪው አስታውቋል።

ጂሚ ከ8 ዓመቱ ጀምሮ ህይወቱ እስካለፈበት ጊዜ ድረስ በታማኝነት ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን ሲያገለግል መቆየቱን ሚኒስትሪው በፌስቡክ ገጹ አሳውቋል።

ከ1969 ዓ.ም በራድዮ፡ በ1970 በመጽሄት ህትመት እና በ1973 ጀምሮ ደግሞ በቴሌቭዥን የወንጌል አገልግሎት ይታወቃል።

ጂሚ በተለይ በ1987 ዓ.ም በብራዚል ሪዮ ዲ ጃኔሮ በነበረው የወንጌል ክሩሴድ ከ127 ሺህ ሰዎች ወንጌል ሰምተዋል።

ጂሚ ስዋጋርት በተደጋጋሚ የወሲብ ቅሌት ስሙ የሚነሳ የነበረ ቢሆንም በንስሃ ተመልሶ ሲያገለግል ነበረ።
ተሶሼትድ ፕሬስ እና ክርስቲያን ፖስት ናቸው ያስነበቡት።
ለተጨማሪ መረጃ የፌስቡክ ገፃችንን ይከታተሉ
https://www.facebook.com/CInewsethiopia

ISIS በሶሪያ 25 ክርስቲያኖችን ገደለጥቃቱ የተፈጸመው በደማስቆ የግሪክ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ነው። አጥፍቶ ጠፊ ባደረሰው ፍንዳታ ከሞቱ 25 ሰዎች በተጨማሪ 59 ጉዳት ደርሶባቸ...
24/06/2025

ISIS በሶሪያ 25 ክርስቲያኖችን ገደለ

ጥቃቱ የተፈጸመው በደማስቆ የግሪክ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ነው። አጥፍቶ ጠፊ ባደረሰው ፍንዳታ ከሞቱ 25 ሰዎች በተጨማሪ 59 ጉዳት ደርሶባቸዋል።

እሁድ ጠዋት ክርስቲያኖች ቅዱስ ኤሊያስ በተባለው ቤተ ክርስቲያን ለጸሎት ተሰብስበው ነበረ። ጥቃት አድራሹ ወደ ቤተ ክርስቲያኑ ገብቶ ተኩስ ከከፈተ በኋላ የአጥፍቶ ማጥፋት ፍንዳታውን እንዳደረገ ተገልጿል።

በግሪክ ኦሮቶዶክስ ቤ/ክ የአንጾኪያ ፓትሪያርክ አደጋውን አስመልክተው በሰጡት መግለጫ ጸሎት እናድርግ፣ ለተጎዱ ሰዎች ደግሞ ድጋፍ እናድርግ ሲሉ ተደምጠዋል። የሃገሪቱ ባለስልጣናት በበኩላቸው ሃገሪቱ በሽግግር ላይ ባለችበት ወቅት ወደ ቀውስ ለማስገባት የተደረግ ሙከራ ነው ሲል ገልጾታል።

ISIS ለጥቃቱ ሃላፊነት የወሰደ ሲሆን፣ በአረብ ሃገራት እና በሌሎች አካባቢዎችም ክርስቲያኖችን እና አአስተኛ የሚባሉ ቡድኖችን ለማጥፋት እየተንቀሳቀሰ ይገኛል።

በሽር አል አሳድ ከስልጣ ከተወገዱ በኋላ ይሄ ክርስቲያኖች ላይ የተፈጸመ ከባድ ጥቃት ነው። ISIS በሰሜናዊ ሶሪያ አካባቢዎች ድጋሚ ለመንቀሳቀስ ሙከራ እያደረገ ይገኛል።

ሶሪያ ማለት የመጀምሪያ ክርስቲያኖች “ክርስቲያን” የሚለውን ስም ያገኙባት #አንጾኪያ መገኛ የሆነች ምድር ናት። ዋና ከተማዋ ደማስቆ ደግሞ ጳውሎስ ክርስቲያኖችን ሊያሳድድ ሲሄድ ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር የተገናኘባት ምድር ናት።
The Christian Post & Allarab News እንዳስነበቡት
ለተጨማሪ መረጃ የፌስቡክ ገፃችንን ይከታተሉ
https://www.facebook.com/CInewsethiopia

 በ    37  #ኢትዮጵያውያን ላይ የሞት ቅጣት ተፈፃሚ ሊደረግ መሆኑን የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ገለፁበሳዑዲ አረቢያ ከአደንዛዥ ዕፅ ዝውውር ጋር በተያያዘ ቢያንስ 37 ኢትዮጵያውያን...
20/06/2025



በ 37 #ኢትዮጵያውያን ላይ የሞት ቅጣት ተፈፃሚ ሊደረግ መሆኑን የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ገለፁ

በሳዑዲ አረቢያ ከአደንዛዥ ዕፅ ዝውውር ጋር በተያያዘ ቢያንስ 37 ኢትዮጵያውያን የሞት ቅጣት ይጠብቃቸዋል ሲሉ 31 የሲቪል ማህበረሰብ እና የሰብዓዊ መብቶች ተሟጋች ድርጅቶች በጋራ ባወጡት መግለጫ አስታወቁ። የኢትዮጵያ ዜጎችን ጨምሮ መቶዎች በሚቆጠሩ የውጭ ሀገር ዜጎች ላይ የሞት ቅጣት ተፈፃሚ ሊደረግባቸው እንደሚችል ተገልጿል።

ደርጅቶቹ ባወጡት የጋራ መግለጫ፤ ከህገ ወጥ አደንዛዥ ዕፅ ጋር በተያያዘ የሞት ቅጣት እየጨመረ መሆኑን ገልጸው፤ በተለይ በእስር ላይ የሚገኙ የኢትዮጵያ፣ #ሶማሊያና #ግብፅ ዜጎች ህይወት "ከፍተኛ ስጋት እንደፈጠረባቸው" ገልጸዋል።

መግለጫው፤ በተያዘው ዓመት ሰባት ኢትዮጵያውያን እና 19 የሶማሊያ ዜጎች “ሃሺሽ በማዘዋወራቸው” ግድያ እንደተፈጸመባቸው ገልጿል። በተጨማሪም “ሰኔ 9 ፣ 2017 ዓ/ም ሶስት የኢትዮጵያ ዜጎች እንደተገደሉ" እና ሌሎች ደግሞ በማንኛውም ጊዜ ልንገደል እንችላለን በሚል ስጋት ውስጥ እንዳሉ አመላክተዋል።
Via addis standard
ተጨማሪ ያንብቡ፡ https://addisstandard.com/Amharic/?p=8171
ለተጨማሪ መረጃ የፌስቡክ ገፃችንን ይከታተሉ
https://www.facebook.com/CInewsethiopia

በኢየሩሳሌም የሚገኙ ክርስቲያኖች ለጋዛ አስቸኳይ ድጋፍ እንዲደረግ ጥሪ አቀረቡ።ከኢየሩሳሌም የፍትህ ድምጽ የወጣው መግለጫ ‘በአሁኑ ሰዓት 2 ሚሊየን የጋዛ ነዋሪዎች እና 24 የእስራኤል ታጋቾ...
20/06/2025

በኢየሩሳሌም የሚገኙ ክርስቲያኖች ለጋዛ አስቸኳይ ድጋፍ እንዲደረግ ጥሪ አቀረቡ።

ከኢየሩሳሌም የፍትህ ድምጽ የወጣው መግለጫ ‘በአሁኑ ሰዓት 2 ሚሊየን የጋዛ ነዋሪዎች እና 24 የእስራኤል ታጋቾች ሕይወታቸው አደጋ ላይ ወድቀው ይገኛሉ።” በማለት አስቸኳይ የእርዳታ ጥሪውን አቅርቧል።
“በቅርቡ በጋዛ እየተከሰተ ያለውን ከፍተኛ የጦርነት ውጥረት አስመልክቶ ድምጻችንን እያሰማን ነው።” በማለት ነው ራሱን “የኢየሩሳሌም የፍትሕ ድምጽ” በማለት የሚጠራው ቡድን ያስታወቀው።
በወጣው መግለጫም ላይም የቀድሞ የላቲን ፓትሪያሪክ ሚቼል ሳባህ እና የግሬክ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ጳጳስ አታላህ ሃና እንዲሁም የቀድሞ የሉተራን ቤተ ክርስቲያን ጳጳስ ሙኒብ ዩናን ፊርማ ይገኝበታል። ከሌሎች ከ12 መካከል ደግሞ የላቲን ፓትሪያሪኬት ስራ አስፈጻሚ የሆኑት ሳሚ ኤል የሱፍ እና በእስራኤል የኢየሱሳውያን ማህበር መሪ የሆኑት ዴቪድ ኔሃውስ ይገኙበታል።
“ድምጻችን ለዓለም መሪዎች ባይደርስም የሚያዩ እና የሚሰሙን ሁላቸውም እርምጃ እንዲወስዱ እናበረታታለን” በማለት ተናግረዋል። በመግለጫቸውም በአንድ አመት ከግማሽ ውስጥ የተከሰተውን ሞት እና ውድመት “ አሸባሪ” በማለት ያነሱት ሲሆን በየቀኑ በአስር የሚቆጠሩ ሰዎች ሕይወታችውን ማጣታቸውንም አንስተዋል። ይህም እንዳለ የተከሰተው ንጽሀንን የሚያገለግሉ የጤና ተቋማት በፈራረሱበት ግዜ መሆኑ ግጭቱን የበለጠ አስጊ አድርጎታል።
ቡድኑ አክሎም የእስራኤል ባለስልጣናት የጋዛ ችግር የሰብዓዊ እርዳታ ስርጭት እንደሆነ ቢያነሳም በአሜሪካ ድጋፍ የሚደረግለት የጋዛ ሰብዓዊ ድጋፍ እርዳታን የሚያሰራጭበት መንገድ አመቺ እንዳልሆነ ጠቅሷል። ከዛም በተጨማሪ የጋዛ ዜጎች መመገቢያ ለማግኘት ወደ እርዳታ መስጫዎች በሚያመሩበት ጊዜ መገደላቸው ረሀብ ሽሽት የወጡ ሰዎች የአሩር ሰለባ እንዲሆን አድርጓቸዋል።
የጋዛ ነዋሪዎች አስፈላጊውን እርዳታ እንዲያገኙ ለእስራኤል ባለስልጣናት መገዛት እንደሚጠበቅባቸው ቡድኑ ያነሳ ሲሆን የምግብ አቅርቦትን ለጦር ስልት መጠቀም የጄኒቫን ስምምነት የሚጥስ እንደሆነ ተናግረዋል።
የእስራኤል ባለስልጣናት ዋና ዓላማ ፍልስጤማውያንን ከቦታቸው ማፈናቀል መሆኑን እንደሚያምኑም ተናግረዋል።
ለዓለም ዓቀፉ ማህበረሰብ ባደረጉት ጥሪም “ተስፋ እንዳትቆርጡ እንለምናችኋለን።” በማለት አስፍረዋል። በክርስቶስ ትንሳኤ እና በመንፈስ ቅዱስ ሀይል እንነሳ ፣ በጋዛ ላሉ ወንድሞች እና እህቶቻችን እንቁም በማለት ጥሪያቸውን አቅርበዋል።
በቅርቡም በመቶዎች የሚቆጠሩ እስራኤላውያን ሰብዓዊ መብቶች እንዲከበሩ ጥሪ እያቀረቡ በአውራ ጎዳናዎች ላይ ሰላማዊ ሰልፍ ሲወጡ ተስተውለዋል።
ከዚህም ባለፈ ክርስቲያን ኤድ ወደ ጋዛ በመርከብ ሊገቡ የነበሩ እርዳታዎች በእስራኤል ሀይሎች መታገዱን አንስቷል። ከመጋቢት ወር አንስቶም ወደ ጋዛ የገባ የሰብዓዊ እርዳታ ድጋፍ የለም።
መረጃውን ከዘ ታብሌት አገኘነው

ለተጨማሪ መረጃ የፌስቡክ ገፃችንን ይከታተሉ
https://www.facebook.com/CInewsethiopia

ከዓመታት በፊት የዩኒቨርሲቲ ተማሪ ሳለሁ አሁን ርዕሱንና ጸሐፊውን የማላስታውሰውን የታሪክ መጽሐፍ አንብቤ ነበር። (አንብቦ ለመጨረስ የማይመች ግዙፍ መጽሐፍ ስለ ነበር ገጾቹን አገላብጬ ነበር...
19/06/2025

ከዓመታት በፊት የዩኒቨርሲቲ ተማሪ ሳለሁ አሁን ርዕሱንና ጸሐፊውን የማላስታውሰውን የታሪክ መጽሐፍ አንብቤ ነበር። (አንብቦ ለመጨረስ የማይመች ግዙፍ መጽሐፍ ስለ ነበር ገጾቹን አገላብጬ ነበር ማለት ይቀላል)። ይህ መጽሐፍ የሀገራትንና ሕዝቦችን ከታሪክ ህልውና የመክሰም ትወራዎችን በሚዘረዝርበት ርዕስ ስር - በትክክል ካስታወስኩ - ወደ ሰባት የሚሆኑ መላ ምቶችን ያስቀምጣል። እነዚህን መላ ምቶች ከዘረዘረ በኋላ የአይሁድ ሕዝብ ከእነዚህ መላ ምቶች በአንዱም ሊገለጽ እንደማይችል ያሳስባል። መላ ምቶቹ ትክክል ከሆኑ የአይሁድ ሕዝብ እንደ ማንኛውም ህልውናው እንደ ከሰመ ሕዝብ መጥፋት የነበረበት ቢሆንም በልዩ ሁኔታ ተጠብቆ እስከ ዛሬ ድረስ አለ። በታሪክ ሁሉ በአይሁድ ሕዝብ ላይ የደረሰውን መከራና እንግልት ስንመለከት ህልውናው ተጠብቆ መኖሩ ተዓምር የሚያሰኝ ነው።

መጽሐፍ ቅዱስን ስንመለከት የአይሁድ ሕዝብ እንዲጠፋ ከፍተኛ ጥረት ያደረገ ሐማ ስለ ተባለ ፋርሳዊ (ኢራናዊ) ታሪክ እናነባለን። በመጽሐፈ አስቴር መሠረት ሐማ የአይሁድን ሕዝብ ክፉኛ የሚጠላ ሰው የነበረ ሲሆን የአይሁድ ሕዝብ እንዲጠፋ ለማድረግ ከፍተኛ የጥፋት ድግስ አዘጋጅቶ ነበር። ነገር ግን ሐሳቡ ከሽፎ ለአይሁዳዊው ለመርዶክዮስ ባዘጋጀው መስቀያ ላይ እርሱ ራሱ ተሰቅሏል (አስቴር 7፡10)። በሌላ ወገን ደግሞ የአይሁድ ሕዝብ በምርኮ ሲሠቃይ ከነበረበት የግፍ አገዛዝ ነጻ ወጥቶ ወደ ሀገሩ እንዲመለስና እንደ ሕዝብ ህልውናው እንዲቀጥል ስላደረገ ሌላ ኢራናዊ ንጉሥ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እናነባለን። የንጉሡ ስም ቂሮስ ሲሆን የአይሁድ ሕዝብ ህልውና እንዲቀጥል ሰበብ ከሆኑት ሰዎች መካከል ዋነኛው ነው (ዕዝራ 1፡2)።

ፖለቲከኞች እንደሚሉት በፖለቲካው ዓለም ዘላቂ ጥቅም እንጂ ዘላቂ ወዳጅም ሆነ ጠላት የለም። ዛሬ እርስ በርስ ለመጠፋፋት የሚቀጣቀጡት እስራኤልና ኢራን ከሃምሳ ዓመታት በፊት በፓህላቪ ዘመን ወዳጆች ነበሩ። በአያቶላዎች ዘመን ደግሞ ጠላቶች ሆነዋል። ነገ ደግሞ ተመልሰው ወዳጅ ሊሆኑ ይችላሉ።

እግዚአብሔር አምላክ ከአይሁድ ሕዝብ ጋር ያለውን ጉዳይ ገና እንዳልጨረሰ መጽሐፍ ቅዱስን ካነበበ ሰው የተሰወረ አይደለም። ብሔራዊ ንስሐ አድርገው ወደ መሲሁ የሚመለሱበት ዘመን ይመጣል (ዘካርያስ 12፡10፣ ሮሜ 11:25–26 ፣ ሆሴዕ 3:4–5)። ሰይጣን ይህንን ሕዝብ ማጥፋት ይፈልግ የነበረው ለመሲሁ መንገድ በመሆን የአብርሃም በረከት ተፈጻሚ እንዳይሆን ነበር። የመሲሁ በረከት በዚህ ሕዝብ አማካይነት ስለ ተፈጸመ አሁን ደግሞ በበቀል ይህንን ሕዝብ ይፈልገዋል። በነገረ ፍጻሜ ውስጥ ካለው ሚና አንጻርም ይህ ሕዝብ እንዲጠፋ የሰይጣን ምኞት ነው።

በመጨረሻው ዘመን ከሚከሰቱት አስጨናቂ ክስተቶች መካከል አንዱ የጎግ ማጎግ እስራኤልን ለማጥፋት መሰብሰብ ነው (ሕዝቅኤል 38፡8)። በእስልምና የነገረ ፍጻሜ አስተምህሮ መሠረት መጨረሻ ከመሆኑ በፊት ሙስሊሞች የአይሁድ ሕዝብ ላይ ጭፍጨፋ እንደሚፈጽሙ ይታመናል (Sahih Muslim Book 54, Hadith 105)። በተለይም ደግሞ የሺአ ሙስሊሞች ማሕዲ ብለው የሚጠሩት ሐሰተኛ ክርስቶስ ሲገለጥ የአይሁድን ሕዝብ እንደሚጨፈጭፍ ተስፋ ያደርጋሉ። ለዚህ ነው እስራኤልን እንደ ሀገር፣ አይሁድንም እንደ ሕዝብ የሚጠሉት። በመጽሐፍ ቅዱስ መሠረት ደግሞ ጌታ እስራኤልን ይታደጋታል (ራዕይ 20፡7–9)። የሚገርመው ነገር በመጨረሻው ዘመን እስራኤልን ለማጥፋት ከሚሰበሰቡት ሀገራት መካከል ሁሉም ማለት በሚቻልበት ሁኔታ አሁን የሙስሊም ሀገራት ናቸው። (በዚህ ውስጥ ግን ሳኡዲ አረብያ አልተካተተችም። ምናልባት ሁኔታዎች ተለዋውጠው ሳኡዲ የክርስቲያን ሀገር ወደ መሆኑ ትለወጥ ይሆን? አናውቅም።) At this point, I might sound like an apocalyptic preacher but all of this is right there in the Bible.

ሐሳቤን ሳጠቃልል፦ ለኢየሩሳሌም ሰላም እንጸልይ (መዝሙር 122፡6)። እግዚአብሔር ሕዝበ እስራኤልን እንዲታደግ፣ ከሁሉ በላይ ደግሞ መሲሁን ወደ ማወቅ እንዲመጡ እንዲረዳቸው እንጸልይ። ለእስራኤል ብቻ ሳይሆን ለሁሉም የዓለም ሕዝቦች ሰላም እንጸልይ። ክስተቶችን ደግሞ በቃሉ ውስጥ በተጻፈው መሠረት እንመዝን። ሰላም ለእስራኤል! ሰላም ለኢራን!

©Daniel


ለተጨማሪ መረጃ የፌስቡክ ገፃችንን ይከታተሉ
https://www.facebook.com/CInewsethiopia

ሰላም ሰላም ቤተሰቦች 👋እስራኤልና ኢራን ከሃሙስ ለሊት ጀምሮ ጦርነት ላይ ናቸው። ምድር በየትኛውም አቅጣጫ ብንጄድ በጦርነት እየነደደች ነው። ረሃብ፣ የተፈጥሮ አደጋም እንዳለ ሆኖ የመጨረሻው...
19/06/2025

ሰላም ሰላም ቤተሰቦች 👋

እስራኤልና ኢራን ከሃሙስ ለሊት ጀምሮ ጦርነት ላይ ናቸው። ምድር በየትኛውም አቅጣጫ ብንጄድ በጦርነት እየነደደች ነው። ረሃብ፣ የተፈጥሮ አደጋም እንዳለ ሆኖ የመጨረሻው መጨረሻ ላይ መድረሳችን ከዚህ በላይ ማረጋገጫ የለም።

እስራኤል ጀነራሎችንና ሳይንቲስቶችን ከገደለችበት ቅፅበት ጀምሮ ሁለቱም በሚሳኤል እየተታኮሱ ነው። በሁለቱም ጎራ ያሉ ሃገራት ሊረዷቸው እየተንደረደሩ ነው ይህ ነገር 3ኛው የአለም ጦርነትን ይቀሰቅሳል ተብሎ ተፈርቷል። እንደ አንድ ክርስቲያንስ ምን ታስባላቹ ? የኛስ አቋም ምን ሊሆን ይገባል ?
እኘሰ አንድ ፅሑፍ እናጋራችኋለን እስከዛው እስኪ እናንተ ሃሳባቹን አጋሩን ተባረኩ 🤗
©Christian mezmure
ለተጨማሪ መረጃ የፌስቡክ ገፃችንን ይከታተሉ
https://www.facebook.com/CInewsethiopia

ይህንን የበቀል ትርክት የት እናቁም?  #ይህ በቀል በቀለኛውን ያጠፋዋል በሚል ርዕስ የተዘጋጀውን መጽሀፍ ለመመረቅ ለተገኙት እና መጽሀፉን ለሚያነቡ ሁሉ ምላሽ እንዲሰጡበት የተቀመጠ ጥያቄ ነ...
16/06/2025

ይህንን የበቀል ትርክት የት እናቁም? #ይህ በቀል በቀለኛውን ያጠፋዋል በሚል ርዕስ የተዘጋጀውን መጽሀፍ ለመመረቅ ለተገኙት እና መጽሀፉን ለሚያነቡ ሁሉ ምላሽ እንዲሰጡበት የተቀመጠ ጥያቄ ነው።

በመጋቢ ጻዲቁ አብዱ ተጽፎ የተዘጋጀው እና በ149 ገጾች ተዋቅሮ በ3 ምዕራፎች የተከፋፈለው “በቀል በቀለኛውን ያጠፋዋል” የሚል ርዕስ ያለው መጽሐፍ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች እና የአብያተክርስቲያናት መሪዎች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶችን ጨምሮ ወዳጆቻቸዉ በተገኙበት በአድዋ መታሰቢያ ሙዚየም ተመርቋል።

በመረሃ ግብሩ ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ክብርት ው/ሮ አዳነች አቤቤ “በቀልን በመተው የሚያጣሉንን አጀንዳዎች መክረን ለአንዴና እና ለመጨረሻ ጊዜ መፍታት ያስፈልጋል” ብለዋል።

ክብርት ከንቲባዋ አክለው መጸሐፉ ወቅቱን የጠበቀ፣ አብሮነት እንዲዳብር ትልቅ አስተዋጽኦ ያለው፣ በቀል አንደማይጠቅም እና ከበቀል ይልቅ ሰላም አስፈላጊ መሆኑን የሚያሳይ መሆኑን አንስተዋል።

ሀገር ተቀምጠን እንመካከር ባለችበት በዚህ ወቅት ስለ በቀል አክሳሪነት እና ስለ ይቅርታ አሻጋሪነት መጻፍ ሞራል የሚጠይቅ በመሆኑ ፓስተር ጻዲቁ ይህንን ድርሻ ተወጥተዋል ያሉት ደግሞ የመጽሀፉን ሀገራዊ ፋይዳውን የተናገሩት ዶ/ር አምባዬ ኦጋቶ ናቸው።

የመጽሀፉን ስነጽሑፋዊ ዳሰሳ ያቀረቡት ጋሽ ንጉሴ ቡልቻ ይህ መጽሀፍ በቀል በቀለኛውን እንደሚያጠፋ ብቻ ሳይሆን ከበቀል መመለስ እንደሚቻል ጭምር የሚጠቁም እሮሮ ብቻ ሳይሆን ተስፋ ተናጋሪም መጽሐፍ እንደሆነ አንስተዋል።

በመጽሀፉ ላይ አስተያየታቸውን የሰጡት አምባሳደር መሐመድ ድሪር በበኩላቸው ደራሲው (ፓስተር ጻዲቁ) በኤዶማውያን ዘንድ ለዘመናት ሳይወገድ የቆየው የበቀል ቁርሾ ውጤትን በመተረክ እንደሆነ አንስተው ለዘመናት የቆየ በሀገራችን ያለን ቂም የምናቆምበት ዘመን ላይ ደርሰናል ያሉ ሲሆን ጦርነት ውጤቱ እልቂት እና ቂምን ማሻገር ስለሆነ በቃ ልንል ይገባል ብለዋል።

ይህ መጽሀፍ ጥቂት አመታትን ቀደም ብሎ ታትሞ አንብበን ቢሆን ኖሮ በሃገራችን የተከሰቱ ጥፋቶችን ሁሉ መታደግ የሚችል ነበር ያሉት ደግሞ የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጠቅላይ ጸሀፊ ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ታጋይ ታደለ ናቸው።

የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ካርዲናል የሆኑት ካርዲናል ብረሃነ ኢየሱስ ሱራፌል ቂም በቀል ተሽሮ ወንድሞች ተደጋግፈው የሚኖሩባት ሃገራችንን በድጋሜ እንደምንመለከት አሁንም ተስፋ አለን በማለት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

አልሰማ ብለን ብዙ ነገሮች ሆነዋል እየሆኑም ነው ያሉት የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል ጠቅላይ ጸሀፊ ቄስ ደረጀ ጀመበሩ ይህንን መጽሀፍ የምናነብ ሁሉ በቃ ብለን ወደ ሕይወታችን ገብቶ ከበቀል እና ከጥፋት እራሳችንን እና እጃችንን የምንጠብቅበት ዘመን እንዲሆን መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

የፓስተር ጻድቁ አብዶ የመጀመሪያ መፅሐፍ የሆነው “በቀል በቀለኛውን ያጠፋዋል” መጸሐፍ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ክ የተገኙ ተወካዮችን ጨምሮ አባቶች በመመረቅ ለትውልድ በረከት እንዲሆን በይፋ መርቀውታል።

በመድረኩ ዶ/ር ማሙሻ ደንታ #የእግዚአብሔርን ቃል በማካፈል ዘማሪት መስከረም ጌቱ እና ሪትም ኳየር በዝማሬ አገልግለዋል።
በዮሐንስ ግርማ

ለተጨማሪ መረጃ የፌስቡክ ገፃችንን ይከታተሉ
https://www.facebook.com/CInewsethiopia

በሕንጸት የመጽሐፍ ክበብ፣  ሐምሌ 13 ቀን፥ 2017 ዓ.ም. ለውይይት የሚቀርበው መጽሐፍ፣ “አሁን የሆነውን የሆነ?" የተሠኘው፥ በመለሰ ወጉ (ዶ/ር) የተጻፈው ግለ ታሪክ መጽሐፍ ይኾናል። ...
16/06/2025

በሕንጸት የመጽሐፍ ክበብ፣ ሐምሌ 13 ቀን፥ 2017 ዓ.ም. ለውይይት የሚቀርበው መጽሐፍ፣ “አሁን የሆነውን የሆነ?" የተሠኘው፥ በመለሰ ወጉ (ዶ/ር) የተጻፈው ግለ ታሪክ መጽሐፍ ይኾናል። በውይይቱ ላይ መታደም የምትሹ ኹሉ፣ ከሣር ቤት ወደ ቫቲካን ኢምባሲ በሚወስደው መንገድ ላይ በሚገኘው የኢትዮጵያ ሥነ መለኮት ድኅረ ምረቃ ት/ቤት (EGST) መሰብሰቢያ አዳራሽ በ9 ሰዓት ላይ እንደትገኙ በአክብሮት እንጋብዛለን።

ለተጨማሪ መረጃ የፌስቡክ ገፃችንን ይከታተሉ
https://www.facebook.com/CInewsethiopia

 #የናይጄሪያ እርሻ ሚኒስቴር ለአገሪቱ የምግብ ዋስትና ሠራተኞቹ ጾም እና ጸሎት እንዲያደርጉ ጥሪ አቀረበ።ናይጄሪያ የምግብ ዋስትናን እንድታረጋግጥ ፈጣሪን ለመማጸን ፆም እና ጸሎት እንዲያደር...
15/06/2025

#የናይጄሪያ እርሻ ሚኒስቴር ለአገሪቱ የምግብ ዋስትና ሠራተኞቹ ጾም እና ጸሎት እንዲያደርጉ ጥሪ አቀረበ።
ናይጄሪያ የምግብ ዋስትናን እንድታረጋግጥ ፈጣሪን ለመማጸን ፆም እና ጸሎት እንዲያደርጉ የአገሪቱ የእርሻ ሚኒስቴር ሠራተኞቹን መጠየቁን ተከትሎ ውዝግብ ተፈጥሯል።

በናይጄሪያ እርሻ ሚኒስቴር የሰው ኃይል አስተዳደር ክፍል ኃላፊ አማካኝነት ለመሥርያ ቤቱ ሠራተኞች በተሰራጫው ማስታወሻ የሚኒስትር መሥሪያ ቤቱ ባልደረቦች ለተከታታይ ሦስት ሰኞዎች በሚካሄደው የተማጽኖ ፆም እና ጸሎት ላይ እንዲሳተፉ ይጠይቃል።

ይህ ዜና መውጣቱን ተከትሎ አንዳንድ ናይጄሪያውያን መንግሥታቸው በአገሪቱ እያነረ ያለውን የምግብ ዋጋ እንዲቀንስ ለማድረግ ያለውን ቁርጠኝነት ጥያቄ ውስጥ በመክተት ተችተዋል።

የፆም ጸሎት ጥሪው መነጋገሪያ መሆኑን ተከትሎ የናይጄሪያ እርሻ ሚኒስቴር ቅዳሜ ዕለት ባወጣው መግለጫ ማስተባበያ ሰጥቷል።

ጥሪው በአገሪቱ ያለውን የምግብ ዋስትና ችግር ለመቅረፍ ጸሎት የመንግሥት ይፋዊ ፖሊሲ አለመሆኑን አመልክቶ፣ ነገር ግን ጸሎቱ የሠራተኞችን ደኅንነት ለማዳበር ነው ብሏል።

ለተጨማሪ መረጃ የፌስቡክ ገፃችንን ይከታተሉ
https://www.facebook.com/CInewsethiopia

ከሞዴልነት ወደ መነኩሴነትበጆርጂያ ውስጥ እጅግ ታዋቂ ከሆኑ የወንድ ሞዴሊንግ አክተሮች መካከል ላሻ ቦርድዚኩል አንዱና ተጠቃሹ ነው ፤ ላሻ በአንድ ወቅት Mr Georgia እና Mr Valint...
14/06/2025

ከሞዴልነት ወደ መነኩሴነት

በጆርጂያ ውስጥ እጅግ ታዋቂ ከሆኑ የወንድ ሞዴሊንግ አክተሮች መካከል ላሻ ቦርድዚኩል አንዱና ተጠቃሹ ነው ፤ ላሻ በአንድ ወቅት Mr Georgia እና Mr Valintin የሚሉ የአሸናፊነትን ማዕረግ ለማግኘት የቻለ ነው ፤ አሁን ላይ ላሻ ቦርድዚኩል በምንኩስና ህይወት ይገኛል ፤ ምንም እንኳን በኦርቶዶክሳዊ ቤተሰብ ውስጥ ላደገ ክርስቲያን እንዲህ ያለው ነገር እጅግ ቀላል ቢሆንም ነገር ግን ውሳኔው ብዙዎችን አነጋግሯል ፤

አሁን ላይ ላሻ ቦርድዚኩል በግሪክ በሚገኝ ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያን ውስጥ ምንኩስናን ተቀብሎ ይኖራል ፤ ውሳኔውን አስመልክቶ እንዲህ ሲል በማህበራዊ ሚዲያ ይህንን አካፍሏል ፤


'' ከተወሰነ ጊዜ በፊት በህይወቴ ውሰጥ ሁሉም ነገር ተለዋወጠ ፤ በዚህ ምድር ላይ እውነተኛ ሰላምና ደስታ ዘለዓለማዊ ህይወት ሊኖረኝ የሚችለው ትክክለኛውን መስመር ከተከተልኩኝ ብቻ ነው ፤ ለዛም ነው ለመመንኮስ የወሰንኩት ፤ የሰዎች ትኩረት የምስብ ሞዴል መሆንን አልፈለኩም ፤ በጆርጅያ ባሉ ገዳማት ውስጥ ብመነኩስ እንደልቤ ከሰው ዓይን ልሰወር አልችልም ፤ ለዛም ነው በግሪክ በሚገኘው ቤተክርስቲያን ውስጥ ያለሁት ፤ ቀሪውንም ህይወቴ ለእግዚአብሔር ሰጥቼ ለመኖር የወሰንኩት በዚሁ ገዳም ነው ፤ በውሳኔዬ ምክንያት በማወቅም ይሁን ባለማወቅ የጎዳዋቸው ሰዎችን እያሰብኩ እግዚአብሔር ምህረቱን እንዲሰጠኝ ስል በቀሪ ዘመኔ እልጸያለሁ ፤''

ከእግዚአብሔር ሰላምና ፍቅር ጋር

አባ ዲዮናስዮስ
ላሻ ቦርድዚኩል ምኩስናን ከተቀበለ በኋላ አባ ዲዮናስዮስ ተሰኝቷል
ለተጨማሪ መረጃ የፌስቡክ ገፃችንን ይከታተሉ
https://www.facebook.com/CInewsethiopia

ለብራዚል ብሔራዊ ቡድን ተሰልፎ መጫወት ለብዙዎች ተጫዋች እንደ ህልም ነዉ የሚቆጠረዉ ምክንያቱም ካላት የተጫዋች ብዛትና ጥራት አንፃር በእንግሊዝ ፕሪምየርሊግ ለፉልሃም የሚጫወተዉ አንድሬስ ፔ...
14/06/2025

ለብራዚል ብሔራዊ ቡድን ተሰልፎ መጫወት ለብዙዎች ተጫዋች እንደ ህልም ነዉ የሚቆጠረዉ ምክንያቱም ካላት የተጫዋች ብዛትና ጥራት አንፃር በእንግሊዝ ፕሪምየርሊግ ለፉልሃም የሚጫወተዉ አንድሬስ ፔሬራ "ከረጅም አመታት በኃላ ለብራዚል ብሔራዊ ቡድን ተጠርቶ መሠለፍ የቻለ ሲሆን ደስታዉን ሲገልፅ "በእያንዳንዷ ሰአት ተስፋ ባለመቁረጥ ዉስጥ ጠንክሬ በመስራቴ የረዳከኝ አንተ ስለሆንክ "ስለ ሁሉም ነገር እግዚአብሔር ይመስገን " በማለት እግዚአብሔርን አመስግነዋል ::

ብዙ የተደረገለት አምላኩን ያመሰግናል !!ለተጨማሪ መረጃ የፌስቡክ ገፃችንን ይከታተሉ
https://www.facebook.com/CInewsethiopia

Address

Djibouti Street
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Christian Independent/ክርስቲያን ኢንዲፔንደንት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Christian Independent/ክርስቲያን ኢንዲፔንደንት:

Share