
30/08/2025
ሰሚ ያጣው የክርስትያኖች ሰቆቃ በፓኪስታን !
ፓኪስታን በፕላኔታችን ከሚገኙ ሀገራት መካከል ቁጥር አንድ ለክርስትያኖች የማትመች ምድራዊ ሲኦል የሆነች ሀገር መባሏና አማኞችም እየደረሰባቸው ያዉን ሰቆቃ የአለም ህዝብ እንዲረዳል ሲሉ ሰላማዊ ሰልፍ ማድረጋቸዉ ተሰማ ።
ዲሚትራ ስታይኮ የተባለው የዜና አዉታር በፓኪስታን ውስጥ ያለው አናሳ ክርስቲያን ህዝብ ላይ ለሰሚው የሚከብድ የፍትህ መጓደል ስድብ መገለል በውሸት ውንጀላ የታጠቁ አካላትም ጥቃት እየፈፀሙ ቢሆንም በሀገሪቱ የሚገኘው ከህዝቡ 1.6 በመቶው ብቻ የሚሆነው ክርስቲያን ስርአታዊ ስደት እና መገለልን
ላይ ይገኛል ።
በርካታ ችግሮችን በመቋቋም በጽናት የቀጠሉት ክርስትያኖችም በተወለዱበት ሀገር እንደዜጋ እንዲታዩ በሰላማዊ ሰልፍ ጠይቀዋል ሲል አርብ እለት ባወጣው ዘገባ ገልጿል ።
በፑንጃብ ግዛት ከተፈጸመው የጃራንዋላ ጥቃት ከሁለት ዓመት በኋላም ቢሆን የስድብ ሕጎችን ማሻሻል፣ የዳኝነት ተጠያቂነትን ማረጋገጥ እና ሃይማኖታዊ ጭፍን ጥላቻን ለመዋጋት የትምህርት ዘመቻዎችን ማድረግ ባለመቻሉ በክርስትያኖች ላይ ባለ ብዙ አቅጣጫ ጥቃት እየደረሰና የክርስቲያን ማህበረሰቦችን በተለይም ሴቶችን እና ህፃናትን - በኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ምስቅልቅል ተዳርገዋል ተብሏል ።
መንግስታዊ ድጋፍ በሚደረግለት አክራሪ ሀይልም 26 አብያተ ክርስቲያናትን እና ከ80 በላይ ቤቶችን ወድሟል ይህም- በፓኪስታን ታሪክ ውስጥ ከነበሩት እጅግ የከፋ ፀረ ክርስቲያናዊ ጥቃቶች አንዱ ሲሆንም - አንድም የጥፋተኝነትና የተጠያቂነት ውሳኔ አልተረጋገጠም ሲል ዲሚትራ ስታይኮው በዜና ማሰራጫ ዴፌንስ ኔት ላይ ጽፏል።
በ2025 እንደ ክርስቲያን ለመኖር በዓለም ላይ ካሉት በጣም አስቸጋሪ ቦታዎች አንዷ ሆና የቀጠለችዉ ፓኪስታን ሰኔ 4፣ 2025 በፋይሳላባድ የሚገኘው የፀረ ሽብር ፍርድ ቤት ቤተክርስቲያንን አቃጥለዋል እና የክርስቲያን ቤት ዘርፈዋል የተባሉ 10 ግለሰቦችን በነፃ አሰናብቷል ያለው ዘገባዉ በነሀሴ 16 ቀን 2023 ለተፈፀመው ጥቃት ፍትህ የሚፈልጉ ክርስቲያኖች ማስፈራሪያ እየደረሰባቸው እንደሆነ አብራርቷል ።
እ.ኤ.አ. ኦገስት 16፣ 2025 ክርስቲያኖች የፍትህ እጦትን ለመቃወም በጃራንዋላ ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ ሙከራ ቢያደርጉም መንግስት የሀይል እርምጃ ወስዷል ።
የተጎጂዎች ኮሚቴ የመንግስትን እንቅስቃሴ በማውገዝ ማህበረሰቡን ለመከፋፈል የሚደረገውን ጥረት እንዲያቆም ጥሪ አቅርቧል ።
አስተባባሪው ላላ ሮቢን ዳንኤል “በጣም አዝነናል” ብሏል። "ሁሉም ክርስቲያኖች ሰላማዊ የመቀመጥ እና የማህበራዊ ሚዲያን የመጠቀም የማምለክ ነፃነት ፍትህን እንዲሰጠን እንጠይቃለን." ብሏል
አክሎም ክርስቲያን ሴቶችና ልጃገረዶች በተለይም ድሆች ወይም አካል ጉዳተኞች እየጨመሩ የሚሄዱ የአፈና፣ የአስገድዶ መድፈር እና የግዳጅ እምነት ተከታይ እንዲሆኑ የማስገደድ ጉዳዮች እየተፈጸመ መሆኑን በመገንዘብ ትኩረት እንዲሰጠን በማለት ጥሪ አቅርቧል ። ሲል ያስነበበው የፓኪስታን አብያተክርስቲያናት ድህረገጽና ዲሚትራ ስታይኮው የዜና ወኪል ነዉ።
ይህ በእንዲህ እንዳለ አምነስቲ ኢንተርናሽናል እንደዘገበው በጃራንዋላ ግርግር በቁጥጥር ስር ከዋሉት 5,213 ተጠርጣሪዎች መካከል 380 ያህሉ ብቻ ናቸው ፍርድ ቤት የቀረቡት የተቀሩት ግን ተለቀዋል ሲል ፍትህ መጉደሉን ገልጿል ።
በተመሳሳይ ከአንድ አመት በኋላም 228ቱ ዋስትና ሲፈቀድላቸው 77ቱ ደግሞ ክሳቸው ተቋርጧል። የደቡብ እስያ የአምነስቲ ምክትል ክልላዊ ዳይሬክተር ባቡ ራም ፓውዴል “የተጠያቂነት ቃል ቢገባም የባለሥልጣናቱ ውድቀት ጥፋተኛ ያለመከሰስ ሁኔታ እንዲፈጠር አድርጓል” በማለት ጭቆና እንዳለ አረጋግጧል ።
የኔታ ቲዩብ ዘጋቢ ፦ ታዴ የማመይ ልጅ
https://www.facebook.com/CInewsethiopia