BACO TUBE

BACO TUBE የሐዋርያት ሚዲያ - HAWARYAT MEDIA YouTube ገፅን🔴SUBSCRIBE🔴 ያድርጉ
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://youtube.com/?si=W7ffhtFUAaqQDkCZ

09/08/2026

አጥቷል ጎሎበታል❤

03/08/2026

ለዚ ያደረስከኝ እኔ ማነኝ❤ #ኦርቶዶክሳዊ #መዝሙር #ተዋሕዶ #አዲስ #እየሱስ

31/07/2026


#ኦርቶዶክሳዊ #መዝሙር #ተዋህዶ

ድንግል ማርያም አማላጅ ናት። #ማርያም አማላጄ ናት። #እየሱስ #ኦርቶዶክሳዊ  ゚viralシ  ゚
30/07/2026

ድንግል ማርያም አማላጅ ናት።
#ማርያም አማላጄ ናት።
#እየሱስ
#ኦርቶዶክሳዊ

゚viralシ


የእዚህ ቤት ኢየሱስ**የእዚህ ቤት ኢየሱስ በድንግል ማርያም ማኅጸን ያደረው ያ በቤቴልሄም የተገለጠው ልዑል ነው።  በዶኪማስ ቤት ከእናቱ ጋር የተገኘው  ፤ቀራንዮ ላይ አይተውት  ደካማ ነው ...
27/07/2026

የእዚህ ቤት ኢየሱስ
**

የእዚህ ቤት ኢየሱስ በድንግል ማርያም ማኅጸን ያደረው ያ በቤቴልሄም የተገለጠው ልዑል ነው።

በዶኪማስ ቤት ከእናቱ ጋር የተገኘው ፤ቀራንዮ ላይ አይተውት ደካማ ነው ሲሉት በትንሳኤ ሞትን የወጋ ንጉስ ...የእዚህ ቤት ኢየሱስ ነው

ሐዋርያት የገለጡት፣አባቶች ስለክብሩ ተከራክረው ያጸኑት፣ወንጌል ቅድስና እና ፍቅሩን የምታስነብብለት እርሱ ክርስቶስ የእዚህ ቤቱ ኢየሱስ ነው።

"እናንተን የሚቀበል እኔን ይቀበላል" በሚል የወንጌል አንቀጽ ህግ ደንግጎ መመርያ ሰጥቶ ወዳጆቹን ወዶ እንድንወድ ያስገደደን ኢየሱስ ..... እርሱ የእዚህ ቤት ኢየሱስ ነው።

ቅዱሳን መላእክት በፍርሃት የሚንቀጠቀጡለት፣ምድር ርዳ የምታከብረው፤.... በመወለዱ ማነስ፣በመሞቱ መቅለል፣በመገለጡ ጥበት ያልገደበው ያ ኢየሱስ የእዚህ ቤት ራሷ ነው።

በእውነት ኢየሱስ ያመኑት የማያሳፍር የታመነ ጌታ ነው!!! በእውነት ክርስቶስ የደከሙትን የሚያሳርፍ ጽኑ የሠላም ንጉስ ነው።

ከተቀበልነው ኢየሱስ ውጪ የሚልቅ ኢየሱስ የለም !!!

26/07/2026

እንኳን አደረሳችሁ ለቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ በዓል❤
#ኦርቶዶክሳዊ #እየሱስ #ገብርኤል

ቅዱስ ገብርኤል ዋስ ጠበቃ፣ጥላ ከለላ ይሁነን❤ የሰላምን❤ የደስታን❤ የፍቅርን❤ የአንድነትን❤ የብስራት ዜና ያሰማን🙏አሜን 🙏💕  #ኦርቶዶክሳዊ  #ገብርኤል  #እየሱስ  #ኢየሱስ
26/07/2026

ቅዱስ ገብርኤል ዋስ ጠበቃ፣ጥላ ከለላ ይሁነን❤ የሰላምን❤ የደስታን❤ የፍቅርን❤ የአንድነትን❤ የብስራት ዜና ያሰማን🙏
አሜን 🙏💕
#ኦርቶዶክሳዊ #ገብርኤል #እየሱስ #ኢየሱስ

የእናታችን ቅድስት ኪዳነ ምህረት ምልጃ እና ረድኤት አይለየን🙏የማያልፍ የምሕረት ቃል ኪዳኗ ዘወትር ይታሰባል ኪዳን የሚለው ቃል ተካየደ ከሚለው የግእዝ ግስ የወጣ ሲሆን ትርጉሙም ተማማለ፣ ተ...
23/07/2026

የእናታችን ቅድስት ኪዳነ ምህረት ምልጃ እና ረድኤት አይለየን🙏

የማያልፍ የምሕረት ቃል ኪዳኗ ዘወትር ይታሰባል

ኪዳን የሚለው ቃል ተካየደ ከሚለው የግእዝ ግስ የወጣ ሲሆን ትርጉሙም ተማማለ፣ ተስማማ፣ ውል ገባ ማለት ነው፡፡ ኪዳነ ምሕረት ማለትም ደግሞ የምሕረት ቃል ኪዳን ማለት ነው፡፡ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለእመቤታችን ድንግል ማርያም ስለሰው ልጆች ይቅርታ የገባላት ኪዳን ነው፡፡ እግዚአብሔርን ለሚፈሩት፣ ለሚያከብሩት፣ ለሚወዱትና ለሚወዳቸው ሁሉ በተለያዩ ጊዜያት ብዙ ኪዳናትን ሰጥቷል፡፡ የኪዳነ ምሕረት ሥዕል በመባል የሚታወቀው ሥዕል በቤተ ክርሰቲያናችን በስፋት ከሚሳሉት የወላዲተ አምላክ ሥዕል ጭብጦች ውስጥ አንዱ ሲሆን። ከጌታችን ኢየሱስ ቃልኪዳን ስትቀበል በጎሎጎታ የሚያሳየው ሥዕል ትክክለኛው ገላጭ ሥዕል ሲሆን፤ ይህ ሥዕል እንደ ቤተ ክርስቲያኑ ስፋት የሚጨመረው ጭብጥ ሊለያይ ይችላል፡፡

ለምሳሌ በዚህ ሥዕል ዘይቤ ላይ የሚታዩት መላእክት ቁጥራቸው ሊበዛ አሊያም ሊያንስ ይችላል፡፡ በዚህ ሥዕል እመቤታችንና ጌታችን ቆመው አሊያም ተቀምጠው ጌታችን በቅዱሳን እጆቹ የእናቱን ቅዱሳን እጆች በመያዝ ቃል ኪዳን ሲገባላት አሊያም በቅዱሳት እጁ ቃል ሲገባላት የሚያሳይ ዓይነት ሥዕል ነው፡፡ በዚህ መልኩ እመቤታችን ከተሳለችባቸው አብያተክርስቲያናት መካከል ጎርጎራ ደብረ ሲና (17ኛው መ.ክ.ዘ)፣ አብርሐወ አጽብሐ (19ኛው መ.ክ.ዘ)፣ መቐለ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ (20ኛው መ.ክ.ዘ)፤ ከጥንታውያን ብራና መጻሕፍት ከተመለከትን በአክሱም ጽዮን ቤተክርስቲያን ግምጃ ቤት የሚገኘው የ17ኛው መ.ክ.ዘ ተአምረ ማርያም ተጠቃሽ ናቸው፡፡ ገዳማውያንም ዘወትር በሥዕሏ ፊት ቆመው ይለምኗታል፡፡ እርሷም ልመናና ጸሎታቸውን ታሳርጋለች፡፡ ገዳማቸውን እንደግፍ፣ በዓታቸውን እናጽና፣ ከበረከታቸውመ እንካፈል፡፡

ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የተሰጠው ኪዳን፣ ቀድመው ለነበሩ ኪዳናት ማለትም ኪዳነ አዳም፣ ኪዳነ ኖህ፣ ኪዳነ መልከ ጸዴቅ፣ ኪዳነ አብርሃም፣ ኪዳነ ሙሴና ኪዳነ ዳዊት መደምደሚያ ነው፡፡ ዘለዓለማዊ ስለ ሆነው የማያልፍ የምሕረት ቃል ኪዳን እየታሰበም ዕለቱ በመዝሙር፣ በማኅሌትና በቅዳሴ ይከበራል፡፡ በክርስቶስ ክርስቲያን ለምንባል ለእኛ ለሐዲስ ኪዳን የቤተ ክርስቲያን ልጆችም ይህ አዲስ ውል የተደረገልን ለነፍሳችን ድኅነት በመሆኑ በስሟ እየተማጸንን እንዲሁም መታሰቢያዋን እያደረግን ለተራቡት ማብላት፣ ለተጠሙት ማጠጣትና የተቸገሩትን መርዳት ይገባናል፡፡ ገዳማውያን በበቃል ኪዳኗ ታምነው፣ ዘወትር በሥዕሏ ፊት በጸሎት ይተጋሉ፡፡ ገዳማቸውን እንደግፍ፣ በዓታቸውን እናጽና ከበረከታቸው እንካፈል፡፡

ድጋፍ ለማድረግ፦ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444

22/07/2026

ስለወደደኝ አዳነኝ❤ #ተዋህዶ #መዝሙር #ኦርቶዶክሳዊ #ገፅ ゚viralシ

ቅዱስ ሩፋኤል ከክፉ ነገር ሁሉ ይከልለን፤ ምልጃ እና ረድኤቱም አይለየን🙏ቊጥሩ ከሰባቱ ሊቃነ መላእክት ሲሆን፤ “ሩፋ” ማለት ሐኪም፤ ኤል ማለት እግዚአብሔር ማለት ሲኾን ሩፋኤል ማለት “እግዚ...
20/07/2026

ቅዱስ ሩፋኤል ከክፉ ነገር ሁሉ ይከልለን፤ ምልጃ እና ረድኤቱም አይለየን🙏

ቊጥሩ ከሰባቱ ሊቃነ መላእክት ሲሆን፤ “ሩፋ” ማለት ሐኪም፤ ኤል ማለት እግዚአብሔር ማለት ሲኾን ሩፋኤል ማለት “እግዚአብሔር ሐኪሜ ነው” ማለት ነው፡፡
ቅዱስ ኤጲፋንዮስም በመጽሐፈ አክሲማሮስ “በራማ ሰማይ የሚገኘውን ሁለተኛውን ዐሥሩን ነገድ መናብርት ሲላቸው አለቃቸው ቅዱስ ሩፋኤል ነው፤ እነዚህም ረቂቅ የሆነ የመብረቅ ጋሻ የእሳት ጦር ይዘው ከነፋስ ይልቅ የፈጠኑ ሲሆኑ በራማ በሁለተኛው ክፍል ላይ አስፍሯቸዋል፡፡

ቅዱስ ሩፋኤል ነገደ መናብርት የሚባሉትን ራማ በሚባለው ሰማይ የሚኖሩትን ነገደ መላእክት የሚመራቸው ናቸው፡፡ አባ ጊዮርጊስም በሰዓታቱ “ጽርሐ አርያም አዳራሹ፤ የትጉሃን መኖሪያ ቦታው የሚኾን እግዚአብሔር ቅዱስ፣ ቅዱስ፣ ቅዱስ ተብሎ በአንድነት በሦስትነት ይመሰገናል፤ ካህናተ ሰማይ በዙሪያው ይቆማሉ፤ በዙፋኑ ፊት እየሰገዱ አክሊሎቻቸውን ያወርዳሉ፤ እሳትነቱ በሚበርቅ፣ በሚል ጊዜ እንዳይመታቸው ይንቀጠቀጣሉ” ይላል፡፡

ቅዱስ ሩፋኤል ከሚመራው ከዚህ ነገድ 24ቱ ካህናተ ሰማይ ወጥተዋል፡፡” ይለናል፡፡ በመጽሐፈ ሄኖክ 6÷3 ላይም “በሰው ቁስል ላይ የተሾመ ከከበሩ መላእክት አንዱ ቅዱስ ሩፋኤል ነው” ተብሏል፡፡ ሊቁ ቅዱስ ባስልዮስም “በፊቱ የሚቆሙ የመላእክት ሰራዊትም ሁሉ ጩኸው ያመሰግኑታል፤ የመላእክት አለቆችም ለማይታይ ለባለዚህ ስም ዘንበል ብለው ይሰግዳሉ፤ ዙፋኑን የሚሸከሙ አርባዕቱ እንስሳ ጩኸው ያመሰግኑታል፤ ዕጣንን የተመሉ የወርቅ ማዕጠንት በእጆቻቸው ያለ ሃያ አራቱ ካህናተ ሰማይ ይኸውም የቅዱሳን ጸሎት ነው እስከ ዘላለሙ ሕያው በሆነው ፊት የሚቀበለው መሥዋዕት አድርገው ወደ ላይ ያሳርጋሉ” በማለት አስተምሯል፡፡

ቅዱስ ሩፋኤል ፈታሔ ማኀፀን ወሰፋድል። መወለድ መንፈሳዊ። ወሐኪም ሰማያዊ ይባላል። የወላድ ማኀፀን እንዲፈታ በእግዚአብሔር ስለተሾመ አዋላጅ ብትኖርም ባትኖርም ቅዱስ ሩፋኤል በዚያ አይታጣም፡፡ በተለይ በባላገር ያሉ ሴቶች በምጥ ጊዜ ሁሉ መልክአ ሩፋኤል በአንገታቸው ያነግታሉ፣ ይጸልያሉ፣ የተጸለየበትንም ጸበል ይጠጣሉ፤ በፍጥነትም ይወልዳሉ። በየወሩ በ13 ቀን መታሰቢያ በዓሉ የሚከበር ሲሆን ጳጉሜ 3 ደግሞ ዓመታዊ በዓሉ ነው፡፡ የቅዱስ ሩፋኤል በረከትና ረድኤቱ አይለየን፤ ምልጃው ይጠብቀን፡፡ ገዳማውያንም ይህን ተራዳኢነቱን በመታመን ዘወትር በጸሎታቸው ይጠሩታል፡፡ ገዳማቸውን በመደገፍና በዓታቸውን በማጽናት የበረከታቸው ተሳታፊ እንሁን፡፡

ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444

Address


Alerts

Be the first to know and let us send you an email when BACO TUBE posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share