Dawuro Media Network

Dawuro Media Network This is promoter center....
(1)

ስታርታፖ ኮሙኒቲ በአዳዲስ የቴክኖሎጂ ፈጠራዎች ላይ  በማተኮር ለነገው ትውልድ መሰረት መጣል እንደሚጠበቅባቸው  ዶ/ር ባይሳ በዳዳ ገለፁ።========================በኢኖቬሽንና ቴ...
19/08/2025

ስታርታፖ ኮሙኒቲ በአዳዲስ የቴክኖሎጂ ፈጠራዎች ላይ በማተኮር ለነገው ትውልድ መሰረት መጣል እንደሚጠበቅባቸው ዶ/ር ባይሳ በዳዳ ገለፁ።
========================
በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር እና በኮሪያ አለም ዓቀፍ ተራህዶ ድርጅት ሲደገፉ የነበሩ ሰርታርታፖች ዓመታዊ የጋራ መድረካቸውን በኢኖቢዝኬ የኢንኩቤሽን ማዕከል አካሄዱ።

መድረኩ ስታርታፖቹ ያላቸውን ልምድ ለማጋራት፣ የስራ ትብብርና ትስስርን ለመፍጠርና የጋራ የሆነ ህብረት ለመመስረት ያለመ ነው።

በፕሮግራሙ ላይ የተገኙት የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ባይሳ በዳዳ ከሀገራዊ ስታርታፖች ትብብርና ትስስር የሚገኙ አቅሞችን ለአዳዲስ የቴክኖሎጂ ፈጠራዎችና ለሀገራዊ ኢኮኖሚ ልማት ግቦች ስኬት ወሳኝ ሚና እንዳለው ገልፀዋል።

የኢትዮጵያ ስታርታፖች በአለም አቀፍ ደረጃ እውቅና እያገኙ ነው ያሉት ሚኒስትር ዴኤታው ዓለም ከደረሰበት የቴክኖሎጂ ምዕራፍ ላይ ለመድረስ ፈጠራ በሀገራችን ባህል ሆኖ በማህበረሰብ ውስጥ ሊጎለብት ይገባል ብለዋል።

ሀገራዊ የስታርታፕ አዋጅ መፅደቅ የፈጠራ እድገትን እጅግ እንዲፋጠን ያደርገዋል ያሉት ሚኒስትር ዴኤታው ዘርፉ ህጋዊ እውቅና፣ ግልፅ ምዝገባ፣ የተሻሻለ የገንዘብ አቅርቦት፣ የታክስ ማበረታቻዎች እና ጠንካራ የአቅም ግንባታ እርምጃዎችን፣ ለሥነ-ምህዳር ገንቢዎች ጠንካራ ድጋፍና ሌሎች እገዛዎችን እንደሚሰጥም አስገንዝበዋል።

የኮሪያ አለም ዓቀፍ ተራህዶ ድርጅት prof. kwak jaesung (project manager kyunghee university ) በኢትዮጵያ የስታርታፕ ዘርፉን ለማጎልበት በትብብር ላይ ተመስርተው ሰፋፊ ስራዎችን በመስራት ላይ እንደሆኑ ገልፀው በቀጣይ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ጠቁመዋል።

በመድረኩ ከኮሪያ በመጡ ባለሙያዎች ስልጠና የመስጠት፣ የፓናል ውይይት፣ የተመረጡ ስታርታፖች ልምድ የማጋራትና በጋራ ለመስራት የሚያስችል ምክክሮች ተደርገዋል።

Ministry of Innovation and Technology - Ethiopia

የአንጋፋው አርቲስት ደበበ እሸቱ ሥርዓተ ቀብር ተፈጸመ 👉 የአርቲስቱ የዓይን ብሌን ለደምና ሕብረህዋስ ባንክ አገልግሎት ተለግሷልነሐሴ 13/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) የአንጋፋው አርቲስት ደበበ ...
19/08/2025

የአንጋፋው አርቲስት ደበበ እሸቱ ሥርዓተ ቀብር ተፈጸመ

👉 የአርቲስቱ የዓይን ብሌን ለደምና ሕብረህዋስ ባንክ አገልግሎት ተለግሷል

ነሐሴ 13/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) የአንጋፋው አርቲስት ደበበ እሸቱ ሥርዓተ ቀብር ዛሬ ከቀኑ 8 ሰዓት ላይ በመንበረ ጽባኦት ቅድስት ስላሴ ካቴድራል ቤተክርስቲያን ተፈፅሟል።

ከሥርዓተ ቀብሩ ቀደም ብሎ በብሔራዊ ቴአትር የአስከሬን ሽኝት መርሐ ግብር የተከናወነ ሲሆን፤ በዚህም መርሐ ግብር ላይ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ሃላፊዎች ተገኝተው አርቲስቱ በኪነጥበቡ ዘርፍ ላበረከተው ዘመን አይሽሬ ሥራዎች ክብር የአበባ ጉንጉን አስቀምጠዋል። በተጨማሪም በክብር መዝገብ ላይ የሀዘን መግለጫቸውን አኑረዋል፡፡

በመድረኩም ከአርቲስቱ ዘመን አይሽሬ ሥራዎች ውስጥ በፎቶና በቪዲዮ ቅንጭብ ቀርበዋል፡፡

ከዚህም በማስከተል ከቀኑ 8 ሰዓት ላይ የአርቲስቱ ሥርዓተ ቀብር በመንበረ ጽባኦት ቅድስት ስላሴ ካቴድራል ቤተክርስቲያን የተፈጸመ ሲሆን፤ በሥርዓተ ቀብሩ ላይም ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የአርቲስቱ ቤተሰቦች፣ ወዳጅ ዘመዶች፣ የሥራ አጋሮች እና አድናቂዎቹ ተገኝተዋል።

ከዚህ በተጨማሪም አርቲስት ደበበ እሸቱ ቃልኪዳን በገባው መሠረት በባለቤታቸው ወ/ሮ አልማዝ እና አጠቃላይ ቤተሰቦቻቸው መልካም ፍቃድ ለኢትዮጵያ ደምና ሕረህዋስ ባንክ አገልግሎት ስለተለገሰ የዓይን ባንክ መሪ ስራ አስፈፃሚ ዶ/ር አምሳለ ጌታቸው ባሉበት የዓይን ብሌኑ ተነስቷል።

የተነሳው የዓይን ብሌን አስፈላጊው ፍተሻ ተደርጎለት ለአገልግሎት ይውላል ያሉት የዓይን ባንክ መሪ ሥራ አስፈፃሚዋ፤ በሕይወት እያሉ ቃል በመግባት ደጋፊዎቻቸውና ወዳጅ ቤተሰቦቻቸውም ቃል እንዲገቡ በማስተማር መልካም ሥራ ሰርቶ እንዳለፈ ገልጸዋል።

በዚህም "አርቲስቱ ሕይወቱ ቢያልፉም ብርሃኑና ሥሙ ከመቃብር በላይ ህያው አድርጎ አልፏል" ሲሉ ተናግረዋል።

አርቲስት ደበበ በኢትዮጵያ ዘመናዊ የኪነ ጥበብ ታሪክ ታላቅ ዐሻራ ያኖረ አርቲስት ሲሆን፤ በሬዲዮ እና የቴሌቪዥን ድራማ፣ በቴአትር፣ በፊልምና በጋዜጠኝነት ሙያ በርካታ ሥራዎችን ለአድማጭ ተመልካች አቅርቧል፡፡

አርቲስት ደበበ እሸቱ ከሃገሩ አልፎ በአፍሪካ እና በመላው ዓለም የኢትዮጵያን ባህል እና ጥበብ በማሳየት ሀገሩን ያስተዋወቀ እና ያስከበረ ታላቅ የባህል አምባሳደር እና የጥበባት ባለሙያም ነበር፡፡

ከነዚህም መካከል ታላላቆቹ የ1969ኙ የአልጄሪያ የአፍሪካ የባህል ፌስቲቫል የ1977ቱ የናይጄሪያ የመላው ጥቁር ሕዝቦች የባህል ፌስቲቫል /FESTAC/ ይገኙበታል፡፡

በ1983 በዓለም አቀፉ የዩኔስኮ የቴአትር ኢንስቲቲዩት/IT/ ኮንፈረንስ የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ ሆኖ በመሳተፍ የአፍሪካ አህጉር እስተባባሪ ሆኖ ለመመረጥ በቅቷል፡፡

ይህም በዚያ ደረጃ ያገለገለ ለሃገሩ እና ለአህጉሩ የቴአትር ጥበብ ክፍተኛ አስተዋጽኦ የሰጠ ብቸኛ ኢትዮጵያዊ ያደርገዋል።

የዩኔስኮው የአፍሪካ የቴአትር አስተባባሪነት ስኬታማ ስራም በዚያው አመት የአፍሪካ የክዋኔ ጥበባት ማኅበር/Union of African Performing Artists/ Tሬዝዳንት አድርጎ አስመርጦታል፡፡

ይህም እስከዛሬ ለመላው የኢትዮጵያ ከያንያን አርዓያ ሆኖ እንዲታይ ያደረገው ስኬት ነው፡፡ ደበበ እሸቱ በ1986 በቶሮንቶ ዩኒቨርሲቲ፣ በ1989 በርሊን የብሬሽት ኮንፈረንስ፣ በዳካሩ የዩኔስኮ የአፍሪካ ባህል አምባሳደር መሆን ችሏል።

አርቲስት ደበበ እሸቱ የጉማ የሕይወት ዘመን ተሸላሚ ለኢትዮጵያ ፊልም ላደረገው አስተዋጽኦ ከፍተኛ ሽልማት ሲሆን፤ በተጨማሪም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ "ኢትዮጵያን ስላገለገሉ ኢትዮጵያ ታመሰግኖታለች" በሚል የሀገሪቱን ከፍተኛ የክብር ሜዳሊያ ተበርክቶለታል።

አርቲስቱ ባደረበት ሕመም በሕክምና ሲረዳ ቆይቶ፤ በተወለደ በ84 ዓመቱ እሁድ ነሐሴ 11 ቀን 2017 ከዚህ ዓለም በሞት መለየቱ ይታወቃል፡፡

የአንጋፋው አርቲስት ደበበ እሸቱ ባለትዳርና የአራት ልጆች አባት እንዲሁም የስምንት ልጆች አያት ነበር።

#አሐዱ

19/08/2025
19/08/2025
‎የዳውሮ  ብሔር ዘመን መለወጫ ቶክ በዓ በዓልን በጋራ ለማክበር የማሪ ማንሳ ወረዳ መንግሥት 100 ሺህ ብር ገቢ አድርጓል።‎‎ቶኪ ቤዓ በዓል ማህበራዊ መስተጋብርን የሚያጠናክር፤ የዳዉሮ ብሔ...
19/08/2025

‎የዳውሮ ብሔር ዘመን መለወጫ ቶክ በዓ በዓልን በጋራ ለማክበር የማሪ ማንሳ ወረዳ መንግሥት 100 ሺህ ብር ገቢ አድርጓል።

‎ቶኪ ቤዓ በዓል ማህበራዊ መስተጋብርን የሚያጠናክር፤ የዳዉሮ ብሔር የማንነቱ መገለጫ በመሆኑ ለበዓሉ ድምቀት የማሪ ማንሳ ወረዳ መንግስት አመራር እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ከሚያደርገው ድጋፍ ውጪ መቶ ሺህ ብር በተከፈተው አካውንት ገቢ አድርጓል እናመሰግናለን ‼️

‎እርስዎም የዳውሮ ብሔር ዘመን መለወጫ ቶኪ በዓ በዓልን በድምቀት ለማክበር እንዲቻል ለዚሁ ዓላማ በተከፈተው የባንክ አካውንት የአቅምዎትን ያህል ገንዘብ ገቢ በማድረግ ድርሻዎትን እንድወጡና በዓሉን የጋራ በዓል እንድያደርጉ ተጋብዘዋል።

‎እንኳን አደረሰን!

Mari Mansa Woreda Government Communication Affairs Office

ህዝብ የሚያነሷቸውን የመልካም አስተዳደርና የአገልግሎት አሰጣጥ ችግሮችን ማረም እንደሚገባ ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ።በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል “ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌ...
19/08/2025

ህዝብ የሚያነሷቸውን የመልካም አስተዳደርና የአገልግሎት አሰጣጥ ችግሮችን ማረም እንደሚገባ ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ።

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል “ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሃገር” በሚል መርህ ቃል ባለፉት ዐራት ቀና በቦንጋ ከተማ ስካሄድ የቆየው ክልል አቀፍ የአመራር ውይይት ተጠናቋል።

በመድረኩ ማጠቃለያ የቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ ማብራሪያ የሰጡት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)፥ በየደረጃው ያለው አመራር ህዝብ የሚያነሷቸውን የመልካም አስተዳደርና የአግልግሎት አሰጣጥ ችግሮችን ፈጥኖ ማረም እንደሚገባ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያን ብሄራዊ ጥቅም ለማስከበር መንግሥት በቁርጠኝነት እየሰራ መኾኑን ነው ርዕሰ መስተዳድሩ የገለጹት።

በዚህም ሁለንተናዊ ዕድገት በማፋጠን ቀጣይነት ያለውን የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በለውጡ መንግሥት የተጀመረው ተግባር እምርታዊ ለውጥ እያስመዘገበ እንደሚገኝም ተናግረዋል።

በቀጣይም ውስጣዊ አንድነትን በማጠናከር የውጭ ተጋላጭነትን መከላከል እንደሚገባ ያስገነዘቡት ርዕሰ መስተዳድሩ፥ አብሮነትንና ህብረ ብሔራዊ አንድነትን የሚሸረሽሩ ተግባራት መከላከል ይገባል ብለዋል።

ኑሮ ውድነት ለመቋቋም የግብርና ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ፣ የገበያ ቁጥጥር ስርዓት ማሻሻል እንዲሁም የንግድ አሻጥር መከላከል ይገባል ያሉት ርዕሰመስተዳድሩ፤ በሁሉም ዘርፍ የተገኙ ስኬቶችን በማጠናከር ትኩረት የሚሹ ጉዳዮችን አቅም በፈቀደው መጠነ መፍታት እንደሚገባም አስገንዝበዋል።

በየደረጃው የሚገኝ አመራር ህዝባዊነት ስሜትን የተላበሰ አገልግሎት በመስጠት የተጀማመሩ የኢኮኖሚ አርበኝነት በማጠናከር የገቢ አቅምን ለማሳደግ ተገቢውን ትኩረት እንዲሰጥ ጠይቀዋል።

ስልጠናው በአመራሩ ዘንድ የአስተሳሰብና የተግባር አንድነት በመፈጠር የሪፎርም ሥራዎቻችንን ይበልጥ ውጤታ ለማድረግ የሚረዳ መኾኑን የጠቆሙት የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፍቅሬ አማን አመራሩ የማስፈፅምና የመፈፀም አቅሙን በማጎልበት የፓርቲው ራዕይ ለማሳካት ከመቸውም ጊዜ በተሻለ ዝግጁ መሆን ይጠበቅበታል ብለዋል።

የውይይቱ ተሳታፊ አመራሮች በበኩላቸው መድረኩ በሁሉም አመራር ዘንድ በሀገራዊ፣ በቀጠናዊ እና በአካባቢያዊ ነባራዊ ጉዳዮች ላይ የጋራ ግንዛቤ የፈጠር መሆኑን በመጠቀስ ለቀጣይ ተልዕኮ የሚያዘጋጅ እንደሆነም ተናግረዋል ሲል የዘገበው የክልሉ የመንግሥት ኮሚዩኒኬሽን ነው።

Southwest Communications

ከእንግዲህ ውጪ ሀገር ለመሄድ መንከራተት ቀረ፣ እንዴት ካላችሁን፣🤔 ሉቄ የፓስፖርት ጉዳዮች አስፈጻሚ ዳውሮ ታርጫ ላይ ሥራ ጀመረ።💪❤         መልካም ዜና ለፓስፖርት ፈላጊዎች በሙሉ፣ፓስ...
19/08/2025

ከእንግዲህ ውጪ ሀገር ለመሄድ መንከራተት ቀረ፣ እንዴት ካላችሁን፣🤔 ሉቄ የፓስፖርት ጉዳዮች አስፈጻሚ ዳውሮ ታርጫ ላይ ሥራ ጀመረ።💪❤

መልካም ዜና ለፓስፖርት ፈላጊዎች በሙሉ፣

ፓስፖርትን ማንኛውም ዜጋ ማግኘት እንዲችል የቦታ ርቀት ሳይገድቦ እዚሁ ታርጫ ከተማ ላይ በቀላሉ ማግኘት ይችላሉ።

በዳውሮ ዞን የታርጫ ከተማ መቀመጫ አድረገን፣ ለፓስፖርት ፈላጊ ወገኖች አግልግሎት እየሰጠን እንገኛለን። አገልግሎቱን ለመጠቀም የምትፈልጉ በአካል ወይም በስልክ ማገኘት የምትችሉ መሆኑን ስንገልጽ በታላቅ ደስታ ነው።

👇

1. አዲስ ፓስፖርት ለማውጣት
፠ የታደሰ የቀበሌ መታወቂያ
፠ የልደት ካርድ
፠ ስልክ ቁጥር
2. ለእድሳት
፠ ጉርድ ፎቶግራፍ
፠ ጊዜ ያለፈው ፓስፖርት
፠ ስልክ ቁጥር
3. የጠፋ/የተሰረቀ ለማውጣት
፠ የቀበሌ መታወቂያ
፠ ጉርድ ፎቶግራፍ
፠ የፖሊስ ማስረጃ ደብዳቤ
፠ ስልክ ቁጥር
4. ከ18 ዓመት በታች
፠ የወላጅ መታወቂያ
፠ የልጅ የልደት ካርድ
፠ ስልክ ቁጥር
5. ስም ለመቀየር ወይም ለማስተካከል
፠ ጉርድ ፎቶግራፍ
፠ ፓስፖርት ኮፒ
፠ የፍርድ ቤት ወረቀት
፠ ስልክ ቁጥር
አድራሻችን ዳውሮ ታርጫ እናት ቃ/ህ/ቤተ/ያን ዝቅ ብሎ High school ፊት ለፊት ለበለጠ መረዳ 0955562502 ይደውሉ።አስተማማኝ፣ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት https://chat.whatsapp.com/CJ51UyW1Lvd2RMi1DgqTDb?mode=ac_t

Dawuro Media Network

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የቱሪስት መስህቦችን ከጎበኙ ቱሪስቶች ከ500 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ተገኘ| |በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የሚገኙ የቱሪስት መስህብ ሥፍራዎችን ከጎበኙ የሀገር ውስጥና የው...
19/08/2025

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የቱሪስት መስህቦችን ከጎበኙ ቱሪስቶች ከ500 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ተገኘ

| |በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የሚገኙ የቱሪስት መስህብ ሥፍራዎችን ከጎበኙ የሀገር ውስጥና የውጭ ቱሪስቶች ከ500 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ መገኘቱን የክልሉ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ አስታወቀ።

የቢሮው ኃላፊ ወይንቱ መልኩ ለኢዜአ እንደገለጹት በክልሉ የሚገኙ የቱሪስት መስህብ ስፍራዎችን የማልማትና የማስተዋወቅ ሥራዎች በስፋት እየተከናወኑ ነው።

ቀደም ሲል ትኩረት ያልተሰጣቸው ታሪካዊ፣ ባህላዊና ተፈጥሯዊ የቱሪስት መስህብ ስፍራዎችን በማልማትና በማስተዋወቅ የቱሪስት ፍሰቱን ለመጨመር በተሰሩ ስራዎች ውጤት እያመጣ መሆኑንም ገልጸዋል።

በተለይ በክልሉ ያለው ሰላም ለቱሪስት ፍሰቱ መጨመር አስተዋጽኦ ማድርጉን ጠቅሰው ከዘርፉ የሚገኘው ገቢም እያደገ መምጣቱን ተናግረዋል፡፡

በዚህም በተጠናቀቀው የ2017 በጀት ዓመት ከቱሪዝም ዘርፍ 546 ሚሊዮን ብር ገቢ በመሰብሰብ ከዕቅድ በላይ መፈጸሙን ገልጸዋል።

በተጨማሪም በክልሉ የሚከበሩ ባህላዊና ህዝባዊ በዓላት ለቱሪስት ፍሰት እየጨመረ መምጣት ትልቅ አስተዋጽኦ ማድረጋቸውን ቢሮ ሀላፊዋ አክለዋል።

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከሚገኙ የቱሪስት መስህብ ስፍራዎች መካከል የማዜ፣ የኦሞ፣ የማጎና የነጭ ሣር ብሔራዊ ፓርኮች ይገኛሉ።

የኮንሶና የጌዴኦ ማራኪ መልክኣ ምድር፣ በክልሉ የሚገኙ ብሔረሰቦች ድንቅ ባህሎችና የታችኛው የኦሞ ሸለቆ መካነ-ቅርስም ተጠቃሽ ናቸው።

ከእነዚህ በተጨማሪ የብሔረሰቦቹ የምስጋናና የዘመን መለወጫ ባህላዊ ክብረ በዓላት፣ ባህላዊ ክዋኔዎችና የሙዚቃ ስልተ-ምት በክልሉ የቱሪስቶችን ቀልብ የሚስቡ የቱሪስት ሀብቶች መሆናቸው ታውቋል።

© #ኢዜአ

ከሰሞኑን የሚከበረውን የዳውሮ ብሄር የዘመን መለወጫ    በዓልን በተመለከተ ለማስታወቂያ የሚሆን፣ የቪዲዮ እና የፎቶ ሥራዎች ጀርባ ድንቅ የሙያ ብቃቱን እያስመዘገበ የሚገኝ የካሜራ ማንን ተዋ...
19/08/2025

ከሰሞኑን የሚከበረውን የዳውሮ ብሄር የዘመን መለወጫ በዓልን በተመለከተ ለማስታወቂያ የሚሆን፣ የቪዲዮ እና የፎቶ ሥራዎች ጀርባ ድንቅ የሙያ ብቃቱን እያስመዘገበ የሚገኝ የካሜራ ማንን ተዋወቁት።

አማኑኤል ዘውዴ ይባላል፣ ለሙያው የተሰጠ እና በዘርፉ የተማረ እንዲሁም የበቃ ባለሙያ ሲሆን በአሁኑ ሰዓት በማሮታ ስቲዲዮ እየሰራ የሚገኝ ድንቅ ወጣት ነው።

የሚሰሩትን እናበረታታ እውቅና እንስጥ!

Dawuro Media Network Mihiret Mitiku Jcs Best

እንደዚህ ዓይነት ውብ የዳውሮ ባህል ልብስ ከፈለጋችሁ💛🖤❤️ 🤳 Friye Design 0912685973 አለላችሁ  💛🖤❤️💛🖤❤️💛🖤❤️አድራሻ 📍   Dawuro Media Network
19/08/2025

እንደዚህ ዓይነት ውብ የዳውሮ ባህል ልብስ ከፈለጋችሁ💛🖤❤️

🤳 Friye Design 0912685973 አለላችሁ

💛🖤❤️💛🖤❤️💛🖤❤️
አድራሻ 📍

Dawuro Media Network

 #ቶኪበዓ እየደረሰ ነው። ለቶኪ_በዓ በቆንጆ የዳውሮ ባህል ልብስ መዋብ እና መዘነጥ ከፈለጉ:-  +251_917_40_78_10   +251_912_68_59_73           ትክክለኛ ምርጫ ...
19/08/2025

#ቶኪበዓ እየደረሰ ነው።
ለቶኪ_በዓ በቆንጆ የዳውሮ ባህል ልብስ መዋብ እና መዘነጥ ከፈለጉ:-

+251_917_40_78_10

+251_912_68_59_73
ትክክለኛ ምርጫ ነው።

Dawuro Media Network fans

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በመደመር ሐሳብ ላይ የጻፉት አራተኛውንና "የመደመር መንግሥት" የተሰኘውን አዲስ መጽሐፍ በተመለከተ ከፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ጋር ያደረጉት ቃለ መጠይቅ ነገ ነ...
19/08/2025

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በመደመር ሐሳብ ላይ የጻፉት አራተኛውንና "የመደመር መንግሥት" የተሰኘውን አዲስ መጽሐፍ በተመለከተ ከፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ጋር ያደረጉት ቃለ መጠይቅ ነገ ነሐሴ 14 ቀን 2017 ዓ.ም ከምሽቱ 2:30 ይጠብቁ።

#መደመር

Address

Addis Ababa

Telephone

+251935126304

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Dawuro Media Network posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Dawuro Media Network:

Share