Divers Media Network - DMN

Divers Media Network - DMN This is promoter center....
(2)

የዳሸን ባንክ ክሬቲቭ ቻሌንጅ የ6 ሚሊዮን ብሩ አሸናፊዎች ታውቀዋል!እንኳን ደስ ያላችሁ!         #የዳሸንክሬቲቭቻሌንጅ
03/08/2026

የዳሸን ባንክ ክሬቲቭ ቻሌንጅ የ6 ሚሊዮን ብሩ አሸናፊዎች ታውቀዋል!

እንኳን ደስ ያላችሁ!

#የዳሸንክሬቲቭቻሌንጅ

በስራና ክህሎት ሚኒስቴር ድጋፍ በሰሜን ቤንች ወረዳ የሚገነባው የሞዴል ቅድመ-መደበኛ ትምህርት ቤት የመሠረት ድንጋይ ተቀመጠ።​በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ድጋፍ በሰሜን ቤንች ወረዳ የሚገነባው ...
03/08/2026

በስራና ክህሎት ሚኒስቴር ድጋፍ በሰሜን ቤንች ወረዳ የሚገነባው የሞዴል ቅድመ-መደበኛ ትምህርት ቤት የመሠረት ድንጋይ ተቀመጠ።

​በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ድጋፍ በሰሜን ቤንች ወረዳ የሚገነባው የ"መንጃጅ ሞዴል ቅድመ-መደበኛ (መዋለ ሕፃናት) ትምህርት ቤት ግንባታ ማስጀመሪያ የመሠረት ድንጋይ የማስቀመጥ ሥነ-ሥርዓት በዛሬው ዕለት ተካሄደ።

​በመርሃ-ግብሩ ላይ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ዴኤታ ዶክተር ተሻለ ደሬቻ እና የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ዴኤታ አቶ ሰለሞን ሶካን ጨምሮ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል፣ የቤንች ሸኮ ዞንና የሰሜን ቤንች ወረዳ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም የአካባቢው ማህበረሰብ ተገኝተዋል።

​ይህ የሚገነባው ዘመናዊ ሞዴል ቅድመ-መደበኛ ትምህርት ቤት የሕፃናትን ቀዳሚ የትምህርት ዕድገት ለማፋጠን ጥራት ያለው የትምህርት መሠረት ለመጣል እና የአካባቢውን ማህበረሰብ የትምህርት ጥያቄ ለመመለስ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው በሥነ-ሥርዓቱ ላይ ተገልጿል።

​በመርሃ-ግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ዴኤታ ዶክተር ተሻለ ደሬቻ በሀገር አቀፍ ደረጃ እስከዛሬ 8 ዙሮች የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር መካሄዱን ጠቅሰው ባለፉት 7 ዙሮች 48 ቢሊዮን ችግኞች መተከላቸውን እና በአጠቃላይ 56 ቢሊዮን ችግኞችን ለማድረስ ታቅዶ እየተሠራ መሆኑን አስታውቀዋል።

የዛሬው ዕለት አገር አቀፍ የአንድ ቀን መርሃ-ግብር 800 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል ያለመ መሆኑን ጠቁመው የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱሥራ ባልደረቦች በሰሜን ቤንች ወረዳ 10 ሺህ የቡና ችግኞችን በመትከል የበኩላቸውን አሻራ ማሳረፋቸውን ገልጸዋል።

​ኢትዮጵያ ለአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ ያላት ቁርጠኝነት ለአለም ማሳየቷን የገለጹት ዶክተር ተሻለ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ቀጣዩን የኮፕ 32 (COP32) ጉባኤ እንድታዘጋጅ መመረጧ አንዱ ማሳያ መሆኑን ተናግረዋል።

አያይዘውም በወረዳው የተከናወነው የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ሰው ያለውን ማጋራት፣ መቁረስ እና መደመር አለበት በሚለው መርህ ላይ የተመሰረተ መሆኑን አንስተዋል።

​የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕረግ የመሠረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪና የመንገድ ልማትና ትራንስፖርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ፋጁዋ ሳፒ በበኩላቸው ሰሜን ቤንች ወረዳ 10 ሺህ የቡና ችግኞችን መትከሉን ገልጸው ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የትምህርት ስብራትን ለመጠገን ቅድመ-መደበኛ ትምህርት ቤት ግንባታ ላይ እያበረከተ ያለው አስተዋጽኦ የማይተካ መሆኑን አድንቀዋል።

​የቤንች ሸኮ ዞን የብልፅግና ፓርቲ የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊና የርዕሰ መስተዳድር ተጠሪ አቶ ማርቆስ ጎቢ በሰጡት አስተያየት ክልሉ የትምህርት ውጤታማነትን ለማረጋገጥ የቅድመ-መደበኛ ትምህርትን ማስፋፋት ዋና ግብ አድርጎ እየሠራ መሆኑን ገልጸዋል።

የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ትምህርት የሀገር ዕድገት መሠረት መሆኑን ተገንዝቦ ይህንን ወሳኝ ችግር ለመፍታት ያደረገውን የበጎ አድራጎት ፕሮግራም በዞኑ አስተዳደር እና በክልሉ ስም ከፍተኛ ምስጋና አቅርበዋል።

​የሚኒስቴሩ ከፍተኛ አመራሮች ፕሮጀክቱ በተቀመጠለት የጊዜ ሰሌዳና የጥራት ደረጃ ተጠናቆ ለተገልጋዮች ክፍት እንዲሆን አስፈላጊው ክትትልና ድጋፍ እንደሚደረግ አረጋግጠዋል።

የአካባቢው ነዋሪዎችና አመራሮችም በወረዳው ለሚገነባው ትምህርት ቤት ምስጋናቸውን አቅርበው ግንባታው በፍጥነት እንዲጠናቀቅ አስፈላጊውን በጎ ፈቃደኝነትና ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል ሲል የዘገበው የዞኑ የመንግሥት ኮሚዩኒኬሽን ነው።

በሰሜን ሸዋ ጻድቃኔ ማርያም ገዳም በመሬት መንሸራተት አደጋ የ14 ሰዎች ሕይወት አለፈበሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ስር በሚገኘው ታሪካዊው የጻድቃኔ ደብረ ምጥማቅ ቅድስት ማርያም ገዳም በደረሰ ...
03/08/2026

በሰሜን ሸዋ ጻድቃኔ ማርያም ገዳም በመሬት መንሸራተት አደጋ የ14 ሰዎች ሕይወት አለፈ

በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ስር በሚገኘው ታሪካዊው የጻድቃኔ ደብረ ምጥማቅ ቅድስት ማርያም ገዳም በደረሰ ድንገተኛ የመሬት መንሸራተትና ርዕደ መሬት የ14 ሰዎች ሕይወት ሲያልፍ፣ በ5 ሰዎች ላይ ደግሞ የከባድና ቀላል አካል ጉዳት መድረሱ ተገለጸ።

አደጋው የተከሰተው ከክረምቱ ወቅታዊ ሁኔታ ጋር ተያይዞ በጣለው ከፍተኛ ዝናብ ምክንያት ሲሆን፣ በወቅቱ

* ለጸበል፣
* ለሱባኤና
* ለንግስ ከአራቱም አቅጣጫዎች በገዳሙ ተገኝተው በነበሩ ምዕመናን ላይ ጉዳቱ መድረሱ ታውቋል።

የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ በአደጋው ስፍራ በአካል በመገኘት ለሕይወታቸው ያለፉት ጸሎተ ፍትሐት ያደረሱ ሲሆን፣ ለተጎዱትና ለተጨነቁት ምዕመናንም አባታዊ ቃለ በረከትና የማጽናኛ ትምህርተ ወንጌል ሰጥተዋል።

ሀገረ ስብከቱ በደረሰው ድንገተኛ የመርዶ አደጋ ጥልቅና መሪር ኀዘን የተሰማው መሆኑን ገልጾ፣ ለሞቱት ዕረፍተ ነፍስን፣ ለተጎዱት ፈጣን ፈውስን እንዲሁም ለቤተሰቦቻቸው መጽናናትን ተመኝቷል።

ልዑል እግዚአብሔር አምላካችን በገዳሙ የተሰበሰቡትን ቅዱሳን አባቶችንና እናቶችን ጸሎት ተቀብሎ፣ ለሞቱት ወገኖቻችን በገነተ መንግሥቱ ዕረፍተ ነፍስን እንዲያድልልን፣

በሕክምና ላይ ለሚገኙት ተጎጂዎች አልጋቸውን አንስቶ ፈጣን የሕሊናና የሥጋ ፈውስን እንዲልክልን፣

እንዲሁም ለቤተሰቦቻቸውና ለጠቅላላው የቤተክርስቲያን ልጆች የመንፈስ ቅዱስን መጽናናት እንዲያሳድርልን ከዕንባ ጋር በጸሎት እንለምናለን።

መረጃው የሰሜን ሽዋ ሀገረ ስብከት አቡቀለምሲስ ሚዲያ ነው::

Via:- ጉርሻ page

03/08/2026
  🌿🌿🌿በአንድ ጀምበር 800 ሚሊዮን ችግኞች የመትከል መርሐ ግብር በይፋ ተጀምሯል።በአንድ ጀምበር 800 ሚሊዮን ችግኞችን የመትከል ታሪካዊ መርሐ ግብር በይፋ መጀመሩን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን...
03/08/2026

🌿🌿🌿
በአንድ ጀምበር 800 ሚሊዮን ችግኞች የመትከል መርሐ ግብር በይፋ ተጀምሯል።

በአንድ ጀምበር 800 ሚሊዮን ችግኞችን የመትከል ታሪካዊ መርሐ ግብር በይፋ መጀመሩን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር እናትዓለም መለሰ አብሥረዋል።

ሚኒስትሯ በመግለጫቸው እንዳሉት ኢትዮጵያውያን እንደተለመደው ታሪክ ይሠራሉ።

ኑ ተስፋን እንትከል ሲሉ ጥሪ ያቀረቡት ሚኒስትሯ፣ ዛሬ ታሪካዊ በሆነችው ቀን ኢትዮጵያውያን በአንድ ጀምበር 800 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል መሬትን ይዳስሳሉ፣ መሬትም ቃሏን የምታፀናበት ነው ብለዋል።

800 ሚሊዮን ችግኞች፣ በተግባር እና በሐሳብ አንድነት በመደመር ዕሳቤ እናሳካለንም ብለዋል።
Ethiopian Broadcasting Corporation



02/08/2026
እድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ሕፃናትን ወደ ትምህርት ቤት መላክ የሁሉም ኃላፊነት መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አሳሰበ።-------------------------- // ----------------...
02/08/2026

እድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ሕፃናትን ወደ ትምህርት ቤት መላክ የሁሉም ኃላፊነት መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አሳሰበ።

-------------------------- // ------------------------

(ሐምሌ 26/2018 ዓ.ም) የ2019 የትምህርት ዘመን ተማሪዎችን ወደ ትምህርት ቤት የመመለስ የትምህርት ንቅናቄ ሰነድ በአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ የምክክር መድረክ ቀርቦ በባለድርሻ አካላት ውይይት ተደርጎበታል።

በመድረኩ ላይ ክብርት ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ አየለች እሸቴ እንደገለጹት፣ በአጠቃላይ ትምህርት አዋጅ መሠረት ለትምህርት የደረሱ ሁሉም ዜጎች ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ወደ ትምህርት ቤት እንዲገቡ ማድረግ የመንግሥትና የማኅበረሰቡ የጋራ ኃላፊነት ነው።

በመሆኑም ሕብረተሰቡ ልጆቹን ወደ ትምህርት ቤት በመላክ እንዲሁም በተለያዩ የሰው ሰራሽና የተፈጥሮ ችግሮች ምክንያት ከትምህርት ገበታ ውጪ የነበሩ ተማሪዎች እንደገና ወደ ትምህርት ገበታቸው እንዲመለሱ በማድረግ ኃላፊነቱን እንዲወጣ ሚኒስትር ዴኤታዋ ጥሪ አቅርበዋል።

በተጨማሪም በየደረጃው ያሉ የትምህርት ዘርፍ አመራሮች፣ ባለሙያዎችና ባለድርሻ አካላት ሁሉም እድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ሕፃናትን እንዲሁም ልዩ ፍላጎት ያላቸው ዜጎችን በሙሉ ወደ ትምህርት ቤት እንዲገቡ በማድረግ ረገድ የራሳቸውን ሚና እንዲወጡ አሳስበዋል።

ተማሪዎችን ወደ ትምህርት ቤት ማምጣት ብቻ ሳይሆን እንዲቆዩና ጥራቱን የጠበቀ ትምህርት በማግኘት በቂ እውቀትና ክህሎት እንዲያዳብሩ ልዩ ስትራቴጂ ቀይሶ መሥራት እንደሚገባም አስገንዝበዋል።

የ2019 የትምህርት ዘመን የትምህርት ንቅናቄ ሰነድን ያቀረቡት የትምህርት ጥራትና ፕሮግራሞች መሪ ሥራ አስፈጻሚ ዶ/ር ዩሐንስ ወጋሶ በበኩላቸው በ2019 የትምህርት ዘመን 30 ሚሊዮን ተማሪዎችን ለመመዝገብ ዕቅድ መያዙን ገልጸው ይህንን ለማሳካት ከትምህርት ሚኒስቴር እስከ ትምህርት ቤት ድረስ የተቀናጀ የትምህርት ንቅናቄ እንደሚካሄድ አብራርተዋል።

በዚህም የ2019 የትምህርት ዘመን የትምህርት ቤት ምዝገባ ከነሐሴ 26 እስከ ጳጉሜ 5 እንደሚካሄድ ጠቅሰው በየትምህርት ቤቱ ውይይት የሚደረግበት የንቅናቄ ሰነድ መዘጋጀቱን አብራርተዋል።

በንቅናቄ ሰነዱ መሠረት ለትምህርት የደረሱ ሁሉም ሕፃናት ወደ ትምህርት ቤት እንዲገቡ ቤት ለቤት የማስተዋወቅና የቅስቀሳ ሥራ እንደሚከናወን ገልጸው ተማሪዎችን ወደ ትምህርት ቤት ማምጣት ብቻ ሳይሆን እስከ ትምህርት ዘመኑ መጨረሻ ድረስ በትምህርት እንዲቆዩና እንዲያጠናቅቁ በልዩ ትኩረት እንደሚሠራም ጠቁመዋል ሲል የዘገበው የኢፌዲሪ ትምህርት ሚንስቴር ነው።

Southwest Education Bureau Divers Media Network - DMN

02/08/2026

የባህል አምባሳደሯ ጽጌ ምን አለች?

"የዛሬ አሻራችን የነገ ተስፋችን ነው!" ክቡር አቶ አልማው ዘውዴ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊSouthwest Communicatio...
01/08/2026

"የዛሬ አሻራችን የነገ ተስፋችን ነው!" ክቡር አቶ አልማው ዘውዴ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ

Southwest Communications Southwest Education Bureau

ኑ አስደናቂ የዓለማችንን ታሪኮች ይከታተሉ፣ ለሕይወት ስንቅ የሚሆኑ ታሪኮች ይማሩ!🙏       በማድረግ ይወዳጁ 🙏❤
01/08/2026

ኑ አስደናቂ የዓለማችንን ታሪኮች ይከታተሉ፣ ለሕይወት ስንቅ የሚሆኑ ታሪኮች ይማሩ!🙏
በማድረግ ይወዳጁ 🙏❤

🔥 ያልተነገረው የኔልሰን ማንዴላ እውነተኛ ታሪክ! | Nelson Mandela Story በዚህ ቪዲዮ የደ...

Address

Addis Ababa

Telephone

+251935126304

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Divers Media Network - DMN posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Divers Media Network - DMN:

Shortcuts

Share