Exclusive Ethiopia

Exclusive Ethiopia ለተመረጡ ቃለ መጠይቆች ብቻ ☕️ ☕️

የመራቢያ አካሉ በመታመሙ ሁለት ጨዋታም አይሰለፍም ተባለክለቡ እንዳስታወቀው ከሆነ ላሚን ያማል የመራቢያ አካሉ አካባቢ እንደታመመ እና ልምምድ ለመስራትም እንደተቸገረ ክለቡ ባርሲልና አስታውቋ...
13/09/2025

የመራቢያ አካሉ በመታመሙ ሁለት ጨዋታም አይሰለፍም ተባለ

ክለቡ እንዳስታወቀው ከሆነ ላሚን ያማል የመራቢያ አካሉ አካባቢ እንደታመመ እና ልምምድ ለመስራትም እንደተቸገረ ክለቡ ባርሲልና አስታውቋል። በዚህም ምክንያት ከነገው የቫሌንሽያ ጨዋታ እና ከኒውካስል ጨዋታ አይሳተፍም።

ለምርምር ወደሕዋ እንድትጓዝ የተመረጠችው ኢትዮጵያዊትእመቤት መሀባው ትባላለች። ከልጅነቷ አንስቶ ለሕዋ ሳይንስ ፍቅር እንደነበራት ታስታውሳለች።በኋላም በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨር...
10/09/2025

ለምርምር ወደሕዋ እንድትጓዝ የተመረጠችው ኢትዮጵያዊት

እመቤት መሀባው ትባላለች። ከልጅነቷ አንስቶ ለሕዋ ሳይንስ ፍቅር እንደነበራት ታስታውሳለች።

በኋላም በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ትምህርቷን እየተከታተለች ሳለ በሕዋ ሳይንስ የትምህርት ዘርፍ ስኮላርሺፕ አግኝታ ወደሕንድ አቀናች።

በኋላም አሜሪካ ውስጥ በሕዋ ሳይንስ ምርምር ላይ የሚሰራውን ታይታንስ ስፔስ ኢንዱስትሪን መቀላቀል ችላለች።

በዚያም በኤሮስፔስ ኢንጂነርነት ሙያዋ የተለያዩ የምርምር ሥራዎችን እያከናወነች ይገኛል።

የምትሰራበት የሕዋ ምርምር ተቋም በእ.አ.አ. በ2029 ወደጠፈር ለሚያደርገው ጉዞ እመቤት መሀባውን ከተጓዥ ተመራማሪዎች መካከል አንዷ እንድትሆን መርጧታል።

ለዚህ ምርጫ የተለያዩ መስፈርቶች ቢኖሩትም፤ ግዳጁን ለመፈፀም በአካል፣ በስነልቦናም ሆነ በምርምር ሥራዋ ብቁ መሆኗ ካስመረጧች ምክንያቶች መካከል ዋነኞቹ መሆናቸውን ነው የገለፀችው።

ወጣቷ የሕዋ ሳይንስ ባለሙያ ለጠፈር ጉዞዋ የሚረዳትን የተለያዩ ዝግጅቶች እያደረገች ሲሆን፤ በቡድን የሚደረገውን ዝግጅት ደግሞ እ.አ.አ. በ2026 አካባቢ እንደምትጀምር ነው የተናገረችው።

በምድር ምህዋር ላይ በመሽከርከር የተለያዩ ምርምሮችን ማከናወንን የሚያካትተውን የሕዋ ጉዞ ዕድሉን የኢትዮጵያን ስም ከፍ ለማድረግ እንደምትጠቀምበት ተናግራለች።

በተለይም ወደሕዋ በሚኖራት ጉዞ ላይ የኢትዮጵያን ሰንደቅ አላማ ይዛ የመሄድ ፍላጎት እንዳላትም አሳውቃለች።

በተለያዩ ዓለም አቀፍ ደረጃዎች ዕውቅና እያገኘች የመጣችው እመቤት፤ ለስፔስ ጄኔሬሽን አድቫይዞሪ ካውንስል የኢትዮጵያ ተወካይ በመሆን እያገለገለች ይገኛል።

ከአፍሪካ ስፔስ ሊደርስ አዋርድ በ2024 ከአፍሪካ 4 ተሸላሚ ወጣቶች መካከል አንዷም ነበረች።

ዓለም አቀፉ አስትሮናውቲካል ፌዴሬሽንም በ2025 ተስፈኛ ከሆኑ የሕዋ ሳይንስ ባለሙያዎች መካከል አንዷ መሆኗን አሳውቋል።

በጌትነት ተስፋማርያም

ሰበር ዜና - አቶ ለማ መገርሳ ተነፈሱ"ስለሚፈሰው ደም በጋራ መቋጫ ልናበጅለት ግድ ይለናልም” አሉየቀድሞ የኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ፕረዝደንትና የአገር መከላከያ ሚኒስትር አቶ ለማ ...
09/09/2025

ሰበር ዜና - አቶ ለማ መገርሳ ተነፈሱ

"ስለሚፈሰው ደም በጋራ መቋጫ ልናበጅለት ግድ ይለናልም” አሉ

የቀድሞ የኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ፕረዝደንትና የአገር መከላከያ ሚኒስትር አቶ ለማ መገርሳ በህዳሴ ግድብ መጠናቀቅ የተሰማቸውን ደስታ ገለፁ።

አቶ ለማ ለOMN በላኩት መግለጫ “በመላው የኢትዮጵያውያን ተሳትፎና ጥረት የተገነባው ታላቁ የህዳሴ ግድብ በመጠናቀቁ እንኳን ደስ አላችሁ፣ እንኳን ደስ አለን” ብለዋል።

“እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ከትንሽ እስከ ትልቅ: ከደሃ እሰከ ሀብታም ይህንን ግድብ ለመገንባት የአቅሙን ያህል ሀብት በማዋጣት አሻራውን ያሳረፈበት ታሪካዊ ግድብ ነው” ያሉት አቶ ለማ፣ “የአንድነታችን ተምሳሌት ነው። ከዚህ ግድብ በቀጥታ ከምናገኘው ጥቅም በላይ ታሪካዊ የምያሰኘው: መላው ኢትዮጵያዊ ሁሉ አንድ የሆነበትና በአንድነት በጋራ የማይደፈረውን ደፍሮ መስራቱ ነው” ብለዋል።

ይህም የሚያሳየው ኢትዮጵያዊያን ስተባበሩ ደማቅ ታሪክ መስራት እንደሚችሉ መሆኑን ገልፀዋል።

ስለሆነም መላው ኢትዮጵያውያን ምንግዜም አንድነታቸው የድላቸው መሠረት መሆኑን በመገንዘብ ለነገይቱ የተሻለች ኢትዮጵያ: አንድነታቸውን መጠበቅና ማጠናከር የግድ መሆኑን አስረድተዋል።

“ይህንን ታሪካዊ የህዳሴ ግድብ አስጀምረው በማጠናቀቅ ሂደት ውስጥ አስተዋጽኦ የነበራቸው የአገራችን መሪዎችና ባለሙያዎች ሁሉ እንደየድርሻቸውና አስተዋጽኦአቸው መጠን ምስጋና ይገባቸዋል” ብለዋል።

“ከዚሁ ህዳሴ ግድብ ምርቃት ጎን ለጎን በየቀኑ ስለሚጠፋው የዜጎቻችን ህይወት: ስለሚፈሰው ደምና ስለምታነባው ኢትዮጵያዊ እናት: በጥቅሉ ስለአገራችን ሠላምና ደህንነት ቆም ብለን ልናስብበትና በጋራ መቋጫ ልናበጅለት ግድ ይለናል” ብለዋል አቶ ለማ መገርሳ።

OMN

በ14 ዓመታት የታላቁ የሕዳሴ ግድብ ግንባታ ጉዞ ውስጥ ከ15ሺ በላይ ሰዎች ሕይወታቸው አልፏል !!ሕዳሴ የደም ዋጋም ተከፍሎበታል !ሪፖርተር የእንግሊዘኛው መጽሔት ከውሃና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ኢ...
02/09/2025

በ14 ዓመታት የታላቁ የሕዳሴ ግድብ ግንባታ ጉዞ ውስጥ
ከ15ሺ በላይ ሰዎች ሕይወታቸው አልፏል !!

ሕዳሴ የደም ዋጋም ተከፍሎበታል !

ሪፖርተር የእንግሊዘኛው መጽሔት ከውሃና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ኢንጂነር ሃብታሙ ኢተፋ ጋር ያደረገውን ቆይታ አውጥቷል።

በቆይታው ማብቂያ ጠያቂው ጋዜጠኛ በእውቀት አበበ ይህን ጠየቀ ...እርሳቸውም መለሱ
Is it true that as many as 15,000 people died while building the dam over the past 14 years?

Yes, that is true.
በገንዘብ በጊዜና በብዙ መስዋዕትነት ብቻ አይደለም ሕዳሴ በ15 ሺ የአገራችን ልጆች ደምም ጭምር ነው የተገነበው ።

ኢንተርናሽናል ዳኛ ባምላክ ተሰማ ራሱን ከዳኝነት ዓለም ለማግለል መወሰኑን አስታወቀ።ያለፉትን ረጅም ዓመታት በወጥነት በሀገር ውስጥ እና ዓለም አቀፍ መድረኮች በዳኝነት ያገለገለው ባምላክ ተሰ...
31/08/2025

ኢንተርናሽናል ዳኛ ባምላክ ተሰማ ራሱን ከዳኝነት ዓለም ለማግለል መወሰኑን አስታወቀ።

ያለፉትን ረጅም ዓመታት በወጥነት በሀገር ውስጥ እና ዓለም አቀፍ መድረኮች በዳኝነት ያገለገለው ባምላክ ተሰማ ከዳኝነት ዓለም ራሱን ለማግለል መወሰኑን ለፊፋ በላከው መልዕክት አስታውቋል።

በዓለም ዋንጫ፣ የአፍሪካ ዋንጫ፣ ቻን፣ ቻምፒየንስ ሊግ፣ ኮንፌሬዴሽን ዋንጫ፣ የዓለም ክለቦች ዋንጫ እና ኦሊምፒክን ጨምሮ በርካታ ሀገራዊ እና ዓለም አቀፋዊ ታላላቅ ጨዋታዎችን በመምራት የሀገሩን ስም ከፍ አድርጎ ያስጠራው ባምላክ ኢትዮጵያን በሀገር አቀፍም ሆነ በዓለም አቀፍ መድረክ በማገልገሉ ኩራት እንደሚሰማው ገልጾ ፊፋ ለሰጠው ዕድል በማመስገን ከኢንተርናሽናል ዳኝነት ራሱን ማግለሉን አስታውቋል።

"ዩኒቨርሲቲዎች የሚጠበቅባቸውን መሥፈርቶች ካላሟሉ አዳሪ ትምህርት ቤቶች ይደረጋሉ" ዶክተር ብርሃኑ ነጋ
29/08/2025

"ዩኒቨርሲቲዎች የሚጠበቅባቸውን መሥፈርቶች ካላሟሉ አዳሪ ትምህርት ቤቶች ይደረጋሉ"

ዶክተር ብርሃኑ ነጋ

“የኢትዮጵያ ሥም ይቀየር የሚል ጥያቄ ቀርቦልናል”  -የምክክር ኮሚሽኑ ከኢትዮጵያ ውጭ ከሚገኙ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን አጀንዳዎችን ማሰባሰብ የጀመረው የኢትዮጵያ ሀገራዊ የም...
29/08/2025

“የኢትዮጵያ ሥም ይቀየር የሚል ጥያቄ ቀርቦልናል” -የምክክር ኮሚሽኑ

ከኢትዮጵያ ውጭ ከሚገኙ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን አጀንዳዎችን ማሰባሰብ የጀመረው የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን “የኢትዮጵያ ሥም ይቀየር የሚል ጥያቄ ቀርቦልኛል” አለ። ይህንን ለሉዓላዊ ሚዲያ የተናገሩት ኮሚሽኑ ካሉት 11 ኮሚሽነሮች ውስጥ አንዱ የሆኑት ዮናስ አዳዬ (ዶ/ር) ናቸው።

መቼም ዘንድሮ አይሰማ ነገር የለም🤔🤐

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Exclusive Ethiopia posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category