ሁዳ መልቲሚዲያ / Huda Multimedia

ሁዳ መልቲሚዲያ / Huda Multimedia ሁዳ መልቲሚዲያ
ጠቃሚ ናቸው የምንላቸውን መልእክቶች ቪዲዮዎችና ስነ ፅሁፎች ወደ እናንተ እናደርሳለን
(2)

ሁዳ መልቲሚዲያ: ንጹሀ ኢስላማዊ እውቀቶችን በማስጨበጥ ላይ እንሰራለን።

ሁዳ መልቲሚዲያ
----------------------
በቴሌግራም
t.me/huda4eth
በፌስቡክ
fb.com/huda4etb
በዩትዩብ
https://goo.gl/WK5K5N
ያግኙን

18/09/2025

ከመስከረም 16 እስከ 26 8ኛ ዙር ልዩ የዑምራ ፓኬጅ
ምዝገባ እየተገባደደ ነው ፈጥነው ይመዝገቡ
--------

*ቪዛ
*የደርሶ መልስ ቲኬት
*በመካ ቁርስን ያካተተ ምርጥና ለሀረም ቅርብ ሆቴሎች በሁለቱም ሀረሞች
*የታሪካዊ ቦታዎች ጉብኝት
*ሾፒንግ በጅዳ ከተማ
----------

ለመመዝገብ
0967237373 ይደውሉ
ወይም በቴሌግራም t.me/umraLemon
ያናግሩን

15/09/2025

ካንተ ጋር...በአቡበከር ይርጋ

☀ ሁዳ መልቲሚዲያ
----------------------
በቴሌግራም
t.me/huda4eth
በፌስቡክ
fb.com/huda4eth
በዩትዩብ
https://youtube.com/?si=TnzH2hQKlhUTLvIx
በ ቲክ ቶክ

ያግኙ

የ2017 የመጅሊስ ምርጫ የምስጋና እና የእውቅና ፕሮግራም የአዲስ አበባ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት በአድዋ 00 አዳራሽ እያካሄደ ባለው የምስጋናና የእውቅና ፕሮግራም ላይ ምር...
14/09/2025

የ2017 የመጅሊስ ምርጫ የምስጋና እና የእውቅና ፕሮግራም የአዲስ አበባ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት በአድዋ 00 አዳራሽ እያካሄደ ባለው የምስጋናና የእውቅና ፕሮግራም ላይ ምርጫው የተሳካ ይሆን ዘንድ አስተዋፅኦን ላበረከቱ የተለያዩ ሚዲያዎች ምስጋናና ሰርተፍኬት ፕሮግራም ተካሂዷል።

በዚህም መሰረት የተለያዩ ሚዲያዎች ሰርቲፊኬት የተቀበሉ ሲሆን የተወሰኑትን ለመጥቀስ ያክል EBC, Fana, Addis Media Network, OBN እና ሌሎችም የሀገር ውስጥ ሚዲያዎች እንዲሁም ከኢስላማዊ ሚዲያዎች ውስጥ ሚዲያችን ሁዳ መልቲሚዲያን ጨምሮ ሀሩን ሚዲያ፣ አፍሪካ ቲቪ፣ ነጃሺ ቲቪ፣ ነሲሓ ቲቪ፣ ሀሚልተን ቲቪ፣ ዛውያ ቲቪ፣ ሚንበር ቲቪ፣ በረካ መልቲሚዲያ፣ OIM፣ Prime Media እና ሌሎችም የምስጋና ሰርተፍኬት ተሰጥቷቸዋል። ሚዲያችንም በዚሁ አጋጣሚ ምስጋናውን ያቀርባል

የአዲስ አበባ መጅሊስ በአድዋ 00 አዳራሽ የአዲስ አበባ ክፍለ ከተማዎችና ወረዳዎች ተመርጠው የመጡ አዲስ ተመራጮችን የሰበሰበ የእውቅና ፕሮግራም ሂደቱ በመቀጠል በየክፍለ ከተማው ምርጫው በተ...
14/09/2025

የአዲስ አበባ መጅሊስ በአድዋ 00 አዳራሽ የአዲስ አበባ ክፍለ ከተማዎችና ወረዳዎች ተመርጠው የመጡ አዲስ ተመራጮችን የሰበሰበ የእውቅና ፕሮግራም ሂደቱ በመቀጠል በየክፍለ ከተማው ምርጫው በተሳካ ሁኔታ ይጠናቀቅ ዘንድ አስተዋፅኦ ያበረከቱ የምርጫ አስፈፃሚዎችን የምስጋና ሽልማት ተሸልመዋል።

በዛሬው እለት የአዲስ አበባ መጅሊስ በአድዋ 00 አዳራሽ የአዲስ አበባ ክፍለ ከተማዎችና ወረዳዎች ተመርጠው የመጡ አዲስ ተመራጮችን የሰበሰበ የእውቅና ፕሮግራም አካሂዷል። በፕሮግራሙ መክፈቻ ...
14/09/2025

በዛሬው እለት የአዲስ አበባ መጅሊስ በአድዋ 00 አዳራሽ የአዲስ አበባ ክፍለ ከተማዎችና ወረዳዎች ተመርጠው የመጡ አዲስ ተመራጮችን የሰበሰበ የእውቅና ፕሮግራም አካሂዷል። በፕሮግራሙ መክፈቻ ላይ በቃሪእ ኢብራሂም ኸይረዲን ሙሀመድ የመክፈቻ ቁርአን የተጀመረ ሲሆን በመቀጠልም የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ፕሬዝዳንት የሆኑት ሸህ ሱልጣን አማን ኤባ የመክፈቻ ንግግር አድርገዋል። በንግግራቸው ዳግም የአዲስ አበባ መጅሊስ ፕሬዝዳንት ለመሆን የመረጣቸውን ህዝብ አመስግነው አዲስ አበባን እንደ ከተማም ሆነ እንደ ሙስሊም ነዋሪዎቿ ወደ ልህቀትና ወደ ተሻለ ማንነት ከፍ ለማድረግ ከህዝቡ ጋር በተናበበ ሁኔታ ለመስራት ዝግጁ መሆናቸውን እንደ አዲስ አበባ መጅሊስ ፕሬዝዳንትነት አሳውቀዋል!

በመቀጠልም ከምርጫ ቦርድ ወንድማችን ኢብራሂም ሙሉሸዋ የምርጫውን ሂደት አስመልክቶ የተናገረ ሲሆን
የምርጫው ሂደት በግልፅነትና በፍትሃዊነት በሚዲያ እየታየ የተካሄደ የምርጫ ሂደት የነበረ መሆኑን ጠቅሰው በአዲስ አበባ በየመስጂዱ የነበሩ የምርጫ አስፈፃሚዎችን አናግረው ፍፁም ግልፅና ለማንም ያልተሰወረ የአመራረጥ ሂደትን አልፈው ተመራጮች እንደተመለመሉ መረጃ መሰብሰብ መቻላቸውን ገልፀዋል! ታዳሚውም ይህን እውነታ በተክቢራ አረጋግጧል!

ቀጣይ ፕሮግራሞችን የምናሳውቅ ይሆናል....

በዛሬው በአድዋ 00 አዳራሽ እየተካሄደ በሚገኘው የአ/አበባ ከተማ ክፍለ ከተሞችና ወረዳዎች መጅሊስ ተመራጮች አደረጃጀት ፕሮግራም ላይ ወንድማችን ቃሪእ ኢብራሂም ኸይረዲን ሙሀመድ ኢትዮጵያን ...
14/09/2025

በዛሬው በአድዋ 00 አዳራሽ እየተካሄደ በሚገኘው የአ/አበባ ከተማ ክፍለ ከተሞችና ወረዳዎች መጅሊስ ተመራጮች አደረጃጀት ፕሮግራም ላይ ወንድማችን ቃሪእ ኢብራሂም ኸይረዲን ሙሀመድ ኢትዮጵያን ወክሎ በቁርአን በመወዳደር የሀገራችንን ስም እያስጠራ የሚገኘው ወንድማችንን መጅሊሱ የእውቅናና የማበረታቻ ሽልማት ሸልሞታል።

የስብሰባውን ፍሬ ሀሳብ የምንገልፅ ይሆናል ይጠብቁን!

13/09/2025

ከመስከረም 16 እስከ 26 8ኛ ዙር ልዩ የዑምራ ፓኬጅ
--------

*ቪዛ
*የደርሶ መልስ ቲኬት
*በመካ ቁርስን ያካተተ ምርጥና ለሀረም ቅርብ ሆቴሎች በሁለቱም ሀረሞች
*የታሪካዊ ቦታዎች ጉብኝት
*ሾፒንግ በጅዳ ከተማ
----------

ለመመዝገብ
0967237373
ወይም በቴሌግራም t.me/umraLemon
ያናግሩን

13/09/2025

አባታችን አደም በቀደር አሳበዋል ወይ??

☀ ሁዳ መልቲሚዲያ
----------------------
በቴሌግራም
t.me/huda4eth
በፌስቡክ
fb.com/huda4eth
በዩትዩብ
https://youtube.com/?si=TnzH2hQKlhUTLvIx
በ ቲክ ቶክ

ያግኙ

አላህ አባትህን ይማርልህ የጀነት ያርግልህ ኋ! ሰላሃዲን መስጂድም ያልቃል ኢንሻአላህ
12/09/2025

አላህ አባትህን ይማርልህ የጀነት ያርግልህ ኋ! ሰላሃዲን መስጂድም ያልቃል ኢንሻአላህ

11/09/2025

8ኛ ዙር ልዩ የዑምራ ጉዞ ከመስከረም 16 እስከ 26
(Sep 26 to Oct 06) ከኡስታዝ ሁሴን አለሙ ጋር
----------------
7 ቀን በመካ
3 ቀን በመዲና
-------------

በዚህ የዑምራ ፓኬጅ የተካተተው:-

* ቪዛና የደርሶ መልስ ቲኬት
* ለ2ቱም ሀረሞች ቅርብ የሆኑ ጥራታቸውን የጠበቁ ሆቴሎች
* ቁርስ ያካተተ
* ሙሉ የትራንስፖርት ወጪ
* በመካና በመዲና የታሪካዊ ቦታዎች ጉብኝት
* የዑምራ አደራረግ ቅድመ ስልጠና እና የልምድ ልውውጦች
* ሾፒንግ ያካተተ ፓኬጅ
-------------

ቀድመው ለሚመዘገቡ ደንበኞች ቅናሽ አዘጋጅተናል! በተጨማሪም ለቤተሰብና በግሩፕ ለሚጓዙ ታላቅ ቅናሽ አዘጋጅተናል
-------------
ይደውሉ

0967237373

በቴሌግራም
ወደ ቻናላችን ለመቀላቀል t.me/lemon_umra

አድራሻ:-
መርካቶ አዲስ አድማስ ህንፃ 4ኛ ፎቅ 402 ወይም ጦር ሀይሎች ድሪም ታወር 1ኛ ፎቅ 101

ሌመን ዑምራ

ከኢትዮጵያ ሙስሊሞች የጋራ ፎረም የተሰጠ መግለጫ የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ለዘመናት ዋጋ የከፈሉለት የተቋም ግንባታ ትግል በህዝቦች የተባበረ ትግል እውን ሆኗል!ጳጉሜ 2 ቀን 2017: አዲስ አበባ...
07/09/2025

ከኢትዮጵያ ሙስሊሞች የጋራ ፎረም የተሰጠ መግለጫ

የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ለዘመናት ዋጋ የከፈሉለት የተቋም ግንባታ ትግል በህዝቦች የተባበረ ትግል እውን ሆኗል!

ጳጉሜ 2 ቀን 2017: አዲስ አበባ ፣ ኢትዮጵያ

የኢትዮጵያ ሙስሊሞች የጋራ ፎረም፣ መላው የሀገራችን ሙስሊሞች ለዘመናት በናፍቆት ሲጠብቁት የነበረው እና በከባድ መስዋዕትነት የታጀበው የተቋም ግንባታ ትግል ፍሬ በማፍራቱ ለመላው ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች እንኳን ደስ አለን! እንኳን ደስ አላችሁ! ለማለት ይወዳል።

የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ጠንካራ፣ ሁሉን አቃፊና ህዝባዊ መሠረት ያለው ተቋም ለመገንባት ያደረጉት ትግል ታሪካዊ ዳራው እጅግ ረጅም ነው። ይህ ትግል፣ በአያት ቅድመ አያቶቻችን የጀመረ፣ በትውልድ ቅብብሎሽ ለዛሬው ማንነታችን የበቃ፣ በውስጡም ስፍር ቁጥር የሌለው ዋጋ የተከፈለበት ጉዞ ነው። ወንድሞቻችንና እህቶቻችን በእስር ተንገንተዋል፤ በንፁህ ደማቸው ምድርን አርሰዋል፤ በውድ ህይወታቸው ለዚህች ቀን ብርሃን መፈንጠቅ ዋጋ ከፍለዋል። ዛሬ ያ ሁሉ መስዋዕትነት ከንቱ እንዳልቀረና የትውልዱ ጩኸት ሰሚ አግኝቶ ለታሪካዊ ድል በመብቃታችን ልባችን በሀሴት ተሞልቷል። ለዚህች ታላቅ ቀን ያበቃንን አላህ (ሱ.ወ) እያመሰገንን፣ ለመላው የኢትዮጵያ ሙስሊሞች በድጋሚ እንኳን ደስ አላችሁ እንላለን።

ይህንን ታላቅ ድል ተከትሎ፣ ከልዩ ወረዳዎችና የከተማ አስተዳደሮች እስከ ዞን፣ ክልልና ፌደራል መዋቅር ድረስ በህዝብ ንቁ ተሳትፎ ወደ ኃላፊነት ለመጣችሁ አዲሱ አመራር ፎረማችን ከባድ አደራን ያስተላልፋል። ህዝበ ሙስሊሙ የሰጣችሁ አማና፣ የግል ክብር መገለጫ ሳይሆን፣ የከፈለውን መስዋዕትነት የምትዘክሩበትና ህልሙን እውን የምታደርጉበት ታላቅ ኃላፊነት መሆኑን አውቃችሁ በቀንና በሌሊት ልትተጉ ይገባል። የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ከእናንተ የሚጠብቀው ሁሉን አቃፊ፣ ፍትሐዊ፣ በሸሪዓ እውቀትና በዘመናዊ አስተዳደር የተደገፈ ብቁ መሪነትን ነው። በመሆኑም የህዝቡን የዘመናት ዋጋ የሚመጥን፣ በሁሉም ሙስሊሞች ዘንድ ተቀባይነት ያለው፣ ጠንካራ መጅሊስን እውን እንድታደርጉ ጥሪያችንን እናቀርባለን።

በሀገራችን ታሪክ በዚህ ደረጃ መላውን መስጂዶች ያሳተፈና ህዝባዊ መሠረት የያዘ የምርጫ ስርዓት ሲካሄድ ይህ የመጀመሪያው ነው። ይህ ሂደት ቀላል እንዳልነበር ሁላችንም የምንገነዘበው ሐቅ ነው። ምርጫው እንዳይካሄድና ለሌላ ጊዜ እንዲራዘም የተለያዩ ውስጣዊና ውጫዊ ተግዳሮቶች የነበሩ ቢሆንም፣ በህዝቡ ፅናትና በቅን ልቦና ባላቸው አካላት ትብብር ይህንን ሁሉ ተሻግረን ለድል በቅተናል። በመሆኑም ይህ ታሪካዊ ምርጫ በሰላማዊ ሁኔታ ተጀምሮ እንዲጠናቀቅ የበርካታ አካላት የጋራ ጥረት ውጤት መሆኑን እንገነዘባለን።

ከፌደራል እስከ ክልልና ከተማ አስተዳደር ድረስ የተዋቀሩ የምርጫ አስፈጻሚ ቦርዶች፣ ሂደቱ ለዚህ ምዕራፍ እንዲበቃ የበኩላቸውን አስተዋፅኦ ያበረከቱ የቀድሞ የመጅሊሱ አመራሮችና የመስጂድ አስተዳደሮች፣ እንዲሁም በየደረጃው የሚገኙ የፀጥታ መዋቅሮች፣ እንዲሁም ለሰላም ሚኒስቴር ላደረጉት አስተዋጽፅኦ ከፍ ያለ ምስጋናችንን እናቀርባለን።

በተለየ ሁኔታም የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ እና አስተዳደራቸው፣ የሙስሊሙ ማኅበረሰብ የራሱን መሪዎች በራሱ እንዲመርጥ ምቹ ሁኔታዎችን በመፍጠርና መንግሥት አስፈላጊውን ትብብር ከማድረግ በዘለለ ርቀቱን ጠብቆ የምርጫውን ነጻነትና ፍትሐዊነት እንዲከበር ላደረጉት ታሪካዊ አስተዋፅኦ ፎረማችን የላቀ ምስጋናውንና አክብሮቱን ይገልፃል።

በመጨረሻም መላው ህዝባችን በዚህ ምርጫ ወደ ኃላፊነት ከመጡ አመራሮች ጋር በትብብርና በቅንጅት በመስራት፣ ለጋራ ስኬትና ለተቋማዊ ልዕልና እንዲተጋ የኢትዮጵያ ሙስሊሞች የጋራ ፎረም ጥሪውን እያስተላለፈ የፎረማችን አባላት ላለፉት ወራት ከመንግስት ከፍተኛ ሀላፊዎች ፣ የመጅሊስ አመራሮች፣ የምርጫ አስፈፃሚ ቦርዶችና ከልዩ ልዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር ከፍተኛ ውይይትና ምክክሮችን በማድረግ እንዲሁም ምርጫውን የተመለከቱ በርካታ ስራዎችን ሌት ተቀን በመስራት ሂደቱ ስኬታማ እንዲሆን ከፍተኛ አስተዋፅኦ አበርክተዋል። የፎረማችን አባላት ሲያደረጉ ለነበረው ጥረትም በህዝባችን ስም ምስጋናችን የላቀ ነው።

የኢትዮጵያ ሙስሊሞች የጋራ ፎረም
ጳጉሜ 2 ቀን 2017
አዲስ አበባ ፣ ኢትዮጵያ

Address

Kolfe
Addis Ababa
1000

Website

http://www.huda4eth.com/

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ሁዳ መልቲሚዲያ / Huda Multimedia posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to ሁዳ መልቲሚዲያ / Huda Multimedia:

Share

Category