ሁዳ መልቲሚዲያ / Huda Multimedia

  • Home
  • ሁዳ መልቲሚዲያ / Huda Multimedia

ሁዳ መልቲሚዲያ / Huda Multimedia ሁዳ መልቲሚዲያ
ጠቃሚ ናቸው የምንላቸውን መልእክቶች ቪዲዮዎችና ስነ ፅሁፎች ወደ እናንተ እናደርሳለን
(1)

ሁዳ መልቲሚዲያ: ንጹሀ ኢስላማዊ እውቀቶችን በማስጨበጥ ላይ እንሰራለን።

ሁዳ መልቲሚዲያ
----------------------
በቴሌግራም
t.me/huda4eth
በፌስቡክ
fb.com/huda4etb
በዩትዩብ
https://goo.gl/WK5K5N
ያግኙን

በኦሮሚያ ክልል በሸገር ሲቲ ከተማ የሚገኘዉ አቡ ዘር መስጂድና መድረሳ መፍረሱ ታወቀ።♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️በኦሮሚያ ክልል በሸገር ከተማ መልካ ኖኖ...
26/07/2025

በኦሮሚያ ክልል በሸገር ሲቲ ከተማ የሚገኘዉ አቡ ዘር መስጂድና መድረሳ መፍረሱ ታወቀ።
♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️

በኦሮሚያ ክልል በሸገር ከተማ መልካ ኖኖ ክፍለ ከተማ በመልካ ገፈርሳ ወረዳ ወረዳ የሚገኘዉ አቡዘር መስጂድና መድረሳ በዛሬው እለት ከፈጅር ሶላት ቡኅላ መፍረሱ ታወቀ።

የአቡዘር መስጂድና መድረሳ በኦሮሚያ ክልል እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የእዉቅና ሰርተፍኬት የተሰጠዉ፣ በወቅፍ አማካኝነት ተበርክቶ አገልግሎት እየሰጠ የሚገኝ ነበር።

የአቡዘር መስጂድ ከዚህ ቡኅላ እንደማይፈርስ ከከተማው ከንቲባ ከዶር ተሾመ ጋር መነጋገሩና ከታች ባያያዝነዉ በሰርተፍኬትነት በማረጋገጥ የኦሮሚያ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት በሆኑት ሸይኽ ጋሊ ሙክታርና በዶር ሙሀመድ ሷልህ አማካኝነት ማረጋገጫ ተሰጥቶት እንደነበር ያሳያል።

በዛሬው እለት የፈጅር ሶላት እንደተጠናቀቀ የአፍራሽ ግብረ ኀይል በመምጣት የአቡዘር መስጂድና መድረሳን ማፍረሱና ማቴሬያሎችን ጭምር መዉስዳቸዉ ተረጋግጧል።

የአቡዘር መስጂድና መድረሳ ምርጫ ከሚካሄድባቸዉ መስጂዶችና የአከባቢዉ ሙስሊም የምርጫ ካርድ የወሰደበት ሲሆን ይህም ከምርጫ አካሄድ አንጻር እንቅፋት መሆኑ እሙን ነዉ።

በአቡዘር መስጂድና መድረሳ ከምዕመናኑ ሰጋጅ ውጪ 260 የመድረሳ ተማሪዎችን በቋሚነት ያስተናግድ ነበር።

በኦሮሚያ ክልል የሸገር ሲቲ መጅሊስ ፕሬዝደንት ዶር ሙሀመድ ሷልህ ከሸገር ሲቲ ከንቲባ ዶር ተሾመ ጋር በመደዋወል እንደተነጋግሩና መስጂዱ እንደማይፈርስ እንደተነገራቸዉ ለመስጂዱ ኮሚቴዎች በቃል ቢናገሩም በዛሬዉ እለት በተግባር መስጂዱ ፈርሷል።

በሸገር ሲቲ ከተማ ከዚህ ቀደም በርካታ መስጂዶች በህገ ወጥ ሽፋን በማፍረስ መሪውን(አስተዳዳሪዉን) የኀይማኖት ተቋም በመናቅና ክብር በመንፈግ እኩይ ተግባር መፈጸሙ የሚታወስ ሲሆን በዛሬው እለትም በተመሳሳይ መልኩ እንዲፍርስ ተደርጓል።

የሸገር ሲቲ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤ ፕሬዝደንት ዶር ሙሀመድ ሷልህ መስጂዱ ከሰዓት ቡኅላ መፍረሱን እንደሰሙ የገለጹልን ሲሆን የሸገር ሲቲ ከንቲባ ዶር ተሾመ መስጂዶች ከዚህ ቡኅላ አናፈርስም በማለት እንደተናገሩና ከዚህ ቀደም በፈረሱ መስጂዶች ምትክ ለመስጠት ቃል የገባነውን እየሰሩ እንደሚገኙ እንደነገሯቸዉ ገልጸዉልናል።

ከክልሉ የመንግስት የስራ ኅላፊዎች እንዳገኘነዉ መረጃ ከሆነ በወቅፍ የተሰጡ በርካታ መስጂዶችን ለማፍረስ እቅድ እንዳለ ተሰምቷል።

የሚመለከታችሁ የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ከፍተኛ የስራ ኅላፊዎች፣ የፀጥታና የፍትሕ አካላት በተደጋጋሚ ጊዜ በሸገር ሲቲ ሙስሊሞች ላይ ኀይማኖታዊ ተቋማቶቻቸዉና መድረሳዎቻቸዉ በተለያዩ ጊዜያት በተደጋጋሚ እየፈረሱ፤ መብቶቻቸዉ እየተጣሱ እንደሚገኝ የሚታወቅ ሲሆን ይህ አካሄድ ወዳልተፈለገ ግጭት የሚያመራ በመሆኑ የእኩይ ድርጊቱ ፈፃሚዎችን ለሕግ እንድታቀርቡና መሳጂዶችን በመገንባት ኅላፊነታችሁን እንድትወጡ እናሳዉቃለን።

26/07/2025

በዲናቹ ተስፋ አትቁረጡ

☀ ሁዳ መልቲሚዲያ
----------------------
በቴሌግራም
t.me/huda4eth
በፌስቡክ
fb.com/huda4eth
በዩትዩብ
https://youtube.com/?si=TnzH2hQKlhUTLvIx
በ ቲክ ቶክ

ያግኙ

ነጃሺ ኢትዮ ኢስላሚክ  ትረስት የተሰኘ በደቡብ አፍሪካ ያለ የኢትዮጵያውያን ትረስት ለፍልስጤማውያን እርዳታ አደረሰ~~~~~~~~~~~ በደቡብ አፍሪካ ነጃሺ ኢትዮ ኢስላሚክ  ትረስት አማካይነት...
26/07/2025

ነጃሺ ኢትዮ ኢስላሚክ ትረስት የተሰኘ በደቡብ አፍሪካ ያለ የኢትዮጵያውያን ትረስት ለፍልስጤማውያን እርዳታ አደረሰ
~~~~~~~~~~~

በደቡብ አፍሪካ ነጃሺ ኢትዮ ኢስላሚክ ትረስት አማካይነት ለፍልስጤማውያን የጋዛ ነዋሪዎች ይደርስ ዘንድ የተሰባሰበ ገንዘብ በትክክል ለተረጂዎች ደርሶ አስፈላጊው የምግብና ሌሎች መሰረታዊ አቅርቦቶች ለህዝቡ መድረሱን በምስልና በቪዲዮ በታገዘ ማረጋገጫ ማየት ተችሏል።

ከቦታው በተላከ የቪዲዮና የምስል ማስረጃ መሰረት ለተራቡት የጋዛ ነዋሪዎች ምግብ ሲከፋፈል ከመታየቱም በላይ የምስጋና መልዕክቶችም ተላልፈዋል።
ከነጃሺ ኢስላሚክ ትረስት በተጨማሪ እዛው በደቡብ አፍሪካ ጆሀንስበርግ የሚንቀሳቀሰው የጆሀንስበርግ የሙስሊም ሴቶች የሰደቃ ጀምዓም ከአባላቶቹ በኩል ያሰባሰበው ዕርዳታም በመጀመርያው ዙር ተልኮ ለተረጂዎች ደርሷል።

ትረስቱ ማህበረሰቡን በማነሳሳት ትልቅና አመርቂ ስራ የሰራ ሲሆን ይበልጥ የዕርዳታው መድረስ የህዝቡን ተነሳሽነት ጨምሮታል። በአንድ ዙር የተጀመረው የዕርዳታ ማሰባሰብ ወደ 4 ዕርከን ከመሸጋገሩም ሌላ የህዝቡ መነሳሳት በመጨመሩ ለሌላ ዙር ተነሳሽነት እየታየ ያለበት ሁኔታም እየተስተዋለ ነው።
"በዚህ ስራ ላይ ነጃሺ ትረስት ህዝቡን በማነሳሳት ለዚህ ትልቅና በጎ ዓላማ በማስተባበሩ አላህ ምንዳቸውን ይክፈላቸው፣የደቡብ አፍሪካ ኢትዮ ሙስሊም ላደረገውም ትብብር ትልቅ ክብር ይገበዋል።" ሲል የትረስቱ አመራር ምስጋናዉን አቅርቧል፡፡

እንደ ትረስቱ ገለጻ ይህንን ለማሳካት የነበረ ሂደት ቀላል እንዳልነበረና የተለያዩ የበጎ አድራጎት ድርጅቶችን ማግኘትና ባለው ቀጭን መስመር ለማለፍ ጊዜና ተግስት አስፈልጎ ነበር፡፡

እኛም ይህ የሚመሰገን ተግባር የፈጸሙ በደቡብ አፍሪካ የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን ለሌሎችም አርአያ እንደሚሆኑ በማመን፣ ዛሬ ንጹሃን ጋዛዊያን ሆን ተብሎ በጦር መሳርያና በርሃብ በጅምላ እንዲያልቁ ሲደረግ ተቀምጬ አላይም በሚል ዘር፣ ሃይማኖትና አህጉር ሳይለየው በተለያዩ የአለማችን ክፍል ያለው ህዝብ በነቂስ ወጥቶ የሚችለዉን ለማድረግ በሚጥርበትና እንቅልፍ ባጣበት በዚህን ሰአት ኢትዮጵያዊያኖችም ድርጊቱን ከመጥላትና ከማዉገዝ ጀምረን የምንችለዉን በማድረግ ከንጹሃን ጋዛዊያን ጎን በመቆም ሰብዓዊነትን ከፍ በማድረግ ታሪክ ልንጽፍ ይገባል እንላለን!

ምንጭ

25/07/2025

እርስ በርስ መከባበር አለብን

☀ ሁዳ መልቲሚዲያ
----------------------
በቴሌግራም
t.me/huda4eth
በፌስቡክ
fb.com/huda4eth
በዩትዩብ
https://youtube.com/?si=TnzH2hQKlhUTLvIx
በ ቲክ ቶክ

ያግኙ

"አሜሪካ ወዳ አይደለም የምትቀጠቅጣቸው" 1 ብር--------1 ብር ላይቭ ላይ የመጣችን አንዲት የጋዛ ሴት ካባረራት በኋላ "መሪ ጌታ አላቸው ወይ... እንዴት ነው ላይቭ ላይ የሚገቡት..."...
24/07/2025

"አሜሪካ ወዳ አይደለም የምትቀጠቅጣቸው" 1 ብር
--------
1 ብር ላይቭ ላይ የመጣችን አንዲት የጋዛ ሴት ካባረራት በኋላ "መሪ ጌታ አላቸው ወይ... እንዴት ነው ላይቭ ላይ የሚገቡት..." ወዘተ ካለ በኋላ ጋዛውያን ደጋግመው ላይቭ ላይ መምጣታቸው እንደሰለቸው ለመግለፅ "አሜሪካም ወዳ አይደለም የምትቀጠቅጣቸው¡" አለ።

አንተ ጠግበህ ጥጋብ አላስተኛህ ብሎ ላይቭ ቁጭ ብለህ ታድራለህ! እነሱ የሚቀምሱት ስላጡ ነው ላይቭ እየመጡ የረበሹህ!!

በህይወት እያለን ባለንበት ዘመን በተመሳሳይ ሰአት እንደኛው በህይወት ያሉ ተመሳሳይ ፕላኔት ላይ በሀገራቸው በግፍ ተገፍተው መጠጊያ ያጡና የሚልሱት የሚቀምሱት አጥተው ቀናት ሲያስቆጥሩ ትላንት በቦ*ም*ብ ተገ*ለው በሞት በተገላገሉ ወንድምና እህቶቻቸው እየቀኑ ያሉ እንደኛው አይነት ሰዎች እኛን ሰው ናችሁ ብለው ለሰው የምናዝን መስሏቸው አብሉን ሊሉን ቢመጡ እኛ "ሰዎች" ግን "ማን ነው ፈቶ የለቀቀብን?" ስንል ገፋናቸው! ረሀባቸውና እልቂታቸው ሳይሆን እነሱን በአይናችን ማየታችን ረበሸን!! ዳግም እንዳይረብሹን "ምነው ባለቁ..." ብለን ተመኘንላቸው። የተሰራባቸውን ግፍ "ለካ ልክ ነበር!" በማለት ቀደስነው!!
ሰውነት ይህ ከሆነ ሰው መሆኔን ጠላሁ! ለተበዳይ ማዘን ለተበዳይ መፍረድ ተበዳይን መርዳት ያልቻለ ሰውነት ምኑ ነው "ሰው" ያሰኘው?

እንስሳው በሬ ወንድሙን ፊቱ ብታር*ደው ደሙን ሲያይ ይበረግጋል እኮ!! እኛ ግን በሺዎች የሚቆጠሩት የፍልስጤ*ማ #ውያን ደም በፊታችን ሲፈስ እያየን ምን ያህል ነው የነዘረን?
የሰው ያህል??
አይደለም። ወላሂ አይደለም።
አዎ ካልን አሁንም እንደ "ሰው" ዋሽተናል ክደናል። ምክንያቱም ምላሻችን እና ስራችን በግልፅ ይመሰክራል!!

ሆነም ቀረ 1 ብር ሰው ለሰው ማዘኑን ካቆመ ቢከርምም እሱ በግልፅ ገለፀው እንጂ ሌላ አልሰራም!!

ለሁላችንም ልቦናችንን አላህ ይመልስልን!! ከተበዳይ ጎን መቆምን ይስጠን!! ሌላ ምንም አይባልም!!

23/07/2025

በሁሉም ለሁሉም ፤ የሁሉም አበርክትሆ የሚያስፈልግበት ወቅት ላይ እንገኛለን!

ሐምሌ 15/2017 ፡ አዲስ አበባ/ኢትዮጵያ

‎إِنَّمَا ٱلْمُؤْمِنُونَ إِخْوَةٌۭ فَأَصْلِحُوا۟ بَيْنَ أَخَوَيْكُمْ ۚ وَٱتَّقُوا۟ ٱللَّهَ لَعَلَّكُمْ تُرْحَمُونَ
ምዕመናኖች ወንድማማቾች ናቸው፡፡ በሁለት ወንድሞቻችሁም መካከል አስታርቁ፡፡ ይታዘንላችሁም ዘንድ አላህን ፍሩ፡፡(48:10)

በማህበረሰባችን የሀሳብ መድረክ ላይ ሰሞኑን የሚስተዋሉት፣ ቀዝቃዛ ቢመስሉም ከጀርባው ከፍተኛ አደጋን ያረገዙ የቃላት ፍጭቶች፣ የኢትዮጵያ ሙስሊሞች የጋራ ፎረምን በከፍተኛ ስጋት ውስጥ ከቶታል። በተለይም በብዙ መስዋዕትነት ለተቋማዊ ለውጥ በጎ አስተዋፅኦ ያበረከቱ የማህበረሰብ አንቂዎችና መሪዎች በአንድ ወገን፣ በሌላ በኩል ደግሞ የዲኑ ምሰሶ የሆኑት ዑለሞቻችን በሚገኙበት መድረክ ላይ፣ አንዱ የሌላውን ሚናና ክብር ለማሳነስ የሚደረገው ሙከራና የሚኬድበት ርቀት በእጅጉ አሳዝኖናል። ወቅቱን ያልጠበቀ አጀንዳና ተጨባጩን የሳተ እልህ፣ በጊዚያዊ ልዩነት፣ ማህበረሰቡንና ተቋሙን ዘላቂ ዋጋ እንዳያስከፍል ስጋታችን የከፋ ነው። በመሆኑም፣ የአደባባይ መካረሮችንና ትንኮሳዎችን በማቆም፣ ችግሮችን በሆደ ሰፊነትና በመከባበር በዝግ ውይይት መፍታት፣ የነገ የማይባል የዛሬ የህልውና ጉዳይ መሆኑን ፎረማችን በአፅንኦት ያሳስባል።

የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ተቋም ህልውናና የትውልድን አቅጣጫ በሚወስኑ ወሳኝ የታሪክ ምዕራፎች ላይ፣ ከውጭ ከሚሰነዘር ጥቃት በላይ አስከፊው ከውስጥ የሚነሳ የአስተሳሰብ ቀውስ ነው።

ዛሬ የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ተቋማዊ ጉዟቸውን ለማፅናት በሚታትሩበት ወቅት፣ የዑለሞችን ሚናና ክብር በሚፈታተን መልኩ የሚቀርቡ ሀሳቦች፣ የማህበረሰቡን መሰረታዊ ምሰሶ የሚያናጉ መሆናቸውን መገንዘብ ያሻል። ይህ ክርክር በተቋማዊ አሰራር ማሻሻያ ስም የሚቀርብ ቢመስልም፣ ከጀርባው የያዘው የጥበብን ዙፋን በአስተዳደር ወንበር፣ የመሪነትን ግርማ በተራ ክህሎት የመተካት አደገኛ አዝማሚያ ነው። ጉዳዩ የዑለማና የምሁር ሽኩቻ ሳይሆን የተቋማችንን ነፍስና የዲኑን አደራ የማስጠበቅ የህልውና ጥያቄ ነው።

የዚህ ሁሉ ጉዳይ ልብ ያለው ዑለሞች የነብያት ወራሾች መሆናቸው ላይ ነው። ነብያት ያወረሱን ዲርሃምና ዲናርን ሳይሆን እውቀትን ነው። ይህንን የተቀደሰ ውርስ የተሸከሙትን ዑለሞች በወረቀት መስፈርት ብቻ ማጣጣል፣ በዚህ ዘመን ነብይ ቢኖር ኖሮ "የዩኒቨርሲቲ ዲግሪ ስለሌለህ አንቀበልህም" ከማለት የማይተናነስ ከባድ ድፍረትና ታሪካዊ ስህተት ነው።

በዚህ የውይይት መድረክ ላይ ሁለት ወሳኝ ፅንሰ-ሀሳቦችን ለይቶ ማወቅም ያስፈልጋል፤ እነርሱም "የዲን አመራር" እና "አክቲቪዝም" ናቸው። የዲን አመራር (Leadership) ማለት በቁርኣንና በሐዲስ ጥልቅ እውቀት ላይ ተመስርቶ፣ ለማህበረሰቡ ዘላለማዊ መርህንና የማይለወጥ አቅጣጫን የማስቀመጥ የጥበብ ሃላፊነት ነው። አመራርነት የመርከቧን መዳረሻና መንገድ የመወሰን ስልጣን ነው። አክቲቪዝም (Activism) በበኩሉ በዚያ መንገድ ላይ ለሚገጥሙ ወቅታዊ ችግሮች የሚሰጥ ፈጣን ምላሽና የንቅናቄ ጉልበት ነው። አክቲቪዝም የመርከቧን ሞተር ማቀጣጠልና አደጋ ሲመጣ መጮህ ነው። አንዱ ያለሌላኛው ሙሉ አይደለም፤ ጉልበት ያለ አቅጣጫ ትርምስን ይፈጥራል፤ አቅጣጫ ያለ ጉልበት ደግሞ በወረቀት ላይ ከቀረ ንድፈ-ሀሳብ አይዘልም።

የሚገርመው የዘመናዊ አመራር ሳይንስ፣ የዑለማን የጥበብ አመራር የበላይነት ያረጋግጣል። የዘመኑ የአስተዳደር ጥበብ እንደሚያስተምረው፣ የአንድ ተቋም የበላይ መሪ ስኬት የሚለካው በልዩ የሙያ ዘርፉ ባለው የቴክኒክ ክህሎት ሳይሆን፣ አጠቃላይ ሁኔታውን የመተንተን፣ የረጅም ጊዜ ራዕይ የመንደፍና የተለያዩ ክፍሎችን አቀናጅቶ የማየት ፅንሰ-ሀሳባዊ ክህሎቱ (Conceptual Skill) ነው። ይህንን የዘመኑ ሳይንስ "ራዕይ" ሲለው፣ ኢስላማዊው ጥበብ ደግሞ "ሒክማ" (ጥበብ) እና "በሲራ" (የውስጥ እይታ) በማለት ከዘመናት በፊት አስቀምጦታል። ዘመናዊው አስተዳደር ስለ "አደራ" (Accountability) ሲናገር፣ ኢስላም "አማና" በማለት የመሪነትን የላቀ መለኮታዊ ተጠያቂነት ያስተምራል። ስለዚህ የዑለሞቻችን ጥበብ፣ ለዘመናዊ አመራር ባዕድ ሳይሆን የላቀ መንፈሳዊ መሰረቱ ነው።

የዚህ የተሳሳተ መከራከሪያ መሰረቱ የዑለሞችን እውቀት "ኋላ ቀር" እና "ከዘመኑ ያፈነገጠ" አድርጎ የመፈረጅ ስሁት ድምዳሜ ነው። የሌላ እምነት መንፈሳዊ መሪዎችን የትምህርት ምንጭ እያደነቁ፣ የዑለሞቻችንን እድሜ ልክ የለፉበትን እውቀትና የፒኤችዲ ማዕረግ ማጣጣል፣ ማጉደልና መታፈር ያለባቸውን ዑለማዎች የንቀትን በር በመክፈት ተሰሚነታቸውን የሚያወድም አደገኛ መንገድ ነው።

የእስልምና እውቀት ሁለንተናዊ ባህሪው ተዘንግቶ፣ የኢትዮጵያዊ ዓሊም የእውቀት መሰረት በገጠሪቷ ኢትዮጵያ ወይንም በተወሰነ ዓለም አቀፍ ጂኦግራፊያዊ ክልል የመነጨ በማስመሰልም ይቀርባል። እውነታው ግን የቁርኣን ብርሃን ፀሀይ እንጂ የመንደር ኩራዝ አይደለም፤ በሁሉም ምድር ላይ እኩል ያበራል። የዑለሞቻችን የዘመናት የትምህርት ስርዓት ራሱ ይህንን ሁለንተናዊ ጥበብ ከሚኖሩበት ዘመን ተጨባጭ ሁኔታ ጋር የማጣጣም ብቃትን በተሟላ መልኩ ያስታጥቃል። በዚህም የተነሳ ተቺዎቹ ራሳቸው የታላቁን ሊቅ ኢብኑል ጀውዚን ሶስት ምሰሶዎች (ፊቅሁ-ሸሪዓ፣ ፊቅሁል-ዋቂዕ እና ፊቅሁ-ተንዚል) እየጠቀሱ፣ ይህንን የዳበረ ስርዓት ህይወታቸውን ሙሉ የሚኖሩትን ዑለሞች "ከዘመኑ ጋር አይሄዱም" ብለው መደምደማቸው፣ በተራሳ ተቃርኖ ነው።

በየትኛውም የአለም ተጨባጭ መሪነት አስተዳደራዊ ጥበብ ነው። ለዚህ ጥሩ ምሳሌ የሀገራችንን ትልቅ ተቋም መከላከያ ሚንስቴርን በኃላፊነት ሲመሩ የነበሩትም ሆኑ አሁን የሚመሩት ሲቪሎች የወታደራዊ ሳይንስ ምሩቅ መሆን የሚል መስፈርት አልተቀመጠላቸውም። ወዲህም የሂሳብ አልያም በፊዚክስ ተመርቀው ታሪክ ከመፃፍ ያላገዳቸው ሙህራን ፣ የዑለሞችን ሁለንተናዊ (Holistic) እውቀት አስተዳደርን፣ ህግን፣ ስነ-ልቦናንና ማህበራዊ ጉዳዮችን የሚዳስስ ሆኖ ሳለ፣ "ለአስተዳደር ብቁ አይደሉም" ብሎ መፈረጅ ተገቢ ነው ብለን አናምንም።

ከላይ እንደገለፅነው በሰሞኑ የአደባባይ ሙግቶች ውስጥ ሁለት አውዳሚ ፅንፎች ሲንፀባረቁ እናያለን። በአንድ በኩል፣ አንዳንድ የዲኑ መሪዎች የምሁራንንና የአክቲቪስቶችን ገንቢ ሚና ከልክ በላይ በማሳነስ ሁሉንም በር የመዝጋት አዝማሚያ ይታይባቸዋል። በሌላ በኩል ደግሞ፣ አንዳንድ ምሁራን (አክቲቪስት) የዑለሞችን የዘመናት ጥበብና የመሪነት ሚና በመዘንጋት፣ ተቋሙን ህይወት አልባ የቢሮክራሲ ማሽን ለማድረግ ይሞክራሉ። ይህ የተቋሙን ነፍስ እንደመግደል ይቆጠራል። ስለዚህ ሁለቱም ተቃርኖዎች ለጋራ ቤታችን ስጋት መሆናቸውን ተገንዝበን፣ ዑለሞቻችንን ከፊት በማድረግ አንዱ የሌላውን ዋጋ በሚያውቅበት የመከባበርና የመደጋገፍ መካከለኛ መንገድ ላይ ልንቆም ይገባል።

በመጨረሻም ሁላችንም ልንስማማበት የሚገባው ሀቅ፣ የምንገነባው ተቋም የዑለማውም፣ የምሁሩም፣ የወጣቱም፣ የሴቷም፣ የአክቲቪስቱም፣ የሁሉም ሙስሊም የጋራ ቤት መሆኑን ነው። ይህ ቤት የሚፀናው፣ ምሰሶዎቹ የሆኑት ዑለሞች በጥበባቸው ሲከበሩ፣ ግድግዳዎቹና ጣራው የሆኑት ምሁራን በብቃታቸው ሲገነቡ፣ እንዲሁም ነዋሪዎቹ የሆኑት ህዝቡና አክቲቪስቶች ድምፃቸው ሲሰማ ነው። ይህንን የጋራ ቤት በተግባር እውን ለማድረግ የሚያስችለው መፍትሄ ያለው "ወይ ዑለማ ወይ ምሁር" የሚለውን የተሳሳተ ምርጫ በሚያፈርስ ባለሁለት እርከን የአመራር መዋቅር (Two-Tier Governance Structure) ውስጥ ነው። በዚህ ሞዴል የበላይ የዑለማዎች ምክር ቤት (Supreme Council) የተቋሙን ራዕይና መንፈሳዊ አቅጣጫ ሲያስቀምጥ፣ በዘመናዊ ክህሎት የተደራጀው የስራ አስፈጻሚ አካል (Executive Body) ደግሞ ያንን ራዕይ ወደ መሬት አውርዶ በብቃት ይተገብራል።

ስለዚህ የኛ ትውልድ ድርሻ የየራሳችንን ሚና በመናናቅ ለበላይነት መሻኮት ሳይሆን፣ ሁላችንም በዑለማ መሪነት ተከባብረን የጥበብን አመራር ከክህሎት ጉልበት ጋር በማዋሀድ ለቀጣዩ ትውልድ የማያፍሩበት ጠንካራና የተከበረ ተቋም ማስረከብ ነው። ቤት ዘግቶ በውይይት ሊፈቱ የሚገባቸውን ልዩነቶች በአደባባይ እያወጡ መጓተት ትርፉ መበታተን ነው። አላህ ልቦናችንን በማስተባበርና በመተዛዘን ላይ ያፅናልን። በተለይ በተቋሙ ሁለንተናዊ ሚናና የላቀ አበርክቶ የነበራቸው አካሎች ስኬቱንም ውድቀቱን በመጋራት በእንዲህ አይነቱ ፈታኝ ወቅት ላይ በጋራ በመቆም ጠንካራ ተቋም መመስረት የማያድር የቤት ስራ ነው። ከድህረ-ምርጫ በኋላም ተሻጋሪ ችግር እንዲኖር በሚመስል መልኩ ከየትኛውም ወገን በአደባባይ የሚሰነዝሩ አራራቂ ቃላቶች ታርመው ሁሉም በመክሊቱ በጎ አበርክቶ እንዲኖረው መስራት ኃላፊነትን መወጣት አደራንም አለማጉደል ነው።

ጥበብ ይመራል፤ ክህሎት ይከተላል!

የኢትዮጵያ ሙስሊሞች የጋራ ፎረም
ሐምሌ 12/2017: አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ

በዛሬው እለት የመጅሊስ ምርጫ አስፈጻሚ ቦርድ የሰጡት መግለጫ በ አራት ተከታታይ ሳምንት ሲከናወን የነበረው የመራጮች ምዝገባ በሁሉም ክ/ከተሞች በ119  ወረዳዎች በ324 የምርጫ ጣብያዎች የ...
22/07/2025

በዛሬው እለት የመጅሊስ ምርጫ አስፈጻሚ ቦርድ የሰጡት መግለጫ በ አራት ተከታታይ ሳምንት ሲከናወን የነበረው የመራጮች ምዝገባ በሁሉም ክ/ከተሞች በ119 ወረዳዎች በ324 የምርጫ ጣብያዎች የመራጮች ምዝገባ አንደተካሄደና ሂደቱም ፍፁም ሰላማዊ አንደነበረ ተገልጽዋል::

22/07/2025

በዲንህ ቀጥ በል!

☀ ሁዳ መልቲሚዲያ
----------------------
በቴሌግራም
t.me/huda4eth
በፌስቡክ
fb.com/huda4eth
በዩትዩብ
https://youtube.com/?si=TnzH2hQKlhUTLvIx
በ ቲክ ቶክ

ያግኙ

21/07/2025

325.8k Followers, 70 Following, 2.4m Likes - Watch awesome short videos created by Ramzin Real Estate

21/07/2025

አላህ ለመርየም ልጅ ሰጣት ወይስ ጅብሪል

☀ ሁዳ መልቲሚዲያ
----------------------
በቴሌግራም
t.me/huda4eth
በፌስቡክ
fb.com/huda4eth
በዩትዩብ
https://youtube.com/?si=TnzH2hQKlhUTLvIx
በ ቲክ ቶክ

ያግኙ

20/07/2025
20/07/2025

ህብረት ለውጤት!! ማሻአ አላህ!! ሁላችሁንም እናመሰግናለን!!

Address


Website

http://www.huda4eth.com/

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ሁዳ መልቲሚዲያ / Huda Multimedia posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to ሁዳ መልቲሚዲያ / Huda Multimedia:

Shortcuts

  • Address
  • Alerts
  • Contact The Business
  • Claim ownership or report listing
  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share