Harun media ሃሩን ሚዲያ

Harun media ሃሩን ሚዲያ ዓላማችን በሙስሊሙ ማህበረሰብ ዘንድ የመረጃ ክፍተት እንዳይኖር መትጋት ነው።

26/10/2025

"ለኡማው አይናችን የሆነን ተቋም ማጠናከር የሁላችንም ሀላፊነት ነው።" የበድር ኢትዮጵያ አመራሮች

በበለጠ አቅምና ተደራሽነት ለመከወን የታቀደ ብሩህ ወደፊት.. ኖቬምበር 15 በDMV የማይቀርበት መሰናዶ!

© ሀሩን ሚዲያ

ሙስሊሙ ማህበረሰብ ለቱሉ ድምቱ የሙስሊም መካነ መቃብር አጥር ግንባታ የበኩሉን እንዲያበረክት ጥሪ ቀረበ!- ሀሩን ሚዲያ፥ ጥቅምት 16/2018በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ምክር...
26/10/2025

ሙስሊሙ ማህበረሰብ ለቱሉ ድምቱ የሙስሊም መካነ መቃብር አጥር ግንባታ የበኩሉን እንዲያበረክት ጥሪ ቀረበ!

- ሀሩን ሚዲያ፥ ጥቅምት 16/2018

በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት አዘጋጅነት በዛሬው ዕለት የቱሉ ድምቱ የሙስሊም መካነ መቃብር የማፅዳት ስራ ተከናውኗል።

በመርኅ ግብሩ ላይ የአዲስአበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ከፍተኛ አመራሮች፤ የአቃቂ ቃሊቲ የመጅሊስ አመራሮች፤ የክፍለ ከተማው የመንግስት የስራ ሀላፊዎች እና በርካታ የአከባቢው ሙስሊም ማህበረሰብ ተሳታፊ ሆነዋል።

በመድረኩ የተገኙት የአዲስአበባ መጅሊስ ፕረዚዳንት ሸይኽ ሱልጣን ሐጅ አማን አዲስአበባ መጅሊስ ባለው አቅም የማህበረሰቡን ጥያቄ ለመመለስ እንደሚሰራ ገልፀዋል። በመርኅ ግብሩ የተገኙ የአዲስአበባ እና የቃሊቲ ክፍለ ከተማ መጅሊስ አመራሮች መልዕክቶችን አስተላልፈዋል።

የቱሉ ድምቱ የሙስሊም መካነ መቃብር አጠቃላይ የአጥር ስፋቱ 1300 ሜትር መሆኑ የተገለፀ ሲሆን ሙሉ አጥሩን ለማጠር 25 ሚሊየን ብር ይፈጃል ተብሏል። ከዚህ ውስጥ የአካባቢው ማህበረሰብ ባደረገው እርብርብ አራት ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ 200 ሜትር አጥር መታጠሩ ተገልጿል።

ቀሪውን 1100 ሜትር አጥር ህዝበ ሙስሊም በጋራ በመተባበር እንዲያሳጥር እና መቃብር እንድከበረ የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ መጅሊስ ጥሪ አቅርቧል።

ቱሉ ድምቱ የሙስሊሙ መካነ መቃብር ረጅሙ ዘመን ያስቆጠረና ለአቃቂ ቃሊቲ፣ ለቦሌ እና ኮዬ ፈጨ ክፍለ ከተማን ጨምሮ ለበርካታ የአካባቢው ነዋሪዎች አገልግሎት እንደሚሰጥ ተገልጿል።

© ሀሩን ሚዲያ

በስልጤ ዞን የሚገኘው አስ ሰላም መርከዝ ለ2ኛ ዙር ያስተማራቸውን የቁርኣን ሃፊዞችን በድምቀት አስመረቀ!- ሀሩን ሚዲያ ደቡብ ስቱዲዮ፥ ጥቅምት 16/2018በስልጤ ዞን ሳንኩራ ዓለም ገበያ ከ...
26/10/2025

በስልጤ ዞን የሚገኘው አስ ሰላም መርከዝ ለ2ኛ ዙር ያስተማራቸውን የቁርኣን ሃፊዞችን በድምቀት አስመረቀ!

- ሀሩን ሚዲያ ደቡብ ስቱዲዮ፥ ጥቅምት 16/2018

በስልጤ ዞን ሳንኩራ ዓለም ገበያ ከተማ መርከዝ አስ-ሰላም የቁርአን ሂፍዝ ማዕከል ለ2ኛ ዙር ያስተማረቸው የቁርኣን ሃፊዞችን በድምቀት አስመርቋል፡፡

በዘንድሮ በአዳሪ 44 እና በተመላላሽ 8 በድምሩ 52 ተማሪዎችን በሂፍዝ በተለያዩ አጫጭር ኪታቦችን በማስቀራት በዛሬው ዕለት ማስመረቁም ነው የተገለፀው።

ተማሪዎቹ ከሀገሪቱ ከተለያዩ ቦታቸው የመጡ መሆናቸውንና ወደ ትውልድ ቀያቸው በመመለስም የአካባቢው ማህበረሰብ የተማሩትን ቁርኣን እንደሚያስቀሩ የመርከዙ ስራ አስኪያጅ ሸይኽ ሸምሱ ሃጂ ጀማል ለሀሩን ሚዲያ ተናግረዋል።

በዕለቱ በተማሪዎች ቁርዓን ፣መነባነብ ኹጥባ፣ ደዕዋ የቀረበ ሲሆን ቁርዓንን በሂፍዝ ተምረው የጨረሱና ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎችም ሽልማትና ሰርተፊኬት ተበርክቶላቸዋል።

በመጨረሻም መድረሳውን ለማጠናቀር የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ-ግብር ተካሂዷል።

በመርኅ ግብሩ ላይ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መጅሊስ ፕሬዝደንት እና የመርከዙ ጠቅላላ ጉበኤ ዋና ሰብሳቢ አማም ሃጂ አብዱልሃዲ አህመድ፣ሸይኽ ሳዲቅ ወጌቦ የክልሉ የሐጅና ዑምራ፤የህዝብ ግንኙነት እና ሚድያ ዘርፍ ኃላፊ፣ሸይኽ ሙስጠፋ ጀማል የማዕከላዊ ኢትዮጲያ ክልል እ/ጉ/ም/ቤት ስራ አስፈጻሚ ፣የስልጤ ዞን መጅሊስ ዋና ሰብሳቢ ሸይኽ አብድረሂም አህመዲን የመርከዙ የበላይ ጠባቂ ሸይኽ ኡስታዝ ሃጂ ኸድር ሃጂ ሳሊያ ፣የሳንኩራ ወረዳ መጅሊስ ዋና ሰብሳቢ እና የመርከዙ የቦርድ ዋና ሰብሳቢ ሃጂ ያሲን ሃጂ ሁሴን፣የወረዳው መጅሊስ ምክትል ሰብሳቢ ሸይኽ አጣር ሼኽ ሱሌ የአለም ገበያ ከተማ አስተዳደር መጅሊስ ዋና ሰብሳቢ፣ሸይኽ ሃጂ ከድር ኪያር፣የሳንኩራ ወርዳ ወ/ሮ ተሚማ ሙዴ ፣ የአለምገበያ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ረሻድ ሀሰን እና ሌሎችም ከተለያዩ የፌደራል እና የክልል የክብር እንግዶች ተገኝተዋል።

© ሀሩን ሚዲያ

የማንንም መብት ሳንነካ ቀና ብለን ለመሄድ መስራት አለብን...ኡስታዝ ኑሩ ቱርኪ||HarunMedia||
26/10/2025

የማንንም መብት ሳንነካ ቀና ብለን ለመሄድ መስራት አለብን...ኡስታዝ ኑሩ ቱርኪ||HarunMedia||

HARUN MEDIA የሙስሊሙ ዑማ ቀዳሚ ድምጽ !

25/10/2025

Al-Amin Ethiopian muslim community Huston Texsas Fundraising

25/10/2025

በበለጠ አቅምና ተደራሽነት ለመከወን የታቀደ ብሩህ ወደፊት.. ኖቬምበር 15 በDMV የማይቀርበት መሰናዶ!

አንድ ኡማ፣ አንድ ግብ

© ሀሩን ሚዲያ

ቂርቆስ ክፍለ ከተማ መጅሊስ በቀጣይ ትላልቅ ፕሮጀክቶችን በመስራት ለሌሎች ክፍለ ከተማዎች አርአያ መሆን ይኖርበታል ሲሉ አቶ ሙሐመድ ካሳ ተናገሩ!- ሀሩን ሚዲያ፥ ጥቅምት 15/2018 በአዲስ...
25/10/2025

ቂርቆስ ክፍለ ከተማ መጅሊስ በቀጣይ ትላልቅ ፕሮጀክቶችን በመስራት ለሌሎች ክፍለ ከተማዎች አርአያ መሆን ይኖርበታል ሲሉ አቶ ሙሐመድ ካሳ ተናገሩ!

- ሀሩን ሚዲያ፥ ጥቅምት 15/2018

በአዲስ አበባ የቂርቆስ ክፍለ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት የትውውቅ እና የምስጋና መርኅ ግብር በዛሬው ዕለት በተወፊቅ(ፍልውሃ) መስጅድ አካሂዷል፡፡

የእለቱን መርኅግብር በንግግር የከፈቱት የቂርቆስ ክፍለ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ዋና ስራ አስፈፃሚ ሸህ ሙሀመድ ሙስጠፋ ናቸው::

ለዛሬው ቀን እንድንበቃ የተለያዩ ሰዎች ታላቅ አስተዋጽኦ አድርገዋል ያሉ ሲሆን በተለየ መልኩ ደግሞ መጅሊሱ እንዲጠናከርና ኢስላማዊ ባንክ እንዲኖረን ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጅ ዑመር ኢድሪስ ያደረጉት አበርክቶ ሁሌም የሚታወስ ነው ብለዋል::

የ2017 የመጅሊስ ምርጫ እንዲካሄድ ትልቁን ሚና የተወጡት የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሸይኽ ሀጂ ኢብራሂም ቱፋን አመስግነዋል::

አክለውም በቀጣዩ የሀላፊነታችን ዘመን ለሙስሊሙ ተጠቃሚነት ከመንግስት መዋቅሮች ጋር በጋራ የምንሰራበት እድልን ማስፋት አለብን ሲሉ ተናግረዋል፡፡

የቂርቆስ ክፍለ ከተማ የ2017 ምርጫ አስፈፃሚ ዋና ሰብሳቢ አሊ ሙሀመድ የተሻለ የምርጫ ሂደት ተካሂዶ ወደ ሀላፊነት የመጣችሁ ሙስሊሞች ከልዩነት እና ከወገንተኝነት ነፃ ሆናችሁ ሙስሊሙን እንድታገለግሉ ሲል መልእክቱን አስተላልፏል::

በእለቱ ከምርጫው ጋር በተያያዘ አስተዋጽኦ ላደረጉ አካላት ከአዲስ አበባ የ2017 የመጅሊስ ምርጫ አስፈፃሚ የቦርድ አባል ከሙሐመድ ካሳ እጅ እውቅና ተበርክቶላቸዋል::

ወንድም ሙሐመድ ካሳ በእለቱ መልእክቱን ሲያስተላልፍ እኛ በተሰጠን ሀላፊነት የማሻገሩን ስራ ሰርተን እዚ ደርሰናል ቀጣዩ ሙስሊሙን ማገልገል የተመራጮቹ ሀላፊነት ነው ብለዋል::

ቂርቆስ ክፍለ ከተማ በቀጣይ ትልልቅ ፕሮጀክቶችን በመስራት ለሌሎች ክፍለ ከተማዎች አርአያ መሆን ይኖርበታል ሲሉ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል::

የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ቀጣይ የስራ እንቅስቃሴ እና የትኩረት አቅጣጫን በተመለከተ በክፍለ ከተማው መጅሊስ ዋና ፀሀፊ ኢንጂነር ኢስሀቅ አብዱልአዚዝ ገለፃ ተደርጓል::

ኢንጂነር ኢስሀቅ በገለፃቸው ከከፍተኛ ምክር ቤቱ በሚሰጠን አቅጣጫ መሰረት በክፍለ ከተማችን ውስጥ ውጤታማ ተግባራትን ለመስራት የተቋም ልህቀትን ማሳደግ አስፈላጊ ነው ብለዋል::

የአዲስ አበባ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ዋና ስራ አስኪያጅ ሀጅ ሪያድ ጀማል፤በትውልድ የቅብብሎሽ ትግል በመጣ ውጤት ለዚህ መብቃታችን አስደሳች ነው ብለዋል::

ቂርቆስ ክፍለ ከተማ ሁለቱን ታላላቅ ኢዶች የሚከናወኑበት እንዲሁም የታላላቅ አሊሞች እና መሳጂዶች መገኛ እና የከተማዋ እምብርት ላይ እንደመገኘታችሁ የበለጠ ሀላፊነት ስለሚኖርባችሁ በዛ ልክ እንድትዘጋጁ ሲሉ አሳስበዋል::

መርኅግብሩ ያለፉትን ሶስት አመታት የክፍለ ከተማውን መጅሊስ ያገለገሉ አመራሮችን እንዲሁም የምርጫ ሂደት ላስተባበሩ አካላት እውቅና በመስጠት ፍፃሜውን አግኝቷል::

© ሀሩን ሚዲያ

ቡራዩ ለሚገኘው ሰልሀዲን መስጅድ የአንድ ሚሊዮን ብር ድጋፍ ተደረገ!- ሀሩን ሚዲያ፥ ጥቅምት 15/2018በቡራዩ ክፍለ ከተማ በግንባታ ላይ ለሚገኘው ሰልሀዲን መስጅድ በዛሬው ዕለት የአንድ ሚ...
25/10/2025

ቡራዩ ለሚገኘው ሰልሀዲን መስጅድ የአንድ ሚሊዮን ብር ድጋፍ ተደረገ!

- ሀሩን ሚዲያ፥ ጥቅምት 15/2018

በቡራዩ ክፍለ ከተማ በግንባታ ላይ ለሚገኘው ሰልሀዲን መስጅድ በዛሬው ዕለት የአንድ ሚሊዮን ብር ድጋፍ ተደርጓል።

ድጋፉን ያደረጉት በዴልታ ትራቭል መስከረም 25 ኡምራ ያደረጉ ጀምዓዎች ሰደቀተል ጃሪያ ይሆን ዘንድ ማበርከታቸው ነው የተገለጸው።

የርክክብ መርኃ ግብሩ በዛሬው ዕለት ቡራዩ በሚገኘው ሰልሀዲን መስጅድ የተካሄደ ሲሆን በመርኅ ግብሩ ላይ የቡራዩ መጅሊስ አመራሮች፣ የደልታ ትራቭል መስራች እና ስራአስኪያጅ፣ የደልታ ትራቭል መስከረም 25 የኡምራ ጀምዓ ተወካይ፣ የሰልሀዲን መስጅድ የግንባታ አስተባባሪ ኮሚቴ እና ጀምዓዎች ተገኝተዋል።

የደልታ ትራቭል መስከረም 25 የኡምራ ጀምዓ መሪ የነበሩት ሼይኽ ኑረላኽ ሐሚድን በዝግጅቱ ላይ ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት እንዲህ አይነት በጎ ተግባራት የሚበረታታ እና በአላህም የሚወደድ ነው ያሉ ሲሆን ለመሰል ተቋማት አርያ ነው ብለዋል።

የደልታ ትራቭል ባለቤት እና ስራ አስኪያጅ ወንድም ዩኑስ አብዱ በበኩሉ በእንዲህ አይነት ኸይር ስራ ላይ ተሳታፊ በመሆናቸው መደሰታቸውን ገልፆ ወደፊትም ይህንኑ ተግባር አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አስታውቋል።

የሰልሀዲን መስጅድ የግንባታ አስተባባሪ ኮሚቴ ወንድም ሙባረክ አደም በበኩሉ ሰልሀዲን መስጅድ ከግንባታው ጅማሬ አንስቶ የብዙ ሙስሊሞች ተሳትፎ እንደነበር ገልፆ የደልታ ትራቭል መስከረም 25 የኡምራ ጀምዓ ያደረገው ድጋፍ ብዙ ስራዎችን ለመስራት በአስፈላጊው ጊዜ የተገኘ ድጋፍ ነው ብሏል።

ሰልሀዲን መስጅድ ግንባታ በአሁኑ ሰአት በጥሩ ሁኔታ እየተከናወነ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን የቀረው ወሳኝ ምዕራፍ ማለትም የፊንሽንግ ስራ ላይ ሁሉም ሙስሊም ማህበረሰብ በመረባረብ እንዲያግዝ ጥሪ ቀርቧል።

ሰልሀዲን መስጅድ አሁን ባለው መድረሳ ከ890 በላይ መደበኛ ተማሪዎች እንዲሁም በርካታ እናቶችን እያስተማረ እንደሚገኝ ተገልጿል።

© ሀሩን ሚዲያ

📌 የፕሮግራም ጥቆማ በስልጤ ዞን ሳንኩራ ዓለም ገበያ ከተማ በመርከዝ አስ-ሰላም የቁርኣን ሂፍዝ ማዕከል 2ኛ ዙር ታላቅ የምረቃ እና የመዝጊያ ፕሮግራም የፊታችን እሁድ ጥቅምት 16 ይካሄዳል!...
24/10/2025

📌 የፕሮግራም ጥቆማ

በስልጤ ዞን ሳንኩራ ዓለም ገበያ ከተማ በመርከዝ አስ-ሰላም የቁርኣን ሂፍዝ ማዕከል 2ኛ ዙር ታላቅ የምረቃ እና የመዝጊያ ፕሮግራም የፊታችን እሁድ ጥቅምት 16 ይካሄዳል!

በዕለቱ በተማሪዎች ቁርዓን፣ ነድዋ ፣መነባነብ ኹጥባ፣ ደዕዋ ቁርዓንን በሂፍዝ ተምረው የጨረሱ ድንቅ ተማሪዎች ሽልማት፣ በተለያዩ ኡስታዞች የነሲሃ/የደዕዋ ፕሮግራሞች እና ሌሎችም ይቀርባሉ።

በእለቱ የሚገኙ የክብር እንግዶች፣
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ መጅሊስ ፕሬዝደንት እና የመርከዙ ጠቅላላ ጉበኤ ዋና ሰብሳቢ አማም ሐጂ አብዱልሃዲ አህመድ፣ የስልጤ ዞን መጅሊስ ዋና ሰብሳቢ ሸይኽ አብድረሂም አህመዲን፣ የመርከዙ የበላይ ጠባቂ ሼይኽ ኡስታዝ ሃጂ ኸድር ሃጂ ሳሊያ፣ የሳንኩራ ወረዳ መጅሊስ ዋና ሰብሳቢ እና የመርከዙ የቦርድ ዋና ሰብሳቢ ሃጂ ያሲን ሃጂ ሁሴን የወረዳው መጅሊስ ምክትል ሰብሳቢ ሼኽ አጣር ሼኽ ሱሌ የአለም ገበያ ከተማ አስተዳደር መጅሊስ ዋና ሰብሳቢ ሸይኽ ሃጂ ከድር ኪያር እና ሌሎችም ከተለያዩ የፌደራል እና የክልል የክብር እንግዶች እንደሚታደሙም ተገልጿል፡፡

© ሀሩን ሚዲያ (ደቡብ ስቱዲዮ)

"ከሀርፍ እስከ ጀዘሪ"የዋህደቱ ኒሳዕ ጣፋጭ አንደበቶች||HarunMedia||https://youtu.be/AKSlq8F1254
24/10/2025

"ከሀርፍ እስከ ጀዘሪ"የዋህደቱ ኒሳዕ ጣፋጭ አንደበቶች||HarunMedia||
https://youtu.be/AKSlq8F1254

በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኘው የተውፊቅ(ፍልውሃ) መስጂድ ግንባታ ሊጀመር መሆኑ ተገለፀ!- ሀሩን ሚዲያ፥ ጥቅምት 14/2018 በአዲስ አበባ ከተማ በቂርቆስ ክ/ከተማ ወረዳ 07 የሚገኘው ተውፊ...
24/10/2025

በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኘው የተውፊቅ(ፍልውሃ) መስጂድ ግንባታ ሊጀመር መሆኑ ተገለፀ!

- ሀሩን ሚዲያ፥ ጥቅምት 14/2018

በአዲስ አበባ ከተማ በቂርቆስ ክ/ከተማ ወረዳ 07 የሚገኘው ተውፊቅ መስጂድ ዙሪያውን በብሎኬት ተገንብቶ አገልግሎት ሲስጥ የቆየ ሲሆን፤ መስጅዱን በአዲስ መልኩ ለመገንባት ስምምነት መደረጉ ተገልጿል።

መስጂዱን በተሻለ መልኩ ለመገንባት የአዲሰ አበባ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት እና የሚድሮክ ኢንቬስትመንት ግሩፕ ከዚህ ቀደም ስምምነት ማድረጋቸው ተገልጿል።

በ1978 ዓ.ል የተመሠረተውና በቂርቆስ ክ/ከተማ ወረዳ 07 የሚገኘው ተውፊቅ መስጂድ ዙሪያውን በብሎኬት ተገንብቶ አገልግሎት ሲስጥ የቆየ ሲሆን ውብ፣ የሙስሊሙን እሴት የሚናገር፤ ሁለንተናዊ አገልግሎት የሚሰጥ መስጂድ ለመገንባት ከመጪው ሰኞ ጀምሮ የተለዋጭ መስገጃ ሰፍራ ግንባታ ይጀመራል ተብሏል።

አዲስ፣ ደረጃውን የጠበቀና የተለያዩ አገልግሎቶች የተሟሉለት ታላቅ መስጂድ በሚድሮክ ኢንቬስትመንት ግሩፕ ሙሉ ወጪ እንደሚገነባ ታውቋል።

ዛሬ ግንባታውን ለማስጀመር የአ/ አ/ከ/እ/ጉ/ከ/ም/ቤት ፕሬዝደንት ሼይኽ ሱልጣን አማን ኤባ፣ ም/ፕሬዝደንቱ ሼህ ሙሐመድ ሸሪፍ፣ ዋና ፀሀፊው ኡስታዝ ሺሐቡዲን ሼህ ኑራ፤ የኢስላማዊ ተቋማት ዘርፍ ተጠሪና የስራ አስፈጻሚ አባል ኡስታዝ አዩብ ደርባቸውና ሌሎች የምክር ቤቱ ሥራ አስፈፃሚ አባላት የተገኙ ሲሆን ከሚድሮክ ኢንቬስትመንት ግሩፕ አቶ ጀማል አህመድን ጨምሮ የተለያዩ ሀላፊዎች ተገኝተዋል።

የአዲስ አበባ መጅሊስ ፕሬዝደንት ሼይህ ሱልጣን አማን ኤባ ኢትዮጵያዊው ባለሀብት ሼህ ሙሐመድ ሁሴን ዓሊ አላሙዲን በኢትዮጵያ ለሚያከናውኗቸው ሁለንተናዊና የላቁ የልማትና የማሕበራዊ መልካም ስራዎች ምስጋናቸውን ማቅረባቸውን የከፍተኛ ምክር ቤቱ ህዝብ ግንኙነት ዘገባ ያመላክታል።

© ሀሩን ሚዲያ

📌 የዳዕዋ ፕሮግራም ጥቆማ ''በድንገት ትለያለክ!' በሚል ርዕስ በኡስታዝ ካሚል ጣሀ  የዳዕዋ ፕሮግራም ይኖራል 📅 ነገ ጥቅምት 15 -  02 -2018⏰ ከዙሁር ሶላት ቡሀላ 🕌 በመርካቶ ባዩ...
24/10/2025

📌 የዳዕዋ ፕሮግራም ጥቆማ
''በድንገት ትለያለክ!' በሚል ርዕስ
በኡስታዝ ካሚል ጣሀ የዳዕዋ ፕሮግራም ይኖራል
📅 ነገ ጥቅምት 15 - 02 -2018
⏰ ከዙሁር ሶላት ቡሀላ
🕌 በመርካቶ ባዩሽ መስጂድ
ተሰናድቷል፣ ሁላችሁም ተጋብዛቹሀል።
አዘጋጅ፦ የባዩሽ መስጅድ ጀመዓ
የሚዲያ አጋር ሀሩን ሚዲያ

© ሀሩን ሚዲያ

Address

Https://maps. App. Goo. Gl/ZN47MPhnMDPQd422A
Addis Ababa
1000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Harun media ሃሩን ሚዲያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Harun media ሃሩን ሚዲያ:

Share

ሃሩንቲዩብ

ሀሩንቲዩብ የተለያዩ አስተማሪ የሆኑ የዳእዋ ልዩ ልዩ ዝግጅቶችን ለእናንተ ያደረሳል