Harun media ሃሩን ሚዲያ

Harun media ሃሩን ሚዲያ ዓላማችን በሙስሊሙ ማህበረሰብ ዘንድ የመረጃ ክፍተት እንዳይኖር መትጋት ነው።

በሀዲያ ዞን ሌሙ ወረዳ ለአምስት ቀበሌዎች አገልግሎት የሚሰጡ የንፁህ ውሃ ቦኖዎች ተመረቁ!- ሀሩን ሚዲያ፥ ሐምሌ 20/2017በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሀዲያ ዞን ሌሞ ወረዳ በሌሳ ቀበሌ ለ...
27/07/2025

በሀዲያ ዞን ሌሙ ወረዳ ለአምስት ቀበሌዎች አገልግሎት የሚሰጡ የንፁህ ውሃ ቦኖዎች ተመረቁ!

- ሀሩን ሚዲያ፥ ሐምሌ 20/2017

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሀዲያ ዞን ሌሞ ወረዳ በሌሳ ቀበሌ ለአምስት ቀበሌዎች አገልግሎት የሚሰጡ የንፁህ መጠጥ ውሃ ቦኖዎች በዛሬው ዕለት ተመርቀዋል።

የንፁህ መጠጥ የውሃ ቦኖዎቹ የተገነቡት በኡስታዝ አባድር አማካኝነት ስሟ እንዳይጠቀስ በፈለገች እህት፣ በወንድም አንዋር እና በሌሎችም ወገኖች በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ እንዲሁም በአካባቢው ማህበረሰብ ትብብር መሆኑ ተገልጿል።

በዛሬው ዕለት የተመረቁት የንፁህ ውሃ ቦኖዎቹ ከአምስት መቶ ስልሳ ሺህ ብር በላይ በሆነ የገንዘብ ወጭ እና በማህበረሰቡ የጉልበት ድጋፍ የተገነቡት ሶስት የንፁህ ውሃ ቦኖዎች እና አንድ 20 ሺህ ሊትር ውሃ መያዝ የሚችል ታንከር ሲሆን በአጠቃላይ ለሶስት ቀበሌ ማህበረሰብ ተጠቃሚ ያደርጋሉ ተብሏል።

በመርኅ ግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት የሰሜን በሌሳ ቀበሌ ሊቀመንበር አቶ ጌታቸው ሽኩር "የተሰራው ስራ ታሪካዊ ስራ ነው ያሉ ሲሆን የአካባቢው ማህበረሰብ ከዚህ ቀደም ውሃ ፍለጋ በሌሊት አውሬ ጋር እየተጋፈጠ ብዙ መስዕዋትነት ይከፍል ነበር አሁን ግን ያን እንግልት ማስቀረት መቻል ትልቅ ነገር ነው ብለዋል።

የቀበሌው አስተዳዳሪ አቶ ዳንኤል አቢቦ በበኩላቸው ይህን አይነት ለማህበረሰቡ እፎይታ የሚሰጡ ስራዎች ለሀገርም ለወገን ያለው ጥቅም የጎላ ነው ብለዋል። በርካታ የአካባቢው ነዋሪዎችም የውሃ ቦኖዎቹ በመገንባታቸው ደስታቸውን ገልፀዋል።

በመርኅ ግብሩ ላይ የውሃ ቦኖዎቹ ግንባታ እንዲሳካ አስተዋጽኦ ያደረጉት ዑስታዝ አባድር፣ ኡስታዝ ሸምሰዲን፣ ኡስታዝ ረሻድን ጨምሮ በርካታ የአካባቢው ማህበረሰብ ተገኝቷል። በዝግጅቱ ማጠቃለያ የውሃ ቦኖዎቹ ግንባታ እንዲሳካ አስተዋጽኦ ላደረጉ አካላት ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።

© ሀሩን ሚዲያ

ወደ ጋዛ የእርዳታ መኪኖች መግባት መጀመራቸው ተገለጸ።- ሀሩን ሚዲያ፥ ሀምሌ20/2017የሰብዓዊ እርዳታ ቁሳቁሶችን የያዙ መኪኖች ከግብፅ ወደ ጋዛ ጉዞ መጀመራቸው ተገልጿል።በዛሬው ዕለት ጉዞ...
27/07/2025

ወደ ጋዛ የእርዳታ መኪኖች መግባት መጀመራቸው ተገለጸ።

- ሀሩን ሚዲያ፥ ሀምሌ20/2017

የሰብዓዊ እርዳታ ቁሳቁሶችን የያዙ መኪኖች ከግብፅ ወደ ጋዛ ጉዞ መጀመራቸው ተገልጿል።

በዛሬው ዕለት ጉዞ የጀመሩት መኪኖች 100 ሲሆኑ የሰብዓዊ ድጋፍ አቅርቦቶችንና 840 ቶን ዱቄትና ሌሎችንም የምግብ ፓኬጆች ማካተታቸው ተገልጿል።

© ሀሩን ሚዲያ

ካሊድ ኢብኑ ወሊድ መርከዝ የቁርኣን ሃፊዞችን አስመረቀ!- ሀሩን ሚዲያ፥ ሐምሌ 19/2017በኦሮሚያ ክልል ባሌ ሮቤ የሚገኘው ካሊድ ኢብኑ ወሊድ መርከዝ በቁርኣን ሂፍዝ ያስተማራቸውን 40 ተማ...
26/07/2025

ካሊድ ኢብኑ ወሊድ መርከዝ የቁርኣን ሃፊዞችን አስመረቀ!

- ሀሩን ሚዲያ፥ ሐምሌ 19/2017

በኦሮሚያ ክልል ባሌ ሮቤ የሚገኘው ካሊድ ኢብኑ ወሊድ መርከዝ በቁርኣን ሂፍዝ ያስተማራቸውን 40 ተማሪዎች በድምቀት ማስመረቁ ተገልጿል።

ኻሊድ ኢብኑ ወሊድ መርከዝ የቁርኣን ሂፍዝ ተማሪዎችን ያስመረቀው ለ4ተኛ ዙር መሆኑ የተገለፀ ሲሆን በምርቃ መርኅግብሩ ላይም ኡለማዎች፣ ኡስታዞች፣ እንዲሁም የኦሮሚያ መጅሊስ አመራሮች መገኘታቸው ታውቋል።

© ሀሩን ሚዲያ

በደሴ ከተማ ቦሩ ሜዳ የሚገኝ መስጅድ አጥር በፀጥታ ሀይሎች መፍረሱ ተገለፀ!-ሀሩን ሚዲያ፣ ሐምሌ 19/2017በደቡብ ወሎ ዞን ደሴ ከተማ መናፈሻ ክፍለ ከተማ ቦሩ ሜዳ የሚገኝ መስጅድ ዛሬ ማ...
26/07/2025

በደሴ ከተማ ቦሩ ሜዳ የሚገኝ መስጅድ አጥር በፀጥታ ሀይሎች መፍረሱ ተገለፀ!

-ሀሩን ሚዲያ፣ ሐምሌ 19/2017

በደቡብ ወሎ ዞን ደሴ ከተማ መናፈሻ ክፍለ ከተማ ቦሩ ሜዳ የሚገኝ መስጅድ ዛሬ ማለዳ ከፈጅር ሰላት በኋላ በፀጥታ ሀይሎች መፍረሱን ከስፍራው ለሀሩን ሚዲያ የደረሰን መረጃ ያመላክታል።

መስጅዱ ክረምት በመግባቱ ምክንያት ወደ መስጅድ የሚያስገባውን መተላለፊያ መንገድ ላይ ማስተካከያ በማድረግ አጥሩን በቅርቡ እድሳት ያከናወነ መሆኑን የገለፁት የመስጅዱ አስተዳዳሪዎች ነገር ግን ከፍለ ከተማው አመራሮች ያለፍቃድ አጥራችኋል በሚል የተለያዩ ማስፈራሪያ ሲደርስባቸው እንደነበር ገልጸዋል።

በጉዳዩ ዙሪያ የቀበሌው አመራሮች ከአካባቢው ሙስሊም ማህበረሰብ ውይይት ለማድረግ ባሳለፍነው ረቡዕ ቀጠሮ ይዘው የነበረ ቢሆንም አመራሮች አስቸኳይ ስብሰባ ገጥሟቸዋል በሚል ለነገ እሁድ ተለዋጭ ቀጠሮ ይዘው እንደነበር ተገልጿል።

ይሁንና ዛሬ ማለዳ የሱቢኺ ሰላት ከተሰገደ በኋላ በአምስት ፓትሮል ተጨነው በመጡ የፀጥታ ሀይሎች የመስጅዱ አጥር ሙሉ በሙሉ ማፍረሳቸው ተነገሯል። ከዚህ በተጨማሪም የመስጅዱን ኢማም እና በሰአቱ ቁርአን እየቀሩ የነበሩ ልጆችን አስከ ቀኑ አምስት ሰአት አስረው መልቀቃቸው ተገልጿል።

በጉዳዩ ዙሪያ ሀሩን ሚዲያ የደሴ ከተማ እስልምና ጉዳዮችን የጠየቀ ሲሆን መጅሊሱ ከመናፈሻ ክፍለ ከተማ አመራሮች ጋር ውይይት ማድረጉን ገልፆ ችግሩን ተወያይቶ እንደሚፈታ ምላሽ መስጠቱን አስታውቀዋል። በጉዳዩ ዙሪያ በመጭው ሰኞ የቦሩ ሜዳ አካባቢ ሙስሊሞች ጋር ውይይት ለማድረግ ቀጠሮ መያዛቸው ተገልጿል።

ቦሩ ሜዳ የሚገኘው መስጅደል አንዋር ከ15 አመት በላይ ለአካባቢው ሙስሊም ማህበረሰብ አገልግሎት ሲሰጥ እንደነበር ተመላክቷል።

© ሀሩን ሚዲያ

ቁርኣንን የሃፈዙ 450 ተማሪዎች ተመረቁ!- ሀሩን ሚዲያ፥ ሐምሌ 19/2017በሱማሌ ክልል በጅግጅጋ ከተማ የሚገኘው ኢማሙ ሻድቢ መርከዝ በቁርኣን ሂፍዝ እና በአርብኛ ቋንቋ ያስተማራቸውን 45...
26/07/2025

ቁርኣንን የሃፈዙ 450 ተማሪዎች ተመረቁ!

- ሀሩን ሚዲያ፥ ሐምሌ 19/2017

በሱማሌ ክልል በጅግጅጋ ከተማ የሚገኘው ኢማሙ ሻድቢ መርከዝ በቁርኣን ሂፍዝ እና በአርብኛ ቋንቋ ያስተማራቸውን 450 ተማሪዎችን በዛሬው ዕለት በድምቀት ማስመረቁ ተገልጿል።

ኢማሙ ሻድቢ መርከዝ ተማሪዎችን ያስመረቀው ለ10 ዙር መሆኑ የተገለፀ ሲሆን በዝግጅቱ ላይ ኡለማዎች፣ ኡስታዞች፣ ጥሪ የተደረገቸው እንግዶች፣ በርካታ የጅግጅጋ ከተማ ነዋሪዎች መገኘታቸውን የዘገበው ሀኑን ቲቪ ነው።

© ሀሩን ሚዲያ

የኦሮሚያ መጅሊስ ለገዛው የዋና መስሪያ ቤት ህንፃ ቀሪ ክፍያ የሚውል የገቢ ማሰባሰቢያ መረሃ ግብር በነገው ዕለት እንደሚያካሂድ ገለፀ! - ሀሩን ሚዲያ፥ ሐምሌ 17/2017የኦሮሚያ ክልል እስ...
24/07/2025

የኦሮሚያ መጅሊስ ለገዛው የዋና መስሪያ ቤት ህንፃ ቀሪ ክፍያ የሚውል የገቢ ማሰባሰቢያ መረሃ ግብር በነገው ዕለት እንደሚያካሂድ ገለፀ!

- ሀሩን ሚዲያ፥ ሐምሌ 17/2017

የኦሮሚያ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክርቤት በአዲስአበባ ከተማ ቦሌ ክ/ከተማ በቦሌ ቡልቡላ ወረዳ 12 ባለ 11 ወለል (G+10 ) የሆነ ዘመናዊ ህንጻ ግዢ መፈጸሙ የሚታወስ ነው።

የኦሮሚያ መጅሊስ ህንፃ ግዢውን የፈፀመው በ300 ሚሊዮን ብር መሆኑን የገለፀ ቢሆንም የተከፈለው ክፍያ 100 ሚሊዮን ብር ብቻ መሆኑን በመግለጫው ላይ ተነስቷል።

የኦሮሚያ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሸይኽ ጋሊ ሙክታር እንዳሉት ህዝበ ሙስሊሙን በመተማመን የህንፃው ግዢ እንደተፈፀመ በመግለፅ ቀሪው የ200 ሚሊዮን ብር ክፍያ እንዲጠናቀቅ ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል።

ለህንፃው ቀሪ 200 ሚሊዮን ያልተጠናቀቀ ክፍያ ለመክፈል በነገው ዕለት ጁመዓ ሀምሌ 18/2017 በአዲስ አበባ ከተማ፣ በሸገር ከተማ እና በኦሮሚያ ክልል በተለያዩ ዞኖችና ወረዳዎች ሙስሊሞችን ያሳተፈ የገቢ መሰባሰቢያ ፕሮግራም እንደሚካሄድ ገልፀዋል።

በዛሬው መግለጫ ላይ የተገኙት ኡስታዝ አህመዲን ጀበል ባስተላለፉት መልዕክት የኦሮሚያ መጅሊስ ላከናወነው የህንፃ ግዢ ምስጋናቸውን አቅርበው ያለበት እዳ እንዲከፈል ሁላችንም የድርሻችን ልንወጣ ይገባል ብለዋል።

የኦሮሚያ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ላለፉት ዓመታት ሰፊውን የኦሮሚያ ሙስሊም የሚወክል ህንፃ እንዳልነበረው በዛሬው መግለጫ ላይ የተነሳ ሲሆን ይህን የህንፃ ግዢ ለፈፀሙ የኦሮሚያ መጅሊስ አመራሮች በዝግጅቱ ላይ የተገኙ ኡስታዞች አመስግነዋል።

ህዝበ ሙስሊሙም የኦሮሚያ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ያለበትን እዳ እንዲከፈል በነገው ዕለት በሚካሄደው የገቢ ማሰባሰቢያ መርኅግብር ላይ በንቃት እንዲሳተፍ ጥሪ ቀርቧል።

© ሀሩን ሚዲያ

ሒጅራ ባንክ የሲራራ አዋርድ የስራ ፈጠራ ውድድር ለአሸናፊዎች የሽልማት መርሃ ግብር አካሄደ!- ሀሩን ሚዲያ፣ ሐምሌ 17/2017ስራ ፈጣሪ እና ትጉህ ወጣቶችን ለማበረታት ታስቦ በሂጅራ ባንክ ...
24/07/2025

ሒጅራ ባንክ የሲራራ አዋርድ የስራ ፈጠራ ውድድር ለአሸናፊዎች የሽልማት መርሃ ግብር አካሄደ!

- ሀሩን ሚዲያ፣ ሐምሌ 17/2017

ስራ ፈጣሪ እና ትጉህ ወጣቶችን ለማበረታት ታስቦ በሂጅራ ባንክ አዘጋጅነት ሲካሄድ የቆየው የሲራራ አዋርድ የስራ ፈጠራ ውድድር ተጠናቋል።

የሽልማት መርኃ ግብሩ በዛሬው ዕለት በኢሊሌ ሆቴል የተካሄደ ሲሆን በመርኃ ግብሩ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች የአዲስአበባ እና የኦሮሚያ መጅሊስ አመራሮች ፣ የባንኩ የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት፣ የባንኩ ማኔጅመንት እና ሌሎች ተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት በድምቀት ተከናውኗል።

በአንደኛ ደረጃ አሸናፍነት ያጠናቀቀው ስራ ፈጣሪ ዶ/ር ሚልኪያስ አህመድ ሲሆን፣ ለግብርና ምርታማነት በጣም አስፈላጊ የሆነ እና ለአፈር ማዳበሪያነት የሚውል ኦርጋኒክ ማዳበሪያ ከእንስሳት አጥንት በመፍጠር የማህበረሰቡን ችግር የሚያቃል ድንቅ የፈጠራ ዉጤት ያበረከተ ሲሆን የ 3 ሚልየን የቀርደል ሀሰን ፋይናንስኪንግ እና የ 300 መቶ ሺ ብር ተሸላሚ ሆኗል።

በመቀጠል 2ኛ ደረጃን በመያዝ ያጠናቀቀዉ ስራ ፈጣሪ ዩሱፍ አሊ የገበሬዎችን የዕለት ከዕለት አድካሚና ኋላቀር የአሰራር ዘዴዎችን ወደ ተሻሻለ ደረጃ ለማምጣት በማሰብ የእህል ማጨጃ ማሽንን በመስራት እና ለገበያ በማቅረብ (production and selling of crop harvesting machine) ባለው የፈጠራ ሃሳብ በማቅረብ ያሸነፈ ሲሆን የ1 ሚልየን ቀርደል ሀሰን ፋይናንሲንግ እና የ 200 መቶ ሺህ ብር ተሸላሚ ሆኗል።

እንዲሁም ሙሃመድ ጁሃር በትንሽ ኃይል የሚሰራ የዶሮ እንቁላል ማፈልፈያ ማሽን በመስራት የሶስተኛ ደረጃ አሸናፊ በመሆን ያጠናቀቀ ሲሆን 500 ሺ የቀርድ ፋይናንሲንግ ሺልማት እና 100 መቶ ሺ ተሸላሚ ሆኗል። በተጨማሪም ጣሂር ኢሳ እና ኢሳቅ ጋሊ (በአብሮነት) እንዲሁም ኢብራሂም አሊ በቅደም ተከተል 4ኛ እና 5ኛ ደረጃን በመያዝ ውድድሩን አጠናቀዋል።

© ሀሩን ሚዲያ

Address

Скопје

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Harun media ሃሩን ሚዲያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Harun media ሃሩን ሚዲያ:

Share

ሃሩንቲዩብ

ሀሩንቲዩብ የተለያዩ አስተማሪ የሆኑ የዳእዋ ልዩ ልዩ ዝግጅቶችን ለእናንተ ያደረሳል