Harun media ሃሩን ሚዲያ

Harun media ሃሩን ሚዲያ ዓላማችን በሙስሊሙ ማህበረሰብ ዘንድ የመረጃ ክፍተት እንዳይኖር መትጋት ነው።

በንጉሥ ነጃሺ ዙርያ የተሠራ "አርዱ ሲድቅ" ዘጋቢ ፊልም ምርቃትና ሲምፖዚየም መካሄዱ ተገለፀ!- ሀሩን ሚዲያ፥ ታህሳስ 4/2018ትካል ረድኤት ቢላል (ቢላል ኤይድ) የኢትዮጵያን ገጽታ በዓለም...
13/12/2025

በንጉሥ ነጃሺ ዙርያ የተሠራ "አርዱ ሲድቅ" ዘጋቢ ፊልም ምርቃትና ሲምፖዚየም መካሄዱ ተገለፀ!

- ሀሩን ሚዲያ፥ ታህሳስ 4/2018

ትካል ረድኤት ቢላል (ቢላል ኤይድ) የኢትዮጵያን ገጽታ በዓለም መድረክ ላይ በበጎ ለማስተዋወቅ በንጉሥ ነጃሺና በነቢዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) ባልደረቦች ዙርያ ያዘጋጀውን ዘጋቢ ፊልም ዛሬ በአዲስ አበባ አድዋ ሙዚየም ማስመረቁ ተገልጿል።

የሲምፖዚየሙ ዋና ዓላማ በትግራይ ክልል በሚገኘው በንጉሥ ነጃሺ መስጅድ የሚገኙ ቅርሶችን ሙስሊሙ ማኅበረሰብ እንዲያውቅ ከማድረግ ባሻገር እንዲጠቀምበት መሆኑን የፕሮግራሙ አዘጋጅ አሚር ሳሊህ መናገራቸውን ሚንበር ቲቪ ዘግቧል።

የነጃሺ ታሪክ በዓለም ትልቅ ቅርስ ሆኖ እያለ በተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) አለመመዝገቡን የገለጹት አሚር፤ ለማስመዝገብ ነጃሺ ዜሮ ዜሮ መንደር በሚል ኢኒሼቲቭ ተጀምሮ እንቅስቃሴ ላይ እንደሚገኙ አስረድተዋል።

‘አርዱ ሲድቅ’ ወይም የእውነት ምድር በሚል ዘጋቢ ፊልም መዘጋጀቱን የፕሮግራሙ አስተባባሪዎች ገልጸዋል።

ዘጋቢ ፊልሙ ከኢትዮጵያ ባለፈ በውጪ ሀገሮች ለማሳየትም ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የሲምፖዝየሙ አዘጋጅ ለሚንበር ቲቪ ተናግረዋል። በቀጣይ በሳዑዲ ጂዳ ከተማ ለማቅረብ የተዘጋጁ ሲሆን በአምስት ቋንቋዎች መተርጎሙን ገልጸዋል።

የፕሮግራሙ የክብር እንግዳ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የምሥራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር አቶ ጌታቸው ረዳ፤ የነጃሺ ታሪክ “ለእስልምና መስፋፋት ያለውን ትልቅ ትርጉም የሚገልጽ ነው” ያሉ ሲሆን ታሪኩንም የሁላችንም ታሪክ ነው ብለዋል።

በዝግጅቱ ከአቶ ጌታቸው ረዳ በተጨማሪ የቀድሞው የኢትዮጵያ አየር ኃይል ዋና አዛዥ ሜጀር ጀነራል አበበ ተክለ ሃይማኖትን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች መገኘታቸው ተመላክቷል።

© ሀሩን ሚዲያ

በአልነጃሺ ዙርያ የተዘጋጀው ዘገቢ ፊልም |ቆይታ በአልነጃሺ ዙርያ ሲምፖዚየም አዘጋጅ ከሆኑት ከአቶ አሚር ሳሊህ ጋር||HarunMedia||
11/12/2025

በአልነጃሺ ዙርያ የተዘጋጀው ዘገቢ ፊልም |ቆይታ በአልነጃሺ ዙርያ ሲምፖዚየም አዘጋጅ ከሆኑት ከአቶ አሚር ሳሊህ ጋር||HarunMedia||

HARUN MEDIA የሙስሊሙ ዑማ ቀዳሚ ድምጽ !

ለሰላቢዎች ወዮላቸው!ኡስታዝ ካሚል ጣሀ|ዳዕዋ መደምጥ ያለበት ወሳኝ መልዕክት ||HarunMedia||
11/12/2025

ለሰላቢዎች ወዮላቸው!ኡስታዝ ካሚል ጣሀ|ዳዕዋ መደምጥ ያለበት ወሳኝ መልዕክት ||HarunMedia||

HARUN MEDIA የሙስሊሙ ዑማ ቀዳሚ ድምጽ !

- የነፃ ስልጠና መርኀ ግብር ጥቆማ!ታላቅ የስልጠና ፕሮግራም ለወጣቶች በዘርፉ ከፍተኛ ልምድ ባላቸው በተወዳጅ ኡስታዞች በኡስታዝ ሱፊያን ዑስማን (self-development)በኡስታዝ አህመዲ...
11/12/2025

- የነፃ ስልጠና መርኀ ግብር ጥቆማ!

ታላቅ የስልጠና ፕሮግራም ለወጣቶች በዘርፉ ከፍተኛ ልምድ ባላቸው በተወዳጅ ኡስታዞች

በኡስታዝ ሱፊያን ዑስማን (self-development)

በኡስታዝ አህመዲን ጀበል ( impact- making)

በኡስታዝ ሺሀአቡዲን ኑራ (fundamental- leadership)

ከእነዚህ ،ኡስታዞች በተጨማሪ በሌሎች ታላላቅ ኡስታዞች በሳምንት ሁለት ቀን ማክሰኞ እና ሐሙስ
ከ ምሽቱ 2፡40 ጀምሮ በሀላል አርአያ ወጣቶች የወቅፍና የበጎ አድራጎት ማህበር የቴሌግራም ቻናል በቀጥታ ስርጭት

የስልጠናው ቻናል እሄን ሊንክ በመጫን ወደ ስልጠናው ይቀላቀሉ

https://t.me/HalalArayaWetatochChannel

የመጀመሪው ስልጠና ዛሬ ሐሙስ ማታ በኡስታዝ ሱፊያን ዑስማን (self-development)
2:40 ጀምሮ
ሰዓት ማክበር ኢስላማዋ ግዴታችን ነው!
ለበለጠ መረጃ ስልነው
0930491946

Telegram:- t.me/HalalArayaWetatochgroup

ፈጥነው ይመዝገቡ !
ምንም ዓይነት ክፍያ የለውም!

ከእኛ የሚጠበቀው ተምረን ሰልጥነን እራሳችንን፤ዲናችንና ሀገራችንን ማበልፀግ ነው ።

© በሀላል አርአያ ወጣቶች የወቅፍና የበጎ አድራጎት ማህበር የተዘጋጀ

10/12/2025

وَيْلٌ لِّلْمُطَفِّفِينَ
''ለሰላቢዎች ወዮላቸው''
በኡስታዝ ካሚል ጧሃ ነገ ሀሙስ ምሽት 12:45 በሀሩን ሚዲያ ይጠብቁን

በሞሮኮ ለኢትዮጵያ ሙስሊሞች የተበረከተ ሽልማት እና ተያያዥ ጉዳዮች||HarunMedia||
10/12/2025

በሞሮኮ ለኢትዮጵያ ሙስሊሞች የተበረከተ ሽልማት እና ተያያዥ ጉዳዮች||HarunMedia||

HARUN MEDIA የሙስሊሙ ዑማ ቀዳሚ ድምጽ !

በሞሮኮ ንጉሥ ሙሀመድ 6ኛ የአፍሪካ ኡለማ ፋውንዴሽን 7ኛ ጠቅላላ ጉባኤ ተሳታፊዎች የእንኳን ደህና መጣችሁ አቀባበል እና መግለጫ መርኅ ግብር እየተካሄደ ይገኛል!- ሀሩን ሚዲያ፥ ታህሳስ 01...
10/12/2025

በሞሮኮ ንጉሥ ሙሀመድ 6ኛ የአፍሪካ ኡለማ ፋውንዴሽን 7ኛ ጠቅላላ ጉባኤ ተሳታፊዎች የእንኳን ደህና መጣችሁ አቀባበል እና መግለጫ መርኅ ግብር እየተካሄደ ይገኛል!

- ሀሩን ሚዲያ፥ ታህሳስ 01/2018

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕረዚዳንት በሸይኽ ሐጅ ኢብራሂም ቱፋ የተመራው ልዑክ በሞሮኮ ንጉሥ ሙሀመድ 6ኛ የአፍሪካ ኡለማ ፋውንዴሽን 7ኛ ጠቅላላ ጉባኤ ተሳታፊዎች የእንኳን ደህና መጣችሁ አቀባበል እና መግለጫ መርኅ ግብር እያካሄደ ይገኛል።

በጠቅላይ ም/ቤቱ መሰብሰቢያ አዳራሽ እየተካሄደ በሚገኘው መርኅ ግብር የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ምክትል ፕረዚዳንት ሸይኽ ሐሚዲ ሙሳ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ባለፉት ሶስት አመታት በዲብሎማሲ ረገድ ሰፊ ስራ መሰራቱን አንስተው በ36 ሀገራት የኢትዮጵያ ኢስላማዊ እሴት እና ታሪኮችን ለአለም የማስተዋወቅ ስራ ተሰርቷል ብለዋል።

ተቀዳሚ ምክትል ፕረዚዳንቱ ሸይኽ አብዱልከሪም ሸይኽ በድረድን በበኩላቸው በሞሮኮ የነበረው ጉዞ ስኬታማና ከእስካሁኑ የተለዬ ሀገራችንም ከፍ ያለችበት ነበር ብለዋል።

የጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዚዳንት ሸይኽ ሐጅ ኢብራሂም ተፋ በመርኅ ግብሩ ላይ ባደረጉት ንግግር በሞሮኮ በነበራቸው ቆይታ የሀገራችን ኢስላማዊ ታሪክ ከፍ ያለበት ብዙ ያገኘንበት ነበር ብለዋል። በጉባኤው ላይ 48 ሀገራት የተሳተፉ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን ኢትዮጵያ ከተለያዩ ሀገራት ጋር አብሮ የመስራት ዕድል ያገኘችበት እንደነበር ሸይኽ ሐጅ ኢብራሂም አያይዘው ገልጸዋል።

በሞሮኮ በነበረው የንጉሥ ሙሀመድ 6ኛ የአፍሪካ ኡለማ ፋውንዴሽን ጠቅላላ ጉባኤ የጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕረዚዳንት ሸይኽ ሐጅ ኢብራሂም ቱፋ በዳዕዋ እና ለእስልምና መጠናከር ላበረከቱት ጉልህ አስተዋጽኦ ከሞሮኮ ንጉሥ ሙሐመድ ስድስተኛ የአፍሪካ ዑለማ ፋውንዴሽን ሽልማት እንደተበረከተላቸው ተገልጿል።

© ሀሩን ሚዲያ

09/12/2025

በከምባታ ዞን መስጂድና መድረሳ ለማስገንባት ታልሞ ታላቅ የዳዕዋና የገቢ ማሰባሰቢያ ተካሄደ

በከምባታ ዞን መስጂድና መድረሳ ለማስገንባት ታልሞ ታላቅ የዳዕዋና የገቢ ማሰባሰቢያ ተካሄደ||HarunMedia||
09/12/2025

በከምባታ ዞን መስጂድና መድረሳ ለማስገንባት ታልሞ ታላቅ የዳዕዋና የገቢ ማሰባሰቢያ ተካሄደ||HarunMedia||

HARUN MEDIA የሙስሊሙ ዑማ ቀዳሚ ድምጽ !

08/12/2025

የፊታችን ጃንዋሪ 3 በአትላንታ እና አካባቢው በመስጅደል ሙእሚኒን የማይቀርበት ልዩ መሰናዶ..!

© ሀሩን ሚዲያ

የኢፋዳ ኢስላማዊ ድርጅት የመክፈቻ ጉባኤ||HarunMedia||
08/12/2025

የኢፋዳ ኢስላማዊ ድርጅት የመክፈቻ ጉባኤ||HarunMedia||

HARUN MEDIA የሙስሊሙ ዑማ ቀዳሚ ድምጽ !

በከምባታ ዞን ታላቅ የዳዕዋ ፕሮግራም ተካሄደ!- ሀሩን ሚዲያ ደቡብ ስቱዲዮ፥ ህዳር 28/2018 በማዕከላዊ ኢትዮጲያ ክልል በከምባታ ዞን በሀደሮ ጡንጦ ዙሪያ ወረዳ ጡንጦ ከተማ ታላቅ የዳዕዋ...
07/12/2025

በከምባታ ዞን ታላቅ የዳዕዋ ፕሮግራም ተካሄደ!

- ሀሩን ሚዲያ ደቡብ ስቱዲዮ፥ ህዳር 28/2018

በማዕከላዊ ኢትዮጲያ ክልል በከምባታ ዞን በሀደሮ ጡንጦ ዙሪያ ወረዳ ጡንጦ ከተማ ታላቅ የዳዕዋ መርኅግብር በዛሬው ዕለት ተካሂዷል፡፡

የዳዕዋ ፕሮግራሙ የተካሄደው በአት-ተዓውን የዳዕዋና እስላማዊ አስተምሮ ማህበር ጋር በመተባበር መሆኑም ነው የተገለፀው።

የዝግጅቱ ዋነኛ ዓላማ ለአካባቢው ማህበረሰብን ኢስላማዊ አስተምሮ ማካሄድ ሲሆን በተጨማሪም በአካባቢው መስጂድና መድረሳ ባለመኖሩ የመስጂድ መስሪያ ቦታ መግዛትና መስጂድና መድረሳ ለመገንባት ያለመ ነው።

አካባቢው ላይ የሚኖሩ ሙስሊሞች ቁጥራቸው አናሳ በመሆኑ በራሳቸው አቅም መስጂድ መገንባት ስላልቻሉ
በአት-ተዓውን የዳዕዋና እስላማዊ አስተምሮ ማህበር ጋር በመተባበር የረዥም ጊዜ ህልማቸው እውን እንዲሆንላቸው መስጂድ እንዲገነባለቸው በመላው ዓለም ለሚገኙ ሙስሊሞች ድጋፍ እንደሚሹ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።

በሌላ በኩል ከተማው ላይ የሚኖሩ ሙስሊሞች መቀበሪያ ቦታም ጭምር እንደሌላቸውና ይህንንም ጥያቄያቸውን እስከ ፌደራል መዋቅር ድረስ ቢያቀርቡም ጉዳያቸውን የያዘው አመራር በየጊዜው እየተቀያየረብን ችግሩ ሳይፈታ ቆይቷል ሲሉ ለሀሩን ሚዲያ ተናግረዋል፡፡

መርሃ- ግብሩ ላይ ኡስታዝ መሀመድ ፈረጅ፣ ሃጂ ሺፋ መሀመድ፣ ሃጂ አብዱረህማን አንጀጆ፣ ኡስታዝ ሳዲቅ መሀመድ፣ የሀላባ፣ የወላይታ፣ የአረካ፣ የጠንባሮ ጀማዖች፣ ኡለማኦች መሻይኮች የአከባቢው ማህበረሰቦች ተገኝተዋል።

ለመስጅድ መግዣ የሚሆን ቦታ ድጋፍ ለማድረግ፦

ንግድ ባንክ 1000544368471

የአካውንት ስም በጡንጦ ከተማ አዲስ ለሚቋቋመው መስጅድ የሚል መሆኑንም አዘጋጆቹ ገልፀዋል፡፡

- ሀሩን ሚዲያ ደቡብ ስቱዲዮ በስፍራው ተገኝቶ ያጠናቀረውን የቪዲዮ ዘገባ በቀጣይ ወደናንተ የምናደርስ ይሆናል።

© ሀሩን ሚዲያ

Address

Https://maps. App. Goo. Gl/ZN47MPhnMDPQd422A
Addis Ababa
1000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Harun media ሃሩን ሚዲያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Harun media ሃሩን ሚዲያ:

Share

ሃሩንቲዩብ

ሀሩንቲዩብ የተለያዩ አስተማሪ የሆኑ የዳእዋ ልዩ ልዩ ዝግጅቶችን ለእናንተ ያደረሳል