Harun media ሃሩን ሚዲያ

Harun media ሃሩን ሚዲያ ዓላማችን በሙስሊሙ ማህበረሰብ ዘንድ የመረጃ ክፍተት እንዳይኖር መትጋት ነው።

ከአምባሳደር ሙሀመድ ድሪር ጋር ቆይታ ነገ ቅዳሜ በአሜሪካ ስለሚካሄደው ሀገራዊ ምክክር ስብሰባ |Harun Meida
29/08/2025

ከአምባሳደር ሙሀመድ ድሪር ጋር ቆይታ ነገ ቅዳሜ በአሜሪካ ስለሚካሄደው ሀገራዊ ምክክር ስብሰባ |Harun Meida

HARUN MEDIA የሙስሊሙ ዑማ ቀዳሚ ድምጽ !

የፎቶ ዘገባ!ሀሩን ሚዲያ ከመወዳ ትምህርት ቤት እና ከቢዋይዲ ቴክኖሎጂ ጋር በመተባበር ለ6 ሳምንታት በዌብአፕ እና አፕ ዲቨሎፕመንት እና በተለያዩ የቴክኖሎጂ እና ኢስላማዊ የማንነት እነጻ ሲ...
29/08/2025

የፎቶ ዘገባ!

ሀሩን ሚዲያ ከመወዳ ትምህርት ቤት እና ከቢዋይዲ ቴክኖሎጂ ጋር በመተባበር ለ6 ሳምንታት በዌብአፕ እና አፕ ዲቨሎፕመንት እና በተለያዩ የቴክኖሎጂ እና ኢስላማዊ የማንነት እነጻ ሲያስተምራቸው የቆዩ 67 ተማሪዎችን በዛሬው ዕለት በቢላሉል ሀበሺ አዳራሽ አስመርቋል።

- በመርኅ ግብሩ ላይ ከተነሱ ምስሎች መካከል ከፊሎቹ ከታች ተያይዞ ቀርቧል።

© ሀሩን ሚዲያ

ሀሩን ሚዲያ ከሁለት ተቋማት ጋር በመተባበር በቴክኖሎጂና ኢስላማዊ ማንነት ላይ ያተኮረ ስልጠና ሲሰጣቸው የነበሩ ተማሪዎቹን አሰመረቀ!- ሀሩን ሚዲያ፥ ነሐሴ 23/2017ሀሩን ሚዲያ ከመወዳ ት...
29/08/2025

ሀሩን ሚዲያ ከሁለት ተቋማት ጋር በመተባበር በቴክኖሎጂና ኢስላማዊ ማንነት ላይ ያተኮረ ስልጠና ሲሰጣቸው የነበሩ ተማሪዎቹን አሰመረቀ!

- ሀሩን ሚዲያ፥ ነሐሴ 23/2017

ሀሩን ሚዲያ ከመወዳ ትምህርት ቤት እና ከቢዋይዲ ቴክኖሎጂ ጋር በመተባበር ለ6 ሳምንታት በዌብአፕ፣ዲቨሎፕመንት እና በተለያዩ የቴክኖሎጂ እና ኢስላማዊ የማንነት እነጻ ሲያስተምራቸው የቆዩ ተማሪዎችን በዛሬው ዕለት በቢላሉል ሀበሺ አዳራሽ አስመርቋል።

ተመራቂ ተማሪዎቹ በዌብና አፕ ዲቨሎፕመንት (Web and App Development) ፣ ኢስላማዊ ማንነት( Understanding Islam and Islamic History)፣ ልምድ ማጋራት (Mentorship)፣ ማንነት እነፃ (Personal Development) ላይ ያተኮረ ልዩ የክረምት ስልጠና በአዲስ አበባ ካራ ቆሬ በሚገኘው መወዳ ትምህርት ቤት ውስጥ ስልጠና ሲከታተሉ የነበሩ ሲሆን በዛሬው ዕለት የመወዳ ት/ቤት አመራሮች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች የተመራቂ ተማሪ ቤተሰቦችና ተማሪዎች በተገኙበት ተመርቀዋል።

በምረቃ ፕሮግራሙ ላይ የሀሩን ሚዲያ የሀገር ውስጥ ስቱዲዮዎች ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ባህሩ አባስ ተገኝተው ባስተላለፉት መልእክት ሀሩን ሚዲያ መረጃዎችን ከማድረስ በተጨማሪ ትውልድ ተኮር የሆኑ ስራዎችን እየሰራ መሆኑን ገልጸው በዛሬው ዕለት የተመረቁ ተማሪዎችም ሚዲያው ታዳጊ ልጆችን ማብቃት ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ መሆኑን ማሳያ መሆኑን ተናግረዋለል።

የመወዳ ት/ቤት ም/ስራአስኪያጅ የሆኑት አቶ አብደላ ከድር መወዳ ትምህርት ቤት በሁሉም ዘርፍ ተማሪዎችን ብቁ ለማድረግ እየሰራ መሆኑን አንስተው በተለይም ለቴክኖሎጂ ትኩረት በመስጠት ይሰራል ብለዋል።

ተመራቂ ተማሪዎች በክረምቱ ኮርስ ከወሰዱባቸው የዌብሳይት እና አፕሊኬሽን ማበልፀግ የተግባር ስራ በማከናወን ለታዳሚው አቅርበዋል። በዝግጅቱ ማጠቃለያ የክረምት ስልጠና ለወሰዱ ተማሪዎች ሰርቲፊኬት ተበርክቶላቸዋል።

© ሀሩን ሚዲያ

የጉራጌ ዞን እስልምና ጉዳዮች ም/ቤት መሥራች ጠቅላላ ጉባዔና የዞኑን የስራ አስፈፃሚ አባላት ምርጫ አካሄደ። - ሀሩን ሚዲያ ደቡብ ስቱዲዮ ነሐሴ23/2017 በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የጉራጌ...
29/08/2025

የጉራጌ ዞን እስልምና ጉዳዮች ም/ቤት መሥራች ጠቅላላ ጉባዔና የዞኑን የስራ አስፈፃሚ አባላት ምርጫ አካሄደ።

- ሀሩን ሚዲያ ደቡብ ስቱዲዮ ነሐሴ23/2017

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የጉራጌ ዞን እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት መሥራች ጠቅላላ ጉባኤዉንና የስራ አስፈፃሚ አባላት ሞርጫ አካሂዷል።

በ2017 ምርጫ በአምስቱም ዘርፍ ከኡለማዎች፣ከሙህራን፣ከወጣቶች፣ከሴቶችና ከስራ ማህበረሰብ ክፍሎች ህዝበ ሙስሊሙን ሊወክሉ የሚችሉ አባላትን በመምረጥ መስራች ጉባዔ በመመሥረት ለቀጣይ አምስት አመት ዞኑን የሚመሩ ስራ አስፈፃሚዎችን ምረጡ ተገልጿል።

በዚህም መሰረት፦

የጉራጌ ዞን እስልምና ጉዳዮች ምክርቤት ፦ሸይኽ አባስ ያሲን ሰብሳቢ

- ኡስታዝ ጀሚል ሁሴን ምክትል ሰብሳቢ

- ኡስታዝ ሷሊህ ጀማል ፀሃፊ

-ኡስታዝ አብድልፈታ ሼህ ተማም አባል

- ኡስታዝ ጅላሉ ያሲን አባል

- ኡስታዝ ሀሰን ሸሪፍ አባል

-ሀጅ ነስሩ ያሲን አባል

-ሚፋታህ ያሲን አባል
- ሀምዲያ ሳዲቅ አባል
ሆነው ሲመረጡ ቀጥሎ ላለው መጅሊስ መዋቅር ጉራጌ ዞንን የሚወክሉ ተወካዮች

- ሸይኽ ሰአድ ጅላሉ የፌደራል ተወካይ

-ሸይኽ አብድልበር ዘይን የክልል ተወካይ

-ሸይኽ ባቂል በደዊ የክልል ተወካይ

-ሸይኽ በህጃ አብድልጀሊል የክልል ተወካይ

-አቶ ደጉ አብራር የክልል ኦዲትና ኢ/ተወካይ በመሆን ተመርጠው በጉባዔው ፊት ቃለ መኃላ ፈፅመዋል ።

በዚህ የጠቅላላ ጉባዔ ምስረታ ላይ የፌደራል ምርጫ አስፈፃሚ ኡስታዝ ሪያድና የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ አቶ ፉዓድ ሙሀመድ እንዲሁም ሌሎችም የክልሉና የዞኑ መጅሊስ የ2017ምርጫ አስፈፃሚ ቦርድ አባላት ተገኝቷ ሲል የዘገበዉ የጉራጌ ዞን መንግስት ኮሚኒኬሽን ነው።

© ሀሩን ሚዲያ

የማስታወቂያ ሰዓት በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው የሂራዕ STEM ኤግዚቢሽን እነሆ ደጃችን ደርሷል።ሂራዕ የሙስሊም ተማሪዎች ማኅበር ከተመሰረተ ጊዜ አንስቶ ላለፉት  #አምስት አመታት በሙስሊም ተማ...
29/08/2025

የማስታወቂያ ሰዓት

በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው የሂራዕ STEM ኤግዚቢሽን እነሆ ደጃችን ደርሷል።

ሂራዕ የሙስሊም ተማሪዎች ማኅበር ከተመሰረተ ጊዜ አንስቶ ላለፉት #አምስት አመታት በሙስሊም ተማሪዎች ስነ–ምግባርና አካዳሚ ልህቀት ዙርያ እየሰራ ይገኛል። ተማሪዎች በመልካም ስነ–ምግባር ታንፀው በእውቀት በልፅገው ሁለንተናዊ ከፍታን እንዲጎናፀፉ በተለያየ መንገድ እየተንቀሳ የሚገኘው ሂራዕ ዛሬ ደግሞ በልዩ ፕሮግራም መጥቶላችሇል።
•••

ተማሪዎች የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ምህንድስናና ሂሳብ (STEM) እውቀታቸውን ከእስላማዊ እሴቶች ጋር እንዴት እንዳዋሃዱ የሚያሳይ ልዩ የፈጠራ ኤግዚቢሽን ተዘጋጅቷል።

#ዝግጅቱም እሁድ፣ ነሐሴ 25,2017 አ.ል ከጠዋቱ 1:00 ጀምሮ እስከ ምሽት 11:00 ዊንጌት #በአወሊያ አዳራሽ ይካሄዳል።

መሪ ሃሳብ፦ የታነፁ የ STEM (ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ምህንድስናና፣ ሂሳብ) ኢኖቬተሮችን/ ተመራማሪዎች ለወደፊቷ በቴክኖሎጂ ለበለፀገች ኢትዮጵያ

ይህ ኤግዚቢሽን ለሁሉም ዕድሜ የሚሆኑ አስደሳችና አስተማሪ ዝግጅቶችን አጣምሮ የያዘ ነው። ከሚቀርቡት ፕሮግራሞች መካከል፡-

• ሜካኒካልና ሶፍትዌር ምህንድስና፣ ኢንፎርሜሽን ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ፣ ፋርማሲና የጥርስ ህክምና፣ ኬምስትሪ ሌሎችም ርዕሰ ጉዳዮች ላይ በዘርፉ ካሉ ባለሙያዎች ጋር ቆይታ ይኖራል። በተጨማሪም ይጎበኛሉ።

• በድር ገፅ ልማት፣ ግራፊክ ዲዛይን፣ ኮንቴንት ክሪኤሽን፣ የካሊግራፊ ጥበብ፣ ኢፖክሲ፣ ሂና፣ ልብስ ዲዛይን፣ የወረቀት ፓኬጂንግ፣ የአበባ ዲዛይን እና የተለያዩ የእደ-ጥበብ ሥራዎች ላይ የተሰማሩ ተማሪዎች ሥራዎቻቸውን የሚያቀርቡበት።

• ሂጃብ፣ እውቀት በኢስላም፣ ቁርአንና ሳይንስ፣ የመሳሰሉት ላይ ሰፋ ያለ ውይይት ይኖራል።

ሌሎችም አሸላሚ ውድድሮች እንደ:

(VR)

#ችግር የመፍታት ክህሎት እና የመሳሰሉት ይኖራሉ።

ለመመዝገብ👉https://forms.gle/WwRPDbdzCYTtmdpZ9

ለበለጠ መረጃ
0900004848
0964521722

ቴሌግራም 👉 https://t.me/HiraEslamicMidea

ፌስቡክ 👉
https://www.facebook.com/share/1PvshNQnmA/

ኢንስታግራም 👉
https://www.instagram.com/stories/hira_muslim_students_page1/3691995877007125001?utm_source=ig_story_item_share&igsh=MndocGtlamQxcTdr

ለሁላችንም የማይረሳ ቀን ይሆናል!
#ሒራ #ፈጠራ #ኤግዚቢሽን #ኢስላም #ሂጃብ #ሙስሊምፈጣሪዎች #ኢትዮጵያ #እምነትናልህቀት #ስራፈጠራ #ቴክኖሎጂ #እስላማዊእሴቶች #ሳይንስ #ምህንድስና #አዲስአበባ

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር  ቤት ሃጅ ኢብራሂም መሀመድ ስራጅን የም/ቤቱ ፕሬዘዳንት አድርጎ መምረጡ ተገለፀ፡፡- ሀሩን ሚዲያ፥ነሀሴ 22/2017የቤኒሻንጉል ጉሙዝ...
28/08/2025

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ሃጅ ኢብራሂም መሀመድ ስራጅን የም/ቤቱ ፕሬዘዳንት አድርጎ መምረጡ ተገለፀ፡፡

- ሀሩን ሚዲያ፥ነሀሴ 22/2017

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት የም/ቤቱ የአስፈፃሚ አካላት የመጨረሻ ምርጫ አካሂዷል።

በክልሉ የእስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ሲመሰረት የመጀመሪያው መሆኑን የገለፁት የምርጫ ቦርዱ ምክትል አስተባባሪ አቶ መሀመድ ኢብራሂም ቀደም ብሎ በክልሉ በሁሉም ዞኖች እና ወረዳዎች የእጩ አስፈፃሚዎች ምርጫ ሲካሄድ ቆይቷል ብለዋል።

የማጠቃለያ ምርጫው ሲካሄድም በሙስሊሙ ማህበረሰብ ዘንድ ከተመረጡ ኡለሞች ከምሁራን እና ከወጣቶች የተውጣጡ 11 ስራ አስፈፃሚዎች መመረጣቸውን አቶ መሀመድ ገልፀዋል።

ም/ቤቱ ባካሄደው የማጠቃለያ ምርጫም ሃጅ ኢብራሂም መሀመድ ስራጅን በድጋሜ የም/ቤቱ ፕሬዘዳንት እና ሼህ ኡመር ሃጅ አኑርን ደግሞ ም/ፕሬዘዳንት አድርጎ መምረጡ ተገልጿል።

የተካሄደው ምርጫም የምርጫ ህጉን በጠበቀና ባከበረ መልኩ በሰላም መጠናቀቁን ም/አስተባባሪው አስታውቀዋል።

የክልሉ እስልምና ጉዳዮች ም/ቤት በይፋ መስረቱ በክልሉ ላለዉ የሙስሊሙ ማህበረሰብ ፍይዳው የጎላ መሆኑን ገልፀው በሀገሪቱ ሰላምን ልማትን እና አንድነትን ለማረጋገጥ ለሚሰራው ስራም የበኩላቸውን ለመወጣት እንደሚጥሩ ተመራጭ ስራ አስፈፃሚዎች ተናግረዋል።

በምርጫ ሂደቱም ከኡለማዎች፣ከምሁራን ፣ከወጣቶች እና ከማህበረሰብ የተውጣጡ የእምነቱ ተከታዮች ተሳትፈዋል ሲል የዘገበዉ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ሚዲያ ነዉ።

© ሀሩን ሚዲያ

የስልጤ ዞን እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት መሥራች ጠቅላላ ጉባዔ እና የዞኑን የስራ አስፈፃሚ አባላት ምርጫ አካሄደ።- ሀሩን ሚዲያ ደቡብ ስቱዲዮ፥ነሃሴ22/2017በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የስ...
28/08/2025

የስልጤ ዞን እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት መሥራች ጠቅላላ ጉባዔ እና የዞኑን የስራ አስፈፃሚ አባላት ምርጫ አካሄደ።

- ሀሩን ሚዲያ ደቡብ ስቱዲዮ፥ነሃሴ22/2017

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የስልጤ ዞን እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት በ2017 ምርጫ መስራች ጉባዔውን በማድረግ በ አምስቱም ዘርፍ የስራ አስፈጻሚ አባላት ምርጫ አካሂዷል።

በዝሁ መሰረት፦

የስልጤ ዞን እስልምና ጉዳዮች ምክርቤት፦

1/ ሼኽ አ/0ረሂም አህመዲን ሰብሳቢ

2/ ሼኽ አብራር ቡሽራ ተቀዳሚ ምክትል ሰብሳቢ

3/ ሼኽ ሁሴን አብደላ ምክትል ሰብሳቢ

4/ ኡስታዝ ጁሃር ሰዒድ ዋና ፃሃፊ

5/ኡስታዝ ጀማል ጎሽባሮ ም/ፀሃፊ
እንዲሁም ቀጥሎ ላለው መጅሊስ መዋቅር ስልጤ ዞንን የሚወክሉ ተወካዮች፦

1ኛ ኢማም ሐጂ አብዲል ሃዲ አህመድ ቡርሃን

2ኛ ኡስታዝ ሙስጠፋ ሙሀመድ

3ኛ ሸይኽ ሙስጠፋ ጀማል

4ኛ ሸይኽ አብዲሰላም አንዋር

5ኛ ሸይኽ ከይረዲን ሙሀመድ

6ኛ ሸይኽ ሥራጅ ሸሪፍ
በመሆን ተመርጠው በጉባዔው ፊት ቃለ መኃላ መፈፀማቸዉ ተገልጿል።

ጉባዔው ላይ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ አቶ ፉዓድ ሙሀመድ ፣ የስልጤ ዞን ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ዘይኔ ቤልካ ፣ከወረዳና ከተማ አስተዳደሮች የመጡ የመጅሊስ ስራ አስፈጻሚዎችና እና ሌሎችም የክልሉና የዞኑ መጅሊስ ምርጫ አስፈፃሚ ቦርድ አባላት ተገኝተዋል።

በመጨረሻም የዞኑ ምርጫ አስፈጻሚ አካላት ምርጫው ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ላደረጉት ለስልጤ ዞን አስተዳደርና ለስልጤ ዞን ሰላምና ጸጥታና መምሪያ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

© ሀሩን ሚዲያ

- ልዩ የምርቃት ፕሮግራም መግቢያ በነፃበቴክኖሎጂና ኢስላማዊ ማንነት ላይ ያተኮረ ስልጠና ምርቃት ፕሮግራም!ሀሩን ሚዲያ በዌብና አፕ ዲቨሎፕመንት (Web and App Development) ፣ ...
28/08/2025

- ልዩ የምርቃት ፕሮግራም መግቢያ በነፃ

በቴክኖሎጂና ኢስላማዊ ማንነት ላይ ያተኮረ ስልጠና ምርቃት ፕሮግራም!

ሀሩን ሚዲያ በዌብና አፕ ዲቨሎፕመንት (Web and App Development) ፣ ኢስላማዊ ማንነት( Understanding Islam and Islamic History)፣ ልምድ ማጋራት (Mentorship)፣ ማንነት እነፃ (Personal Development) ላይ ያተኮረ ልዩ የክረምት ስልጠና በአዲስ አበባ ካራ ቆሬ በሚገኘው መወዳ ትምህርት ቤት ውስጥ ስልጠና ሲከታተሉ የነበሩ ተማሪዎች የምርቃት ፕሮግራም ታላላቅ የቴክኖሎጂና የስራ ፈጠራ ባለሙያዎች በተገኙበት ይካሄዳል።

ስለሆነም እርሶ በፕሮግራሙ ላይ እንዲገኙ በታላቅ አክብሮት ተጋብዘዋል፡፡
ቀን፦ ጁሙአ ነሀሴ 23/2017/ Friday August 29, 2025
ቦታ፦በቢላሉል ሀበሽ አዳራሽ
ሰአት፦ ከቀኑ 8፡00
መግቢያ ፦ በነጻ
ዋና አዘጋጅ፦ ሀሩን ሚዲያ
ተባባሪ አዘጋጆች፦ቢዋይድ ቴክኖሎጂስና መወዳ ትምህርት ቤት

© ሀሩን ሚዲያ

ፀባይ ይኑርህ!||ኡስታዝ ካሚል ጣሀ||ልዩ ሙሀደራ||HarunMedia||
28/08/2025

ፀባይ ይኑርህ!||ኡስታዝ ካሚል ጣሀ||ልዩ ሙሀደራ||HarunMedia||

HARUN MEDIA የሙስሊሙ ዑማ ቀዳሚ ድምጽ !

በአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት የ ክ/ከተማ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ምስረታ እና የስራ አሰፈፃሚዎች ምርጫ በሰላም መጠናቀቁ ተገለፀ!- ሀሩን ሚዲያ፥ ነሀሴ 22/2017በአዲስ ...
28/08/2025

በአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት የ ክ/ከተማ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ምስረታ እና የስራ አሰፈፃሚዎች ምርጫ በሰላም መጠናቀቁ ተገለፀ!

- ሀሩን ሚዲያ፥ ነሀሴ 22/2017

በአዲስ አበባ በሁሉም ክፍለከተሞች የተካሄደው የክፍለከተማ መጅሊስ ስራ አስፈፃሚ ምርጫ ቦበሰላም መጠናቀቁን የአዲስ አበባ መጅሊስ ምርጫ አስፈፃሚ ቦርድ ገልጿል።

ሀሩን ሚዲያም በዛሬው ዕለት በሶስት ክፍለ ከተሞች፦ በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለከተማ፣ በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለከተማና በቂርቆስ ክፍለከተማ በመገኘት የምርጫ ሂደቱን አስመልክቶ በስፍራው ተገኝቶ ተከታትሏል።

በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለከተማ የነበረው የምርጫ ሂደትም ሰላማዊ እንደነበር በስፍራው የተገኘው ባልደረባችን ከማል ኑርዬ ያደረሰን መረጃ ያመላክታል።

ሌላው የሀሩን ሚዲያ ባልደረባ ሲራጅ ሙሰማ በአቃቂ ቃሊቲና በቂርቆስ ክፍለከተማ የነበረው የምርጫ ሂደት ከአምስት ዘርፎች የስራ አስፈፃሚ አባላትን በመምረጥ ሰላማዊ በሆኑ መልኩ መጠናቀቁንም ገልጿል።

በዛሬው ውሎ የክፍለ ከተማውን የስራ አስፈጻሚ አባላትና የኦዲትና ኢንስፔክሽን አባላትን ከመምረጥ ባለፈ ክፍለ ከተማውን ወክለው አዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት የሚገቡ ሰዎችም መለየታቸው ተገልጿል።

© ሀሩን ሚዲያ

ቢላሉል ሀበሺ የልማትና መረዳጃ ዕድር ከ26 በላይ ለሚሆኑ በሽታዎች ነጻ ህክምና አገልግሎት ሊሰጥ ነው።- ሀሩን ሚዲያ፣ ነሀሴ 22/2017ቢላሉል ሀበሺ የልማትና መረዳጃ እድር የ25ኛ አመት ...
28/08/2025

ቢላሉል ሀበሺ የልማትና መረዳጃ ዕድር ከ26 በላይ ለሚሆኑ በሽታዎች ነጻ ህክምና አገልግሎት ሊሰጥ ነው።

- ሀሩን ሚዲያ፣ ነሀሴ 22/2017

ቢላሉል ሀበሺ የልማትና መረዳጃ እድር የ25ኛ አመት የምስረታ በዓሉን አስመልክቶ ከአፔክስ ኢንዲያን ሆስፒታል ጋር በመተባበር አነስተኛና መካከለኛ ገቢ ላላቸው የማህበረሰብ ክፍሎች ከሀገር ውስጥ እና ከህንድ ሀገር በመጡ ባለሙያዎች ነጻ የቀዶ ጥገና አገልግሎት ሊሰጥ መሆኑን አስታውቋል።

ህክምናው ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ የሚሰጥ ሲሆን በአንደኛው ዙር ቀድመው ለተመዘገቡ 30 ታማሚዎች ነጻ የቀዶ ጥገና አገልግሎት ይደረግላቸዋል።

ከዚህ በፊት ለ22 ታካሚዎች ውጤታማ የሆነ ነጻ የቀዶ ጥገና የተደረገ ሲሆን ከክ/ሀገር ለሚመጡ ታካሚዎች እንደየሁኔታው ቅድሚያ እንደሚሰጣቸው አስታውቋል።

በመሆኑም ይህንን የቀዶ ጥገና ለማድረግ የምትፈልጉ ሁሉ ሴሚት በሚገኘው ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፊት ለፊት አፔክስ ኢንዲያን ሆስፒታል መረጃውን ማግኘት ይችላሉ።

ምዝገባው ለሁለት ሳምንት ብቻ እንደሚቆይ የተነገረ ሲሆን፦ በ0972787878 /0972797979 ወይንም 0987151515 የህክምና ዶክመንቶችን በመላክ እንዲሁም በመደወል ተጨማሪ መረጃዎችን ማግኘት ይችላሉ።

ነጻ የቀዶ ጥገና የሚደረግላቸው በሽታዎችን በአስተያየት መስጫ ሳጥናችን ላይ ይመልከቱ።

© ሀሩን ሚዲያ

Address

Https://maps. App. Goo. Gl/ZN47MPhnMDPQd422A
Addis Ababa
1000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Harun media ሃሩን ሚዲያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Harun media ሃሩን ሚዲያ:

Share

ሃሩንቲዩብ

ሀሩንቲዩብ የተለያዩ አስተማሪ የሆኑ የዳእዋ ልዩ ልዩ ዝግጅቶችን ለእናንተ ያደረሳል