Shalom Tube ሻሎም-ቲዩብ

Shalom Tube ሻሎም-ቲዩብ የሻሎም ቲዩብ ቤተሰብ በመሆን አዳዲስ የሚወጡ እና የቆዩ መልዕክቶችን,መዝሙሮችን, መረጃዎችን ይከታተሉ::

 #የአፋልጉኝበፎቶው  ላይ የምታዩት ግለሰብ  ስሙ   አዲሱ  ፍስሐ  ሲሆን በተለምዶ  ባቢ  እና ቢላል  በመባልም  ይታወቃል  ተወልዶ ያደገው   ድሬዳዋ ከተማ  ሲሆን ከሚኖርበት  ሰባተኛ ...
18/07/2025

#የአፋልጉኝ

በፎቶው ላይ የምታዩት ግለሰብ ስሙ አዲሱ ፍስሐ ሲሆን በተለምዶ ባቢ እና ቢላል በመባልም ይታወቃል ተወልዶ ያደገው ድሬዳዋ ከተማ ሲሆን ከሚኖርበት ሰባተኛ ከሚባለው ሰፈር መኖሪያ ቤት ከወጣ ሁለት አመት አልፎታል እሱን ለማግኘት ቤተሰብ ብዙ ጥረት ቢያደርግም ልናገኘው ስላልቻልን ድሬዳዋ እና አካባቢው የምትገኙ ወገኖቻችን እንትተባበሩን ስንል እንጠይቃለን::
ፈላጊ ወንድም እና እህቶቹ
0995455943- ትዕግስት ፍስሐ
0915171787
0911024566
በእነዚህ ስልኮች ብትጠቁሙን ውለታ ከፋይ ነን::
ሼር ይደረግ!

ተመስገን ማርቆስ...ዘማሪ ነው። ሻሸመኔዎች በልዩነት የምንወደው ዘማሪ ነው!ልጆች ሆነን ዘወትር ማክሰኞ ሻሸመኔ ሸዋበር  ቃለህይወት ቤተክርስቲያን መሄድ ያስደስተን ነበር። ብዙ ምክኒያቶች አ...
21/06/2025

ተመስገን ማርቆስ...

ዘማሪ ነው። ሻሸመኔዎች በልዩነት የምንወደው ዘማሪ ነው!

ልጆች ሆነን ዘወትር ማክሰኞ ሻሸመኔ ሸዋበር ቃለህይወት ቤተክርስቲያን መሄድ ያስደስተን ነበር። ብዙ ምክኒያቶች አሉን። እኔ በግሌ ቃለህይወት የመሄጃ ምክኒያቴ ወንጌል አልነበረም። ሐቅ መናገር ይኖርብኛል። ስብከቱን የምሰማበት ብስለት የለኝም። ቸርች የምሄደው ተመስገን ማርቆስን እና ፓስተር ጌቱ ዱሬሳን ለማየት ነው። ስለ ፓስተር ጌቱ ሌላ ጊዜ እፅፋለሁ።

ተመስገን ማርቆስ ሲዘምር ደስ ይላል። ነገረ ስራው ሁሉ በትህትና የተሞላ ነው። ሁላችንም እንወደዋለን። እንደምንወደው ያውቃል። ሰዎች ስለሚወዱት አይኮፈስም።

የመጀመሪያ የመዝሙር አልበሙን 96 አ.ም ክረምት ላይ አወጣ። የአልበሙ ርዕስ ፋሬስ ይላል። የተወሰንን ልጆች ቅፅል ስሙን ፋሬስ አልነው። በሳይክል ወደ ቤት ስሄድ እየተጫጫህን "ተሜ" እንለዋለን። ከሳይክል ወርዶ ያቅፈናል። በቁም ነገር ቆሞ ያናግረናል።

ታላላቆቹን ያከብራል። የሚገርመኝ ለህፃናትም ለአባቶችም እኩል አክብሮት ነበረው። የአስር አመት ልጅ መንገድ ላይ ቢያስቆመው በትህትና ያናግረዋል። ትህትና ሲባል የማስመሰል ትህትና ሳይሆን እውነተኛ ትህትና ነው።
ዱርዬዎችን በወዳጅነት ስሜት ያናግራል። አመፀኞችን አይገፋም።

ሻሸመኔ መንገድ ዳር ድንች በዳጣ ይሸጣል። ወጣቶች ተሜን ድንች እንብላ ሲሉት አብሮ ይበላል።

በጉባኤ መሐከል "ፀጉርህ አደገ" ቢሉት አይቀየምም። ሄዶ ፀጉሩን ይቆረጣል።

ሶስት አልበሞች እስኪሰራ ድረስ ከሻሸመኔ አልወጣም ነበር። "ፋሬስ ፥ ሀይል አለ እና እግዚአብሔር ይበልጣል" የሚሉ ሶስት አልበሞች ሰርቶ ሻሸመኔ ይኖር ነበር።

አድገን መንፈሳዊ የኪነጥበብ ቡድን መሰረትን። ያኔ ተሜ ተባባሪያችን ሆነ።

ከቀናት በአንዱ ኤርገዶ ጫማ ፥ አሮጌ ቲሸረት መናኛ ሱሪ ለብሰን ወደ ቤቱ ሄድን። በር ስናንኳኳ ከፈተልን። በቤቱ ሳሎን አስተናደን። የምንፈልገውን ጠየቀን። ትንሽ ብር እንፈልጋለን አልነው። ከፈለግነው በላይ ሰጠን። እየሳቀ "ሀብታም ስትሆኑ አንድ በአንድ ምሳ ትጋብዙኛላችሁ" አለን። ተስማምተን ተለያየን። ስልክ ቁጥሩን ሰጥቶን "ስትፈልጉኝ ደውሉልኝ። ባስፈልግኳችሁ ጊዜ ብታዙኝ እታዘዛለሁ" አለን።

እሱን ለማዘዝ እኛ ማን ነን?

ከሻሸመኔ ወጥቶ ወደ አሜሪካ የሚያቀናበት ጊዜ ደረሰ። ያን ቀን በእያንዳንዱ ሰው ውስጥ የነበረው ሃዘን ጥልቅ ነበር።

ህፃናት በልጆች ትምህርት ጊዜ እየተገኘ ይጎበኛቸዋልና አዘኑ። ወጣቶች በሚፈልጉት ጊዜ ሁሉ ይተባበራቸዋልና አዘኑ። ታላላቆች አክባሪያቸው እና ታዛዣቸው ነውና አዘኑ።

ተመስገን ማርቆስ ትሁት ሰው ነው። የቤተክርስቲያን መሪዎችን በክፉ አንስቶ አያውቅም። ከትህትና ጎድሎ አያውቅም። ታዛዥ ሰው ነው።

ብዙ ተወዳጅ መዝሙሮች አሉት።

"ገና ነው ገና ገና"
"ደሙ ሀይል ጉልበቴ"
"እግዚአብሔር ይበልጣል"
"ዛሬም ሀይለኛ ነው"
"የኪደን ልጅ"
"ዋጋ ሚጠይቅ ነው ክርስትና"
"በጨነቀኝ ጊዜ ፀሎቴን"
"ነጋ ለሊቱ ነጋ"
ወ ዘ ተ

የሻሸመኔ ሰዎች ተመስገንን በመዝሙሮቹ ብቻ ሳይሆን በማይለወጥ ትህትናው እና ሰው አክባሪነቱ ያውቁታል። ለቤተክርስቲያን ያለው ታዛዥነት ሁሌም የሚታወስ ነው። ለታናናሾቹ አረአያ ነው።

ተመስገን ማርቆስ❤
ተስፋኣብ ተሾመ✍️

ወዳገለገለችው ጌታ ወደ አባቷ ሄዳለች 🥺 ለመላው ቤተሰብ እና በእሷ ህክምና በብዙ የተሯሯጣቹ ወዳጆቼ እግዚአብሔር ያበርታቹ!በኢየሱስ የሚያምን ቢሞት እንኳን ህያው ነውና 🙏🏾😭
02/06/2025

ወዳገለገለችው ጌታ ወደ አባቷ ሄዳለች 🥺

ለመላው ቤተሰብ እና በእሷ ህክምና በብዙ የተሯሯጣቹ ወዳጆቼ እግዚአብሔር ያበርታቹ!

በኢየሱስ የሚያምን ቢሞት እንኳን ህያው ነውና 🙏🏾😭

23/03/2025

Tekeste Getnet || እንዳንተ ያለ ከቶ የለምና...

 #አስቸኳይ በጅማ ዞን ሰጠማ ወረዳ ጋትራ ከተማ ሐሙስ በ04/07/2017 ከሌሊቱ 9:00 ሰዓት ጥላችን አንግበው በተደራጁ ቡድኖች የኢትዮጵያ ወንጌላዊውት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ምዕመ...
15/03/2025

#አስቸኳይ

በጅማ ዞን ሰጠማ ወረዳ ጋትራ ከተማ ሐሙስ በ04/07/2017 ከሌሊቱ 9:00 ሰዓት ጥላችን አንግበው በተደራጁ ቡድኖች የኢትዮጵያ ወንጌላዊውት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ምዕመናን እና በንብረቶቻቸው እንዲሁም በቤተ ክርስቲያኒቱ የማምለኪ አዳራሽ ላይ አሰቃቂ ጥቃት ተፈፅሟል።

ጥቃቱን አስመልክቶ የኦሮሚያ ክልል መንግሥት አስተዳደርና ፀጥታ ቢሮ፣ የጅማ ዞን እና የጋትራ ወረዳ የተፈፀመውን ህገ ወጥ ተግባር ተጣርቶ አፈጣኝ ምላሽ እንዲሰጥ የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ጥሪ አቅርባለች።

ከጉዳዩም ጋር ጥብቅ ፀሎት እንዲደረግ ቤተ ክርስቲያን ጥሪዋን አቅርባለች።

የደብዳቤውም ዝርዝር ሀሳብ ከዚህ በታች እንደሚከተለው ቀርቧል።

* * * * * * * * * *

የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ
ማህበራነ ምዕመናንና ምዕመናን በሙሉ፡፡

የእግዚአብሔር ጸጋና ሠላም ይብዛላችሁ፡፡

ሰሞኑን በጅማ ዞን፤ ሰጠማ ወረዳ ጋትራ ከተማ ባለው ማህበረ ምዕመናችንና በምዕመናኑ ላይ የደረሰውን ጉዳት አስመልክቶ ጉዳዩ ለሚመለከታቸው አካላት ከታች በተመለከተው መሠረት ጥያቄ ቀርቧል፡፡ ይህንና ከዚህ ጋር ተያይዘው ባሉት ጉዳዮች ላይ ብርቱ ጸሎት እንዲደረግ እንጠይቃለን፡፡

የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ በመላ ሀገሪቱ በሰላም ግንባታ፣ በተለያዩ በልማት እና የማህበራዊ አገልግሎት ስራዎችን ስትሰራ ቆይታለች ለወደፊትም አጠናክራ ትቀጥላለች። የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ከሌሎች የሀይማኖት ድርጅቶች ጋር በመሆን ለሀገር በሚጠቅሙ የተለያዩ ጉዳዮች ላይ ትልቅ ሚና እየተጫወተችም ትገኛለች።

ነገር ግን ከዚህ በተቃራኒ ሐሙስ 04/07/2017 ከሌሊቱ 9፡00 ሰዓት ላይ በጅማ ዞን በሰጠማ ወረዳ በጋቲራ ከተማ ለእምነታችን ጥላቻ ያላቸው ግለሰቦች ራሳቸውን በማደራጀት በምዕመናኖቻችን እና በንብረታቸው ላይ ዘግናኝ ድርጊትን ፈጽመዋል። በተጨማሪም ምዕመናኖቻችን የሚያመልኩበትን የጸሎት ቤት አቃጥለው ከነሙሉ ንብረት አውድመውታል። በደረሰው ጉዳት 9 አባሎቻችን በእጃቸው፣በጭንቅላታቸው፣በአንገት እና በሌሎች የሰውነት ክፍሎቻቸው ላይ በተለያዩ ስለታማ መሳሪያዎች ከባድ ጉዳት ደርሶባቸዋል። የ14 ሰዎችን ቤት ሰብረው በመግባት ንብረታቸውን ሁሉ በሙሉ አውድመዋል። በጋቲራ ከተማ የሚገኘው የምእመናን የጸሎት ቤት በእሳት ተቃጥሏል። በጸሎት ቤቱ ውስጥ ያለው ንብረት በሙሉ ወድሟል።

ይህ የለውጥ መንግስት በሀገሪቱ ውስጥ መሰረታዊ ስራዎችን እየሰራ ባለበት እና የሃይማኖት እኩልነት ተረጋግጦ ባለበት ሁኔታና ማንም ሰው የፈለገውን ማምለክ በሚችልበት በዚህ ወቅት ድርጊቱ መፈፀሙ የበለጠ አሳዝኖናል ። የእኛ እና የተጎዱ ምዕመናኖቻችን ሞራልም በእጅጉ ተነክትቷል፤ በጋቲራ ከተማ በሚገኙ ልጆች እና ሴቶች ላይ የደረሰው የስነ-ልቦና ጉዳትም እንዲሁ በቀላሉ የሚታለፍ ጉዳይ አይደለም፡፡

ለዚህ ለደረሰው አደጋ ፈጣን ምላሽ ለመስጠት በጅማ ዞን አመራር በኩል እየተደረገ ያለውን ጥረት ሁሉ እያደነቅን፣ የኦሮሚያ ብሔራዉ ክልላዊ መንግስት አስተዳደርና ፀጥታ ቢሮ ለዚህ ጉዳይ ትኩረት ሰጥቶ ጉዳዩን በቅርበት እንዲከታተል እና አፋጣኝ እርምጃ እንዲወሰድ፡

1. የአካል ጉዳት ለደረሰባቸው ምእመናን አስፈላጊው የህክምና ድጋፍ በአስቸኳይ እንዲደረግላቸው፣

2. በንብረታቸውና በመኖሪያ ቤታቸው ላይ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸው ምእመናን መኖሪያ ቤታቸው እንዲሰራና የወደሙ ንብረቶቻቸው እንዲተኩ ሊደረግ ይገባል።

3. የተፈናቀሉ ምዕመናኖቻችን ወደ ቤታቸው እንዲመለሱና ህጋዊ ከለላ እንዲደረግላቸው፣

4. የምእመናን የጸሎት ቤት በእሳት በመቃጠሉ የጸሎት ቤቱና በውሰጡ የነበሩ የወደሙ ንብረቶች በሙሉ ወደ ቦታቸው እንዲመለሱ፣

5. መንግስት ባለበት ሀገር የህግ የበላይነትንና የሃይማኖት እኩልነትን በመጣስ እነዚህን ድርጊቶችና ወንጀሎች በፈጽሙ አካላት ላይ ትምህርታዊ የሆነ ህጋዊ እርምጃ እንዲወሰድ፡፡
በአጠቃላይ ለኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት አስተዳደርና ፀጥታ ቢሮ ከላይ በተጠቀሱት ጉዳዮች በአፋጣኝ አጣርቶ በተፈፀመ ህገወጥ ድርጊቶች ላይ አስፈላጊና አስተማሪ እርምጃ እንዲወስድ በትህትና እንጠይቃለን። ለሚደረግልን ድጋፍ እና ህጋዊ እርምጃ ምስጋናችን ከፍ ያለ ነው።
ከሰላምታ ጋር፡፡

ግልባጭ፡

- ለኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት አስተዳደርና ጸጥታ ቢሮ
ፊንፊኔ

- ለጅማ ዞን አስተዳደር
ጅማ

ወጣት ሆይ ያሰብኩት ሁሉም አልተሳካም! ብቸኛ ነኝ!  ለማንም ለምንም አልጠቅምም አትበል:: እግዚአብሔር የፈጠረህ  ክቡር እና ለአካሉ አስፈላጊ ስለሆንክ ነው:: ለምንም ነገር ለአንተ የረፈደ...
13/03/2025

ወጣት ሆይ ያሰብኩት ሁሉም አልተሳካም! ብቸኛ ነኝ! ለማንም ለምንም አልጠቅምም አትበል:: እግዚአብሔር የፈጠረህ ክቡር እና ለአካሉ አስፈላጊ ስለሆንክ ነው:: ለምንም ነገር ለአንተ የረፈደህ መሰለህ እንጂ የእሱ ሃሳብ እና እቅድ በጊዜው ውብ ሆኖ ሰምሮልህ ታያለህ:: እየተቸገርክም ቢሆን ጠብቀው!

ት.ኢሳ 40:31 እግዚአብሔርን በመተማመን የሚጠባበቁ ግን ኃይላቸውን ያድሳሉ፤ እንደ ንስር በክንፍ ይወጣሉ፤ ይሮጣሉ፥ አይታክቱም፤ ይሄዳሉ፥ አይደክሙም።

ቤተክርስቲያን በዚህ ሃሳብ ለወጣቱ አፅንኦት ሰጥታ መፀለይ አለባት! ገና ስንት ነገር ማድረግ የሚችሉ ልጆች ለሰይጣን ሃሳብ በር እየከፈቱ ነው:: ይሄን የሰይጣን ስትራቴጂ እግዚአብሔር ይስበረው!

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ከቢሊ ግራሀም ኢቫንጀልስቲክ አሶሴሽን ጋር በጋራ በመሆን ያዘጋጀው ፤ " መለኮታዊ ጉብኝት ለኢትዮጵያ " የተሰኘው መረሃ ግብር  በአዲ...
08/03/2025

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ከቢሊ ግራሀም ኢቫንጀልስቲክ አሶሴሽን ጋር በጋራ በመሆን ያዘጋጀው ፤ " መለኮታዊ ጉብኝት ለኢትዮጵያ " የተሰኘው መረሃ ግብር በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ እየተካሄደ ይገኛል።

ትራምፕ ዛሬ ቆፍጠን ባለ ንግግር እንዲህ አሉ እኔ በስልጣን በምሆንበት ጊዜ ሁሉ ከአሁን ጀምሮ በአሜሪካ ላይ ሁለት አይነት ፆታ ብቻ ይኖራል ወንድ እና ሴት።ቀጥለውም ልጆቻችን ልክ እንደ ማሽ...
20/01/2025

ትራምፕ ዛሬ ቆፍጠን ባለ ንግግር እንዲህ አሉ
እኔ በስልጣን በምሆንበት ጊዜ ሁሉ ከአሁን ጀምሮ በአሜሪካ ላይ ሁለት አይነት ፆታ ብቻ ይኖራል ወንድ እና ሴት።
ቀጥለውም ልጆቻችን ልክ እንደ ማሽን ጾታቸውን የሚመርጡበት ጊዜ አብቅቷል ብለዋል።

ትክክለኛው የ ፓስተር ታምራት ሃይሌ Pastor Tamirat Haileየፌስቡክ ገፅ ከስር Mention የምናረግላቹ ሲሆን በእሱ ስም ሃሰተኛ የፌስቡክ ፔጆችን የከፈታቹ ሰዎች በጌታ ፍቅር ስሙን...
19/12/2024

ትክክለኛው የ ፓስተር ታምራት ሃይሌ Pastor Tamirat Haile
የፌስቡክ ገፅ ከስር Mention የምናረግላቹ ሲሆን በእሱ ስም ሃሰተኛ የፌስቡክ ፔጆችን የከፈታቹ ሰዎች በጌታ ፍቅር ስሙን እንድትቀይሩ ወይም እንድታጠፉ እንላለን:: በውሸት የሚመጣ ማንኛውም ነገር መልሶ እራስን ስለሚጎዳ...

ትክክለኛው ገፅ ከስር ያስቀመጥንላቹ ወይም mention ላይ ያረግነው ስለሆነ መልዕክቱን ለሌሎችም እንዲደርስ በማድረግ በየጊዜው የምለቀቁትን ትምህርቶች,ዝማሬዎች እና ሌሎችንም ይከታተሉ:: 👇👇
https://www.facebook.com/share/19crcv2fna/?mibextid=LQQJ4d

በዚህ ዘመን በኖሩና ደግመን ደጋግመን በሰማናቸው/በተባረክንባቸው ብዬ ከተመኘኋቸው ዘማሪዎች መካከል ለእኔ ግንባር ቀደሙ ነው። ዘማሪ ታደሰ እሸቴ።ለመዝሙሮቹ የተጋነነ ትልቅ ፍቅር አለኝ። ደግ...
18/12/2024

በዚህ ዘመን በኖሩና ደግመን ደጋግመን በሰማናቸው/በተባረክንባቸው ብዬ ከተመኘኋቸው ዘማሪዎች መካከል ለእኔ ግንባር ቀደሙ ነው። ዘማሪ ታደሰ እሸቴ።
ለመዝሙሮቹ የተጋነነ ትልቅ ፍቅር አለኝ። ደግሜ ደጋግሜ ብሰማቸው አልጠግባቸውም። የዘመራቸው ዝማሬዎች አድማጭን ለፀሎት እና አምልኮ ከመጋበዛቸውም ባለፈ ለእግዚአብሔር ቃል የነበረውን ቅርበት የሚመሠክሩም ናቸው። ብዙ ጊዜ በጉባኤ የዝማሬ አምልኮ ላይ የዝማሬ አምልኮ መሪዎች/ዘማሪያን የእርሱን ዝማሬዎች ይዘምራሉ/ያዘምሩንማል። አብዛኛው ሠው የማን ዝማሬዎች እንደሆኑ ግን አያውቃቸውም።
ብዙዎቹ ዝማሬዎቹ በጉባኤ የሚዘመሩ ሳይሆኑ በግል ጊዜ ወስደን የምናደምጣቸው አይነት መዝሙሮች ናቸው። ለጥሞና የሚጋብዙ። እርጋታው እና የአዘማመር ስታይሉ በጣም ደስስስ የሚል ለጆሮ የሚመች አይነት ነው።

ለምሳሌ:-ከዝማሬዎቹ መካከል
🎸 አትቸኩልም አንተ ደግሞም አትዘገይም
🎸 የእግዚ/ር ምህረቱ ብዙ ደካሞችን ማገዙ
🎸 ርኆቦት 2× እግዚ/ር አስፍቶልኛል
🎸 መሸሸጊያ ዋሻ2× መከታ ጋሻችን 2×
🎸 ጊዜ ማይለውጥህ የኔ ጌታ
🎸 ከባርነት ቀንበር ያወጣኸኝ
🎸 አቤኔዘር 2× እስከ ዛሬ ድረስ እግዚ/ር ረድቶናል
🎸 እግዚአብሔርን ጠብቄው አላፈርኩኝም
🎸 መፈታቴን አውጃለሁ ለጠላቴም እነግረዋለሁ
🎸 በለቅሶ ዘርን ዘርተን ነበረ በደስታ አጭደናል
🎸 እግዚ/ር ብርሃኔና መድኃኒቴ ነው

የማስታውሳቸው ናቸው።

በተለይ የጊታር🎸 ዝማሬዎቹ🎤😮!!! 😭🙏🙏

ዛሬ በሕይወት በመካከላችን ባይኖርም ዝማሬዎቹ ግን አሁንም ትውልድ የሚፅናናባቸው እና የሚታነፅባቸው ናቸው።

እንድታደምጧቸው ጋበዝኳችሁ❤🙏 ብሩካን ናችሁ
............✍️ ምስጋና ዮናስ..............

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Shalom Tube ሻሎም-ቲዩብ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Shalom Tube ሻሎም-ቲዩብ:

Share