Shalom Tube ሻሎም-ቲዩብ

Shalom Tube ሻሎም-ቲዩብ የሻሎም ቲዩብ ቤተሰብ በመሆን አዳዲስ የሚወጡ እና የቆዩ መልዕክቶችን,መዝሙሮችን, መረጃዎችን ይከታተሉ::

መጽሐፍ ቅዱስን ወደ ኦሮምኛ የተረጎመችዉ አስቴር ጋኖ ‼️መጽሐፍ ቅዱስን ወደ ኦሮምኛ በመተርጎም ላይ ከፍተኛ አስተዋጽዎ ያደረገች፤ የኦሮምኛ ስነ ጽሑፍና ስነ ቃል ላይ አሻራዋን ጥላ ያለፈችዉ...
07/08/2025

መጽሐፍ ቅዱስን ወደ ኦሮምኛ የተረጎመችዉ አስቴር ጋኖ ‼️

መጽሐፍ ቅዱስን ወደ ኦሮምኛ በመተርጎም ላይ ከፍተኛ አስተዋጽዎ ያደረገች፤ የኦሮምኛ ስነ ጽሑፍና ስነ ቃል ላይ አሻራዋን ጥላ ያለፈችዉ ኢትዮጵያዊ አስቴር ጋኖ በ1872 በኢሉባቦር ግዛት ተወልዳ በ1962 ዓ.ም ነቀምቴ ውስጥ ከዚህ አለም በሞት የተለየች ኢትዮጵያዊት ስትሆን ስሟ ከሚጠራበት ስራዎች መካከል የሚጠቀሰው ከአነሲሞስ ነሲብ ጋር መጽሐፍ ቅዱስን ወደኦሮምኛ መተርጎሟ ነው።

ገና በለጋ እድሜዋ በሊሙ ኢናሪያ ባሪያ ፈንጋዮች ተይዛ በሽያጭ ለባርነት ወደ አረብ ሀገር በመወሰድ ላይ እያለች ይዟት ይነጉድ የነበረው ጀልባ በጣልያን መርከበኞች በቁጥጥር ስር በመዋሉ ከባርነት ተርፋ እምኩሉ (ኤርትራ ውስጥ) የስዊድን ሚሲዮን የሴቶች ት/ቤት በመግባት ትምህርቷን ጨርሳለች።

እንደተመረቀችም የመጀመሪያ ስራዋ የኦሮመኛ መዝገበ ቃላትን ማጠናቀር ነበር። ይህም መዝገበ ቃላት አነሲሞስ ነሲብ በ1893 አዲስ ኪዳንን በ1899 ደሞ ሙሉውን መጽሐፍ ቅዱስን ወደ ኦሮምኛ እንዲተረጉም ረድቶታል።

በ1894 ከአነሲሞስ ጋር በመሆን ‘የኦሮሞ (ለዚህ ጽሑፍ ሲባል ቃሉ ተቀይሯል) ፊደል መጽሐፍ’ የሚል መጽሐፍ አሳትማለች።

የመጽሐፉ ይዘትም፦ የእረኛ ዘፈኖች፤ የሕፃናት ዘፈኖች፤ የፍቅር ዘፈኖች፤ ምሳሌዎች፤ ተረት ተረቶች፤ እንቆቅልሾች፤ የሕፃናት ጨዋታዎች፤ የአቴቴ ዘፈኖች፤ የኦሮሞ ፀሎቶች፤ የመሳሰሉትን ያጠቃልላል።

በ1904 ከአነሲሞስ ጋር በመሆን ከእምኩሉ ወደ ወለጋ ተመለሰች። እስከ አለተ ዕረፍቷ ድረስ በነቀምቴ ከተማ ወንጌላዊት መካነ ኢየሱስ ቤተ ክርስቲያን በማገልገልና ለአካባቢዉ ነዋሪዎችም መሰረታዊ ትምህርት በመስጠት አሳልፋለች። ዘመኗን ህይወቷን ለእግዚአብሔር ስራ ሰጥታ ያገለገለችዉ አስቴር ጋኖ በ1962 ዓ.ም በነቀምቴ ከዚህ ዓለም ድካም አርፋለች።

Bible Association

ጋሽ ግርማ ሐናኖ (አሁን ፓስተር) ዛሬ በመጋቢት ተሾመዋል!! በቃለ ህይወት ቤተ ክርስቲያን ለረዥም ዘመናት ያገለገሉትን ጋሽ ግርማ ሐናኖ በኮልፌ ቃለ ህይወት ቤተክርስቲያን መሪነት ዛሬ በኤገ...
03/08/2025

ጋሽ ግርማ ሐናኖ (አሁን ፓስተር) ዛሬ በመጋቢት ተሾመዋል!!

በቃለ ህይወት ቤተ ክርስቲያን ለረዥም ዘመናት ያገለገሉትን ጋሽ ግርማ ሐናኖ በኮልፌ ቃለ ህይወት ቤተክርስቲያን መሪነት ዛሬ በኤገስት አዳራሽ በዓለ ሲመታቸው ተከናውኗል።

የመክፈቻ ንግግር በጋሽ ሽፈራው ወልደሚካኤል የተከናወነ ሲሆን ጋሽ ሽፈራው በንግግራቸው "መጋቢነት ትልቅ ሐላፊነት ነው።" ብለዋል።

በአሼ የቃለህይወት አጥቢያ የጀመሩት አገልግሎት ወደ አገር አቀፋዊነት ስላደገላቸው ወደ አዲስ አበባ በመምጣታቸው በአቃቂ ቃለ ህይወት አባልነት ለረጅም ጊዜ ያገለገሉት ጋሽ ግርማ ሀናኖ በአጥቢያ ቤ/ክርስቲያን ተከላ ፣ የመጽሀፍ ቅዱስ ትምህርት ተቋማትን በማቋቋም እና በማስተማር እንዲሁምቃሉን በሀገር ውስጥም ከሀገር ውጪም በማስተማር ከፍተኛ ሚና ተጫውተዋል። በብሄራዊ ደረጃ የኢትዮጵያ ቃለ ህይወትመጽሀፍ ቅዱስ ቢሮን መርተዋል። ዛሬ የተቀበሉት በዓለ ሲመ ት እና እውቅና ከፊት ለፊታቸው ላሉ የአገልግሎት ቀናት በጎ ተጽእኖ የሚያመጣ እንደሆነ ሙሉ እምነታቸው ነው!

በመርሐ ግብሩ ላይ ስለ ፓስተር ግርማ ከተነገረው መሐል ላለፉት 60 አመታት በላይ አገልግለዋል። በተለያዩ ቤተክርስቲያን በሰጠቻቸው ሐላፊነቶች በተለያዩ የአገሪቱ ክልሎች፣ በታማኝነትና በትጋት አገልግለዋል። በተለያዩ ስፍራ የቃለ ህይወት አጥቢያ ቤተ ክርስቲያናትን ተክለዋል።

ፓስተር ግርማ ሐናኖ የሐዋርያው ዮሐንስ ግርማና የሌሎች ስድስቱ ልጆች አባት፣ የ 17 የልጅ ልጆች አያት ናቸው።

ዛሬ በኮልፌ ቃለ ህይወት ቤተክርስቲያን በመጋቢነት ተሹመዋል። መርሐ ግብሩም በፓስተር መስፍን ሙልጌታ ተከናውኗል።

ተመስገን ማርቆስ...ዘማሪ ነው። ሻሸመኔዎች በልዩነት የምንወደው ዘማሪ ነው!ልጆች ሆነን ዘወትር ማክሰኞ ሻሸመኔ ሸዋበር  ቃለህይወት ቤተክርስቲያን መሄድ ያስደስተን ነበር። ብዙ ምክኒያቶች አ...
21/06/2025

ተመስገን ማርቆስ...

ዘማሪ ነው። ሻሸመኔዎች በልዩነት የምንወደው ዘማሪ ነው!

ልጆች ሆነን ዘወትር ማክሰኞ ሻሸመኔ ሸዋበር ቃለህይወት ቤተክርስቲያን መሄድ ያስደስተን ነበር። ብዙ ምክኒያቶች አሉን። እኔ በግሌ ቃለህይወት የመሄጃ ምክኒያቴ ወንጌል አልነበረም። ሐቅ መናገር ይኖርብኛል። ስብከቱን የምሰማበት ብስለት የለኝም። ቸርች የምሄደው ተመስገን ማርቆስን እና ፓስተር ጌቱ ዱሬሳን ለማየት ነው። ስለ ፓስተር ጌቱ ሌላ ጊዜ እፅፋለሁ።

ተመስገን ማርቆስ ሲዘምር ደስ ይላል። ነገረ ስራው ሁሉ በትህትና የተሞላ ነው። ሁላችንም እንወደዋለን። እንደምንወደው ያውቃል። ሰዎች ስለሚወዱት አይኮፈስም።

የመጀመሪያ የመዝሙር አልበሙን 96 አ.ም ክረምት ላይ አወጣ። የአልበሙ ርዕስ ፋሬስ ይላል። የተወሰንን ልጆች ቅፅል ስሙን ፋሬስ አልነው። በሳይክል ወደ ቤት ስሄድ እየተጫጫህን "ተሜ" እንለዋለን። ከሳይክል ወርዶ ያቅፈናል። በቁም ነገር ቆሞ ያናግረናል።

ታላላቆቹን ያከብራል። የሚገርመኝ ለህፃናትም ለአባቶችም እኩል አክብሮት ነበረው። የአስር አመት ልጅ መንገድ ላይ ቢያስቆመው በትህትና ያናግረዋል። ትህትና ሲባል የማስመሰል ትህትና ሳይሆን እውነተኛ ትህትና ነው።
ዱርዬዎችን በወዳጅነት ስሜት ያናግራል። አመፀኞችን አይገፋም።

ሻሸመኔ መንገድ ዳር ድንች በዳጣ ይሸጣል። ወጣቶች ተሜን ድንች እንብላ ሲሉት አብሮ ይበላል።

በጉባኤ መሐከል "ፀጉርህ አደገ" ቢሉት አይቀየምም። ሄዶ ፀጉሩን ይቆረጣል።

ሶስት አልበሞች እስኪሰራ ድረስ ከሻሸመኔ አልወጣም ነበር። "ፋሬስ ፥ ሀይል አለ እና እግዚአብሔር ይበልጣል" የሚሉ ሶስት አልበሞች ሰርቶ ሻሸመኔ ይኖር ነበር።

አድገን መንፈሳዊ የኪነጥበብ ቡድን መሰረትን። ያኔ ተሜ ተባባሪያችን ሆነ።

ከቀናት በአንዱ ኤርገዶ ጫማ ፥ አሮጌ ቲሸረት መናኛ ሱሪ ለብሰን ወደ ቤቱ ሄድን። በር ስናንኳኳ ከፈተልን። በቤቱ ሳሎን አስተናደን። የምንፈልገውን ጠየቀን። ትንሽ ብር እንፈልጋለን አልነው። ከፈለግነው በላይ ሰጠን። እየሳቀ "ሀብታም ስትሆኑ አንድ በአንድ ምሳ ትጋብዙኛላችሁ" አለን። ተስማምተን ተለያየን። ስልክ ቁጥሩን ሰጥቶን "ስትፈልጉኝ ደውሉልኝ። ባስፈልግኳችሁ ጊዜ ብታዙኝ እታዘዛለሁ" አለን።

እሱን ለማዘዝ እኛ ማን ነን?

ከሻሸመኔ ወጥቶ ወደ አሜሪካ የሚያቀናበት ጊዜ ደረሰ። ያን ቀን በእያንዳንዱ ሰው ውስጥ የነበረው ሃዘን ጥልቅ ነበር።

ህፃናት በልጆች ትምህርት ጊዜ እየተገኘ ይጎበኛቸዋልና አዘኑ። ወጣቶች በሚፈልጉት ጊዜ ሁሉ ይተባበራቸዋልና አዘኑ። ታላላቆች አክባሪያቸው እና ታዛዣቸው ነውና አዘኑ።

ተመስገን ማርቆስ ትሁት ሰው ነው። የቤተክርስቲያን መሪዎችን በክፉ አንስቶ አያውቅም። ከትህትና ጎድሎ አያውቅም። ታዛዥ ሰው ነው።

ብዙ ተወዳጅ መዝሙሮች አሉት።

"ገና ነው ገና ገና"
"ደሙ ሀይል ጉልበቴ"
"እግዚአብሔር ይበልጣል"
"ዛሬም ሀይለኛ ነው"
"የኪደን ልጅ"
"ዋጋ ሚጠይቅ ነው ክርስትና"
"በጨነቀኝ ጊዜ ፀሎቴን"
"ነጋ ለሊቱ ነጋ"
ወ ዘ ተ

የሻሸመኔ ሰዎች ተመስገንን በመዝሙሮቹ ብቻ ሳይሆን በማይለወጥ ትህትናው እና ሰው አክባሪነቱ ያውቁታል። ለቤተክርስቲያን ያለው ታዛዥነት ሁሌም የሚታወስ ነው። ለታናናሾቹ አረአያ ነው።

ተመስገን ማርቆስ❤
ተስፋኣብ ተሾመ✍️

ወዳገለገለችው ጌታ ወደ አባቷ ሄዳለች 🥺 ለመላው ቤተሰብ እና በእሷ ህክምና በብዙ የተሯሯጣቹ ወዳጆቼ እግዚአብሔር ያበርታቹ!በኢየሱስ የሚያምን ቢሞት እንኳን ህያው ነውና 🙏🏾😭
02/06/2025

ወዳገለገለችው ጌታ ወደ አባቷ ሄዳለች 🥺

ለመላው ቤተሰብ እና በእሷ ህክምና በብዙ የተሯሯጣቹ ወዳጆቼ እግዚአብሔር ያበርታቹ!

በኢየሱስ የሚያምን ቢሞት እንኳን ህያው ነውና 🙏🏾😭

23/03/2025

Tekeste Getnet || እንዳንተ ያለ ከቶ የለምና...

 #አስቸኳይ በጅማ ዞን ሰጠማ ወረዳ ጋትራ ከተማ ሐሙስ በ04/07/2017 ከሌሊቱ 9:00 ሰዓት ጥላችን አንግበው በተደራጁ ቡድኖች የኢትዮጵያ ወንጌላዊውት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ምዕመ...
15/03/2025

#አስቸኳይ

በጅማ ዞን ሰጠማ ወረዳ ጋትራ ከተማ ሐሙስ በ04/07/2017 ከሌሊቱ 9:00 ሰዓት ጥላችን አንግበው በተደራጁ ቡድኖች የኢትዮጵያ ወንጌላዊውት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ምዕመናን እና በንብረቶቻቸው እንዲሁም በቤተ ክርስቲያኒቱ የማምለኪ አዳራሽ ላይ አሰቃቂ ጥቃት ተፈፅሟል።

ጥቃቱን አስመልክቶ የኦሮሚያ ክልል መንግሥት አስተዳደርና ፀጥታ ቢሮ፣ የጅማ ዞን እና የጋትራ ወረዳ የተፈፀመውን ህገ ወጥ ተግባር ተጣርቶ አፈጣኝ ምላሽ እንዲሰጥ የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ጥሪ አቅርባለች።

ከጉዳዩም ጋር ጥብቅ ፀሎት እንዲደረግ ቤተ ክርስቲያን ጥሪዋን አቅርባለች።

የደብዳቤውም ዝርዝር ሀሳብ ከዚህ በታች እንደሚከተለው ቀርቧል።

* * * * * * * * * *

የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ
ማህበራነ ምዕመናንና ምዕመናን በሙሉ፡፡

የእግዚአብሔር ጸጋና ሠላም ይብዛላችሁ፡፡

ሰሞኑን በጅማ ዞን፤ ሰጠማ ወረዳ ጋትራ ከተማ ባለው ማህበረ ምዕመናችንና በምዕመናኑ ላይ የደረሰውን ጉዳት አስመልክቶ ጉዳዩ ለሚመለከታቸው አካላት ከታች በተመለከተው መሠረት ጥያቄ ቀርቧል፡፡ ይህንና ከዚህ ጋር ተያይዘው ባሉት ጉዳዮች ላይ ብርቱ ጸሎት እንዲደረግ እንጠይቃለን፡፡

የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ በመላ ሀገሪቱ በሰላም ግንባታ፣ በተለያዩ በልማት እና የማህበራዊ አገልግሎት ስራዎችን ስትሰራ ቆይታለች ለወደፊትም አጠናክራ ትቀጥላለች። የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ከሌሎች የሀይማኖት ድርጅቶች ጋር በመሆን ለሀገር በሚጠቅሙ የተለያዩ ጉዳዮች ላይ ትልቅ ሚና እየተጫወተችም ትገኛለች።

ነገር ግን ከዚህ በተቃራኒ ሐሙስ 04/07/2017 ከሌሊቱ 9፡00 ሰዓት ላይ በጅማ ዞን በሰጠማ ወረዳ በጋቲራ ከተማ ለእምነታችን ጥላቻ ያላቸው ግለሰቦች ራሳቸውን በማደራጀት በምዕመናኖቻችን እና በንብረታቸው ላይ ዘግናኝ ድርጊትን ፈጽመዋል። በተጨማሪም ምዕመናኖቻችን የሚያመልኩበትን የጸሎት ቤት አቃጥለው ከነሙሉ ንብረት አውድመውታል። በደረሰው ጉዳት 9 አባሎቻችን በእጃቸው፣በጭንቅላታቸው፣በአንገት እና በሌሎች የሰውነት ክፍሎቻቸው ላይ በተለያዩ ስለታማ መሳሪያዎች ከባድ ጉዳት ደርሶባቸዋል። የ14 ሰዎችን ቤት ሰብረው በመግባት ንብረታቸውን ሁሉ በሙሉ አውድመዋል። በጋቲራ ከተማ የሚገኘው የምእመናን የጸሎት ቤት በእሳት ተቃጥሏል። በጸሎት ቤቱ ውስጥ ያለው ንብረት በሙሉ ወድሟል።

ይህ የለውጥ መንግስት በሀገሪቱ ውስጥ መሰረታዊ ስራዎችን እየሰራ ባለበት እና የሃይማኖት እኩልነት ተረጋግጦ ባለበት ሁኔታና ማንም ሰው የፈለገውን ማምለክ በሚችልበት በዚህ ወቅት ድርጊቱ መፈፀሙ የበለጠ አሳዝኖናል ። የእኛ እና የተጎዱ ምዕመናኖቻችን ሞራልም በእጅጉ ተነክትቷል፤ በጋቲራ ከተማ በሚገኙ ልጆች እና ሴቶች ላይ የደረሰው የስነ-ልቦና ጉዳትም እንዲሁ በቀላሉ የሚታለፍ ጉዳይ አይደለም፡፡

ለዚህ ለደረሰው አደጋ ፈጣን ምላሽ ለመስጠት በጅማ ዞን አመራር በኩል እየተደረገ ያለውን ጥረት ሁሉ እያደነቅን፣ የኦሮሚያ ብሔራዉ ክልላዊ መንግስት አስተዳደርና ፀጥታ ቢሮ ለዚህ ጉዳይ ትኩረት ሰጥቶ ጉዳዩን በቅርበት እንዲከታተል እና አፋጣኝ እርምጃ እንዲወሰድ፡

1. የአካል ጉዳት ለደረሰባቸው ምእመናን አስፈላጊው የህክምና ድጋፍ በአስቸኳይ እንዲደረግላቸው፣

2. በንብረታቸውና በመኖሪያ ቤታቸው ላይ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸው ምእመናን መኖሪያ ቤታቸው እንዲሰራና የወደሙ ንብረቶቻቸው እንዲተኩ ሊደረግ ይገባል።

3. የተፈናቀሉ ምዕመናኖቻችን ወደ ቤታቸው እንዲመለሱና ህጋዊ ከለላ እንዲደረግላቸው፣

4. የምእመናን የጸሎት ቤት በእሳት በመቃጠሉ የጸሎት ቤቱና በውሰጡ የነበሩ የወደሙ ንብረቶች በሙሉ ወደ ቦታቸው እንዲመለሱ፣

5. መንግስት ባለበት ሀገር የህግ የበላይነትንና የሃይማኖት እኩልነትን በመጣስ እነዚህን ድርጊቶችና ወንጀሎች በፈጽሙ አካላት ላይ ትምህርታዊ የሆነ ህጋዊ እርምጃ እንዲወሰድ፡፡
በአጠቃላይ ለኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት አስተዳደርና ፀጥታ ቢሮ ከላይ በተጠቀሱት ጉዳዮች በአፋጣኝ አጣርቶ በተፈፀመ ህገወጥ ድርጊቶች ላይ አስፈላጊና አስተማሪ እርምጃ እንዲወስድ በትህትና እንጠይቃለን። ለሚደረግልን ድጋፍ እና ህጋዊ እርምጃ ምስጋናችን ከፍ ያለ ነው።
ከሰላምታ ጋር፡፡

ግልባጭ፡

- ለኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት አስተዳደርና ጸጥታ ቢሮ
ፊንፊኔ

- ለጅማ ዞን አስተዳደር
ጅማ

ወጣት ሆይ ያሰብኩት ሁሉም አልተሳካም! ብቸኛ ነኝ!  ለማንም ለምንም አልጠቅምም አትበል:: እግዚአብሔር የፈጠረህ  ክቡር እና ለአካሉ አስፈላጊ ስለሆንክ ነው:: ለምንም ነገር ለአንተ የረፈደ...
13/03/2025

ወጣት ሆይ ያሰብኩት ሁሉም አልተሳካም! ብቸኛ ነኝ! ለማንም ለምንም አልጠቅምም አትበል:: እግዚአብሔር የፈጠረህ ክቡር እና ለአካሉ አስፈላጊ ስለሆንክ ነው:: ለምንም ነገር ለአንተ የረፈደህ መሰለህ እንጂ የእሱ ሃሳብ እና እቅድ በጊዜው ውብ ሆኖ ሰምሮልህ ታያለህ:: እየተቸገርክም ቢሆን ጠብቀው!

ት.ኢሳ 40:31 እግዚአብሔርን በመተማመን የሚጠባበቁ ግን ኃይላቸውን ያድሳሉ፤ እንደ ንስር በክንፍ ይወጣሉ፤ ይሮጣሉ፥ አይታክቱም፤ ይሄዳሉ፥ አይደክሙም።

ቤተክርስቲያን በዚህ ሃሳብ ለወጣቱ አፅንኦት ሰጥታ መፀለይ አለባት! ገና ስንት ነገር ማድረግ የሚችሉ ልጆች ለሰይጣን ሃሳብ በር እየከፈቱ ነው:: ይሄን የሰይጣን ስትራቴጂ እግዚአብሔር ይስበረው!

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ከቢሊ ግራሀም ኢቫንጀልስቲክ አሶሴሽን ጋር በጋራ በመሆን ያዘጋጀው ፤ " መለኮታዊ ጉብኝት ለኢትዮጵያ " የተሰኘው መረሃ ግብር  በአዲ...
08/03/2025

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ከቢሊ ግራሀም ኢቫንጀልስቲክ አሶሴሽን ጋር በጋራ በመሆን ያዘጋጀው ፤ " መለኮታዊ ጉብኝት ለኢትዮጵያ " የተሰኘው መረሃ ግብር በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ እየተካሄደ ይገኛል።

ትራምፕ ዛሬ ቆፍጠን ባለ ንግግር እንዲህ አሉ እኔ በስልጣን በምሆንበት ጊዜ ሁሉ ከአሁን ጀምሮ በአሜሪካ ላይ ሁለት አይነት ፆታ ብቻ ይኖራል ወንድ እና ሴት።ቀጥለውም ልጆቻችን ልክ እንደ ማሽ...
20/01/2025

ትራምፕ ዛሬ ቆፍጠን ባለ ንግግር እንዲህ አሉ
እኔ በስልጣን በምሆንበት ጊዜ ሁሉ ከአሁን ጀምሮ በአሜሪካ ላይ ሁለት አይነት ፆታ ብቻ ይኖራል ወንድ እና ሴት።
ቀጥለውም ልጆቻችን ልክ እንደ ማሽን ጾታቸውን የሚመርጡበት ጊዜ አብቅቷል ብለዋል።

ትክክለኛው የ ፓስተር ታምራት ሃይሌ Pastor Tamirat Haileየፌስቡክ ገፅ ከስር Mention የምናረግላቹ ሲሆን በእሱ ስም ሃሰተኛ የፌስቡክ ፔጆችን የከፈታቹ ሰዎች በጌታ ፍቅር ስሙን...
19/12/2024

ትክክለኛው የ ፓስተር ታምራት ሃይሌ Pastor Tamirat Haile
የፌስቡክ ገፅ ከስር Mention የምናረግላቹ ሲሆን በእሱ ስም ሃሰተኛ የፌስቡክ ፔጆችን የከፈታቹ ሰዎች በጌታ ፍቅር ስሙን እንድትቀይሩ ወይም እንድታጠፉ እንላለን:: በውሸት የሚመጣ ማንኛውም ነገር መልሶ እራስን ስለሚጎዳ...

ትክክለኛው ገፅ ከስር ያስቀመጥንላቹ ወይም mention ላይ ያረግነው ስለሆነ መልዕክቱን ለሌሎችም እንዲደርስ በማድረግ በየጊዜው የምለቀቁትን ትምህርቶች,ዝማሬዎች እና ሌሎችንም ይከታተሉ:: 👇👇
https://www.facebook.com/share/19crcv2fna/?mibextid=LQQJ4d

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Shalom Tube ሻሎም-ቲዩብ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Shalom Tube ሻሎም-ቲዩብ:

Share