Wtv Xog Waran,Tilmaan iyo Maaweelo

14/10/2025
09/10/2025
07/10/2025
04/10/2025

የተፈጥሮ ጋዝ ምንድን ነው?
*************

ኢትዮጵያ በሶማሌ ክልል ካሉብ በዓመት 111 ሚሊዮን ሊትር ማምረት የሚችለውን የኦጋዴን ፈሳሽ የተፈጥሮ ጋዝ ፕሮጀክት የመጀመሪያ ዙር አስመርቃለች።

በተመሳሳይም በዓመት 1.33 ቢሊዮን ሊትር የማምረት አቅም የሚኖረውን ሁለተኛውን ዙር ፕሮጀክትም አስጀምራለች።

ለመሆኑ ይህ ፈሳሽ የተፈጥሮ ጋዝ ከሌሎች ነዳጆች በምን ይለያል?

የተፈጥሮ ጋዙ በዋናነት ሚቴን (Methane) ከተባለ የጋዝ አይነት የሚሰራ ሲሆን፤ በጣም ዝቅተኛ በሆነ የሙቀት መጠን ማቀዝቀዝን በሚያካትት ሂደት ወደ ፈሳሽነት እንደሚለወጥም ባለሙያዎች ያስረዳሉ።

የተፈጥሮ ጋዙ ከጥልቅ ጉድጓድ በሚወጣበት ጊዜ እንደ ነዳጅነት ከማገልገሉ በፊት እንዲጣራ ይደረጋል ይላሉ ባለሙያዎች።

ኢትዮጵያ ማምረት የጀመረችው የተፈጥሮ ጋዝ ለኢንዱስትሪዎች፣ ለትራንስፖርት እንዲሁም ለቤት ፍጆታ የኃይል አቅርቦት አገልግሎት መስጠት የሚችል ነው የሚሉት የዘርፉ ባለሙያና አማካሪ አዶናይ አብረሃ ናቸው፡፡

በአንድ ኪሎ ግራም የታመቀ (ኮምፕሬስድ የሆነ) የተፈጥሮ ጋዝ ለአንድ ተሽከርካሪ በአማካይ 34 ኪሎ ሜትር የሚያስጉዝ ሃይልን ይሰጣል ይላሉ።

ከዋጋው አንፃር ሲታይ ደግሞ ከአንድ ሊትር ቤንዚን ወይም ናፍጣ እጅግ ባነሳ ዋጋ በገበያው ለማግኘት ያስችላል ብለዋል፡፡

በቤንዚን እና በናፍጣ የሚሰሩ መኪናዎችን ወደ ጋዝ በመቀየር የተፈጠረውን ዕድል መጠቀም ይገባል ያሉት ባለሙያው፤ ይህም ሀገሪቱ የምታወጣውን የውጭ ምንዛሬ ማስቀረት ያስችላል ሲሉ አስረድተዋል።

ኢትዮጵያ ያስመረቀችው ፈሳሽ የተፈጥሮ ጋዝ የአካባቢን ብክለትን ከመቀነስ አንፃር ከቤንዚን እና ከናፍጣ መሰል ነዳጆች የተሻለ ውጤታማ መሆኑንም የጠቆሙት።

በሀገረ ሕንድ ከ6ሚሊዮን በላይ ተሽከርካሪዎች የተፈጥሮ ጋዝ በመጠቀም የአካባቢ ብክለትን ለመቀነስ ከፍተኛ ጥረት በማድረግ ላይ ናቸው ሲሉ ባለሙያው ይናገራሉ።

የተፈጥሮ ጋዝ በኢትዮጵያ ያለውን የበካይ ጋዝ መጠን በመቀነስ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው የገለጹት አዶናይ ቻይና፣ ብራዚል እና ህንድ የመሳሳሉ ሀገራት በስፋት ይጠቀሙበታል ብለዋል።

በዓመት 111 ሚሊዮን ሊትር የተፈጥሮ ጋዝ የማምረት አቅም ያለው የኦጋዴን ፈሳሽ የተፈጥሮ ጋዝ ፕሮጀክት ግንባታ ኢትዮጵያ የሚትከተለውን የአረንጎዴ ኢኮኖሚ ልማት በመደገፍ ትልቅ አበርክቶ እንደሚኖረው ተገልጿል።

በመሀመድ ፊጣሞ

30/09/2025
10/09/2025

Wasiirka Wasaarada Maaliyada dalkeena itoobiya, Mudane Axmed Shide, oo bulshada lawadaagay hambalyada sanadka cusub ee 2018 T.I.

**********************

"Waxaan urajaynayaa dhamaan walaalahayga itoobiya in uu sanadkan noo noqdo mid Nabad, caafimaad, Guul iyo farxad aynu wada gaadhno".

Mudane Axmed Shide, Wasiirka Wasaarada Maaliyada Itoobiya.

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Wtv posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share