Federal Public Procurement Service -PPS

Federal Public Procurement Service -PPS Perform procurement of public organization common user items and nationally strategic utilities; render efficient and effective property disposal service;

የመንግስት ግዥ አገልግሎት በሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 184/2002 ሐምሌ 2 ቀን 2002 ዓ.ም ሲቋቋም ዓላማዎቹ የመንግስት መስሪያ ቤቶች የሚጠቀሙባቸውን ተመሳሳይ ዕቃና አገልግሎቶች እንዲሁም አገራዊ ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ያላቸው እቃዎችና አገልግሎቶች ከከፍተኛ ግዥ የሚገኘውን ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ በሚያስገኝ ተመጣጣኝ ዋጋ፣ በተገቢው ጊዜና በተፈላጊው ጥራት እንዲቀርቡ ማስቻል፣በሽያጭ እንዲወገዱ ውሳኔ የተሰጠባቸውን የመንግስት መ/ቤቶች ንብረቶች በተቀላጠፈ አኳኋን በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲወገዱ ማስቻል እና ለመንግስት የልማት ድርጅቶች በዕቃና አገልግሎት ግዥ እንዲሁም በንብረት ማስወገድ ረገድ እገዛ ማድረግ ናቸው፡፡

20/10/2025

እንዲያውቁት!
የፌዴራል መንግስት ግዥ አገልግሎት አጭር የጥሪ ማዕከል 6622
ውድ የተቋማችን ተገልጋዮች እና ባለድርሻ አካላት!
የመንግስት ግዥ አገልግሎት የመንግስት ኤሌክትሮኒክ ግዥ ስርዓት (e-GP) ሲስተምን በመጠቀም ለፌዴራል ባለበጀት መ/ቤቶች እና የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች አገልግሎት የሚውሉ ሀገራዊ ስትራቴጂያዊ ጠቀሜታ ያላቸውን ዕቃዎች እና የጋራ መጠቀሚያ ዕቃዎችን በየዓመቱ በቢሊየን ብር በማዕከል ግዥ ይፈጽማል፡፡
በሌላ በኩል ተቋማት ውሳኔ ሰጥተው የሚልኳቸውን ያገለገሉ ተሽከርካሪዎችንና ልዩ ልዩ ንብረቶችን በሽያጭ በማስወገድ ለመንግስት ከፍተኛ ገቢ ከማስገኘት በተጨማሪ ያለጥቅም ተከማችተው የነበሩ ንብረቶች የያዙትን ቦታ በማስለቀቅ የአካባቢ ብክለትን በመቀነስ እና ምቹ የሥራ አካባቢን በመፍጠር የበኩሉን አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል፡፡
በመሆኑም አገልግሎቱ በሚያከናውናቸው ስራዎች እና በሚሰጣቸው አገልግሎቶች ላይ ሃሳብ እና አስተያየት እንዲሁም ቅሬታ ለመቀበል የአገልግሎቱ አጭር የጥሪ ማዕከል የሆነው 6622 ከዛሬ ጥቅምት 10 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ስራ ላይ የዋለ መሆኑን ለመግለጽ እንወዳለን፡፡

17/10/2025
የአገልግሎቱ ሠራተኞች መንግስት ላደረገው የደመወዝ  ጭማሪ ምስጋና አቀረቡ ****************** ዜና፡ አዲስ አበባ፣ ጥቅምት  07 ቀን 2018 ዓ.ም የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደ...
17/10/2025

የአገልግሎቱ ሠራተኞች መንግስት ላደረገው የደመወዝ ጭማሪ ምስጋና አቀረቡ
******************
ዜና፡ አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 07 ቀን 2018 ዓ.ም የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ፖሊሲ ትግበራን በላቀ ደረጃ ለማስፈፀም እና የኑሮ ውድነቱ በመንግስት ሰራተኛው ላይ የሚያደርሰውን ጫና በመገንዘብ መንግስት ከመስከረም 1/2018 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ የሚሆን በሲቪል ሰርቪስ ታሪክ ከፍተኛ የሆነ የደመወዝ ጭማሪ ማድረጉ ይታወቃል፡፡ ስለሆነም መንግስት ዋጋ ከፍሎ ላደረገው የደመወዝ ጭማሪ ማመስገን ተገቢ በመሆኑ በዛሬው ዕለት መላው የአገልግሎቱ ሠራተኞች እና አመራሮች በተገኙበት በአገልግሎቱ አዳራሽ የምስጋና መርሐ ግብር ተካሂዷል፡፡
በመርሐ ግብሩ ላይ የተገኙት የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ክቡር አቶ አስማረ ይገዙ እንዳሉት መንግስት የመንግስት ሠራተኛውን የኑሮ ጫና ተረድቶ ያደረገው የደመወዝ ጭማሪ የሠራተኛውን ኑሮ ከመደጎም ባለፈ ሠራተኛው በየተሰማራበት የስራ መስክ በተረጋጋ መንፈስ ውጤታማ ስራ መስራት እንዲችል ትልቅ አስተዋጽኦ አለው በማለት ይህን ላደረገው መንግስታችን በአገልግሎቱ ሰራተኞቸ ስም ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡
በሌላ በኩል በመርሐ ግብሩ የተሳተፉ ሠራተኞችም መንግስት በአሁኑ ሰዓት ያለበትን ሁኔታ እንደሚረዱ ጠቁመው፤ የመንግስት ሠራተኛውን የኑሮ ጫና ለመቀነስ የደመወዝ ጭማሪ መደረጉ ደስታ እንደፈጠረላቸው ተናግረዋል፡፡ የተደረገው ጭማሪም ስራቸውን የበለጠ ተግተው እንዲሰሩ የሚያበረታታ መሆኑን ገልጸዋል። ለተደረገላቸው ጭማሪም መንግስትን አመስግነዋል፡፡
በመጨረሻም ዋና ዳይሬክተሩ ሁላችንም የአገልግሎቱ አመራርና ሠራተኞች ይህንን ላደረገልን መንግስት ምስጋና እያቀረብን፤ ተገልጋይን በቅንነትና በታማኝነት በማገልገል፤ በተነሳሽነት ስሜት እና በትጋት ስራዎችን በመፈፀም የተቋማችን ተልዕኮ በማሳካት የበኩላችን አስተዋጽኦ ማበርከት ይጠበቅብናል በማለት ባስተላለፉት መልዕክት የዕለቱ መርሐ ግብር ተጠናቋል፡፡

የመንግስት ግዥ አገልግሎት አመራሮችና ሠራተኞች 18ኛውን የሰንደቅ ዓላማ ቀን በዓል አከበሩ**************ዜና፣ አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 03 ቀን 2018 ዓ.ም የመንግስት ግዥ አገልግሎት...
13/10/2025

የመንግስት ግዥ አገልግሎት አመራሮችና ሠራተኞች 18ኛውን የሰንደቅ ዓላማ ቀን በዓል አከበሩ
**************
ዜና፣ አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 03 ቀን 2018 ዓ.ም የመንግስት ግዥ አገልግሎት አመራሮችና ሠራተኞች 18ኛውን የሰንደቅ ዓላማ ቀን በዓል ከፕላንና ልማት ሚኒስቴርና ከመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን አመራርና ሠራተኞች ጋር በጋራ በመሆን “ሠንደቅ ዓላማችን ለኢትዮጵያ ታላቅ የከፍታ ዘመን ብስራት፣ለብሔራዊ አንድነታችን፣ለሉዓላዊነታችን እና ለኢትዮጵያ ህዳሴ!” በሚል መሪ ቃል በደማቅ ሁኔታ አክብረዋል፡፡
በዕለቱም የፕላንና ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር ጽ/ቤት ኃላፊና ከፍተኛ አማካሪ ወ/ሮ ሐና አበበ፣ የመንግስት ግዥ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ክቡር አቶ አስማረ ይገዙ፣ የግዥና ውል አስተዳደር ዘርፍ ም/ዋና ዳይሬክተር ክቡር አቶ ክፍሌ ገ/ማርያምን ጨምሮ የሶስቱም ተቋማት የሥራ ኃላፊዎች እና ሠራተኞች ተገኝተዋል፡፡
ዕለቱን በማስመልከትም ሰንደቅ ዓላማችን የሀገራችን ክብርና ነጻነት እንዲሁም የኅብረ ብሔራዊ አንድነታችን መገለጫ እና የአብሮነታችንና የሉዓላዊነታችን ዓርማ መሆኑን የሚያንፀባርቅ መልዕክት የተላለፈ ሲሆን፤ ብሔራዊ የሰንደቅ ዓላማ መዝሙር በመዘመር እና የሰንደቅ ዓላማ መስቀል ስነስርዓት በማካሄድ ፕሮግራሙ ተጠናቋል፡፡

አስደሳች የውጤት ዜና!  ገንዘብ ሚኒስቴር የምስጋናና ዕውቅና ደብዳቤ ለአገልግሎቱ ሰጠ************************ ዜና፣ አዲስ አበባ፣ መስከረም 26 ቀን 2018 ዓ.ም የመንግስት ...
06/10/2025

አስደሳች የውጤት ዜና!
ገንዘብ ሚኒስቴር የምስጋናና ዕውቅና ደብዳቤ ለአገልግሎቱ ሰጠ
************************
ዜና፣ አዲስ አበባ፣ መስከረም 26 ቀን 2018 ዓ.ም የመንግስት ግዥ አገልግሎት የ2017 በጀት ዓመት የሂሳብ ሪፖርቱን ከተሰጠው የጊዜ ገድብ በፊት በጥራት አጠናቆ ቀድሞ በመዝጋት ለገንዘብ ሚኒስቴር በማቅረቡ በዛሬው ዕለት ከገንዘብ ሚኒስቴር የምስጋናና ዕውቅና ደብዳቤ ተሰጥቶታል፡፡
በሚኒስቴር መ/ቤቱ የተሰጠው ይህ የምስጋናና ዕውቅና ደብዳቤ ለሌሎች ተቋማት ጥሩ ተሞክሮ የሚሆን በቀጣይ የአገልግሎቱ አመራሮችና መላው ሰራተኞች ለበለጠ ውጤት በትጋትና በቁርጠኝት እንዲሰሩ የሚያነሳሳ ተግባር ነው በማለት የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ክቡር አቶ አስማረ ይገዙ አድናቆታቸውን ገልጸዋል፡፡
ክቡር አቶ አስማረ አክለውም ጥሩ አፈጻጸምን መሰረት ያደረገ ምስጋናና ዕውቅና መሰጠት ተገቢ እና የሚያበረታታ መሆኑን ገልጸው፤ ይህን ላደረጉ የገንዘብ ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች ልባዊ ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡
ዋና ዳይሬክተሩ ይህ ውጤት እንዲመጣ ርብርብ ላደረጉ የአገልግሎቱ አመራሮች፣ ለስራ አመራር ዋና ስራ አስፈጻሚ፣ ለግዥና ፋይናንስ የስራ ክፍል ኃላፊና ሰራተኞች እንዲሁም ከስራው ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ላላቸው ሌሎች የስራ ክፍሎችም ምስጋና እና አድናቆታቸውን ገልጸዋል፡፡

110 ተሽከርካሪዎችን ግዥ ለመፈጸም የጨረታ ማስታወቂያ ወጣ  *********************ዜና፡ አዲስ አበባ፣ መስከረም 22 ቀን 2018 ዓ.ም የመንግስት ግዥ አገልግሎት ለኢትዮጵያ ጉም...
02/10/2025

110 ተሽከርካሪዎችን ግዥ ለመፈጸም የጨረታ ማስታወቂያ ወጣ
*********************
ዜና፡ አዲስ አበባ፣ መስከረም 22 ቀን 2018 ዓ.ም የመንግስት ግዥ አገልግሎት ለኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን አገልግሎት የሚውሉ 100 ፒክአፕ እና ከ5-7 መቀመጫ ያላቸውን 10 ስቴሽንዋገን ተሽከርካሪዎችን በመንግስት ኤሌክትሮኒክስ የግዥ ሥርዓት (e-GP system) ግዥ ለመፈጸም በ e-GP ፖርታል ላይ የጨረታ ማስታወቂያ አውጥቷል፡፡

30/09/2025

መስከረም 12 ቀን 2018 ዓ.ም የወጣ
በሽያጭ የሚወገዱ ያገለገሉ ተሽከርካሪዎች የጨረታ ማስታወቂያ
Forwarded From Ethiopian Broadcasting Corporation

25/09/2025

የጨረታ ማስታወቂያ
ያገለገሉ ተሽከርካሪዎችን በግልጽ ጨረታ ለመሸጥ የወጣ የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር PPS/VP7FBI/02/01/2018
የኢ.ፌ.ዴ.ሪ የመንግሥት ግዥ አገልግሎት ንብረትነታቸው የኢትዮጵያ ሜቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት፣ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት፣ የፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት፣ የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ፣ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር፣ የግብርና ሚኒስቴር እና የፐብሊክ ሰርቪስ ትራንስፖርት አገልግሎት ተከርካሪዎችን ባሉበት ቦታና ሁኔታ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡
በመሆኑም የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟላ ማንኛውም ተጫራች በጨረታው ላይ መወዳደር ይችላል፡፡
1. በጨረታው ላይ የሚወዳደር ማንኛውም ተጫራች ዜግነቱ ኢትዮጵያዊ መሆኑ ያለበት ሲሆን የጨረታውን ሰነድ ለመግዛት ሲመጣ ይህንኑ የሚያረጋግጥ ሰነድ ወይም መታወቂያ ማቅረብ ያስፈልጋል፡፡
2. ተጫራቾች 6 ኪሎ በሚገኘው የኢ.ፌ.ዴ.ሪ የመንግሥት ግዥ አገልግሎት ግዥና ፋይናንስ ስራ አስፈጻሚ ቢሮ በመምጣት የተሽከርካሪዎቹን ዝርዝር መረጃ፣ የተጫራቾች መመሪያ እና የዋጋ ማቅረቢያ ቅጽ የያዘ ሰነድ የማይመለስ ብር 700.00 (ሰባት መቶ ብር) በመንግሥት ግዥ አገልግሎት የንግድ ባንክ ሂሳብ ቁጥር 1000003785018 ላይ ገቢ በማድረግና ያስገቡበትን የባንክ ስሊፕ ይዘው በመቅረብ የጨረታውን ሰነድ መግዛት ይችላሉ፡፡
3. ተጫራቾች የጨረታውን ሰነድ ከገዙ በኋላ ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ዘወትር በሥራ ቀናት ከጠዋቱ 3፡00 እስከ 10፡00 ሰዓት ባለው ጊዜ ውስጥ ተሽከርካሪዎቹን ከላይ በተጠቀሱት መ/ቤቶች በአካል በመሄድ መመልከት ይችላሉ፡፡
4. ተጫራቾች የሚገዙትን ተሸከርካሪ ለእያንዳንዱ የጨረታ መነሻ ዋጋ 5% (አምስት በመቶ) የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ (CPO) ከጨረታ ሰነዱ ጋር በማያያዝ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ከጨረታው ሳጥን መዝጊያ ሰዓት በፊት ማስገባት አለባቸው፡፡ የሚዘጋጀው የጨረታ ማስከበሪያ ሲፒኦ ከአዲስ አበባ ከተማ ውጭ ከሆነ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅርንጫፎች ብቻ መሆን ይኖርበታል፡፡
5. የጨረታው የመገምገሚያ መስፈርት ዋጋ፣ የተሟላ የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ሲፒኦ (CPO) እንዲሁም በሰነዱ የተገለጹትን አሟልቶ መገኘት ይሆናል፡፡ ይሁንና የተሽከርካሪውን የመነሻ ዋጋ 5% (አምስት በመቶ) ያላስያዘ እንዲሁም በሠነዱ የተቀመጡ ሌሎች ነጥቦችን ያላሟላ ተጫራች ከጨረታው ውድቅ ይደረጋል፡፡
6. ተሽከርካሪው ቀደም ሲል ያልተከፈለ የቦሎ ዕዳ ካለበት በባለንብረቱ መሥሪያ ቤት የሚሸፍን ሲሆን የጉምሩክ ቀረጥ ግብር እዳ ካለበት፣ የስም ማዛወሪያ፣ የትራንዚት እና ሌሎች ወጪዎች ግን በገዥው የሚሸፈን ይሆናል፡፡
7. የጨረታ ማስገቢያ ሳጥኑ ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ20ኛው ቀን ከጠዋቱ 4:00 ሰዓት ላይ ተዘግቶ በዚያኑ ቀን በ4፡15 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በመንግሥት ግዥ አገልግሎት መሰብሰቢያ አዳራሽ ይከፈታል፡፡ ነገር ግን የመክፈቻ ቀኑ የስራ ቀን ላይ ካልሆነ (ቅዳሜ ወይም እሁድ ላይ ከዋለ) ወይም በዓል ቀን ላይ ከዋለ ቀጥሎ ባለው የሥራ ቀን ላይ ይከፈታል፡፡ ሆኖም ተጫራቹ በራሱ ምርጫ ጨረታው በሚከፈትበት ጊዜ ሳይገኝ ቢቀር የጨረታውን መከፈት አያስቀረውም፡፡
8. በጨረታው አሸናፊ የሆኑ ተጫራቾች አሸናፊነታቸው በተገለፀላቸው ከ7 (ሰባት) የስራ ቀናት በኋላ ባሉት 5 (አምስት) ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ ያሸነፉበትን ዋጋ በሙሉ መክፈል ይኖርባቸዋል፡፡
9. ይሁንና ሙሉ ክፍያውን በተጠቀሰው የጊዜ ገደብ ውስጥ መክፈል ካልቻሉ ያስያዙት የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ተወርሶ ለመንግስት ገቢ ይደረጋል::
10. በጨረታው አሸናፊ የሆኑ ተጫራቾች ያሸነፉባቸውን ተሽከርካሪዎች ሙሉ ክፍያ ከፍለው እስከሚወስዱ ድረስ ለውል አተገባበር ዋስትና የሚሆን የጠቅላላ ዋጋውን 10% (አስር በመቶ) በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ (CPO) ማስያዝ አለባቸው፡፡
11. አገልግሎቱ ያወጣውን የጨረታ ሰነድ በስሙ ሳይገዛ የተወዳደረ ማንኛውም ተጫራች ከውድድሩ ውድቅ ይደረጋል፡፡
12. አሸናፊ ተጫራቾች ያሸነፉበትን ገንዘብ አጠቃለው በመክፈል ተሽከርካሪውን በ10 (አስር) ቀናት ውስጥ የማንሳት ግዴታ አለባቸው፡፡
13. አገልግሎቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው፡፡
አድራሻ፡- የኢ.ፌ.ዴ.ሪ የመንግሥት ግዥ አገልግሎት 6 ኪሎ የካቲት 12 ሰማዕታት
ሐውልት አደባባይ ፊት ለፊት
ለበለጠ መረጃ፡- በስልክ ቁጥር 0974730134 ወይም 0913785606 በመደወል መጠየቅ ይቻላል፡፡
የፌዴራል መንግስት ግዥ አገልግሎት
አዲስ አበባ

ዜና አቅርቦት **********                                                                                                     ...
16/09/2025

ዜና አቅርቦት
********** በሀገራችን የመጀመሪያ የሆኑ የኤሌክትሪክ የውሃ ቦቴ ተሽከርካሪዎች ግዥ ተፈፀመ
ዜና:አዲስ አበባ፣ መስከረም 06 ቀን 2018 ዓ.ም የመንግስት ግዥ አገልግሎት በገንዘብ ሚኒስቴር ትዕዛዝ የተለያዩ ተሽከርካሪዎችን ለፌዴራል ተቋማት እና ለመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ግዥ የሚፈጸም መሆኑ ይታወቃል፡፡
በዚህም መሰረት አገልግሎቱ በመንግስት ኤሌክትሮኒክስ የግዥ ስርዓት (e-GP) በግልፅ ጨረታ ግዥ ከፈፀመባቸው የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ውስጥ በሀገራችን የመጀመሪያ የሆኑ ከ14,000 እስከ 16,000 ሊትር ውሃ የመያዝ አቅም ያላቸው 8 የኤሌክትሪክ የውሃ ቦቴ ተሽከርካሪዎች ግዥ በመፈፀም ወደ አገር ውስጥ ገብተው በአገልግሎቱ ግቢ ደርሰዋል።
በቅርቡ በሚመለከተው ባለሙያ አስፈላጊው ፍተሻ ተደርጎ የገንዘብ ሚኒስቴር ለተቋማት በሚሰጠው ድልድል መሰረት ርክክባቸው ይፈጸማል።

Address

Addis Ababa
Addis Ababa

Telephone

0111223703

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Federal Public Procurement Service -PPS posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Federal Public Procurement Service -PPS:

Share