17/07/2025
አገልግሎቱ ያገለገሉ ተሽከርካሪዎችን እና ልዩ ልዩ ንብረቶችን በሽያጭ ሊያስወግድ ነው
***************
ዜና፡ አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 10 ቀን 2017 ዓ.ም የመንግስት ግዥ አገልግሎት የ17 መ/ቤቶች ንብረት የሆኑ ያገለለገሉ ተሽከርካሪዎችን፣ የ2 መ/ቤቶች ቁርጥራጭ ብረታብረቶችን እንዲሁም የ6 መ/ቤቶች ልዩ ልዩ ንብረቶችን ባሉበት ቦታና ሁኔታ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡
ስለሆነም ተጫራቾች ሐምሌ 7 እና 8 ቀን ቀን 2017 ዓ.ም በወጣው የአዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ የተቀመጡ ዝርዝር መስፈርቶችን በመመለከት በጨረታው ላይ መወዳደር የሚችሉ መሆኑን ያሳውቃል፡፡
የመንግሥት ግዥ አገልግሎት