Federal Public Procurement Service -PPS

Federal Public Procurement Service -PPS Perform procurement of public organization common user items and nationally strategic utilities; render efficient and effective property disposal service;

የመንግስት ግዥ አገልግሎት በሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 184/2002 ሐምሌ 2 ቀን 2002 ዓ.ም ሲቋቋም ዓላማዎቹ የመንግስት መስሪያ ቤቶች የሚጠቀሙባቸውን ተመሳሳይ ዕቃና አገልግሎቶች እንዲሁም አገራዊ ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ያላቸው እቃዎችና አገልግሎቶች ከከፍተኛ ግዥ የሚገኘውን ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ በሚያስገኝ ተመጣጣኝ ዋጋ፣ በተገቢው ጊዜና በተፈላጊው ጥራት እንዲቀርቡ ማስቻል፣በሽያጭ እንዲወገዱ ውሳኔ የተሰጠባቸውን የመንግስት መ/ቤቶች ንብረቶች በተቀላጠፈ አኳኋን በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲወገዱ ማስቻል እና ለመንግስት የልማት ድርጅቶች በዕቃና አገልግሎት ግዥ እንዲሁም በንብረት ማስወገድ ረገድ እገዛ ማድረግ ናቸው፡፡

17/07/2025

አገልግሎቱ ያገለገሉ ተሽከርካሪዎችን እና ልዩ ልዩ ንብረቶችን በሽያጭ ሊያስወግድ ነው
***************
ዜና፡ አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 10 ቀን 2017 ዓ.ም የመንግስት ግዥ አገልግሎት የ17 መ/ቤቶች ንብረት የሆኑ ያገለለገሉ ተሽከርካሪዎችን፣ የ2 መ/ቤቶች ቁርጥራጭ ብረታብረቶችን እንዲሁም የ6 መ/ቤቶች ልዩ ልዩ ንብረቶችን ባሉበት ቦታና ሁኔታ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡
ስለሆነም ተጫራቾች ሐምሌ 7 እና 8 ቀን ቀን 2017 ዓ.ም በወጣው የአዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ የተቀመጡ ዝርዝር መስፈርቶችን በመመለከት በጨረታው ላይ መወዳደር የሚችሉ መሆኑን ያሳውቃል፡፡
የመንግሥት ግዥ አገልግሎት

17/07/2025

የጨረታ ማስታወቂያ
ያገለገሉ ልዩልዩ ንብረቶች በግልጽ ጨረታ ለመሸጥ የተዘጋጀ የጨረታ ሰነድ ቁጥር PPS/NVP-6FBI/01/11/2017
የኢ.ፌ.ዴ.ሪ የመንግሥት ግዥ አገልግሎት ንብረትነታቸው የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎዩኒቨርሲቲ፣ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር፣ የአሶሳ ዩኒቨርሲ፣ የታላቁ ህዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ ፕሮጀክት ጽ/ቤት፣ እና የሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ የሆኑ የተለያዩ ንብረቶች ባሉበት ቦታና ሁኔታ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡
ስለሆነም ተጫራቾች ከዚህ በታች የተመለከቱትን መስፈርቶች በማሟላት ቀርበው መወዳደር ይችላል፡፡
1. በጨረታው ላይ የሚወዳደር ማንኛውም ተጫራች ዜግነቱ ኢትዮጵያዊ መሆኑ ያለበት ሲሆን የጨረታውን ሰነድ ለመግዛት ሲመጣ ይህንኑ የሚያረጋግጥ ሰነድ ወይም መታወቂያ ማቅረብ ያስፈልጋል፡፡
2. ተጫራቾች 6 ኪሎ በሚገኘው የኢ.ፌ.ዴ.ሪ የመንግሥት ግዥ አገልግሎት ግዥና ፋይናንስ ስራ አስፈፃሚ ቢሮ በመምጣት የንብረቶች ዝርዝር መረጃ፣ የተጫራቾች መመሪያ እና የዋጋ ማቅረቢያ ቅጽ የያዘ ሰነድ የማይመለስ ብር 500.00 (አምስት መቶ ብር) በመንግሥት ግዥ አገልግሎት የንግድ ባንክ ሂሳብ ቁጥር 1000003785018 ላይ በቴሌ ብር እና ሲቢኢ ብርን በመጠቀም የጨረታውን ሰነድ መግዛት ይችላሉ፡፡
3. ተጫራቾች የጨረታውን ሰነድ ከገዙ በኋላ ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ዘወትር በሥራ ቀናት ከጠዋቱ 3፡00 እስከ 10፡00 ሰዓት ባለው ጊዜ ውስጥ ንብረቶቹን ከላይ በተጠቀሱት መ/ቤቶች በአካል በመሄድ መመልከት ይችላሉ፡፡
4. ተጫራቾች የሚገዙትን ንብረቶች ለእያንዳንዱ የጨረታ መነሻ ዋጋ 2% (አስር በመቶ) የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ (CPO) ከጨረታ ሰነዱ ጋር በማያያዝ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ከጨረታው ሳጥን መዝጊያ ሰዓት በፊት ማስገባት አለባቸው፡፡ የሚዘጋጀው የጨረታ ማስከበሪያ ሲፒኦ ከአዲስ አበባ ከተማ ውጭ ከሆነ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅርንጫፎች ብቻ መሆን ይኖርበታል፡፡
5. የጨረታው የመገምገሚያ መስፈርት ዋጋ፣ የተሟላ የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ሲፒኦ (CPO) እንዲሁም በሰነዱ የተገለጹትን አሟልቶ መገኘት ይሆናል፡፡ ይሁንና የንብረቶቹን የመነሻ ዋጋ 2% (አስር በመቶ) ያላስያዘ እንዲሁም በሠነዱ የተቀመጡ ሌሎች ነጥቦችን ያላሟላ ተጫራች ከጨረታው ውድቅ ይደረጋል፡፡
6. የጨረታ ማስገቢያ ሳጥኑ ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ16ኛው ቀን ከጠዋቱ 4:00 ሰዓት ላይ ተዘግቶ በዚያኑ ቀን በ4፡15 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በመንግሥት ግዥ አገልግሎት መሰብሰቢያ አዳራሽ ይከፈታል፡፡ ነገር ግን የመክፈቻ ቀኑ የስራ ቀን ላይ ካልሆነ (ቅዳሜ ወይም እሁድ ላይ ከዋለ) ወይም በዓል ቀን ላይ ከዋለ ቀጥሎ ባለው የሥራ ቀን ላይ ይከፈታል፡፡ ሆኖም ተጫራቹ በራሱ ምርጫ ጨረታው በሚከፈትበት ጊዜ ሳይገኝ ቢቀር የጨረታውን መከፈት አያስቀረውም፡፡
7. በጨረታው አሸናፊ የሆኑ ተጫራቾች አሸናፊነታቸው በተገለፀላቸው ከ7 (ሰባት) የስራ ቀናት በኋላ ባሉት 5 (አምስት) ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ ያሸነፉበትን ዋጋ በሙሉ መክፈል ይኖርባቸዋል፡፡ ይሁንና ሙሉ ክፍያውን በተጠቀሰው የጊዜ ገደብ ውስጥ መክፈል ካልቻሉ ያስያዙት የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ተወርሶ ለመንግስት ገቢ ይደረጋል::
8. በጨረታው አሸናፊ የሆኑ ተጫራቾች ያሸነፉባቸውን ንብረቶች ሙሉ ክፍያ ከፍለው እስከሚወስዱ ድረስ ለውል አተገባበር ዋስትና የሚሆን የጠቅላላ ዋጋውን 2% (አስር በመቶ) በጥሬ ገንዘብ ወይም በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ (CPO) ማስያዝ አለባቸው፡፡
9. አገልግሎቱ ያወጣውን የጨረታ ሰነድ በስሙ ሳይገዛ የተወዳደረ ማንኛውም ተጫራች ከውድድሩ ውድቅ ይደረጋል፡፡
10. አሸናፊ ተጫራቾች ያሸነፉበትን ገንዘብ አጠቃለው በመክፈል ንብረቶቹን በ10 (አስር) ቀናት ውስጥ የማንሳት ግዴታ አለባቸው፡፡
11. አገልግሎቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው፡፡

አድራሻ፡- የኢ.ፌ.ዴ.ሪ የመንግሥት ግዥ አገልግሎት 6 ኪሎ የካቲት 12 ሰማዕታት
ሐውልት አደባባይ ፊት ለፊት
ለበለጠ መረጃ፡- በስልክ ቁጥር 011-122 37-08 ወይም 011-122 37 36 በመደወል መጠየቅ ይቻላል፡፡

የፌዴራል መንግስት ግዥ አገልግሎት
አዲስ አበባ

17/07/2025

የጨረታ ማስታወቂያ
ቁርጥራጭ ብረታ ብረቶችን በጨረታ ለመሸጥ የወጣ የጨረታ ሰነድ
ቁጥር PPS/NVP-2FBI/02/11/2017
የኢ.ፌ.ዴ.ሪ የመንግሥት ግዥ አገልግሎት ንብረትነታቸው የአዳማ ዩኒቨርሲቲ የውሃና ኢነርጅ ሚኒስቴር፣ የሆኑ ቁርጥራጭ ብረታ ብረቶችን ባሉበት ቦታና ሁኔታ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡
ስለሆነም ተጫራቾች ከዚህ በታች የተመለከቱትን መስፈርቶች በማሟላት ቀርበው መወዳደር ይችላሉ፡፡
1. በጨረታው ላይ የሚወዳደሩት በማዕድን ሚኒስቴር የተለዩ የብረት አቅላጭ የግል ድርጅቶች የሆኑና የጨረታውን ሰነድ ለመግዛት ሲመጡ ይህንኑ የሚያረጋግጥ ማስረጃ እና መታወቂያ ማቅረብ የሚችሉ ናቸው፡፡
2. ተጫራቾች 6 ኪሎ በሚገኘው የኢ.ፌ.ዴ.ሪ የመንግሥት ግዥ አገልግሎት ግዥና ፋይናንስ ስራ አስፈጻሚ ቢሮ በመምጣት የብረቶቹን ዝርዝር መረጃ፣ የተጫራቾች መመሪያ እና የዋጋ ማቅረቢያ ቅጽ የያዘ ሰነድ የማይመለስ ብር 500.00 (አምስት መቶ ብር) በመንግሥት ግዥ አገልግሎት የንግድ ባንክ ሂሳብ ቁጥር 1000003785018 ላይ ገቢ በማድረግና ያስገቡበትን የባንክ ስሊፕ ይዘው በመቅረብ የጨረታውን ሰነድ መግዛት ይችላሉ፡፡
3. ተጫራቾች የጨረታውን ሰነድ ከገዙ በኋላ ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ዘወትር በሥራ ቀናት ከጠዋቱ 3፡00 እስከ 10፡00 ሰዓት ባለው ጊዜ ውስጥ ብረታ ብረቶቹን ከላይ በተጠቀሱት መ/ቤቶች በአካል በመሄድ መመልከት ይችላሉ፡፡
4. ተጫራቾች ለሚወዳደሩበት ለእያንዳንዱ ቁርጥራጭ የብረት ዓይነት የጨረታ መነሻ ጠቅላላ ዋጋውን 2% (ሁለት በመቶ) ዋስትና ያላስያዘ የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ (CPO) ከጨረታ ሰነዱ ጋር በማያያዝ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ከጨረታው ሳጥን መዝጊያ ሰዓት በፊት ማስገባት አለባቸው፡፡
5. የሚዘጋጀው የጨረታ ማስከበሪያ ሲፒኦ ከአዲስ አበባ ከተማ ውጭ ከሆነ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅርንጫፎች ብቻ መሆን ይኖርበታል፡፡
6. የጨረታው መገምገሚያ መስፈርት ዋጋ፣ የተሟላ የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ሲፒኦ (CPO) እንዲሁም በሰነዱ የተገለጹትን አሟልቶ መገኘት ይሆናል፡፡ ይሁንና የብረታ ብረቶቹን ጠቅላላ ግምታዊ ዋጋ 2% (ሁለት በመቶ) ዋስትና ያላስያዘ እንዲሁም በሠነዱ የተቀመጡ ሌሎች ነጥቦችን ያላሟላ ተጫራች ከጨረታው ውድቅ ይደረጋል፡፡
7. የጨረታ ማስገቢያ ሳጥኑ ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ16ኛው ቀን ከጠዋቱ 4:00 ሰዓት ላይ ተዘግቶ በዚያኑ ቀን በ4፡15 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በመንግሥት ግዥ አገልግሎት መሰብሰቢያ አዳራሽ ይከፈታል፡፡ ነገር ግን የመክፈቻ ቀኑ የስራ ቀን ላይ ካልሆነ (ቅዳሜ ወይም እሁድ ላይ ከዋለ) ወይም በዓል ቀን ላይ ከዋለ ቀጥሎ ባለው የሥራ ቀን ላይ ይከፈታል፡፡ ሆኖም ተጫራቹ በራሱ ምርጫ ጨረታው በሚከፈትበት ጊዜ ሳይገኝ ቢቀር የጨረታውን መከፈት አያስቀረውም፡፡
8. በጨረታው አሸናፊ የሆኑ ተጫራቾች አሸናፊነታቸው በተገለፀላቸው ከ7 (ሰባት) የስራ ቀናት በኋላ ባሉት 5 (አምስት) ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ ያሸነፉበትን ዋጋ በሙሉ መክፈል ይኖርባቸዋል፡፡ ይሁንና ሙሉ ክፍያውን በተጠቀሰው የጊዜ ገደብ ውስጥ መክፈል ካልቻሉ ያስያዙት የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ተወርሶ ለመንግስት ገቢ ይደረጋል::
9. በጨረታው አሸናፊ የሆኑ ተጫራቾች ያሸነፉባቸውን ብረታ ብረቶች ሙሉ ክፍያ ከፍለው እስከሚወስዱ ድረስ ለውል አተገባበር ዋስትና የሚሆን የጠቅላላ ዋጋውን 2% (ሁለት በመቶ) በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ (CPO) ማስያዝ አለባቸው፡፡
10. ተጫራቾች ያሸነፉትን ቁርጥራጭ ብረታ ብረቶች በራሳቸው ወጪ በማጓጓዝ የሚዛንና ሌሎች ወጪዎችን በመሸፈን ብረታ ብረቱ ከሚገኝበት ስፍራ ቅርብ በሆነ ፕሪንት አውት ማውጣት በሚችል የመንግስት የምድር ሚዛን በማስመዘን ውል በፈረሙ በ10 የስራ ቀናት ውስጥ ቁርጥራጭ ብረታ ብረቱን በማንሳት ማጠናቀቅ አለባቸው፡፡ ግምታዊ መጠኑ ከፕሪንት አውት ከሚገኘው ትክክለኛ የብረቱ መጠን ጋር የሚኖረው ልዩነት ታስቦ አሸናፊው ተጫራች ተጨማሪ ክፍያ የሚኖርበት ከሆነ የውል ጊዜው ከመጠናቀቁ በፊት ልዩነት የሚኖረውን ሂሳብ መክፈል ያለበት ሲሆን በትርፍነት የሰጠው ተመላሽ የሚደረግለት ገንዘብ ካለም በአገልግሎቱ ተመላሽ የሚደረግ ይሆናል፡፡
11. አገልግሎቱ ያወጣውን የጨረታ ሰነድ በስሙ ሳይገዛ የተወዳደረ ማንኛውም ተጫራች ከውድድሩ ውድቅ ይደረጋል፡፡
12. አሸናፊ ተጫራቾች ያሸነፉበትን ገንዘብ አጠቃለው በመክፈል ንብረቶቹን በ10 (አስር) ቀናት ውስጥ የማንሳት ግዴታ አለባቸው፡፡
13. አገልግሎቱ የተሻለ አማራጭ ወይም ሌላ ጨረታውን ለመሰረዝ የሚያበቃ ምክንያት ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው፡
አድራሻ፡- የኢ.ፌ.ዴ.ሪ የመንግሥት ግዥ አገልግሎት 6 ኪሎ የካቲት 12 ሰማዕታት
ሐውልት አደባባይ ፊት ለፊት
ለበለጠ መረጃ፡- በስልክ ቁጥር 09 13 78 56 06 ወይም 0912034552 በመደወል መጠየቅ ይቻላል፡
የፌዴራል መንግስት ግዥ አገልግሎት
አዲስ አበባ

17/07/2025

የጨረታ ማስታወቂያ
ያገለገሉ ተሽከርካሪዎችን በግልጽ ጨረታ ለመሸጥ የወጣ የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር PPS/VP-17FBI/01/11/2017
የኢ.ፌ.ዴ.ሪ የመንግሥት ግዥ አገልግሎት ንብረትነታቸው የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት፣የፍትህ ሚኒስቴር፣ የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ፣ የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር፣ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣን ፣የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር፣ የገንዘብ ሚኒስቴር፣የግብርና ሚኒስቴር፣ሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ፣ የኢትዮጵያ አእምሮአዊ ንብረት ባለስልጣን፣ የአምራች ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት፣የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን፣ የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት፣የኢትዮጵያ የጂኦሎጂካል ኢንስቲትዩት፣ የውጪ ጉዳይ ሚ/ር እና የትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ ሚ/ር ተሽከርካሪዎችን ባሉበት ቦታና ሁኔታ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡
በመሆኑም የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟላ ማንኛውም ተጫራች በጨረታው ላይ መወዳደር ይችላል፡፡
1. በጨረታው ላይ የሚወዳደር ማንኛውም ተጫራች ዜግነቱ ኢትዮጵያዊ መሆኑ ያለበት ሲሆን የጨረታውን ሰነድ ለመግዛት ሲመጣ ይህንኑ የሚያረጋግጥ ሰነድ ወይም መታወቂያ ማቅረብ ያስፈልጋል፡፡
2. ተጫራቾች 6 ኪሎ በሚገኘው የኢ.ፌ.ዴ.ሪ የመንግሥት ግዥ አገልግሎት ግዥና ፋይናንስ ስራ አስፈጻሚ ቢሮ በመምጣት የተሽከርካሪዎቹን ዝርዝር መረጃ፣ የተጫራቾች መመሪያ እና የዋጋ ማቅረቢያ ቅጽ የያዘ ሰነድ የማይመለስ ብር 700.00 (ሰባት መቶ ብር) በመንግሥት ግዥ አገልግሎት የንግድ ባንክ ሂሳብ ቁጥር 1000003785018 ላይ ገቢ በማድረግና ያስገቡበትን የባንክ ስሊፕ ይዘው በመቅረብ የጨረታውን ሰነድ መግዛት ይችላሉ፡፡
3. ተጫራቾች የጨረታውን ሰነድ ከገዙ በኋላ ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ዘወትር በሥራ ቀናት ከጠዋቱ 3፡00 እስከ 10፡00 ሰዓት ባለው ጊዜ ውስጥ ተሽከርካሪዎቹን ከላይ በተጠቀሱት መ/ቤቶች በአካል በመሄድ መመልከት ይችላሉ፡፡
4. ተጫራቾች የሚገዙትን ተሸከርካሪ ለእያንዳንዱ የጨረታ መነሻ ዋጋ 5% (አምስት በመቶ) የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ (CPO) ከጨረታ ሰነዱ ጋር በማያያዝ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ከጨረታው ሳጥን መዝጊያ ሰዓት በፊት ማስገባት አለባቸው፡፡ የሚዘጋጀው የጨረታ ማስከበሪያ ሲፒኦ ከአዲስ አበባ ከተማ ውጭ ከሆነ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅርንጫፎች ብቻ መሆን ይኖርበታል፡፡
5. የጨረታው የመገምገሚያ መስፈርት ዋጋ፣ የተሟላ የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ሲፒኦ (CPO) እንዲሁም በሰነዱ የተገለጹትን አሟልቶ መገኘት ይሆናል፡፡ ይሁንና የተሽከርካሪውን የመነሻ ዋጋ 5% (አምስት በመቶ) ያላስያዘ እንዲሁም በሠነዱ የተቀመጡ ሌሎች ነጥቦችን ያላሟላ ተጫራች ከጨረታው ውድቅ ይደረጋል፡፡
6. ተሽከርካሪው ቀደም ሲል ያልተከፈለ የቦሎ ዕዳ ካለበት በባለንብረቱ መሥሪያ ቤት የሚሸፍን ሲሆን የጉምሩክ ቀረጥ ግብር እዳ፣ የስም ማዛወሪያ፣ የትራንዚት እና ሌሎች ወጪዎች ግን በገዥው የሚሸፈን ይሆናል፡፡
7. የጨረታ ማስገቢያ ሳጥኑ ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ20ኛው ቀን ከጠዋቱ 4:00 ሰዓት ላይ ተዘግቶ በዚያኑ ቀን በ4፡15 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በመንግሥት ግዥ አገልግሎት መሰብሰቢያ አዳራሽ ይከፈታል፡፡ ነገር ግን የመክፈቻ ቀኑ የስራ ቀን ላይ ካልሆነ (ቅዳሜ ወይም እሁድ ላይ ከዋለ) ወይም በዓል ቀን ላይ ከዋለ ቀጥሎ ባለው የሥራ ቀን ላይ ይከፈታል፡፡ ሆኖም ተጫራቹ በራሱ ምርጫ ጨረታው በሚከፈትበት ጊዜ ሳይገኝ ቢቀር የጨረታውን መከፈት አያስቀረውም፡፡
8. በጨረታው አሸናፊ የሆኑ ተጫራቾች አሸናፊነታቸው በተገለፀላቸው ከ7 (ሰባት) የስራ ቀናት በኋላ ባሉት 5 (አምስት) ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ ያሸነፉበትን ዋጋ በሙሉ መክፈል ይኖርባቸዋል፡፡ ይሁንና ሙሉ ክፍያውን በተጠቀሰው የጊዜ ገደብ ውስጥ መክፈል ካልቻሉ ያስያዙት የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ተወርሶ ለመንግስት ገቢ ይደረጋል::
9. በጨረታው አሸናፊ የሆኑ ተጫራቾች ያሸነፉባቸውን ተሽከርካሪዎች ሙሉ ክፍያ ከፍለው እስከሚወስዱ ድረስ ለውል አተገባበር ዋስትና የሚሆን የጠቅላላ ዋጋውን 5% (አስር በመቶ) በጥሬ ገንዘብ ወይም በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ (CPO) ማስያዝ አለባቸው፡፡
10. አገልግሎቱ ያወጣውን የጨረታ ሰነድ በስሙ ሳይገዛ የተወዳደረ ማንኛውም ተጫራች ከውድድሩ ውድቅ ይደረጋል፡፡
11. አሸናፊ ተጫራቾች ያሸነፉበትን ገንዘብ አጠቃለው በመክፈል ተሽከርካሪውን በ10 (አስር) ቀናት ውስጥ የማንሳት ግዴታ አለባቸው፡፡
12. አገልግሎቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው፡፡

አድራሻ፡- የኢ.ፌ.ዴ.ሪ የመንግሥት ግዥ አገልግሎት 6 ኪሎ የካቲት 12 ሰማዕታት
ሐውልት አደባባይ ፊት ለፊት
ለበለጠ መረጃ፡- በስልክ ቁጥር 0913785606 ወይም 011-122 37 36 በመደወል መጠየቅ ይቻላል፡፡

የፌዴራል መንግስት ግዥ አገልግሎት
አዲስ አበባ

"በመትከል ማንሰራራት"   የአገልግሎቱ አመራርና ሠራተኞች  የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር አካሄዱ    *** ****** ***                                           ...
17/07/2025

"በመትከል ማንሰራራት"
የአገልግሎቱ አመራርና ሠራተኞች የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር አካሄዱ
*** ****** ***
ዜና፣ አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 10 ቀን 2017 ዓ.ም የመንግስት ግዥ አገልግሎት አመራርና ሰራተኞች ከገንዘብ ሚኒስቴር እና ሌሎች ተጠሪ ተቋማት ጋር በመተባበር በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ የችግኝ ተከላ መርሃግብር በዛሬው ዕለት ለ2ኛ ጊዜ አከናውነዋል።
በመርሐግብሩ ላይ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ገንዘብ ሚኒስቴር ሚኒስትር ክቡር አቶ አህመድ ሽዴ፣ የመንግስት ግዥ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ክቡር አቶ አስማረ ይገዙ እና የአገልግሎቱን ም/ዋና ዳይሬክተሮች ጨምሮ ሌሎች የየተቋማቱ አመራሮችና ሰራተኞች ተሳትፈዋል።
በተጨማሪም እንደ ሀገር በዘንድሮው የክረምት ወራት ለመትከል የታቀደውን 7.5 ቢሊዮን ችግኞችን በመትከል ዕቅድ ውስጥ አገልግሎቱ የበኩሉን አስተዋጽኦ ለማበርከት መላው ሠራተኞቹን በማሳተፍ ተጨማሪ ችግኞችን የመትከል መርሐ ግብር በቀጣይ ሳምንት ለማከናወን የቅድመ ዝግጅት ስራ እየሰራ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡

የውጤት ዜና! በአገልግሎቱ የ10 ዓመት ታሪክ ከንብረት ሽያጭ የተሰበሰበው ገቢ በ2017 በጀት ዓመት ከፍተኛው ውጤት ሆኖ ተመዘገበ**************ዜና፡ አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 07 ቀን 2...
14/07/2025

የውጤት ዜና!
በአገልግሎቱ የ10 ዓመት ታሪክ ከንብረት ሽያጭ የተሰበሰበው ገቢ በ2017 በጀት ዓመት ከፍተኛው ውጤት ሆኖ ተመዘገበ
**************
ዜና፡ አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 07 ቀን 2017 ዓ.ም የመንግስት ግዥ አገልግሎት በ2017 በጀት ዓመት የ42 የመንግስት መ/ቤቶች 201 ተሽከርካሪዎች እና የ15 መ/ቤቶች ልዩ ልዩ ንብረቶችን በሽያጭ በማስወገድ 275.8 ሚሊየን ብር ወይም የዕቅዱን 115% ገቢ ተገኝቷል፡፡ ይህም ገቢ ከ2016 በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር በ61.9 ሚሊዮን ብር (28.9%) ብልጫ እንዳለው ለማወቅ ተችሏል፡፡
በዚህም መሰረት ፅዱ ተቋም የመፍጠር እና 201 ተሽከርካሪዎች በመወገዳቸው ይዘውት የነበረው በአማካይ 3618 ካሬ ሜትር ቦታ ለስራ ምቹ የማድረግ ስራ ተሰርቷል፡፡ በተጨማሪም ሌሎች ልዩ ልዩ ንብረቶች ይዘውት የነበሩበት ሰፋ ያለ ቦታን በማስለቀቅ ለኮሪደር ልማትና ለስራ ምቹ ሁኔታ እንዲፈጠር ተደርጓል፡፡
አገልግሎቱ በ10 ዓመት ታሪኩ ከንብረት ሽያጭ የሰበሰበው ገቢ በ2017 በጀት ዓመት ከፍተኛ የሚባለው ውጤት መሆኑ ተገልጿል፡፡
በ2018 በጀት ዓመትም ተሽከርካሪዎችንና ልዩ ልዩ ንብረቶችን በሽያጭ በማስወገድ 350 ሚሊየን ብር ለመንግስት ገቢ ለማድረግ በዕቅድ መያዙን አሳውቋል፡፡

12/07/2025

አስደሳች የውጤት ዜና!
የመንግስት ግዥ አገልግሎት በ2017 በጀት ዓመት ያስመዘገባቸውን ስኬታማ አፈጻጸሞች እናብስርዎ!
1. የመንግስት የኤሌክትሮኒክ የግዥ ስርዓት (e-GP) ሲስተምን በመጠቀም በርካታ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች እና የአስፓልት የስትራቴጅክ ግዥዎችን እንዲሁም የማዕቀፍ ስምምነት ግዥዎችን ከ15.8 ቢሊየን ብር በላይ ግዥ ፈጽሟል፡፡
2. የማዕቀፍ ስምምነት እና ስትራቴጃዊ ግዥ በድምሩ 21 ውሎችን በ12.7 ቢሊየን ብር ፈርሟል፡፡
3. በንብረት ማስወገድ በኩል በሽያጭ ከተወገዱ 201 ተሽከርካሪዎች እና ልዩ ልዩ ንብረቶች 275.8 ሚሊየን ብር ገቢ በማግኘት የዕቅዱን 115 በመቶ ማሳካት ችሏል፡፡ ይህም ባለፉት አስር ዓመታት በአገልግሎቱ ታሪክ ትልቁ የአፈጻጸም ውጤት ሆኖ ተመዝግቧል፡፡
4. አገልግሎቱ ከተቋቋመ ጀምሮ ለረጅም ዓመታት ሳይወራረዱ የቆዩ ሂሳቦች 100 ፐርሰንት እንዲወራረዱ ተደርጓል፡፡
5. ከ2011 በጀት ዓመት ጀምሮ ያልተዘጉ 118 ውሎች እንዲዘጉ ተደርጓል፡፡
6. ከሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን በተገኘ ፈቃድ መሰረት 36 ክፍት የስራ መደቦችን ማሟላት ተችሏል፡፡
7. የአገልግሎቱን ስራዎች ዲጂታላይዝ አድርጎ ከመሄድ አንጻር የኮርፖሬት ኢ-ሜይል፣ የኋትስአፕ፣ የቴሌግራም እና ማህበራዊ ድረ-ገጾችን በመጠቀም የተቋሙ የመረጃ ልውውጥ ወረቀት አልባ እንዲሆን በማድረግ ያለ አግባብ የሚባክነውን ውጭና ጊዜ መቆጠብ ተችሏል፡፡
8. የአገልግሎቱ አመራሮችና ሰራተኞች የኢኮኖሚ ድጋፍ የሚያስፈልጋቸውን 9 የአገልግሎቱ ሠራተኞች ህጻናት ልጆችን በየወሩ በቋሚነት 800 ብር የገንዘብ ድጋፍ አድርገዋል፡፡ ይህም መልካም ስራ ለሌሎች ተቋማት አርዓያ መሆን ችሏል።
9. በክረምት በጎ አድራጎት ሥራ አገልግሎቱ ከባለድርሻ አካላት ከ4.5 ሚሊዮን ብር በላይ በመሰብሰብ በጉለሌ ክ/ከተማ ወረዳ 03 አስተዳደር ስር የሚገኙ የ5 አቅመ ደካማ ቤቶችን ሙሉ እድሳትና ግንባታ ስራ እንዲጀመር ተደርጓል።
10. ከአገልግሎቱ ባለድርሻ አካላት በተደረገው የሃብት ማፈላለግ ስራ 2.3 ሚሊዮን ብር በመሰብሰብ በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ለሚገኙ በእንጀራ መጋገር ስራ ላይ ለተደራጁ እናቶች ድጋፍ ተደርጓል።
ለዚህ ስኬታማ አፈጻጸም የአገልግሎቱ ከፍተኛ አመራሮች ቁርጠኝነት፣ ትጋት፣ ክትትል እና በቅንጅት መስራት ትልቁን ድርሻ የሚወስድ ሲሆን በየደረጃው ያሉ ሁሉም የስራ ኃላፊዎችና ፈጻሚዎችም ላበረከቱት አስተዋጽኦ ምስጋና ይገባቸዋል።

የግዥ አገልግሎት ማኔጅመንት በ2017 ሪፖርትና በ2018 ዕቅድ ላይ ተወያይቶ አፀደቀ***************ዜና፡ አዲስ አበባ፣ ሀምሌ 04 ቀን 2017 ዓ.ም የመንግስት ግዥ አገልግሎት ማኔጅ...
11/07/2025

የግዥ አገልግሎት ማኔጅመንት በ2017 ሪፖርትና በ2018 ዕቅድ ላይ ተወያይቶ አፀደቀ
***************
ዜና፡ አዲስ አበባ፣ ሀምሌ 04 ቀን 2017 ዓ.ም የመንግስት ግዥ አገልግሎት ማኔጅመንት በአገልግሎቱ የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት እና በ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ በዛሬው ዕለት ውይይት አካሂዷል፡፡
የመነሻ ውይይት የተጠቃለለ ሪፖርት እና ዕቅድ በስትራቴጂክ ጉዳዮች ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ረድኤት ተክሉ በኩል ከቀረበ በኋላ ከማኔጅመንት አባላት አስተያየትና ጥያቄዎች ተነስተው ማብራሪያ እና ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል፡፡
በ2017 በጀት ዓመት በርካታ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች እና የአስፓልት የስትራቴጅክ ግዥዎችን እንዲሁም የማዕቀፍ ስምምነት ግዥዎችን ከ15.8 ቢሊየን ብር በላይ ግዥ መፈፀም መቻሉ፤ 21 የማዕቀፍ ስምምነት እና ስትራቴጃዊ ግዥ ውሎችን በ12.7 ቢሊየን ብር ውል መፈረም መቻሉ፣ ለረጅም ዓመታት ሳይወራረዱ የቆዩ ሂሳቦች 100 ፐርሰንት እንዲወራረዱ መደረጉ፣ ከ2011 በጀት ዓመት ጀምሮ ያልተዘጉ 118 ውሎች እንዲዘጉ የተደረገ መሆኑ፣ በንብረት ማስወገድ በኩል በሽያጭ ከተወገዱ 201 ተሽከርካሪዎች እና ልዩ ልዩ ንብረቶች 275.8 ሚሊየን ብር ገቢ በማግኘት የዕቅዱን 115 በመቶ ማሳካት መቻሉ እና አበረታች ውጤት መሆኑ፣ የሰው ኃይሉን ለማሟላት የተደረገው ጥረት አበረታች መሆኑ፣ የአገልግሎቱን ስራዎች ዲጂታላይዝ አድርጎ ከመሄድ አንጻር አበረታች ስራ መሰራቱ የሚያበረታታ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡
እንዲሁም ከተጠቃሚ መ/ቤቶች እና አቅራቢ ድርጅቶች ጋር የምክክር መድረክ በማካሄድ ተቀራርቦ ለመስራት የተደረገው ጥረት ውጤታማ መሆኑ እና በሌሎች የስራ ክፍሎችም አበረታች እና ስኬታማ ሥራዎች የተሰሩ መሆናቸውን የአገልግሎታችን ዋና ዳይሬክተር ክቡር አቶ አስማረ በመጥቀስ ለተገኘው የሚያበረታታ ውጤት እና ስኬቶች እውቅና መስጠት ተገቢ መሆኑን በአፅኖት በመግለጽ እውቅና ሰጥተዋል፡፡
ዋና ዳይሬክተሩ አክለውም በ2017 በጀት ዓመት አፈፃፀማችን በተገኘው ውጤት ሳንዘናጋ የ2018 በጀት ዓመት ዕቅዳችን ፈጻሚዎችን በማስተባበር ሰፋ አድርገን በማቀድና ከዚህ በላይ በመፈጸም የተሰጠንን ተልዕኮ በሚገባ ማሳካት እንደሚጠበቅብን በዋና ዳይሬክተር አቅጣጫ በመስጠት፤ የቀረበውን ሪፖርትና ዕቅድ በማፅደቅ ውይይቱ ተጠናቋል፡፡

የውጤት ዜና! አገልግሎቱ 98 በመቶ በጀቱን በመጠቀም ከባለፉት አምስት ዓመታት ከፍተኛውን አፈጻጸም  አስመዘገበዜና፣ አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 02 ቀን 2017 ዓ.ም የመንግስት ግዥ  አገልግሎት ...
09/07/2025

የውጤት ዜና!
አገልግሎቱ 98 በመቶ በጀቱን በመጠቀም ከባለፉት አምስት ዓመታት ከፍተኛውን አፈጻጸም አስመዘገበ
ዜና፣ አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 02 ቀን 2017 ዓ.ም የመንግስት ግዥ አገልግሎት የ2017 የበጀት አፈጻጸም ከባለፉት 5 ተከታታይ ዓመታት አንጻር ሲታይ የተፈቀደን በጀት በመጠቀም ከፍተኛ አፈጻጸም (98%) ሆኖ ተመዝግቧል፡፡
ለዚህ ውጤት መገኘት ከበላይ አመራሩ ከፍተኛ ክትትል በተጨማሪ በጀቱን በአግባቡ በመቆጣጠር፣ የተፈቀደው በጀት ለታቀዱ ስራዎች በአግባቡ ህግና አሰራርን ጠብቆ ስራ ላይ እንዲውል የቁጥጥር ስራውን በመስራት የስትራቴጅክ ጉዳዮች ኃላፊ እና ባለሙያዎች ትልቁን ደርሻ የሚወስዱ ሲሆን ከስራው ጋር ቀጥተኛ ትስስር ያላቸው የግዥና ፋይናንስ እንዲሁም የመሰረታዊ አገልግሎት የስራ ክፍሎች አመራሮችና ፈጻሚዎችም ላበረከቱት አስተዋጽኦ ምስጋና ይገባቸዋል።

"በመትከል ማንሰራራት"   የአገልግሎቱ አመራርና ሠራተኞች 7ኛውን ዙር የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር አካሄዱ    ***********                                       ...
08/07/2025

"በመትከል ማንሰራራት"
የአገልግሎቱ አመራርና ሠራተኞች 7ኛውን ዙር የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር አካሄዱ
***********
ዜና፣ አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 01 ቀን 2017 ዓ.ም የመንግስት ግዥ አገልግሎት አመራርና ሰራተኞች ከገንዘብ ሚኒስቴር እና ሌሎች ተጠሪ ተቋማት እንዲሁም ከፕላንና ልማት ሚኒስቴር እና ተጠሪ ተቋማት አመራርና ሰራተኞች ጋር በጋራ በዛሬው ዕለት በእንጦጦ ፓርክ በመገኘት 7ኛውን ዙር የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር አከናውነዋል።
በመርሐግብሩ ላይ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ገንዘብ ሚኒስቴር ሚኒስትር ክቡር አቶ አህመድ ሽዴ፣ የመንግስት ግዥ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ክቡር አቶ አስማረ ይገዙ እና የአገልግሎቱን ም/ዋና ዳይሬክተሮች ጨምሮ ሌሎች የየተቋማቱ አመራሮችና ሰራተኞች ተሳትፈዋል።
በተጨማሪም እንደ ሀገር በዘንድሮው የክረምት ወራት ለመትከል የታቀደውን 7.5 ቢሊዮን ችግኞችን በመትከል ዕቅድ ውስጥ አገልግሎቱ የበኩሉን አስተዋጽኦ ለማበርከት በተያዘው ወር መላው ሠራተኞቹን በማሳተፍ ተጨማሪ ችግኞችን የመትከል መርሐ ግብር ያካሂዳል፡፡

በበጎ አድራጎትና ስብዕና ግንባታ ላይ ያተኮረ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ *******ዜና፣ አዲስ አበባ፣ ሰኔ 27 ቀን 2017 ዓ.ም የመንግስት ግዥ አገልግሎት ከየስራ ክፍሎች ለተውጣጡ...
04/07/2025

በበጎ አድራጎትና ስብዕና ግንባታ ላይ ያተኮረ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ
*******
ዜና፣ አዲስ አበባ፣ ሰኔ 27 ቀን 2017 ዓ.ም የመንግስት ግዥ አገልግሎት ከየስራ ክፍሎች ለተውጣጡ ለአገልግሎቱ ወጣት ሠራተኞች በበጎ አድራጎት እና ስብዕና ግንባታ ላይ ያተኮረ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጥቷል፡፡
ስልጠናው ወጣትነት እና ስብዕና ምንነት ፣ የስብዕና ግንባታ ለአገልግሎቱ ወጣት ሠራተኞች ያለው ፋይዳ በሚሉ ርዕሰ ጉዳዮች ዙሪያ የተሰጠ ሲሆን ፤ የስልጠናው ዋና ዓላማ በስነምግባር የታነፀ እና ምክንያታዊ ወጣት በመፍጠርና የተለያዩ በጎ ተግባራትን መስራት የሚያስችል አስተሳሰብ በማላበስ ፤ ተቋሙንም ሆነ አካባቢያቸውንና ሀገራቸውን በጋራ ለማልማት እና ማገልገል እንዲችሉ አቅም ለመፍጠር ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑን ተገልጿል ፡፡
የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናው በአገልግሎቱ የሴቶች፣ ህፃናትና ማህበራዊ ጉዳዮች አካቶ ትግበራ የስራ ክፍል አስተባባሪነት የተዘጋጀ ሲሆን ስልጠናውም በሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የወጣቶች ስብዕና ልማት ዴስክ ኃላፊ በአቶ አብዱለጢፍ መሀመድ ተሰጥቷል፡፡

በስራ ሥነ-ምግባር እና በደንበኞች አያያዝ ላይ ያተኮረ ስልጠና ተሰጠ  ዜና፡ ሰኔ 21 ቀን 2017 ዓ.ም የመንግስት ግዥ አገልግሎት ከፌዴራል ሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ጋር በመተባበር...
28/06/2025

በስራ ሥነ-ምግባር እና በደንበኞች አያያዝ ላይ ያተኮረ ስልጠና ተሰጠ
ዜና፡ ሰኔ 21 ቀን 2017 ዓ.ም የመንግስት ግዥ አገልግሎት ከፌዴራል ሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ጋር በመተባበር በስራ ሥነ-ምግባርና በደንበኞች አያያዝ ላይ ያተኮረ ስልጠና ለአገልግሎቱ አመራርና ሰራተኞች ተሰጥቷል፡፡
ሰልጠናውን ያስጀመሩት የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ መልካሙ ደፋሊ እንዳሉት፤ የመንግስት ግዥ አገልግሎት፡ አገልግሎት ሰጪ ተቋም እንደመሆኑ፤ አመራርና መላው ሠራተኛ ለሚሰጠው አገልግሎት ሙያዊ ስነ ምግባር ተላብሶ ተገልጋዩን በፍትሃዊነት እና በቅንነት በማገልገል ተቋሙን ውጤታማ ማድረግ ይገባል ብለዋል፡፡ በመሆኑም የሠራተኛውን ግንዛቤ የሚያሰፉ መሰል ስልጠናዎች መሰጠታቸው ፋይዳቸው የጎላ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
ስልጠናው ከፌዴራል ስነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን የስልጠና ዴስክ ኃላፊ በሆኑት በአቶ ፍቃዱ በረና የተሰጠ ሲሆን ፤ ስለ ሥነ-ምግባር እና የስራ ላይ ስነ ምግባር ምንነት፣ በአገልግሎት አይነቶችና አሰጣጥ ዙሪያ፤ በደንበኛ አያያዝ በሚሉ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ትኩረት በማድረግ ግንዛቤ አስጨብጠዋል።
በመጨረሻም ስልጠናውን ያጠቃለሉት የዋና ዳይሬክተር ጽ/ቤት ኃላፊው አቶ መልካሙ ደፋሊ እንዳሉት ስልጠናው በበጀት ዓመቱ ማጠናቀቂያ ላይ መሰጠቱ ሁላችንም አገልግሎት አሰጣጣችን ምን ይመስል ነበር፣ ተገቢውን የስራ ስነምግባር ተላብሰን ስራችን ፈጽመናል ወይ? የሚለውን የምናይበት እና ለቀጣይ 2018 በጀት ዓመት ጥንካሬያችን አጉልተን፣ ክፍተቶታችን ደግሞ አስተካክለን ተገቢውን አገልግሎት ለመስጠት ዝግጅት የምናደርግበት ወሳኝ ጊዜ ነው በማለት ገልጸዋል፡፡

Address

Addis Ababa

Telephone

0111223703

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Federal Public Procurement Service -PPS posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Federal Public Procurement Service -PPS:

Share