Abebe Tarekegn

Abebe Tarekegn Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Abebe Tarekegn, Digital creator, Addis Ababa.

25/03/2026
17/03/2026

#ግብር

በኢትዮጵያ የባንክ ዘርፍ የሚሰሩ ሰራተኞች ባንኮች ለሰራተኞቻቸው በሚሰጧቸው ዝቅተኛ ወለድ ያላቸው ብድሮች ላይ እየተጣለ ያለው ግብር በመካከለኛ ገቢ ላይ ባሉ ባለሙያዎች ላይ ከፍተኛ የሆነ የኢኮኖሚ ጫና እየፈጠረ መሆኑን በመግለጽ ስጋታቸውን ገልጸዋል።

ኑሯቸውን ከፍተኛ የሆነ ጫና ላይ እንደወደቀም ገልጸዋል።

የዘርፉ ተወካዮች እንደሚሉት ለቤትና ለተሽከርካሪ መግዣ የሚውሉ የብድር ጥቅማጥቅሞች የሚታሰቡበት የግብር ቀመር የሰራተኞችን የተጣራ ወርሃዊ ገቢ በከፍተኛ ሁኔታ የቀነሰ መሆኑን አመልክተዋል።

ችግሩ የሚመነጨው ባንኮች ለሰራተኞቻቸው በሚሰጡት ዝቅተኛ 7% ወለድ እና መንግሥት እንደ ገበያ ወለድ በሚወስደው 15 በመቶ መካከል ያለው ልዩነት እንደ እንደ ሰራተኛው ገቢ ተቆጥሮ የገቢ ግብር ስለሚታሰብበት ነው።

​ለበርካታ ዓመታት የኢትዮጵያ የፋይናንስ ተቋማት ሰራተኞቻቸውን ለማቆየት እና ለማበረታታት የቤት እና የተሽከርካሪ ብድሮችን በ7 በመቶ የቅናሽ ወለድ ሲሰጡ ቆይተዋል።

ይሁን እንጂ የቅርብ ጊዜ የግብር ኦዲት አሰራሮች የ15 በመቶ የገበያ ወለድን እንደ መነሻ በመውሰድ በሁለቱ መካከል ያለውን የ8 በመቶ ልዩነት እንደ ሰራተኛው ገቢ በመቁጠር ግብር እንዲታሰብበት እያደረጉ ይገኛሉ።

ሰራተኞች በእጃቸው ባላገኙትና እንደ ገቢ ባልተቀበሉት የገንዘብ ልዩነት ላይ ግብር መክፈላቸው ተገቢ እንዳልሆነ በገንዘብ ሚኒስቴር በተዘጋጀ የምክክር መድረክ ላይ ቅሬታቸውን አቅርበዋል።

ለምሳሌ በቀረበ አንድ ማሳያ 30,000 ብር ጠቅላላ ወርሃዊ ደሞዝ የሚከፈለው ሰራተኛ የገቢ ግብር፣ የጡረታ መዋጮ እና የብድር እዳ ተቀናሽ ሲደረግበት በእጁ የሚቀረው የተጣራ ክፍያ ወደ 4,400 ብር ዝቅ ሊል እንደሚችል ተጠቁሟል።

የኢትዮጵያ ባንኮች ማህበር እና የፋይናንስ ተቋማት የሰራተኞች ማህበራት ፌዴሬሽን በዚህ የታክስ አሰላል ላይ የተገደበ ጣሪያ እንዲቀመጥ ለመንግሥት ጥያቄ ያቀረቡ ሲሆን ችግሩ ካልተፈታ ዘርፉ ልምድ ያላቸውን ባለሙያዎች ሊያጣ እንደሚችል አስጠንቅቀዋል።

ከገንዘብ ሚኒስቴር ግን በወቅቱ ይህ ነው የተባለ መልስ አልተሰጠም።

መንግሥት የግብር መሠረቱን ማስፋፋት የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳ ዋነኛ ዓላማ መሆኑን ከዚህ ቀደም ብሎ አጽንኦት ሰጥቶበታል።

የፋይናንስ ባለሙያዎች እንደሚጠቁሙትም መንግሥት በቅርቡ ግብር የማይከፈልበትን የገቢ ጣሪያ ከ600 ብር ወደ 2,000 ብር ማሳደጉ ዝቅተኛ ገቢ ያላቸውን ዜጎች ጫና ለመቀነስ የታለመ እርምጃ ቢሆንም በመካከለኛ ገቢ ላይ የሚገኙ ሰራተኞች ግን አሁንም እየጨመረ የመጣ የግብር ጫና እየገጠማቸው ይገኛል።

በሌላ በኩል የግብር ባለሙያዎች በአዲሱ የገቢ ግብር ረቂቅ ደንብ ላይ የሊሚትድ ላይቢሊቲ ፓርትነርሺፕ (LLP) ኩባንያዎች ትርፍ ባከፋፈሉ በ30 ቀናት ውስጥ ታክስ እንዲከፍሉ መገደዳቸው እና የቅድመ ታክስ ክፍያ አሰላልፍ ላይ ክርክር ያለባቸው የኦዲት ግኝቶች ጭምር መካተታቸው በንግዱ ማህበረሰብ ላይ የአስተዳደርና የጥሬ ገንዘብ ፍሰት ጫና ሊፈጥር እንደሚችል ስጋታቸውን ገልጸዋል።

በሌላ በኩል የታክስ ባለሙያዎች በአዲሱ የገቢ ግብር ረቂቅ ደንብ ውስጥ በተካተቱ ሌሎች ድንጋጌዎች ላይ ስጋታቸውን ገልጸዋል።

የሕግ ባለሙያዎች እንደሚጠቁሙት የሊሚትድ ላይቢሊቲ ፓርትነርሺፕ (LLP) ተቋማት የሚከፋፈል ገቢ በከፈሉ በ30 ቀናት ውስጥ ታክስ እንዲከፍሉ መገደዳቸው በሙያዊ አገልግሎት ሰጭ ድርጅቶች ላይ ተደጋጋሚ የታክስ ማሳወቂያና ከፍተኛ የሕግ ተገዥነት ወጪን በማስከተል ተጨማሪ የአስተዳደር ጫና ሊፈጥር ይችላል።

ሌላው ስጋት ከቅድመ ታክስ ክፍያ (Advance Tax Payment) ቀመር ጋር የተያያዘ ሲሆን ስሌቱ ባለፈው ዓመት የታክስ ማሳወቂያ ላይ መመስረቱና ክርክር ያለባቸው የኦዲት ግኝቶች ጭምር እንዲካተቱ መደረጉ ቢዝነሶች የተጋነነ ቅድመ ክፍያ እንዲፈጽሙ በማስገደድ የጥሬ ገንዘብ ፍሰት ጫና ሊፈጥር እንደሚችል ባለሙያዎች አስረድተዋል።

በተጨማሪም " ማንኛውም ክፍያ እንደ የሚከፋፈል ገቢ ይቆጠራል " የሚለው አገላለጽ እንደ ለንግድ አጋሮች የሚሰጥ ብድር ያሉ ሕጋዊ የገንዘብ ዝውውሮችን በስህተት በታክስ እንዲፈረጁ ሊያደርግ እንደሚችል አቶ ጥበበ የተባሉ ባለሙያ አስጠንቅቀዋል።

ይህንን አደጋ ለመከላከልም ደንቡ ተገቢው ማስረጃ በሚቀርብበት ጊዜ ለየት ያሉ ሁኔታዎችን እንዲያስተናግድ ሆኖ እንዲሻሻል ምክረ ሃሳብ አቅርበዋል።

ይህ መረጃ ሙሉ ባለቤትነቱ የካፒታል ጋዜጣ / Capital Newspaper ነው።

መጋቢት 7 ቀን 2018 ዓ/ም

16/03/2026

✉️ Russian President Vladimir Putin expressed deep condolences to Ethiopian President Taye Atske Selassie and Ethiopian Prime Minister Abiy Ahmed over the tragic consequences of landslides in southern Ethiopia

✍️Esteemed Mr. President,

Esteemed Mr. Prime Minister,

Please accept my deepest condolences in connection with the tragedic consequences of landslides and floods in the South of your country.
Please convey words of sincere sympathy and support to the families of victims as well as wishes for a quick recovery to all injured by violence of these natural disasters.

Sincerely,

Vladimir Putin

Moscow, March 16, 2026

https://shorturl.at/SRLgd

15/03/2026
14/03/2026
13/03/2026

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Abebe Tarekegn posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share