Gize Media

Gize Media Gize is one of the best Ethiopian infotainment media. We provide with multidimensional access to the

እንኳን ለጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሠላም አደረሳችሁ! አደረሰን! 🙏በአገር ውስጥና በመላው ዓለም ለምትገኙ የክርስትና እምነት ተከታይ ለሆናችሁ ሁሉ እንኳን ለእየ...
06/01/2026

እንኳን ለጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሠላም አደረሳችሁ! አደረሰን! 🙏

በአገር ውስጥና በመላው ዓለም ለምትገኙ የክርስትና እምነት ተከታይ ለሆናችሁ ሁሉ እንኳን ለእየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ!🙏

በዓሉ የሰላምና የደስታ እንዲሆንላችሁ ከልብ እንመኛለን። መልካም የልደት በዓል! 🙏 መልካም የገና በዓል! 🙏



አዳዲስ መረጃዎች እንዲደርስዎ👇
https://t.me/gize_media

ፔጃችንን LIKE በማድረግ ቤተሰብ አድርጉን 👇
https://www.facebook.com/GizeMereja?mibextid=ZbWKwL

የቤቶች ድራማ አይረሴዋ አርቲስት ሰብለ ተፈራ (ትርፌ) የክብር መታሰቢያ ተደረገላት።በዓድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም የቤቶች ድራማ 13ኛ ዓመት ልዩ ክብረ በዓል ላይ ፣ ለቀድሞዋ የድራማው ተዋና...
27/12/2025

የቤቶች ድራማ አይረሴዋ አርቲስት ሰብለ ተፈራ (ትርፌ) የክብር መታሰቢያ ተደረገላት።

በዓድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም የቤቶች ድራማ 13ኛ ዓመት ልዩ ክብረ በዓል ላይ ፣ ለቀድሞዋ የድራማው ተዋናይ አርቲስት ሰብለ ተፈራ (ትርፌ) የክብርና የመታሰቢያ ፕሮግራም ተካሂዷል።

አርቲስት ሰብለ ተፈራ በ2008 ዓ.ም ሕይወቷ ማለፉ አይዘነጋም።

:- ዶትስትሪም



አዳዲስ መረጃዎች እንዲደርስዎ👇
https://t.me/gize_media

ፔጃችንን LIKE በማድረግ ቤተሰብ አድርጉን 👇
https://www.facebook.com/GizeMereja?mibextid=ZbWKwL

 ! 😮 8 ሚሊዮን ብር ገቢ እንዲገባ ያደረገው ቲክቶክን ወደ ታላቅ በጎ ተግባር የለወጠው ወጣቱ ጀግና!ዛሬ እጅግ አስደናቂ እና ልብ የሚነካ ታሪክ በቲክቶክ ዓለም ተመዝግቧል! ወጣቱ ተፅዕኖ ...
15/11/2025

! 😮 8 ሚሊዮን ብር ገቢ እንዲገባ ያደረገው ቲክቶክን ወደ ታላቅ በጎ ተግባር የለወጠው ወጣቱ ጀግና!

ዛሬ እጅግ አስደናቂ እና ልብ የሚነካ ታሪክ በቲክቶክ ዓለም ተመዝግቧል! ወጣቱ ተፅዕኖ ፈጣሪ አዶናይ የረምዚን ሪል እስቴት Challenge ቃሉን ጠብቆ ታላቅ ስኬት አስመዝግቧል!

ረምዚን ሪል እስቴት በቲክቶክ 1 ሚሊዮን ተከታዮችን (Followers) ካስገባችሁኝ፣ 8 ሚሊዮን የኢትዮጵያ ብር ለባቡል ኸይር የበጎ አድራጎት ድርጅት አስገባለሁ ባለው መሰረት ቲክቶከሩ አዶናይ ባለው ትልቅ ተፅዕኖ ፈጣሪነት እና ህዝባዊ ድጋፍ ጥሪ በማቅረቡ ምክንያት በዛሬው ዕለት በአንድ ቀን ውስጥ 1 ሚሊዮን እንዲገባ አድርጓል!

በዚህም ምክንያት 8 ሚሊዮን ብር ለበጎ አድራጎት እንዲገባ አስችሏል!

አንድ ግለሰብ ትልቅ ለውጥ ማምጣት እንደሚችል በተግባር አሳይቷል!

ይህ ስኬት ከቲክቶክ ባለፈ ትብብርና በጎነትን
የሚያሳይ ብሩህ ምሳሌ ነው! በዚህም ይህ ወጣት አምባሳደር ሆኖ ሊሾም ይገባዋል!

:- Gursha



አዳዲስ መረጃዎች እንዲደርስዎ👇
https://t.me/gize_media

ፔጃችንን LIKE በማድረግ ቤተሰብ አድርጉን 👇
https://www.facebook.com/GizeMereja?mibextid=ZbWKwL

S25 ስልክ ቀምቶ ቱቦ የገባው ሌባከአንድ ግለሰብ ስልክ ቀምቶ የቆሻሻ ማስወገጃ ቱቦ ውስጥ በመግባት ሊያመልጥ የነበረ ተጠርጣሪ ከ5 ሰዓታት ቆይታ በኋላ ከነ ኤግዚቢቱ መያዙን የአዲስ አበባ ...
24/10/2025

S25 ስልክ ቀምቶ ቱቦ የገባው ሌባ

ከአንድ ግለሰብ ስልክ ቀምቶ የቆሻሻ ማስወገጃ ቱቦ ውስጥ በመግባት ሊያመልጥ የነበረ ተጠርጣሪ ከ5 ሰዓታት ቆይታ በኋላ ከነ ኤግዚቢቱ መያዙን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ገለጸ።

ተጠርጣሪው የቅሚያ ወንጀሉን ፈጽሞ የፍሳሽ ቆሻሻ ማስወገጃ ቱቦ ውስጥ በመግባት ሊያመልጥ ሲል በቁጥጥር ስር የዋለው ጥቅምት 12 ቀን 2018 ዓ/ም በየካ ክ/ከተማ ወረዳ 5 አቤቤ ሱቅ ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ ነው።

ተጠርጣሪው የግል ተበዳይ ከባንክ ብር አውጥተው ሲወጡ ጠብቆ የዋጋ ግምቱ 120 ሺ ብር የሚያወጣ Sumsung Ultra S25 ስማርት ስልክ በመንጠቅ በአካባቢው ወደሚገኝ የቆሻሻ ማስወገጃ ቱቦ ውስጥ ገብቷል።

የወንጀል ድርጊቱ ከተፈጸመ በኋላ የግል ተበዳይ የይድረሱልኝ ጥሪ በማሠማታቸው የአካባቢው ህብረተሰብ እና ፖሊስ ወዲያው ቦታው ላይ በመድረስ ተጠርጣሪው በገባበት የፍሳሽ ቆሻሻ ማስወገጃ ቱቦ ውስጥ ተከታትሎ በመግባት ሊያወጡት መቻላቸውን የየካ ክፍለ ከተ ማ ፖሊስ መምሪያ ገልጿል።

ተጠርጣሪው ከቱቦው ውስጥ ሲወጣ ስልኩን ትቶ የወጣ ቢሆንም ፖሊስ ተጠርጣሪውን በድጋሚ ወደ ቱቦው ውስጥ ይዞ በመግባት ስልኩን ከጣለበት ውሃ ውስጥ እንዲያወጣው ማደረጉን የምርመራ መዝገቡ ያስረዳል።

በእንደዚህ ዓይነት የወንጀል ተግባር ላይ የሚሰማሩ ወንጀል ፈጻሚዎች ከህግ እንደማያመልጡ አውቀው ከድርጊታቸው ሊቆጠቡ እንደሚገባ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አሳስቧል።



አዳዲስ መረጃዎች እንዲደርስዎ👇
https://t.me/gize_media

ፔጃችንን LIKE በማድረግ ቤተሰብ አድርጉን 👇
https://www.facebook.com/GizeMereja?mibextid=ZbWKwL

አሁን ቤት ስገባ መ/ር ዶ/ር ዘበነ ለማ ሰይፉ ሾ ላይ ቀርቦ እያወራ ነው። ስለብዙ ነገሮች ደስ የሚል ትንተና እየሰጠ ነው። እና እያየሁት በቁምነገር ለመከታታል አቃተኝ። በሌላ አይደለም ዘሪ...
12/10/2025

አሁን ቤት ስገባ መ/ር ዶ/ር ዘበነ ለማ ሰይፉ ሾ ላይ ቀርቦ እያወራ ነው። ስለብዙ ነገሮች ደስ የሚል ትንተና እየሰጠ ነው። እና እያየሁት በቁምነገር ለመከታታል አቃተኝ። በሌላ አይደለም ዘሪቱ ከበደ በመፅሃፏ ላይ የሰጠችው ስም እየታወሰኝ እንጂ!

"ሃበሻ ምንም ነገር እንዳያገኝብህ ከፈለክ መፅሃፍ ውስጥ ደብቀው..." የሚለው አባባል እውነት መሆኑ የተገለጠልኝ በዚህ ዓመት ነው። እንዲህ እንድል ያስደፈረኝም የፈረደበት ይሄው የዘሪቱ "ከልጅነት እስከ ልጁነት..." የተሰኘው መፅሃፍ ነው።

በዚህ በቲክቶክ'ና በፌስቡክ የሚነሱ ትናንሽ የግለሰቦች ጉዳይ እንኳን ሳይቀር መነጋገሪ በሚሆንበት ሰዓት ፣ የዘሪቱ መፅሃፍ መነጋጋሪ ሳይሆን ያለፈው የፃፈቻቸው ሃሳቦች መፅሃፍ ውስጥ በመደበቃቸው ብቻ ይመስለኛል።

እንደዛ ባይሆን ኖሮ በታአምር ልናልፋቸው የማይገቡ ፣ መነጋጋሪያ ሊሆኑ የሚገቡ በጣም ብዙ አወዛጋቢ ጉዳዬችን በውስጥ ይዟል!

ከእነዛ ውስጥ አንዱ ዘሪቱ ለመምህር ዘበነ የሰጠችው ስም ነው። ስሙን ያወጣችው እንዲሁ አይደለም። እሷም ስለ ስሙ አመጣጥ'ና አወጣጡ ገፅ 52 ላይ በደንብ አድርጋ ተርካዋለች።

ዘሪቱ በልጅነቷ ለእህትና ወንድሞቿ ፣ ከዛም አድጋና ወልዳ ለልጆቿ ህፃን እያሉ ከተረት ባለፈ ከእራሷ ፈጥራ የምትነግራቸው የውሸት ፣ ሊታመኑ የማይችሉ አድቬንቸር ታሪኮች ነበሩ። እነዛን ታሪኮች እሷም ሆኑ ልጆቿ የሚግባቡት ስም "ድሽድሽ..." የሚል ነው።

"የድሽ ድሽ ታሪክ ንገሪን ካሏት..." የሆነ ታሪክ ፈጥራ ትነግራቸዋለች።

እና ልጆቼ አድገው እኔ ካቆምኩ በኋላ የድሽድሽ ታሪክ የሚናገሩ የሃይማኖት አባት መጡ ብላ መምህር ዘበነ ላይ በሰፊው ትሄድባቸዋለች።

ከጓደኞቿም ጋር "የድሽ ድሽ አባት..." (የተረት አባት) ብለው እንደሚጠሯቸው ፅፋለች። 🙂

ዘሪቱ ይሄን መፃፏ ልክ ይሁን አይሁን አላውቅም። ግን ተፅኖ ይሄው እኔ እንኳን ቃለምልልሱን እያየሁ የሚታወሰኝ እሷ ያወጣችው ስም ሆኖ ለብቻዬ ፈገግ እላለሁ።

ብቻ የዘሪቱ መፅሃፍ የዚህ አይነት ብዙ አወዛጋቢ ነገሮችን በውስጡ ይዟል። እስኪ አንብቡትና እንወያይበት። 😑

:- ሙስተጃብ ነኝ



አዳዲስ መረጃዎች እንዲደርስዎ👇
https://t.me/gize_media

ፔጃችንን LIKE በማድረግ ቤተሰብ አድርጉን 👇
https://www.facebook.com/GizeMereja?mibextid=ZbWKwL

11/10/2025

ኢትዮጵያዊው ስደተኛ በአሜሪካ ጎዳና 😥

ይህ ልጅ የጎዳና ተዳዳሪ ከሆነ 5 ዓመት ሆኖኛል ይላል። ለሁለት ዓመት ለT- Mobil and Metro ሰርቻለሁ ወደ ጎዳና እንዴት እንደወጣሁ አላውቅም ይላል።

ብዙ ኢትዮጵያን ከሀገር የሚወጡት በፖለቲካ ፣ በችግር እና የተሻለ ነገር ለማግኘት ነው። በሰው ሀገር የተመኙትን መሆን ቀላል አይደለም። እንኳን ለብቻ ተሰደህ ፣ ቤተሰብ እያለህ እንኳን ከባድ ነው።

ብዙዎች በእግዚያአብሔር እርዳታ ከጉድ ወጥተው በሰው ሀገር ስራ ፣ ቤት እና መኪና ኖሯቸው የተመቸ ኑሮ ይኖራል። አንድአንዶች ደግሞ ህልማቸው ጠፍቶ ባክነው አጉል ቦታ ይገኛሉ።

ይህ ልጅ ኢትዮጵያ ውስጥ እናት ፣ አባት ፣ እህት እና ወንድም ሊኖሩት ይችላሉ። ወደ አሜሪካ የመጣው ቀጥታ በአውሮፕላን ፣ ወይንም ደግሞ በአውሮፕላን እና በእግር ብዙ ሀገራትን እና መንገዶችን አቋርጦ ይሆናል።

የሆነው ሆኖ ይሄ ልጅ አሜሪካ ውስጥ ላለፉት 5 ዓመታት የጎዳና ተዳዳሪ ሆኗል። ልጄ አሜሪካ ሀገር ከገባ በኋላ ዘጋኝ ፣ ጠፋብኝ የምትል እናትም ትኖራለች። ሞቶ ይሆንም ትላለች። ግን ልጅዋ በህይወት አለ።

የአሜሪካ ጎዳና ቤቱ ሆኖ። በነገራችን ላይ ጠያቂው ኦረገን ላይ የጎዳና ተዳዳሪ መሆን እንዴት ነው ብሎ ሲጠይቀው ፣ ይህ ልጅ የመለሰው ምንም አይልም ብሎ ነው። እንዴት ሲለው ብዙ ነገር ታገኛለህ አለው።

:- መንበረ ካሳዬ



አዳዲስ መረጃዎች እንዲደርስዎ👇
https://t.me/gize_media

ፔጃችንን LIKE በማድረግ ቤተሰብ አድርጉን 👇
https://www.facebook.com/GizeMereja?mibextid=ZbWKwL

ለመላዉ የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሰላም አደረሳችሁ ፤ አደረሰን! አዳዲስ መረጃዎች እንዲደርስዎ👇https://t.me/gize_mediaፔጃችንን LIKE በማድ...
26/09/2025

ለመላዉ የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሰላም አደረሳችሁ ፤ አደረሰን!



አዳዲስ መረጃዎች እንዲደርስዎ👇
https://t.me/gize_media

ፔጃችንን LIKE በማድረግ ቤተሰብ አድርጉን 👇
https://www.facebook.com/GizeMereja?mibextid=ZbWKwL

"ያስፈራሩኝ የነበሩት በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውለዋል!"👉 ድምፃዊት ዳግማዊት ፀሐዬ✍️ድምጻዊት ዳግማዊት ፀሐዬ፣ በማህበራዊ ሚዲያ አማካኝነት ለረጅም ጊዜ ሲያስፈራራትና ሲያንገላታት የነበረው ግለ...
25/09/2025

"ያስፈራሩኝ የነበሩት በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውለዋል!"

👉 ድምፃዊት ዳግማዊት ፀሐዬ✍️

ድምጻዊት ዳግማዊት ፀሐዬ፣ በማህበራዊ ሚዲያ አማካኝነት ለረጅም ጊዜ ሲያስፈራራትና ሲያንገላታት የነበረው ግለሰብ በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋሉን አስታወቀች።

የግለሰቡ መያዝ በበርካቶች ዘንድ እፎይታን ሲፈጥር፣ ጉዳዩ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ሰፊ መነጋገሪያን በመፍጠር ሴቶች በኦንላይን ለሚደርስባቸው ጥቃት የሚሰጠውን ማህበራዊ ምላሽ በድጋሚ እንዲፈተሽ አድርጓል።

ዳግማዊት በማህበራዊ ገጿ ላይ "ትዝ አላችሁ እሱ ካልተያዘ ኢትዮጵያዊነቴን እሰርዛለሁ ብዬ ነበር! ተመስገን ለሁሉም ጊዜ አለው... ወንጀለኛው ተይዟል!" ስትል የደረሰችበትን የስነ-ልቦና ጫናና የግለሰቡን መያዝ ተከትሎ የተሰማትን እፎይታ ገልጻለች።

ግለሰቡ በሌሎች ሰዎች ላይም የገንዘብ ማጭበርበር እንደፈጸመ ፍንጭ የሰጠ ሲሆን፣ ተከሳሹ ነገ ፍርድ ቤት እንደሚቀርብም አስታውቃለች።

ድምጻዊቷ ላደረጉላት ፈጣን ምላሽ የአዲስ አበባ እና የፌደራል ፖሊስን አመስግናለች።



አዳዲስ መረጃዎች እንዲደርስዎ👇
https://t.me/gize_media

ፔጃችንን LIKE በማድረግ ቤተሰብ አድርጉን 👇
https://www.facebook.com/GizeMereja?mibextid=ZbWKwL

ጉድ ሳይሰማ መስከረም አይጠባ እንዲሉ... 8ኛው ሺህ ማለት አሁን ነው!ኦጂ የተባለ ናይጄሪያዊ ወጣት እናት እና ልጅን ማስረገዙ መነጋገሪያ ሆኗል፡፡ 😯🤔ኦጂ መጀመሪያ የፍቅር ግኙነት የነበረው...
15/09/2025

ጉድ ሳይሰማ መስከረም አይጠባ እንዲሉ... 8ኛው ሺህ ማለት አሁን ነው!

ኦጂ የተባለ ናይጄሪያዊ ወጣት እናት እና ልጅን ማስረገዙ መነጋገሪያ ሆኗል፡፡ 😯🤔

ኦጂ መጀመሪያ የፍቅር ግኙነት የነበረው ከልጅቷ ጋር ቢሆንም ልጅቷ ለእናቷ ኦጂ በደንብ እንደሚንከባከባት እና ጥሩ የፍቅር ጊዜ እያሳለፈች እንደሆነ ትነግራታለች፡፡

በዚህ ጊዜ እናት የልጇ ጓደኛ ላይ ፍላጎት ያድርባታል ፣ በመጨረሻም እናቷም ለኦጂ ጥያቄ ታቀርብና ልጇም ትስማማ እና እናት እና ልጅ በኦጂ ፍቅር ጭልጥ ይላሉ፡፡ ከዛም በተመሳሳይ ሁኔታ ያረግዛሉ፡፡

እናት ወንድ ልጅ ልጅ ደሞ ሴት ልጅ እንደሚወልዱ በሃኪም ተረጋገጠ፡፡ ኦጂንም ሰርፕራይዝ አደረጉት፡፡ አሁን እናት እና ልጅ በቅርቡ የልጅ እናት ይሆናሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

(ከማሕበራዊ ሚዲያ የተገኘ)



አዳዲስ መረጃዎች እንዲደርስዎ👇
https://t.me/gize_media

ፔጃችንን LIKE በማድረግ ቤተሰብ አድርጉን 👇
https://www.facebook.com/GizeMereja?mibextid=ZbWKwL

ፈጣሪ ወጥቶ ከመቅረት ይጠብቀን🙏አሳዛኝ ክስተት! በአሜሪካ አንድ በበርካታ ክሶች የሚታወቅ ጥ*ቁ*ር ወጣት ዩክሬናዊት ወጣት ላይ ባደረሰው የ ግ ድ ያ ወ ን ጀ ል አለምን አሳዝኗል።ወጣቷ በዩ...
12/09/2025

ፈጣሪ ወጥቶ ከመቅረት ይጠብቀን🙏
አሳዛኝ ክስተት!

በአሜሪካ አንድ በበርካታ ክሶች የሚታወቅ ጥ*ቁ*ር ወጣት ዩክሬናዊት ወጣት ላይ ባደረሰው የ ግ ድ ያ ወ ን ጀ ል አለምን አሳዝኗል።

ወጣቷ በዩክሬን ጦርነት ምክንያት በስደት አሜሪካ የገባች ስትሆን ማምሻዋን ስራ ውላ በአውቶብስ ወደ ቤቷ እየተጓዘች ባለበት ከኃላዋ የተቀመጠው ሞ ት የጠማው ነፍሰ ገ ዳ ይ አንገቷን በ*ስ*ለ*ት በመውጋት ሕይወቷ እንዲያልፍ አድርጓል።

በክስተቱ ላይ እጅግ ኣሳዛኝ የነበረው ሌላው ክስተት አውቶብስ ውስጥ የነበሩ ተሳፋሪዎች ወንጀለኛውን ለመያዝም ይሁን ተጎጂዋን ለማዳን ምንም ጥረት አለማድረጋቸው ነበር።

ክስተቱ የአሜሪካ ባለስልጣናትን እጅግ አስቆጥቷል - ሰው ጥላውን የማያምንበት ዘመን ላይ ደርሰናል።

:- MinAddis



አዳዲስ መረጃዎች እንዲደርስዎ👇
https://t.me/gize_media

ፔጃችንን LIKE በማድረግ ቤተሰብ አድርጉን 👇
https://www.facebook.com/GizeMereja?mibextid=ZbWKwL

የጊዜ ጀግና እንጂ የሰው ጀግና የለም!ማንም ሰው የቆመ ቢመስለው እንዳይወድቅ ይጠንቀቅ!ከታች በምስሉ ላይ የምትመለከቱት ወጣት ወንዴ ቶን ይባላል ታዋቂ ዘፋኝ ነው... ከ2አመት በፊት "ፎቶዬ...
11/09/2025

የጊዜ ጀግና እንጂ የሰው ጀግና የለም!
ማንም ሰው የቆመ ቢመስለው እንዳይወድቅ ይጠንቀቅ!

ከታች በምስሉ ላይ የምትመለከቱት ወጣት ወንዴ ቶን ይባላል ታዋቂ ዘፋኝ ነው... ከ2አመት በፊት "ፎቶዬን አይቼው የልጅነቴን" በሚል ዘፈኑ ብዙዎቻችን እናቀዋለን በYoutube ከ323ሺህ ሰው በላይ እይታን አግኝቶለታል።

አሁን ላይ ግን የህይወት እንቅፋቶች አደናቅፈውት ከነበረበት ቦታ ወርዶ ሽሮሜዳ አካባቢ ሊስትሮነት እየሰራ ይገኛል።

ዝቅ ማለትም ሆነ ከፍ ማለትም በጊዜው ቢሆንም የምር ግን ወንድ ልጅ አይጣ... ወንዴ ጥንካሬህ ብርታትህ ለሌሎች አስተማሪ ነው እግዚአብሔር ካንተ ጋር ይሁን።🙏

:- MinAddis



አዳዲስ መረጃዎች እንዲደርስዎ👇
https://t.me/gize_media

ፔጃችንን LIKE በማድረግ ቤተሰብ አድርጉን 👇
https://www.facebook.com/GizeMereja?mibextid=ZbWKwL

Address

Addis Ababa
1000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gize Media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share