14/01/2026
በአይሾው ስፒድ (IShowSpeed) የአዲስ አበባ ጉብኝት ወቅት ብዙዎች ወደ እሱ ለመጠጋትና ባህላችንን ለማስተዋወቅ ሲቸገሩ እንዲሁም ሲጋፉ ተመልክተን ነበር።
ቋንቋውም ሆነ ግርግሩ ተደማምሮ መልእክት ለማስተላለፍ ሲከብድ፣ ምራፌ ገብረማርቆስ የተባለ ይህ ድንቅ ኢትዮጵያዊ ግን በፍጥነት ነገሮችን በሙሉ በእርጋታ ተቆጣጠራቸው።
በምስሉ ላይ እንደምትመለከቱት፣ ምራፌ በብቃት ከመተርጎም አልፎ፣ ስፒድ ስለ ኢትዮጵያ ታሪክና ባህል ትክክለኛውን መረጃ እንዲያገኝና እንዲረዳ ትልቅ ስራ ሰርቷል።
በተለይም በአድዋ ድል መታሰቢያ አካባቢ ሲደርሱ፣ ምራፌ ለቦታውና ለሰማዕታት ጀግኖች ያለውን ክብር ለማሳየት ስፒድን ጫማውን እንዲያወልቅና በባዶ እግሩ እንዲራመድ ጠይቆታል።
የሚገርመው ነገር፣ ስፒድም ይህንን ጥያቄ ያለ ምንም ማመንታት ተቀብሎ በባዶ እግሩ በመሄድ ለጀግኖቻችን ክብር እንዲሰጥ አድርጓል። ብዙዎች በግርግር መሃል ሲጠፉ፣ ምራፌ ግን በተረጋጋ መንፈስ ስፒድን እየመራ የኢትዮጵያን ታላቅነት በደንብ አስረድቷል።
አሁን ላይ የኢትዮጵያ ኢንተርኔት ማህበረሰብ የዚህን ሰው ብቃትና በራስ መተማመን እያደነቀው ይገኛል። እንግዳን በአግባቡ ማስተናገድና ታሪክን ማስከበር ማለት ይህ ነው! ምራፌ፣ በሰዎች መሃል ጎልተህ በመውጣትህና ሀገርህን በዚህ መልኩ በማስጠራትህ ክብር ይገባሃል!
:- Ethio Lead
አዳዲስ መረጃዎች እንዲደርስዎ👇
https://t.me/gize_media
ፔጃችንን LIKE በማድረግ ቤተሰብ አድርጉን 👇
https://www.facebook.com/GizeMereja?mibextid=ZbWKwL