Asham TV / አሻም ቲቪ

Asham TV / አሻም ቲቪ Asham TV is a privately owned media company, based in Addis Ababa, Ethiopia, that provides news and other programs
(1)

26/07/2025

የዝግጅት ጥቆማ - አሻም ወቅታዊ በዚህ ሳምንት

የአሻም ወቅታዊ ዝግጅት ክፍል በዚህ ሳምንት ከአዲስ አበባ ከተማ 748 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ወደ ሚገኘው የጎንደር ዩኒቨርስቲ አቅንታለች፡፡ በዚህም በዩኒቨርስቲው እየተከበረ የሚገኘውን የ70 አመት የምስረታ እና የዩኒቨርስቲው የማስተማሪያ ሆስፒታል 100ኛ አመት (አንድ ምዕተ-ዓመት) ክብረ- በዓላት እንዲሁም ዩኒቨርስቲው የሚታወቅበትን ‹‹የጎንደር የቃል ኪዳን ቤተሰብ›› ሀገር ዓቀፍ የልምድ ልውውጥ መርሀ ግብሩን መነሻ በማድረግ የዩኒቨርስቲውን የ70 ዓመታት ጉዞ ወደ ኋላ እንዲያስቃኙዋት ከዩኒቨርስቲው የምርምርና የትብብር ም/ፕሬዝዳንት አይንእሸት አዳነ (ዶ/ር) ጋር ቆይታ አድርጋለች፡፡
ከዚህ በተጨማሪ ም/ፕሬዝዳንቱ አሁናዊ የዩኒቨርስቲው ፕሮጀክቶች መኖራቸውንም አንስተው ነግረዋታል፡፡ይህንኑ ዛሬ ምሽት ከ2፡00 ሰዓት ጀምሮ በሚተላለፈው አሻም ወቅታዊ ሳምንታዊ ዝግጅት ትከታተሉት ያመቻችሁ ዘንድ በአሻም የቴሌቭዥን ቀጥታ እና በተመሳሳይ ሰዓት በዩቱብ ቻናላችን ማግኘት እንደምትችሉ ለመጠቆም እንወዳለን፡፡

አሻም ለሁላችን!

25/07/2025

🎻 በዚህ ሳምንት

ስለ #ኮንቴምፖራሪ #ክላሲካል ሙዚቃ ከዕውቋ #ኦስትሪያዊ ቫዮሊኒስት አኔት ፍሪትዝ ጋር ያደረገውን ቆንጆ ቆይታ ቅዳሜ ምሽት 1:00 ሰዓት ላይ በ 🎻 ይጠብቁን።

🎻 this week

presents the renowned Annette Fritz about music stay tuned on Saturday at 7pm on 🎻

🏷ኢጋድ አስቀድሞ ግጭትን የመከላከል ዲፕሎማሲ ልዩ ትኩረት በመስጠት የዲፕሎማሲ ተልዕኮዎችን በማዘጋጀት እየሰራ መሆኑ ተጠቆመ፡፡🏷ኢትዮጵያ የጣሊያን በግብርና፣ በጤና ፣በትምሕርት እና በኢነርጂ...
25/07/2025

🏷ኢጋድ አስቀድሞ ግጭትን የመከላከል ዲፕሎማሲ ልዩ ትኩረት በመስጠት የዲፕሎማሲ ተልዕኮዎችን በማዘጋጀት እየሰራ መሆኑ ተጠቆመ፡፡

🏷ኢትዮጵያ የጣሊያን በግብርና፣ በጤና ፣በትምሕርት እና በኢነርጂ ዘርፎች የቆየ እና ጠንካራ ግንኙነት ያላቸው መሆኑ ተጠቆመ፡፡

🏷ሀገራዊ የ2018 በጀት አመት እቅድ እና የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት 2018 በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ ውይይት ተካሄደ፡፡

ሀገር አቀፍ እና ዓለም አቀፋዊ ወቅታዊ ጉዳዮችን በትኩሱ ለተመልካች በማድረስ አሻም ቴሌቪዥን ከፍተኛ ተቀባይነት አግኝታልች፡፡ አሻም ሰባት እንዲሁም አሻም ምሽት ዜና የሕዝብ ድምጽ በ....

📖እንቆቅልሽ/ህ
25/07/2025

📖እንቆቅልሽ/ህ

🏷በኢትዮጵያ የተደራጀ የመረጃ ቋት አለመኖሩ ለጥናትና ምርምር ተግዳሮት እንደሆነ ተገለጸ፡፡🏷አንጋፋው የጎንደር ዩኒቨርስቲ የመማሪያ ሆስፒታል አንድ ምዕተ አመቱን በዛሬው ዕለት ደፈነ።🏷የመታሃ...
24/07/2025

🏷በኢትዮጵያ የተደራጀ የመረጃ ቋት አለመኖሩ ለጥናትና ምርምር ተግዳሮት እንደሆነ ተገለጸ፡፡

🏷አንጋፋው የጎንደር ዩኒቨርስቲ የመማሪያ ሆስፒታል አንድ ምዕተ አመቱን በዛሬው ዕለት ደፈነ።

🏷የመታሃራ ስኳር ፋብሪካ በ2017 በጀት አመት የእቅዱን 90 በመቶ ማሳት መቻሉን ለአሻም ተናገሩ፡፡

https://youtu.be/RUkSf1eXNvU

የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈፃሚ ፍሬሕይወት ታምሩአሻም ዜና|ዕለተ ሐሙስ ፣ሐምሌ 17 ቀን 2017 ዓ.ምየኢትዮ - ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈፃሚ ፍሬህይወት ታምሩ የ2017 በጀት ዓመት የስራ ሪ...
24/07/2025

የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈፃሚ ፍሬሕይወት ታምሩ

አሻም ዜና|ዕለተ ሐሙስ ፣ሐምሌ 17 ቀን 2017 ዓ.ም

የኢትዮ - ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈፃሚ ፍሬህይወት ታምሩ የ2017 በጀት ዓመት የስራ ሪፖርት ባቀረቡበት በዛሬው ዕለት የሚመሩት የቴሌኮም ተቋማቸው 162 ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘቱን ይፋ በማድረግ የደበኞቹ ቁጥርም መጨመሩን አስታውቀዋል።
ኢትዮ - ቴሌኮም በ2017 በጀት ዓመት ዲጂታል ኢትዮጵያ እውን ለማድረግ የተለያዩ አዳዲስ ስራዎች አገልግሎት ላይ መዋላቸው ተጠቁሟል።
በተጨማሪም ደንበኛ ከማፍራት አንጻር በበጀት ዓመቱ ብቻ 7 ሚሊዮን አዳዲስ ደንበኛ በማፍራት 99 ነጥብ 7 በመቶ እቅዱን ማሳካት የተቻለ መሆኑን የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ የሆኑት ወይዘሪት ፍሬህይውት ታምሩ ገልጸዋል።
ከባለፈው በጀት ዓመት አንጻር በ6 ነጥብ 2 በመቶ ማደግ የቻለበት መሆኑ ተጠቁሟል። ይህ በእንዲህ እንዳለም የቴሌብር አጠቃላይ ደንበኞች ቁጥር 54 ነጥብ 84 ሚሊዮን መድረሱ እና የ 4 ነጥብ 93 ትሪሊየን ብር ዝውውር መፈፀሙም ዋና ሥራ አስፈፃሚዋ መናገራቸውን አሻም በስፍራው በታደመችበት ሰምታለች።
በአጠቃላይ በአሁን ሰዓት 86 ነጥብ 1 ሚሊዮን ዲቫይሶች ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር መገናኘታቸው በአመታዊ ሪፖርቱ ተጠቁሟል።
ተጨማሪ ዝርዝር መረጃዎችን በምሽት የቢዝነስ ዘገባ ላይ ይከታተሉ።

በመሀመድንጉስ አብዱ

አሻም ለሁላችን!

አንጋፋው የጎንደር ዩኒቨርስቲ የመማሪያ ሆስፒታል 100ኛ ዓመቱን በዛሬው ዕለት ደፈነ።የአሻም ዜና | ዕለተ ሐሙስ ፣ሐምሌ 17 ቀን 2017 ዓ.ምበኢትዮጵያ  በተለይም በጤናው ዘርፍ ቀደምትና ...
24/07/2025

አንጋፋው የጎንደር ዩኒቨርስቲ የመማሪያ ሆስፒታል 100ኛ ዓመቱን በዛሬው ዕለት ደፈነ።

የአሻም ዜና | ዕለተ ሐሙስ ፣ሐምሌ 17 ቀን 2017 ዓ.ም

በኢትዮጵያ በተለይም በጤናው ዘርፍ ቀደምትና የመጀመሪያው ትውልድ ከሚባሉ ዩኒቨርስቲዎች ውስጥ የሚመደው የጎንደር ዩኒቨርስቲ የተመሠረተበትን 70ኛ ዓመት እና የመማሪያ ሆስፒታሉ ምስረታ ደግሞ 100ኛ ዓመቱን መድፈኑን አስመልክቶ በዛሬው እለት የተለያዩ መርሀ ግብሮችን በማዘጋጀት በድምቀት እያከበረ ይገኛል።

በመርሀ ግብሩ ከታደሙ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች መካከልም የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ኢንዲስትሪ ሚኒስትሩ መላኩ አለበል እንደሚገኙበትም አሻም በስፍራው መመልከት ችላለች። በዚሁ መድረክ ንግግር ያደረጉት ሚኒስትሩ ከሰሞኑ ዩኒቨርስቲው ካከበራቸው በዓላት መካከል አንዱ ስለሆነው የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች የቃል ኪዳን ቤተሰብ ላይ ያላቸውን አስተያየት አክለዋል። በዚህም የከተማው ማህበረሰብ እያደረገ የሚገኘው ይበል የሚያስብል በጎ እና የሚያስተሳስር ስራ ኢትዮጵያን በአንድነት የሚያጸና ተግባር ነውም ሲሉ አድንቀዋል።

ተጨማሪ ዝርዝር መረጃዎችን በምሽት የዜና እወጃ ሰዓት ይጠብቁ።

ኢየሩሳሌም ዓለሙ

ከጎንደር

አሻም ለሁላችን!

🏷አማራጭ የመምህራን ትምህርት ፕሮግራም ሊተገበር እንደሆነ ተገለፀ፡፡🏷ኢትዮጵያ በአህጉራዊ ፈተናዎች ውስጥ ዘላቂ የምግብ ሥርዓት ለመገንባት እየሰራች  መሆኑን የፕላንና ልማት ሚኒስቴር ገለጸ፡...
24/07/2025

🏷አማራጭ የመምህራን ትምህርት ፕሮግራም ሊተገበር እንደሆነ ተገለፀ፡፡

🏷ኢትዮጵያ በአህጉራዊ ፈተናዎች ውስጥ ዘላቂ የምግብ ሥርዓት ለመገንባት እየሰራች መሆኑን የፕላንና ልማት ሚኒስቴር ገለጸ፡፡

https://youtu.be/uwb55NvJ7y8?si=VVAtWv8hZPbtzGrN

🏷የባሕር - ዳር ከተማ የምሽት ሰዓት ገደብ መነሳቱን የከተመዋ ፖሊስ መምሪያ ለአሻም ገለፀ ።🏷የኢትዮጵያ አየር መንገድ 118 ሚሊየን ዶላር የሚያወጡ የአውሮፕላን ክፍሎች መለዋወጫ እንዳለው ...
23/07/2025

🏷የባሕር - ዳር ከተማ የምሽት ሰዓት ገደብ መነሳቱን የከተመዋ ፖሊስ መምሪያ ለአሻም ገለፀ ።

🏷የኢትዮጵያ አየር መንገድ 118 ሚሊየን ዶላር የሚያወጡ የአውሮፕላን ክፍሎች መለዋወጫ እንዳለው አስታወቀ፡፡

🏷ህብረተሰቡ የሀገር ውስጥ ምርትን የማይጠቀመው በምርቶች ላይ በሚታየው የጥራት ችግር ነው ሲል ማህበሩ አስታወቀ ።

🏷ድህነትና ስራ አጥነት በኢትዮጵያ እንዳይሰራፋ ትብብር ኢትዮጵያ ከፍተኛ አስተዋፆ እያደረገ መሆኑ ተጠቆመ

https://youtu.be/esbOLe-7c20

የባሕር ዳር ከተማ የምሽት ሰዓት ገደብ መነሳቱን የከተመዋ ፖሊስ መምሪያ ለአሻም ገለፀ ።የአሻም ዜና| ዕለተ ረቡዕ ሐምሌ 16 ቀን 2017 ዓ.ምበክልሉ ተቀስቅሶ የነበረውን የፀጥታ መደፍረስ ...
23/07/2025

የባሕር ዳር ከተማ የምሽት ሰዓት ገደብ መነሳቱን የከተመዋ ፖሊስ መምሪያ ለአሻም ገለፀ ።

የአሻም ዜና| ዕለተ ረቡዕ ሐምሌ 16 ቀን 2017 ዓ.ም

በክልሉ ተቀስቅሶ የነበረውን የፀጥታ መደፍረስ ተከትሎ አለመረጋጋቶች ከነበሩባቸው የክልሉ ከተሞች አንዱ ባህርዳር እንደነበረች ለአሻም ያስታወሱት፤የከተማው ፖሊስ መምሪያ አዛዥ ኮማንደር ዋለልኝ ቢምረው ናቸው። ሰላምና ፀጥታውን በአንፃራዊነት ለመመለስ የፀጥታ ሀይሉ የተቀናጀ ስራ ነውም ብለዋል።

በክልሉ የመልካም አስተዳደር ጋር በተያያዘ ግጭት ተቀስቅሶ ነበር ያሉት ኮማንደሩ ፤ ይህንኑ ግርግር ተጠቅመው ለግል ጥቅማቸው የሰሩ በከተመዋ ዝርፊያ ፣ ግድያ እና የንብረት ውድመት ፈፅመዋል ብለዋል።

በ2015 ዓ.ም መገባደጃ ጀምሮ በክልሉ በተቀሰቀሰው ግጭትን ተከትሎ ሰላምና ፀጥታውን ለማረጋጋት አስቸኳይ የጊዜ አዋጅ በመታወጁ ክልሉ በኮማንድ ፖስት ስር መቆየቱንም አስታውሰዋል።
በዚህም ከ1 ዓመት ለተሻገረ ጊዜ የባሕር-ዳር ከተማ የምሽት የሰዓት ገደብ ለእግረኛ እስከ ምሽት 2 ሰዓትና ለትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪ ተሽከርካሪዎች ደግሞ እስከ ምሽት 12:00 ሰዓት እንደነበር ኮማንደሩ አስታውሰዋል።

ይሁን እንጂ በከተመዋ የፀጥታ አካላቱ በሰሩት የቀናጀ ባሉት ስራ የከተማዋን ሰላምና ፀጥታዋን በአንፃራዊነት መመለስ በመቻሉ የምሽት የሰዓት ገደቡ የከተማው ም/ቤት መክሮ ከሰሞኑ ማንሳቱን ኮማንደሩ ለአሻም ገልፀውላታል። በዚህም ለሞተርና ለባለሶስት እግር ተሽከርካሪዎች (ባጃጅ) እስከ ምሽቱ 12 ሰዓት ብቻ የነበረው ገደብ ሲቀጥል፤ ለእግረኛና ለሌሎች ተሽከርካሪዎች ደግሞ ሙሉ ለሙሉ (ለ24 ሰዓት) ክፍት መደረጉን አረጋግጠዋል።
የክልሉን ሰላም የማይፈልጉ ያሏቸውና ፀረ -ሰላም ኃይል የተባሉ አካላት የክልሉን ህዝብ ብሎም የከተመዋን ህዝብ ሰላምና ፀጥታ፣ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ላይ ከፍተኛ አሉታዊ ጫና ማሳደራቸውን ተናግረዋል።

በግጭቱም ያልታጠቁ ሰላማዊ ሰዎች ግድያ ፣የመንገድ መዘጋት፣ የማህበራዊ መስተጋብር መሸርሸር፣ ማህበረሰቡ ሰቆቃ ውስጥ የገባበት ፣የመሰረተ ልማቶች ውድመት፣ የፋብሪካ ምርቶችን ማቀሳቀስ አለመቻል ደረጃ ላይ ተደርሶ እንደነበርም አስታውሰው፤ አሁን ባለው ነባራዊ ሁኔታ ከተማዋ ከኮማንድ ፖስት ውጭ በመሆን ወደ ቀደመ ሰላሟ እየተመለሰች በመሆኗ የቱሪስት ፍሰቱም እየጨመረ ነው ሲሉ ለአሻም የነገሯት ደግሞ የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ ጎሹ እንዳለማሁ ናቸው። " የታጠቀ እና ፀረ-ሰላም" ሲሉ የጠሩት አካልም በማህበራዊ ሚዲያ በተደራጀ መልኩ ያለ በማስመሰል ፕሮፖጋንዳ የሚነዛው እንጂ መሬት ላይ እየከሰመ ነውም ሲሉ አጣጥለዋቸዋል።

ተጨማሪ ዝርዝር መረጃዎችን በምሽት የዜና እወጃ ሰዓት ይጠብቁን።

ኢየሩሳሌም ዓለሙ

ከባሕር-ዳር

አሻም ለሁላችን!

🏷የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው የግሉ ዘርፍ በሀገራዊ ኢኮኖሚው ላይ ያለውን ሚና ማሳደጉን የገንዘብ ሚኒስቴር አስታወቀ ።🏷የትምህርት ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት አመራሮችና ሰራተኞች የአረንጓዴ አሻራ...
23/07/2025

🏷የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው የግሉ ዘርፍ በሀገራዊ ኢኮኖሚው ላይ ያለውን ሚና ማሳደጉን የገንዘብ ሚኒስቴር አስታወቀ ።

🏷የትምህርት ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት አመራሮችና ሰራተኞች የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በሸገር ከተማ አካሄዱ።

🏷ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ለሀገራዊ ዕድገት የማይተካ ሚና አለው ተባለ።

🏷የንግድ ተቋማት የምሽት የንግድ እንቅስቃሴ የከተማዋን ፈጣን ዕድገት ተከትሎ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ እንቅስቃሴን ይበልጥ እንደሚያሳድግ ተጠቆመ።

ሀገር አቀፍ እና ዓለም አቀፋዊ ወቅታዊ ጉዳዮችን በትኩሱ ለተመልካች በማድረስ አሻም ቴሌቪዥን ከፍተኛ ተቀባይነት አግኝታልች፡፡ አሻም ሰባት እንዲሁም አሻም ምሽት ዜና የሕዝብ ድምጽ በ....

Address

Addis Ababa

Opening Hours

Monday 08:30 - 17:30
Tuesday 08:30 - 17:30
Wednesday 08:30 - 17:30
Thursday 08:30 - 17:30
Friday 08:30 - 14:30
Saturday 08:30 - 00:00

Telephone

+251902484020

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Asham TV / አሻም ቲቪ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Asham TV / አሻም ቲቪ:

Share

Category