Alem TV

Alem TV Alem TV is an international Television channel based in Addis Ababa, Ethiopia focusing on Economic,

መረጃ ለአንድ ሀገርና ህዝብ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ እድገት እጅግ ከፍተኛ ሚና ይጫወታል፡፡ “የመረጃ ዘመን” በመባል በሚታወቀው የ21ኛው ክፍለ ዘመን መረጃ የህይወት አንዱና ዋነኛው አካል ሆኗል፡፡ ዘመናዊ የመረጃና የኮሚኒኬሽን ቴክኖሎጂ መስፋፋት ለመረጃ ዝውውር ከፍተኛ እገዛ አድርጓል፡፡ የድረ-ገጽ /ኢንተርኔት/ ቴክኖሎጂ ጥቅም ላይ ከዋለበት የ1990ዎቹ መጀመሪያ ጀምሮ የዓለማችን የኢኮኖሚ፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ለውጦች ዋነኛ ማዕከል ሆኖ በማገልገል ላይ ይገኛል-መረጃ፡፡

አፍሪካ እንደ ቀሪው የዓለም ክፍል ሁሉ ከዚህ ዘርፍ ተጠቃሚ ሆናለች፡፡ በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ኢንተርኔትን ጨምሮ የሌሎች የመረጃ ቴክኖሎጂዎች

ማለትም ሬድዮ፣ ቴሌቪዥን፣ የተንቀሳቃሽ ስልክ ወዘተ አገልግሎቶች ተጠቃሚዎች መሆን ችለዋል፡፡ በተለያዩ የሙያ መስክ፣ የትምህርትና የኑሮ ደረጃ ያሉ ወጣት አፍሪካዊያን ከዚህ ቴክኖሎጂ ተቋዳሽ ሆነዋል፡፡ ባብዛኛው የአፍሪካ ሀገሮች ከተሞችና መንደሮች ነዋሪዎች ለማህበራዊም ሆነ ለኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ዘመኑ ያፈራቸውን የመገናኛ ዘዴዎች በስፋት ይጠቀማሉ፡፡ ኢትዮጲያ ከነዚህ የአፍሪካ ሀገሮች አንዷ ናት፡፡ የኢትዮጲያ የመረጃና የኮሚኒኬሽን ቴክኖሎጂ በተለያዩ መለኪያዎች ሲመዘንናከሰሃራ በታች ካሉ ከሌሎች የአፋሪካ ሀገሮች አንጻር እንኳ ሲወዳደር “አማካኝ” ተብሎ ሊፈረጅ ቢችልም ባለፉት ጥቂት ዓመታት በዘርፉ የታየው መሻሻልና ለውጥ ቀላል አይደለም፡፡ በኢትዮጲያ ውስጥ በዝቅተኛ ደረጃ ከሚገኙ የሚዲያ ዘርፎች አንዱ የቴሌቪዥን ዘርፉ ነው፡፡ ኢትዮጲያ ውስጥ አገልግሎት የሚሰጡ የቴሌቪዥን ጣቢያዎች በቁጥርም ሆነ በጥራት “በማደግ ላይ ያለ” ሊባል የሚችል ነው፡፡ የሌሎች የሚዲያ መስኮች ማለትም የእድገት ደረጃም ከቴሌቪዥን ዘርፉ ብዙ የተለየ አይደለም፡፡ በዚህም ምክንያት በመረጃ ፍላጎትና አቅርቦት መካካል ሰፊ ልዩነት እንዲኖር ግድ ሆኗል፡፡ ዜጎች የመረጃ ፍላጎታቸውን ለማርካት በተለያዩ ቋንቋዎች የሚዘጋጁ የውጭ ሀገር የመረጃ ምንጮችን ለመጠቀም ሙከራ ቢያደርጉም በቋንቋና በአቅም ውስንነት ምክንያት ቁጥሩ ቀላል የማይባል የህብረተሰብ ክፍል አስተማማኝና ወቅታዊ መረጃ የማግኘት እድሉ ተገድቧል፡፡

በመሆኑም ይህንን የመራጃ እጥረት በተወሰነ ደረጃ መቀነስና ዜጎች አስተማማኝና ፈጣን መረጃ በቀላሉ እንዲያገኙ ማድረግ፣ የሀገራችንን ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚዊና ፖለቲካዊ እድገት በመረጃ አቅርቦት ማገዝ እጅግ አስፈላጊ ነው፡፡ ሳይንስና ቴክኖሎጂን ማስፋፋትና የቴክኖሎጂ ሽግግርን ማሳለጥ፣ በዜጎች ክፍሎች መካከል ባህላዊ መስተጋብርን ማገዝ እንዲሁም ዜጎች በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ አማራጭ የመረጃ ምንጭ እንዲኖራቸው መርዳት ይደር የማይባል የወቅቱ አንገብጋቢ ጥያቄ ሆኗል፡፡ ከላይ በትንሹ የተገለጹት ዓልአቀፋዊ እና ሀገራዊ ምክንያቶች ለ“ዓለምቲቪ” መወለድ ዋነኛ ምክንያቶች ናቸው፡፡ ጣቢያው እ.ኤ.አ. 2015 በቱርክ በተመዘገበና “ብራይት ሚዲያ ኔትዎርክ” ኃ.የ.የግል ኩባንያ አማካኝነት የተመሰረተ ሲሆን ስርጭቱን ከቱርክ ሪፖብሊክ የኢስታንቡል ከተማ ያስተላልፋል፡፡ ዓለምቲቪ በሚሰጠው የሚዲያ አገልግሎት በተለይም በኢትዮጲያ ውስጥ ያለውን የመረጃ ክፍተት ለማስወገድና በሀገር ውስጥም ሆነ ከሀገር ውጪ የሚኖሩ ኢትዮጲያውያን ፈጣንና አስተማማኝ መረጃ ማግኘት ይችሉ ዘንድ ከፍተኛ ሚና እንደሚጫወት ይጠበቃል፡፡

የቴሌቪዥን ጣቢያው ፕሮግራሞቹንና የሚዲያ ስራዎቹን በድረገጽ፣ በዌብ ቲቪና በሳተላይት አማካኝነት እንዲሁም በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያዎች የሚያሰራጭ ሲሆን በአቀራረብም ሆነ በይዘታቸው ልዩ ፕሮግራሞችን በማዘጋጀት ተመልካቾችን እያዝናና ለማስተማር እንዲሁም ለሀገራችን የሚዲያ ሴክተር መሻሻል ተግቶ ይሰራል፡፡

“ዓለምቲቪ” የመረጃ ዓለም!!

26/01/2020

ዓለም ቲቪ በአዲስ መልክ እንቅስቃሴ ጀመረ!!
ዓለም ቲቪ ላለፉት ጥቂት ዓመታት አንድ ጠንካራ እና ተጽኖ ፈጣሪ የቴሌቪዥን ጣቢያ ሆኖ ለመውጣት ሲያደርገው የነበረው ጥረት በፋይናንስ እና ሌሎች ተግዳሮቶች ምክንያት የተስተጓጎለ ቢሆንም፣ ድርጅቱ ያጋጠሙትን መሰናክሎች አልፎ ራእዩን እውን ለማድረግ ስራውን ለአፍታም ሳያቋረጥ ቀጥሏል፡፡

ዓለም ቲቪ ዛሬም ጥረቱን አጠናክሮ በመቀጠል እና ወሳኝ የአደረጃጀት ለውጥ በማድረግ ለሀገራችን አንድ ተጨማሪ የቴሌቪዥን አገልግሎት ለመፍጠር በአዲስ ኃይል እና አደረጃጀት እንቅስቃሴ ጀምሯል፡፡

ዓለም ቲቪ በተለይ ባለፉት ሁለት አመታት በሀገራችን የተፈጠረውን የፖለቲካ ለውጥ ታሳቢ ያደረገ የፕሮግራም እና የኮንሴፕት ሽግሽግ ያደረገ ሲሆን፣ በሀገራችን የብሮድካስቲንግ ህግ መሰረት የአሰራር ለውጥ ለማካሄድ የሚያሰፈልጉ የህግ ማሻሻያዎችንም በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡

በተለያዩ የፖሊሲ፣ አስተዳደራዊ፣ የቴክኖሎጂ፣ የሰው ኃይል እና ሌሎች ተያያዥ ችግሮች የታጠረውን የሀገራችን የፕሮድካስቲግ ሴክተር፣ በአንድ እርምጃ ወደፊት ለማራመድ አስተዋጾ ይኖረዋል ተብሎ የሚጠበቀው የዓለም ቲቪ እውን ሆኖ ለማየት የቴሌቪዥኑ አደራጆች በአዲስ አስተሳሰብ እና አመራር እንቅስቃሴ ጀምረዋል፡፡
የዓለም ቲቪ ፕሮግራሞችን በቴሌቪዥን መስኮት የምናይበትን ግዜ ሩቅ አይሆንም፡፡

ከዓለም ቲቪ ፕሮግራሞች አንዱ የሆነውን “ለውጥ” የተሰኘ ፕሮግራም ለቅምሻ ጀባ ብለናል፡፡

ዓለም ቲቪ፡ የመረጃ አለም፡፡

26/06/2018

በእርሶ ግምት በኢትዮጲያ ውስጥ በመካሄድ ላይ ባለው ለውጥ ቀንደኛ ተቃዋሚ ማን ሊሆን ይችላል?
ሀሳብዎን በኮሜንት ይግለጹ

በደሴና በደብረማቆስ ከተሞች ዶ/ር አብይ ህመድን የሚደግፍ ሰልፍ ተካሄደ፡፡ ዘገባው የኢቢሲ ነው፡፡
24/06/2018

በደሴና በደብረማቆስ ከተሞች ዶ/ር አብይ ህመድን የሚደግፍ ሰልፍ ተካሄደ፡፡ ዘገባው የኢቢሲ ነው፡፡

Ethiopian Broadcasting Corporation is a national media which disseminates its news and programs world wide via Television,Radio and Website

24/06/2018

Ethiopian Broadcasting Corporation is a national media which disseminates its news and programs world wide via Television,Radio and Website

23/06/2018
ዛሬ በአዲስ አበባ የተካሄደውን የድጋፍና የምስጋና ሰልፍ እንዲሁም ሰልፉን ለማወክ የተቃጣውን ኃላፊነት የጎደለው ጥቃት በርካታ የዓለም አቀፍ የሚዲያ ተቋማትና የዜና አውታሮች ሰፊ ሽፋን የሰጡ...
23/06/2018

ዛሬ በአዲስ አበባ የተካሄደውን የድጋፍና የምስጋና ሰልፍ እንዲሁም ሰልፉን ለማወክ የተቃጣውን ኃላፊነት የጎደለው ጥቃት በርካታ የዓለም አቀፍ የሚዲያ ተቋማትና የዜና አውታሮች ሰፊ ሽፋን የሰጡት ሲሆን አልጀዚራ እንደሚከተለው ዘግቦታል፡፡

Explosion at rally attended by supporters of reformist Prime Minister Abiy Ahmed kills at least one and wounds scores.

23/06/2018

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Alem TV posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Alem TV:

Share