ተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከል - Tewahedo Media Center - TMC

ተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከል - Tewahedo Media Center - TMC "TMC was established by His Beatitude Abune Henok on July 30, 2021.
(2)

Our mission is to ensure that Orthodox Christians have access to vital information and that the Gospel is readily available to all." አላማ

1.ተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አማራጭ ድምፅ በመሆን የቅድስት ቤተ ክርስቲያናችንን ሀገራዊ እና ዓለምአቀፋዊ አገልግሎቶችን ፣ የስብከተ ወንጌል አገልግሎትን ፣ የቋንቋ ብዝኃነትን በማስተናገድ መላው ኦርቶዶክሳውያን የቤተ ክርስቲያናቸውን ሁለንተናዊ እንቅስቃሴ ዶግማዋንና ቀኖናዋን በጠበቀ መልኩ ተደራሽ ለማድረግ የተሰናዳ ተቋም ነው።

2.ዘመናዊ የሆነ የሚዲያ ተቋም አደ

ረጃጀትን በመጠቀም በሀገራችን በከተማና በገጠር እንዲሁም ከሀገረ ኢትዮጵያ ውጭ ያሉ ኦርቶዶክሳውያን ምዕመናን ተዓማኒና ፈጣን መረጃዎችን እንዲያገኙ ማድረግ።

3. .ለአንድ የሚዲያ ተቋም የሚያስፈልጉ ተግባራትን በመከወን የቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን አማራጭ ድምፅ በመሆን ምዕመናን የወንጌል አገልግሎትንና መረጃዎችን አግኝተው ለሌሎች ወዳጆቻቸው እንዲያደርሱ በማድረግ የቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ድምፅ በዓለም ላይ ከፍ ብሎ እንዲሰማ ማድረግ።

ወእሁበክሙ ኖሎተ ዘከመ ልብየ ወይርዕዩክሙ በጥበብ ወበእእምሮ፤ እንደ ልቤም በግ ጠባቆችን እሰጣችኋለሁ በእውቀትና በማስተዋልም ይጠብቁአችኋል።  ኤርምያስ ፫፥፲፭የብፁዕ አቡነ ሄኖክ ሊቀ ጳጳስ...
09/07/2025

ወእሁበክሙ ኖሎተ ዘከመ ልብየ ወይርዕዩክሙ በጥበብ ወበእእምሮ፤ እንደ ልቤም በግ ጠባቆችን እሰጣችኋለሁ በእውቀትና በማስተዋልም ይጠብቁአችኋል። ኤርምያስ ፫፥፲፭

የብፁዕ አቡነ ሄኖክ ሊቀ ጳጳስ የአቀባበል መርሐግብር ሐምሌ 10 ቀን 2017 ዓ.ም በጆሐንስበርግ መንበረ ጵጵስና ጽርሐ ጽዮን መድኃኔዓለም ካቴድራል

ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ ለ1 መቶ 60 አገልጋዮች ሥልጣነ ክህነት ሰጡ ! ሐምሌ 2 ቀን 2017 ዓ.ም [ተ.ሚ.ማ/ አዲስ አበባ] ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክር...
09/07/2025

ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ ለ1 መቶ 60 አገልጋዮች ሥልጣነ ክህነት ሰጡ !

ሐምሌ 2 ቀን 2017 ዓ.ም [ተ.ሚ.ማ/ አዲስ አበባ]

ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያና የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በ2 ወረዳዎች ያካሄዱትን ሐዋርያዊ ጉዞ አጠናቀዋል።

ብፁዕነታቸው በምንጃር እና በሸንኮራ ወረዳዎች ለ4 ቀናት ያካሄዱትን ሐዋርያዊ ጉዞ ለ1 መቶ 30 የአብነት ደቀ መዛሙርት የዲቁና ለ30 ዲያቆናት የቅስና ሥልጣነ ክህነት በመስጠት ሐዋርያዊ ጉዟቸውን አጠናቀዋል።

ብፁዕነታቸው ባካሔዱት ሐዋርያዊ ጉዞ በሸንኮራ ወረዳ ቤተ ክህነት የተከናወኑ የልማት እንቅስቃሴ የአረርቲ ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተ ክርሰቲያን የሕንጻ ግንባታ ጎብኝተው ለተከናወኑ ተግባራት ቃለ በረከትና የሥራ መመሪያ ሰጥተዋል።

ከ6 መቶ 23 ዓመታት በላይ አገልግሎት የሰጠውንና በ2 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር ግንባታው የተከናወነውን ከ18 አድባራትና ከ44 በላይ ታቦታት የሚከብሩበት የኢራንቡቲ የጥምቀተ ባሕርና ግድብ ባርከውና መርቀው ተግባሩን ላከናወኑ ሁሉ እውቅናና ምሥጋና እንዲሁም ቃለ በረከት ሰጥተዋል።

ከመላው የሀገራችን ክፍል የተውጣጡ በ10 በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ በርካታ ምእመናን በተገኙበተ የመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ዓመታዊ ክብረ በዓል ላይ በታሪካዊው በሸንኮራ ደብረ መንክራት ቅዱስ ዮሐንስ ቤተ ክርስቲያን ከዋዜማው ጀምረው በመገኘት አገልግሎቱንና ሥርአቱን በመምራት በበዓሉ ላይ ለታደሙ ሕዝበ ክርስቲያን ትምህርተ ወንጌልና ቃለ በረከት ሰጥተዋል።

በትናንትናው ዕለትም ለ1 መቶ 30 የአብነት ደቀ መዛሙርት የዲቁና ለ30 ዲያቆናት የቅስና ሥልጣነ ክህነት የሰጡ ሲሆን ስለክብ ክህነትና ስላለው ሐዋርያዊ ሓላፊነትና ስለሚያስገኘ በረከት በሰፊው አስተምረዋል።

በተጨማሪም ሥልጣነ ክህነት እያፀፀ በመጣበት በዚህ አስቸጋሪ ወቅት የተሰጣቸውን ክህነት አክብረው ምእመናንና ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን መጠበቅና ማስጠበቅ እንደሚገባቸው አባታዊ ምክርና ቃለ በረከት በመስጠት ሐዋርያዊ ጉዟቸውን አጠናቀው በክብር ተመለስዋል ሲል አቡቀለምሲስ ሚዲያ ዘግቧል።

የዕለቱን ወንጌል እናንብብ !ሐምሌ 2 ቀን 2017 ዓ.ምየማቴዎስ ወንጌል ም 19 ፥ 16 - ፍጻሜመልካም ዕለተ ረቡዕ  !
09/07/2025

የዕለቱን ወንጌል እናንብብ !
ሐምሌ 2 ቀን 2017 ዓ.ም
የማቴዎስ ወንጌል ም 19 ፥ 16 - ፍጻሜ

መልካም ዕለተ ረቡዕ !


ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ወደ ሰሜን አሜሪካ ሐዋርያዊ ጉዞ አደረጉ !ሐምሌ 1  ቀን 2017...
08/07/2025

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ወደ ሰሜን አሜሪካ ሐዋርያዊ ጉዞ አደረጉ !

ሐምሌ 1 ቀን 2017 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ)


ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በዛሬው ዕለት ለሐዋርያዊ ጉዞ ወደ ሰሜን አሜሪካ አቅንተዋል።

የቅዱስነታቸው የክብር አሸኛኘትም ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የደቡብ ምዕራብ ሸዋ እና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ የምስካየ ኅዙናን መድኃኔ ዓለም ገዳም የበላይ ሓላፊ፣ የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ፤ ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የራያ ሀገረ ስብከት፣የቅርስ ጥበቃ ቤተ መጻሕፍት ወመዘክር መምሪያ፣የማኅበራት ምዝገባ፣ክትትልና ቁጥጥር መምሪያ ሊቀ ጳጳስ፤ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፤ የቅዱስ ሲኖዶስ ጽሕፈት ቤት፤የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽሕፈት ቤት፤ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሥራ ሓላፊዎች በተገኙበት፦ በመጀመርያ በጽርሐ መንበረ ፓትርያርክ ፤ በመቀጠልም በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ተከናውኗል፡፡

ቅዱስነታቸው ባለፉት ተከታታይ ዓመታት ተመሳሳይ ሐዋርያዊ ጉዞዎችን ማድረጋቸው የሚታወስ ነው፡፡

የብፁዕ ወቅዱስነታቸው በረከት አይለየን!

በጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ሰብከት 55 አዳዲስ አማንያን ተጠመቁ ! ሐምሌ 1 ቀን 2017 ዓ.ም [ተ.ሚ.ማ/ አዲስ አበባ] በጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ሰብከት በኧሌ  ዞን ወረዳ ቤተ ክ...
08/07/2025

በጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ሰብከት 55 አዳዲስ አማንያን ተጠመቁ !

ሐምሌ 1 ቀን 2017 ዓ.ም [ተ.ሚ.ማ/ አዲስ አበባ]

በጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ሰብከት በኧሌ ዞን ወረዳ ቤተ ክህነት ስር በሚገኘው የጉማ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን መምህራን ባደረጉት የተቀናጀ ጥረት ፤ በቃርቃርቴ ስብከተ ኬላ 55 ሰዎች ከሌላ እምነት አምነውና ተጠምቀው በትናንትናው ዕለት የሥላሴን ልጅነት ተቀብለዋል ።

ይህን መንፈሳዊ ተግባር ለማገዝ በወረዳው ማዕከል የሚገኘው ማኅበረ ቅዱሳን የበኩሉን አስተዋጽኦ ማድረጉን ጨምሮ የሀገረ ስብከቱ ሚዲያ ዘግቧል።

የዕለቱን ወንጌል እናንብብ !ሐምሌ 1 ቀን 2017 ዓ.ምየዮሐንስ ወንጌል ም 20 ፥ 19 - ፍጻሜመልካም ዕለተ ሠሉስ  !
08/07/2025

የዕለቱን ወንጌል እናንብብ !
ሐምሌ 1 ቀን 2017 ዓ.ም
የዮሐንስ ወንጌል ም 20 ፥ 19 - ፍጻሜ

መልካም ዕለተ ሠሉስ !


የመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ በዓለ ልደት አከባበር በሸንኮራ ደብረ መንክራት ቅዱስ ዮሐንስ ቤተ ክርስቲያን የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ በተገኙበት በምስልሰኔ 30 ቀን...
07/07/2025

የመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ በዓለ ልደት አከባበር በሸንኮራ ደብረ መንክራት ቅዱስ ዮሐንስ ቤተ ክርስቲያን የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ በተገኙበት በምስል

ሰኔ 30 ቀን 2017 ዓ.ም(ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ)
+++

ምስል፦ አቡቀለምሲስ ሚዲያ

ብፁዕ  አቡነ ናትናኤል የሚኒሶታ፣ ኮሎራዶና አካባቢው አህጉረ ስብከት ሊቀጳጳስ  በዴንቨር ኮሎራዶ ደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው። ሰኔ 30 ቀን 2017 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ )ብፁዕነታ...
07/07/2025

ብፁዕ አቡነ ናትናኤል የሚኒሶታ፣ ኮሎራዶና አካባቢው አህጉረ ስብከት ሊቀጳጳስ በዴንቨር ኮሎራዶ ደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው።

ሰኔ 30 ቀን 2017 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ )

ብፁዕነታቸው ዴንቨር ኢንተርናሽናል አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ ብፁዕ አቡነ ኤልያስ ሲዊዲን ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ ብፁዕ አቡነ ጢሞቴዎስ የዳውር ኮንታ ሐላባ ጠባሮ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ የሀገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጅ መልአከ ብርሃን ዘለዓለም መንግስቱ፣ መልአከ መዊዕ ቀሲስ ሔኖክ ተገኝ የሀገረ ስብከቱ ዋና ፀሐፊ ፣የገዳማት የአድባራት አስተዳዳሪዎች ፣እንዲሁም በከተማው የሚገኙ ካህናትና መዘምራን ደማቅ አቀባበል አድርገውላቸዋል።

ለብፁዕ አቡነ ናትናኤል መንበረ ጵጵስና ዳግማዊት ግሸን ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን ደማቅ የአቀባበል መርሐ ግብር የተደረገላቸው መሆኑን የሀገረ ስብከቱ ሚዲያ ክፍል በላከልን ዘገባ ገልጿል።

የቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ በዓለ ልደት በቦሌ ደብረ ሳሌም መድኃኔዓለም፣ ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅና አቡነ አረጋዊ ካቴድራል ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ ሊቀ ጳጳስ በተገኙበት ተከብሯል።አከባበር በፎቶሰኔ ...
07/07/2025

የቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ በዓለ ልደት በቦሌ ደብረ ሳሌም መድኃኔዓለም፣ ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅና አቡነ አረጋዊ ካቴድራል ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ ሊቀ ጳጳስ በተገኙበት ተከብሯል።

አከባበር በፎቶ
ሰኔ 29 ቀን 2017 ዓ.ም [ተ.ሚ.ማ/ አዲስ አበባ]

ፎቶ፦ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ

አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ሰኔ ሠላሳ በዚህች ዕለት ነቢይ ሰማዕትና ሐዋርያ የሆነ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ተወለደ ። +++ ሰኔ ሠላሳ በዚህች ዕለት ነቢይ ...
07/07/2025

አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ሰኔ ሠላሳ በዚህች ዕለት ነቢይ ሰማዕትና ሐዋርያ የሆነ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ተወለደ ።

+++

ሰኔ ሠላሳ በዚህች ዕለት ነቢይ ሰማዕትና ሐዋርያ የሆነ መጥምቁ ዮሐንስ ተወለደ። ይህም በእናቱ ማኅፀን ውስጥ ሳለ ለእግዚአብሔር ልጅ የሰገደው ነው። ይህም በመድኅን ክርስቶስ ራስ ላይ እጁን ጭኖ በውኃ ያጠምቀው ዘንድ የተገባው ነው። በቅዱስ ወንጌል እንደ ተነገረ ወንድ ልጅን ትወልድ ዘንድ የኤልሳቤጥ የፅንሷ ወራት በተፈጸመ ጊዜ ወንድ ልጅን ወለደች። ዘመዶቿና ጐረቤቶቿ እግዚአብሔር ቸርነቱን እንዳበዛላት በሰሙ ጊዜ ስለርስዋ ደስ አላቸው።

በስምንተኛውም ቀን ሊገዝሩት መጡ በአባቱ ስም ዘካርያስ ብለው ጠሩት። እናቱ ግን አይሆንም ዮሐንስ ይባል አለች። ከዘመዶችሽ ስሙ እንዲህ የሚባል የለም አሏት። አባቱንም ጠቅሰው ማን ሊባል ትወዳለህ አሉት። እርሱም ብራና ለምኖ ስሙ ዮሐንስ ይባል ብሎ ጻፈ። ሁሉም አደነቁ። ያን ጊዜም አንደበቱ ከድዳነት ተፈትቶለት ተናገረ እግዚአብሔርንም ፈጽሞ አመሰገነው። ስለ ልጁና ስለ መድኃኒታችን መምጣት ልጁ ዮሐንስም የልዑል ነቢይ እንደሚባልና በእግዚአብሔርም ፊት እንደሚሔድ ትንቢት ተናገረ።

ሰብአ ሰገልም መጥተው ከሔዱ በኋላ ሄሮድስ ሕፃናትን በገደላቸው ጊዜ ስለ ሕፃኑ ዮሐንስ ለሄሮድስ ነገሩት እንዲገድሉትም ጭፍሮችን ላከ ጭፍሮችም ወደ አባቱ ዘካርያስ መጡ ሕፃኑንም ከእርሱ ፈለጉት አባቱም አንሥቶ በትከሻዎቹ ተሸክሞ ወደ ቤተ መቅደስ ከእርሱ ጋራ እንዲሔዱና ሕፃኑን ከዚያ እንዲወስዱት ወታደሮችን ለመናቸው።

ከዚህም በኋላ ሕፃኑን በመሠዊያው ጠርዝ ላይ አኖረውና ከዚህ ራሳችሁ ተቀብላችሁ ውሰዱት አላቸው ወዲያውኑ የእግዚአብሔር መልአክ ነጥቆ ወደ በረሀ ወሰደው። ጭፍሮችም ባላገኙት ጊዜ አባቱ ዘካርያስን ገደሉት። ሕፃኑ ግን አድጎ ለእስራኤል እስከተገለጠበት ጊዜ ድረስ በበረሀ ውስጥ ኖረ።

የእግዚአብሔርን መንገድ ጥረጉ ጥርጊያውንም አስተካክሉ እያለ በምድረ በዳ የሚጮህ የዐዋጅ ነጋሪ ድምፅ እነሆ ብሎ ኢሳይያስ የተናገረለት ይህ ነው። ሚልክያስም ስለሱ እንዲህ አለ። በፊትህ ጐዳናዬን አስተካክሎ የሚጠርግ መልእክተኛዬን እኔ እሰዳለሁ።

ራሱ መድኃኒታችንም ስለርሱ ሲናገር ሴቶች ከወለዱአቸው መጥምቁ ዮሐንስን የሚበልጠው የለም ብሏል። ይህ የእግዚአብሔርን ልጅ በአጠመቀውና የማትዳሠሥ ራሱን በዳሠሠው ጊዜ የምወደው ልጄ ይህ ነው እርሱን ስሙት የሚል የአብን ቃል ሰምቷልና።

ዳግመኛም ክብር ይግባውና በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ራስ ላይ መንፈስ ቅዱስ ወርዶ ሲቀመጥ አየ። እኛም መድኃኒታችን እንዲምረንና ይቅር እንዲለን በአማላጅነቱ እያመን መታሰቢያውን እናድርግ፡፡

ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳን ጻድቃንና ሰማዕታት ጸሎት መንፈሳውያን በሆኑ በቅዱሳን መላእክትም አማላጅነት ይልቁንም አምላክን በወለደች በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በጸሎቷና በአማላጅነቷ ከሰይጣን ወጥመድ ያድነን።

የዕለቱን ወንጌል እናንብብ !ሰኔ 30 ቀን 2017 ዓ.ምየሉቃስ ወንጌል ም 1 ፥ 57 - 80(ፍጻሜ)መልካም ዕለተ ሰኑይ  !
07/07/2025

የዕለቱን ወንጌል እናንብብ !
ሰኔ 30 ቀን 2017 ዓ.ም
የሉቃስ ወንጌል ም 1 ፥ 57 - 80(ፍጻሜ)

መልካም ዕለተ ሰኑይ !


የወልቂጤ ቅዱስ ዜና ማርቆስ መንፈሳዊ ኮሌጅ ለ 3  ተከታታይ ዓመታት ሲያስተምራቸው የነበሩ ደቀ መዛሙርትን አስመረቀ ! ሰኔ 29 ቀን 2017 ዓ.ም [ተ.ሚ.ማ/ አዲስ አበባ] የወልቂጤ ቅዱስ...
06/07/2025

የወልቂጤ ቅዱስ ዜና ማርቆስ መንፈሳዊ ኮሌጅ ለ 3 ተከታታይ ዓመታት ሲያስተምራቸው የነበሩ ደቀ መዛሙርትን አስመረቀ !

ሰኔ 29 ቀን 2017 ዓ.ም [ተ.ሚ.ማ/ አዲስ አበባ]

የወልቂጤ ቅዱስ ዜና ማርቆስ መንፈሳዊ ኮሌጅ ለተከታታይ 3 ዓመታት ሲያስተምራቸው የነበሩ 22 ደቀ መዛሙርትን በዲፕሎማ እንዲሁም ለአንድ ወር ሲሰለጥኑ የነበሩ 38 ካህናትን በሰርተፊኬት በዛሬው ዕለት አስመርቋል።

በምርቃት መርሐ ግብሩ ላይጨብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ የጉራጌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ የኮሌጁ መሥራችና የበላይ ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዕ አቡነ ናትናኤል የቅድስት ሀገር ኢየሩሳሌም ገዳማት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ የሲዳማ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት የደቡብ ኦሞ እና አሪ ዞኖች ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዕ አቡነ ገሪማ የጌዴኦ የአማሮ እና ቡርጂ ዞኖች ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ፕሮፌሰር አባ ኃይለ ገብርኤል የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ አካዳሚክ ምክትል ፕሬዚዳንት ፣ የሀገረ ስብከቱ የሥራ ኃላፊዎች ፣ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ፣ የተመራቂ ተማሪዎች ቤተሰቦች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

ተመራቂ ደቀ መዛሙርቱ ከምርቃት መርሐ ግብሩ በፊት ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ተቀብለዋል።

©ሳሌም የጉራጌ ሀገረ ስብከት ሚዲያ

Address

Queen Elizabeth II Street
Addis Ababa
2QJ7+RXQ

Telephone

+251913502324

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከል - Tewahedo Media Center - TMC posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share