ተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከል - Tewahedo Media Center - TMC

ተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከል - Tewahedo Media Center - TMC "TMC was established by His Beatitude Abune Henok on July 30, 2021. Therefore, our media strives to protect believers from these influences. Values

1.

Our mission is to ensure that Orthodox Christians have access to vital information and that the Gospel is readily available to all." About Us

Tewahedo Media Center is dedicated to teaching Christians in Ethiopia and around the world about the true love of our Lord and Savior Jesus Christ. Established by His Beatitude Abune Henok on 30 July 2021 the centre aims to ensure that Orthodox Christians h

ave access to vital information and that the Gospel is readily available. Vision

Our vision is to make the beliefs, culture, and teachings of the One, Apostolic, all-knowing, international Orthodox Tewahido Churches easily accessible worldwide, free from restrictions. Our mission focuses on spreading the Word of God through Tewahedo Media Center, adapting to the technological advancements of our times. Mission

We recognise the challenges posed by secular media, which can lead believers away from God's law and the order of our holy church. We work to enhance church administration by addressing differing opinions fairly and providing valuable information. Additionally, we highlight the activities of our Holy Church on the international stage and support relationships with other churches that share sacramental and dogmatic ties. Our commitment extends to helping churches and individuals in need through organised charity work. Spirituality
2. Fairness
3. Balance
4. Legality
5. Trueness
6. Accountability
7. Accessibility
8. Trustworthiness
9. Involvement

Together, these principles guide our efforts to serve the community and uphold the teachings of our faith.

ቅዱስ ሲኖዶስ በሦስተኛው ቀን ውሎው "ገድለ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ" በሚል እየተሠራጨ ያለውን መጽሐፍ አወገዘ፡፡ ጥቅምት 14/2018 ዓ.ም [ተ.ሚ.ማ/ አዲስ አበባ]የቅዱስ ሲኖዶስ ም...
24/10/2025

ቅዱስ ሲኖዶስ በሦስተኛው ቀን ውሎው "ገድለ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ" በሚል እየተሠራጨ ያለውን መጽሐፍ አወገዘ፡፡

ጥቅምት 14/2018 ዓ.ም [ተ.ሚ.ማ/ አዲስ አበባ]

የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባዔ በሦስተኛ ቀን ውሎው ከአጀንዳ 7-13 ባሉት ላይ ውይይት ማድረጉና ውሳኔ ሰጥቷል።

ረዳት ፕሮፌሰር መምህር ዳንኤል ሰይፈሚካኤል የጥናትና ምርምር መምሪያ እና የቅዱስ ሲኖዶስ የኮሚዩኒኬሽን ሓላፊ ዛሬም ማብራሪያውን የሰጡ ሲሆን።

በአጀንዳ ቁጥር 7 ከአርሲ ሀገረ ሰብከት ካህናትና ምእመናን የቀረበውን አቤቱታ በተመለከተ ቅዱስ ሲኖዶስ ተወያይቶ ውሳኔ ማሳለፉን ገልጸዋል፡፡

ቅዱስ ሲኖዶስ የአርሲ ሀገረ ስብከት ካህናት እና ምእመናን ያቀረቡትን አቤቱታ በንባብ በማድመጥ ጉባኤው የቀረበውን አቤቱታ አስተዳደራዊ ብቻ ሳይሆን የሒሳብ ጉዳዮችም ያሉበት በመሆኑ ዝርዝር ማጣራት ስለሚያስፈልገው በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት በኩል አጣሪ ተመድቦ በሚቀርበው ሪፖርት ጉዳዩ በቋሚ ሲኖዶስ እንዲታይ እና ውሳኔ እንዲሰጥበት ጉባኤው መወሰኑን ጨምረው ገልጸዋል።

በአጀንዳ ቁጥር 8 የተወያየውና ውሳኔ ያሳለፈው የሸካ ዞን ራሱን ችሎ ሀገረ ስብከት እንዲሆን የቀረበውን ጥያቄ በተመለከተ መሆኑን ነው ሓላፊው የገለጹት፡፡

በዚህም የሸካ ዞን ራሱን ችሎ በሀገረ ስብከት ደረጃ እንዲቋቋም በቀረበው ጥያቄ መነሻነት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ በግንቦቱ ርክበ ካህናት በሰጠው ውሳኔ መሠረት በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት በኩል ተጠንቶ እንዲቀርብ መደረጉን ጉባኤው አስታውሷል፡፡

በተስጠው ውሳኔ መሠረት ከመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት የተላኩት ልዑካን ያቀረቡት ጥናት ተቀባይነት ያገኘ በመሆኑ፤ የሸካ ዞን ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት ተብሎ ራሱን ችሎ በሀገረ ስብከት ደረጃ እንዲቋቋም እና ብፁዕ አቡነ ሕዝቅኤል ሊቀጳጳስ ሀገረ ስብከቱ እንዲያደራጁና እንዲመሩ ይደረግ በማለት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ውሳኔ ማሳለፉን በዕለታዊ ማብራሪያቸው ገልጸዋል፡፡

በአጀንዳ ቁጥር 9 በአንድ ግለሰብ ተዘጋጅቶ "ገድለ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ" በሚል እየተሠራጨ ያለውን መጽሐፍ አስመልክቶ ውሳኔ ማሳለፉን ገልጸዋል፡፡

ይኸውም በአንድ ግለሰብ ተዘጋጅቶ "ገድለ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ" በሚል እየተሠራጨ ያለውን መጽሐፍ የተመለከቱ የታላቁ ደብረ ሊባኖስ አንድነት ገዳም መምህር የሆኑት መጋቤ ምሥጢር አባ ክንፈሚካኤል ለመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ጽ/ቤት መጽሐፉ እንዲመረመር ጥያቄ ማቅረባቸውን ተከትሎ፤ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ጽ/ቤት መጽሐፉ እንዲመረመር እና ያለበት ግድፈትና የስሕተት ትምህርት ተለይቶ እንዲቀርብ ወደ ሊቃውንት ጉባኤ የመራው ሲሆን፤ የሊቃውንት ጉባኤውም መጽሐፉን በሚገባ በመመርመር መጽሐፉ ያለበትን ግድፈትና የስሕተት ትምህርት ነቅሶ በማውጣት ከውሳኔ ሐሳብ ጋር አቅርቧል።

ቅዱስ ሲኖዶስም ቀደም ሲል በሊቃውንት ጉባዔ ተመርምሮ ያለበት ግድፈትና የስሕተት ትምህርት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስያንን የማይወክል በመሆኑ "ገድለ ዮሐንስ መጥምቀ መለኮት" በማለት ተጽፎ የቀረበው መጽሐፍ የቤተክርስቲያንን አስተምህሮ የሚያዛባ ሆኖ ስለተገኘ በቅዱስ ሲኖዶስ መወገዙ ተገልጿል፡፡

መጽሐፉ በውስጥ የየያዛቸው የተሳሳቱ ትምህርቶች በሙሉ ተቀባይነት የሌላቸው ሲሆን ቅዱስ ሲኖዶስ ታትሞ ሥርጭት ላይ የዋለው መጽሐፍ ሥርጭቱ እንዲታገድ፣ በድጋሚም እንዳይታተም፣ በማናቸውም ሁኔታ መጽሐፉ ለማጣቀሻም ሆነ ለምርምር እንዳይውል በመወሰን ይህም ውሳኔ ለየአህጉረ ሰብከቱ በሰርኩላር ደብዳቤ እንዲላክ በማለት መወሰኑ ተገልጿል።

ቅዱስ ሲኖዶስ የሊቃውንት ጉባኤ የጀመረውን የማጣራት ሥራ በሌሎችም መጻሕፍት እንዲቀጥል እና ከምስጋና ጋር መመሪያው እንዲደርሰው፤ መጽሐፉን አሳትመው ያሰራጩት ግለሰብ በቋሚ ሲኖዶስ ተጠርተው እንዲጠየቁና የፈጸሙት ስሕተት በተመሳሳይ እንዳይደግሙ ጥብቅ መመሪያ እንዲሰጣቸው መወሰኑ ተገልጿል።

መጽሐፉ እንዲመረመር ያደረጉት የታላቁ ደብረ ሊባኖስ አንድነት ገዳም መምህር መጋቤ ምሥጢር አባ ክንፈሚካኤልን ቅዱስ ሲኖዶስ ማመስገኑን ሓላፊው ገልጸዋል::

በአጀንዳ ቁጥር 10 በዩናይትድ ኪንግደምና አየርላንድ ሀገረ ስብከት ሥር የሚገኙ 18 አብያተ ክርስቲያናት ኅብረት ተወካዮች ነን የሚሉ ወገኖች ባቀረቡት ማመልከቻ መነሻነት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የውጭ ጉዳይ መምሪያ ጉዳዩን በመመልከት በሰጠው መግለጫ ላይ ተወያይቷል፡፡

በዚህም ቅዱስ ሲኖዶስ የክፍሉ ሊቀጳጳስ ብፁዕ አቡነ ያዕቆብ የሀገረ ስብከቱን መዋቅር በማጠናከር በቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጣቸውን ሓላፊነት በመወጣት፤ በአካል በሀገረ ስብከታቸው በመገኘት አሉ የተባሉ ችግሮችን በመፍታት በግንቦቱ የርክበ ካህናት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ የአፈጻጸም ሪፖርት እንዲያቀርቡ ውሳኔ ማስተላለፉን በመግለጫቸው ገልጸዋል፡፡

በአጀንዳ ቁጥር 11 በዩናይትድ ስቴትስ ኦፍ አሜሪካ ካልፎርኒያ ኔቫዳና ኦሪዞና ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት በሀገረ ስብከቱ ሥር መንፈሳዊ ኮሌጅ ለመክፈትና የአብነት ትምህርት ማስመስከሪያ ት/ቤት ለማቋቋም ዕርዳታና እውቅና እንዲሰጠው ባቀረበው የዕውቅና ጥያቄ ላይ በመወያየት መንፈሳዊ ኮሌጁና የአብነት ትምህርት ማስመስከሪያ ት/ቤቱ እንዲከፈት የተፈቀደ መሆኑን የገለጹ ሲሆን፤ የትምህርት አሰጣጥ፣ ፖሊሲውንና ሥርዓተ ትምህርቱን፣ የሰው ኃይል ትመናውንና መዋቅራዊ ተጠሪነቱን በተመለከተ ለመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ትምህርትና ማሠልጠኛ መምሪያ ቀርቦ እንዲመረመርና የመጨረሻ ጥናቱ ለግንቦት 2018 ዓ.ም የቅዱስ ሲኖዶስ ርክበ ካህናት ምልዓተ ጉባኤ እንዲቀርብ ሲል ውሳኔ ማሳለፉ ተገልጿል::

በአጀንዳ ቁጥር 12 እና 13 በካናዳ በሚገኙ አህጉረ ስብከቶች ዙርያ ውሳኔ ማሳለፉን የገለጹ ሲሆን፤ በዚህም ውሳኔ ብፁዕ አቡነ መቃርዮስ ያቀረቡት ጥያቄ በተመለከተ የኹለቱ አህጉረ ስብከት አስተዳደር ከዚህ ቀደም በግንቦት 15 ቀን 2017 ዓ.ም በተደረገው የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ውሳኔ መሠረት እንዲፈጸም ሆኖ አንዱ በአንዱ ጣልቃ ባለመግባት በሕገ ቤተ ክርስቲያን አንቀጽ አርባ ንዑስ ቁጥር 3 የተመለከተው ድንጋጌ ተጠብቆ እንዲሠራበት በማለት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ወስኗል፡፡

ብፁዕ አቡነ አብርሃም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መካከለኛው ካናዳ ኤድመንተን እና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ የሀገረ ስብከቱ ስያሜ እንዲስተካከል በማለት ያቀረቡትን ጥያቄ ምልዓተ ጉባኤው ተቀብሎ የሀገረ ስብከቱ ስያሜ የመካከለኛው ካናዳ ኤድመንተንና አካባቢው በሚለው እንዲስተካከል በማለት ምልዓተ ጉባኤው በመወሰን የዕለቱን ስብሰባ ማጠናቀቁን ረዳት ፕሮፌሰር መምህር ዳንኤል ሰይፈሚካኤል ገልጸዋል፡፡
©EOTCTV

የዕለቱን ወንጌል እናንብብ !ጥቅምት 14 ቀን 2018 ዓ.ምየማቴዎስ ወንጌል ም 19 ፥ 26 - 30መልካም ዕለተ አርብ !
24/10/2025

የዕለቱን ወንጌል እናንብብ !
ጥቅምት 14 ቀን 2018 ዓ.ም
የማቴዎስ ወንጌል ም 19 ፥ 26 - 30

መልካም ዕለተ አርብ !


የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በሁለተኛ ቀን ውሎው ለተለያዩ አህጉረ ስብከት የብፁዓን አባቶች ምደባ አከናውኗል።በዚህ መሠረት ብፁዕ አቡነ ኤውስጣቴዎስ የኢሉባቡር ሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ የም...
23/10/2025

የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በሁለተኛ ቀን ውሎው ለተለያዩ አህጉረ ስብከት የብፁዓን አባቶች ምደባ አከናውኗል።

በዚህ መሠረት

ብፁዕ አቡነ ኤውስጣቴዎስ የኢሉባቡር ሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ የምዕራብ ወለጋ ሀገረ ስብከትን ደርበው እንዲመሩ

ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የደቡብ ወሎና በአማራ ክልል የኦሮምያ ብሔረሰብ ዞን ኬሚሴ አህጉረ ስብከትን ደርበው እንዲመሩ።

ብፁዕ አቡነ ቶማስ የአዊና የመተከል አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የምሥራቅ ጎጃም ሀገረ ስብከትን ደርበው እንዲመሩ

ብፁዕ አቡነ ኒቆዲሞስ የምሥራቅ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት ጳጳስ የምሥራቅ ወለጋና የሆሮጉድሩ ወለጋ አህጉረ ስብከትን ደርበው እንዲመሩ ቅዱስ ሲኖዶስ በሁለተኛ ቀን የጉባኤው ውሎው ወስኗል።

ሃይማኖታዊና ባሕላዊ ክብረ በዓላትን በተመለከተ ምክክር መደረጉ ተገለጸ!!ጥቅምት 13/2018 ዓ.ም [ተ.ሚ.ማ/ አዲስ አበባ]በኢፌዲሪ ባህልና ስፖርት ሚኒስቴር በሀገራችን የሚገኙ ባህላዊና ሃ...
23/10/2025

ሃይማኖታዊና ባሕላዊ ክብረ በዓላትን በተመለከተ ምክክር መደረጉ ተገለጸ!!

ጥቅምት 13/2018 ዓ.ም [ተ.ሚ.ማ/ አዲስ አበባ]

በኢፌዲሪ ባህልና ስፖርት ሚኒስቴር በሀገራችን የሚገኙ ባህላዊና ሃይማኖታዊ ክብረ በዓላትን በተመለከተ የተዘጋጀው ሀገራዊ ፕሮፋይል ላይ ተጨማሪ ግብአቶች ለማሰባሰብ የተዘጋጀ አገራዊ ምክክር ጉባኤ በዛሬው ዕለት ቦሌ በሚገኘው በዋሽንግተን ሆቴል የተካሄደ ሲሆን፤

በምክክር መድረኩ የኢፌዴሪ ባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሚኒስቴር ዲኤታ ወ/ሮ ነፊሳ መሐዲ በኢትዮጵያ ኹለት ዓይነት በዓላት አሉ፤ ሃይማኖታዊ ይዘት ያላቸው በዓላት እና ባህላዊ ይዘት ያላቸው በዓላት ሲሆኑ በአጠቃላይ ከ146 በላይ በዓላት በሀገራችን እንዳሉ የዳሰሳ ጥናቶች ይጠቁማሉ ብለዋል ሚኒስቴ ዴኤታዋ፡፡

በዕለቱ የተገኙት የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጠቅላይ ጸሐፊ ቀሲስ ታጋይ ታደለ በሀገራችን ያሉት ሃይማኖታዊና ባህላዊ በዓላት ጠቃሚ እሴታቸውን ጠብቀው እንዲሄዱ ለማድረግ የባለድርሻ አካላት ውይይትና የሕግ ማዕቀፎች አስፈላጊ በመሆኑ የጋራ እሴቶቻችን የሚያስጠብቁ በዓላት የሃይማኖት በዓላትና የባህል በዓላት በየራሳቸው መስመር እንዲሄዱ የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ሰፊ ኃላፊነት አለበት ብለዋል ጠቅላይ ፀሐፊው፡፡

በግብአት ማሰባሰቢያ የውይይት መድረኩ በዶ/ር ተስፋነሽ የመወያያ ጥናት የቀረበ ሲሆን ጥናቱን መሠረት አድርጎ ከየቤተእምነቱ አባቶች በተነሳው ተመሳሳይ ሃሳብ የጥናት ሰነዱ ለየቤተ እምነቱ ተልዕኮ በቂ ጥናት ተደርጎ ለሚንስቴር መስሪያ ቤቱ የሚላክ ቢሆን በሚል የጋራ ስምምነት ተደርሷል፡፡

የጥናቱና የሰነዱ መደራጀት ለህዝቦች ትስስርና ለሀገረመንግስት ግንባታ ሚናቸው የጎላ መሆኑ በውይይቱ ተግልጿል፡፡

በጉባኤው የኢፌዴሪ ባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሚኒስቴር ዲኤታ ወ/ሮ ነፊሳ መሐዲ፣ የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጠቅላይ ፀሐፊ ሊቀትጉሃን ቀሲስ ታጋይ ታደለ፣ ከየቤተ እምነቱ የመጡ ተወካዮች፣ የሚኒስትር መ/ቤቱ ከፍተኛ ባለሞያዎች ተገኝተዋል፡፡

©የ/ኢ/ኦ/ተ/ቤተክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

https://youtu.be/txuW9M8DgwQ?si=xWKqfFFY-VlKjaba
23/10/2025

https://youtu.be/txuW9M8DgwQ?si=xWKqfFFY-VlKjaba

ተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከል የኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እውነተኛ ድምፅ🔗 Explore Our Channel: Tewahedo Media Center 🎥 About TMC:Dive into the rich tapestry of Ethiopian Orth...

“የዘመኑን ጥበብና ስልት ያልተከተለ ሐዋርያዊ ተልእኮአችንና አስተዳደራችንም ምእመናንን አላረካም፤ ክፍተቱ የሚድያ ቀለብ ከመሆንም አልፎ በጎቻችን በሌሎች እንዲዘረፉ ትልቅ በር እየከፈተ ነው"...
23/10/2025

“የዘመኑን ጥበብና ስልት ያልተከተለ ሐዋርያዊ ተልእኮአችንና አስተዳደራችንም ምእመናንን አላረካም፤ ክፍተቱ የሚድያ ቀለብ ከመሆንም አልፎ በጎቻችን በሌሎች እንዲዘረፉ ትልቅ በር እየከፈተ ነው" ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ

የዕለቱን ወንጌል እናንብብ !ጥቅምት 13 ቀን 2018 ዓ.ምየሉቃስ ወንጌል ም 12 ፥ 27 - 32መልካም ዕለተ ሐሙስ !
23/10/2025

የዕለቱን ወንጌል እናንብብ !
ጥቅምት 13 ቀን 2018 ዓ.ም
የሉቃስ ወንጌል ም 12 ፥ 27 - 32

መልካም ዕለተ ሐሙስ !


የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባዔ የመጀመሪያ ቀን ውሎው በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ ውሳኔ ሰጠ።ጥቅምት 12/2018 ዓ.ም [ተ.ሚ.ማ/ አዲስ አበባ]የቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት በሰጠው ዕለታዊ መግለጫ በ...
22/10/2025

የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባዔ የመጀመሪያ ቀን ውሎው በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ ውሳኔ ሰጠ።

ጥቅምት 12/2018 ዓ.ም [ተ.ሚ.ማ/ አዲስ አበባ]

የቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት በሰጠው ዕለታዊ መግለጫ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በዓመት ሁለት ጊዜ የሚከናወነው የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባዔ የጥቅምት ወር ምልዓተ ጉባዔውን ጥቅምት 11 ቀን በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም በመክፈቻ ጸሎት መጀመሩን አስታውሷል።

የቅዱስ ሲኖዶስ ጽሕፈት ቤትን በመወከል መግለጫውን የሰጡት መምህር ዳንኤል ሰይፈሚካኤል ምልዓተ ጉባዔው ዛሬ ጥቅምት 12 ቀን የመጀመሪያ ቀን ጉባዔውን ያከናወነ ሲሆን 16 አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ ማጽደቁን ገልጸዋል።

በጠዋቱ ውሎ 7 ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳትን አጀንዳ እንዲቀርጹ ውሳኔ ያሳለፈ ሲሆን እነዚህም ሊቃነ ጳጳሳት ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ፣ ብፁዕ አቡነ ሕዝቅኤል ፣ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ፣ ብፁዕ አቡነ ናትናኤል፣ ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ፣ ብፁዕ አቡነ ሩፋኤል እና ብፁዕ አቡነ ገብርኤል ናቸው ፡፡ ኮሚቴው በብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ በሰብሳቢነት በብፁዕ አቡነ ዲዎስቆሮስ በአስረጂነት ተሰብስቧል።

ምልዓተ ጉባኤው በከሰዓቱ ውሎም ከ16ቱ አጀንዳዎች በ4ቱ ላይ ውሳኔ መስጠቱን ያስታወቀ ሲሆን እነዚህም ውሳኔዎች፦

1 ቅዱስነታቸው በጠዋቱ የመክፈቻ ጸሎት ያስተላለፉት መልዕክት በቀጣይ የሥራ መመሪያ አድርጎ ምልዓተ ጉባዔው አጽድቋል፡፡

2 ከጥቅምት 4-10 በነበረው የሰበካ መንፈሳዊ ዓለም ዓቀፍ ጉባኤ የነበሩ የቡድን ውይይቶች በቃለ ጉባኤ ቀርቦ ቃለ ጉባዔውን ምልዓተ ጉባዔው የ2018 ዓ.ም የሥራ መመሪያ አድርጎ አፅድቋል፡፡

3 ሀገራዊ ሰላምን አስመልክቶ ምልዓተ ጉባዔው በግንቦት ወር ተወያይቶ ሊቃነ ጳጳሳትን የያዘ ኮሚቴ ያዋቀረ ሲሆን ኮሚቴው የተሰጠውን ኃላፊነት አጠንክሮ እንዲቀጥል ተወያይቶ አጽድቋል፡፡

4 በትግራይ የተፈጠረው ወቅታዊ ክፍፍልን አስመልክቶ የተወያየ ሲሆን በውይይቱም ሕዝቡ ሕዝባችን አብያተ ክርስቲያናቱም የቤተክርስቲያን ሀብት እንደመሆናቸው ቀደም ብሎ የተዋቀረው የሰላም ኮሚቴ ሥራውን አጠንክሮ እንዲቀጥል በምልዓተ ጉባኤው ወስኗል፡፡

ጉባዔው በነገው ዕለትም ቀጥሎ በቀሪዎቹ 12 አጀንዳዎች ላይ ውይይት ያደርጋል፡፡
©EOTCTV

"አማንያን የመንፈስና የሥነ ልቡና ሰላም ከማጣታቸውም በላይ አካላቸው ለሞትና ለጉዳት፤ ሃብታቸው ለዝርፊያና ለውድመት እየተዳረገ ነው፡፡" ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ
22/10/2025

"አማንያን የመንፈስና የሥነ ልቡና ሰላም ከማጣታቸውም በላይ አካላቸው ለሞትና ለጉዳት፤ ሃብታቸው ለዝርፊያና ለውድመት እየተዳረገ ነው፡፡" ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ

የሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ ለመምህራን እና የአስተዳደር ሠራተኞች ያዘጋጀው  የአቅም ግንባታ ሥልጠና  ተጠናቀቀ።ጥቅምት 12 ቀን 2018 ዓ.ም [ተሚማ/ አዲስ አበባ]በኢት...
22/10/2025

የሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ ለመምህራን እና የአስተዳደር ሠራተኞች ያዘጋጀው የአቅም ግንባታ ሥልጠና ተጠናቀቀ።

ጥቅምት 12 ቀን 2018 ዓ.ም [ተሚማ/ አዲስ አበባ]

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ከሚገኙ መንፈሳዊ ኮሌጆች አንጋፋው የብዙ ሊቃውንት ማፍሪያ የሆነው የሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ ለመምህራን እና አስተዳደር ሠራተኞች የአቅም ግንባታ ሥልጠና የሰጠ ሲሆን።

ሥልጠናውን ከሰጡት መምህራን መካከል አንዱ ፕሮፈሰር አባ ኃይለገብርኤል ግርማ የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርስቲ አካዳሚክ ምክትል ፕሬዚዳንት ሲሆኑ በማስተማር ሥነ ዘዴ ( Pedagogical Sciences) የማስተማር ጽንሰ-ሐሳብ እና ልምምድ እንዲሁም ሥነ ዘዴዎችን ዙሪያ ሥልጠና ተሰጥተዋል።

በሥልጠናው የማስተማር ሥነ ዘዴ እና ስልቶች ፣ ፍልስፍናዎች፣ የማስተማሪያ ቴክኒኮችን፣ የትምህርት እንቅስቃሴዎችን፣ እና የተማሪን ትኩረት እና ትምህርት ግምገማን ጨምሮ በአስተማሪዎች እና በተማሪዎች መካከል ያለውን መስተጋብር ሂደት ምን መምሰል እንዳለበት ገለጻ አቅርበዋል።

በሥልጠናው ማኅበራዊ፣ ፖለቲካዊ እና ሥነ-ልቦናዊ እድገትን እና መምህራን ተማሪዎችን እንዴት መከታተል እንዳለባቸው የሚያስረዱ ሐሳቦች ተነስተው ውይይት ተደርጎባቸዋል ።

በዕለቱ የተሰጠው ሌላው ሥልጠና በመ/ር ይቅርባይ እንዳለ በተቋማዊ አስተዳደርና አሰሠራር እንዲም ውጤታማ የጊዜ አጠቃቀም በሚል ርዕስ ገለጻ አቅርበዋል።

በሥልጠናው ውጤት ተኮር ሥራ ለመሥራት በዕቅድ እና ስትራቴጂ አመራር አርአያነት እና መልካም ምሳሌ መሆን አስፈላጊነት ላይ ገለጻ አቅርበው ከተሳታፊዎች ጋር ውይይት ተደርጓል።

ኮሌጁ መምህራን እና የአስተዳደር ሠራተኞች አቅም ለማጎልበት በበጀት ዓመቱ ተከታታይ ሥልጠናዎችን እንደሚሰጥ የገለጹት የኮሌጁ የሕዝብ ግንኙነት ክፍል ሓላፊ በኩረ ሰላም ብርሃኑ ሻረው ኮሌጁ ባለው አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት 17 መማሪያ ክፍሎች የሕንጻ ግንባታ በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ማብቃት መቻሉን ገልጸው ሥልጠናው ኮሌጁ እያከናወነ ያለውን ልማት በሰለጠነ የሰው ኃይል ለማሳደግ ወሳኝ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል።
©EOTCTV

"የባዕዳን ስም የማጥፋት ዘመቻ፣ የቤተ ክርስቲያኗን እምነት ከመንቀፍና ከማብጠልጠል በላይ አልፎ የቅዱሳንን ቅዱስ ሥዕል በአደባባይ እስከ መቅደድ ተደርሶአል" ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ
22/10/2025

"የባዕዳን ስም የማጥፋት ዘመቻ፣ የቤተ ክርስቲያኗን እምነት ከመንቀፍና ከማብጠልጠል በላይ አልፎ የቅዱሳንን ቅዱስ ሥዕል በአደባባይ እስከ መቅደድ ተደርሶአል" ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ

“የዘመኑን ጥበብና ስልት ያልተከተለ ሐዋርያዊ ተልእኮአችንና አስተዳደራችንም ምእመናንን አላረካም፤ ክፍተቱ የሚድያ ቀለብ ከመሆንም አልፎ በጎቻችን በሌሎች እንዲዘረፉ ትልቅ በር እየከፈተ ነው"...
22/10/2025

“የዘመኑን ጥበብና ስልት ያልተከተለ ሐዋርያዊ ተልእኮአችንና አስተዳደራችንም ምእመናንን አላረካም፤ ክፍተቱ የሚድያ ቀለብ ከመሆንም አልፎ በጎቻችን በሌሎች እንዲዘረፉ ትልቅ በር እየከፈተ ነው" ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ

የቅዱስነታቸው የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ የመክፈቻ መልእክት ከዚህ እንደሚከተለው ይቀርባል።

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

• ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ
የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፤

• ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ
የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፣

• ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት፣

በአጠቃላይ በዚህ ዓመታዊ ቅዱስ ጉባኤ የተገኛችሁ በሙሉ፤
የጎደለብንን እየሞላ አገልግሎታችንን እያቃና ከዚህ ላደረሰን፣ ይህንን ዓመታዊና ሐዋርያዊ ጉባኤያችንን ለማካሄድም ለሰበሰበን ለአምላካችን ለእግዚአብሔር ምስጋና እናቀርባለን፡፡

“ወእፌጽም ታሕጻጸ ሕማሙ ለክርስቶስ በሥጋየ በእንተ ሥጋሁ እንተ ይእቲ ቤተ ክርስቲያኑ፡- ስለ አካሉ ማለትም ስለ ቤተክርስቲያኑ ስል በሥጋዬ በክርስቶስ መከራ የጎደለውን እፈጽማለሁ” (ቈላ.፩÷፳፬)

ያለንበት ዓለም በሁሉም ነገር በጉድለቱ የሚታወቅ ነው፤ ጉድለት ባይኖርና ሁሉም የሞላለት ቢሆን ኖሮ ፍጥረት እርስ በርስ የሚተረማመስበት ሁኔታ አይኖርም ነበር ወይም አሁን ባለበት ደረጃ የከፋ አይሆንም ነበር፡፡

እግዚአብሔር ሁሉንም አሟልቶ መፍጠር ወይም መስጠት የሚችል ከሃሊ አምላክ ቢሆንም፣ እሱ ባወቀ ፍጥረትን ሁሉ ጉድለት ያለበት አድርጎ ፈጥሮታል፤ በዚህም ምክንያት እያንዳንዱ ጉድለቱን ለመሙላት በሚያደርገው ፍትጊያ እየተጋጨ እርስ በርስ ሲተረማመስ ማየቱ የተለመደ ነው፡፡ ምድራዊቷ ቤተ ክርስቲያንም በጐዶሎው ዓለም እስካለች ድረስ ከሚመጣው ፈተና አታመልጥም፤ ይህም በመሆኑ ቅዱስ ጳውሎስ ለቈላስይስ ሰዎች “የጎደለውን እፈጽማለሁ” በማለት ሲጽፍ እናስተውላለን፡፡

• ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት!

በጐዶሎው ዓለም የምትኖር ቤተ ክርስቲያን ጉድለቷን ለመሙላት ብዙ መሥዋዕትነት ከፍላለች፤ ቤተ ክርስቲያን ለቀጣዩ ትውልድ መሸጋገርና የጐደለባትን ለመሙላት ስትል ከቅዱሳን ሐዋርያት አንሥቶ እስካለንበት ዘመን ድረስ ብዙና የብዙ ብዙ አበው ካህናትን፣ ሊቃውንትንና ምእመናንን ከደም ጠብታ፣ እስከ ቁስ ስጦታ ገብራለች፡፡

አሁን በምድር ላይ ያለችው ቤተ ክርስቲያን የዚህ ሁሉ ውጤት ናት፤ ቤተ ክርስቲያን እንደ ሌላው ጊዜ ሁሉ ዛሬም የጐደለባት ብዙ ነገር አለ፤ በተቻለ መጠን እርሱን ለሟሟላት መጣርና በተሻለ ሁኔታ ወደፊት ማሻገር ደግሞ የዚህ ጉባኤ ተቀዳሚ ተግባር ነው፡፡ በዚህ ረገድ ይህ ጉባኤ ብቻው አይደለም፤ በብዙ ሚሊዮኖች የሚቈጠሩ የእግዚአብሔር ልጆች ድምፁን ለመስማት ከዙሪያው ሆነው በጉጉት ይጠብቃሉ፡፡ እነኝህ የእግዚአብሔር ልጆች ለመስማት ብቻ ሳይሆን ድምፁን ሰምተው ለመታዘዝም የተዘጋጁ ናቸው፣ ከሁሉ በላይ ደግሞ “ሁለትም ሦስትም ሆናችሁ በስሜ በተሰበሰባችሁበት እኔ በመካከላችሁ እገኛለሁ” በማለት ጉባኤውን የመሠረተው አምላክ ከዚህ ጉባኤ መካከል አለ፡፡

በመሆኑም ይህ ጉባኤ የተወሰን አባቶች ብቻ ሳንሆን ብዙ ሰማውያንና ምድራውያን ባለድርሻ ያሉበት፣ መንፈስ ቅዱስም በመንፈስ የሚመራው እንደሆነ የማይታበል ነው፡፡ ከዚህ አንጻር ጉባኤው በምድር ያለችውን የእግዚአብሔር መንግሥት በበላይነት የሚመራ ነውና፣ ያለበት ኃላፊነት ከባድና እጅግ የላቀ ነው፡፡ ጉባኤው ኃላፊነቱን በአግባቡ ሲወጣ የሚሰጠው ሽልማት ታላቅ እንደሆነ ሁሉ፣ ኃላፊነቱን በትክክል ካልተወጣ ደግሞ ተጠያቂነቱ በዚያው ልክ ከባድ ነው፤ ብዙ ከተሰጠው ብዙ ይፈለጋል ተብሎአልና፡፡

• ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት!

እኛ በአገልግሎትና በመሪነት በምንገኝበት በዚህ ዘመን ቤተ ክርስቲያን የጐደሉባት ነገሮች ብዙ ናቸው፤ ከሁሉ በላይ በውስጣችን የአንድነት ጐድለት በስፋት ይታያል፤ ለተሰየምንለት መለኮታዊ ተልእኮ አንድ ሐሳብ፣ አንድ ቃል፣ አንድ ልብ ሆነን መሰለፍ ያለመቻል ክፍተት እየተንጸባረቀ ነው፡፡ የዘመኑን ጥበብና ስልት ያልተከተለ ሐዋርያዊ ተልእኮአችንና አስተዳደራችንም ምእመናንን አላረካም፤ ክፍተቱ የሚድያ ቀለብ ከመሆንም አልፎ በጎቻችን በሌሎች እንዲዘረፉ ትልቅ በር እየከፈተ ነው፡፡ በእነዚህ ዓበይት ጉዳዮች እና በመሳሰሉት ጉድለቶቻች ላይ ፈጣን፣ ቈራጥና አዋጭ የሆነ ሥራ ካልሰራን ለወደፊት የቤተ ክርስቲያንን ህልውና ጥያቄ ውስጥ መክተቱ አይቀሬ ነው፡፡

• ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት!

ቤተ ክርስቲያናችን በተጠቀሱት ችግሮች ተከባ ባለችበት ሁኔታ የሀገራችን ሰላም መቀዛቀዝ ደግሞ ሌላው ተጨማሪ ጉድለትን እያስከተለብን ነው፡፡ አማንያን የመንፈስና የሥነ ልቡና ሰላም ከማጣታቸውም በላይ አካላቸው ለሞትና ለጉዳት፤ ሃብታቸው ለዝርፊያና ለውድመት እየተዳረገ ነው፡፡ ይኽም ሁሉ ሆኖ ፍትሕን እያገኙ አይደለም፤ አብያተ ክርስቲያናትም በምእመናን ፍልሰት እየተዘጉም እየተቃጠሉም ነው፡፡

ከዚህም ሌላ የሌለን ነገር እንዳለ አስመስሎ ከየአቅጣጫው የሚወረወረው የባዕዳን ስም የማጥፋት ዘመቻ፣ የቤተ ክርስቲያኗን እምነት ከመንቀፍና ከማብጠልጠል በላይ አልፎ የቅዱሳንን ቅዱስ ሥዕል በአደባባይ እስከ መቅደድ ተደርሶአል፤ በቤተ ክርስቲያናችን ህልውና ላይ በዓላማ የተነሡ አካላት የላኳቸው እንዳሉ በሚመስል መልኩ በስመ ተሐድሶ የሚደረገው እንቅስቃሴ የኛው መለያ የሆነውን ንዋየ ቅድሳትና ልብሰ ተክህኖ፣ መዝሙርና ሥርዓተ አምልኮ በመጠቀም ቤተ ክርስቲያናችንን በአደባባይ እየተዳፈረ ይገኛል፡፡

ይህ አላስፈላጊ ተግባር የሀገሪቱን ዜጎች በእኩልነት የሚያስተዳድረውን ሕገ መንግሥት በቀጥታ የሚፃረር ድርጊት ነው፤ ሆኖም በሕግ የሚጠይቅና የሚያስቆም አካል አልተገኘም፤ እኛም ዝምታን የመረጥን መስለናል፡፡ ነገር ግን መፍትሔው ዝምታ ሳይሆን በሕግ አግባብ ነገሩን ለመፍታት መንቀሳቀስ እንደሆነ ሁሉም ሊገነዘበው ይገባል፡፡

• ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት!

በዘመናችን እየተከሠተ ያለው ችግር ስንዘረዝር ውለን ብናድር መናገሩ በራሱ መፍትሔ ሊያመጣልን አይችልም፤ ጉባኤው ከዚህ በላይ መናገር እንደሚችልም እንገነዘባለን፤ ነገር ግን ለዚህ ሁሉ ችግር ዘላቂ መፍትሔ ሊያመጣ የሚችል መደላድል ይህ ጉባኤ በዚህ ስብሰባ ሊተልም ይገባል ብለን ከአደራ ጋር ማሳሰብ እንወዳለን፡፡ በሌላ በኩል በሀገራችን ያለው ያለመረጋጋት በሕዝባችን አጠቃላይ ሥነ ልቡና በሀገሪቱ አንድነትና ዕድገት የሚያስከትለውን ጫና በቀላሉ የሚታይ አይሆንም፤ የሕዝቡ ሥነ ልቡና ከተጐዳ የነገው ዕድል ጤናማ ይሆናል ተብሎ አይታሰብም፡፡

ችግሩ እየታየ ያለው በዋናነት በሀገራችን ፖለቲከኞች በመሆኑ ነገሩ የተወሳሰበና የተራዘመ እንዲሆን አድርጎታል፤ በመሆኑም ይህ የርስ በርስ ግጭት ቆሞ ችግሮች በውይይትና በድርድር በመፍታት የወንድማማች እልቂት የሚያስቆም የሰላምና የዕርቅ ዕድል ቅድሚያ እንዲሰጠው ጉባኤው የበኩሉን ጥረት ማድረግ ይገባዋል፡፡ የነገው ትውልድ ልማታዊ ተስፋ እውን ሊሆን የሚችለው ሰላምና አንድነት ሲኖር ነውና መንግሥት፣ ተፎካካሪ ፖለቲከኞችና ነፍጥ ያነሡ ወገኖች ሁሉ ለሰላም መስፈንና ለልማት ዕድገት መረጋገጥ ሲባል ወደ መግባባት እንዲመጡ በእግዚአብሔር ስም አባታዊ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡


በመጨረሻም ዓመታዊውና ቀኖናዊው የቅዱስ ሲኖዶስ ዓቢይ ጉባኤ በዛሬው ዕለት በጸሎት የተከፈተ መሆኑን ለሕዝበ ክርስቲያኑ በእግዚአብሔር ስም እናበስራለን፡፡

እግዚአብሔር የተባረከና የተቀደሰ ጉባኤ ያድርግልን፤

እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ

ወስብሐት ለእግዚአብሔር፤ አሜን፡፡

አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት

ጥቅምት ፲፪ ቀን ፳፻፲፰ ዓመተ ምሕረት
አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ

Address

Queen Elizabeth II Street
Addis Ababa
2QJ7+RXQ

Telephone

+251913502324

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከል - Tewahedo Media Center - TMC posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share