ተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከል - Tewahedo Media Center - TMC

ተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከል - Tewahedo Media Center - TMC "TMC was established by His Beatitude Abune Henok on July 30, 2021. Therefore, our media strives to protect believers from these influences. Values

1.
(3)

Our mission is to ensure that Orthodox Christians have access to vital information and that the Gospel is readily available to all." About Us

Tewahedo Media Center is dedicated to teaching Christians in Ethiopia and around the world about the true love of our Lord and Savior Jesus Christ. Established by His Beatitude Abune Henok on 30 July 2021 the centre aims to ensure that Orthodox Christians h

ave access to vital information and that the Gospel is readily available. Vision

Our vision is to make the beliefs, culture, and teachings of the One, Apostolic, all-knowing, international Orthodox Tewahido Churches easily accessible worldwide, free from restrictions. Our mission focuses on spreading the Word of God through Tewahedo Media Center, adapting to the technological advancements of our times. Mission

We recognise the challenges posed by secular media, which can lead believers away from God's law and the order of our holy church. We work to enhance church administration by addressing differing opinions fairly and providing valuable information. Additionally, we highlight the activities of our Holy Church on the international stage and support relationships with other churches that share sacramental and dogmatic ties. Our commitment extends to helping churches and individuals in need through organised charity work. Spirituality
2. Fairness
3. Balance
4. Legality
5. Trueness
6. Accountability
7. Accessibility
8. Trustworthiness
9. Involvement

Together, these principles guide our efforts to serve the community and uphold the teachings of our faith.

የዕለቱን ወንጌል እናንብብ !ሐምሌ 27 ቀን 2017 ዓ.ምየማቴዎስ ወንጌል ም 8 ፥ 1 - 34መልካም ዕለተ ሰንበት  !
03/08/2025

የዕለቱን ወንጌል እናንብብ !
ሐምሌ 27 ቀን 2017 ዓ.ም
የማቴዎስ ወንጌል ም 8 ፥ 1 - 34

መልካም ዕለተ ሰንበት !


በጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት በበጀት ዓመቱ 3372 ኢ- አማንያን መጠመቃቸው ተገለጸ ! ሐምሌ 25 ቀን 2017 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ) በጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት የ፪ኛ ...
02/08/2025

በጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት በበጀት ዓመቱ 3372 ኢ- አማንያን መጠመቃቸው ተገለጸ !

ሐምሌ 25 ቀን 2017 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ)

በጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት የ፪ኛ ዓመት ሀገረ ስብከት አቀፍ ጠቅላላ ጉባኤ በመደረግ ላይ የሚገኝ ሲሆን ፤ በመርሐግብሩ የወረዳ ቤተ ክህነት ሥራ አስኪያጆች የየወረዳ ቤተ ክህነቱን ዓመታዊ የ፩ ዓመት ሪፖርት ያቀረቡ ሲሆን በሪፖርታቸው በድምሩ 3372 ኢ-አማንያን መጠመቃቸውን ገልጸዋል።

የመንበረ ጵጵስናና ወናጎ ወረዳ ቤተ ክህነት በበጀት ዓመቱ 822 ኢ-አማንያን መጠመቃቸውን ገልጸው የስብከተ ወንጌል አገልግሎትን በተመለከተ፣ መልካም አስተዳደርን፣ ሁለገብ ልማትን፣ የአብነት ትምህርት ቤት እና ዘመናዊ ትምህርት ቤትን፣ ሰንበት ትምህርት ቤትን በተመለከተ (የአንድነት ሰንበት ትምህርት ቤት)፣ የአደባባይ ክብረ በዓላት አከባበርን፣ የቤተ ክርስቲያን ምረቃ፣ የመሰረት ድንጋይ መቀመጥ፣ የጠበል አገልግሎት፣ የማረምያ ቤት፣ የፋይናንስ አያያዝ አስተዳደር፣ ፐርሰንት ክፍያ በተመለከተ እንዲሁም የተሀድሶን ሴራ ስለማጋለጥ የተሰሩ ሥራዎችን ገልጸዋል።

የይርጋጨፌ ወረዳ ቤተ ክህነት 823 ኢ-አማንያን ማስጠመቃቸውን ገልጸው የብፁዕ አቡነ ገሪማ ጳጳስ ሐዋርያዊ አገልግሎት፣ ከአድባራት አስተዳዳሪዎች ጋር የተደረጉ ውይይቶችን፣ ስብከተ ወንጌልን ለማስፋፋት የተሰሩ ሥራዎችን፣ በአድባራቱ የተሰሩ ልማቶችን እንደአብነት የግብርና የልማት ሥራዎችን፣ ሰንበት ትምህርት ቤቶች አዲሱን ሥርዓተ ትምህርት እንዲከተሉ ለማድረግ የተሰሩ ሥራዎችን በሰፊው ገልጸዋል።

በኮቾሬና ገደብ ወረዳዎች ቤተ ክህነት 273 ኢ-አማንያን መጠመቃቸውን ገልጸው በዕቅድ ዙሪያ የተደረገ ውይይት፣ የተዘጉ አብያተ ክርስቲያናትን ለማስከፈት የተሰሩ ሥራዎችን፣ የክህነት አሰጣጥን በተመለከተ፣ ሰንበት ትምህርት ቤቶችን ለማቋቋም የተሰሩ ሥራዎችን፣ የስብከት ኬላ ማቋቋምን፣ የአቅም ማጎልመቻ ሥልጠናዎችን በተመለከተ፣ የተቸገሩ አብያተ ክርስቲያናትን መለየትና ማቋቋምን በተመለከተ፣ የንግስ በዓላትን መምህራንን መመደብ መቆጣጠር የመሳሰሉትን ሥራዎች አቅርበዋል።

የቡሌና ረጴ ወረዳ ቤተ ክህነት 127 ኢ-አማንያንን ማስጠመቃቸውን ገልጸው በስብከተ ወንጌል፣ ሁለንተናዊ የልማት ሥራዎችን፣ በሰንበት ትምህርት ቤት የተሰሩ ሥራዎችን፣ በፐርሰንት የተሰሩ ሥራዎችን፣ በአብነት ተማሪዎች ዙርያ የተሰሩ ሥራዎችን ገልጸዋል።

የኮሬ ወረዳ ቤተ ክህነት 594 ኢ-አማንያንን ማስጠመቃቸውን ገልጸው የብፁዕ አባታችንን ሐዋርያዊ አገልግሎት፣ የአገልጋይ እጥረት ያለባቸውን አብያተ ክርስቲያናትን አገልጋይ በመመደብ እንዲሁም ንዋየ ቅድሳትን ሟሟላት፣ ስብከተ ወንጌል አገልግሎትን ለማስፋፋት የተሰሩ ሥራዎችን ገልጸዋል።

የቡርጂ ወረዳ ቤተ ክህነት 733 ኢ-አማንያንን ማስጠመቃቸውን ገልጸው የብፁዕ ሊቀጳጳሱን ሐዋርያዊ አገልግሎት፣ ስብከተ ወንጌልን ተደራሽ ከማድረግ አንጻር የተሰሩ ሥራዎች፣ ሥራዎችን ከማዘመን አንጻር የተሰሩ ሥራዎችን ሪፖርት አድርገዋል።

©ኤክቱስ የሀገረ ስብከቱ ሚዲያ

ብፁዕ አቡነ ናትናኤል ሊቀ ጳጳስ ቅድስት ሀገር ኢየሩሳሌም ሲደርሱ አቀባበል ተደረገላቸው ። ሐምሌ 14 ቀን 2017 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ) የቅድስት ሀገር  ኢየሩሳሌም ገዳማት ሊቀ ጳ...
02/08/2025

ብፁዕ አቡነ ናትናኤል ሊቀ ጳጳስ ቅድስት ሀገር ኢየሩሳሌም ሲደርሱ አቀባበል ተደረገላቸው ።

ሐምሌ 14 ቀን 2017 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ)

የቅድስት ሀገር ኢየሩሳሌም ገዳማት ሊቀ ጳጳስ ሆነው በቅዱስ ሲኖዶስ የተመደቡት ብፁዕ አቡነ ናትናኤል ትናንት ከሰዓት በኋላ በሰላም ቅድስት ሀገር ኢየሩሳሌም ሲደርሱ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።

ከብፁዕነታቸው ጋር ብፁዕ አቡነ መልከ ጸዴቅ የጉራጌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የቅዱስ አቡነ ዜና ማርቆስ መንፈሳዊ ኮሌጅ የበላይ ሐላፊ ፣ እንዲሁም የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽ/ቤትና የድርጅት ሐላፊዎች፣ የሚዲያ ባለሙያዎች ከኢትዮጵያ አብረው ተጉዘዋል።

የቅድስት ሀገር ኢየሩሳሌም ገዳማት ዋና መጋቢ አባ ተክለ ሃይማኖት ኃይለ ማርያም እና የገዳማቱ አበው መነኮሳት ቲላቪቭ አየር መንገድ በመገኘት አቀባበል ያደረጉላቸው ሲሆን በርካታ መነኮሳትና መዘምራን ደብረ ገነት ኪዳነ ምሕረት ገዳም በመገኘት የእንኳን ደህና መጡ አቀባበል አድርገውላቸዋል::

ብፁዕ አቡነ ናትናኤል ቀደሚም ሲል በአሜሪካ የኮሎራዶና አካባቢው ሀገረ ስብከትን በአባትነት የመሩ ሲሆን ከ2017 ዓ/ም ግንቦት ርክበ ካህናት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ውሳኔ በኋላ የቅድስት ሀገረ ኢየሩሳሌም ገዳማት ሊቀ ጳጳስ ሆነው እንዲያገለግሉ መዛወራቸው የሚታወስ ነው።

©የመረጃው ምንጭ ደወል ሚዲያ ነው።

የዕለቱን ወንጌል እናንብብ !ሐምሌ 26 ቀን 2017 ዓ.ምየማቴዎስ ወንጌል ም 1 ፥ 18 - ፍጻሜ መልካም ዕለተ ቀዳሚት ሰንበት  !
02/08/2025

የዕለቱን ወንጌል እናንብብ !
ሐምሌ 26 ቀን 2017 ዓ.ም
የማቴዎስ ወንጌል ም 1 ፥ 18 - ፍጻሜ

መልካም ዕለተ ቀዳሚት ሰንበት !


የዕለቱን ወንጌል እናንብብ !ሐምሌ 25 ቀን 2017 ዓ.ምየማርቆስ ወንጌል ም 13 ፥ 5 - 14መልካም ዕለተ አርብ  !
01/08/2025

የዕለቱን ወንጌል እናንብብ !
ሐምሌ 25 ቀን 2017 ዓ.ም
የማርቆስ ወንጌል ም 13 ፥ 5 - 14

መልካም ዕለተ አርብ !


ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን አዲስ አበባ ላይ  ለምታከናውነው የልማት ሥራ ምክክርና ስልጠና ተካሄደ።ሐምሌ 24 ቀን 2017 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ)በአዲስ አበባ "የከተማ አስተዳደሩ ...
31/07/2025

ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን አዲስ አበባ ላይ ለምታከናውነው የልማት ሥራ ምክክርና ስልጠና ተካሄደ።

ሐምሌ 24 ቀን 2017 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ)

በአዲስ አበባ "የከተማ አስተዳደሩ የኮሪደር ልማትና የመልሶ ማቋቋም ተሞክሮን” በተመለከተ በከተማው ከንቲባ የተወከሉ ከፍተኛ ባለመያዎች ከቋሚ ሲኖዶስ አባላት እና ከመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት አስተዳደር ጉባኤ አባላት ጋር የተገናኙበት የሥልጠናና የምክክር ጉባኤ ተካሄደ፡፡

በጉባኤው ላይ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ የምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፣ የምሥራቅ ትግራይና ራያ አህጉረ ስብብከት ሊቀ ጳጳስ፣ ብፁዓን አበው የቋሚ ሲኖዶስ አባላት ተካፍለዋል፡፡

ከከተማው አስተዳደር ወገን ከመጡ ባለሙያዎች ኢንጂነር ወንደወሰን ባንጃው የአዲስ አበባ መሬት ልማት አስተዳደር ምክትል ቢሮ ኃላፊ፤ በከተማዋ የተሠሩ ሥራዎች፣ በኮሪደር ልማት የተገኘው ውጤትና ሂደቱን በተመለከተ ለጉባኤው አብራርተዋል፡፡

ኃላፊው እንደገለጹት አስተዳደሩ ከተማዋ ለትራንስፖርት ምቹ እንድትሆን አድርጓል። አያይዘውም ቤተክርስቲያን ከፍተኛ የልማት ሥራ ባለሙያ መሆኗንና በኢትዮጵያ የሪል ስቴት ግንባታ ታሪክ ፈር ቀዳጅ እንደነበረች ጠቅሰው አሁን ያሉ መሪዎቿም የቀደመውን የቤተክርስቲያኗን ማንነት ይዘው መጓዝ ይገባቸዋል ሲሉ አስተያየት ሰጥተዋል፡፡

ለከተማ አስተዳደሩ ውጤታማነት የአመራሩ ድጋፍና ክትትል መኖርን አብነት አድርገው የጠቀሱት ምክትል ሓላፊው በተመሳሳይ መልኩም ቅድስት ቤተክርስቲያን በቀጣይ ለምትሠራው ልማት በኃላፊነት ላይ ያሉ አባቶች ድርሻ ከፍተኛ ሊሆን እንደሚገባ አስረድተዋል፡፡

ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ በበኩላቸው:- “የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በክብርት ከንቲባ አዳነች አቤቤ እየለማች ነው፡፡ በአጭር ጊዜም በርካታ የልማት ሥራዎች ተሠርተው ተመልክተናል፡፡ እኛም ከአስተዳደሩ ተሞክሮ እንድንወስድ ከንቲባዋ ጋር ሄደን ባነጋገርናቸው ወቅት ጥያቄያችንን ተቀብለው ባለሙያዎች ልከውልናል፤ ምስጋናችንን እናቀርባለን" ብለዋል።

ብፁዕነታቸው የቀደሙት የቤተ ክርስቲያን አባቶችና ቅዱሳን ፓትርያርኮች ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ባስልዮስ እና ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቴዎፍሎስ አርቆ አሳቢዎች እንደነበሩ ገልጸው:- "በእነርሱ ዘመን ተሠርተው የተገኙት ሕንጻዎች በርካታ ናቸው፡፡ ወደኋላ እንዳንቀር በተሻለ መልኩ ወደፊት እንድንሄድ አድርገዋል፡፡ አሁንም ከአስተዳደሩ ከመጡት ባለሙያዎች ሙያዊ ሥልጠና ስለሰጡን እናመሰግናለን” ሲሉ ተናግረዋል፡፡

ብፁዕ አቡነ መልከ ጸዴቅ የጉራጌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በሰጡት አስተያየት “የመምሪያ ኃላፊዎች፣ የቋሚ ሲኖዶስ አባላት፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መሥራት እንዳለባቸው በማሰብ ሁለታችሁም ብፁዓን አባቶች ክብርት ከንቲባዋ ዘንድ ሄዳችሁ በቀጣይ ስለሚሠራው ሥራ ማወያየታችሁን አደንቃለሁ፤ ክብርት ከንቲባዋም የሥራ ፍሬዎቻቸውን እያሳዩ ተባብረን እንሠራ ብለው አሠልጣኞችም ስለላኩ ሊመሠገኑ ይገባል፣ ሥልጠናውም በጣም ጥሩ ሥልጠና ነበር” ሲሉ ገልጸዋል፡፡

በመርሐ ግብሩ ላይ ከተሳታፊዎች ለተነሡት ጥያቄዎች ከከተማው አስተዳደር የመጡት ባለሙያዎች ምላሽ ሰጥተዋል፣ ተሞክሮአቸውንም አካፍለዋል፡፡

በጉባኤው የጠቅላይ ቤተክህነት የመምሪያ ሓላፊዎች፣ የኮሪደር ልማት ዐቢይ ኮሚቴ አባላት፣ የቤቶችና ሕንጻዎች ልማት ድርጅት፣ የኮንስትራክሽን ጽ/ቤት የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡
©eotc tv

ቱሪዝም እና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ጥቅም በሚል ርእስ ውይይት ተካሄደ፡፡ሐምሌ 24/2017 ዓ.ም [ተሚማ/ አዲስ አበባ]የኢትዮጵያ  ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅ...
31/07/2025

ቱሪዝም እና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ጥቅም በሚል ርእስ ውይይት ተካሄደ፡፡

ሐምሌ 24/2017 ዓ.ም [ተሚማ/ አዲስ አበባ]

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በሀገሪቱ ክፍሎች የሚገኙ ጥንታውያን አድባራትና ገዳማት በኪነ ሕንፃቸው፣ ድንቅ የሆኑ የግድግዳና የጣሪያ ላይ ሥዕላቶቻቸው፣ ዕድሜ ጠገብ የብራና መጻሕፍትና የሌሎች የቱሪስት መስህቦች ባለቤት ናት፡፡

እነዚህ የቱሪስት መስኅቦችን ለመመልከት የሚመጡ ብዙ የውጭ ሀገራት ጎብኚዎች ገንዘባቸው በሀገራችን የሚገኙ ሆቴሎችን እና መሰል ጉዳዮች ከማበልፀግ ከማድመቅ ባሻገር የመስኅቦቹን ባለቤት ቤተክርስቲያንን የበይ ተመልካች ያደረጉ ጉዳዮች ከሆኑ ዋል አደር ማለቱ በውይይቱ አጽንኦት ተሰጥቶታል።

በዚህም ቤተ ክርስቲያን በቱሪዝም ዘርፍ ልማት ላይ ያላትን ከፍተኛ ሚና እና በተጠቃሚነቱ ረገድ ያላትን ሁኔታ መሠረት ያደረገ ውይይት የቤተ ክርስቲያን ቅርሳቅርስ፣ የቤተመጻሕፍት ወመዘክር ሙዚየም እና የቱሪዝም መምሪያ ዋና ኀላፊ በኩረ ትጉሃን ምትኩ ከንቲባ፣ በመምሪያው ሥር የቱሪዝም ዋና ክፍል ኀላፊ ክብርት ወ/ሮ ምንታምር ከኢ.ፌ.ዲ.ሪ ቱሪዝም ሚንስቴር ሚንስትር ወ/ሮ ሰላም ካሳ ጋራ ውይይት አድርገዋል፡፡

የተከበረው ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እስከአሁን የነበረው እንዳለ ሆኖ በቀጣይ ለሚደረጉ የቱሪዝም ልማት እንቅስቃሴ ከተሳታፊነት እስከ ተጠቃሚነት ቤተክርስቲያንን ያማከለ ሥራ እንዲሠራ እና የልምድ ልውውጦችን እንዲሁም ስልጠናዎች ላይም የጋራ ተሳትፎ እንዲያደርግ በውይይቱ ተጠይቋል።

ሚንስትሯ ወ/ሮ ሰላም በውይይቱ ላይ እንደገለጹት የቱሪዝም መስህቦችን ማራኪ ለማድረግና በቱሪዝም ዘርፍ ያሉ እንቅስቃሴዎችን ለማሳደግ ቁርጠኞች መሆናቸውን ገልጸው በበጀት ዓመቱ ዘርፉን ለማሳደግ በሚደረገው ጥረት ላይ ቤተ ክርስቲያን ተሳታፊ እንድትሆን እንሠራለን ብለዋል።

ቤተ ክርስቲያን ከቱሪዝም ሚንስቴር ጋር ለመሥራት የሚያስችላትን ይሁንታ በማግኘቷ ምስጋናችን ላቅ ያለ ነው ሲሉ የመምሪያው ዋና ኀላፊ በኩረ ትጉሃን ምትኩ ተናግረዋል፡፡

©የኢ/ኦ/ተ/ቤተ ክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

31/07/2025

የዕለቱን ወንጌል እናንብብ !ሐምሌ 24 ቀን 2017 ዓ.ምየማቴዎስ ወንጌል ም 9 ፥ 16 - 22መልካም ዕለተ ሐሙስ  !
31/07/2025

የዕለቱን ወንጌል እናንብብ !
ሐምሌ 24 ቀን 2017 ዓ.ም
የማቴዎስ ወንጌል ም 9 ፥ 16 - 22

መልካም ዕለተ ሐሙስ !


https://youtu.be/CH_8qEnTJ80?si=diF5xGlZ9f0m097Q
30/07/2025

https://youtu.be/CH_8qEnTJ80?si=diF5xGlZ9f0m097Q

ተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከል የኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እውነተኛ ድምፅ🔗 Explore Our Channel: Tewahedo Media Center 🎥 About TMC:Dive into the rich tapestry of Ethiopian Orth...

የብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ 35ኛ ዓመት መታሰቢያ መርሐ ግብር ተካሄደ !ሐምሌ 23 ቀን 2017 ዓ.ም [ተ.ሚ.ማ/ አዲስ አበባ] የብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ 35ኛ ዓመት መታሰቢያዠ መርሐ ግብር በ...
30/07/2025

የብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ 35ኛ ዓመት መታሰቢያ መርሐ ግብር ተካሄደ !

ሐምሌ 23 ቀን 2017 ዓ.ም [ተ.ሚ.ማ/ አዲስ አበባ]

የብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ 35ኛ ዓመት መታሰቢያዠ መርሐ ግብር በትናንትናው ዕለት ሐምሌ 22 ቀን 2017 ዓ.ም ከምሽቱ 11:00 ሰዓት በማኅበረ ቅዱሳን 3ኛ ወለል ንቡረ እድ ድዠሜጥሮስ አዳራሽ የማኅበሩ ነባር እና አዳዲስ አባላት በተገኙበት ተካሄዷል።

የማኅበረ ቅዱሳን ዋና ሥራ አስፈጻሚ የሆኑት መምህር ዋሲሁን በላይ በመርሐ ግብሩ ላይ መልእክት ያስተላለፉ ሲሆን በማኅበረ ቅዱሳን ታሪክ ባለፉት 35 ዓመታት ብፁዕነታቸውን ጨምሮ ሌሎች አባቶችም ሲዘከሩ መቆየታቸውን ገልጸዋል።

በየአምስት ዓመቱ የአቡነ ጎርጎርዮስን መታሰቢያ እንደሚደረግ የገለጹት ዋና ሥራ አስፈጻሚው ለማኅበሩ መመሥረትና እዚህ ደረጃ እንዲደርስ ትልቁን ድርሻ ከተወጡ አባቶች መካከል ቀዳሚው አባታችን ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ናቸው በማለት ተናግረዋል።

ዋና ሥራ አስፈጻሚው አክለውም ብፁዕነታቸው ከነበራቸው ርዕይ መካከል በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚማረውን ትውልድ ለቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ማሰለፍ በከፊል በማኅበረ ቅዱሳን መሳካቱን ገልጸው በ467 ግቢ ጉባኤያት ውስጥ ከ210 ሺህ በላይ ተማሪዎች ስለ መንፈሳዊ ሕይወት እና ስለ ቤተክርስቲያን አገልግሎት እየተማሩ ይገኛሉ ብለዋል።

በተጨማሪም ማኅበሩ በ24 ከተሞች ላይ በብፁዕነታችው ስም ባቋቋማቸው ትምህርት ቤቶች ውስጥ ከ35ሺህ በላይ ተማሪዎች በሥነ ምግባር ታንጸው ቤተ ክርስቲያን እና አገር ተረካቢ እንዲሆኑ ለማድረግ እየተሠራ እንደሆነ ገልጸዋል።

በመርሐ ግብሩ ላይ ሊቀ ትጉኀን ቀሲስ ዶ/ር ሙሉጌታ ስዩም ብፁዕነታቸው ከማኅበረ ቅዱሳን ጋር የነበራቸው ግንኙነት ምን እንደሚመስል የሚያሳይ ጽሑፍ ያቀረቡ ሲሆን አቡነ ጎርጎርዮስ ትውልዱን በመቅረጽ ወደ ቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ለማሰማራት የጣሉት መሠረትና የተጫወቱት ሚና ከፍተኛ መሆኑን ተናግረዋል።

ዜና ሕይወቱ ለብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ በሚል ርእስ ተጨማሪ ጽሑፍ ያቀረቡት ቀሲስ ሰሎሞን ወንድሙ በበኩላቸው ብፁዕነታቸው መምህር፣ ሕጻናት አሳዳጊ፣ የቤተ ክርስቲያን ሐዋርያዊ ተልእኮ ከቅዱስ ሲኖዶስ ተቀብለው በኃላፊነት የሠሩ፣ ሥርዓተ ትምህርት ይቀርጹ የነበሩ አባት መሆናቸውን ከሠሯቸው ሥራዎች መካከል የጠቀሱ ሲሆን በአጠቃላይ "ቤተ ክርስቲያን ሰው በሚያስፈልጋት ዘመን አባት ሆነው የተገኙ ናቸው።" በማለት ተናግረዋል።
©ማኅበረ ቅዱሳን

Address

Queen Elizabeth II Street
Addis Ababa
2QJ7+RXQ

Telephone

+251913502324

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከል - Tewahedo Media Center - TMC posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share