Gibe Addis

Gibe Addis Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Gibe Addis, Digital creator, Addis Ababa.

የአባጅፋር ቤተ መንግስት እድሳትና ምስጋናዬHaaromsa masaraa mooti Abbaa Jifaar fi galatefannaa koo✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅Masaraan mooti Abbaa Jifa...
13/11/2025

የአባጅፋር ቤተ መንግስት እድሳትና ምስጋናዬ
Haaromsa masaraa mooti Abbaa Jifaar fi galatefannaa koo
✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅
Masaraan mooti Abbaa Jifaar haala kanaan baayyee midhagee haaromfameera. Haaromsi amma kan haga harraa mara irraa calaan xiyyeefannaan guddaan qabamee waan hojjatameef sadarkaan marasaraa olkaaseera.

Akka nama waggaa torba dura masaraa Abbaa Jifaari xiyeefannaan akka kennamuuf midiyaa hawaasaatiin barreesera. Ajjasumas wagga shan dura qamaan mummicha ministeeraa Dr Abiy Ahmed Ali fi Preezdaanti motummaa naannoo Oromiyaa obboo shimallis Abdisaa gaafataa tureetti haala kanaan haaroomu isaatti galatoomaa jechun barbaada.

Waggaa 7 dura barreefama toora peeji kiyya kanaan maxanseefi suura masarichi yeroo digamuuf waa xiqqoon hafu maxxansa linki barreefama kana jala jirun ilaali.
🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴

የአሁኑ የንጉሥ አባጅፋር ቤተ መንግስት እድሳት ከእስካሁኖቹ ሁሉ እጅግ ከፍተኛ በሆነ ትኩረት በላቀ ሁኔታ በመታደሱ እንደምታዩት አምሮበታል። የዛሬ ሰባት ዓመት በማህበራዊ ሚዲያ ቤተ መንግሰቱ አደጋ ላይ መሆኑን ጠቅሼ እድሳት እንዱደረግለት ስወተውት ነበር።

ከአምስት ዓመት በፊት ለጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አሕመድ እና ለኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት ለአቶ ሽመልስ አብዲሳ በአካል በመቅረብ ለቤተመንግሰቱ ትኩረት እንዲሰጠው እንደጠየቀ ሰው ቤተ መንግስቱ በዚህ በላቀ መልኩ በመታደሱ ምስጋናዬን ከፍ ባለ ሁኔታ ማቅረብ እወዳለሁ። እድሳቱ የቤተመንግሰቱን ደረጃ ከፍ በማድረጉ ደስ ብሎኛል።

የዛሬ 7 ሰባት ዓመት ቤተመንግስቱ ሊፈርስ ጫፍ ላይ በነበረበት ጊዜ በዚሁ የፌስቡክ ገጽ የለጠፍኩትን ጽሁፍና በዚያን ጊዜ በምን ሁኔታ ላይ እንደነበረ ከዚህ በታች ባለው ሊንክ ይመልከቱ።

👇
https://www.facebook.com/share/p/1SJoujspE9/

09/11/2025
በመጨረሻ የባ/ዳር ተወላጁ መልዕክተኛው ሰይፉ ላይ በመቅረብ ራሱን ገልጧል‼️
09/11/2025

በመጨረሻ የባ/ዳር ተወላጁ መልዕክተኛው ሰይፉ ላይ በመቅረብ ራሱን ገልጧል‼️

በኢትዮጵያ ታሪክ ዕድገትና ውጣውረድ  ውስጥ ዘመን የማይሽረውን አሻራ ማኖር የቻለ ታላቅ ሰዉ ፣ታላቅ ምሁርና ፈላስፋ ፕሮፌሰር ላጲሶ ጌ.ዴሌቦ  ሕልፈተ ህይወት ልብ ሰባሪ ነው።  ነፍስ ይማር...
09/11/2025

በኢትዮጵያ ታሪክ ዕድገትና ውጣውረድ ውስጥ ዘመን የማይሽረውን አሻራ ማኖር የቻለ ታላቅ ሰዉ ፣ታላቅ ምሁርና ፈላስፋ ፕሮፌሰር ላጲሶ ጌ.ዴሌቦ ሕልፈተ ህይወት ልብ ሰባሪ ነው።
ነፍስ ይማር።

የእኔ ጥቅም ከሕዝብ ጥቅም  ይበልጣል የሚሉ ጥቅመኞች ! በፍ/ቤት የመንግስትን ሀብት የሚያስመልሱ  ጠንካራ ተቋማት መሪዎች  ላይ ለምን ጥቅሜ ተነካ የሚሉ ግለሰቦች  በሚዲያ ዘመቻ  የፍ/ቤት...
04/11/2025

የእኔ ጥቅም ከሕዝብ ጥቅም ይበልጣል የሚሉ ጥቅመኞች !

በፍ/ቤት የመንግስትን ሀብት የሚያስመልሱ ጠንካራ ተቋማት መሪዎች ላይ ለምን ጥቅሜ ተነካ የሚሉ ግለሰቦች በሚዲያ ዘመቻ የፍ/ቤት ውሳኔን እያጣጠሉ እየተመለከትን ነው፡ ፡

አንዳንድ ግለሰቦች ከለውጡ በፊት ከጥቀመኛ ባለስልጣኖች ጋር ተመሳጥረው የወስዱትን የመንግሥት ይዞታ በፍ/ቤት ለመንግስት እንዲያሰረክቡ ሲወሰንባቸው ቀድሞ የለመዱትን ሕገ ወጥነት ተግባር የማያስተናግድ የሥራ መሪ ሲያጋጥማቸው በማህበራዊ ሚዲያ ጥቅማቸው ሊያሰከብሩ ሲንቀሳቀሱ እያየን ነው፡ ፡

በተለይ አሁን ላይ የመንግስትና የሕዝብ ጥቅም ይከበር ብለው የቆሙን የተቋም መሪዎች ማበረታት የሚጠበቅ ሆኖ ሳለ ጭራሽ ሙሰኛ ብለው ቢቻላቸው ለማሸማቀቅ ጥረት ሲያደርጉ ስንመለኮት የጉዳዩን አሳሳቢነት በግልፅ ያሳያል።

በተለይ የመንግስት ደጋፊ ነኝ የሚሉ ነገር ግን የመንግስትና የሕዝብ ጥቅምን የሚያስከብሩ ጠንካራ ሐቀኛ መሪዎችን ስም በማጥፋት መልሰው መንግስትን የሚወጉ ግለሰቦች አንድ ሊበሉ ይገባል ።

እነዚህ ግለሰቦች ያልተረዱት ነገር ቢኖር መንግስት ከሚኮራባቸው ውጤቶች አንዱ የመንግሥት ይዞታዎችና ቤቶችን ለማስመለሰ የተሰራው ሥራ ነው፡ ፡

አንትነህ አብርሃም የተበለውም ግለሰብ
በፍ/ቤት ተከራክሮ ማሸነፍ ሰያቅተውና ከለውጥ በሕገውጥ መንገድ የወሰደው የመንግስት ቦታን ፍ/ቤት ለፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን እንዲመለሰ ተወስኗል።

ክርክሩ የጀመረው በስር መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ሲሆን ኮርፖሬሽኑ ቦታውን ለፓርላማ አባላት መኖሪያ ፍሳሽ ቆሻሻ ማጣሪያ ጣቢያነት የሚጠቀምበት ሲሆን በዚህ ቦታ ላይ በወረራ የያዙት የእነ አንተነህ አብርሃም እናት ወ/ሮ ሳራ ጀግሬ ቦታውን አስረክቡ ሲባሉ ከግለሰቦች በስጦታ ተሰጥቶኝ ነው አለቅም ማለታቸውን ተከትሎ ይዞታውን እንዲያስረክቡ በማለት ክስ ተመሰርቶባቸው ፍ/ቤት ለፌቤኮ ወስኗል።

በመቀጠልም የሳራ ወራሽ ነን የሚሉ ልጆች በ3 የተለያየ ጊዜ የመቃወም አቤቱታ በፍ/ብ/ስ/ስ/ህ/ቁ 358 መሰረት አቅርበዉ በሶስቱም ላይ ተወስኖባቸዋል።

አሁን ላይ ከአራቱ ተከራካሪዎች አንደኛው ልጅ አንተነህ አብርሀም ሰበር ድረስ ጉዳዩን ወስደውት በተቋሙ መልሶ ተሰጥቷቸው ለምርመራ ለ30/3/2018 ዓ.ም ተቀጥሯል።

አንተነህ አብርሀም ያለ አግባብ የያዘው መሬት መሆኑን ጠንቅቆ ስለሚያውቅና በእጁ ማስረጃ የሚበል ነገር ሰለሌለው የሰበር ውሳኔ የተለየ አይሆንም በሚል ግምት የተቋሙን መሪዎች ስም እያነሳ ስም ለማጥፋት ጥረት እያደረገ እንደሆነ ሰምተናል።

የፌቤኮ ዋና ሥራ አስፈፃሚ በያዙት ጠንካራ አቋም ሊኮሩ ይገባል ። እኛም በሕዝባዊ አቋማችሁና የግል ጥቅማችሁን ትታችሁ ሕገወጦችን ለመጋፈጥ በመወሰናችሁ አድንቀናል።

ከእውነታው ውጭ መረጃን ለማዛባት የሚደረጉ ጥረቶች የማይቋሙ ከሆነና ያለ መረጃ ግለሰብ ተኮር ስም ማጥፋቶች ከቀጠሉ ጉዳዩ በሕግ እንዲታይ ማድረግም ይገባል።

መንግስትም ያወጣውን የሚዲያ አጠቃቀም አዋጅ ሲጣስ ዝም ብሎ መመልከት የለበትም ።አስፈላጊውን ሕጋዊ እርምጃ ሊወስድ ይገባል።

የእኔ ጥቅም ከሕዝብ ጥቅም ይበልጣል የሚሉ ጥቅመኞች !

በፍ/ቤት የመንግስትን ሀብት የሚያስመልሱ ጠንካራ ተቋማት መሪዎች ላይ ለምን ጥቅሜ ተነካ የሚሉ ግለሰቦች በሚዲያ ዘመቻ የፍ/ቤት ውሳኔን እያጣጠሉ እየተመለከትን ነው፡ ፡

አንዳንድ ግለሰቦች ከለውጡ በፊት ከጥቀመኛ ባለስልጣኖች ጋር ተመሳጥረው የወስዱትን የመንግሥት ይዞታ በፍ/ቤት ለመንግስት እንዲያሰረክቡ ሲወሰንባቸው ቀድሞ የለመዱትን ሕገ ወጥነት ተግባር የማያስተናግድ የሥራ መሪ ሲያጋጥማቸው በማህበራዊ ሚዲያ ጥቅማቸው ሊያሰከብሩ ሲንቀሳቀሱ እያየን ነው፡ ፡

በተለይ አሁን ላይ የመንግስትና የሕዝብ ጥቅም ይከበር ብለው የቆሙን የተቋም መሪዎች ማበረታት የሚጠበቅ ሆኖ ሳለ ጭራሽ ሙሰኛ ብለው ቢቻላቸው ለማሸማቀቅ ጥረት ሲያደርጉ ስንመለኮት የጉዳዩን አሳሳቢነት በግልፅ ያሳያል።

በተለይ የመንግስት ደጋፊ ነኝ የሚሉ ነገር ግን የመንግስትና የሕዝብ ጥቅምን የሚያስከብሩ ጠንካራ ሐቀኛ መሪዎችን ስም በማጥፋት መልሰው መንግስትን የሚወጉ ግለሰቦች አንድ ሊበሉ ይገባል ።

እነዚህ ግለሰቦች ያልተረዱት ነገር ቢኖር መንግስት ከሚኮራባቸው ውጤቶች አንዱ የመንግሥት ይዞታዎችና ቤቶችን ለማስመለሰ የተሰራው ሥራ ነው፡ ፡

አንትነህ አብርሃም የተበለውም ግለሰብ
በፍ/ቤት ተከራክሮ ማሸነፍ ሰያቅተውና ከለውጥ በፊት በሕገወጥ መንገድ የወሰደው የመንግስት ቦታን ፍ/ቤት ለፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን እንዲመለሰ ተወስኗል።

ክርክሩ የጀመረው በስር መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ሲሆን ኮርፖሬሽኑ ቦታውን ለፓርላማ አባላት መኖሪያ ፍሳሽ ቆሻሻ ማጣሪያ ጣቢያነት የሚጠቀምበት ሲሆን በዚህ ቦታ ላይ በወረራ የያዙት የእነ አንተነህ አብርሃም እናት ወ/ሮ ሳራ ጀግሬ ቦታውን አስረክቡ ሲባሉ ከግለሰቦች በስጦታ ተሰጥቶኝ ነው አለቅም ማለታቸውን ተከትሎ ይዞታውን እንዲያስረክቡ በማለት ክስ ተመሰርቶባቸው ፍ/ቤት ለፌቤኮ ወስኗል።

በመቀጠልም የሳራ ወራሽ ነን የሚሉ ልጆች በ3 የተለያየ ጊዜ የመቃወም አቤቱታ በፍ/ብ/ስ/ስ/ህ/ቁ 358 መሰረት አቅርበዉ በሶስቱም ላይ ተወስኖባቸዋል።

አሁን ላይ ከአራቱ ተከራካሪዎች አንደኛው ልጅ አንተነህ አብርሀም ሰበር ድረስ ጉዳዩን ወስደውት በተቋሙ መልሶ ተሰጥቷቸው ለምርመራ ለ30/3/2018 ዓ.ም ተቀጥሯል።

አንተነህ አብርሀም ያለ አግባብ የያዘው መሬት መሆኑን ጠንቅቆ ስለሚያውቅና በእጁ ማስረጃ የሚበል ነገር ሰለሌለው የሰበር ውሳኔ የተለየ አይሆንም በሚል ግምት የተቋሙን መሪዎች ስም እያነሳ ስም ለማጥፋት ጥረት እያደረገ እንደሆነ ሰምተናል።

የፌቤኮ ዋና ሥራ አስፈፃሚ በያዙት ጠንካራ አቋም ሊኮሩ ይገባል ። እኛም በሕዝባዊ አቋማችሁና የግል ጥቅማችሁን ትታችሁ ሕገወጦችን ለመጋፈጥ በመወሰናችሁ አድንቀናል።

ከእውነታው ውጭ መረጃን ለማዛባት የሚደረጉ ጥረቶች የማይቋሙ ከሆነና ያለ መረጃ ግለሰብ ተኮር ስም ማጥፋቶች ከቀጠሉ ጉዳዩ በሕግ እንዲታይ ማድረግም ይገባል።

መንግስትም ያወጣውን የሚዲያ አጠቃቀም አዋጅ ሲጣስ ዝም ብሎ መመልከት የለበትም ።አስፈላጊውን ሕጋዊ እርምጃ ሊወስድ ይገባል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዛሬ ለምክር ቤቱ ማብራሪያ እና ምላሽ ይሰጣሉ።የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 42ኛ መደበኛ ስብሰባውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) በተገኙበት ዛሬ ያካሂዳል።ጠቅላይ...
03/07/2025

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዛሬ ለምክር ቤቱ ማብራሪያ እና ምላሽ ይሰጣሉ።

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 42ኛ መደበኛ ስብሰባውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) በተገኙበት ዛሬ ያካሂዳል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በመገኘት ከምክር ቤት አባላት ለሚነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽ እና ማብራሪያ ይሰጣሉ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በስብሰባው ላይ የመንግስትን የ2017 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈፃጸም አስመልክቶ ከምክር ቤቱ አባላት ለሚነሱላቸው ጥያቄዎች ማብራሪያ እና ምላሽ ይሰጣሉ።

ምክር ቤቱ የፌዴራል መንግሥት የ2018 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀት ያጸድቃል ተብሎም ይጠበቃል።

በስብሰባው የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮች እና የዓለም አቀፍ ተቋማት ተጠሪዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ ታዋቂ ግለሰቦች እና የተፎካካሪ ፓርቲ አመራሮች ይገኛሉ።

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gibe Addis posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share