Anova Media

Anova Media Anova Media is an infotainment media, connect with us.

  በኳስ ተጫዋቹ ሞት ውሳኔ ተላለፈ።ሰበር ዜና - የፍርድ ቤት ውሳኔ ዜና* 16 ዓመት አደይ ጌታቸው ፅኑ እስራት * 15 ዓመት ሉንጎ ሉቃስ ፅኑ እስራት የአለልኝ አዘነ ግድያ እና የተላለፈው...
22/07/2025

በኳስ ተጫዋቹ ሞት ውሳኔ ተላለፈ።
ሰበር ዜና - የፍርድ ቤት ውሳኔ ዜና

* 16 ዓመት አደይ ጌታቸው ፅኑ እስራት
* 15 ዓመት ሉንጎ ሉቃስ ፅኑ እስራት

የአለልኝ አዘነ ግድያ እና የተላለፈው ፍርድ!

የቀድሞው እግር ኳስ ተጫዋች አለልኝ አዘነን በመግደል ወንጀል ተከሰው የነበሩት ባለቤቱ ወ/ሮ አደይ ጌታቸው እና የእህቷ ባል ሉንጎ ሉቃስ በጋሞ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት የጽኑ እስራት ተፈረደባቸው።

ፍርድ ቤቱ በዛሬው ዕለት ባስተላለፈው ውሳኔ፣

1. ወ/ሮ አደይ ጌታቸው የ16 ዓመት ጽኑ እስራት ሲፈረድባቸው፣

2. የባለቤቱ የእህቷ ባል (ሉንጎ ሉቃስ) ላይ ደግሞ የ15 ዓመት ጽኑ እስራት ተበይኖበታል።

ይህ አስደንጋጭ ክስተት የተከሰተው አለልኝ አዘነ እና ባለቤቱ ከተጋቡ ከ15 ቀናት በኋላ መጋቢት 17 ቀን 2016 ዓ.ም. ነበር።

ፍርድ ቤቱ በሰውና በሰነድ ማስረጃዎች መሠረት ወንጀሉ መፈጸሙን ካረጋገጠ በኋላ ይህን ውሳኔ ማሳለፉ ታውቋል።

የአለልኝ አዘነ ግድያ በብዙዎች ዘንድ አስደንጋጭ እና አሳዛኝ ክስተት ሆኖ ሲነገር ቆይቷል።

  አምስት የአንድ ቤተሰብ አባላት ህይወታቸው አልፋል።አምስት የአንድ ቤተሰብ አባላት በመሬት መንሸራተት ህይወታቸው ማለፉ ተዘገበ።በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኣሪ ዞን በደቡብ ኣሪ ወረዳ ኮመር ቀ...
21/07/2025

አምስት የአንድ ቤተሰብ አባላት ህይወታቸው አልፋል።

አምስት የአንድ ቤተሰብ አባላት በመሬት መንሸራተት ህይወታቸው ማለፉ ተዘገበ።

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኣሪ ዞን በደቡብ ኣሪ ወረዳ ኮመር ቀበሌ ውልሽር በሚባል አካባቢ ትናንት ምሽት 4:00 ገደማ በተከሰተ የመሬት መንሸራተት አደጋ ከአንድ ቤት የአምስት ሰዎች ሕይወት ተቀጥፏል። ‎

የአደጋው ሰለባ የሆኑት አባትና እናት ከ3 ልጆች ጋር ነው ተብሏል። EThio Times

በአፍንጫ ኢንፌክሽን አፍንጫውን ያጣው ወጣት ግንባሩ ላይ አዲስ አፍንጫ እንዲያድግ ተደረገለት📌ግንባሩ ላይ እንዲያድግ የተደረገው አፍንጫም ወደ ቦታው በትክክል እንዲተከል ተድርጓል ነው የተባለ...
15/07/2025

በአፍንጫ ኢንፌክሽን አፍንጫውን ያጣው ወጣት ግንባሩ ላይ አዲስ አፍንጫ እንዲያድግ ተደረገለት

📌ግንባሩ ላይ እንዲያድግ የተደረገው አፍንጫም ወደ ቦታው በትክክል እንዲተከል ተድርጓል ነው የተባለው

|በቻይና አስደናቂ የህክምና ታሪክ ተመዝግቧል። በአፍንጫው ላይ በደረሰበት ከባድ ኢንፌክሽን ምክንያት አፍንጫውን ያጣ አንድ ወጣት፣ ዶክተሮች በፈጠራ የህክምና ዘዴ አዲስ አፍንጫ በግንባሩ ላይ በማደግ ወደ ትክክለኛው ቦታው ከመተካታቸው በፊት ተአምር ፈጽመዋል ነው የተባለው።

ይህ ህክምና የጀመረው ወጣቱ በደረሰበት ኢንፌክሽን ምክንያት አፍንጫው በእጅጉ በመጎዳቱ እና ሙሉ በሙሉ በመጥፋቱ ነበር ተብሏል። የቻይና ሐኪሞችም ለዚህ ችግር መፍትሄ ለመስጠት ወሰኑ። በመጀመሪያ የግንባሩን ቆዳ እና የጎድን አጥንት ጨምሮ ሌሎች ቁሳቁሶችን በመጠቀም በአፍንጫው ቅርጽ መሠረት አዲስ አፍንጫ በግንባሩ ላይ በጥንቃቄ እንዲያድግ አደረጉ ይላል ዘገባው። ይህ ሂደት አዲሱ አፍንጫ ትክክለኛውን የደም አቅርቦት እና ቅርፅ እንዲይዝ አስችሎታል ተብሎለታል።

ከበርካታ ወራት እድገት በኋላ፣ በግንባሩ ላይ ሙሉ በሙሉ ያደገው አፍንጫ ወደ ትክክለኛው ቦታው በስኬት ተተክሏል የተባለ ሲሆን ይህ ልዩ እና ውስብስብ ሂደት የዘመናዊ የህክምና ሳይንስን አቅም በድጋሚ ያሳየ ሲሆን፣ ለወደፊቱ የቲሹ መልሶ ማልማት (tissue regeneration) እና የመተካት ቀዶ ጥገናዎች (transplant surgeries) ትልቅ ተስፋን የሚሰጥ ነው ተብሎለታል።

  ኢቢሲ ለጋዜጠኛ ቴዎድሮስ ካሳሁን የስራ እድል አመቻቸ ኢቢሲ ለጋዜጠኛ እና የፕሮግራም አቅራቢ ቴዎድሮስ ካሳሁን የስራ እድል ማመቻቸቱን እና ቴዎድሮስ ዝግጁ በሚሆንበት ጊዜ ስራ መጀመር እን...
13/07/2025

ኢቢሲ ለጋዜጠኛ ቴዎድሮስ ካሳሁን የስራ እድል አመቻቸ

ኢቢሲ ለጋዜጠኛ እና የፕሮግራም አቅራቢ ቴዎድሮስ ካሳሁን የስራ እድል ማመቻቸቱን እና ቴዎድሮስ ዝግጁ በሚሆንበት ጊዜ ስራ መጀመር እንደሚችል ገለፀ፡፡

ኢቢሲ ወደ ይዘት በሚል ከጀመራቸው አዳዲስ እና ተወዳጅ መሰናዶዎች መካከል 'እሁድ ቤት' አንደኛው ሲሆን፤ በእሁድ ቤት በዚያራ መሰናዶ ላይ ጋዜጠኛ ቴዎድሮስ በእንግድነት ቀርቧል፡፡

ጋዜጠኛ ቴዎድሮስ የበርካታ ሞያዎች ባለቤት ሲሆን ፊልሞች፣ የመድረክ ስራዎች እንዲሁም በቴሌቪዥን አቅራቢነት አገልግሏል፡፡

በቅርቡ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ባጋራው የእርዳታ ጥሪ በብዙዎች መነጋገሪያ የነበረው ቴዎድሮስ፤ ከእሁድ ቤት ዚያራ መሰናዶ ጋር በነበረው ቆይታ፤ አስቸጋሪ ጊዜያትን ማሳለፉን ተናግሯል፡፡

“የሆነ ስራ እጀምር እና ይበላሽብኛል“ የሚለው ቴዎድሮስ፤ በውስጡ የሚሰሙት መጥፎ ስሜቶች እንደነበሩም አንስቷል፡፡

ጋዜጠኛ ቴዎድሮስ ካጋጠመው ችግር በኋላ ወደ ገዳም በማምራት የፀሎት እና ጽሞና ጊዜ እንዳሳለፈ ገልፆ፤ ገዳም በነበረበት ወቅት ባጋራው ቪዲዮ ብዙዎች አለኝታነታቸውን እንዳሳዩት ተናግሯል፡፡

ወዳጆቼ፣ ጓደኞቼ እንዲሁም መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ያደረገልኝ ድጋፍ እና አለኝታነት የሚደነቅ ነው ለዚህም ምስጋና አቀርባለሁ ብሏል፡፡

ኢቢሲ ባመቻቸለት የስራ እድል እጅግ በጣም መደሰቱን የገለፀው ጋዜጠኛ ቴዎድሮስ፤ “ይህን እድል ማግኘቴ ትልቅ እድል ነው“ ሲል ተናግሯል፡፡

  የፖሊስ መረጃበምትሰራበት መኖሪያ  ቤት ውስጥ ተገድላ የተገኘችው ሟች ሀብታም ወርቁን በተመለከተ  በአንዳንድ  ማህበራዊ ሚዲያ የተሰራጨው መረጃ ሐሰተኛ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ...
13/07/2025

የፖሊስ መረጃ

በምትሰራበት መኖሪያ ቤት ውስጥ ተገድላ የተገኘችው ሟች ሀብታም ወርቁን በተመለከተ በአንዳንድ ማህበራዊ ሚዲያ የተሰራጨው መረጃ ሐሰተኛ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አስታወቀ፡፡

ሰኔ 30 ቀን 2017 ዓ/ም በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1 አለም ባንክ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ-ክርስቲያን አካባቢ ከቀኑ 11፡45 ሠዓት ላይ የቤት ሰራተኛ የሆነችው ሀብታም ወርቁ በምትሰራበት በመኖሪያ ቤት ውስጥ በስለት ተወግታ መሞቷን እና እህትማማቾች የሆኑ የአስርና የሰባት ዓመት ዕድሜ ያላቸው ህፃናትን አግተው የነበሩ ተጠርጣሪዎችን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ሐምሌ 5 ቀን 2017 ዓ/ም በቁጥጥር ስር ማዋሉንና ህፃናቱን ከነ ሙሉ ጤንነታቸው ለቤተሰቦቻቸው ማስረከቡን የሚገልፅ መረጃ ማሰራጨቱ ይታወቃል።

ይሁን እና በአንዳንድ ማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ ፖሊስ ታግተው የነበሩ ህፃናትን ማስለቀቁን እና ተጠርጣሪዎቹን ስለ መያዙ ብቻ እንጂ ስለሟች ሀብታም ወርቁ ያለው ነገር የለም በሚል እና በተለይ "አስከሬኗም ሳይመረመር" ወደ ትውልድ አካባቢዋ ተልኳል ተብሎ የተሰራጨው መረጃ ሐሰተኛ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ገልጿል።

የአዲስ አበባ ፖሊስ ሰኔ 30 ቀን 2017 ዓ/ም ሟች ሀብታም ወርቁን በምትሰራበት ቤት ውስጥ ህይወቷ እንዳለፈ የደረሰውን መረጃ መነሻ በማድረግ አስፈላጊውን ፖሊሳዊ ተግባር ከማከናወን ጀምሮ አስከሬኑን በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ተገቢው የፓቶሎጂ ምርመራ እንዲደረግ ወደ ሆስፒታሉ ያስገባ ሲሆን የምርመራ ውጤቱን በመጠባበቅ ላይ ይገኛል፤ ከዚህም ጋር ተያይዞ የተጠረጠሩ ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራውን አጠናክሮ የቀጠለ ሲሆን በቀጣይ የምርመራ ውጤቱን ለህዝብ እንደሚያሳውቅ ገልጿል።

አንዳንድ ግለሰቦች ማህበራዊ ሚዲያን በመጠቀም የተሳሳተ መረጃ የሚለቁ ሲሆን በቀጣይም ሀሰተኛ መረጃ የሚያሰራጩ ግለሰቦችን ተከታትሎ ተገቢውን ህጋዊ እርምጃ እንደሚወሰድ የአዲሰ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አስታውቋል።

  የእድሜ ልክ ፅኑ እስራት ተፈርዶባቸዋል!በእንስት ዘውዱ ሃፍቱ የጭካኔ የግድያ የተከሰሱት ተጠርጣሪዎች ጥፋተኞች ተብለው የፍርድ ውሳኔ ተላለፈባቸው። ተከሳሾቹ ለፍርድ ውሳኔ ማቅለያ ይሆነናል...
11/07/2025

የእድሜ ልክ ፅኑ እስራት ተፈርዶባቸዋል!

በእንስት ዘውዱ ሃፍቱ የጭካኔ የግድያ የተከሰሱት ተጠርጣሪዎች ጥፋተኞች ተብለው የፍርድ ውሳኔ ተላለፈባቸው።

ተከሳሾቹ ለፍርድ ውሳኔ ማቅለያ ይሆነናል በማለት " የቆየ ህመም አለብን " ቢሉም የመቐለ ዓይደር ስፔሻላይዝድ ሪፈራል ሆስፒታል ሃኪሞች የምርመራ ማስረጃ " የቆየ ህመም የለባቸውም " ሲል ምላሽ ሰጥቷል።

የመቐለ ማእላዊ ፍርድ ቤት በእንስት ዘውዱ ሃፍቱ አሰቃቂ ግድያ የመጨረሻ የፍርድ ውሳኔ ውሎ ምን ይመስል ነበር ?

የተጠርጣሪ ጠበቆች ትናንት ሀምሌ 3 " ደምበኞቻችን የቆየ ህመም አለባቸው ይህንን ለማረጋገጥ የህክምና ማስረጃ ለአርብ ሀምሌ 4 እናቀርባለን " ብለው ነበር።

ፍርድ ቤቱ ይህን ተቀብሎ ለዛሬ የመጨረሻ ውሳኔ ለመስጠት ቀነ ቀጠሮ ሰጥቶ ነበር።

ዛሬ አርብ ሀምሌ 4/2017 ዓ.ም ከመንግስት ሰራተኞች የስራ ሰዓት በፊት ቤተሰብ የሚገኙባቸው የሚድያና የሴቶች መብት ተቆርቋሪዎች በፍርድ ቤቱ በራፍ ደርሰው ተሰባስበዋል።

ተከሳሾች ለውሳኔ ማቅለያ ይሆነናል ብለው የጠየቁት የህክምና ማስረጃ የቆየ ህመም እንደሌለባቸው አረጋግጧል።

ዳኞችም ይህን ካረጋገጡ በኋላ በተከሳሾች ላይ ውሳኔ ሰጥተዋል።

አንደኛና ሁለተኛ ተከሳሾች ያሬድ ገብረስላሰ በላይ እና ኣንገሶም ሃይለማርያም በእድሜ ልክ ፅኑ እስራት እንዲቀጡ ፍርድ ቤቱ ወስኗል።

በፍርድ ቤቱ ውሳኔ አለመርካታቸው የገለፁት አስተያየት ሰጪዎች የወንጀል ደርጊቱን ከማጠራት እስከ ምርመራና ውሳኔ ድረስ በችግሮች የተተበተበ እንደነበር በመግለፅ ማረሚያ ቤት የፍርድ ውሳኔውን በጥብቅ እንዲተገብረው ጠይቀዋል።

"የጭካኔ ግድያው የሞት ፍርድ ያሰጥ ነበር " ያሉ ሌሎች አስተያየት ሰጪዎች ደግሞ " የተበዳይ ቤተሰቦች ወደ ቀጣዩ የፍርድ ቤት ይግባኝ ይጠይቁ " ብለዋል።

ከነሀሴ 2015 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ሀምሌ 4/2017 ዓ.ም የተጓዘው የእንስት ዘውዱ ሃፍቱ ግድያ በዚሁ ተቋጭቷል ሲል የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ መረጃውን ልኳል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ መቐለ የእንስቷን ግድያ ከመነሻው እስከ ፍርድ ሂደቱ ሲከታተል ቆይቷል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ

  ጋዜጠኛ ታደሰ ሚዛን አረፈአንጋፋው ጋዜጠኛ ታደሰ ሚዛን (ፒኤችዲ)  በአሜሪካ ሲያትል ከተማ በህመም ምክንያት ማረፉ ተሰምቷል ።  ታደሰ ሚዛን በኢቢሲ ሚዲያ ዳሰሳ በሚል ፕሮግራም በይበልጥ...
10/07/2025

ጋዜጠኛ ታደሰ ሚዛን አረፈ

አንጋፋው ጋዜጠኛ ታደሰ ሚዛን (ፒኤችዲ) በአሜሪካ ሲያትል ከተማ በህመም ምክንያት ማረፉ ተሰምቷል ።

ታደሰ ሚዛን በኢቢሲ ሚዲያ ዳሰሳ በሚል ፕሮግራም በይበልጥ ይታወቅ ነበር ።
ነፍስ ይማር!!

  አትሌት ቀነኒሳ በቀለ “ባዶ ወረቀት ተሰጥቶኝ ንብረቱ ለሌላ ባለሀብት ተሽጧል” በሚል ከፍተኛ ቅሬታ አቀረበአትሌቱ ጉዳዩ ለሚመለከታቸው አካላት ቅሬታ እያሰማ እንደሚገኝና አመራሮቹ ጉዳዩን ...
09/07/2025

አትሌት ቀነኒሳ በቀለ “ባዶ ወረቀት ተሰጥቶኝ ንብረቱ ለሌላ ባለሀብት ተሽጧል” በሚል ከፍተኛ ቅሬታ አቀረበ

አትሌቱ ጉዳዩ ለሚመለከታቸው አካላት ቅሬታ እያሰማ እንደሚገኝና አመራሮቹ ጉዳዩን ለማስጨረስ በሚል ከፍተኛ ገንዘብ እንደተቀበሉም ተነግሯል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ቤቶችና ኮንስትራክሽን ቢሮ ኃላፊ የሆኑት አቶ ብርሃኑ ዘውዴ ለአትሌት ቀነንሳ በቀለ በጋሞ ዞን አርባምንጭ ዙሪያ ወረዳ የእንቨስትመንት መሬት እንዲሰጥ በወቅቱ የዞኑ አስተዳደሪ አሁን ላይ ደግሞ የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ አባይነህ አበራ አማካይነት መሬት ሳይሰጥ ባዶ ደብዳቤ ብቻ ሰጥተው እንደነበር ለWT ሚዲያ የደረሰው የቅሬታ መረጃ ያመለክታል።

አትሌት ቀነንሳ በቀለ የእንቨስትመንት መሬት ሳይረከብ ደብዳቤ ብቻ በተቀበለበት ቦታ ላይ ግለሰቦች ሲያመርቱ የነበረው ሙዝ በዞኑ አስተባባሪነት አቶ ኢያሱ ወንድወሰን ለተባለ ተሸጥል።

በዚህ የተነሳ አትሌቱ ለሚመለከታቸው አካላት ቅሬታ እያሰማ እንደሚገኝና አመራሮቹ ጉዳዩን ለማስጨረስ በሚል ከፍተኛ ገንዘብ እንደተቀበሉም ለWT ሚዲያ የደረሰው መረጃ ያመለክታል።

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በተለይም ጋሞ ዞን አብዛኞቹ የእንቨስትመንት ጥያቄዎች በህጉ መሠረት በክልሉ ካቢኔ ተወሰነው መተላለፍ ሲገባው በአመራሮቹ ትዕዛዝ ብቻ እየተላለፈ እንደሆነ WT ሚዲያ በተደጋጋሚ በመረጃና በሰነድ በማስደገፍ መዘገቡ ይታወሳል።

ሰበር ዜና‼️  ለአንዱአለም ጎሳ የተሰጠው ሽልማት ተነጠቀ!የሃጫሉ ሁንዴሳ ፋውንዴሽን ይቅርታ ጠይቆ ለአንዱአለም የሰጠውን ሽልማት መነጠቁን አስታወቀ። ይህ ውሳኔ የህብረተሰቡን ድምፅ ያዳመጠ ...
05/07/2025

ሰበር ዜና‼️
ለአንዱአለም ጎሳ የተሰጠው ሽልማት ተነጠቀ!

የሃጫሉ ሁንዴሳ ፋውንዴሽን ይቅርታ ጠይቆ ለአንዱአለም የሰጠውን ሽልማት መነጠቁን አስታወቀ።

ይህ ውሳኔ የህብረተሰቡን ድምፅ ያዳመጠ እና አዎንታዊ ምላሽ የሰጠ መሆኑን ብዙዎች ገልጸዋል።

የሽልማቱ መነጠቅን ተከትሎ፣ ለቀነኒ ፍትህ የማግኘት ጥያቄዎች በህብረተሰቡ ዘንድ ዳግም እያየሉ መጥተዋል።

የመርማሪ አካላት ምርመራውን እና ክሱን በድጋሚ እንዲያዩት ጥሪ ቀርቧል፤

በተለይም በነፍስ ማጥፋት ወንጀል ብቻ ሳይሆን የቤት ውስጥ ጥቃትንም ጨምሮ ሁሉንም ገጽታዎች ማካተት እንዳለበት ተጠቁሟል።

የዚህ ጥያቄ አቅራቢዎች፣ ትግላቸውን በማህበራዊ ሚዲያ ብቻ ሳይወሰኑ በመሬት ላይም አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አስታውቀዋል።

ይህ ዘመቻ በየቤቱ የቤት ውስጥ ጥቃት ለሚደርስባቸው ምስኪን ሴቶች ሁሉ የሚደረግ ትግል መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል።
Zena24

  አትሌት ኃይሌ ገብረሥላሴ በልጁ መጽሐፍ ተጻፈለትከጀግናው አትሌት ኃይሌ ገብረሥላሴ ስኬቶች ጀርባ ያሉ ሚስጥሮችን ያካተተና በልጁ ሜላት ኃይሌ ገብረሥላሴ የተዘጋጀ አዲስ መጽሐፍ ለንባብ ሊበ...
05/07/2025

አትሌት ኃይሌ ገብረሥላሴ በልጁ መጽሐፍ ተጻፈለት

ከጀግናው አትሌት ኃይሌ ገብረሥላሴ ስኬቶች ጀርባ ያሉ ሚስጥሮችን ያካተተና በልጁ ሜላት ኃይሌ ገብረሥላሴ የተዘጋጀ አዲስ መጽሐፍ ለንባብ ሊበቃ ነው።

ይኸ በሜላት ኃይሌ ገብረሥላሴ የተዘጋጀው መጽሐፍ በአማርኛ "የኃይሌ ኃይሎች"በእንግሊዝኛ "Dissecting Haile" የተሰኘ ርዕስ ተሰጥቶታል።

መጽሐፉ የኢትዮጵያዊውን የረጅም ርቀት አትሌት እና ስራ ፈጣሪ የአትሌት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ ከእረኝነት ዘመኑ አንስቶ ያለውን ድንቅ ሕይወት፣መርሆች እና ዘላቂ ትሩፋት የሚዳስስ ከመሆኑ ባሻገር ከኃይሌ ገብረሥላሴ ስኬቶች ጀርባ ያሉ ሚስጥሮችን ያካተተ መጽሐፍ መሆኑን ደራሲዋ ሜላት ኃይሌ ገብረሥላሴ ተናግራለች።

አትሌት ኃይሌ ብዙውን የህይወት ታሪኩን ህዝብ የሚያውቀው ቢሆንም መጽሐፉ የሚያተኩረው የህይወትና የስራ ፍልስፍናው ላይ እንደሆነም ተነግሯል።

ለዚህም ልጁ እንደመሆኗ ከሌሎች ሰዎች በተለየ የአትሌት ኃይሌ ህይወት ለማወቅና ለመፃፍ እንዳስቻላት ሜላት ኃይሌ ገብረሥላሴ ገልጻለች።

በ12 ምዕራፍ ተከፋፍሎ የተዘጋጀውን መጽሐፍ ለማሰናዳት አንድ ዓመት እንደፈጀ ተነግሯል።

መጽሐፉ በአማርኛና በእንግሊዝኛ ቋንቋዎች እንዲሁም በብሬል የተሰናዳ እንደሆነም ተገልጿል።

"የኃይሌ ኃይሎች" ወይም "Dissecting Haile" መጽሐፍ የፊታችን ነሐሴ 2017 ዓ.ም በይፋ ለአንባቢያን የሚቀርብ ሲሆን በአዲስ አበባ ከተማ ማስጀመሪያ ዝግጅት፣ በመቀጠልም ዓለም አቀፍ ደረጃ ዝግጅቶች እንደሚኖሩ ተገልጿል።

በአማዞን፣ በቴሌብር፣ በተለያዩ የኦንላይን አማራጮችና እንዲሁም መጽሐፍት መሸጫ መደብሮች መፅሀፉ በኤሌክትሮኒክ አማራጮችና በሀርድ ኮፒ ከነሐሴ 2017 ዓ.ም መጨረሻ ጀምሮ በትዕዛዝ ለአንባቢያን ይቀርባል።

  አስደንጋጭ መረጃ!እንጦጦ ላይ ያሉ ባህር ዛፎች ሙሉ በሙሉ ይነሳሉ በአዲስ አበባ ተራራማ ቦታ በእንጦጦ ላይ የሚገኙት ባህር ዛፎች በቀጣይ ሦስት ዓመታት ውስጥ ሙሉ በሙሉ እንደሚነሱ እና በ...
04/07/2025

አስደንጋጭ መረጃ!

እንጦጦ ላይ ያሉ ባህር ዛፎች ሙሉ በሙሉ ይነሳሉ

በአዲስ አበባ ተራራማ ቦታ በእንጦጦ ላይ የሚገኙት ባህር ዛፎች በቀጣይ ሦስት ዓመታት ውስጥ ሙሉ በሙሉ እንደሚነሱ እና በሀገር በቀል ዛፎች እንደሚተኩ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ግርማ ሰይፉ ገልጸዋል።

ባህር ዛፍ ውሃ የመምጠጥ አቅሙ ከፍተኛ ስለሆነ እና መዲናዋ የከርሰ ምድርን ውሃ በአግባቡ ለመጠቀም እየሠራች በመሆኑ ዛፎቹን መተካት አንዱ መፍትሔ መሆኑን ቢሮ ኃላፊው ተናግረዋል።

ባህር ዛፎቹ ሲነሱ ግን በእጥፍ በሀገር በቀል ዛፎች እና ስነ ምህዳሩን ለማስተካከል በሚችሉ ዛፎች እየተተኩ መሆኑንም መናገራቸውን ኤ ኤም ኤን ዘግቧል፡፡

የአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር ከተጀመረ ወዲህ ከእንጦጦ ተነስተው ወደ መሀል ከተማ የሚፈሱት ወንዞች የውሃ መጠን መጨመሩንም ኃላፊው ተናግረዋል፡፡

በእንጦጦ ፓርክ ከሚገኙ የዛፍ አይነትቶች ባህር ዛፍ አብዛኛውን ቦታ ይሸፍናል።
(ኤ ኤም ኤን)

  ሐጫሉ አዋርድ የአንዱዓለም ጎሳን ሽልማት ነጥቆ ይቅርታ እንዲጠይቅ ተጠየቀየሐጫሉ ሁንዴሳ አዋርድ አዘጋጅ የሆነው ሐጫሉ ሁንዴሳ ፋውንዴሽን ድምጻዊ አንዱዓለም ጎሳን ከሸለመ በኋላ በህዝቡ ቅ...
04/07/2025

ሐጫሉ አዋርድ የአንዱዓለም ጎሳን ሽልማት ነጥቆ ይቅርታ እንዲጠይቅ ተጠየቀ

የሐጫሉ ሁንዴሳ አዋርድ አዘጋጅ የሆነው ሐጫሉ ሁንዴሳ ፋውንዴሽን ድምጻዊ አንዱዓለም ጎሳን ከሸለመ በኋላ በህዝቡ ቅሬታ አጋጥሞታል። በተለይ የሞዴል ቀነኒ አዱኛ ህይወቷ ከማለፉ በፊት ጥቃት ይደርስባት እንደነበር የሚያመለክቱ ምስሎች ከወጡ በኋላ በህዝቡ ዘንድ ቁጭት እና እልህ የታከለበት እንደ አዲስ ጉዳዩ እንዲነሳ ሆኗል።

የሞዴል ቀነኒ አዱኛ እጮኛ የነበረው ድምጻዊ አንዱዓለም ጎሳ የተሸለመው ሽልማት ተነጥቆ ፋውንዴሽኑ በ24 ሰዓት ውስጥ ለህዝቡ መግለጫ እንዲሰጥ ዘመቻም ተጀምሯል።

Address


Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Anova Media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

  • Address
  • Alerts
  • Claim ownership or report listing
  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share