Anova Media

Anova Media Anova Media is an infotainment media, connect with us.

እንኳን ለደመራና መስቀል በዓል አደረሳችሁ
26/09/2025

እንኳን ለደመራና መስቀል በዓል አደረሳችሁ

11/09/2025
የጤና፣ የስኬት፣ የመልካምነት ዓመት ይሁንልን!
11/09/2025

የጤና፣ የስኬት፣ የመልካምነት ዓመት ይሁንልን!

  ያሰበውም፣ የሞከረውም፣ የጀመረውም፣ ያስቀጠለውም፣ የፈፀመውም መልካም አድርገዋል። ራሳቸውን ያጡትም የማይረሳ አሻራ አኑረዋል። ኢትዮጵያዊያንም ታሪክ ሰርተዋል። ህዳሴው ለምረቃ በቅቷል። አ...
09/09/2025

ያሰበውም፣ የሞከረውም፣ የጀመረውም፣ ያስቀጠለውም፣ የፈፀመውም መልካም አድርገዋል። ራሳቸውን ያጡትም የማይረሳ አሻራ አኑረዋል። ኢትዮጵያዊያንም ታሪክ ሰርተዋል። ህዳሴው ለምረቃ በቅቷል። አንድ የሆንባቸው ነገሮች ሁሉ ውጤታቸው እስከምን ድረስ እንደሆነ አሳይቶናል።

"መኖር በጊፍት ሪልስቴት"  ጊፍት ሪልስቴት በ2% ቅድመ ክፍያ ብቻ ቤቶችን ለሽያጭ አቀረበ።ሪልስቴቱ ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ድጋፍ የሚውል ባለሁለት መኝታ ቤት አበርክቷል።ጊፍ...
29/08/2025

"መኖር በጊፍት ሪልስቴት"

ጊፍት ሪልስቴት በ2% ቅድመ ክፍያ ብቻ ቤቶችን ለሽያጭ አቀረበ።

ሪልስቴቱ ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ድጋፍ የሚውል ባለሁለት መኝታ ቤት አበርክቷል።

ጊፍት ሪልስቴት እስከ ጳጉሜ 1, 2017 ባቀረበው ልዩ የሽያጭ እድል እስከ 25% ቅናሽ የተደረገባቸው ናቸው።

ለሽያጭ የቀረቡት 2000 ምቹና ዘመናዊ ቤቶች ሲሆኑ ቦሌን ጨምሮ በከተማው እምብርት ቦታዎች የሚገኙ መሆኑ ተነግሯል።

እስከ 45% የባንክ ብድር የተመቻቸላቸው መኖሪያ ቤቶችና የንግድ ሱቆችን ያቀረበው ጊፍት ሪልስቴት በለገሀር እየተገነባ የሚገኘውን ከ12,000 በላይ ቤቶችና የንግድ ሞሎች የሚይዘውን መንደር ቀጣይ ምዕራፍ አስተዋውቋል።

ከ20 ዓመታት በላይ በሪልስቴት ልማት ላይ የካበተ ልምድ ያለው ጊፍት ሪልስቴት በተለያዩ የከተማዋ አካባቢዎች ገንብቶ ያስረከባቸው መኖሪያ ቤቶች ትልቅ ስምና ዝና ያተረፈለት መሆኑ ይነገርለታል።

  ከመስከረም ጀምሮ ለሠራተኛው ተጨማሪ የደመወዝ ማሻሻያ ለማድረግ መንግሥት ወሰነ ከመስከረም 2018 ጀምሮ ለመንግሥት ሠራተኛው ተጨማሪ የደመወዝ ማሻሻያ ለማድረግ መንግሥት ወስኗል፡፡ የፌደራ...
18/08/2025

ከመስከረም ጀምሮ ለሠራተኛው ተጨማሪ የደመወዝ ማሻሻያ ለማድረግ መንግሥት ወሰነ

ከመስከረም 2018 ጀምሮ ለመንግሥት ሠራተኛው ተጨማሪ የደመወዝ ማሻሻያ ለማድረግ መንግሥት ወስኗል፡፡

የፌደራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ባወጣው መግለጫ፤ መንግሥት የዜጎችን የኑሮ ሁኔታ ለማሻሻል የሀገር ዐቅም የሚፈቅደውን ርምጃ እየወሰደ ነው ብሏል፡፡

በዚህም ለመንግሥት ሠራተኛው ተጨማሪ የደመወዝ ማሻሻያ ለማድረግ መንግሥት መወሰኑን አስታውቋል፡፡

በማሻሻያው ዝቅተኛው የመንግሥት ሠራተኛ ደመወዝ ከብር 4 ሺህ 760 ወደ ብር 6 ሺህ እንዲያድግ ይደረጋል ነው ያለው።

ከፍተኛው የመንግሥት ሠራተኛ ደመወዝ ከብር 21 ሺህ 492 ወደ ብር 39 ሺህ እንዲያድግ ይደረጋል ብሏል።

የዲግሪ ተመራቂ መነሻ ደመወዝ ከብር 6 ሺህ 940 ወደ ብር 11 ሺህ 500 የሚሻሻል መሆኑን ገልጿል።

ከሲቪል ሰርቪስ ውጭ በተለያዩ ዘርፎች የተሠማሩ የመንግሥት ሠራተኞች ደመወዝም ማሻሻያ እንደሚደረግበት አስታውቋል።

ይህ የደመወዝ ማስተካከያ ከ160 ቢሊዮን ብር በላይ ተጨማሪ በጀት ጠይቋል ያለው ኮሚሽኑ፤ ይሄም ለደመወዝ የሚወጣውን ጠቅላላ ዓመታዊ የመንግሥት ወጪ 56ዐ ቢሊዮን ብር ያደርሰዋል ብሏል።

  አርቲስት ደበበ እሸቱ ማረፉ ተሰማአንጋፋው አርቲስት ደበበ እሸቱ ከዚህ ዓለም ድካም አርፏልዋል።አርቲስት ደበበ ሕክምናውን በተለያዩ ሆስፒታሎች ይከታተል ነበር።ለአርቲስቱ ቤተሰቦችና ወዳጆች...
17/08/2025

አርቲስት ደበበ እሸቱ ማረፉ ተሰማ

አንጋፋው አርቲስት ደበበ እሸቱ ከዚህ ዓለም ድካም አርፏልዋል።

አርቲስት ደበበ ሕክምናውን በተለያዩ ሆስፒታሎች ይከታተል ነበር።

ለአርቲስቱ ቤተሰቦችና ወዳጆች መፅናናትን እንመኛለን።
getutemesgen

  ሰው ማጠቢያ ማሽን ተሰራ!ጃፓን ሰው ማጠቢያ ማሽን መስራቷ ተዘገበ።ጃፓን ውስጥ የሚገኘው የሳይንስ ኩባንያ፣ ሰውን በ15 ደቂቃ ውስጥ የሚያጥብ፣ የሚያደርቅ እና የሚያዝናና የሰው ማጠቢያ ማ...
17/08/2025

ሰው ማጠቢያ ማሽን ተሰራ!

ጃፓን ሰው ማጠቢያ ማሽን መስራቷ ተዘገበ።

ጃፓን ውስጥ የሚገኘው የሳይንስ ኩባንያ፣ ሰውን በ15 ደቂቃ ውስጥ የሚያጥብ፣ የሚያደርቅ እና የሚያዝናና የሰው ማጠቢያ ማሽን ፈጥሮ ለዓለም አሳውቋል።

ይህ ማሽን አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ የተባለውን ዘመናዊ ቴክኖሎጂ በመጠቀም የሚሰራ ሲሆን፣ በቀጣዩ ዓመት በሚካሄደው ኤክስፖ 2025 ላይ ለአንድ ሺህ ጎብኚዎች እንዲሞከሩት ይቀርባል ተብሏል።

ማሽኑ ከሰውነት ባዮሜትሪክ መረጃ የሚሰበስቡ ዳሳሾች (sensors) የተገጠሙለት ሲሆን፣ የእያንዳንዱን ተጠቃሚ የልብ ምት እና የሰውነት ሁኔታ በመለየት ለግለሰቡ የሚመጥን የውሀ ሙቀት እና ፍሰት ያስተካክላል ተብሏል።

በ15 ደቂቃ ውስጥ ሙቅ ውሃ፣ የአየር አረፋዎች እና የውሃ ግፊት በመጠቀም ሰውነትን ያጥባል፤ ሙሉ በሙሉ ያደርቃል ተብሏል።

በተጨማሪም የሰውየውን ስሜት ተንትኖ የሚያዝናኑ ምስሎችንና ድምጾችን ወደ ውስጥ በማስተላለፍ የአእምሮ እረፍት እንዲያገኝ ያግዘዋል ነው የተባለው።

ይህ ፈጠራ፣ በተለይ በጃፓን በዕድሜ የገፉ ሰዎች እየበዙ በመምጣታቸው ከሰው እርዳታ ውጪ እራሳቸውን እንዲያጸዱ ለማስቻል እና የጤና ባለሙያዎችን ጫና ለመቀነስ ታስቦ የተፈጠረ ነው ተብሏል።

ይህ ዘመናዊ ማሽን ቤት ግንባታ ዘርፍ ዲዛይንን ሙሉ በሙሉ እንደሚቀይረው ታምኗል።

  ወደ ውጭ ሀገር እልካለሁ በማለት ከተለያዩ ግለሰቦች ከ1.3 ሚሊየን ብር በላይ አጭበርብሮ የተሰወረን ግለሰብ ፖሊስ በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራ መሆኑን አስታወቀ፡፡ጌትነት እንዳሻው...
15/08/2025

ወደ ውጭ ሀገር እልካለሁ በማለት ከተለያዩ ግለሰቦች ከ1.3 ሚሊየን ብር በላይ አጭበርብሮ የተሰወረን ግለሰብ ፖሊስ በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራ መሆኑን አስታወቀ፡፡

ጌትነት እንዳሻው የተባለ ተከሳሽ በየካ ክ/ከተማ ወረዳ 5 ልዩ ቦታው መገናኛ ሠላም ታወር ህንፃ ላይ ቢሮ ተከራይቶ ‹‹ ኤልያና የጉዞና አማካሪ ድርጅት ›› የሚል ህጋዊ እውቅና የሌለው ድርጅት በመክፈት ሰዎችን ወደ ውጭ ሀገር እልካለሁ በሚል ከተለያዩ ግለሰቦች እስከ 1 ሚሊየን 360ሺህ ብር ድረስ በመቀበል የማጭበርበር ወንጀል ሲፈፅም እንደነበረ ፖሊስ ገልጿል።

ግለሰቡ ግንቦት 09 ቀን 2017 ዓ/ም የግል ተበዳይ ብርቱካን እመብርሀን የተባለች ግለሰብን ወደ ውጭ ሀገር እልክሻለሁ በማለት 340ሺህ ብር በመቀበልና ቼክ እንደማታለያ በመስጠት ግለሰቧንም በተባለው ቀን ወደ ውጪ ሊልክ ባለመቻሉ ለፖሊስ ሪፖርት አድርገዋል፡፡

ከግለሰቧ ክስ በተጨማሪም ሰናይት ተክላይ፣ ሠናይት ገ/ኪዳን እና አብረኀት የተባሉ ግለሰቦች ከእያንዳቸው 340ሺህ ብር በመቀበልና ወደ ውጪ ሀገር እልካችኋለሁ በማለት መሰወሩን በመግለፅ ተጨማሪ ሪፖርት ለፖሊስም ደርሶታል፡፡

የክ/ከተማው ፖሊስ የቀረበለትን ክስ መሰረት በማድረግ ባደረገው መረጃ የማሰባሰብ ተግባር ተጠርጣሪው ዜጎችን ወደ ውጭ ሀገር የመላክ ምንም ዓይነት ህጋዊ ፈቃድ የሌለው ከመሆኑም በተጨማሪ በተለያዩ ክ/ከተሞች በተመሳሳይ የወንጀል ድርጊት ክስ ተመስርቶበት እየተፈለገ እንደሆነም ለመረዳት ተችሏል፡፡

ግለሰቡን ሲፈለግና ሲያፈላለግ የነበረው ፖሊስም ነሐሴ 07 ቀን 2017 ዓ/ም ባደረገው ብርቱ ክትትል ተከሳሽ ይኖርበታል በተባለው ለሚኩራ ክ/ከተማ ወረዳ 14 ልዩ ቦታው የካ አባዶ ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ ከጠዋት 12፡00 ሠዓት ላይ በቁጥጥር ስር ሊውልም ችሏል፡፡

ፖሊስ በግለሰቡ ላይ ተጨማሪ ምርመራ የማስፋት ተግባሩን አጠናክሮ የቀጠለ ሲሆን ከዚህ ቀደም በዚህ ግለሰብ ተመሳሳይ የማጭበርበር ወንጀል ተፈፅሞብኛል የሚል አካል ካለም የካ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ በአካል በመቅረብ መረጃ መስጠት የሚችል መሆኑም ተመላክቷል፡፡
አዲስ ፖሊስ

  ጋዜጠኛ ሶፎንያስ በSheger info YouTube ቀርቦ። አዎ ትንሽ የፊት ለውጥ አለኝበጎደኛ መከዳት......እውቁ ጋዜጠኛ ሶፎኒያስ ዋሲሁን ከብዙ ጊዜ መጥፋት በኋላ ብቅ ብሎ የስሜት ገ...
14/08/2025

ጋዜጠኛ ሶፎንያስ በSheger info YouTube ቀርቦ።

አዎ ትንሽ የፊት ለውጥ አለኝ

በጎደኛ መከዳት......

እውቁ ጋዜጠኛ ሶፎኒያስ ዋሲሁን ከብዙ ጊዜ መጥፋት በኋላ ብቅ ብሎ የስሜት ገነት የሆነ ታሪኩን አካፍሏል።

በተለይም በኢቲቪ ፕሮግራሞቹ በፍጥነትና በአድናቆት በሚቀርበው አቀራረቡ የምናውቀው ሶፎኒያስ፣ ባለፈው ጊዜ ከህዝብ አይን የጠፋው በሰላም አለመሆኑን ገልጿል።

የሚያሳዝነው፣ ሶፎኒያስ በልብ ስብራትና በጭንቀት (stress) ምክንያት ታሞ መልክና ጤንነቱ እንደተጎዳ አሳውቋል። ይህ የሆነው ደግሞ ከባልደረባው ጋር በነበራቸው የስራ ግንኙነት መካድ መሆኑን ገልጿል።

ሁለቱም በጋራ ትልቅ የገንዘብ ጥቅም የሚያስገኝ ፕሮጀክት አቅደው የነበረ ቢሆንም፣ በጓደኛው ክህደት ምክንያት ህልሙ መና እንደቀረ ተናግሯል።

"ከኋላ እራሴን ያገኘውት በሰንሰለት ፀበል ቦታ ነው" የሚለው የሶፎኒያስ ቃል ታሪኩ ምን ያህል አሳዛኝ እንደሆነ ያሳያል።

ይሁን እንጂ ሶፎኒያስ በህይወት ውስጥ ማግኘትና ማጣት የተለመደ መሆኑን በመገንዘብ፣ የሆነው ሆኖ ለፈጣሪ አሳልፎ መስጠትና ነገን በአዲስ መንፈስ መጀመር እንደሚገባ አበክሮ ተናግሯል።

  "ሙዚቃዬን ሰርቃኛለች፣ ይሄን ጉዳይ በዝምታ አላልፈውም" ድምፃዊት ቤተልሄም ዳኛቸው‎‎ሰሞኑን አያ "ጥራኝማ" በተሰኘው ነጠላ ዜማዋ ተወዳጅነት ያተረፈችው ሳምራዊት አዘነ  ከእዚህ በፊት ቅ...
10/08/2025

"ሙዚቃዬን ሰርቃኛለች፣ ይሄን ጉዳይ በዝምታ አላልፈውም" ድምፃዊት ቤተልሄም ዳኛቸው

‎ሰሞኑን አያ "ጥራኝማ" በተሰኘው ነጠላ ዜማዋ ተወዳጅነት ያተረፈችው ሳምራዊት አዘነ ከእዚህ በፊት ቅዳሜ ገብያ በተሰኘው ሙዚቃዋ ተወዳጅነትን አትርፋ በነበረችዋ ኑሮዋን በውጭ ሀገር ባደረገችው በድምጻዊት ቤተልሔም ዳኛቸው ቅሬታ ቀረበበት።

‎ድምጻዊ ቤተልሔም ዳኛቸው በማህበራዊ የትስስር ገጿ ‎«ሰው ባገሩ» ከሚለው አልበሜ ላይ የሚገኝ «አያ ጥራኝ» የሚለው ስራዬ ይገኝበታል።

ይሄን ስራዬን በእደባባይ የተዘረፍኩ ሲሆን ይህንን ጉዳይ ዝም ብየ የማልፈው አይደለም በህግ እጠይቃለሁ ስትል ገልፃለች።
‎እርስዎስ ምን ይላሉ?

  የፀጥታው ምክር ቤት አባላትን በእንባ ያራጩት አምባሳደር❗በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክርቤት የፍልስጤም ተወካይ የሆኑት ሪያድ መንሱር በሀገራቸው እየሆነ ያለው ነገር ሲናገሩ ...
06/08/2025

የፀጥታው ምክር ቤት አባላትን በእንባ ያራጩት አምባሳደር❗

በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክርቤት የፍልስጤም ተወካይ የሆኑት ሪያድ መንሱር በሀገራቸው እየሆነ ያለው ነገር ሲናገሩ በእምባ ታጅበው ነበር።

በእምባና በሲቃ የተካሔደው ስብሰባ በምክርቤቱ ታሪክ የመጀመርያው ነው ተብሏል።

እንደቆሎ እየረገፉ ያሉ ህፃናት የእናቶች ስቃይ የስደተኞች መከራ ከቃል በላይ ናቸው።

ጥርስ አልባውና ለጥቂቶች ብቻ የቆመው የፀጥታ ምክርቤት በህጻናት ላይ እየወረደ ያለውን ጥቃት ማስቆም ተስኖታል።

ዛሬ ላይ ሁሉም ከፈር ከመምጠጥ በዘለለ ያመጣው አንድም መፍትሔ የለም።

በጋዛ በየቀኑ ንፁሀን ዜጎች በእስራኤል ጥቃት ውድ ህይወታቸውን ይሰዋሉ።

ለፍልስጤም መብትና ነፃነት እታገላለሁ የሚለው ሀማስም ቢሆን የህፃናቱን ሞት የማስቆም አቅም የለውም።

እነዚህና ሌሎች ችግሮች ናቸው አምባሳደሩን በእንምባ እንዲያነቡ ያደረጋቸው።

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Anova Media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share