Afela አፍላ

Afela አፍላ አላማችን የጥቁሩ ዕንቁ ኩሩው ህዝብ እውነተኛ ልሳን መሆን ነው።

''ኢስላም ለፈጣሪ እጅን መስጠት እና በትእዛዙ ማደር ማለት ሲሆን
አምልኮትን ሁሉ በብቸኝነት ፍጹም ለአላህ ማድረግ ። ሌሎችን ፍጡራን የስልጣኑ ተጋሪ አለማድረግ፡ ይህን ዩኒቨረስ
ብቻውን የፈጠረለፍጡራን ሁሉ ሲሳያቸውን እሱ ብቻውን የሚመግብለስልጣኑ ተጋሪ ወይም እረዳት ተባባሪ የሌለው
ሃያል ጌታ መሆኑን ማመን። ነገ የትንሳኤ ቀን የፍርዱ ቀን ብቸኛ ባለቤት አላህ መሆኑን ማመን። ይህን ይመስላል
ብለን የምንመስልበት አምሳያ የሌለው ሃያል አምላክ አላህ በመባል ይታወቃል።
ኢስላም ማለት ለአላህ በመመሪያው በማደር ለትእዛዞቹ መንበርከክ ፡ እምነትን እና ልቦናን ለአላህ ፍጹም ማድረግ እና
ከአላህ ዘንድ የመጡ መመሪያዎችን በፍጹምነት ማ

መን ነው።
* አንድ ሰው ''ሙስሊም'' ነው ሊባል የሚቻለው የዚህ ግዙፍ አለም ሆነ ሌላ አለ የሚባለው አለም እና በውስጧ
ያሉት ነገሮች ሁሉ ፈጣሪ ተቆጣጣሪ አስተናባሪ ብቸኛ አምላክ አላህ ነው ብሎ ማመን እና ነቢዩ ሙሃመድ የመጨረሻው
መልእክተኛ ናቸው ብሎ ማመን ነው። ይህም በሌላ አነጋገር በእውነት የሚያመልኩት አምላክ ከአላህ በስተቀር የለም።
ነብዩ ሙሐመድም(ሰላም ለእሳቸው ይሁንና) ባሪያው እና መላክተኛው ናቸው ብሎ ማመን ነው። ይህም በ አረብኛ
«''ላኢላሃ-ኢለሏህ ሙሃመድ ረሱሉሏህ''» በመባል ይታወቃል።
በዓለም ላይ የእምነቱ ተከታዮቹ ከ1.፮ ቢሊዮን በላይ ሆነው ይገኛሉ።
ሱና ማለት የነብዩ ሙሐመድ ንግግር እና ስራ/ስሩ ብለው ያዘዙት እና ሲሰራ እያዩ በዝምታያለፉት (አትስሩ ብለው
ያልከለከሉት) በአጠቃላይ በህይወታቸው የሰሩት ስራ እና እንዲሰራ ያዘዙት ሁሉ ሱና ይባላል።
ማንኛውም ሙስሊም ኢስላምን የሚተገብረው ከነብዩ ሙሐመድ በተማረው መሰረት ብቻ ነው። ኢስላም ሙሉ እምነት ስለሆነ
ከጊዜ ብዛት አነሰ ተብሎ የሚጨመርበት ወይም በዝቷል ተብሎ የሚቀነስለት ነገር የለውም።
- * ሙስሊሞች ለማንኛውም ቦታ እና ጊዜ/ዘመንየሚያገለገል ቁርዓን እና ሃዲስ የሚባል መመሪያ አላቸው። ይህን
መመሪያም ነብዩ ሙሐመድ ባስተማሯቸው ሱና መሰረት ይተገብሩታል።
እነዚህ የ እምነቱን ድንጋጌዎች የሚያስተምሩት መመሪያዎች ቁርአን እና ሃዲስ ሲሆኑ ቁርአን ማለት በ መልአኩ ጅብሪል
አማካኝነት ወደ መሃመድ በወህይ የተወረደ የአላህ ቃል ማለት ነው። ሃዲስ ማለት ደግሞ ነብዩ ሙሐመድ ንግግሮች
ናቸው ።
''ኢስላም'' የነብያት ሁሉ ሃይማኖት መሆኑን ሙስሊሞች ጠንቅቀው ያምናሉ።
ይህ በ መካ አሁን ያለው እና ካዕባ በመባል የሚታወቀው ግንብ በነብዩ ኢብራሂም አብርሃምእና
ልጃቸው ዒስማኤል የተሰራ ነው ብለው ሙስሊሞች ያምናሉ።
ከአላህ ሌላ ያለን ፍጡርም ይሁን ማንኛውም አይነት ነገር ማምለክ በኢስላም ታላቅ ወንጀል ነው።
ኢማን (የልብ ስራ)የእምነት 6 መሰረታዊ ነግሮችን አጠቃልሎ ይዟል።
:1ኛ በአላህ (በአምላክ ወይም በፈጣሪ) ማመን
:2ኛ መላእክት እንዳሉት ማመን
:3ኛ በ''ኪታቡ'' (በመጽሃፎች ማመን)
:4ኛ በ ''ሩሱሎች''(ነብያቶች ማመን)
:5ኛ በመጨረሻው ቀን የፍርድ ቀን (ሞቶ መነሳት) እንዳለ ማመን
:6ኛ በቀደር ማመንን
የሚሉት ሲሆኑ ሰፋ ያለ ትንታኔ የሚያስፈልጋቸው ጉዳዮች ናቸው።
የ''ኢስላም''የተግባር መሰረታዊ ነገሮች 5 ሲሆኑ
:1ኛ አላህ አንድ ነው ሙሀመድ መላክተኛ ነው ብሎ ማመን
:2ኛ ሰላት መስገድ
:3ኝ ዘካ ምጽዋት ማውጣት
:4ና ጾም መጾም
:5ኛ ሃጅ (መካን መጎብኘት)ማድረግ ናቸው።
ከላይ የኢማን መሰረቶች 6 ናቸው ብለናል በመጠኑም ቢሆን በዝርዝር ለማየት እንሞክር
1ኛ በአላህ ማመን ማለት ሲዘረዘር ይህን ዓለም ብቻውን የፈጠረ፡ ብቻውን የሚያስተዳድር እና የሚቆጣጠር፡
ለፍጡራን ሲሳይ የሚለግስ፡ አምላክ አላህ ነው ብሎ ማመን ማለት ነው።
ይህ አለም ካለ ፈጣሪ አልተገኘም። የሰው ልጅም ካለ አላማ ወደዚህ ምድር አልመጣም። ያመጣው አንድ ፈጣሪ
አለው።የመጣውም ለአላማ ነው። የመፈጠራችን አላማም ፈጣሪያችንን ለማምለክ ነው። ይህን አለም መጥኖ አስተካክሎ
የፈጠረው፡ ሰማይን ካለ ምሰሶ ያቆመው
ጸሃይ እና ጨረቃ እንዲሁም ለሊት እና ቀን ሌሎችንም ፕላኔቶች መስመራቸውን ይዘውጠብቀው እንዲጓዙ የሚያደርግ
አምላክ ፈጣሪ አስተናባሪ ተቆጣጣሪ/አላህ ነው ብሎ ማመን አንዱ የኢማን መሰረት ነው።
ከማንኛውም አይነት እንከን እና ጉድለት የጠራ/በሰው ልጅ ላይ የሚታዩ የድክመት ምልክቶች ፍጹም የማይታዩበት
፡የማይበላ እና የማይጠጣ የማይወልድ የማይወለድ ፍጹም የ እሱም ቢጤም ሆነ አምሳያ ስለሌለው ይህን ይመስላል ብለን
ልንመስለው የማንችል ሃያሉ አምላክ አላህ ነው ብሎ ማመን ።
- * እሱ ለምን ሰራህ ተብሎ ሊጠየቅ የማይችል እሱ ግን የፈለገውን የሚሰራ እና የሚጠይቅየሚምር
የሚቀጣ/የሚፈጥር የሚገድል/የሚያስታምም የሚያድን/ የፈለገውን ሰሪ ብቻውን ቀሪ የፍርዱ ቀን ባለቤት አላህ ነው ብሎ
ማመን አስፈላጊ እና የግድ ነው።
2ኛ በመላእክት(በመላኢኮች ማመን) ከብርሃን የተፈጠሩ የማይበሉ የማይጠጡ ከተፈጠሩ ጀምሮ የፈጣሪን ትእዛዝ ብቻ
በመተግበር ላይ የሚዘወትሩ፡ መላእክት አሉት ብሎ ማመን የግድ ሲሆን ከነዚህ መላእክት ዋናዋናዎች ጂብሪል ሜካኤል
ኤስራፊል...የመሳሰሉት ይገኙበታል።
እነዚህ መላእክት ከራሳቸው ምንም ማድረግ የማይችሉ የማይጠቅሙ እና የማይጎዱ በመሆናቸው አምልኮ ለነሱ ተገቢ
አይደለም። እነሱ ፈጣሪያቸውን ሌት ከቀን በቅንንነት ያመልካሉ ፡አመጸኞች አይደሉም። ተግባራቸው የተለያየ ነው።
በጣም ትልቅ ፍጥረት ናቸው። ጅብሪል የሚባለው መላእክት 700 ክንፎች ሲኖሩት አንዱ ክንፍ ብቻ ሲዘረጋ ከጀምበር
መግቢያ እስከ መውጫ ይደርሳል። ይህ የሚያሳየው የ እነዚህ ፈጣሪ ምን ያህል ታላቅ መሆኑን ነው አሏሁ አክበር!!!

13/09/2025

ሀይማኖታዊ ትምህርትን {ግዕዘኛን } በመንግሥት ትምህርት ቤት ማስተማር የሀገሪቱን ህገ- መንግስት መቃረን ነው። የኢፌዴሪ ህገ መንግስት አንቀፅ 11 ንዑስ አንቀፅ 1 ና 2 መንግስት እና ሀይማኖት የተለያዩ መሆናቸውን እና አንዱ በሌላው ጣልቃ እንደማይገቡ ይደነግጋል። ይህንን ድንጋጌ በተቃረነ መልኩ በአማራ ክልል መንግስት ትምህርት ቤት ላይ የአንድን ሀይማኖታዊ ቋንቋ ለማስተማር መሞከር ከህግም፣ ከዕምነት እና ከሞራልም ያፈነገጠ ተግባር ነው። የሌሎችን የዕምነት ነፃነት ያልጠበቀ እና የአንድን ዕምነት ዕሳቤ በግድ ለመጫን የሚደረግ አደገኛ አካሄድ ነው።

ድሮና ዘንድሮ። የማይስማማ ካለ በኮመንት ሐሳቡን መግለፅ ይችላል።
27/07/2025

ድሮና ዘንድሮ። የማይስማማ ካለ በኮመንት ሐሳቡን መግለፅ ይችላል።

06/06/2025

‎ሰበር ! በአዲስ አበባ ጣልያን ትምህርት ቤት ለኢድ ቀን አልዘጋም ማለቱ ተማሪዎች እና ወላጆች በአስቸኳይ እንዲስተካከል ጠየቁ !

‎ትምህርት ቢሮ እንዲሁም መጅሊስ ጨምሮ የሚመለከተው አካል ተቋሙን በማናገር የተደረገዉ ዉሳኔ እንዲስተካከል እንዲያደርጉ እንጠይቃለን ። "ተጨማሪ እና የተማሪ ወላጆች

‎በአዲስ አበባ ሰሜን ሆቴል አካባቢ የሚገኘዉ ጣልያን ትምህርት ቤት ለሙስሊሞች የኢድ አል አደሀ ቀን አልዘጋም ማለቱ ሙስሊም ተማሪዎች እና ወላጆች በአስቸኳይ እንዲስተካከል ጠይቀዋል ።

‎ተማሪዎች ለሚዛን እንደገለፁት ተማሪዎች ዛሬ ወደ ትምህርት ቤቱ ተጠርተዉ አርብ የኢዱ እለት ትምህርት ስለሚኖር እንድትገቡ የሚል ትእዛዝ እንደተሰጣቸዉ ገልፀዋል ።ተማሪዎቹ ከዚህ ቀደም ለበአል ትምህርት ተምረን አናዉቅም ለሙስሊሙም ለሌላ አማኞችም ሲሆን ያሉ ሲሆን ይህ አዲስ እና ግራ እንዳጋባቸዉ ገልፀዉልናል ።

‎ የተማሪ ወላጆች በበኩላቸው በጉዳዩ ዙሪያ ለመነጋገር ከዳይሬክተሯ ጋር ተገናኝቶ የነበረ እንደሆነ ገልፀዉ ቅዳሜ ዝግጅት ስላለብን ተማሪዎች የግድ መግባት አለባቸዉ ከፈለጉ ሙስሊምች አለመግባት ይችላሉ የሚል ምላሽ እንደሰጠቻቸዉ ለሚዛን ገልፀዋል ።

‎ወላጆች ኢደል አደሀ ከሙስሊሞች ዋናዉ በአል ልጆቻችን ትምህርት ቤት አንልክም ያሉ ሲሆን እንዲህ አይነት ከፋፋይ አና በካሌንደር የፀደቀ ብሄራዊ በአል አላከብርም ማለት የሀገሪቱን ህግ አላከብርም ማለት ስለሆነ የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ወይም መጅሊስን ጨምሮ የሚመለከተዉ አካል ትምህርት ቤቱ ንቀቱን አቁሞ እንደ ሀገራችን ተቋማት ሁሉ በኢድ እለት ሊዘጋ ይገባል በማለት ገልፀዋል ።

‎ልጆቻችን በኢድ ቀን ትገባላችሁ ካልሆነ ቅሩ በመባላቸዉ ተረብሸዉ ይገኛሉ አፋጣኝ ምላሽ እንፈልጋለን ብለዋል ።

‎ሚዛን ሚዲያ ከትምህርት ቤቱ መረጃ ለማግኘት ዳይሬክተሯን ለማግኘት ያደረግነዉ ጥረት አልተሳካም ።

ምንጭ ሚዛን ሚዲያ Mizan Media ሚዛን ሚዲያ Mizan Media

 #ኡድሂያ : በኡድሂያ ዙርያ መሰረታዊ ነጥቦች ★1 - ኡድሂያ ማለት በዙልሂጃ ወር አስርኛው ቀን ከሰላተል ኢድ በኋላ ወደ አላህ ለመቃረብ ተብሎ የሚታረድ እርድ ነው ።2- ኡድሂያ በጣም ከጠ...
01/06/2025

#ኡድሂያ : በኡድሂያ ዙርያ መሰረታዊ ነጥቦች ★
1 - ኡድሂያ ማለት በዙልሂጃ ወር አስርኛው ቀን ከሰላተል ኢድ በኋላ ወደ አላህ ለመቃረብ ተብሎ የሚታረድ እርድ ነው ።
2- ኡድሂያ በጣም ከጠነከሩ የነብዩ صلى الله عليه وسلم ሱናዎች መካከል ነው። ኡድሂያ የነብዩ ኢብራሂምን ሱና ህያው ከማድረግ በተጨማሪ ለድሆች እና ችግረኞች መድረስ ነው።

3- ኡድሂያን በተመለከተ አላህ ከኛ የሚፈልገው ለእርሱ ያለንን ፍቅር ፣ፍራቻ፣ ተቅዋና ታዛዥነት ግልጽ ማድረጋችንን ነው ። አላህ እንዲህ ብሏል፤

{ﻟَﻦ ﻳَﻨَﺎﻝَ اﻟﻠَّﻪَ ﻟُﺤُﻮﻣُﻬَﺎ ﻭَﻻَ ﺩِﻣَﺎﺅُﻫَﺎ ﻭَﻟَٰﻜِﻦ ﻳَﻨَﺎﻟُﻪُ اﻟﺘَّﻘْﻮَﻯٰ ﻣِﻨﻜُﻢْ ۚ ﻛَﺬَٰﻟِﻚَ ﺳَﺨَّﺮَﻫَﺎ ﻟَﻜُﻢْ ﻟِﺘُﻜَﺒِّﺮُﻭا اﻟﻠَّﻪَ ﻋَﻠَﻰٰ ﻣَﺎ ﻫَﺪَاﻛُﻢْ ۗ ﻭَﺑَﺸِّﺮِ اﻟْﻤُﺤْﺴِﻨِﻴﻦَ} الحج 37
(አላህን ሥጋዎቿም ደሞቿም ፈጽሞ አይደርሰውም፡፡ ግን ከእናንተ የሆነው ፍራቻ ይደርሰዋል፡፡ እንደዚሁ አላህን በመራችሁ ላይ ልታከብሩት ለእናንተ ገራት፡፡ በጎ ሠሪዎችንም አብስር፡፡» )አል ሐጅ 37
4— የኡድሂያ ትሩፋቱ: ከዓኢሻ (ረ.ዐ) እንደተዘገበው የአላህ መልእክተኛ (ሷለላሁ አለይሂ ወሰለም) እንዲህ አሉ፡-“ከነህር /እርድ/ ቀን ሥራዎች ውስጥ የአደም ልጅ ደምን ከማፍሠስ በላይ ወደ አላህ ተወዳጅ የሆነ አንድም ሥራ አልሠራም። እርዷም የቂያማ ቀን ከነቀንዷ ፣ ፀጉሯና ጥፍሯ ትመጣለች። ደሙም መሬት ላይ ከማረፉ በፊት ከአላህ ዘንድ ቦታ ይይዛል። በዚህም ነፍሣችሁን አስደስቱ (ደስ ይባላችሁ)።” ቱርሙዝይ ዘግበውታል ።
5— ኡድሂያ ለማረድ የተዘጋጀ ሰው ኡድሂያውን እስኪያርድ ድረስ ፀጉሩንም ሆነ ጥፍሩን የሰውነቱን መንካት የለበትም። ከኡሙ ሰለማ (ረ.ዓ) በተላለፈው ሀዲስም ነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ)፡-“አንዳችሁ ኡድሂያ ለማረድ አስቦ አሥርቱ ቀናት የገቡ እንደሆነ ከፀጉሩም ሆነ ከሰውነቱ አንዳቸም ነገር አይንካ።” ብለዋል። (ሙስሊም እና ነሣኢ ዘግበውታል።)
6- ወቅቱ ፣ ኡድሂያ የሚታረደው ከዒድ ሰላት በኋላ ነው ። የአላህ መልዕክተኛ صلى الله عليه وسلم ከኢድ ሰላት በፊት ያረደ ሰው እንዲደግም አዘዋል።

7- የመጨረሻ ቀኑ ከዒድ (10 ዙልሂጃ) ቀን ጀምሮ እስከ 13ኛ ቀን ጸሀይ እስክትጠልቅ ድረስ ኡድሂያን ማረድ ይቻላል።

8- የሚታረደው እንስሳ ጾታው ወንድ ወይም ሴት መሆን ይችላል ። እድሜ ፣ ግመል ከሆነ5 አመት ፣ ከብት 2 አመት ፣ በግ 6 ወር ፍየል 1 አመት የሆናቸው ለኡድሂያ እርድ ይሆናሉ ።

9- ለኡድህያ ማይሆኑ እንስሳዎች፣ የአላህ መልዕክተኛ صلى الله عليه وسلم እንከን ያለባቸውን እንስሳት ለኡድሂያ እንዳናርድ ከልክለዋል።
ሀ— አንድ አይኑ የታወረ፣ የታመመ
ለ— ስብራት ያለበት፣ የሚያነክስ
ሐ—የከሳና የደከመ
መ—የታመመ እንስሳ ለኡድሂያ አይሆንም።

10- የኡድሂያ አንድ እንስሳን ለብቻ ማረድ እንደሚቻለው ሁሉ ለሰባት ሆኖ አንድን ግመል ወይም ከብት መጋራትም ይቻላል በግ ወይም ፍየል ግን ለአንድ ሰው ብቻ ነው ።
11–ለገፋፊው የድካሙ ዋጋ ከስጋው ወይም ቆዳው መሆን የለበትም የልፋቱ ዋጋ ከዚህ ውጭ በሆነ ነገር መሆን አለበት : ዋጋው ተከፍሎት በተጨማሪ ስጋ ወይም ቆዳው ቢሰጠው ችግር የለውም።

12- አንድ ሰው ኡድሂያ ሲያርድ ለራሱ እና በህይወት ላሉም ይሁን በህይወት ለሌሉ ቤተሰቦቹ ነይቶ ሊያርድ ይችላል።

13- የኡድሂያውን ስጋ፣ ለቤት፣ ለስጦታ እና ምግቡን አዘጋጅቶ ሰው ጠርቶ ማብላት ጥሩ ነው ።
14— ከዚህ በዓል (ኢድ አል አድሃ) ጋር ተያይዞ አላህን መዘከር ማብዛት እና አቅም በፈቀደው መጠን ቤተሰብን ዘና ማድረግ ተወዳጅ ነው ፣ ውዱ ነብያችን ሷለላሁ አለይሂ ወሰለም እንዲህ ይላሉ ፣
(أيَّامُ التَّشريقِ أيَّامُ أكلٍ وشُربٍ وبِعالٍ)

★ ሸርጡን ጠብቆ ከሚተገብሩት አላህ ያድርገን

50 k በ1 ወር ውስጥ......
21/01/2024

50 k በ1 ወር ውስጥ......

 #ለ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የሚሰጡ የትምህርት ዓይነቶችን ይፋ  ተደረገ ፡፡⚽⚽⚽⚽⚽⚽⚽⚽⚽⚽⚽⚽በሚኒስቴሩ የሥርዓተ ትምህርት ማበልፀጊያ መሪ ሥራ አስፈፃሚ ቴዎድሮስ ሸዋርገጥ (ዶ/ር) እ...
20/01/2024

#ለ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የሚሰጡ የትምህርት ዓይነቶችን ይፋ ተደረገ ፡፡
⚽⚽⚽⚽⚽⚽⚽⚽⚽⚽⚽⚽

በሚኒስቴሩ የሥርዓተ ትምህርት ማበልፀጊያ መሪ ሥራ አስፈፃሚ ቴዎድሮስ ሸዋርገጥ (ዶ/ር) እንዳሉት "በተያዘው በጀት ዓመት የ2ኛ ደረጃ ትምህርት በአዲሱ ሥርዓተ-ትምህርት መሠረት የትምህርት ዓይነቶች ተለይተው የመማር ማስተማር ሒደቱ እየተካሄደ ይገኛል ነው ያሉት።
ከዚህ ጋር ተያይዞም በ2016 ዓ.ም በ2ኛ ደረጃ መልቀቂያ ፈተና የሚሰጡ የትምህርት ዓይነቶችን መወሰን በማስፈለጉ ለ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በሁለቱም ዘርፎች ስድስት ስድስት የትምህርት ዓይነቶች እንዲሰጡ መወሰኑን ተናግረዋል፡፡

በዚህ መሰረትም የተፈጥሮ ሣይንስ ተማሪዎች እንግሊዝኛ፣ ሒሳብ፣ ፊዚክስ፣ ኬሚስትሪ፣ ባዮሎጂ እና ስኮላስቲክ አፕቲቲውድ ቴስት እንዲወስዱ መወሰኑን ገልጸዋል፡፡

በተመሳሳይ የማህበራዊ ሣይንስ ተማሪዎች እንግሊዝኛ፣ ሒሳብ፣ ታሪክ፣ ጂኦግራፊ፣ ኢኮኖሚክስ እና ስኮላስቲክ አፕቲቲውድ ቴስት የሚፈተኑ ይሆናል ነው ያሉት፡፡

የኢኮኖሚክስ ፈተና ለ2016 ዓ.ም ለ12ኛ ክፍል ብቻ የሚዘጋጅ መሆኑን ጠቁመው ÷ሌሎች የትምህርት ዓይነቶች ከ9 እስከ 11ኛ ክፍሎች በነባሩ ሥርዓተ ትምህርት እንዲሁም የ12ኛ ክፍል በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት እንደሚሆን ተናግረዋል፡፡

የሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች ትምህርት ቢሮዎችም የፈተና አሰጣጡን በተመለከተ ለተማሪዎች፣ ለወላጆች፣ ለመምህራን እና ለትምህርት ማህበረሰቡ ቅድመ ዝግጅት እንዲያደርጉ ከወዲሁ እንዲያሳውቁ አመላክተዋል፡፡

 #የሶማሊያ ክስ_ውድቅ ተደርጓል ተባለ✅✅🇪🇹✅  የፀጥታው ምክርቤት ያቀረበችው ክስ  ✅ #ሶማሊያ ኢትዮጵያ የተመድን ቻርተር በጣሰ መንገድ የግዛቴን አንድነት ተጋፍታለች በዚህም የተመድ የፀጥ...
20/01/2024

#የሶማሊያ ክስ_ውድቅ ተደርጓል ተባለ✅✅🇪🇹✅
የፀጥታው ምክርቤት ያቀረበችው ክስ ✅
#ሶማሊያ ኢትዮጵያ የተመድን ቻርተር በጣሰ መንገድ የግዛቴን አንድነት ተጋፍታለች በዚህም የተመድ የፀጥታው ምክርቤት አስቸኳይ ስብሰባ ጠርቶ ኢትዮጵያ ላይ ውሳኔ ያስተላልፍልኝ ስትል ያቀረበችው ክስ አሁን ላይ የፀጥታው ምክርቤት ሊቀመንበር በሆነችው አጀንዳ ነው ስትል ያጣጣለችው መሆኑ ተሰምቷል።✅

ታላቁን ዓሊም ሼይኽ ሳሊህን እናሳክም የገቢ  ማሰባሰቢያ ዝግጅት  እሮብ ምሽት 2፡00 ጀምሮ በቲክቶክ ቀጥታ ስርጭትቲክቶክ አካውንት https://www.tiktok.com/?lang=enከስር የ...
17/01/2024

ታላቁን ዓሊም ሼይኽ ሳሊህን እናሳክም የገቢ ማሰባሰቢያ ዝግጅት እሮብ ምሽት 2፡00 ጀምሮ በቲክቶክ ቀጥታ ስርጭት
ቲክቶክ አካውንት
https://www.tiktok.com/?lang=en
ከስር የተጠቀሱት የሸይኹ ልጃቸዉ የባንክ አካዉንት ቁጥሮች ናቸዉ።
ሙሉ ስም: Abdusomed Sualih Mustefa
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ: 1000214014355
አቢሲኒያ ባንክ: 80152628
አዋሽ ባንክ: 01304266942800
ዘምዘም ባንክ: 0000320820101

16/01/2024
16/01/2024

Address

Kara Korie
Addis Ababa
ADDISABEBA

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Afela አፍላ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Afela አፍላ:

Share