Afela አፍላ

Afela አፍላ አላማችን የጥቁሩ ዕንቁ ኩሩው ህዝብ እውነተኛ ልሳን መሆን ነው።

''ኢስላም ለፈጣሪ እጅን መስጠት እና በትእዛዙ ማደር ማለት ሲሆን
አምልኮትን ሁሉ በብቸኝነት ፍጹም ለአላህ ማድረግ ። ሌሎችን ፍጡራን የስልጣኑ ተጋሪ አለማድረግ፡ ይህን ዩኒቨረስ
ብቻውን የፈጠረለፍጡራን ሁሉ ሲሳያቸውን እሱ ብቻውን የሚመግብለስልጣኑ ተጋሪ ወይም እረዳት ተባባሪ የሌለው
ሃያል ጌታ መሆኑን ማመን። ነገ የትንሳኤ ቀን የፍርዱ ቀን ብቸኛ ባለቤት አላህ መሆኑን ማመን። ይህን ይመስላል
ብለን የምንመስልበት አምሳያ የሌለው ሃያል አምላክ አላህ በመባል ይታወቃል።
ኢስላም ማለት ለአላህ በመመሪያው በማደር ለትእዛዞቹ መንበርከክ ፡ እምነትን እና ልቦናን ለአላህ ፍጹም ማድረግ እና
ከአላህ ዘንድ የመጡ መመሪያዎችን በፍጹምነት ማ

መን ነው።
* አንድ ሰው ''ሙስሊም'' ነው ሊባል የሚቻለው የዚህ ግዙፍ አለም ሆነ ሌላ አለ የሚባለው አለም እና በውስጧ
ያሉት ነገሮች ሁሉ ፈጣሪ ተቆጣጣሪ አስተናባሪ ብቸኛ አምላክ አላህ ነው ብሎ ማመን እና ነቢዩ ሙሃመድ የመጨረሻው
መልእክተኛ ናቸው ብሎ ማመን ነው። ይህም በሌላ አነጋገር በእውነት የሚያመልኩት አምላክ ከአላህ በስተቀር የለም።
ነብዩ ሙሐመድም(ሰላም ለእሳቸው ይሁንና) ባሪያው እና መላክተኛው ናቸው ብሎ ማመን ነው። ይህም በ አረብኛ
«''ላኢላሃ-ኢለሏህ ሙሃመድ ረሱሉሏህ''» በመባል ይታወቃል።
በዓለም ላይ የእምነቱ ተከታዮቹ ከ1.፮ ቢሊዮን በላይ ሆነው ይገኛሉ።
ሱና ማለት የነብዩ ሙሐመድ ንግግር እና ስራ/ስሩ ብለው ያዘዙት እና ሲሰራ እያዩ በዝምታያለፉት (አትስሩ ብለው
ያልከለከሉት) በአጠቃላይ በህይወታቸው የሰሩት ስራ እና እንዲሰራ ያዘዙት ሁሉ ሱና ይባላል።
ማንኛውም ሙስሊም ኢስላምን የሚተገብረው ከነብዩ ሙሐመድ በተማረው መሰረት ብቻ ነው። ኢስላም ሙሉ እምነት ስለሆነ
ከጊዜ ብዛት አነሰ ተብሎ የሚጨመርበት ወይም በዝቷል ተብሎ የሚቀነስለት ነገር የለውም።
- * ሙስሊሞች ለማንኛውም ቦታ እና ጊዜ/ዘመንየሚያገለገል ቁርዓን እና ሃዲስ የሚባል መመሪያ አላቸው። ይህን
መመሪያም ነብዩ ሙሐመድ ባስተማሯቸው ሱና መሰረት ይተገብሩታል።
እነዚህ የ እምነቱን ድንጋጌዎች የሚያስተምሩት መመሪያዎች ቁርአን እና ሃዲስ ሲሆኑ ቁርአን ማለት በ መልአኩ ጅብሪል
አማካኝነት ወደ መሃመድ በወህይ የተወረደ የአላህ ቃል ማለት ነው። ሃዲስ ማለት ደግሞ ነብዩ ሙሐመድ ንግግሮች
ናቸው ።
''ኢስላም'' የነብያት ሁሉ ሃይማኖት መሆኑን ሙስሊሞች ጠንቅቀው ያምናሉ።
ይህ በ መካ አሁን ያለው እና ካዕባ በመባል የሚታወቀው ግንብ በነብዩ ኢብራሂም አብርሃምእና
ልጃቸው ዒስማኤል የተሰራ ነው ብለው ሙስሊሞች ያምናሉ።
ከአላህ ሌላ ያለን ፍጡርም ይሁን ማንኛውም አይነት ነገር ማምለክ በኢስላም ታላቅ ወንጀል ነው።
ኢማን (የልብ ስራ)የእምነት 6 መሰረታዊ ነግሮችን አጠቃልሎ ይዟል።
:1ኛ በአላህ (በአምላክ ወይም በፈጣሪ) ማመን
:2ኛ መላእክት እንዳሉት ማመን
:3ኛ በ''ኪታቡ'' (በመጽሃፎች ማመን)
:4ኛ በ ''ሩሱሎች''(ነብያቶች ማመን)
:5ኛ በመጨረሻው ቀን የፍርድ ቀን (ሞቶ መነሳት) እንዳለ ማመን
:6ኛ በቀደር ማመንን
የሚሉት ሲሆኑ ሰፋ ያለ ትንታኔ የሚያስፈልጋቸው ጉዳዮች ናቸው።
የ''ኢስላም''የተግባር መሰረታዊ ነገሮች 5 ሲሆኑ
:1ኛ አላህ አንድ ነው ሙሀመድ መላክተኛ ነው ብሎ ማመን
:2ኛ ሰላት መስገድ
:3ኝ ዘካ ምጽዋት ማውጣት
:4ና ጾም መጾም
:5ኛ ሃጅ (መካን መጎብኘት)ማድረግ ናቸው።
ከላይ የኢማን መሰረቶች 6 ናቸው ብለናል በመጠኑም ቢሆን በዝርዝር ለማየት እንሞክር
1ኛ በአላህ ማመን ማለት ሲዘረዘር ይህን ዓለም ብቻውን የፈጠረ፡ ብቻውን የሚያስተዳድር እና የሚቆጣጠር፡
ለፍጡራን ሲሳይ የሚለግስ፡ አምላክ አላህ ነው ብሎ ማመን ማለት ነው።
ይህ አለም ካለ ፈጣሪ አልተገኘም። የሰው ልጅም ካለ አላማ ወደዚህ ምድር አልመጣም። ያመጣው አንድ ፈጣሪ
አለው።የመጣውም ለአላማ ነው። የመፈጠራችን አላማም ፈጣሪያችንን ለማምለክ ነው። ይህን አለም መጥኖ አስተካክሎ
የፈጠረው፡ ሰማይን ካለ ምሰሶ ያቆመው
ጸሃይ እና ጨረቃ እንዲሁም ለሊት እና ቀን ሌሎችንም ፕላኔቶች መስመራቸውን ይዘውጠብቀው እንዲጓዙ የሚያደርግ
አምላክ ፈጣሪ አስተናባሪ ተቆጣጣሪ/አላህ ነው ብሎ ማመን አንዱ የኢማን መሰረት ነው።
ከማንኛውም አይነት እንከን እና ጉድለት የጠራ/በሰው ልጅ ላይ የሚታዩ የድክመት ምልክቶች ፍጹም የማይታዩበት
፡የማይበላ እና የማይጠጣ የማይወልድ የማይወለድ ፍጹም የ እሱም ቢጤም ሆነ አምሳያ ስለሌለው ይህን ይመስላል ብለን
ልንመስለው የማንችል ሃያሉ አምላክ አላህ ነው ብሎ ማመን ።
- * እሱ ለምን ሰራህ ተብሎ ሊጠየቅ የማይችል እሱ ግን የፈለገውን የሚሰራ እና የሚጠይቅየሚምር
የሚቀጣ/የሚፈጥር የሚገድል/የሚያስታምም የሚያድን/ የፈለገውን ሰሪ ብቻውን ቀሪ የፍርዱ ቀን ባለቤት አላህ ነው ብሎ
ማመን አስፈላጊ እና የግድ ነው።
2ኛ በመላእክት(በመላኢኮች ማመን) ከብርሃን የተፈጠሩ የማይበሉ የማይጠጡ ከተፈጠሩ ጀምሮ የፈጣሪን ትእዛዝ ብቻ
በመተግበር ላይ የሚዘወትሩ፡ መላእክት አሉት ብሎ ማመን የግድ ሲሆን ከነዚህ መላእክት ዋናዋናዎች ጂብሪል ሜካኤል
ኤስራፊል...የመሳሰሉት ይገኙበታል።
እነዚህ መላእክት ከራሳቸው ምንም ማድረግ የማይችሉ የማይጠቅሙ እና የማይጎዱ በመሆናቸው አምልኮ ለነሱ ተገቢ
አይደለም። እነሱ ፈጣሪያቸውን ሌት ከቀን በቅንንነት ያመልካሉ ፡አመጸኞች አይደሉም። ተግባራቸው የተለያየ ነው።
በጣም ትልቅ ፍጥረት ናቸው። ጅብሪል የሚባለው መላእክት 700 ክንፎች ሲኖሩት አንዱ ክንፍ ብቻ ሲዘረጋ ከጀምበር
መግቢያ እስከ መውጫ ይደርሳል። ይህ የሚያሳየው የ እነዚህ ፈጣሪ ምን ያህል ታላቅ መሆኑን ነው አሏሁ አክበር!!!

 #የሸገር ከተማ አስተዳደር በተደጋጋሚ እየፈፀመ ያለውን  ሙስሊሙን መስጂድ አልባ የmaድረግ ተግባር እንዲያቆም ተጠየቀ!በሸገር ከተማ አስተዳደር በኮዬ ፈጬ ክፍለከተማ በቱሉ ዲምቱ የሚገኘው ...
15/10/2025

#የሸገር ከተማ አስተዳደር በተደጋጋሚ እየፈፀመ ያለውን ሙስሊሙን መስጂድ አልባ የmaድረግ ተግባር እንዲያቆም ተጠየቀ!

በሸገር ከተማ አስተዳደር በኮዬ ፈጬ ክፍለከተማ በቱሉ ዲምቱ የሚገኘው ሰላም መስጂድ በ3 ቀናት ውስጥ ይፍረስ መባሉን ተከትሎ የሸገር ከተማ መጅሊስ አመራሮች በቦታው በመገኘት ምልከታ አድርገዋል፡፡

የሸገር ከተማ መጅሊስ አመራሮች በምላሻቸው የሸገር ከተማ አስተዳደር በተደጋጋሚ ጊዜ ካለምንም ውይይት መስጂዶችን ማፍረሱን አስታውሰው አሁንም በቱሉዲምቱ የሚገኘውን ሰላም መስጅድን ለማፍረስ መሞከር ሙስሊሙን ያስቆጣ ተግባር መሆኑን ገልፀዋል፡፡

አክለውም እንደ ሸገር መጅሊስ የሰላም መስጂድ ይፈርሳል መባልን ተከትሎ በአካል የሸገር ከተማ ከንቲባን ለማነጋገር ብንሄድም ልናገኘው አልቻልንም ብለዋል፡፡

በሸገር ከተማ የሚገኘው የኮዬ ፈጬ ክፍለከተማ አስተዳደር ያለምንም የፅሁፍ ደብዳቤ የመስጅዱ ቦታ ለልማት ይፈለጋል በሚል ይፈርሳል ማለቱን አንቀበለውም ሲሉ የሸገር ከተማና የኮዬ ፈጬ ክፍለከተማ መጅሊስ አመራሮች ገልፀዋል፡፡

የቱሉ ዲምቱ ሰላም መስጅድ ኮሚቴዎችና የአካባቢው ነዋሪዎች በበኩላቸው በዛሬው ዕለት የፌደራል መጅሊስና የኦሮሚያ መጅሊስ አመራሮችን አናግረው በጎ ምላሽ እንደሰጧቸው ጠቅሰዋል፡፡

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝደንት ሸይኽ ሀጂ ኢብራሂም ቱፋ ከኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳደር ሽመልስ አብዲሳ ጋር በኦሮሚያና በሸገር ሲቲ መስጂዶች እንደማይፈርሱ ስምምነት መፈፀማቸውን ገልፀውልናል ብለዋል፡፡

15/10/2025
አሰላሙ አለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካቱ።....................................................... ታላቁ ዓሊም ክቡር ዶክተር ተቀዳሚ ሙፍቲህ ሃጅ ዑመር እንድሪስ...
15/10/2025

አሰላሙ አለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካቱ።.......................................................
ታላቁ ዓሊም ክቡር ዶክተር ተቀዳሚ ሙፍቲህ ሃጅ ዑመር እንድሪስ የጤና እክል አጋጥሞዋቸው ሆስፒታል በህክምና ላይ ይገኛሉ::
አላህ አፊያቸውን እንዲመልስልን ዱዓ እንናደርግ ።
አላህ ሙሉ አፊያቸውን ይመልስልን

15/10/2025

የማይችል ነገር ይኖራል ብዬ አላስብም።

15/10/2025

I gained 10,589 followers, created 22 posts and received 104 reactions in the past 90 days! Thank you all for your continued support. I could not have done it without you. 🙏🤗🎉

07/10/2025

I gained 10,589 followers, created 18 posts and received 101 reactions in the past 90 days! Thank you all for your continued support. I could not have done it without you. 🙏🤗🎉

ከኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የተሰጠ ወቅታዊ መግለጫ💢💢💢💢💢💢💢💢💢💢💢💢💢💢💢በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ ዞን መካነ ሰላም ከተማ መስከረም 23፣2018 ዓ.ል በመስጂድ ኑር በኢሻ...
04/10/2025

ከኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የተሰጠ ወቅታዊ መግለጫ
💢💢💢💢💢💢💢💢💢💢💢💢💢💢💢

በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ ዞን መካነ ሰላም ከተማ መስከረም 23፣2018 ዓ.ል በመስጂድ ኑር በኢሻ ሰላት ወቅት ወደ መስጂድ የታጠቁ ኃይሎች በመግባት ሃይማኖታዊ ግዴታቸውን በመወጣት ላይ በነበሩ ፦
1 የመስጂድ ዋና ኢማምና የወረዳው መጅሊስ ም/ሰብሳቢ
2 የመስጂድ አመራሮች
3 የመስጂድ ኻዲሞችን አሰቃቂ እና አረመኔያዊ በሆነ ሁኔታ መግደላቸውን የክልሉ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት አረጋግጦልናል።

እነሱም ሸሂድ ሆነዋል አላህ ጀነተል ፍርዶስ ይወፍቃቸው ።

ጠቅላይ ምክርቤቱ የእምነት ተቋማት የተከበሩ ቦታዎች በመሆናቸው ሊጠበቁ እንጅ እንዲህ አይነት አፀያፊ ተግባር የሚፈፀምባቸው መሆን የለባቸውምና ድርጊቱን በፅኑ ያወግዛል።

መላው የሃይማኖት ተቋማትም በእምነት ቦታዎች የሚደረጉ ትንኮሳዎች እና በእምነት ተከታዮች ላይ የተቃጣ መሰል የጅምላ ግድያ
ሊያወግዙና ሊያስቆሙ ይገባል።

ህዝበ ሙስሊሙ ይህንን በሀይማኖት ተቋማት ላይ የተቃጣ አደጋ ለመከላከል መረጃ በመለዋወጥ የሃይማኖት ተቋማትንና አካባቢውን እንዲጠብቅ ጠቅላይ ምክርቤቱ ጥሪውን ያስተላልፋል።

ብዝሃ ሀይማኖት ባለባት ሀገራችን በተለያየ እምነት ውስጥ ያሉ ህዝቦች ለዘመናት ያቆዩተን ሰላማዊ እና መልካም መስተጋብር ሆን ተብሎ ለመናድና ማባሪያ ያጣ ቀውስ ውስጥ እንድንገባ የሚፈልጉ አካላት የፈፀሙት መሆኑን ጠቅላይ ምክርቤቱ ይገነዘባል።

በመጨረሻም ሁሉም ሃይማኖት ተቋማትና መሪዎች ይህ ጉዳይ አብሮ የመኖር እሴት እንዳይሸረሽር ብሎም እንዳያጠፋ ድርጊቱን እንድታወግዙ እንዲሁም በፅኑ እንድትቃወሙ እየጠየቅን መንግስትም ይህንን ተግባር በእምነት ቦታዎችና አባቶች ላይ የፈፀሙት ላይ ህጋዊ እርምጃ እንዲወስድ እንጠይቃለን።

መስከረም 24፣2018 ዓ.ል
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክርቤት

ኢናሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂኡን!*********************መሪር ሃዘን። ስፍራን እየቀያየረ ተደጋግሞ የተገለጸ የጥላቻና ጭካኔ ጥግ። የዛሬዋ ባለተረኛ ወሎ መካነ ሰላም ከተማ ሆናለች። ...
04/10/2025

ኢናሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂኡን!
*********************

መሪር ሃዘን። ስፍራን እየቀያየረ ተደጋግሞ የተገለጸ የጥላቻና ጭካኔ ጥግ። የዛሬዋ ባለተረኛ ወሎ መካነ ሰላም ከተማ ሆናለች። ዘላቂ መፍትሄ ይሻል። በግልጽ የሚታየው ክስተቱ ላይ ብቻ ማተኮር ዘላቂ መፍትሄ አያመጣም።

ወገን ድርጊቱ ልብ ሰባሪ ቢሆንም ከስሜት በላይ ሆኖ መሰል ጥቃቶችን በዘላቂነት እንዴት ማቆም ይቻላል? የሚለው ላይ ማተኮር ይበጃል።

የበፊቶቹን ጥቃቶች አድራሾች የአንዳቸውንም እንኳ ጠንሳሶችንና ፈጻሚዎችን ለይቶ ማውጣት እንዴት ሳይቻል ቀሩ?

ከየትኛውም ወገን እንዴት በጥቃቶቹ ላይ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ሚና የነበራቸውም ወይም ንጹሓንን የመጠበቅ ኋላፊነት ያለባቸው አካላት ተጠያቂ ሳይሆኑ ተዳፍኑ?

ሌላው ቢቀር የአከባቢው አጀንዳዎች አጀንዳችን ናቸው ከሚሉት ሚዲያዎች፣አክቲቪስቶችና የፖለቲካ ሰዎች መካከል
ከክስተቶቹም ሆነ ከአዝማሚያዎቻቸው በመነሳት በጊዜውም ሆነ ከክስተቶቹ በኋላ የምርመራ ጋዜጠኝነትን በመከተል ዝርዝር እውነትን ማውጣት የሚችል ሚዲያም ሆነ አክቲቪስት እንዴት ሊገኝ አልቻለም? ሌላም ሌላም።

ከስሜት በላይ ሆኖ ዘላቂ መፍትሄ ማሰብ እስካልተቻለ በቀር በተመሳሳይ መንገድ እያሰብንና እየተጓዝን፣ እነርሱም እያሰቡና እየተጓዙ የተለየ መፍትሄ እንዴት ሊገኝ ይችላል?

_________________________

በመካነ ሰላም ከተማ የኑር መስጅድ ኢማምን ጨምሮ አራት ሙስሊሞች መገደላቸው ተገለፀ!

በደቡብ ወሎ ዞን ቦረና ወረዳ መካነሰላም ከተማ ቀበሌ 2 የሚገኘው የከተማዋ ቀደምት የሆነው መስጅድ ኑር(ሐጅ ነስሩ መስጅድ) መስጂድ ኢማም የሆኑትን ሼይኽ ጀማል ከማል፣ የመስጁዱ ጥበቃ ሸይኽ ይማምን ጨምሮ እስካሁን አራት ምዕመናን በታጣቂዎች መገደላቸውን ነው ከስፍራው የደረሰን መረጃ የሚያመለክተው።

ከስፍራው በደረሰን መረጃ መሰረት ከተገደሉት ምዕመናን በተጨማሪ የቆሰሉ ሰዎች መኖራቸው ተገልጿል። በዛሬው ዕለት ከኢሻ ሰላት በኋላ በመስጅዱ ዘልቀው የገቡ የታጠቁ ሀይሎች በፈጠሩት ተኩስ ነው ምዕምናኖቹ መገደላቸው የተገለጸው።

ታጣቂ ሀይሎቹ ወደ መስጅድ ሲገቡ አዛን ሲያሰሙ የነበሩትን የመስጅዱን ኢማም ሸይኽ ጀማል ከማልን አዛናቸውን ሳይጨርሱ በተኩስ እሩምታ እንደገደሏቸው ነው የተገለፀው።
@

በመካነ ሰላም ከተማ የኑር መስጅድ ኢማምን ጨምሮ አራት ሙስሊሞች መገደላቸው ተገለፀ!

- ሀሩን ሚዲያ፥ መስከረም 23/2018

በደቡብ ወሎ ዞን ቦረና ወረዳ መካነሰላም ከተማ ቀበሌ 2 የሚገኘው የከተማዋ ቀደምት የሆነው መስጅድ ኑር(ሐጅ ነስሩ መስጅድ) መስጂድ ኢማም የሆኑትን ሼይኽ ጀማል ከማል፣ የመስጁዱ ጥበቃ ሸይኽ ይማምን ጨምሮ እስካሁን አራት ምዕመናን በታጣቂዎች መገደላቸውን ነው ከስፍራው የደረሰን መረጃ የሚያመለክተው።

ከስፍራው በደረሰን መረጃ መሰረት ከተገደሉት ምዕመናን በተጨማሪ የቆሰሉ ሰዎች መኖራቸው ተገልጿል። በዛሬው ዕለት ከኢሻ ሰላት በኋላ በመስጅዱ ዘልቀው የገቡ የታጠቁ ሀይሎች በፈጠሩት ተኩስ ነው ምዕምናኖቹ መገደላቸው የተገለጸው።

ታጣቂ ሀይሎቹ ወደ መስጅድ ሲገቡ አዛን ሲያሰሙ የነበሩትን የመስጅዱን ኢማም ሸይኽ ጀማል ከማልን አዛናቸውን ሳይጨርሱ በተኩስ እሩምታ እንደገደሏቸው ነው የተገለፀው።

© ሀሩን ሚዲያ

03/10/2025

#ኢና ሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂዑን...
በመካነሰላም ኑር መስጂድ ፀረ ሙስሊም የሆነው ፅንፈኛው ታጣቂ ቡድን መስጂድ በመግባት ሙስሊሞችን ጨፍጭፏል።

ኢትዮጵያ ከኤርትራ የሃገርነት እዉቅና ልታነሳ ነዉ ‼️ *********************የአለማቀፍ ህጉ የሻዕቢያ መንግስት አሁን እያራመደ የሚገኘውን ከአለማቀፍ የሉዐላዊነት ፍላጎቶች ጋር የ...
03/10/2025

ኢትዮጵያ ከኤርትራ የሃገርነት እዉቅና ልታነሳ ነዉ ‼️
*********************
የአለማቀፍ ህጉ የሻዕቢያ መንግስት አሁን እያራመደ የሚገኘውን ከአለማቀፍ የሉዐላዊነት ፍላጎቶች ጋር የማይጣጣም አቋም እና ያለበት አጠቃላይ ግዛታዊ ውድቀትን ተከትሎ ኢትዮጵያ ‚ Mother State’s Permission ‛ በሚለው አለማቀፍ ህግ መሰረት በፈረንጆች በ 1993 ለኤርትራ መገንጠል የሰጠችውን እውቅና እንደገና እንድትመረምር የሚፈቅድ መሆኑና ህጉ ኢትዮጵያ ውሳኔዋን መሻር ከፈለገች እውቅናውን በዘላቂነት ማስቀጠል ይገባሻል በሚል ኢትዮጵያን የማያስገድድ ጭምርም እንደሆነ እየተነገረ ይገኛል ።
ኤርትራ አሰብን በሰላማዊ መንገድ የማትሰጥ ከሆነ የሃገርነት እዉቅና ተነጥቃ የኢትዮጵያ ግዛት መሆኗ የማይቀር ነዉ

02/10/2025

አለም ከገባችበት ቅርቃር ልትወጣ የምትችለው ፍትሃዊነትን ስታረጋግጥ ብቻ ነው።

06/06/2025

‎ሰበር ! በአዲስ አበባ ጣልያን ትምህርት ቤት ለኢድ ቀን አልዘጋም ማለቱ ተማሪዎች እና ወላጆች በአስቸኳይ እንዲስተካከል ጠየቁ !

‎ትምህርት ቢሮ እንዲሁም መጅሊስ ጨምሮ የሚመለከተው አካል ተቋሙን በማናገር የተደረገዉ ዉሳኔ እንዲስተካከል እንዲያደርጉ እንጠይቃለን ። "ተጨማሪ እና የተማሪ ወላጆች

‎በአዲስ አበባ ሰሜን ሆቴል አካባቢ የሚገኘዉ ጣልያን ትምህርት ቤት ለሙስሊሞች የኢድ አል አደሀ ቀን አልዘጋም ማለቱ ሙስሊም ተማሪዎች እና ወላጆች በአስቸኳይ እንዲስተካከል ጠይቀዋል ።

‎ተማሪዎች ለሚዛን እንደገለፁት ተማሪዎች ዛሬ ወደ ትምህርት ቤቱ ተጠርተዉ አርብ የኢዱ እለት ትምህርት ስለሚኖር እንድትገቡ የሚል ትእዛዝ እንደተሰጣቸዉ ገልፀዋል ።ተማሪዎቹ ከዚህ ቀደም ለበአል ትምህርት ተምረን አናዉቅም ለሙስሊሙም ለሌላ አማኞችም ሲሆን ያሉ ሲሆን ይህ አዲስ እና ግራ እንዳጋባቸዉ ገልፀዉልናል ።

‎ የተማሪ ወላጆች በበኩላቸው በጉዳዩ ዙሪያ ለመነጋገር ከዳይሬክተሯ ጋር ተገናኝቶ የነበረ እንደሆነ ገልፀዉ ቅዳሜ ዝግጅት ስላለብን ተማሪዎች የግድ መግባት አለባቸዉ ከፈለጉ ሙስሊምች አለመግባት ይችላሉ የሚል ምላሽ እንደሰጠቻቸዉ ለሚዛን ገልፀዋል ።

‎ወላጆች ኢደል አደሀ ከሙስሊሞች ዋናዉ በአል ልጆቻችን ትምህርት ቤት አንልክም ያሉ ሲሆን እንዲህ አይነት ከፋፋይ አና በካሌንደር የፀደቀ ብሄራዊ በአል አላከብርም ማለት የሀገሪቱን ህግ አላከብርም ማለት ስለሆነ የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ወይም መጅሊስን ጨምሮ የሚመለከተዉ አካል ትምህርት ቤቱ ንቀቱን አቁሞ እንደ ሀገራችን ተቋማት ሁሉ በኢድ እለት ሊዘጋ ይገባል በማለት ገልፀዋል ።

‎ልጆቻችን በኢድ ቀን ትገባላችሁ ካልሆነ ቅሩ በመባላቸዉ ተረብሸዉ ይገኛሉ አፋጣኝ ምላሽ እንፈልጋለን ብለዋል ።

‎ሚዛን ሚዲያ ከትምህርት ቤቱ መረጃ ለማግኘት ዳይሬክተሯን ለማግኘት ያደረግነዉ ጥረት አልተሳካም ።

ምንጭ ሚዛን ሚዲያ Mizan Media ሚዛን ሚዲያ Mizan Media

Address

Kara Korie
Addis Ababa
ADDISABEBA

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Afela አፍላ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Afela አፍላ:

Share