26/02/2026
አጂብ ነው መቸስ ! አላህን በቀጥታ ማውራት የቻለው ታላቁ ነብይ ሙሳ (ዐ.ሰ) እና ከእኛ የሆነን እውቀት ሰጠነው በማለት አላህ ያከበራቸው ሰይድና ኸድር (ዐ.ሰ) እንደው ለአንድ ጊዜ እንኳን ምግብ ስጡን ብለው ጠይቀው የሚሰጣቸው አጡ ቢባል ማን ያምናል !
ይመጣሉ ብቻ ተብሎ ቢነገር ለክብራቸው የአንድ ሀገር ህዝብ ወጥቶ ቢቀበላቸው የሚያንሳቸው የአላህ ምርጥ ሰዎች ለአንዴ ብቻ ምናርፍበት ቤታችሁ አስገቡን ብለው ሲጠይቁ እንቢ ከመባላቸው በላይ ምን ይገርማል !?
በቃ ዱኒያ እንዲህ ነች ክብራችሁን ደረጃችሁን ያልተረዱ ሰዎች ምንም ያህል ንቀት ቢያሳዩዋችሁ ልታዝኑ አይገባም ። ደረጃችሁን ሳይረዱ የሰደቡዋችሁ ሰዎች ልክ ሙሳ እና ኸድርን እደናቁዋቸው ሰዎች ናቸው ።
አላህ ብቻ ማን እደሆናችሁ ካወቀ ይበቃል።
وَذَكِّرْ فَإِنَّ الذِّكْرَىٰ تَنفَعُ الْمُؤْمِنِينَ