Ethio-Mereja

Ethio-Mereja Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Ethio-Mereja, Media/News Company, Addis Ababa.

ጥር 1 ቀን 2013ላለፉት 45 አመታት የህወሀት መራሽ እኩይ ሴራ ፊታውራሪ የነበረውን የከሃዲያን አለቃ ስብሃት ነጋን ጨምሮ ዘጠኝ የአፍራሽ ቡድኑ አመራሮች ዛሬ በህግ ወደሚዳኙበት ስፍራ ደር...
09/01/2021

ጥር 1 ቀን 2013

ላለፉት 45 አመታት የህወሀት መራሽ እኩይ ሴራ ፊታውራሪ የነበረውን የከሃዲያን አለቃ ስብሃት ነጋን ጨምሮ ዘጠኝ የአፍራሽ ቡድኑ አመራሮች ዛሬ በህግ ወደሚዳኙበት ስፍራ ደርሰዋል ።

የጥፋት ተልዕኮ ቡድኑ መሪና ስምሪት ሠጪው አቶ ስብሃት ነጋ /አቦይ ስብሐት/ ሠው ሊደርስበት በማይችልበት የተከዜ በረሃ የዝንጀሮ ገደል በሚባል ቦታ ተሸክመው ቢደብቁትም ፣ ጀግናው ሠራዊታችን ከተደበቀበት በረሃ በቁጥጥር ስር አውሎ ተሸክሞ ማውጣቱ ይታወሳል ።

ብ/ጀነራል ተስፋዬ በመግለጫቸው እንዳሣወቁት ዛሬ ሠራዊታችን ባደረገው ኦፕሬሽን አቦይ ስብሃትን ጨምሮ ሌ/ኮ አፀዱ ሪች ፣ ኮ/ል ክንፈ ታደሠ ፣ኮ/ል የማነ ካሕሳይ ፣ አቶ አስገደ ገ/ክርስቶስ ፣ አቶ አምደማርያም ተሠማ ፣ ኮማንደር በረሄ ግርማ በቁጥጥር ስር መዋላቸውንና የሜ/ጀነራል ሀየሎም አርአያ ባለቤት የነበረችው ወ/ሮ አልጋነሽ መለስ ከገደል ላይ ወድቃ መሞቷ መረጋገጡን ትናንት መዘገባችን ይታወሳል ።

መለክ በቃሉ ( ከግዳጅ ቀጣና )
ፎቶግራፍ መለክ በቃሉ

 ❗️⚡️የመከላከያ ሰራዊት ኃይል ስምሪት መምሪያ ኃላፊ ብርጋዴል ጀነራል ተስፋዬ አያሌው ለኢዜአ እንደገለፁት፣ የህወሐት አመራር ስብሃት ነጋ ከተደበቀበት ለሰው ልጅ እጅግ አስቸጋሪ የሆነ ሰር...
08/01/2021

❗️

⚡️የመከላከያ ሰራዊት ኃይል ስምሪት መምሪያ ኃላፊ ብርጋዴል ጀነራል ተስፋዬ አያሌው ለኢዜአ እንደገለፁት፣ የህወሐት አመራር ስብሃት ነጋ ከተደበቀበት ለሰው ልጅ እጅግ አስቸጋሪ የሆነ ሰርጥ ውስጥ በቁጥጥር ስር ውሏል።

በተጨማሪም በቁጥጥር ስር የዋሉ፣

1. የህወሐት አመራርና ስትራቴጂስት፣ ስብሃት ነጋ

2. ሌተናል ኮሎኔል ፀአዱ ሪች- የስብሃት ነጋ ባለቤትና ቀደም ሲል በጦር ሃይሎች ሆስፒተል ሃኪም የነበረች፣ በኋላም በጡረታ የተገለለች

3. ኮሎኔል ክንፈ ታደሰ- ከመከላከያ የከዳ

4. ኮሎኔል የማነ ካህሳይ- ከመለካከያ የከዳ

5. አስገደ ገ/ ክርስቶስ- ከመሃል ሀገር ተጉዞ ቡድኑን የተቀላቀለና ለጊዜው ሃላፊነቱ ያልታወቀ ግለሰብ በቁጥጥር ስር የዋሉ ሲሆን

6. የሜጀር ጀነራል ሃየሎም አርአያ ባለቤት የነበረችና ኑሮዋን በአሜሪካ አድርጋ የቆየች በኋላም ወደ አዲስ አበባ በመምጣት ወደ ህወሐት ተቀላቅላ የነበረች፣ ወይዘሮ አልጋነሽ መለስ ህወሕርትን በመያዝ ኦፕሬሽን ሂደት ውስጥ ለማምለጥ ስትሞክር ገደል በመግባት ህይወቷ ማለፉን ብርጋዴል ጀነራል ተስፋዬ አያሌው ገልፀዋል።

ህወሀት  ጀት አልጣለችም ለምትሉ  ይሄው 😎
09/11/2020

ህወሀት ጀት አልጣለችም ለምትሉ ይሄው 😎

ከጠቅላይ ሚኒስቴር ፅ/ቤት የተሰጠ መግለጫ ኢትዮጵያ በፍጣሪዋ ታምና በሕዝቧ አንድነትና ጽናት የቆመች ሀገር ናት ጥቂት ሰጥተው ብዙ ሊያዟት በሚሞክሩ ተማምና አታውቅም። ሕይወታቸውን ሰጥተው ሊ...
24/10/2020

ከጠቅላይ ሚኒስቴር ፅ/ቤት የተሰጠ መግለጫ

ኢትዮጵያ በፍጣሪዋ ታምና በሕዝቧ አንድነትና ጽናት የቆመች ሀገር ናት ጥቂት ሰጥተው ብዙ ሊያዟት በሚሞክሩ ተማምና አታውቅም። ሕይወታቸውን ሰጥተው ሊታዘዟት በተዘጋጁ ልጆቿ እንጂ። ኢትዮጵያን የፈጠራት አምላኳ ነው። የገነቧት ደግሞ ልጆቿ ናቸው። እነዚህ ልጆቿ በከፈሉት መሥዋዕትነት ዓለምን ጉድ ያሰኙ ታሪኮችን ሠርታለች። እነዚህን አስደናቂ ታሪኮችን ስትሠራ አብረዋት ታሪክ የሠሩ ወዳጆች ነበሯት። የከዷት ወዳጆችም ነበሩ። ይህ ለኢትዮጵያ አዲስ አይደለም።

ነገር ግን የዓለም ታሪክ ያረጋገጣቸው ሁለት ሐቆች አሉ። ኢትዮጵያን ነክቶ በሰላም የኖረ የለም የሚለው ቀዳሚው ነው። ኢትዮጵያውያን በአንድነት ለአንድ ዓላማ ከቆሙ ድል ማድረጋቸው አይቀርም የሚለው ደግሞ ሁለተኛው። የሕዳሴው ግድብ የኢትዮጵያ ግድብ ነው። ኢትዮጵያውያን፣ አሰቡት፤ ኢትዮጵያውያን ጀመሩት፤ ኢትዮጵያውያን ገነቡት፤ ስለዚህ ኢትዮጵያውያን ይጨርሱታል። አይቀሬ ነው።

የሚያዋጣን ኅብረት አንድነታችን ነው። ለእኛ ያለነው እኛ መሆናችንን ዐውቀን ስለ እኛ ጉዳይ እኛው ራሳችን ኢትዮጵያን አለንሽ እንበላት። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን ለኢትዮጵያ እንቁም። ከባዱ ፈተና ከውጭ የሚመጣው አይደለም። ከባዱ ፈተና ተለያይተን ችግሩን ከተጋፈጥነው ነው።

ማንም ገዝቶን አያውቅም። ወደፊትም ማንም አይገዛንም። ታሪክ የሠሩ እጆች ዛሬም አሉ። ኢትዮጵያና ኢትዮጵያውያን ወዳጆቻቸውን ለማክበር እንጂ ጠላቶቻቸውን ለመታዘዝ ተንበርክከው አያውቁም። ዛሬም ወደፊትም አናደርገውም።

ክንዳችንን እናበርታ። ትከሻችንን እናስፋ። ልባችንንም እናጽና። ከውጭና ከውስጥ የተሠነዘረብንን ጥቃት ድል አድርገን መሻገር ብርቃችን እንዳልሆነ እናስመስክር።

በምንምና በማንም ካሰብነው መንገድ እንቀርም። ያቀድነውን ከማሳካት የሚያግደን ምድራዊ ኃይል የለም። አንድ ሆነን የምንይዘው ጋሻ ኃያላኑን ሁሉ ሲመክት የኖረ ነው። ዛሬም ያንን ጋሻ በአንድነት እናንሣ። ሁላችንም፣ በየቦታችን፣ 24 ሰዓት፣ ለኢትዮጵያ እንቁም።

የእንጦጦ ፓርክ በይፋ ተመረቀ፡፡ፓርኩን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ መርቀው ከፍተውታል፡፡ጠቅላይ ሚኒስትሩ በምርቃት ስነ ስርአቱ ላይ በፓርኩ በተለያዩ የስራ መስኮች ለተሰማሩ ድርጅቶች ምስ...
10/10/2020

የእንጦጦ ፓርክ በይፋ ተመረቀ፡፡
ፓርኩን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ መርቀው ከፍተውታል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በምርቃት ስነ ስርአቱ ላይ በፓርኩ በተለያዩ የስራ መስኮች ለተሰማሩ ድርጅቶች ምስጋና አቅርበዋል፡፡
በፓርኩ የስራ እድል የተፈጠረላቸው ከ460 በላይ በአካባቢው የሚገኙ እናቶችም የስራ መስሪያ ቦታቸውን ቁልፍ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ተረክበዋል፡፡
(fbc)

10/10/2020

በነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ ክለሳ ተደረገ
****
ከጥቅምት 01 እስከ 30 ቀን 2013 ዓ.ም ባሉት ቀናት ውስጥ የነዳጅ ምርቶች ችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ ክለሳ መደረጉን የንግድ እና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አስታውቋል።
በዚህም መሠረት በአዲስ አበባ ከተማ የነዳጅ ምርቶች በሊትር ችርቻሮ መሸጫ ዋጋ እንደሚከተለው ሆኗል፡-
ቤንዚን 21 ብር ከ87 ሳንቲም
ኢታኖል ድብልቅ ቢንዚን 21 ብር ከ33 ሳንቲም
ነጭ ናፍጣ 19 ብር ከ09 ሳንቲም
ኬሮሲን 19 ብር ከ09 ሳንቲም
ቀላል ጥቁር ናፍጣ 16 ብር ከ94 ሳንቲም
ከባድ ጥቁር ናፍጣ 16 ብር ከ51 ሳንቲም
የአውሮፕላን ነዳጅ 24 ከ37 ሳንቲም ሆኗል።
የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ ዋጋ ክለሳው ከአዲስ አበባ በተጨማሪ በመላው አገሪቱ በሚገኙ አካባቢዎች እንደየርቀታቸው መጠን ከጥቅምት 01 ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚሆን ተገልጿል።

ጭራሹኑ ሱሰኛ አንበጣ ነዉ የመጣብን!!!
08/10/2020

ጭራሹኑ ሱሰኛ አንበጣ ነዉ የመጣብን!!!

በጆርጅ ፍሎይድ ግድያ የተጠረጠረው የፖሊስ መኮንን በ1 ሚሊዮን ዶላር ዋስ ከእስር ተለቀቀ።ባልታጠቀ ጥቁር አሜሪካዊ ጆርጅ ፍሎይድ ግድያ የተከሰሰው የቀድሞው የአሜሪካ ፖሊስ መኮንን በዋስ ተለ...
08/10/2020

በጆርጅ ፍሎይድ ግድያ የተጠረጠረው የፖሊስ መኮንን በ1 ሚሊዮን ዶላር ዋስ ከእስር ተለቀቀ።

ባልታጠቀ ጥቁር አሜሪካዊ ጆርጅ ፍሎይድ ግድያ የተከሰሰው የቀድሞው የአሜሪካ ፖሊስ መኮንን በዋስ ተለቋል ፡፡

ዴሪክ ቻውቪን የ1ሚሊዮን ዶላር ዋስ በማምጣት ነው ትላንት ጠዋት ከእስር እንደተለቀቀ የፍርድ ቤቱ መረጃዎች ያመለክታሉ ሲል ቢቢሲ ዘግቧል ፡፡

አትሌት ለተሰንበት ግደይ የ5000ሜ የአለም ክብረወሰንን ሰበረች! የ22 ዓመቷ ለተሰንበት ከደቂቃወች በፊት በስፔን ቫሌንሺያ ስታዲዮ ዴል ቱሪያ ባደረገችው የክብረወሰን ውድድር 14:06.65 ...
08/10/2020

አትሌት ለተሰንበት ግደይ የ5000ሜ የአለም ክብረወሰንን ሰበረች!

የ22 ዓመቷ ለተሰንበት ከደቂቃወች በፊት በስፔን ቫሌንሺያ ስታዲዮ ዴል ቱሪያ ባደረገችው የክብረወሰን ውድድር 14:06.65 በመግባት ከዚህ ቀደም በሀገሯ ልጅ አትሌት ጥሩነሽ ዲባባ በ14:11.15 ከ12 ዓመታት በፊት ተይዞ የነበረውን ክብረወሰን አሻሽላለች።

በህዳሴ ግድቡ አካባቢ ያለው የኢትዮጵያ የአየር ክልል ለበረራ ዝግ መደረጉ ተገለጸ!የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ዋና ዳይሬክተር ወሰንየለህ ሁነኛው (ኮሎኔል) ለሪፖርተር እንዳረጋገጡት፣ የታላቁ ...
04/10/2020

በህዳሴ ግድቡ አካባቢ ያለው የኢትዮጵያ የአየር ክልል ለበረራ ዝግ መደረጉ ተገለጸ!

የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ዋና ዳይሬክተር ወሰንየለህ ሁነኛው (ኮሎኔል) ለሪፖርተር እንዳረጋገጡት፣ የታላቁ ህዳሴ ግድብ በሚገነባበት ቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ውስጥ ያለው የኢትዮጵያ የአየር ክልል ከማንኛውም ዓይነት የበረራ እንቅስቃሴ ዝግ እንዲሆን፣ ከሚመለከታቸው የደኅንነት አካላት ጋር በመወያየት ክልከላ ተጥሎበታል።

በመሆኑም የንግድ ወይም የመንገደኞች ማጓጓዣ አውሮፕላኖችም ሆኑ ሌሎች ዓይነት የበረራ እንቅስቃሴዎች፣ ግድቡ በሚገኝበት አካባቢ መከናወን እንደማይችሉ ገልጸዋል።

ይህ ቢሆንም የሚመለከተው አካል በሚሰጠው ልዩ ፈቃድ ብቻ በተከለከለው የአየር ክልል በረራ እንዲደረግ ሊፈቀድ እንደሚችል አስረድተዋል። የአገርን ደኅንነት ለማረጋገጥ እንዲህ ዓይነት ክልከላዎችን መጣል በዓለም አቀፍ አሠራር የተለመደ መሆኑን የገለጹት ዋና ዳይሬክተሩ፣ ኢትዮጵያም የግድቡን ደኅንነት ለማረጋገጥ ሰትል ይህንን ክልከላ መጣሏን ገልጸዋል።

Reporter Newspaper

02/10/2020

ቀነኒሳ በቀለ ከለንደን ማራቶን ውጪ ሆኗል !!!

ፕሮፌሰር መስፍን ወልደ ማርያም አረፉየጂኦግራፊ ምሁሩ ፐሮፌሰር መስፍን ወልደ ማርያም በ90 ዓመታቸው ህይወታቸው አልፏል፡፡ፐሮፌሰር መስፍን በኢትዮጵያ ፖለቲካ እና ታሪክ ዙሪያ በርካታ መጽሐፍ...
30/09/2020

ፕሮፌሰር መስፍን ወልደ ማርያም አረፉ

የጂኦግራፊ ምሁሩ ፐሮፌሰር መስፍን ወልደ ማርያም በ90 ዓመታቸው ህይወታቸው አልፏል፡፡
ፐሮፌሰር መስፍን በኢትዮጵያ ፖለቲካ እና ታሪክ ዙሪያ በርካታ መጽሐፍትን የጻፉ እና በኢትዮጵያ ፖለቲካ ከፍተኛ ተሳትፎ የነበራቸው ምሁር ናቸው፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በፕሮፌሰሩ ህልፈተ ህይወት የተሰማቸውን ሀዘን በትዊተር ገጻቸው ገልጸዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ “የሐሳብ ልዕልና ምልክት፤ የሰላማዊ ትግል አርአያ፣ ላመኑበት ነገር እስከ መጨረሻቸው ሞጋች፣ ላመኑበት እውነት ብቻ የሚቆሙት ፕሮፌሰር መስፍን ወልደ ማርያም በማረፋቸው ጥልቅ ኀዘን ተሰምቶኛል” ያሉ ሲሆን ለቤተሰቦቻቸውም መጽናናትን ተመኝተዋል፡፡
(አል ዐይን)

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethio-Mereja posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share