Mosaic news

Mosaic news Read. Change.

የአዲስ አበባ ፖሊስ በሚሊዮን የሚቆጠር ብር ያዘ**********የአዲስ አበባ ፖሊስ ከብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ድርጅት ጋር በቅንጅት ባከናወነው ኦፕሬሽን በህገ ወጥ የገንዘብ ምንዛ...
18/08/2023

የአዲስ አበባ ፖሊስ በሚሊዮን የሚቆጠር ብር ያዘ
**********
የአዲስ አበባ ፖሊስ ከብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ድርጅት ጋር በቅንጅት ባከናወነው ኦፕሬሽን በህገ ወጥ የገንዘብ ምንዛሬ የተሳተፉ የንግድ ተቋማት ከበርካታ የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገር ገንዘቦች ጋር በቁጥጥር ስር ዋሉ

ከህብረተሰቡ በመጣ ጥቆማ በቦሌ ክ/ከተማ የተለያዩ አካባቢዎች በሚገኙ መጠጥ (ውስኪ) ቤቶች በተደረጉ ጥናቶችና ጥናቶቹን መሰረት ተደርገው በተከናወኑ የኦፕሬሽን ተግባራት በርካታ የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገር ገንዘቦች መያዛቸውን ፖሊስ አስታውቋል።

ውስኪ ቤቶቹ በህጋዊ የንግድ ሽፋን ስም በጥቁር ገበያ ( ህገ ወጥ) የገንዘብ ምንዛሬ ተግባር ላይ ተሰማርተው እንደነበርም መረጋገጡን የአዲስ አበባ ፖሊስ መረጃ ያሳያል፡፡

በአጠቃላይ በአስራ አንድ ቤቶች በተደረገው የጥናትና የኦፕሬሽን ስራዎች በአምስቱ ላይ የኢትዮጵያን ጨምሮ የአስራ አምስት ሀገራት ገንዘቦች ከነ ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ስር መዋላቸው ተገልጿል፡፡

ከተያዙት ገንዘቦችም ውስጥ 2 ሚሊዩን 916 ሺ 800 የኢትዮጵያ ብር፣ 54 ሺ181 የአሜሪካ ዶላር፣ 34 ሺ 50 ዩሮ፣ 305 የእንግሊዝ ፓውንድ፣ 7 ሺ 719 የሳውዲ ሪያል፣ 11ሺ440 ድርሀም፣ 52 ሺ የሊባኖስ ፓውንድ፣ 80 ሺ640 የሱዳን ፓውንድ እንዲሁም የተለያዩ ስድስት ሀገራት የገንዘብ ኖቶች ተይዘዋል፡፡

በህጋዊ የንግድ ስራ ሽፋን ተሰማርተው መሰል የወንጀል ተግባራት ውስጥ የሚገቡ የንግድ ተቋማት ላይ በጥናት ላይ የተመሰረተ የወንጀል መከላከል ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥል የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡

በሐሰተኛ ደረሰኝ ሲሸቅል የከረመው ግለሰብ ተያዘሐሰተኛ የሽያጭ ደረሰኝ አዘጋጅቶ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ በመሸጥ በከፍተኛ የማጭበረበር ወንጀል የተጠረጠረ ግለሰብ በቁጥጥር ሥር ዋለሐሰተኛ የ...
18/08/2023

በሐሰተኛ ደረሰኝ ሲሸቅል የከረመው ግለሰብ ተያዘ

ሐሰተኛ የሽያጭ ደረሰኝ አዘጋጅቶ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ በመሸጥ በከፍተኛ የማጭበረበር ወንጀል የተጠረጠረ ግለሰብ በቁጥጥር ሥር ዋለ

ሐሰተኛ የሽያጭ ደረሰኝ አዘጋጅቶ ለተለያዩ ነጋዴዎችና ድርጅቶች ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ በመሸጥ በከፍተኛ የማጭበረበር ወንጀል የተጠረጠረ ግለሰብ በአዲስ አበባ ከተማ በቁጥጥር ሥር ውሎ ምርመራ እየተጣራበት እንደሚገኝ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ አስታወቀ።

ተጠርጣሪው በቁጥጥር ሥር ሊውል የቻለው አድራሻው የማይታወቅ ሰለሞን ሙሉ ከውን በተባለ ግለሰብ ሐሰተኛ መታወቂያ በማዘጋጀት በዚሁ መታወቂያ የንግድ ፍቃድ በማውጣት የማሽነሪዎች እና የመሣሪያዎች ኪራይና ሽያጭ የንግድ ዘርፍ ላይ ተመዝግቦ ምንም ዓይነት የንግድ ልውውጥ ሳያደርግና የሸጠው እቃ ሳይኖር ሐሰተኛ የሽያጭ ደረሰኝ ለተለያዩ ነጋዴዎችና ድርጅቶች በ30 ቢሊዮን 152 ሚሊዮን 434 ሺህ 002 ብር ከ03 ሣንቲም በመሸጥ መሆኑ ታውቋል።

ግለሰቡ የማጭበርበር ወንጀሉን ከፈፀመ በኋላ ለበርካታ ጊዜያት ተደብቆ የነበረ ቢሆንም የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከአዲስ አበባ ከተማ ገቢዎች ጋር በመተባበር ባደረገው ጠንካራ ክትትል በቁጥጥር ሥር ማዋል መቻሉን
አስታውቋል ።

የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በተጠርጣሪው ላይ ምርመራ እያካሄደ መሆኑን ገልጾ ኅብረተሰቡም ወደ ኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ጠቅላይ መምሪያ ቢሮ በአካል ቀርቦ ተጨማሪ መረጃ በመስጠት የተለመደ ትብብሩን አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ ያቀርባል።

ከአስቸኳይ ጊዜ ጠቅላይ መምሪያ ዕዝ የተሰጠ ወቅታዊ መግለጫ*************************የአስቸኳይ ጊዜ ጠቅላይ መምሪያ ዕዝ ከተቋቋመ ጊዜ ጀምሮ ያከናወናቸውን የመጀመሪያ ምዕራፍ ተ...
09/08/2023

ከአስቸኳይ ጊዜ ጠቅላይ መምሪያ ዕዝ የተሰጠ ወቅታዊ መግለጫ
*************************

የአስቸኳይ ጊዜ ጠቅላይ መምሪያ ዕዝ ከተቋቋመ ጊዜ ጀምሮ ያከናወናቸውን የመጀመሪያ ምዕራፍ ተግባራት ገምግሟል፡፡ የዕዙ የመጀመሪያ ምዕራፍ ዕቅድ በባሕር ዳር፣ ደብረ ማርቆስ፣ በደብረ ብርሃን፣ በላሊበላ፣ በጎንደርና በሸዋ ሮቢት አካባቢ የተሰባሰበውን በዘረፋ እና በጥፋት የተሰማራ ቡድን በመምታትና ከተሞቹን ወደ ሰላማዊ ሁኔታ መመለስ ነበር። እነዚህ አካባቢዎች የተመረጡት ብዙ ሕዝብ የሚኖርባቸው፣ ከፍተኛ የንግድና የቱሪስት እንቅስቃሴ ያለባቸው፣ የፖለቲካና የኢንዱስትሪ ማዕከላት በመሆናቸው ነው።

በዚህ መሠረት በስድስቱ ከተሞች ዙሪያ የመጣው የጥፋት ቡድን መሣሪያውን እንዲያስረክብና እጁን እንዲሰጥ የተሰጠውን ዕድል ባለመጠቀሙ እርምጃ ተወስዶበታል፣ የሕግ የበላይነትም እንዲከበር ተደርጓል። የክልሉ ሕዝብ በዚህ ዘራፊ ቡድኑ የተማረረ በመሆኑ፣ የህግ አስካባሪ አካላት ተልዕኮዋቸውን በስኬት እንዲወጡ ተገቢውን ድጋፍ አድርጓል። ጠቅላይ መመሪያ እዙም የክልሉ ህዝብ ላደረገለት ትብብር ምስጋናውን ያቀርባል።

በአሁኑ ሰዓት ከተሞቹ ከዘረፊዉ መንጋ ስጋት ነጻ ሆነዋል። የመከላከያ ሠራዊቱ እና የክልሉ ህግ አስከባሪ አካላት በየሥርቻው የተራረፈውን ዘራፊ በማጽዳት ላይ ናቸው። ማኅበረሰቡም መረጃ በመስጠት፣ አቅሙ በፈቀደው ሁሉ ለዚህ ስራ ድጋፍ እያደረገ ይገኛል። ሽንፈት የተከናነበው የፅንፈኞች ቡድን በአንዳንድ አካባቢዎች ወደ ቅርስ ቦታዎችና የእምነት ተቋማት በመግባት ለመደበቅ እየሞከረ ነው። የመከላከያ ሠራዊቱ እና የክልሉ ህግ አስከባሪ አካላት ህግ፣ ሥርዓትና ሞራልን ባከበረ መንገድ ሃላፊነታቸውን እየተወጡ ይገኛል። በቀጣይም የመጨረሻውን የማጽዳት እና የመልቀም ተግባር በማከናወን ከተሞቹ በአጭር ጊዜ ወደ ተሟላ ሰላማዊ እንቅስቃሴ እንዲመለሱ ይደረጋል።

በአስቸኳይ ጊዜ ዐዋጁ በተሰጠው ሥልጣን መሠረት የጠቅላይ መምሪያ ዕዙ እስካሁን 14 ተጠርጣሪዎችን በአዲስ አበባ ከተማ በቁጥጥር ሥር ያዋለ ሲሆን ወደፊትም እንደሁኔታው በቁጥጥር ሥር የሚያውላቸውን ግለሰቦች አስመልክቶ አስፈላጊውን መረጃ ለህዝብ ይፋ ያደርጋል።

በመጀመሪያው ምዕራፍ ዕቅድ የተያዘው ከተሞቹን ከዘራፊ የጥፋት ቡድን የማጽዳቱ ተግባር እየተጠናቀቀ በመሆኑ፣
1. ከሐሙስ ነሐሴ 4 ጀምሮ ከላይ በተጠቀሱት ከተሞች መደበኛ የአውሮፕላን በረራ ይጀመራል፤
2. ከባጃጅና ከሞተር ሳይክል በስተቀር ሁሉም ዓይነት የከተማ የትራንስፖርት አገልግሎቶች ወደ አገልግሎት ይገባሉ፤
3. የመንግሥት፣ የማኅበረሰብ አገልግሎት፣ የንግድ፣ የጤና፣ የፋይናንስ፣ ወዘተ. ተቋማት አገልግሎት እንዲሰጡ ይደረጋል።

በዚሁ አጋጣሚ የክልሉ ሕዝብ ራሱን ከዘራፊውና ከጽንፈኛው መንጋ በመነጠልና በመከላከል፣ ከህግ አስከባሪ አካላት ጋር በመሰለፍ ላደረገው ተጋድሎ ዕዙ በድጋሚ ምስጋናውን ያቀርባል።

የአስቸኳይ ጊዜ ጠቅላይ መምሪያ ዕዝ ያስተላለፈው ትዕዛዝና ክልከላ ቁጥር 1
የሕዝብን ሠላምና ደህንነት ለማስጠበቅ የወጣ የሚኒስትሮች ምክር ቤት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ቁጥር 6 /2015 አንቀጽ 5 መሰረት የአስቸኳይ ጊዜ ጠቅላይ መምሪያ ዕዙ የሚከተሉትን ትዕዛዞችና ክልከላዎች ደንግጓል።
1) በባሕርዳር፣ ጎንደር፣ ደብረ ብርሃን፣ ደብረ ማርቆስ፣ ሸዋ ሮቢትና ላሊበላ የሕዝብ የአገልግሎት ሰጪ፣ የመንግሥት፣ የማኅበረሰብና የንግድ ተቋማት ከነሐሴ 4/2015 ጀምሮ ክፍት እንዲሆኑ ታዟል።
2) በባሕርዳር፣ ጎንደር፣ ደብረ ብርሃን፣ ደብረ ማርቆስ፣ ሸዋ ሮቢትና ላሊበላ እስከ ነሐሴ 17፣2015 የሚቆይ የሠዓት እላፊ ገደብ ተጥሏል፡፡ በዚህም መሰረት የድንገተኛ ህክምና አገልግሎት ከሚሰጡ ተሽከርካሪዎች፣ የድንገተኛ ህክምና አገልግሎት ሰጪ ባለሞያዎች እና የፀጥታ አስከባሪ ተቋማት ባልደረቦች ውጪ ለማንኛውም ሰው እና ተሽከርካሪ ከምሽቱ አንድ ሰዐት በኋላ መንቀሳቀስ በጥብቅ የተከለከለ ነው።
3) የአስቸኳይ ጊዜ ጠቅላይ መምሪያ ዕዙ ፈቃድ ውጪ በአማራ ብሔራዊ ክልል ከተሞች የአደባባይ ስብሰባ፣ ሰልፍ እና መሰል እንቅስቃሴዎችን ማድረግ ፈጽሞ የተከለከለ ነው። እንዲሁም በማንኛውም መልኩ የህዝብ እንቅስቃሴን የሚያስተጓጉል እና የትራንስፖርት አገልግሎትን የሚያሰናክል ድርጊት በጥብቅ የተከለከለ ነው።
4) በአማራ ብሔራዊ ክልል ውስጥ ለጸጥታ ሥራ ከሚንቀሳቀሱ የህግ አስከባሪ አካላት እና ከነዚህ አካላት ፈቃድ ውጭ የጦር መሣሪያ ይዞ መዘዋወር ፈጽሞ የተከለከለ ነው።
5) በአማራ ብሔራዊ ክልል ከላይ በተራ ቁጥር አንድ በተገለጹት ከተሞች የባጃጅ እና የሞተር ሳይክል እንቅስቃሴ ከነሐሴ 4 እስከ ነሐሴ 17፣2015 ድረስ ፈጽሞ የተከለከለ ነው።
6) ከባጃጆችና ከሞተር ሳይክሎች በስተቀር ሌሎች የከተማ ትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪዎች ከነሐሴ 4 ጀምሮ ወደ ሥራ የመመለስ እና አገልግሎት የመስጠት ግዴታ አለባቸው።
7) በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ሽፋን ከአስቸኳይ ጊዜ ጠቅላይ መምሪያ ዕዝ ትእዛዝ ውጭ ወቅታዊ ሁኔታን ሰበብ በማድረግ ግለሰቦችን ከመደበኛው ህግ አግባብ ውጪ ማሰር እና ማቆየት፣ የንግድ ቤቶችን ማሸግ እና መሰል እርምጃዎችን መውሰድ በጥብቅ የተከለከለ ነው።
ከላይ የተዘረዘሩትን ትዕዛዞችና ክልከላዎችን በሚጥሱ ላይ በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ አንቀጽ 7 መሰረት ሃይልን በመጠቀም፣ እንዲሁም ሌሎች አግባብነት ያላቸውን እርምጃዎችን በመውሰድ ትዕዛዝና ክልከላዎችን እንዲያስፈጽሙ ለሁሉም የህግ አስከባሪ አካላት ጥብቅ መመሪያ ተሰጥቷል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ባህር ዳር እና ጎንደር ከተሞች በጊዜያዊነት ተቋርጦ የነበረውን መደበኛ በረራ ነገ ነሐሴ 4 ቀን 2015 ዓ.ም. የሚጀምር መሆኑን እየገለጸ፣ ክቡራን መንገደኞቻች...
09/08/2023

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ባህር ዳር እና ጎንደር ከተሞች በጊዜያዊነት ተቋርጦ የነበረውን መደበኛ በረራ ነገ ነሐሴ 4 ቀን 2015 ዓ.ም. የሚጀምር መሆኑን እየገለጸ፣ ክቡራን መንገደኞቻችን በአቅራቢያችሁ በሚገኙት የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሽያጭ ቢሮዎች ወይም ወደጥሪ ማዕከላችን (6787/+251116179900) በመደወል መስተናገድ የምትችሉ መሆኑን በትህትና እናሳውቃለን፡፡

ለተጨማሪ መረጃ ድረ-ገጻችንን (www.ethiopianairlines.com) ይጎብኙ!
ነሐሴ 3 ቀን 2015 ዓ.ም.

#የኢትዮጵያአየርመንገድ

ከአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ (አብን) በወቅታዊ ጉዳዬች የተሰጠ መግለጫ፥              ---------__________-----------_______-------እንደሚታወቀው የአማራ ህዝብ በረ...
09/08/2023

ከአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ (አብን) በወቅታዊ ጉዳዬች የተሰጠ መግለጫ፥
---------__________-----------_______-------
እንደሚታወቀው የአማራ ህዝብ በረጂሙ የሀገራችን ታሪክ ውስጥ ከሁሉም የኢትዮጵያ ህዝቦች ጋር በአንድነት ውጣ-ውረዶችን ያሳለፈ፣ አስደናቂ የሆኑ የአርበኝነት ገድሎችን፣ ማሕበራዊ እና ቤተሰባዊ እሴቶችን የሚጋራ ሀገር ወዳድ ህዝብ ነው።

ሆኖም አላዋቂ እና ፅንፈኛ የሆኑ የግራ ዘመም ኃይሎች በአማራ ህዝብ ላይ ፍፁም የተዛባና መሰረተ-ቢስ የሆነ የሀሰት ትርክት በመፃፍ ለበርካታ ዓስርተ-አመታት የጥላቻ እና የጥቃት ሰለባ እንዲሆን አድርገውታል። በዚህ ምክንያት የአማራ ህዝብ ከፍተኛ ሰብዓዊ እና ቁሳዊ ውድመቶች ተፈፅመውበታል።

በተለይም አማራን መፈረጅና ማጥቃት መደበኛ የፖለቲካ ማደራጃ ያደረጉ ኃይሎች በታሪክ ክፍተት አልፈው ስልጣን ከያዙ በኋላ "አማራ-ጠልነትን" የሀገራዊ ስርዓት እና መዋቅር ማደራጃ አድርገውት ቆይተዋል። የአማራ ህዝብ ከመላው ኢትዮጵያዊያን ወገኖቹ ጋር በመተባበርና ከፍተኛ መስዋዕትነት ከፍሎ ባደረገው መራር ትግልም በወቅቱ የነበረውን ዘረኛ መንግስታዊ ስርዓት ከስልጣን ለማስወገድ መቻሉ የቅርብ ትዝታ ነው።

ነገር ግን ከዚህ ድል በኋላ ታይቶ የነበረው የአማራ ህዝብ ተስፋ ያደረገበትና በስፋት የደገፈው "የለውጥ ሂደት" ከፍትህና እኩልነት አንጻር እንደታሰበው ውጤታማ ሊሆን ሳይችል ቀርቶ ህዝባችን ዛሬም በበዛ ምስቅልቅል ውስጥ እያለፈ ይገኛል። በመንግስት በኩል ከፍተኛ የአመራር ችግር፣ የጠራ ሀገራዊ ራዕይ ዕጦትና በዚህ ምክንያት የተፈፀሙት ሰፊ ማንነት ተኮር ጭፍጨፋዎችና ማፈናቀሎች እንዲሁም ችግሮችን በወቅቱ እና ባግባቡ መፍታት አለመቻል በሰፊው የታየበት ወቅት ነው።

በሀገራችን የተለያዩ አካባቢወች ከተፈፀሙት ብሄር ተኮር ጥቃቶች በተጨማሪ በአማራ ክልል ውስጥ በጦርነቱ ወቅት ለተፈፀሙ ሰብዓዊ ጥቃቶችና ቁሳዊ ውድመቶች በድህረ-ጦርነት ወቅት ተገቢው ስነልቦናዊና ኢኮኖሚያዊ የመልሶ ማቋቋም ስራ አለመሰራቱ፣ የሰነበቱ ጥያቄዎች ዛሬም ድረስ በቂ ግልጽነት ያልተፈጠረባቸው በመሆኑ፣ አጠቃላይ ለህዝብ አጀንዳወች በቂ መድረክ ባለመፈጠሩ ምክንያት ህዝባችን ለጥርጣሬና ለብሶት እንዲጋለጥ ሆኗል። በተለይ በሰሜኑ ጦርነት ማግስት የተካሄዱ የሰላም ስምምነቶች የአፈጻጸም ግልጸኝነት የጎደላቸው በመሆናቸው ቀድሞ የነበሩ ችግሮችን ይበልጥ ማባባሱና ህዝቡንም ለከፍተኛ ጥርጣሬ በማጋለጥ የህዝቡ ተገቢ ጥያቄወች ለሴራ ትንተናና ለውዥንብር ጭምር ምቹ እንዲሆኑ አድርጓል።

የአማራ ክልል መንግስት በጦርነቱና በድህረ-ጦርነት ወቅት ያሳየው አጠቃላይ የአመራር ድክመት፣ የህዝብን ሰላም የሚያደፈርሱ በየሰፈሩ የሚስተዋሉ እንቅስቃሴዎችን ለማረም መድረክ ያለመፍጠር፣ ህግ ያለማስከበር፣ ህዝባችንን ለሰፊ ጥርጣሬ በመጣል የሴራ ትንተና ተጋላጭ እንዲሆን የሚቀነቀኑ አፍራሽ ጥሪወችና ህዝባችንን ከሌሎች ህዝቦች የሚነጥሉ ቅስቀሳወችን የሚያደርጉ ግለሰቦችና ሚዲያወች በህዝባችን ላይ የሚደፉት የየዕለት አጀንዳ ተገቢው ክትትልና የእርምት እርምጃ ስላልተደረገበት፣ ይህንን ለማድረግም ፍላጎት ባለማሳየት ህዝብን ለእረፍት የለሽ አለመረጋጋትና ለሰፊ ጥርጣሬ በመዳረግ፣ የክልሉ መንግስት የመሪነት ሚናውን መወጣት ባለመቻሉ ብሎም አንዳንድ ላልተገቡ እንቅስቃሴወች መስፋፋት የተመቸ ሁኔታን በመፍጠሩና ተባባሪ የመሆን አዝማሚያዎችን ጭምር ማሳየቱ ለችግሮች መፈጠር እና መባባስ ዋና ድርሻ እንዳለው ሊሰመርበት የሚገባ ሲሆን የፌዴራል መንግስቱም ለነዚህ ሁሉ ችግሮች መፈጠር አቻ ተጠያቂ ነው።
በተለይም ከላይ እስከታች ያለው የክልሉ አመራር ለህዝባችን ተገቢውን መንግስታዊ አመራር ከመስጠት ይልቅ የሰፈርና የጎጥ አጀንዳወች ላይ ተቸክሎ በሚያደርገው የመነጣጠቅና የመጠላለፍ ስምሪት ህዝባችንን ጨርሶ በመርሳት ጥያቄወቹ ምላሽ አጥተው ለከፍተኛ ምሬት እንዲወድቅ አድርጎታል።

የክልሉ መንግስት በሀገር አቀፍ ደረጃ የአማራን ህዝብ ጥያቄዎች በውይይትና በድርድር የማስፈፀም ቁርጠኝነትና ብቃት እንደሌለው እና በጭንቅ ወቅቶች ህዝቡን ከማረጋጋት ይልቅ ለመከራ ዳርጎ የሚሸሸና የሚሸሸግ መሆኑም በተደጋጋሚ ታይቷል፣ የአማራን ህዝብ አንድነት ከማጠናከርም ይልቅ ለጠባብ ግለሰባዊና የኋላቀር ፖለቲካ መገለጫ በሆኑ ቡድናዊ አጀንዳዎች የተወጠረ በመሆኑ ከህዝብ እንዲነጠልና ጨርሶ አመኔታ እንዲያጣ አድርጎታል።

የክልሉ አመራር ህዝቡን ለማወያየትም ይሁን ጥያቄዎቹን ለመስማትና ለመመለስ ፍቃደኛ ሳይሆን ቆይቷል። ስለሆነም የአማራ ህዝብ በየአካባቢው ለሚደርሱበት ዘር ተኮር ጥቃቶችና ላሉበት ውስብስብ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች መፍትሄ የሚሰጥ አካል መጥፋት፣ በጦርነት የደረሰበትን መጎሳቆልና ውድመት የሚያክም የተሟላ የመልሶ ማቋቋም መርሀግብር ያለመኖር ለተፈጠሩ ችግሮች ተጠቃሽ ምክንያትና አባባሽ ሆኗል ብለን እናምናለን።

ከሰሞኑ በአማራ ክልል ውስጥ የተከሰተው የሰላም መደፍረስ በአንድም ይሁን በሌላ መልኩ የማይጠበቅ ክስተት አልነበረም። ድርጅታችን የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ ይህንን አስቀድሞ በማየት መንግስት ከሚሰራቸው ተደጋጋሚና ተከታታይ ስህተቶች እንዲጠበቅና የመፍትሄ ጥረት እንዲያደር ስናሳስብ ስለመቆየታችን የቀደሙ መግለጫወቻችን ለዚሁ ምስክር ናቸው። ስለሆነም መፍትሄ ይፈልጉ የነበሩ ጥያቄወች አዳማጭ በማጣታቸው ግልጸኝነት ስላላገኙ፣ የክልሉ መንግስትና የገዥው ብልፅግና ደንታ ቢስነት ገደብ በማጣቱ የአማራ ህዝብ ለተለያዩ አጀንጃ ሰጭዎች ማለትም ህዝባችንን ከሌሎች ወንድም ህዝቦች ጋር የሚያቃቅሩ፣ ወጣቶቻችን ያልተገባ መሰዋዕትነት እንዲከፍሉ፣ ተቋማትንና የሀገር ሽማግሌዎችን፣ የእምነት አባቶችን የማክበር እሴት እንዳይኖረው በመቀስቀስ ለሚያወናብዱ አካላት መደላድል ፈጥሮላቸው ቆይቷል። የክልሉ መንግስት ብቃት ማነስና ወካይ አለመሆን ያስከተለው ምስቅልቅልም ነው። የአማራ ልሂቃን እና የፖለቲካ ሀይሎች እንዲሁም የተለያዩ የሲቪክ አደረጃጀቶች የራሳቸው ድክመት እንዳለ ሁሉ የክልሉ መንግስት እነዚህ አካላት በጋራ እንዳይመክሩና መፍትሄ እንዳያፈላልጉ በስልት መድረክ መነፈጋቸው ተደማሪ ችግር ሆኖ መቆየቱንም አብን ያምናል።

በተጓዳኝ በሰፊ ማእቀፍ ሊመከርባቸው የሚገቡ አንገብጋቢ የህዝብ ጉዳዬች ድንገት የተላለፉ ውሳኔዎች ያስከተሉት ውጤትም ነው። በዚህ ረገድ ሀገራችንና ህዝባችን ጥቃት በተፈጸመባቸው ወቅት የሕዝብ ደጀን በመሆን ከኢትዮጵያዊ ወገኖች ጋር በጋራ ቆመው የሀገር ህልውና በማስጠበቅ ታሪካዊ ሚና የተጫወቱትን የአማራ ልዩ ሀይል አባላት በድንገተኛ መንግስታዊ የውሳኔ እርምጃ ሰራዊቱን መልሶ ማዋቀር ባለመቻሉና ለውዥንብር ተጋልጦ እንዲበተን መሆኑ ከሰሞኑ ለተፈጠረው ችግር ተጨማሪ ምክንያትና አባባሽ ነው ብለንም እናምናለን።

በተመሳሳይ ለሀገር አንድነት፣ ለህዝብ ህልውና፣ ለክብርና ነፃነት የተዋደቁና ዋጋ የከፈሉ የፋኖ አባላቶች ድህረ ጦርነት ወደመደበኛ ህይወት የሚመለሱበት ግልጽና ፈጣን ሀገራዊም ሆነ ክልላዊ መርሀግብር ባለመዘጋጀቱ፣ ታጋዮቹንም ለማወያየትና መፍትሄ ለመፈለግ በቂ መድረክ ባለመፈጠሩ፣ ይልቁንም በችኩል መፈረጃቸው ብሎም የፋኖነት እሴት ከሌላቸውና በህልውና ትግሉ ወቅት ተሳትፎ ካላደረጉ አካላት ጋር አዳብሎ የፋኖን ትግልና አስተዋጽኦ ለማሳነስና በአሉታዊ መልኩ ለመበየን የተሄደበት መንገድና አያያዝ በብዙወች ዘንድ መከፋትን የፈጠረ መሆኑ ሊናቅ አይገባውም።

በተጨማሪም በሀገሪቱ ሰላም መደፍረስ በሁከትና በጥላቻ የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት የተሰማሩ ልዩልዩ አካላት እና በአማራ ህዝብ ስም እየማሉ ህዝባችን ጥያቄወቹን ብሎም ስርዓታዊ በደሉን በሰላማዊ መንገድ መታገሉን አቁሞ ይልቁንም ወደ እርስ በእርስ ግጭት እንዲገባ የሚቀሰቅሱ ኃይሎች ድርሻ ቀላል እንዳልሆነ አብን ያምናል።

ድርጅታችን የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ (አብን) በተደጋጋሚ ላቀረባቸው ጥሪዎች ስርዓቱ ጆሮ ባለመሰጠቱ እና የተሰነዘሩ የመፍትሄ ሀሳቦችንም ገቢራዊ ለማድረግ ባለመሞከሩ ችግሮች እየተጠራቀሙ መምጣታቸው ክልሉን ወደ ለየለት ቀውስ ከቶታል።

በጥቅሉ ከላይ የተገለጹት ተደራራቢ ተግዳሮቶች ተዳምረው ህዝቡን ለውስብስብ ችግር ከመዳረግ ባለፈ በተፈጠረው ቀውስ ምክንያት ህዝባችን በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አስተዳደር ስር እንዲወድቅ ሆኗል። ስለሆነም ድርጅታችን አብን እንደሚከተለው አቋሙን ያሳውቃል:-

1). የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ አተገባበር በከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲመራ፣ በአጭር ግዜ እንዲያልቅ፣ አዋጁን ለማስፈፀም የተሰማሩ አካላትም ከማንነት ተኮር ፍረጃዎች፣ ወከባዎች፣ ከዘፈቀደ እስራትና አካላዊ ጥቃቶችን ባለመፈጸም እንዲሁም በየትኛውም አካል እንዳይፈጸሙ ጥበቃ የማድረግ ግዴታቸውን በአግባቡ እንዲወጡ አጥብቀን ከመጠየቅ በተጨማሪ የፌደራሉ መንግስት አካላት ሚና ለህዝቡ የሚመጥን አስተዳደር እንዲዋቀር መደላድል በመፍጠር እንዲወሰን፣ ህዝባዊ የውይይት መድረኮችም እንዲፈጠሩ፣ ህዝቡም የሰላም ጥረቶችን እንዲደግፍ ጥሪ እናቀርባለን። ክልሉ ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አስተዳደር በአፋጣኝ እንዲወጣም አብን ይጠይቃል።

2). በአማራ ክልል ለተፈጠረው ቀውስ ልዩልዩ አዎንታዊና አሉታዊ ምክንያቶች ቢኖሩም በዋናነት የፌዴራሉና በተለይም የክልሉ መንግስት ሊሰሯቸው ሲገባ ያልሰሯቸው ስራወች ድምር ውጤት መሆኑ ታምኖ ኃላፊነትን በመውሰድ ችግሮቹን ለዘለቄታዊ ሰላም በውይይት ለመፍታት ትኩረት እንዲሰጥ ብሎም ዘላቂ ሰላም ሊያመጣ የሚችል መፍትሄ በህዝብ እጅ ያለ እና ከህዝብ የሚመነጭ በመሆኑ ሁሉንም ባለድርሻዎች ያካተቱ መድረኮች እየተዘጋጁ የህዝቡ የመደመጥ መብት እንዲከበር እንጠይቃለን።

3). በክልሉ የተከሰተው ችግር ዋነኛ ማጠንጠኛ የመንግስትታዊ ስርዓቱ እና የክልሉ የአመራር ክፍተትና ብልሽት በመሆኑ በቀጣይ ማህበረሰቡን የሚመጥን እና በማህበረሰቡ የሚታመንበት አደረጃጀት በየደረጃው ተመስርቶ የአማራ ህዝብ ጥያቄዎች ተቆጥረው ግልጸኝነት እና መተማመን እንዲፈጠርባቸውና ተቋማዊ በሆነ አግባብ ምላሽ እንዲያገኙ እንዲደረግ አበክረን እናሳስባለን።

4). በተቻኮለ የአደረጃጀት ለውጥ ምክንያት የተበተነውን ልዩ ሀይል እና በህልውና ትግሉ ውስጥ አስተዋጽኦ የነበራቸውን የፋኖ አባላት በተመለከተ የፌደራልና የአማራ ክልል መንግስት በአስቸኳይ የጋራ ኃላፊነት ወስደው በሀቀኛ ውይይቶች ላይ የተመሠረተ የሁለቱንም አካላት ክብርና አበርክቶ የሚመጥን መርሀ-ግብር በአስቸኳይ በመንደፍ ገቢራዊ ስራ እንዲሰሩ እንጠይቃለን።

5). በየትኛውም አሰላለፍ እና አግባብ ስለአማራ ህዝብ የተሰለፉ ሀይሎች ጦርነት ዘላቂ ጥቅምን ለማረጋገጥ አስቻይ ባለመሆኑና ይልቁንም ህዝብን ለተደራራቢ የማህበራዊ፣ ሰብአዊና ኢኮኖሚያዊ ድቀት ስለሚዳርግ ለሰላማዊ የፖለቲካ መፍትሄዎች ተገቢውን ስፍራ ሰጥተው ለክልሉ ሰላም መመለስ ታራካዊ ድርሻቸውን እንዲወጡ አብን አበክሮ ይጠይቃል።

6). መላው የአማራ ህዝብ ከሌላው የሀገሪቱ ህዝብ ጋር ያለውን የወንድማማችነት እሴቶች ከሚንዱ ቅስቀሳዎች፤ በራሱ እና በልጅቹ የተመሰረቱ ተቋማትን በተለይም የሀገር መከላከያ ሰራዊት ከሚያጠለሹ መልዕክቶች እንዲሁም የአማራ ህዝብ ማህበራዊ ረፍት እንዲያጣ ከሚመኙ አካላት በስልት የሚሰጡትን አጀንዳዎች በመጸየፍ ወደ ሰላም መድረክ የሚያመሩ መንገዶችን ሁሉ ለመጥረግ አቅሙ የፈቀደውን ርብርብ እንዲያደርግ በአደራ ጭምር እናሳስባለን።

7). መላው የኢትዮጵያ ህዝብ የአማራ ህዝብ ጥያቄዎች የሀሰት ትርክት እና መዋቅራዊ ስርዓት የወለዳቸው፣ ከለውጡ ማግስትም ወዲህ ቢሆን ምላሽ ያላገኙ ብሎም በጦርነት የተቀጠቀጠና ክልሉ አቅሙ ከሚችለው በላይ በተፈናቃይ ወገኖች የጎበጠበት፣ እንዲሁም ተፈናቃይ የታጨቀበት የሀገሪቱ ክፍል መሆኑን በማስታወስና የህዝባችንን ብሶት በተገቢው በመረዳት ህዝባችን ሲያነሳቸው ለቆዩ የከረሙ የፍትህና የእኩልነት ጥያቄወች አጋር ሆናችሁ እንድትቆሙ እንጠይቃለን።

8). ለሰብአዊ መብት ድርጅቶች
ከጦርነት ቅጥቀጣው ባላገገመው በአማራ ክልል ውስጥ የተከሰተው ግጭት እና የታወጀውን የአስቸኳይ ግዜ አዋጅ አስተዳደር ተከትሎ የሚፈጠሩ ሰብአዊ ችግሮችን ለመከታተልና ልዩ ልዩ የህይወት አድን ድጋፎችን ታደርጉ ዘንድ ጥሪ እናቀርባለን።

9). ከወቅታዊ ጉዳይ ጋር በተያያዘ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች በተለይም በአዲስ አበባና በአማራ ክልል ለእስር የተዳረጉ ሰወች ጉዳያቸው በአስቸኳይ ወደ ህግ ቀርቦ እንዲጣራና ተገቢው መፍትሄ እንዲሰጣቸው ስንል እናሳስባለን።

10). መንግስት ለድርድር እና ንግግር ጥሪ እንዲያደርግ

12). ታውቀው ያደሩ የአማራ ሕዝብ ጥያቄዎች ምላሽ እንደሚያገኙ በአደባባይ ዋሰትና እንዲሰጥ

13). አሁን በክልሉ ለተፈጠረው አጠቃላይ የጸጥታ መደፍረስ፣ ለደረሰው ሰብአዊና ቁሳዊ ኪሳራ መንግስት ኃላፊነት እንዲወስድ እና ህዝቡን ይቅርታ እንዲጠይቅ ጥሪ እናቀርባለን።

14). ግጭትና የሰላም እጦት ተወግዶ ዘላቂ ሰላምና ልማት ለሀገራችን ህዝቦች እውን እንዲሆን ሁላችንም ለዚሁ እንድንቆም እያሳሰብን መንግስት ለውይይት ክፍት እንዲሆንና የሰላም ጥረቶችን ሁሉ አሟጦ እንዲጠቀም እናሳስባለን።

15). የወልቃይትና የራያ ጉዳይ ግልጽ መፍትሄ አለማግኘቱ፣ ፍትሃዊ የመሰረተ ልማት ስርጭት ጥያቄ፣ ፍትሃዊ የበጀት ክፍፍል ጥያቄ ፣ የአርሶአደሩ የማዳበሪያ ጥያቄ፣ ገበሬው ያመረተውንም ወደገበያ እንዳይወስድ ተደጋጋሚ የመንገድ መዘጋትና መስተጓጎል ወዘተ ጉዳዮች በቂ መንግስታዊ ትኩረት ሳያገኙ መቆየታቸው ህዝባችንን ለከፍተኛ ምሬት ዳርገውት በመቆየታቸው ለአፍራሽ ፕሮፓንዳ እና ለከፍተኛ ጥርጣሬ ጭምር እንዲጋለጥ አድርገውታል። እናም መንግስት በነዚህ ጉዳዮች ከህዝብ ጋር ግልጽ ውይይት በማድረግ አፋጣኝ መፍትሄ እንዲሰጥ እንጠይቃለን።

16). በተፈጠረው የሰላም መደፍረስ ምክንያት ህይወታቸውን ላጡ ንጹሀን ሰላማዊ ዜጎች የተሰማንን ጥልቅ ሀዘን እየገለጽን ለወዳጅ ዘመዶቻቸው መጽናናትን፣ አካላዊ ጉዳት ለደረሰባቸውም ቶሎ ማገገምን እንመኛለን።

****
በመጨረሻም ለፓርቲአችን የጠቅላላ ጉባኤ አባላት ፓርቲአችን የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ (አብን) የፊታችን ቅዳሜና እሁድ ነሀሴ 6/7 ለማካሄድ ሲዘጋጅበት የነበረው ድርጅታዊ ጠቅላላ ጉባኤ በተፈጠረው ወቅታዊ የሰላም እጦት ምክንያት ላልተወሰነ ግዜ እንዲራዘም የአስፈጻሚ ኮሚቴው ባሳለፍነው እሁድ ሀምሌ 30 ተሰብስቦ የወሰነ መሆኑን እያሳወቅን የሰላሙ ሁኔታ ሲሻሻልና አስቻይ ሁኔታ ሲፈጠር የጉባኤ ቀን የምናሳውቅ መሆኑን እንገልጻለን።

ነሀሴ 03/2015 ዓ.ም
አዲስ አበባ፣ ሸዋ፣ ኢትዮጵያ

ከአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የተሰጠ መግለጫ። ሰሞኑን በክልላችን በአንዳንድ አካባቢዎች ተከስቶ የነበረው በፅንፈኛና በዘራፊ የስልጣን ጥመኛ ቡድኖች በትጥቅ የታገዘ ሁከትና ብጥብጥ በሁሉም...
08/08/2023

ከአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የተሰጠ መግለጫ።

ሰሞኑን በክልላችን በአንዳንድ አካባቢዎች ተከስቶ የነበረው በፅንፈኛና በዘራፊ የስልጣን ጥመኛ ቡድኖች በትጥቅ የታገዘ ሁከትና ብጥብጥ በሁሉም የክልሉ አከባቢዎች ወደ አንፃራዊ ሰላምና መረጋጋት እየተመለሰ ይገኛል።

ከብዙ ትዕግስትና የሰላም አማራጮች በኃላ አሻፈረኝ ብሎ ክልሉን የእልቂትና የትርምስ ማዕከል ለማድረግ በተደራጀ ሁኔታ ከውስጥና ከውጭ ጠላቶቻችን ጋር በማበር በፋይናንስና በፅንፈኛ ሚዲያዎች ታግዞ ጦርነት አውጆ በተለይም ከተሞችን ማዕከል አድርጎ መንግሥትን በመገዳደር ነፍጥ የመዘዘው ኃይል ላይ መንግሥት ህግ የማስከበር ግዴታውን ተጠቅሞ ህግ ወደ ማስከበር ሥራ መገባቱ የሚታወቅ ነው።

በዚህም መሰረት የምንግዜም የሰላም ዘብ የሆነው የሃገር መከላከያ ሰራዊት በእነዚህ ዘራፊና መረን የለቀቁ ፅንፈኛ ቡድኖች ላይ በወሰደው ተመጣጣኝ እርምጃ ሁከት ተከስቶባቸው የነበሩ የክልላችን አብዛኞቹ ከተሞችን ወደ አንፃራዊ ሰላም እየተመለሱ ይገኛል።

በክልላችን ደቡብ ወሎ፣ ሰሜን ወሎ፣ ዋግ ኽምራ፣ ሰሜን ሸዋ፣ ደብረ ብርሃን፣ ሰሜንና ደቡብ ጎንደር አካባቢዎች በንፅፅር ሰላማዊ የሆነ እንቅስቃሴ ያለባቸውና ሕዝባችን በተረጋጋ መንፈስ የዘወትር ህይወቱን እያከናወነ የሚገኝባቸው ናቸው።

በአንፃሩ በክልላችን ርዕሰ መዲና ባሕር ዳር እና ጎንደር ከተሞች መሽጎ ሕዝባችን እንዲታወክ ሲያደርግ የነበረው ዘራፊ ቡድን ከትላንት ምሽት ጀምሮ በተወሰደ እርምጃ ከእነዚህ ፅንፈኛ ቡድኖች ነፃ የማድረግ ሥራ የተሠራ ሲሆን በቀጣይ በሁሉም የክልላችን አካባቢዎች የማያዳግም የህግ የማስከበር ሥራውን አጠናክሮ በመቀጠል ሕዝባችን ያለስጋት የእለት ከለት ሥራውን በተሟላ ሁኔታ እንዲከውን ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን እየገለፅን መላው የክልላችን ሕዝብ ከሀገር መከላከያ ሰራዊት ጎን ተሰልፎ አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርግና ለህግ ማስከበር ተልዕኮው የበኩሉን ትብብር እንዲያደርግ ጥሪ እናስተላልፋለን።

በመጨረሻም ሕዝባችን በፅንፈኛና የጠላት ተላላኪ ሚዲያዎች አሉቧልታ ሳይደናገር ተረጋግቶ ወደ መደበኛ ህይወቱ እንዲመለስ እያሳሰብን ዝርዝር የህግ ማስከበር አፈፃፀሙንና ክልላዊ የሰላም ሁኔታችንን በተከታታይ የምናሳውቅ መሆኑን እንገልፃለን ።

የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት
ነሃሴ 2/12/2015

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ፤ በደም አፋሳሽ ግጭቶች ባለድርሻ የሆኑ አካላትን ለማወያየት አመቺ ሁኔታዎችን ለመፍጠር ዝግጁ መሆኑን አሳወቀየኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በደም አፋሳ...
08/08/2023

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ፤ በደም አፋሳሽ ግጭቶች ባለድርሻ የሆኑ አካላትን ለማወያየት አመቺ ሁኔታዎችን ለመፍጠር ዝግጁ መሆኑን አሳወቀ

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በደም አፋሳሽ ግጭቶች ባለድርሻ አካላትን በማቀራረብ ፣ የልዩነት አጀንዳዎችን ሰብስቦ ለማወያየት እና ለማመካከር አመቺ ሁኔታዎችን ለመፍጠር ዝግጁ መሆኑን ገልጿል።

ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽኑ ዛሬ ማክሰኞ ነሐሴ 2 ፤ 2015 ዓ.ም ካሰራጨዉ መግለጫ ብስራት ራዲዮ እና ቴቪ እንደተመለከተዉ ፤ የሚመለከታቸውን አካላት ልዩነቶቻቸውን በጠረጴዛ ዙሪያ ተቀምጠው በምክክር እንዲፈቱ ጠይቋል።

በመላው ኢትዮጵያ የሚታዩ ግጭቶችም ያላንዳች ቅደመ ሁኔታ ቆመው በአስቸኳይ በምክክር እንዲፈቱ ጥሪ አቅርቧል።

ኮሚሽኑ ለሀገራዊ ምክክሩ የተሳታፊዎች የተሳታፊዎች ልየታ እየተከናወነ ባለበት ሁኔታ በተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች አየታዩ ያሉ ግጭቶች የኮሚሽኑን ስራ አዳጋች እያደረጉበት ይገኛሉ ብሏል።

አማራ ክልል የተከሰተው ግጭት እና አለመረጋጋት እንዳሳሰባቸው በመግለጽ የሲቪክ ተቋማት በጋራ መግለጫ አውጥተዋል። -----------------______------------______-------...
08/08/2023

አማራ ክልል የተከሰተው ግጭት እና አለመረጋጋት እንዳሳሰባቸው በመግለጽ የሲቪክ ተቋማት በጋራ መግለጫ አውጥተዋል።
-----------------______------------______-----------______
እኛ ሥማችን ከዚህ መግለጫ ግርጌ የተዘረዘረው የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች በአማራ ክልል የተከሰተው ግጭት እጅግ አሳስቦናል። ግጭቱን ለመቆጣጠር እና ሰላምና መረጋጋትን ለማስፈን ክልሉ “በመደበኛ የሕግ ማስከበር ስርዓት ለመቆጣጠር አዳጋች” ሆኖብኛል በሚል ለፌዴራል መንግሥቱ አስፈላጊውን የሕግ ማዕቀፍ እንዲተገብር መጠየቁን ሰምተናል። ይህንን ተከትሎ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ተፈፃሚነቱ በክልሉ እና እንዳስፈላጊነቱ በሌሎችም አካባቢዎች የሆነ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ከሐምሌ 28 ጀምሮ ማወጁን አሳውቋል። ግጭቶችን የመከላከልና ሰላም የማስፈን ጉዳይ ጊዜ የማይሰጠው አንገብጋቢ ጉዳይ መሆኑን እናምናለን። ይሁንና ግጭቶች ከጊዜ ወደ ጊዜ ሥር እየሰደዱና እየተስፋፉ ከመሆኑ አንፃር፣ ግጭቶችን ለማስቆም የሚወሰዱ እርምጃዎች የብዙኃንን ደኅንነት፣ የዜጎችን ሰብዓዊ መብቶችና ነጻነቶች አደጋ ላይ የማይጥሉ እንዲሆኑ፤ እንዲሁም የግጭቱ መነሻ መንስዔዎች በሚመለከታቸው አካላት ተለይተው የሚቀርቡ ዘላቂ የመፍትሔ ሐሳቦች ላይ ሁሉን አካታች ምክክሮች እንዲካሔዱና በአግባቡም መተግበር እንዳለባቸውም እንረዳለን።

ስለሆነም፣ የሚመለከታቸው አካላት፣

ግጭቶች በሰላማዊ ዘዴዎች የሚፈቱባቸውን መንገዶች ለማግኘት የሲቪል ማኅበራት፥ የፖለቲካ ፓርቲዎች፥ የእምነት ተቋማት፣ መገናኛ ብዙኃን፣ እና የአገር ሽማግሌዎች የተከሰተው ግጭት በሰላማዊ መንገድ እንዲፈታ የበኩላቸውን ግፊት እንዲያደርጉ፤ በሌሎች የኢትዮጵያ ክልሎች የተጀመሩ የሰላም ጥረቶች እና ሥምምነቶች በአማራ ክልልም በሚንቀሳቀሱ ወገኖች እና በፌዴራሉ እና የክልሉ መንግሥታት መካከል መደረግ የሚችልበት ዕድል እንዲፈለግ፣
ትጥቅን መሠረት ያደረጉ ግጭቶች በሰብዓዊ መብቶች እና በሰብዓዊ ሕግጋት (humanitarian laws) እንዲመሩ እና የንፁኃን ደኅንነት እንዲጠበቅ፤ በሌሎች የኢትዮጵያ ክፍሎች በተከሰቱ ግጭቶች የተፈፀሙ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች፣ ፆታን መሠረት ያደረጉ ጥቃቶች፣ እና ሌሎችም ጉዳቶች በክልሉ እንዳይፈፀሙ ከፍተኛ የመከላከል ሥራዎች እንዲከናወኑና የተጠያቂነት ስርዓት እንዲዘረጋ፣
በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ አፈፃፀም ወቅት የፀጥታ አካላት ያልተመጣጠነ ኃይል እንዳይጠቀሙ፣ ብሔርን መሠረት ያደረጉ ማግለሎች እና ጥቃቶች እንዳይስፋፉ እና የጅምላ እስሮች (indiscriminate mass arrests) እንዳይከናወኑ፣
የማኅበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች እና ብዙኃን መገናኛዎች ግጭት አገናዛቢ አዘጋገብን እንዲተገብሩ፣ የሐሰተኛ እና የተዛቡ መረጃዎችን ስርጭት እንዲገቱ፣ እንዲሁም ሐቁን የሚያንፀባርቁ መረጃዎችን ብቻ ለዜጎች በማድረስ ከግጭት አባባሽነት እንዲቆጠቡ፣
የዜጎች የመገናኛ ዘዴዎች እና ሌሎችም መሠረታዊ አገልግሎች እንዳይቋረጡ ማድረግ እና ሰብዓዊ እርዳታዎች ለሚያስፈልጓቸው በተለይም በአማራ ክልልና አጎራባች አካባቢዎች በሚገኙ የአገር ውስጥ ተፈናቃዮች ባሉባቸው ቦታዎች በአግባቡ እንዲደርሱ ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲደረግ፣
ዝርዝር የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅን ለማስፈጸም የሚወጡ መመሪያዎችና ደንቦች ለዜጎች ተዳራሽ በሆኑ አማራጮች በተከታታይ እንድደርሱ ጥሪያችንን እናቀርባለን።
ሰላም ለኢትዮጵያ!

ይህንን የሰላምና የዘላቂ መፍትሔ ጥሪ ያቀረብን የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች የሚከተሉት ነን።

-የመብቶች እና ዴሞክራሲ ዕድገት ማዕከል (ካርድ)
-የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ተሟጋቾች ማዕከል
-የኢትዮጵያ የሕግ ባለሙያ ሴቶች ማኅበር
-የኢትዮጵያ ሴቶች ማኅበራት ቅንጅት
-አዲስ ፓወርሀውስ
-የኢትዮጵያ ሴቶችና ሕፃናት ማኅበራት ኅብረት
-የሕግ ባለሙያዎች ለሰብዓዊ መብቶች
-የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ድርጅቶች ህብረት
-ሴታዊት ንቅናቄ

ሕ.ወ.ሓ.ት በሚል ስያሜ አዲስ ፓርቲ ለማቋቋም የቀረበውን የዕውቅና ጥያቄ ፍርድ ቤት ውድቅ ማድረጉን ምርጫ ቦርድ አስታወቀ ********** በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እና በእነገ/ሚካኤ...
07/08/2023

ሕ.ወ.ሓ.ት በሚል ስያሜ አዲስ ፓርቲ ለማቋቋም የቀረበውን የዕውቅና ጥያቄ ፍርድ ቤት ውድቅ ማድረጉን ምርጫ ቦርድ አስታወቀ
**********

በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እና በእነገ/ሚካኤል ተስፋዬ መካከል ሐምሌ 28 ቀን2015 ዓ.ም. በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የምርጫ ጉዳይ ክርክር ችሎት የተደረገው ክርክር ውሣኔ ማግኘቱን ምርጫ ቦርድ አስታወቀ፡፡

ፍርድ ቤቱ ሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ሕ.ወ.ሓ.ት) ተብሎ የሚጠራ ክልላዊ ፓርቲ ለመመሥረት የቅድመ ዕውቅና ፍቃድ መጠየቃቸውን መጥቀሱ ተገልጿል፡፡

በተጠቀሰው ስያሜ የሚጠራ ለረጅም ዓመታት የሚታወቅ ፓርቲ የነበረ በመሆኑ፤ በዚሁ ስም አዲስ ፓርቲ ማቋቋም መራጩን የሚያደናግር መሆም ነው የተገለጸው፡፡

ቦርዱ ሰኔ 05 ቀን 2015 ዓ.ም. ሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ሕ.ወ.ሓ.ት) ተብሎ የሚጠራ ክልላዊ ፓርቲ ለመመሥረት የቀረበውን የቅድመ ዕውቅና ጥያቄ ውድቅ ማድረጉ ስሕተት አይደለም በሚል የቦርዱን ውሣኔ እናዳፀና በማበራዊ ትስስር ገፁ ባጋራው መረጃ አስታውቋል፡፡

ከአስአኳይ ጊዜ አዋጅ ጠቅላይ መምሪያ የተሰጠ መግለጫ ************************ በአማራ ክልል እየተከናወነ ያለው የህግ ማስከበር ተግባር በአጭር ጊዜ በማጠናቀቅ ክልሉን ወደ ሰለ...
06/08/2023

ከአስአኳይ ጊዜ አዋጅ ጠቅላይ መምሪያ የተሰጠ መግለጫ
************************

በአማራ ክልል እየተከናወነ ያለው የህግ ማስከበር ተግባር በአጭር ጊዜ በማጠናቀቅ ክልሉን ወደ ሰለማዊ እንቅስቃሴ ለመመለስ የሚያስችሉ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን የአስአኳይ ጊዜ አዋጅ ጠቅላይ መምሪያ እዝ አስታወቀ፡፡
በአማራ ክልል ያጋጠመውን የፀጥታ መደፍረስ በመደበኛ የህግ ማስከበር ስርአት ለመቆጣጠር አዳጋች ሆኖ በመገኘቱ የፌደራል መንግስት አስፈላጊውን የህግ ማዕቀፍ እንዲተገብር የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት መጠየቁ ይታወሳል፡፡

ይህን ተከትሎም የሚኒስትሮች ምክር ቤት በክልሉ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ እንዲተገበር በሙሉ ድምጽ ያጸደቀ ሲሆን፤ አዋጁን የሚያስተባብር ጠቅላይ መምሪያ እዝ ተቋቁሞ ወደ ስራ ገብቷል፡፡

በዛሬው እለትም የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ጠቅላይ መመሪያ እዝ ችግሩን ለመፍታት ያዘጋጀውን እቅድ አፈጻጸም በሚመለከት ውይይት አድርጓል፡፡

የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ጠቅላይ መመሪያ እዝ ዋና ሰብሳቢ አቶ ተመስገን ጥሩነህ በሰጡት መግለጫ፤ በክልሉ በተደራጁ ዘራፊ ቡድኖች የተከሰተው የሰላም መደፍረስ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና አስተዳደራዊ ችግሮችን ፈጥሯል ነው ያሉት፡፡

ዘራፊ ቡድኖች የህዝብ አግልግሎት መስጫ ተቋማት አገልግሎት እንዳይሰጡ ከማስተጓጎል ባሻገር በአንዳንድ አካባቢዎች ማረሚያ ቤቶችን ሰብረው ወንጀለኞችን እንዲያመልጡ እስከማድረግ የደረሰ ውንብድና መፈጸማቸውን ጠቁመዋል

ይህም በተለይ የክልሉ አርሶ አደር የመኸር እርሻ ወቅትን ተረጋግቶ እንዳያከናወን ማድረጉን ጠቅሰው፤ ዜጎች በነጻነት ተንቀሳቅሰው አገልግሎት እንዳያገኙ ማድረጉን ተናግረዋል፡፡

ከዚህ አኳያ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ጠቅላይ መምሪያ በክልሉ የተከሰተውን የጸጥታ መደፍረስ ለመቀልበስ እየሰራ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡

ዘራፊ ቡድኑ የህዝብ መገልገያ ተቋማትን በመዝረፍና በማውደም ጭምር የክልሉ ነዋሪዎች ላይ ከፍተኛ በደል እየፈጸመ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡

መንግስት የትኛውም ጥያቄ በሰላም መፈታት እንዳለበት በጽኑ ያምናል፤ ባለፉት ጊዜያትም ይህንን በተግባር አሳይቷል ብለዋል፡፡

በቀጣይ መንግስት ህግና ስርዓት የማስከበር ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ጭምር ነው የተናገሩት።

በክልሉ እየተከናወነ ያለው የህግ ማስከበር ስራ በአጭር ጊዜ በማጠናቀቅ ክልሉን ወደ ሰላማዊ እንቅስቃሴ ለመመለስ የሚያስችሉ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ገልፀዋል።

ህብረተሰቡ ከመከላከያ ሰራዊት ጎን እንዲቆም እና ሰራዊቱን እንዲደግፍ ጥሪ አቅርበዋል።

የአበራሽ ጠባሳጃውሳ ጎረቤትህን ጠይቅ-------__---------____------ዲያቆን ዳንኤል ክብረት--------____--------___-----፨በመቶ ሺዎች የሚጠጋ ታጣቂ ከ ሁለት ዓመት...
06/08/2023

የአበራሽ ጠባሳ
ጃውሳ ጎረቤትህን ጠይቅ
-------__---------____------
ዲያቆን ዳንኤል ክብረት
--------____--------___-----
፨በመቶ ሺዎች የሚጠጋ ታጣቂ ከ ሁለት ዓመት በላይ ያሠለጠነው መጨረሻው ምን ሆነ?
፨መከላከያን የወጋው ጨፋሪ መጨረሻው ምን ሆነ?
፨እስከ ደብረ ሲና የመጣው መጨረሻው ምን ሆነ?
፨እስከ ጋይንት የደረሰው ፎካሪ መጨረሻው ምን ሆነ?
፨ይሄን ከተማ ተቆጣጠርኩ ሲል የነበረው መጨረሻው ምን ሆነ?
፨አራት ኪሎ ስንቅ ሳይኖረው አራት ኪሎን ሲመኝ የነበረው መጨረሻው ምን ሆነ?
፨አሜሪካና አውሮፓ የነበረውን ዳያስፖራ ሲያንከባልል የነበረው መጨረሻው ምን ሆነ?
፨በዩቱዩብ የሚመራ ጦርነት አደርጋለሁ ብሎ የመጣው መጨረሻው ምን ሆነ?
፨ የምዕራቡ ሚዲያዎች ሲዘግቡለት የነበረው መጨረሻው ምን ሆነ?
ጃውሳ ጎረቤትህን ጠይቅ። የቀናት ዕድሜ አለህ ለመልሱ።

ኢፌድሪ መከላከያ ሠራዊት ሃምሌ 30 ቀን 2015 ዓ.ም "እኛ የምንሸነፈው በነፍሳችን ልናጸናት በቆምንላት ኢትዮጵያችን ፍቅር ብቻ ነው" የምንወጣ የምንወርደው፣የነፍስ ዋጋ የምንከፍለው፣ የትኛ...
06/08/2023

ኢፌድሪ መከላከያ ሠራዊት ሃምሌ 30 ቀን 2015 ዓ.ም

"እኛ የምንሸነፈው በነፍሳችን ልናጸናት በቆምንላት ኢትዮጵያችን ፍቅር ብቻ ነው"

የምንወጣ የምንወርደው፣የነፍስ ዋጋ የምንከፍለው፣ የትኛውንም ፈተና የምንጋፈጠው ስለ ኢትዮጵያና ኢትዮጵያ ብቻ ነው።

አዕምሮውን በመንደር አጥብቦ፣በዕውቀት ሳይሆን በስሜት ልቡን ያሳበጠ፣የስህተቱ ምንጭ የሴረኞች "የጨፍን ላሞኝህ" ሀሳዊ ትርክት መሆኑ በደንብ ይገባናል።በሙያዊ ዲሲፕሊን በሰከነና ጥበብ በተሞላበት የግዳጅ አፈጻጸማችን ሁሉንም ወደ ትክክለኛው ቦታ መመለስ እንደሚቻልም እናውቃለን።

ማንም በነዳው ቁጥር በአጉራ ዘለልነት እኛ ላይ ቃታ ለመሳብ የሚዳዳው የትኛውም ሃይል በአሳፋሪ ድርጊቱ ብናዝንም የመጨረሻ ውጤቱ ምን እንደሆነ ከልምዳችን አሳምረን እናውቃለን።

አሳዛኙ ነገር ከትላንቱ ምስቅልቅል ቀውስ እና ኪሳራ ካተረፈልን ችግር መማር ያልቻሉ "ጦር አውርድ" ባዮች ምን ያህል ለህዝብና ለሀገር ግድ እንደሌላቸው እየታወቀ፤ የእነዚህ እኩያን ተከታይ ጋሻ ጃግሬ መኖሩ ነው።

የፈለገውን ዓይነት ጭምብል ይልበስ በሀገር ህልውናና በህዝብ ሰላም ላይ ተረማምዶ የፍላጎቱን ቅንጣት ማሳካት አይችልም።

እኛን በእጅጉ የሚያሳዝነን የውጭ ሃይሎች ተጋላቢ ፈረሶች፣የስልጣን ጥማተኛ ጃስ ተብዬዎች ዓይናቸውን ጨፍነው በሚለኩሱት እሳት የህዝብን ሰላም ከማወክ አልፈው ማህበራዊ እረፍት ሲነሱት ነው።ያ እኛን ያመናል።

ምንም ሆነ ምን ግን በመስዋዕትነታችን ዋጋ የህዝባችንን ሰላም የሀገራችንን ህልውና አስጠብቀን ምርቱን ከግርዱ በለየ አስተውሎታዊ ግዳጅ አፈጻጸም ኢትዮጵያችንን አጽንተን ከነክብሯ እናስቀጥላታለን።

ለእኛ ከኢትዮጵያ የሚበልጥብን አንዳችም እሳቤ የለም።

ሁሉም ነገር የሚያምረው በሀገር ነውና ስለሀገር መቤዛችን የማይቆም ግዴታችን ነው።

ለማንኛውም ሁሉም በጎ ይሆናል።የሚያሳስበን የምንከፍለው ዋጋ አይደለም።የሀገርና ህዝብ ሰላም እንጂ።

በሀገርና በወገን ያሴረ ስሜት የሚነዳው አጉራ ዘለል ጊዜያዊ እውክታ ይፈጥር ይሆን እንጂ የትም እንደማያደርሰው ራሱም ጠንቅቆ ያውቀዋል።

"እኛን የሚያሸንፈን ማንም ሳይሆን በነፍሳችን ልናጸናት የቆምንላት ኢትዮጵያችን ፍቅር ብቻ ነው።"

Address

Addis Abeba
Addis Ababa

Opening Hours

Monday 09:00 - 17:00
Tuesday 09:00 - 17:00
Wednesday 09:00 - 17:00
Thursday 09:00 - 17:00
Friday 09:00 - 17:00
Saturday 09:00 - 17:00

Telephone

+251911124769

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Mosaic news posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Mosaic news:

Share