Eftan News

Eftan News Accurate information for the public!

29/03/2025
የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ለአራት ወራት እንዲራዘም ተወሰነ።(ኢፍታን ኒውስ፤ ጥር 24/2016 ዓ.ም -  አዲስ አበባ)የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሐምሌ 28 ቀን ፣ 2015 ዓ.ም ባደረገው ስብሰ...
02/02/2024

የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ለአራት ወራት እንዲራዘም ተወሰነ።

(ኢፍታን ኒውስ፤ ጥር 24/2016 ዓ.ም - አዲስ አበባ)

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሐምሌ 28 ቀን ፣ 2015 ዓ.ም ባደረገው ስብሰባ በአማራ ክልል የህዝብን ሰላምና ደህንነት ለማስጠበቅ ያወጣውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ቁጥር 6/2015 ለመቀበልና ለማፅደቅ የወጣውን አዋጅ ቁጥር 1299/2015 ለማራዘም የውሳኔ ሀሳብ ቀርቧል።

ምክር ቤቱ ሶስተኛ ዓመት የስራ ዘመን አንደኛ ልዩ ስብሰባውን ዛሬ ሲያካሂድ የውሳኔ ሀሳቡን ረቂቅ ያቀረቡት የፍትህ ሚኒስትሩ ጌዲዮን ጢሞቲዮስ (ዶ/ር) በአዋጁ መራዘም አስፈላጊነት ላይ ማብራሪያ ማቅረባቸውን ተከትሎ የምክር ቤቱ አባላት ሰፊ ውይይት አድርገዋል።

በመጨረሻም ምክር ቤቱ የቀረበለትን የውሳኔ ሀሳብ በውሳኔ ሀሳብ ቁጥር 5/2016 ሆኖ በ ሁለት ተቃውሞ ፣ በሦስት ድምፀ ታዐቅቦ በአብላጫ ድምጽ ለቀጣይ አራት ወራት እንዲራዘም አፅድቋል።

የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን መራዘም ተከትሎ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አፈፃፀም መርማሪ ቦርድ የስራ ዘመንን ለማራዘም የቀረበለትን የውሳኔ ሀሳብ የውሳኔ ቁጥር 6/2016 ሆኖ በ2 ተቃውሞ በአብላጫ ድምጽ አፅድቋል።

የኢትዮጵያ ፓስፖርት ከዓለም 93ኛ ደረጃ ላይ ሲገኝ ያለ ቪዛም 44 አገራት መግባት ያስችላል ተባለ።(ኢፍታን ኒውስ፤ ጥር 19/2016 ዓ.ም -  አዲስ አበባ)የዓለም የጉዞ ሰነድ ተቀባይነትን...
28/01/2024

የኢትዮጵያ ፓስፖርት ከዓለም 93ኛ ደረጃ ላይ ሲገኝ ያለ ቪዛም 44 አገራት መግባት ያስችላል ተባለ።

(ኢፍታን ኒውስ፤ ጥር 19/2016 ዓ.ም - አዲስ አበባ)

የዓለም የጉዞ ሰነድ ተቀባይነትን አስመልክቶ ቁጥራዊ መረጃና ደረጃን የሚያወጣው ሄንሌይ የተሰኘው ፓስፖርት መለኪያ ተቋም የ2024 የሀገራት ፓስፖርት ጥንካሬ ኢትዮጵያን 93ኛ ደረጃ ላይ አስቀምጧታል።

የኢትዮጵያን ፓስፖርት የያዘ ሰው ያለ ቪዛ ወደ 44 ሀገራት መጓዝ እንደሚችልም ሄንሌይ የፓስፖርት መለኪያ ተቋም አስታውቋል።

ያለ ቪዛ ቀጥታ የሚገባባቸው ሀገራት ባርባዶስ፣ ቤኒን፣ ቦሊቪያ፣ ኩክ ደሴቶች፣ ዶምኒካ፣ ሃይቲ፣ ኬንያ፣ ላኦስ፣ ማዳካስካር፣ ማላዳቪስ፣ ኑዬ፣ ፕላዩ ደሴቶች፣ ፊሊፒንስ፣ ሩዋንዳ፣ ሴኔጋል፣ ሲናጋፖር፣ ስሪላንካ፣ ሴንት ቪንሴንትና ግሬኔድስ፣ ሱሪናሜ፣ ጋምቢያ በመዳረሻ ቪዛ (ቪዛ ኦን አራይቫል) የሚገባባቸው ሀገራት ናቸው።

በተጨማሪም ባንግላዴሽ፣ ቡሩንዲ፣ ካምቦዲያ፣ ኬፕ ቭርዴ፣ ኮሞሮስ ደሴቶች፣ ጂቡቲ፣ ኤርትራ፣ ጋና፣ ጊኒ ቢሳው፣ ኢራን፣ ማካዎ፣ ሞሪታኒያ፣ ሞሪሽስ፣ ሞዛምቢክ፣ ኒካራጉዋ፣ ናይጄሪያ፣ ሳሞዋ፣ ሲሸልስ፣ ሶማሊያ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ሴንት ሉሺያ፣ ታይላንድ፣ ቲሞርሌስት፣ ቶጎ፣ ታቩሉ እና ዚምባቡዌንም እንደሚያጠቃልል መረጃው ያመለክታል።

ኢትዮጵያ የቀይ ባሕር ካውንስል አባል የመሆን መብት አላት - ሰርቫይቭ ዘ ኒውስ(ኢፍታን ኒውስ፤ ሕዳር 8/2016 ዓ.ም. አዲስ አበባ)ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኢትዮጵያ የባ...
18/11/2023

ኢትዮጵያ የቀይ ባሕር ካውንስል አባል የመሆን መብት አላት - ሰርቫይቭ ዘ ኒውስ

(ኢፍታን ኒውስ፤ ሕዳር 8/2016 ዓ.ም. አዲስ አበባ)

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኢትዮጵያ የባሕር በር ማግኘት የሕልውና ጉዳይ ነው ማለታቸውን ተከትሎ የባሕር በር ጉዳይ በሀገር ውስጥ እና በውጭ መገናኛ ብዙሃን መነጋገሪያነቱ አሁንም ቀጥሏል።

በዚህ ዙሪያ ሰፋ ያለ ሀተታ ያስነበበው ሰርቫይቭ ዘ ኒውስ (Survive the News) የተሰኘ የውጭ ሚዲያ፥ "ኢትዮጵያ የቀይ ባሕር ካውንስል አባል የመሆን መብት አላት" ሲል ፅፏል።

የቀይ ባሕር ካውንስል የተቋቋመው በቀይ ባሕር ቀጠና ያሉ ሀገራትን ኢኮኖሚያዊ እና የፀጥታ ጉዳይን በተመለከተ በጋራ ለመሥራት መሆኑን ዘገባው ያትታል።

አጠቃላይ ንግዷን በቀይ ባሕር በኩል የምታካሂድ እና ከቀይ ባህር 60 ኪ.ሜ ርቀት ላይ የምትገኘው ኢትዮጵያን ከቀይ ባሕር ካውንስል ማግለል ተቀባይነት የሌለው ተግባር መሆኑን ሰርቫይቭ ዘ ኒውስ በጉዳዩ ላይ ያስነበበው ሰፋ ያለ ጽሁፍ ያመለክታል።

በዚህ ረገድ ኢትዮጵያን ከቀይ ባሕር ካውንስል ማግለል ምክንያታዊ አለመሆኑን ለማሳየት ዘገባው የአርክቲክ ካውንስልን ልምድ አጋርቷል።

የአርክቲክ ካውንስል ከአርክቲክ ውቅያኖስ ጋር የማይዋሰኑትን ስዊድን እና ፊንላንድን የካውንስሉ ሙሉ አባል አድርጓል።

ከዚህ ባሻገር ከውሃው አካል በ9 ሺህ ኪ.ሜ ርቀት ላይ የሚገኙት ቻይና እና ህንድም በአርክቲክ ካውንስል በታዛቢ አባልነት መካተት ችለዋል።

ከዚህ አኳያ ከቀይ ባሕር 60 ኪ.ሜ ርቀት ላይ የምትገኘውን ኢትዮጵያን ቢያንስ የቀይ ባሕር ካውንስል ታዛቢ አባል አለማድረግ ግርምትን ይፈጥራል ይላል ትንታኔ ጽሁፉ።

ያም ሆነ ይህ ለቀይ ባሕር በቅርብ ርቀት የምትገኝ እና በዓለም ደረጃ ከፍተኛ የሕዘብ ቁጥር ካላቸው ሀገራት ተርታ የምትመደበውን ኢትዮጵያን ያገለለ የቀይ ባሕር ካውንስል የታለመለትን ግብ አይመታም ሲል ዘገባው ጽሁፉን ያጠቃልላል። (EBC)

በሱዳን  አዉሮፕላን ተከስክሶ 9 ሰዎች ሞቱ።  (ኢፍታን ኒውስ፤ ሓምሌ 17/2015 ዓ.ም -  አዲስ አበባ) በፖርት ሱዳን የአየር ማረፊያ አንድ አንቶኖቭ አዉሮፕላን ተከስክሶ የ9 ሰዎች ህይ...
24/07/2023

በሱዳን አዉሮፕላን ተከስክሶ 9 ሰዎች ሞቱ።

(ኢፍታን ኒውስ፤ ሓምሌ 17/2015 ዓ.ም - አዲስ አበባ)

በፖርት ሱዳን የአየር ማረፊያ አንድ አንቶኖቭ አዉሮፕላን ተከስክሶ የ9 ሰዎች ህይወት ማለፉ ተሰምቷል።

በተከሰተው አደጋ ህይዎታቸዉን ካጡት መካከል አራቱ ወታደሮች መሆናቸዉም ተገልጿል።

በፖርት ሱዳን የአየር ማረፊያ ዛሬ ጠዋት ለደረሰዉ የአዉሮፕላን መከስከስ አደጋ መንስኤዉ የቴክኒክ ብልሽት መሆኑን አልጄዚራ ዘግቧል።

አንድ ህፃን ከአደጋዉ መትረፉንም የሀገሪቱ ጦር አስታዉቋል።

በሱዳን በቀጠለው ጦርነት ሳቢያ በሀገሪቱ አገልግሎት እየሰጠ የሚገኘው የአውሮፕላን ማረፊያ ፖርት ሱዳን ብቻ መሆኑም ተጠቅሷል።

የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎቹ በአካል ተገኝተዉ እንደሚመዘገቡ ጥሪ አቀረበ።(ኢፍታን ኒውስ፤ ሓምሌ 14/2015 ዓ.ም -  አዲስ አበባ)የመቐለ ዩኒቨርሲቲ በ2013 ተመራቂ የነበሩ የመጀመርያ ዲ...
21/07/2023

የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎቹ በአካል ተገኝተዉ እንደሚመዘገቡ ጥሪ አቀረበ።

(ኢፍታን ኒውስ፤ ሓምሌ 14/2015 ዓ.ም - አዲስ አበባ)

የመቐለ ዩኒቨርሲቲ በ2013 ተመራቂ የነበሩ የመጀመርያ ዲግሪ መደበኛ ተማሪዎች፣ የድህረ ምረቃ ተማሪዎች፣ የተከታታይ ትምህርትና የማታ ተማሪዎች እና የሕክምና ትምህርት ክፍል ተማሪዎቹ ሐምሌ 26 እና 27 በአካል ተገኝተዉ እንደሚመዘገቡ ጥሪ አቅርቧል፡፡

በዚህም መሰረት በዋናዉ ግቢ፣ በቃላሚኖ ግቢ እና በዓይደር ግቢ ተማሪዎቹ በተጠቀሱት ቀናት እንዲገኙ ዩኒቨርሲቲው አሳስቧል።

በተመሳሳይ ተመራቂ ያልሆኑ የመጀመርያ ዲግሪ መደበኛ ተማሪዎችም ምዝገባቸዉ መስከረም 4 እና 5 /2016 መሆኑንም ጨምሮ ገልጿል፡፡ (አዲስ ማለዳ)

"የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ማድረጋችን በርካታ የጤና ጥቅም አስገኝቶልናል" የ ስፖርቱ ተሳታፊዎች፤(ኢፍታን ኒውስ፤ ሓምሌ 13/2015 ዓ.ም -  ደሴ)በደሴ ከተማ በሚደረገው ሳምንታዊ የአካል ...
20/07/2023

"የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ማድረጋችን በርካታ የጤና ጥቅም አስገኝቶልናል" የ ስፖርቱ ተሳታፊዎች፤

(ኢፍታን ኒውስ፤ ሓምሌ 13/2015 ዓ.ም - ደሴ)

በደሴ ከተማ በሚደረገው ሳምንታዊ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ተሳታፊ በመሆናቸው የተለያዩ የጤናና የስነ ልቦና ጥቅም እያገኙበት እንደሆነ ተሳታፊዎቹ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።

በአካል ብቃት እንቅስቃሴ አሰልጣኝ በ ወ/ሪት ትዕግስት ገብረእየሱስ አማካኝነት በሳምንት ለሶስት ቀናት ያህል የአንድ ሰዓት የአካል ብቃት እንቅስቃሴ እየተሰጠ ይገኛል።

"ዘወትር ማክሰኞ፣ ሃሙስ እና ቅዳሜ ከጥዋቱ 12፡00 ሰዓት እስከ 01፡00 ሰዓት በሚኖረው ስፖርታዊ እንቅስቃሴ ላይ ማንኛውም ፍላጎቱ ያለው ግለሰብ ደሴ ከተማ አስተዳደር ቢሮ ፊት ለፊት ግዮን አምባሰል ሆቴል ጎን ከሚገኘው የአስፋልት መንገድ ላይ በመገኘት መሳተፍ ይችላል" በማለት አሰልጣኝ ትዕግስት ገብረእየሱስ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።

የተለያዩ የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ተማሪዎቻቸውን አስመረቁ።(ኢፍታን ኒውስ፤ ሓምሌ 13/2015 ዓ.ም -  አዲስ አበባ)በሃገራችን ከሚገኙት ከ50 በላይ የመንግስትና የግል ዩኒቨርሲቲዎች መካከ...
20/07/2023

የተለያዩ የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ተማሪዎቻቸውን አስመረቁ።

(ኢፍታን ኒውስ፤ ሓምሌ 13/2015 ዓ.ም - አዲስ አበባ)

በሃገራችን ከሚገኙት ከ50 በላይ የመንግስትና የግል ዩኒቨርሲቲዎች መካከል ከ20 በላይ የሚሆኑት የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ሐምሌ 13 ቀን 2015 ዓ.ም ተማሪዎቻቸውን እያስመረቁ ይገኛሉ።

ተማሪዎቻቸውን ካስመረቁት ዩኒቨርሲቲዎች መካከል፦

- ጅማ ዩኒቨርሲቲ

- ወለጋ ዩኒቨርሲቲ (ነቀምቴ ካምፓስ)

- ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ (በዋናው ግቢ)

- አርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ (ዋናው ግቢ)

- ሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ

- ጂንካ ዩኒቨርሲቲ

- ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ

- ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ

- ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ

- ሰመራ ዩኒቨርሲቲ

- ዲላ ዩኒቨርሲቲ

- እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ

- ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ (በዋናው ግቢ)

- መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ

- ቀብሪ ድሃር ዩኒቨርሲቲ

- ወራቤ ዩኒቨርሲቲ

- ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ

- ደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ

- መቱ ዩኒቨርሲቲ

- አምቦ ዩኒቨርሲቲ

- ሰላሌ ዩኒቨርሲቲ

- ወልድያ ዩኒቨርሲቲ

- ደባርቅ ዩኒቨርሲቲ

- ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ

- አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ

-አዲስ አበባ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ መሆናቸውን ትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል።

በሲንጋፖር ፓስፖርት ከቪዛ ነፃ 192 የአለማችን ሃገራት መግባት በማስቻሉ በ1ኛ ደረጃ ለይ መቀመጡ ተገለጸ።(ኢፍታን ኒውስ፤ ሓምሌ 12/2015 ዓ.ም -  አዲስ አበባ)እንደ አልጀዚራ ዘገባ ...
19/07/2023

በሲንጋፖር ፓስፖርት ከቪዛ ነፃ 192 የአለማችን ሃገራት መግባት በማስቻሉ በ1ኛ ደረጃ ለይ መቀመጡ ተገለጸ።

(ኢፍታን ኒውስ፤ ሓምሌ 12/2015 ዓ.ም - አዲስ አበባ)

እንደ አልጀዚራ ዘገባ በሲንጋፖር ፓስፖርት ከቪዛ ነፃ 192 የአለማችን ሃገራት መግባት የሚያስችል በመሆኑ የቀዳሚነት ደረጃን ይዟል።

ጀርመን፣ ጣሊያን እና ስፔን ሁለተኛ ደረጃ ላይ በመቀመጥ ፓስፖርታቸው 190 ሃገሮች ያለምንም ቪዛ ማስገባት ማስቻሉ ተገልጿል።

እ.ኤ.አ. በ2014 አንደኛ ደረጃን ይዞ የነበረው የየዩናይትድ ስቴትስ ፓስፖርት ወደ ስምንተኛ ደረጃ ዝቅ ሊል መቻሉን አልጀዚራ በዘገባው አስታውሷል።

ከ450 ዓመት በፊት ተቋርጦ የነበረው የኢፋት ወላስማ ሱልጧኔት ሱልጣን ሹመት ተከናወነ።(ኢፍታን ኒውስ፤ ሓምሌ 08/2015 ዓ.ም -  አዲስ አበባ)                           ...
15/07/2023

ከ450 ዓመት በፊት ተቋርጦ የነበረው የኢፋት ወላስማ ሱልጧኔት ሱልጣን ሹመት ተከናወነ።

(ኢፍታን ኒውስ፤ ሓምሌ 08/2015 ዓ.ም - አዲስ አበባ)



በአርጎባ ልማት ማሕበር አስተባባሪነት አርጎባ ልዩ ወረዳ ሐምሌ 3/2015 ዓ.ም ከ450 ዓመት በፊት ተቋርጦ የነበረው የኢፋት ወላስማ ሱልጧኔት ሱልጣን መሀመድ አሽራዬን የአርጎባ ጀበርት የኢፋት ሱልጣኔት ሱልጣን በመሆን ተሹመዋል።

በበዓለ ሲመቱ ላይ የአርጎባ ብሔረሰብ በስፋት ከሚኖርባቸው ከአፋር ፣ ከአማራ፣ ከሀረሪ እና ከኦሮሚያ ክልሎች የብሔረሰቡ አባላት ፤ ዲያስፖራዎች ተገኝተዋል።

የበዓሉ አስተባባሪ የሆነው የአርጎባ ልማት ማህበር የቦርድ ሰብሳቢ አቶ መሀመድ ሙሣ ሹመቱ ያስፈለገበትን ምክንያት ሲገለፁ እየጠፋ ያለውን የአርጎብኛ ቋንቋ እና ባህል ከጥፋት መታደግ እንዲሁም ብሔረሰቡ አባት እንዲኖረው ለማስቻል ነው ብለዋል።

በበዓለ ሲመታቸው ላይ ንግግር ያደረጉት ሱልጣን መሀመድ አሽራዬ ሁሉንም አርጎባ በኩል አይን በማየት ከመንግስት እና ከሌሎች ብሔር ብሔረሰቦች ጋር በጋራ በመሆን እንደሚያገለግሉ አስታውቀዋል። (ድሬ ቲዩብ)

ሐረር ከተማ የዓለም የቅርስ ከተሞች አባል ሆነች።(ኢፍታን ኒውስ፤ ሓምሌ 05/2015 ዓ.ም -  አዲስ አበባ)በዩኔስኮ ዜጎች በሰላም፣ በመቻቻልና በአብሮነት የሚኖሩባት ከተማ በሚል እውቅና የ...
12/07/2023

ሐረር ከተማ የዓለም የቅርስ ከተሞች አባል ሆነች።

(ኢፍታን ኒውስ፤ ሓምሌ 05/2015 ዓ.ም - አዲስ አበባ)

በዩኔስኮ ዜጎች በሰላም፣ በመቻቻልና በአብሮነት የሚኖሩባት ከተማ በሚል እውቅና የተሰጣት ሐረር ከሰሃራ በታች ካሉ ከተሞች የመጀመሪያዋ የዓለም ቅርስ ከተሞች ድርጅት አባል ከተማ ሆና ተመዘገበች፡፡

የሐረሪ ክልል ርዕሰ መተዳድር ኦርዲን በድሪ በካናዳ ኩቢክ ከተማ ሐረር የዓለም የቅርስ ከተሞች አባል ሆና የተመዘገበችበትን ፊርማ አኑረዋል።

ሐረር ከተማ 115 ሀገራትን በአባልነት በያዘው የቅርስ ከተሞች ድርጅት ውስጥ የተመዘገበችው ከፈረንጆቹ ሰኔ ወር 2023 ጀምሮ ነው።

ሐረር ከቅርስ ከተሞች መካከል አንዷ ሆና መመዝገቧ በተማዋ ባህላዊና ታሪካዊ ቅርሶችን ለማልማት እና ለቱሪዝም ዘርፉ እድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ተገልጿል፡፡

የቅርስ ከተሞች በጋራ ጉዳዮቻቸው ተመካክረው አቅጣጫ በማስቀመጥ ተግዳሮቶችን ለመሻገርና እድሎችን ለማስፋት ይጠቅማል መባሉን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ መረጃ ያመላክታል፡፡

ሐረር ከተማ የጁገል ዓለም አቀፍ ቅርስን ጨምሮ በተባበሩት መንግስት የሳይንስ፣ የትምህርትና የባህል ተቋም (ዩኔስኮ) የተመዘገቡ ዓለም አቀፍ ቅርሶች መገኛ ከተማ መሆኗ ይታወቃል፡፡

በሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች ሰኔ 26/2015 ዓ.ም የተሰጠው የሬሜዲያል ፕሮግራም ፈተናዎች መሰረዛቸውን የትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡(ኢፍታን ኒውስ፤ ሰኔ 27/2015 ዓ.ም -  አዲስ አበባ)የ...
04/07/2023

በሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች ሰኔ 26/2015 ዓ.ም የተሰጠው የሬሜዲያል ፕሮግራም ፈተናዎች መሰረዛቸውን የትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

(ኢፍታን ኒውስ፤ ሰኔ 27/2015 ዓ.ም - አዲስ አበባ)

የ2014 ዓ.ም 12ኛ ክፍል ሬሜዲያል ተጠቃሚ ተማሪዎች ፈተና ትናንት ሰኔ 26 ቀን 2015 ዓ.ም በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት መሰጠት መጀመሩ ይታወቃል።

ይሁን እንጂ በፈተና ሂደት በተፈጠሩ ችግሮች ምክንያት የትምህርት ሚኒስቴር የሚከተሉትን ውሳኔዎች ማሳለፉን ገልጿል፡፡

1) ሰኔ 26 ቀን 2015 የተሰጡት የሬሜዲያል ፕሮግራም ፈተናዎች ተሰርዘው ተማሪዎች በቀሩት የትምህርት ዓይነቶች ብቻ እንዲመዘኑ

2) ቀደም ብሎ በሁሉም ሬሜዲያል ፕሮግራም ተጠቃሚ ተማሪዎች ባላቸው ተቋማት ፈተናውን በአንድ ጊዜ ለመስጠት የታቀደው ተሻሽሎ በተለይም ከ150 በላይ የሆኑና ከ200 በላይ ግቢ ያላቸውን የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፈተና ቀርቶ ወደ ፊት በሚወሰን አግባብ ፈተናው በመስከረም ወር 2016 ዓ.ም እንዲሰጥ

3) በመንግስት ተቋማት የሬሜዲያል ፕሮግራም ተጠቃሚ የሆኑትን ተማሪዎች በተያዘው ፕሮግራም መሰረት እንዲሰጥ ውሳኔ አሳልፏል።

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Eftan News posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Eftan News:

Share