Tổng đại lý vé máy bay 247

Tổng đại lý vé máy bay 247 Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Tổng đại lý vé máy bay 247, Churchil Avenue, Addis Ababa.

Shout out to my newest followers! Excited to have you onboard! Behailu Tadese, Teame WeldayWhat would you like to see mo...
20/08/2024

Shout out to my newest followers! Excited to have you onboard! Behailu Tadese, Teame Welday

What would you like to see more of from me?

06/04/2024

🌍🔴🌍🔴🌍🔴🌍🌍🔴🌍🔴🌍🔴🌍🔴🌍
-መሀመድ አያውቅም:
-ኢየሱስ... እንደ አምላክ... ሁሉን ያውቃል
-ኢየሱስ የዘላለምን ህይወት ይሰጣል:ስለዚህ ፈጣሪ ነው።
-በአለም ፍጻሜ ኢየሱስ የሚሽረው የአጋንንትን አለቅነትና ስልጣን ነው።

========

🌍መሀመድ አላውቅም እያለ ነው:-.

46:9:-

«ከመልክተኞች ብጤ የሌለኝ አይደለሁም፡፡ በእኔም በእናንተም ምን እንደሚሥሠራም አላውቅም፡፡ ወደእኔ የሚወረደውን እንጅ ሌላን አልከተልም፡፡ እኔም ግልጽ አስፈራሪ እንጅ ሌላ አይደለሁም» በላቸው፡፡

21:111:-

"እርሱም (ቅጣትን ማቆየት) ምናልባት ለእናንተ ፈተናና እስከ ጊዜው መጠቃቀሚያ እንደሆነም አላውቅም፤ (በላቸው)፡፡"

=====

🌍 ኢየሱስ.... እንደ አምላክ... ሁሉን ያውቃል:-

“ሁሉን እንድታውቅ ማንምም ሊጠይቅህ እንዳትፈልግ አሁን እናውቃለን፤ ስለዚህ ከእግዚአብሔር እንደ ወጣህ እናምናለን አሉት።”
— ዮሐንስ 16፥30
=====
🌍 ኢየሱስ በራሱ ለሰዎች ...የዘላለም ህይወትን የመስጠት ሀይል አለው:-

“እኔም የዘላለም ሕይወትን እሰጣቸዋለሁ፥ ለዘላለምም አይጠፉም፥ ከእጄም ማንም አይነጥቃቸውም።”
— ዮሐንስ 10፥28
🔴🔴🔴 ከፈጣሪ በቀር ለሰዎች የዘላለም ህይወትን መስጠት የሚችል ማን ነው?..ማንም የለም።ስለዚህ የማመልከው የዘላለም ህይወት የሚሰጠኝ ኢየሱስ ፈጣሪ ነው።
=====
🌍ኢየሱስ በአለም ፍጻሜ የሚሽረው አለቅነት እና ስልጣን የአምላክን ሳይሆን የሰይጣንን ነው።

የሰይጣን መንግስት አሁን ባለው ሁኔታ አለቅነትና ስልጣን አለው:-

“መጋደላችን ከደምና ከሥጋ ጋር አይደለምና፥ ከአለቆችና ከሥልጣናት ጋር ከዚህም ከጨለማ ዓለም ገዦች ጋር በሰማያዊም ስፍራ ካለ ከክፋት መንፈሳውያን ሠራዊት ጋር ነው እንጂ።”
— ኤፌሶን 6፥12

“በኋላም፥ መንግሥቱን ለእግዚአብሔር ለአባቱ አሳልፎ በሰጠ ጊዜ አለቅነትንም ሁሉና ሥልጣንን ሁሉ ኃይልንም በሻረ ጊዜ፥ ፍጻሜ ይሆናል።”
— 1ኛ ቆሮንቶስ 15፥24
===

25/02/2024
🌍 መጽሐፍ ቅዱስና " ተቃርኖዎች"  🌍--------------------------------------------------------------- 🌍 በየየለት የህይወት ዘገባዎችም ሆነ በመጽሐፍ ቅዱ...
11/02/2024

🌍 መጽሐፍ ቅዱስና " ተቃርኖዎች" 🌍
---------------------------------------------------------------
🌍 በየየለት የህይወት ዘገባዎችም ሆነ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ "ተቃርኖዎች" አሉ : ነገር ግን ተቃርኖ ሁሉ ሀሰት/ውድቅ/ አይደለም ። ...በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ላሉ ተቃርኖዎች መንስኤዎቹ የተለያዩ ናቸው። 🌍 ተቃርኖን በተመለከተ የተለያዩ እውነታዎች አሉ :: የሚከተለው አንድ እውነታ ነው:-
Oxymoron እየተባሉ የሚጠሩት ተቃርኖዎች በስነ ጽሑፍ ሆን ተብለው የሚገቡ ናቸው ። አላማውም ለስነጽሑፍ ውበት ለመስጠት ነው ።ምሳሌዎች :- Civil war,
absence presence( ከሼክስፒር ጽሑፎች)
*** በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በርካታ ኦክሲሞሮኖች አሉ : ለምሳሌ :- ዳግም ለመወለድ በመጀመሪያ መሞት (ሮሜ .6:17-23, ሮሜ.6:2-4)
*** የሰው ጥበብ ጨለማ መሆኑ (ማቴ .6:23, ኤፌ.4:18).....🌍 🌍 Paradox ሌላው የተቃርኖ አይነት ሲሆን ከኦክሲሞሮን የሚለየው በዐረፍተ ነገር በመነገሩ ነው :: ፓራዶክስ የሆኑ ነገሮች እርስ በርስ የሚቃረኑ / የሚቃረኑ የሚመስሉ/ ነገር ግን እውነት የሆኑ ዘገባዎች ናቸው ። paradox በስነጽሑፍ ሆን ተብሎ ይገባል :- ለምሳሌ:-
Not having a fashion is a fashion.
I must be cruel to be kind.
መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ካሉ የፓራዶክስ ምሳሌዎች መካከል እነዚህ ይጠቀሳሉ:- ራስን በማዋረድ መክበር : ያዕ 4:10, በድካም መበርታት: 2ኛ ቆሮ. 12:10::.....🌍 ሌሎች በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ያሉ ተቃርኖዎች : ታሪክን : ቋንቋን : እና አንዳንድ መንፈሳዊ እውነታዎችን ስናውቅ ...የሚታረቁ... ናቸው ።.....🌍 🌍 እንደዚሁም ደግሞ ሌሎች በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ አሉ የሚባሉ ተቃርኖዎች ...አንዳንድ የጥንት የመጽሐፍ ቅዱስ ገልባጮች ሲጽፉ ከሰሯቸው ስህተቶች የመነጩ ናቸው ።Textual Criticism የሚባለው ሳይንስ ስህተቶቹ የት የት ጋር እንደተሰሩ እና ትክክለኞቹ ንባቦች የትኖቹ እንደሆኑ በመለየት አስቀምጧቸዋል:: ከዚህ አኳያ የሚታዩት ተቃርኖዎች በዚህ መልኩ ይታረቃሉ ።..አንዳንድ ሙስሊም በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ያሉትን ተቃርኖዎች እየጠቀሰ.... በመጽሐፍ ቅዱስ ወጪ እስልምናን.... ለመስበክ ለመንቀሳቀስ ሲሞክር ይታያል :: ይህ ግን ስህተት ነው : ምክንያቱም በቁርአን ውስጥም ተቃርኖዎች አሉ : ይህ ቀጣዩ ሊንክ በቁርአን ያሉትን ተቃርኖዎች ይዘረዝራል :
ይጫኑት :-

3.አማኞችም እንደዚሁ ወደ ሲዖል ይገባሉ (71) ነው፡፡ ነገር ግን በአላህ ምህረት የተነሳ ከዚያ ይወጣሉ (72)፡፡

11/02/2024

ይህን ፔጅ Like ያድርጉ:ይማሩበታል
ክርስቲያኑም አለ:መለሰም ሊንክ:-
ሊንኩን ይጫኑት:-
https://www.facebook.com/chre8?mibextid=ZbWKwL

ይህ 'ፔጅ' በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ እና በክርስቲያናዊ አስተምህሮዎች ላይ ለሚነሱ ጥያቄዎች በመረጃ ላይ የተመሰረቱ መልሶችን ይሰጣል:

09/02/2024

🌺 ኢየሱስ ለአብ ይገዛል(1ኛ ቆሮ.15:28) የሚለው ግራ ይገባሀል? ☘️

🍀 መለኮት በመለኮታዊ ባህሪው 1 እንደሆነ ☘️ሆኖም በአካል 3 አንደሆነ ለሚያምን 🌴 ኢየሱስ ለአብ ይገዛል የሚለውን ለመረዳት ቀላል ነው።☘️ 🌼🌸🌺🌻💐መለኮት(Godhead) በመሠረታዊ ባህሪ (Essence) 1 እንደመሆኑ መጠን ገዢና ተገዢ የለውም🌺 ሆኖም መለኮት 🌸በአካል 3 እንደመሆኑ መጠን ወልድ እና መንፈስ ቅዱስ ፈቃዳቸው ወደ አብ ነው።☘️

☘️☘️ ይህ ....ምሳሌ ፍጹም ባይሆንም.... በመጠኑ ሊያብራራ ይችላል:- ባል እና ሚስት የሁለቱም ተፈጥሮ ("Essence")1 ነው= ሰዎች ናቸው።☘️

☘️ ነገር ግን የሚስት ፈቃድ ወደ ባል ነው።ሚስት ለባሏ የምትገዛውም በፍቅር ላይ ተመስርታ እንጂ የባል ተፈጥሮ ከሰው ውጪ መልዐክ ወይም ሌላ እንዳልሆነ ሁሉ ማለት ነው።☘️

13/01/2024

📜📜📜📜ሉሲፈር ( ሰይጣን) ....እና........666 እንቅስቃሴ ምንነት📜📜📜📜

በመጀመሪያ ሰይጣን :ወደ ሰይጣንነት ከመቀየሩ በፊት በሰማይ እግዚአብሔርን ከሚያገለግሉ እና "ኪሩብ" በመባል ከሚታወቁ የመላዕክት አይነት የሚመደብ ነበረ: ነገር ግን ክፋት :ሀጢአትና አመጽ ከተገኘበት ጊዜ ጀምሮ ሁኔታዎች ተቀይረው "ሰይጣን" ስለሆነ በውስጡ እግዚአብሔር ያስቀመጠው "እሳት" ወጥቶ እንዲበላው ተደርጎ ወደ ምድር ተጥሏል:-

ሕዝቅኤል 28፥16

“በንግድህ ብዛት ግፍ በውስጥህ ተሞላ ኃጢአትንም ሠራህ፤ ስለዚህ እንደ ርኩስ ነገር ከእግዚአብሔር ተራራ ጣልሁህ የምትጋርድ ኪሩብ ሆይ፥ ከእሳት ድንጋዮች መካከል አጠፋሁህ።”
— ሕዝቅኤል 28፥16

📜እዚህ ህዝቅኤል 28 ላይ እግዚአብሔር ...የጢሮስ ንጉስ ውስጥ... ስለነበረው ክፉ መንፈስ (ሰይጣን) እየተናገረ ነው።📜በምዕራፉ ውስጥ አንዳንድ ነገሮች የጢሮስን ንጉስ የሚመለከቱ ቢኖሩም አብዛኛው ግን ውስጡ የነበረውን መንፈስ:ሰይጣንን የሚመለከት ነው።📜በመጽሐፍ ቅዱስ ያሉ ትንቢቶች በአብዛኛው እንደዚህ ናቸው:"በአንድ ድንጋይ ሁለት ወፍ"እንደሚባለው።ለምሳሌ: በኤደን ገነት ነበርህ ይለዋል(ቁጥር 13):ይህ በቀጥታ ሰይጣንን የሚመለከት ነው።"የምትጋርድ ኪሩብ" ይለዋል(ቁጥር 16)።ይህም የጢሮስን ንጉስ ሳይሆን በቀጥታ ሰይጣንን የሚመለከት ነው።

📜ሰይጣን: "ሰይጣን" ከመሆኑ በፊት በሰማይ "አጥቢያ ኮከብ" የሚል ስም ነበረው:-

“አንተ የንጋት ልጅ አጥቢያ ኮከብ ሆይ፥ እንዴት ከሰማይ ወደቅህ! አሕዛብንም ያዋረድህ አንተ ሆይ፥ እንዴት እስከ ምድር ድረስ ተቈረጥህ!”
— ኢሳይያስ 14፥12

📜ሰይጣን ከእግዚአብሔር በላይ እሆናለሁ ብሎ በማሰቡ ከባድ ሀጢአት ወደ "ሰይጣን"ነት ተቀየረ:-

ኢሳይያስ 14
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹³ አንተም በልብህ፦ ወደ ሰምይ ዐርጋለሁ፥ ዙፋኔንም ከእግዚአብሔር ከዋክብት በላይ ከፍ ከፍ አደርጋለሁ፥ በሰሜንም ዳርቻ በመሰብሰቢያ ተራራ ላይ እቀመጣለሁ፤
¹⁴ ከዳመናዎች ከፍታ በላይ ዐርጋለሁ፥ በልዑልም እመሰላለሁ አልህ።
¹⁵ ነገር ግን ወደ ሲኦል ወደ ጕድጓዱም ጥልቅ ትወርዳለህ።

📜ክፋትን የጀመረው ሰይጣን ነው (ሕዝቅኤል 28:15)።

📜ሰይጣን ሐሰትን ነው የሚናገረው:የዚያም ሀሰት ምንጭ እራሱ ነው:-

“እናንተ ከአባታችሁ ከዲያብሎስ ናችሁ የአባታችሁንም ምኞት ልታደርጉ ትወዳላችሁ። እርሱ ከመጀመሪያ ነፍሰ ገዳይ ነበረ፤ እውነትም በእርሱ ስለ ሌለ በእውነት አልቆመም። ሐሰትን ሲናገር ከራሱ ይናገራል፥ ሐሰተኛ የሐሰትም አባት ነውና።”
— ዮሐንስ 8፥44

📜ሰይጣን ነፍሰ ገዳይ ነበረ:ነውም:-

“እናንተ ከአባታችሁ ከዲያብሎስ ናችሁ የአባታችሁንም ምኞት ልታደርጉ ትወዳላችሁ። እርሱ ከመጀመሪያ ነፍሰ ገዳይ ነበረ፤ እውነትም በእርሱ ስለ ሌለ በእውነት አልቆመም። ሐሰትን ሲናገር ከራሱ ይናገራል፥ ሐሰተኛ የሐሰትም አባት ነውና።”
— ዮሐንስ 8፥44

📜📜📜📜📜📜📜📜📜📜📜
የ666 (የሰይጣን አባላት) እንቅስቃሴ ጉዳይ

📜📜666 በመጽሐፍ ቅዱስ የሰይጣን(አውሬው ቁጥር)እንደሆነ ተነግሮናል:-

“አእምሮ ያለው የአውሬውን ቍጥር ይቍጠረው፤ ቍጥሩ የሰው ቍጥር ነውና፥ ቍጥሩም ስድስት መቶ ስድሳ ስድስት ነው።”
— ራእይ 13፥18

📜የሰይጣን አባላት ገንዘብ እንሰጣችኋለን ማታለያ እና ህይወትን ለሰይጣን የመግዛት ስራ:-

📜ሲጀመር ሰይጣን (ሉሲፈር) ይወስድብሀል እንጂ (ህይወትህን ጭምር )ምንም አይሰጥህም።

📜የሰጠህ ቢመስልሀ እንኳ ...ሀሰት...ነው።አዕምሮህ ከሰይጣን ቁጥጥር ውጪ ስለማይሆን ...1,000,000... ሰጠሁህ ቢልህ ከውስጡ... 1 ...ብር ያለ ሰይጣን ፈቃድ መጠቀም
ስለማይቻል የሰይጣን ብር ዘበኛ ነው የምትሆነው።

📜የሰይጣን ምግብ የሰው ደም እና ስጋ ነው።📜ሰዎችን የሚመለምሉት ለሰይጣን ምግብነት ነው። አንዴ ከገባህ እንደው ከፍተኛ ተአምር ካልሆነ በስተቀር አትወጣም:ሰይጣን አባላቱን ያርዳል:ይገላል።ሰይጣን በሰዎች ደካማ ጎን መግባትን ስለሚያውቅ የብር ጉዳይ ነው ርዕሱ........ሆኖም ለማኝ ሆኖ ኖሮ ቢሞት እንኳን አንድ ሰው በምድር የህይወት ነጻነቱን በሰማይ ደግሞ ህይወቱን ያተርፋል።📜

📜የ666 አባላት ነን የሚሉ ሰዎች ሰይጣን አታላይ ስለሆነ ከባድ ማጭበርበር ይፈጽማሉ: ለምሳሌ አባል ከሆናችሁ ከፍተኛ ብር እንሰጣለን ይላሉ:ብሩም እንደተላከ የሚያስመስል ሜሴጅ እንደደረሰም ፎቶ ያሳያሉ።ሆኖም ይህ ባብዛኛው የማጭበርበር ስራ ነው:ስልክ ላይ በሀሰት ለሌላ ሰው በባንክ በኩል ብር እንደገባ አስመስሎ የሚሰራ ሶፍትዌር አለ ይባላል።በዚያ ኤዲት ከዚያም ስክሪንሾት ያደርጉና ይልኩታል።📜አባል መሆን የሚፈልገው ሰው የሚልከው ገንዘብ ትክክለኛ ብር ሲሆን እነርሱ የሚልኩት የሀሰትና የተጭበረበረ መረጃ ነው።📜ካሽ ከሆነም ብዛት ያላውወ ፎርጅድ ብሮች ናቸው።📜በተጨማሪም አባላቶቹ እርስ በርስ ሜሴጅ እየተላላኩ እና ስክሪን ሾት እያደረጉ ለሌላው ሰው በመላክ ያታልሉበታል።

📜 እንዲያው ለነገሩ ግን የሚላከው ገንዘብ ትክክለኛ ቢሆን እንኳን ....የሰይጣን ብር እስከሆነ ድረስ....... የሚላክለት ግለሰብ ገንዘብን አይጠቀምበትም:የተወሰነ ቢጠቀምም ከትንሽ ጊዜ በኋላ ለሰይጣን ምግብ በመሆን ህይወቱን ያጣል:ይታረዳል።

📜የሰይጣን አባላት :666 :በሚስጥር የሰው መስዋዕት ያደርጋሉ።📜አባል የሆነ ሰው ነጻ ህይወት የለውም:24 ሰአት በሰይጣን እና በአባላቱ ከፍተኛ ቁጥጥር ይደረግበታል።📜 አባል የሆነ ሰው ከዚያ የሰይጣን ህብረት መውጣት አይችልም:እወጣለሁ ካለ ወዲያው ይገደላል።📜ትንሽ እንኳ የማምለጥ ዕድል ያለው በከፍተኛ ፍጥነት የጸሎት ቦታ ሄዶ ከሰይጣን ቁጥጥር ነጻ መሆን የሚችል ሰው ነው።

📜በአለም መጨረሻ ሰይጣን ወደ እሳት ባህር (ገሀነም) ነው የሚጣለው: ተከታይ ሰዎችም በሙሉ እንዲሁ :-
“በዚያን ጊዜ በግራው ያሉትን ደግሞ ይላቸዋል፦ እናንተ ርጉማን፥ ለሰይጣንና ለመላእክቱ ወደ ተዘጋጀ ወደ ዘላለም እሳት ከእኔ ሂዱ።”
— ማቴዎስ 25፥41

📜የሰይጣን አባላት ዋና ጠላታቸው ትክክለኛ የኢየሱስ ክርስቶስ ቃል እና ሀይል ያለበት የጸሎት ቦታ ነው።📜ስለዚህም የጌታ ...ቃል እና....የመንፈስ ቅዱስ ሀይል....ያለበት ስፍራ ላይ ፍተኛኛ ጦርነት ይከፍታሉ።

10/01/2024

ሙስሊሞችን በገነት የሚጠብቋቸው
"72 ደናግላን" :...እና "100 እጥፍ ሚስት" በመጽሐፍ ቅዱስ ?

📜ቁርአን በሰማይ ይጠብቋችኋል ብሎ ከሰጠው ተስፋ መሀል ...."አልጋዎች" ...እና...ቆንጆ ሴቶች...መኖራቸውን ያውቁ ኖሯል?

📜
📜📜📜📜📜📜📜📜📜📜📜

📜 ጽሁፉን ለመጀመር ያህል መጽሐፍ ቅዱስ በሰማይ... ጋብቻ... እንደሌለ... ነው የሚነግረን:-

“በትንሣኤስ እንደ እግዚአብሔር መላእክት በሰማይ ይሆናሉ እንጂ አያገቡም አይጋቡምም።”
— ማቴዎስ 22፥30

📜 መጽሐፍ ቅዱስ ከዚህ አለም በኋላ ሰዎች "እንደ መላዕክት" እንደሚሆኑ ነው የሚነግረን:እናም ስጋዊ አካል ስለሌለ መጋባት የለም።

📜በሰማይ ያሉ መላዕክት "መናፍስት"(ዕብ.1:13-14) ናቸው ...ስጋና እና አጥንት ....የላቸውም(ሉቃ.24:39):-

“እኔ ራሴ እንደ ሆንሁ እጆቼንና እግሮቼን እዩ፤ በእኔ እንደምታዩት፥ መንፈስ ሥጋና አጥንት የለውምና እኔን ዳስሳችሁ እዩ አላቸው።”
— ሉቃስ 24፥39

ዕብራውያን 1
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹³ ነገር ግን ከመላእክት፦ ጠላቶችህን የእግርህ መረገጫ እስካደርግልህ ድረስ በቀኜ ተቀመጥ ከቶ ለማን ብሎአል?
¹⁴ ሁሉ መዳንን ይወርሱ ዘንድ ስላላቸው ለማገዝ የሚላኩ የሚያገለግሉም መናፍስት አይደሉምን?

📜“ከሙታንስ ሲነሡ በሰማያት እንዳሉ መላእክት ይሆናሉ እንጂ አያገቡም፥ አይጋቡምም።”
— ማርቆስ 12፥25

📜📜📜📜📜📜📜📜📜📜

📜📜📜ሙስሊሞች መጽሐፍ ቅዱስ በሰማይ "መቶ እጥፍ" ሚስቶች ይጠብቋችኋል ይላል በማለት የሚያራግቡት ጉዳይ ....ሀሰት...ሲሆን ሀዲሳቸው 72 ደናግላን በሰማይ ይጠብቋችኋል ብሎ የሰጠው ተስፋ ላይ ለሚቀርብባቸው ትችት ...አዲስ የጀመሩት...አቅጣጫ ማስቀየሪያ ንግግር ነው።

📜 "መቶ እጥፍ" ....ዘይቤያዊ አገላለጽ ነው።

📜በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እጅግ ብዙ... ዘይቤያዊ አገላለጾች (ተዘዋዋሪ እንጂ ቀጥታ ትርጉም የሌላቸው)...... ሲኖሩ ከእነዚህም አንዱ ..."መቶ እጥፍ"... ነው።
..ምሳሌ ጥቅሶች:-

📜📜ይስሐቅም በዚያች ምድር ዘርን ዘራ፥ በዚያች ዓመትም መቶ እጥፍ አገኘ እግዚአብሔርም ባረከው።”
— ዘፍጥረት 26፥12

📜📜“ሌላውም በመልካም መሬት ላይ ወደቀ፤ በበቀለም ጊዜ መቶ እጥፍ አፈራ። ይህን በተናገረ ጊዜ፦ የሚሰማ ጆሮ ያለው ይስማ ብሎ ጮኸ።”
— ሉቃስ 8፥8

📜📜📜እነዚህ ሁለት ንባቦች እርሻን በተመለከተ "መቶ እጥፍ" ሲሉ ...እጅግ ብዙ...ለማለት እንደ ሆነ ግልጽ ነው።

📜📜“ስለ ስሜም ቤቶችን ወይም ወንድሞችን ወይም እኅቶችን ወይም አባትን ወይም እናትን ወይም ሚስትን ወይም ልጆችን ወይም እርሻን የተወ ሁሉ መቶ እጥፍ ይቀበላል የዘላለምንም ሕይወት ይወርሳል።”
— ማቴዎስ 19፥29

📜 ቁርአን በሰማይ ገነት ..."አልጋዎች"..ሙስሊሞችን እንደሚጠብቋቸው የገለጸ ሲሆን አልጋዎቹም ..."አጎበር"...ያላቸው መሆኑን ይናገራል:-

18:31:-

"እነዚያ ለእነሱ የመኖሪያ ገነቶች ከሥሮቻቸው ወንዞች የሚፈሱባቸው አሏቸው፡፡ በእርሷ ውስጥ ከወርቅ የኾኑን አንባሮች ይሸለማሉ፡፡ ከቀጭን ሐርና ከወፍራም ሐርም አረንጓዴን ልብሶች ይለብሳሉ፡፡ በውስጧ በባለ አጎበር አልጋዎች ላይ የተደገፉ ኾነው (ይቀመጣሉ)፡፡ ምንዳቸው ምን ያምር! መደገፊያይቱም ምንኛ አማረች!"

📜በተጨማሪም ቁርአን በሰማይ ሙስሊሞችን የሚጠብቁ ..."ነጫጭ ሴቶች...እንዳሉ ይናገራል:

52:20:-

"በተደረደሩ አልጋዎች ላይ ተደጋፊዎች ኾነው (በገነት ይኖራሉ)፡፡ ዓይናማዎች በኾኑ ነጫጭ ሴቶችም እናጠናዳቸዋለን፡፡"

📜 📜📜አልጋዎችና ሴቶች በገነት ይጠብቋችኋል ከሚሉት የቁርአን አንቀጾች የምንረዳው....እንደ እስልምና አስተምህሮ...በሰማይ ልክ እዚህ በምድር እንዳለው አይነት...የወንድና የሴት...ግንኙነት እንዳለ ነው።ስለዚህም
72 ደናግላን እንደሽልማት በገነት ይጠብቋችኋል የሚለው የሚስሊሞች ሀዲስ እላይ ካየናቸው ...የቁርአን አንቀጾች አንጻር ...ቃል በቃል...የተጻፈ እንጂ ዘይቤያዊ ትርጉም የለውም።
📜ሆኖም ሙስሊሞች አሁን አሁን 72 ደኛግላን ይጠብቋችኋል የሚለውን ሀዲስ ዴኢፍ (ተቀባይነት የሌለው) ማለት ጀምረዋል።...እኛ እንዳሉት ይህን ሀዲስ ችላ ብንለው እንኳን...ቁርአን ቃል በቃል..በሰማይ ገነት ....አልጋዎችና ሴቶች...እንደሽልማት ለሙስሊሞች እንደሚቀርቡ የተናገረባቸው አንቀጾች ስላሉ ....የቁርአን(መሀመድ ገነት) ...ከአልጋዎችና ሴቶች...ውጪ ሊሳል እንደማይችል ማረጋገጥ ይቻላል።

በጉዳዩ ላይ ተጨማሪ የቁርአን አንቀጾች:-

📜36:56:-

"እነርሱም ሚስቶቻቸውም በጥላዎች ውስጥ ናቸው፡፡ ባለ አጎበር አልጋዎች ላይ ተደጋፊዎች ናቸው፡፡"

📜37:44:-

ፊት ለፊት የሚታያዩ ሲሆኑ በአልጋዎች ላይ (ይንፈላሰሳሉ)፡፡

📜56:15:-

በተታቱ አልጋዎች ላይ ይኾናሉ፡፡

📜76:13:-
ا
"በውስጧ በባለ አጎበር አልጋዎች ላይ ተደጋፊዎች በውስጧ ፀሐይንም ጨረቃንም የማያዩ ሲኾኑ፡፡"

📜83:23:-

"በባለ አጎበር አልጋዎች ላይ ኾነው ይመለከታሉ፡፡"

📜83:35:-

"በባለ አጎበር አልጋዎች ላይ ኾነው የሚመለከቱ ሲኾኑ (ይስቃሉ)፡፡"

📜88:13:-

"በውስጧ ከፍ የተደረጉ አልጋዎች አልሉ፡፡"

📜📜📜የቁርአንን እና የመሀመድን ገነት ...ያለ አልጋዎችና ሴቶች ...ማሰብ አይቻልም።📜📜📜

📜...እና እኛም እንጠይቃለን ...በገነት ...ባለ አጎበር አልጋ ...አለ የሚለው ቁርአን ቀጥታ ከሰማይ የወረደ የአምላክ ቃል ነው? አጎበር በዋናነት ወባ በሽታ እና ሌሎች ትንኞች መከላከያ መሆኑን እናስታውስ።
...

ሀይማኖታዊ ንጽጽር ...3📜 "ሰው ሁሉ ሲወለድ ሙስሊም" ነው  ? እና ጥምቀት እንዲሁም ሌሎች ተያያዥ ርዕሰ-ነገሮች📜📜📜📜📜📜📜📜📜📜📜📜📜📜📜"ሰው ሁሉ ሲወለድ ሙስሊም ነው" የሚለው ንግግር ሀ...
01/01/2024

ሀይማኖታዊ ንጽጽር ...3

📜 "ሰው ሁሉ ሲወለድ ሙስሊም" ነው ? እና ጥምቀት እንዲሁም ሌሎች ተያያዥ ርዕሰ-ነገሮች
📜📜📜📜📜📜📜📜📜📜📜📜📜📜

📜"ሰው ሁሉ ሲወለድ ሙስሊም
ነው" የሚለው ንግግር ሀሰት ነው ምክንያቱም: ሀይማኖት... .ከእምነት.. ብቻ ሳይሆን .... ከዕውቀትም ...ጋር የተገናኘ ነው።📜📜

📜ይሁንና ዕውቀትን ለጊዜው እረስተን ስለ እምነትና ተአምር ብናወራ እንኳን ሰው እንደተወለደ ሙስሊም ተደርጎ በተአምር የሚፈጠር ከሆነ ህጻናት እንደተወለዱ ከመጮህ ይልቅ ለምን ....በአምላክ ተአምር...."አላህ አክበር" በማለት አይናገሩም?
📜ስለ ተመሳሳይ ነገር ስናወራ ኢሳ (ኢየሱስ) በህጻንነቱ በአላህ ተአምር እንደተናገረ በቁርአን ተጽፏል:(3:46):- «በሕፃንነቱና በከፈኒሳነቱ ሰዎቹን ያነጋግራል፡፡ ከመልካሞቹም ነው» (አላት)፡፡

📜ሀይማኖት ስንል የአይሁድ ሀይማኖት :ክርስቲያን: ሙስሊም:ሂንዱ:ቡዲዝም ወዘተ ማለታችን ነው።

📜ገና የተወለዱ ወይም ትንሽ ሳምንታት ያስቆጠሩ ህጻናት እናቶቻቸው ካለማመዷቸው ፈልገው መጥባትን ከመሳሰሉ ያለፈ ልምምድ የተገኘ ዕውቀት አይኖራቸውም።ህጻናት ከፍ እያሉና እያደጉ ሲመጡ ስለ ነገሮች ያላቸው እምነት እያደገ ይመጣል:ደግሞም ከአካባቢያቸው ከሚሰሙት እና ከሚያዩት እንዲሁም ከሚነካኩት ነገር እየተለማመዱ: እየተማሩ እውቀት እያገኙ በዕውቀት እያደጉ ይመጣሉ።📜ሀይማኖት ምን እንደሆነ የሚያውቁት ያን ጊዜ ነው።

📜እምነትና እውቀት የተያያዘ ነው።ስለ አንድ ነገር ...አውቀህ ልታምን... ትችላለህ:ለምሳሌ ሰዎች ማርስ የምትባለው ፕላኔት ላይ ስፔስ ክራፍት ማሳረፋቸውን የሚያሳይ ትክክለኛ ቪዲዮ ካየህ በኋላ ...በማወቅህ... ይህ ነገር በሰው ልጅ አቅም የተቻለ መሆኑን ....ታምናለህ.....።

📜ወይም ስለ አንድ ነገር ከውጤቱ አስቀድመህ ....በማመንህ... ቀጥሎ ስለዚያ ነገር በዝርዝር ...ልታውቅ... ትችላለህ።ለምሳሌ:መንጃ ፈቃድ ልታወጣ እንደምትችል እና ሹፌር ልትሆን እንደምትችል አስቀድመህ ...ታምናለህ:....ከዚያም የመንጃ ፈቃድ ትምህርት ዕውቀት እና ልምምድ ይኖርህና መኪና እንዴት ማሽከርከር እንዳለብህ ...ታውቃለህ።

📜እምነትና እውቀት ባብዛኛው ተያያዥ ናቸው።አንዱ ሌላውን እየቀደመም ይመጣል።ሀይማኖተኛ ለመሆን
እውቀትና እምነት ሁለቱም አብረው መገኘት አለባቸው።📜📜📜የሰው ልጅ ሲወለድ እምነት አብሮ ይፈጠራል (ያ ሀይማኖት አይደለም):ህጻኑ ሲያድግም ስለ ነገሮች ያለው እምነት እያደገ ይሄዳል።📜📜📜

📜ህጻናት ሀይማኖት ካላቸው ወላጆች ሊወለዱ ይችላሉ ነገር ግን አድገው ክፉና ደግ እስከሚለዩ ድረስ.... ሀይማኖታቸው.... ይህ ነው ማለት አይቻልም።ገና የተወለዱ ህጻናት ስለሀይማኖትም ይሁን ስለማንኛውም ነገር ያውቃሉ ብለን መናገር ብንጀምር የሚያስቅ ነገር ከመሆን የዘለለ አይሆንም።

📜እምነት ከሀይማኖት ጋር ብቻ የተያያዘ እንዳልሆነ እናውቃለን:ታክሲ ተሳፍረን የምንከፍለው የምንፈልገው ቦታ እንደሚያደርሰን ስለምናምን ነው:ስራ ተቀጥረን የምንሰራው ደሞዝ ይከፈለናል ብለን ስለምናምን ነው:ቤት የምንሰራው እንኖርበታለን ብለን ስለምናምን ነው እና ወዘተ።እንደዚህ አይነት ብዙ እምነቶቻችንን መጠቃቀስ እንችላለን።

📜እነዚህ እምነቶቻችን ናቸው።ነገር ግን እነዚህ እምነቶቻችን ሀይማኖቶቻችን አይደሉም።

📜በነዚህና በመሳሰሉ ነገሮች እንድናምን የሚያደርገን እምነት የተገኘው በህይወት ከአካባቢያችን ልምምድ እና በተፈጥሮ አብሮን ከተፈጠረ እምነት ነው።

📜📜📜📜ሰው ሲፈጠር በነገሮች ሊያምን የሚይል ፍጡር ተደርጎ ነው :ነገር ግን እንደተወለደ ሀይማኖት ይዞ አይወለድም።ስለዚህም ሰው ሲወለድ ሙስሊም ነው ማለት ግዙፍ ውሸት ነው።📜📜📜📜

📜ህጻናትን የሚያጠምቁ ክርስቲያን ቤተሰቦች ህጻናትን ሲያጠምቁ በጥምቀት እነርሱ ወላጆች አምነው...ለእግዚአብሔር ይለዩታል/ይሰጡታል/ ።ይህ ከወላጆች እምነት አንጻር ነው።ወላጆች በእምነታቸው መሠረት ለክርስቲያንነት ለእግዚአብሔር ለየነው ይላሉ።ከህጻኑ እምነት አንጻር:ህጻን በመሆኑ ምክንያት ስለዚያ ሀይማኖታዊ ጥምቀት ምንም የሚያምነው እና የሚያውቀው ነገር የለም።

📜 ያልተጠመቀና ክርስቲያን ያልሆነ ሁሉ ሀይማኖቱ የግድ ሙስሊም ነው?

አንዳንድ ሙስሊም እንደዚህ ይታለላል።ሆኖም አንድ ሰው የክርስትናን እምነት ሳያምንና ሳይጠመቅ ቢሞት : በዚህ ሀይማኖት ሳይጠቃለል ሞተ: ማለት እንጂ የግድ ሙስሊም ነበር ማለት አይደለም።እንዲህ አይነት ሰው ሀይማኖት አልባ ወይም በሆነ ባዕድ አምልኮ የሚያምን ሊሆን ይችላል።📜የክርስቲያን ቤተሰብ ህጻናት ቢጠመቁም ባይጠመቁም ከፍ እስከሚሉ እና ነፍስ እስከሚያውቁ ድረስ ስለሀይማኖት የሚያውቁት ነገር የላቸውም።📜ህጻናት ሳይጠመቁ ቢሞቱ ያው ሳይጠመቁ/ቤተሰቦቻቸው ....ለእግዚአብሔር... ሳይለዩአቸው ...ሞቱ ማለት እንጂ "ሙስሊም ነበሩ/ሀይማኖታቸው ሙስሊም ነበር ብሎ መናገር ከተራ ቀልድ ያለፈ አይሆንም።

📜📜ሌላው በሙስሊሞች የሚቀርበው ንግግር እስልምና ማለት "መሰጠት"/መታዘዝ/ ስለሆነ በመጽሐፍ ቅዱስ የተጠቀሱት የጥንት ነብያት ሁሉ ሙስሊሞች ናቸው የሚል ነው።ቁርአንም በመጽሐፍ ቅዱስ የተጠቀሱት ነብያት ሙስሊሞች ነበሩ ይላል:ለምሳሌ አብርሃም/ኢብራሂም/ :3:67። 📜ይህ ሀሰት እና የመጽሐፍ ቅዱስ ነብያትን ወደ እስልምና የመስረቅ ዘዴ ነው።📜 ማስረጃዎች ቢያስፈልጉ:-

2.1 መታዘዝ የሚለው ቃል እና ጽንሰ ሀሳብ የእስልምና ሀይማኖት ከመታወቁ ብዙ አመታት በፊት በመጽሐፍ ቅዱስ ተመዝግቦ ይገኛል:(ዘዳ.27:10,ዘዳ.30:2 ,ኢሳ.1:19,)ስለዚህ እውነታው የእስልምና ሀይማኖት ይህን የመታዘዝ ጽንሰ ሀሳብ ከመጽሐፍ ቅዱስ መውሰዱ እና የራሱ ...ብቻ...አድርጎ ለማሳየት መሞከሩ ነው።📜ይህን የሀሰት ንግግር በሌላ ምሳሌ ብናየው እኔ ጋርም ሌሎች ሰዎች ጋርም ያለን አንድ ነገር ....የኔ መለያ ብቻ ...አድርጎ መቁጠር ማለት ነው።📜"መታዘዝ" የመጽሐፍ ቅዱስ :የአይሁድ እንዲሁም የክርስትና ሀይማኖት መለያ ነው።ለነገሩ የትኛውም አምልኮ መታዘዝን ይፈልጋል። ለምሳሌ በመጽሐፍ ቅዱስ የተዘረዘሩት 10ቱ ትዕዛዛት አላማቸው ያው መታዘዝ እንደሆነ ግልጽ ነው(ዘጸ.20)።📜በመጽሐፍ ቅዱስ እግዚአብሔር ስለ መታዘዝ ነው ለነብያት በዋናነት ሲናገር የነበረው።ክርስቶስ በፍቅር እንድንታዘዘው ይፈልጋል(ማር.12:30)
ያለበለዚያ የእርሱ ነን ብንል ትርጉም የለውም።
📜📜መታዘዝ ከሚለው ቃል ጋር አብሮ ለአንድ አምላክ የሚለውን አብረን ብናየው.....ለአንድ አምላክ መታዘዝ እና.... አንድ አምላክን ማምለክ....በመጀመሪያ የተጠቀሰው በመጽሐፍ ቅዱስ ነው (ዘዳ.6:4)።📜በመጽሐፍ ቅዱስ የተጠቀሰው አንድ አምላክን ማምለክ ማለት የእስልምና ሀይማኖት ማለት አይደለም።እንደ ዘዳ.6:4ን የመሳሰሉ ጥቅሶች በተጻፉ ወቅት(የዛሬ 3,400 አመታት አካባቢ) የእስልምና ሀይማኖት ሽታውም አልነበረም።📜በነዚያ ዘመናት ከሀይማኖት ጋር አቻ የሆነ ስም ለመጥቀስ ቢያስፈልግ "ሙሴ"(የታላቁን መሪ ስም) የሚለውን ቃል መጠቀም ይቻላል።📜የጥንት ነብያት በእነዚያ ጊዜያት የነበረውን የአምልኮ ስርአት የ"ሙሴ" በማለት ይጠሩት ነበር (ነህምያ 1:7)።ኢየሱስ ክርስቶስ በብሉይ ኪዳን የነበረውን የአምልኮ ስርአት በአጠቃላይ" ሙሴና ነብያት" በማለት ያመለክት ነበር(ሉቃ.16:31)።"ሙሴና ነብያት" የሚለውን ከሀይማኖት ስም አቻ አድርጎ ማየት ይቻላል።📜የጥንት የአለም ታሪክን ብንመለከት በብሉይ ኪዳን በተለይ ከንጉስ ሰለሞን ሞት በኋላ ዘሮቻቸው በሌሎች ዘንድ "አይሁድ" እየተባሉ ይጠሩ ስለነበር (አስቴር 3:6) የ"ሙሴና ነብያትን" እምነት የሚከተሉ የአይሁድ ሀይማኖት ተከታዮች እየተባሉ ይጠሩ ነበር።ይህ በመጽሐፍ ቅዱስም ከመጽሐፍ ቅዱስ ውጪም ባሉ የጥንት መጽሐፍት ይታወቃል።📜ቀጥሎም ከክርስቶስ ጋር ተያይዞ በኋላ የክርስትና እምነት ተመሰረተ።📜የእስልምና ሀይማኖት የተመሠረተው ከክርስቶስ ልደት በኋላ በ570 ዓ.ም በተወለደው በመሀመድ ነው።እውነታው ይህ ቢሆንም ሙስሊሞች እና ቁርአን እስልምና ቀድሞም በጥንት የመጽሐፍ ቅዱስ ነብያት ዘመን እንደነበር ይናገራሉ:ሆኖም እላይ ካልናቸው ነጥቦች በተጨማሪ ከእስልምናው መስራች መሀመድ በፊት የእስልምና ሀይማኖት ስለመኖሩ የሚያረዳ አንድም አርኪዮሎጂያዊ/የስነ ምድር ቁፋሮ/ ግኝት የለም።የተገኙት የስነ ምድር ቁፋሮ ማስረጃዎች በጥንት ዘመን በርካታ አይነት አምልኮዎችን ያሳያሉ።ስለ እስልምና አጀማመርም ከመሀመድ ልደት በኋላ ያለው ነው። እውነታው

📜ይህን ጉዳይ ("መታዘዝ"/"መሰጠት") እስልምና ነው የሚለውን ንግግር/) እንደ ሙስሊሞች አስተሳሰብ/logic/ ብንወስደው ከጥንት ዘመን ጀምሮ በሜሶጶታሚያ:ባቢሎኒያ:ግብጽ:ግሪክ:ህንድ:ከነአን:ኢራን:መካ:እና ሌሎችም አካባቢዎች በርካታ የጣዖት አምልኮዎች እንደነበሩ የአርኪዮሎጂ ሳይንስ ያስረዳል።አምላኪዎቹም ለጣዖቶቹ ..
መታዘዝ/መሰጠት/ የግድ ነበረባቸው:..እና የመታዘዝ ጽንሰ ሀሳብ በመኖሩ እንደሙስሊሞች እምነት እነዚያ የጣዖት አምልኮዎች እስልምና ነበሩ ማለት ነው።

📜በተጨማሪም በመጽሐፍ ቅዱስ የነበሩ ነብያት ኢየሱስን ጨምሮ ሙስሊም ነበሩ የሚለውን የሙስሊሞች ንግግር ውድቅ የሚያደርገው ዛሬ ሙስሊሞች ለእምነታቸው የሚጠቀሟቸው የግማሽ ጨረቃ እና የኮከብ ምልክቶች ናቸው።📜📜አንድም የመጽሐፍ ቅዱስ ነብይ ለእምነቱ ምልክት ግማሽ ጨረቃ እና ኮከብን አልተጠቀመም።📜 📜ግማሽ ጨረቃንና ኮከብን ስለተጠቀመ የመጽሐፍ ቅዱስ ነብይ በመጽሐፍ ቅዱስ አናነብም:በአርኪዮሎጂ/ስነ ምድር ቁፋሮም/ሳይንስም አልተገኘም።

📜በተቃራኒው ግን በጥንት ዘመን የነበሩ ....የተለያዩ የጣዖት አምልኮዎች የጨረቃን እና የኮከብ ምልክትን እንደ አምላክ ...ተጠቅመውባቸዋል።
📜ይህም የሚያሳየው እስልምና 🕋ከጣዖት አምልኮ ጋር እጅጉን የተዛመደ መሆኑን ነው:-

📜📜 ከጨረቃ ጋር የተያያዘ አምልኮ

የእስልምና አምነት ከጨረቃ እና ኮከብ ጋር እጅጉን የተቆራኘ ነው።የሙስሊም እምነት አምልኮ እና መገለጫ
ከሆኑት ጨረቃና ኮከብ ጋር የተያያዙ በጥንት ዘመን በርካታ የጣዖት አምልኮዎች ነበሩ:- ለምሳሌ
1. ናና/ሲን/ሱኤን/ በመባል ይታወቅ የነበረው የጥንት ሜሶጴታሚያ /ሱሜር/አካድ/አሲሪያ/ባቢሎኒያ/አራም/ ህዝቦች የጨረቃ አምላክ የነበረ ሲሆን መለያው የአሁኑ የሙስሊሞች እምነት ምልክት ...ግማሽ ጨረቃ(Crescent moon) ነበር
2. ኮንሱ: የጥንት ግብጻውያን የጨረቃ አምላክ ሲሆን ራሱ ላይ ሙሉ ጨረቃ እና
የግማሽ ጨረቃ ምልክት ነበረበት
3.የጥንት ግሪክች የጨረቃ አምላክ ሰሊኔ በመባል ይታወቃል
4.ሶማ(ቻንድራ): የሂንዱ የጨረቃ አምላክ ነው
5.ማንጋ: ዞሮአስተሪያን ተብሎ የሚታወቀው የጥንት ኢራናውያን እምነት
የጨረቃ አምላክ ነው
6.ሁባል: የሙስሊም ነብይ መሀመድ የጎሳ ዘሮች (ቁረይሾች) በካባ ሲያመልኩት የነበረው የጨረቃ አምላክ ነው

*** የሚከተሉትን ሊንኮች በመጫን ሙሉ መረጃዎቹን ያንብቡ
https://en.m.wikipedia.org/wiki/Sin_(mythology)

https://en.m.wikipedia.org/wiki/Khonsu

https://en.m.wikipedia.org/wiki/Selene

https://en.m.wikipedia.org/wiki/Chandra

https://en.m.wikipedia.org/wiki/Mah

https://en.m.wikipedia.org/wiki/Hubal

📜📜 አንድ አምላክን ብቻ አመልካለሁ ማለት ጣዖት ላለማምለክ ማረጋገጫ አይሆንም 📜📜
በመጽሐፍ ቅዱስ የጥንት ዘመን እስራኤላውያን ማምለክ ያለባቸው አንድ አምላክ ብቻ እንደሆነ ተደጋግሞ ተነግሯቸዋል( ምሳሌ ጥቅሶች:- ዘዳ.6:14,ዘዳ.29:18,ኢሳ.36:20,1ኛቆሮ.8:5):ይህም በወቅቱ በእስራኤላውያን ዙሪያ የነበሩ ህዝቦች በአብዛኛው በብዙ ጣዖታት አማልክት የመልኩ የነበረ በመሆኑ ነው።📜ነገር ግን አንድ አምላክን ማምለክ የግድ ፈጣሪን ማምለክ አይደለም።📜📜አንድ አምላክ ጣዖትንም ማምለክ አለና።📜📜ወደ ቁርአንም እንደ ሌሎች ርዕሰ ጉዳዮች ሁሉ አንድ አምላክን ብቻ የማምለክን ሀሳብ ከመጽሐፍ ቅዱስ ተወስዷል።

📜ሙስሊሞች እኛ አንድ አምላክን ብቻ ነው የምናመልከው በማለት ይናገራሉ:ይህ ጉዳይ በቁርአንም ትኩረት ተሰጥቶታል።መሀመድም በመካ ይገኙ ከነበሩት 360 ጣዖታት አንዱን ብቻ በማስቀረት ሌሎቹን እንዳጠፋ ታሪክ እና አርኪዮሎጂ ሳይንስ ይናገራል።

📜ነገር ግን ታሪክ እና አርኪዮሎጂ ሳይንስ እንደሚያስረዳው መሀመድ ሌሎቹን በመካ ዙሪያ ይመለኩ ከነበሩት 360 ጣዖታት መካከል አንዱን ብቻ በማስቀረት ሌሎቹን አጥፍቷል:-
..📜 የመሀመድ አያት አብዱል ሙጣሊብም "ሁባል" የተባለ ጣዖትን በመካ ያመልክ እንደነበር እና መሀመድን ወደ ሁባል እንደወሰደው እና መሀመድን ለሁባል እንደሰጠው በሁለት የሙስሊሞች ሀዲሳት (ኢብን ሀሺም እና ጠበሪ ) የተጠቀሰ ነው:-
(Ibn Hisham 37 & Tabari Vol 5: pg 271)"

📜አንድ አምላክን ስለማምለክ (Monotheism) ስናወራ እላይ እንዳልነው ይህ የግድ እውተኛውን አንድ አምላክ /ፈጣሪ/ብቻ የሚያሳይ አይደለም። "አምላክ" ማለት የሚመለክን ነገር/ህላዌ
/ የሚያመለክት ነው።ፈጣሪን አምላክ ልንል እንላለን:አንድን የሚመለክ ጣዖትንም አምላክ ልንል እንችላለን።
በጥንት ዘመን አንድ አምላክን ብቻ የሚያመልኩ ሰዎች ነበሩ:ለምሳሌ "አክሄናቴ"/Akhenate/በመባል የሚታወቀው የጥንቱ የግብጽ ፈርዖን ....በአንድ አምላክ ብቻ... የሚያምን ንጉስ ነበር።ያ አምላክ ግን "አቴን"/Aten/የተባለ የጸሀይ ምስል ነበር።ሌላ ምሳሌ ዞሮአስተርያኒዝም/Zoroasteriasm/ የተባለው የጥንት ኢራናውያን አምልኮ ነው።ዞሮአስተርያኖች በአንድ አምላክ ብቻ ነው የሚያምኑት:አምላካቸውም አሁራ ማዝዳ/Ahura Mazda/ በመባል ይታወቃል። ምንጭ:-
https://www.worldhistory.org/article/1454/monotheism-in-the-ancient-world/
📜እናም እስልምና በአንድ አምላክ ማመንን ስለሚነግረን ብቻ ጅማሬው በፈጣሪ ላይ የተመሠረተ ነው ማለት አይቻልም።እላይ እንዳልነው መሀመድ ሌሎቹን ሲያጠፋ አንድ ጣዖት/አምላክ/ብቻ አስቀርቶ ነበር።አያቱም መሀመድን..... ሁባል ወደ ተባለ ወደ አንድ አምላክ..... ብቻ ወስዶት ነበር።

Sin (/ˈsiːn/) or Suen (Akkadian: 𒀭𒂗𒍪, dEN.ZU[1]) also known as Nanna (Sumerian: 𒀭𒋀𒆠 DŠEŠ.KI, DNANNA[2]) was the Mesopotamian god representing the moon. While these two names originate in two different languages, respectively Akkadian and Sumerian, they were already used interch...

26/12/2023

📜📜ሀይማኖታዊ ንጽጽር....2

ሰላምና ሀይማኖትን በተመለከተ

📜📜የትኛው የሀይማኖት መሪ... ለሀይማኖት ሲባል ብቻ.... ተዋጉ የሚል ትዕዛዝ አስተላልፏል ?... ኢየሱስ ወይስ መሀመድ?
.....ብሉይ ኪዳንና ቁርአን...
📜📜📜📜📜📜📜📜📜📜📜

📜በሀይማኖት መጽሐፍት ውስጥ ስለሚገኙ የጦርነት ወይም ግድያ ንባቦች ርዕሰ ጉዳይ ሲነሳ መታወቅ ያለበት እውነት በብሉይ ኪዳን በዚያ ....የህግ ዘመን.... ለጥንት እስራኤላውያን የተሰጡት መመሪያዎች:-

1. ከሌሎች ህዝቦች ጋር ስለነበራቸው የውጊያ መመሪያዎች (ይህም ሲሆን ልክ እነዚያ ህዝቦች እንዳደረጉባቸው.... መልሰው እንዲበቀሉ.... ለምሳሌ አማሌቃውያን ...ህጻናትን እና ሽማግሌዎችን.... ሳይቀር "ሁሉንም" (ዘዳ.25:17-18).... ስለገደሉ እስራኤላውያንም እንደ ስራቸው ተመሳሳይ ብቀላ እንዲፈጽሙ (1ኛ ሳሙ.15:2 እና 18 እንዲሁም 1ኛ.ሳሙ.15:3) ነበር ትዕዛዝ የተሰጠው ።
ምክንያቱም በሙሴ ህግ መሠረት..... አንድ ጥፋት በተመሳሳይ ቅጣት መካካስ("ጥርስ በጥርስ".....መመለስ ስለነበረበት)
2. በሙሴ የተሰጡ ትዕዛዛትን ለሚጥሱ አንዳንድ ጥፋቶች የተሰጡ መመሪያዎች
3. በሙሴ ከተሰጣቸው የአምልኮ ስርአት ውጪ ሌሎች አማልክትን የሚያመልኩ ላይ የተሰጠ የሞት ፍርድ መመሪያዎች እና ወዘተ።

📜📜📜ሆኖም ይህ ሁሉ ሲሆን ...በዚያ የህግ ዘመንም እንኳን ....ሀይማኖታችሁን ለማስፋፋት እና ሀይማኖታችሁን በሌሎች ላይ ለመጫን/ለሀይማኖታችሁ ሲባል ብቻ... ሄዳችሁ ሌላውን ተዋጉ የሚል ትዕዛዝ... አልተሰጠም።📜📜....የቁርአንና... የብሉይ ኪዳን.... ልዩነት.... እዚህ ጋር ነው።ቁርአን...ስለ እስልምና ሲባል ብቻ ..ተዋጉ.. ይላል(ቁርአን 8:39):-

"ሁከትም እስከማትገኝ ሃይማኖትም ሁሉ ለአላህ ብቻ እስከሚኾን ድረስ ተጋደሏቸው፡፡ ቢከለከሉም አላህ የሚሠሩትን ሁሉ ተመልካች ነው፡፡"
.....የመሀመድ እና የኢየሱስ ትዕዛዛት
📜📜📜📜📜📜📜📜📜📜📜

📜📜 የሙስሊሞች ነበይ መሐመድ በቁርአን በ8፡39 ላይ ....ለሀይማኖት ሲባል ብቻ....እንዲዋጋ ትዕዛዝ እንደ ተሰጠው ተናግሯል:-

"ሁከትም እስከማትገኝ ሃይማኖትም ሁሉ ለአላህ ብቻ እስከሚኾን ድረስ ተጋደሏቸው፡፡ ቢከለከሉም አላህ የሚሠሩትን ሁሉ ተመልካች ነው፡፡"

📜በአዲስ ኪዳን ...የጸጋ ዘመን...መሲህ የሆነው የክርስቲያኖች ጌታ ኢየሱስ ግን በማቴዎስ 5÷44-45 ላይ ‹‹ ...ጠላቶቻችሁን ውደዱ:... ስለሚያሳድዱአችሁም ጸልዩ፤›› በማለት ተቃራኒ መልዕክት አስተላልፏል።አዲስ ኪዳን ....የጸጋ ዘመን...በመሆኑ ....የሰላም ብቻ እንጂ የሞት ፍርድ ህግጋት የሉትም።

📜ይህ ሀሳብ ሲነሳ አንዳንድ ሙስሊሞች ማቴ.10:34-39:ሉቃ.22:36ን የመሳሰሉ ጥቅሶች ላይ ኢየሱስ ስለ "ሰይፍ" እና ግድያ ተናገሯል በማለት ይሰብካሉ።ነገር ግን እነዚህ ኢየሱስ የተናገራቸው የ"ሰይፍ" ንግግሮች....ዐውድ... የመጀመሪያው በኢየሱስ የሚያምኑ.... ስለሚደርስባቸው ....መከራ.... (ማቴ.10:34-39) እንዲሁም ሁለተኛው (ሉቃ.22:36ን) ቀጥታ ትርጉም ያለው ሳይሆን
ዘይቤያዊ....መሆኑን መረዳት ይቻላል።ኢየሱስ ....ለሀይማኖት...በስጋዊ ህይወት ተዋጉ አላለም።📜ለዚህም ብዙ ማረጋገጫ መስጠት የሚቻል ሲሆን እዚህ የሚከተሉትን ንባቦች እንጠቅሳለን:-

“በዚያን ጊዜ ኢየሱስ እንዲህ አለው፦ ሰይፍ የሚያነሡ ሁሉ በሰይፍ ይጠፋሉና ሰይፍህን ወደ ስፍራው መልስ።”
— ማቴዎስ 26፥52

“ኢየሱስም ጴጥሮስን፦ ሰይፍህን ወደ ሰገባው ክተተው፤ አብ የሰጠኝን ጽዋ አልጠጣትምን? አለው።”
— ዮሐንስ 18፥11

📜ሌላው በሙስሊሞች የሚጠቀሰው ራዕ.2:23 ኢየሱስ ከሰማይ እንደ አምላክ ለዮሐንስ ያስተላለፈው ሲሆን በእርሱ ላይ ያመጹ ግለሰቦች ላይ የሞት ቅጣት ፍርድ ያስተላለፈበት ነው እንጂ ለሀይማኖት ግድያን የሚያዝ አይደለም።

25/12/2023

ሀይኖማኖታዊ ንጽጽር:

📜📜ኢየሱስ Vs መሀመድ....ከቁርአንና ከመጽሐፍ ቅዱስ📜📜📜

1. የሙስሊሞች ነቢይ መሐመድ ከአባቱ አብደላ የተወለደ ሲሆን ኢየሱስ ግን በአባት የዘር ግንድ የሰው ዘር አልገባበትም፡፡ (እስልምናና የመሀመድ ታሪክ :ገፅ 24።ሉቃ ምዕራፍ 2። ቁርአን 19÷15-36).....በተጨማሪም ኢየሱስ ከመወለዱ ከብዙ አመታት በፊት በመጽሐፍ ቅዱስ በትንቢት አስቀድሞ የተነገረ ሲሆን (ምሳሌ ጥቅሶች:- ሚክያስ 5:2-“አንቺም ቤተ ልሔም ኤፍራታ ሆይ፥ አንቺ በይሁዳ አእላፋት መካከል ትሆኚ ዘንድ ታናሽ ነሽ፤ ከአንቺ ግን አወጣጡ ከቀድሞ ጀምሮ ከዘላለም የሆነ፥ በእስራኤልም ላይ ገዥ የሚሆን ይወጣልኛል።”
— ሚክያስ 5፥2
እና ኢሳ.7:14 :- “ስለዚህ ጌታ ራሱ ምልክት ይሰጣችኋል፤ እነሆ፥ ድንግል ትፀንሳለች፥ ወንድ ልጅም ትወልዳለች፥ ስሙንም አማኑኤል ብላ ትጠራዋለች።”
— ኢሳይያስ 7፥14
) ......ስለመሀመድ... ልደት... ግን ...አስቀድሞ የተነገረ በቁርአን አንድ እንኳ ትንቢት የለም (ሙስሊሞች ስለ መሀመድ ትንቢት ከቁርአን በማጣታቸው ምክንያቱም ቁርአን የትንቢት መጽሐፍ አይደለምና መሀመድን መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ይፈልጉታል።እናም ስለ መሀመድ ትንቢት መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ አንዳንድ ጥቅሶችን ለመጥቀስ ይሞክራሉ።ሁሉም ሙከራዎች ከአውድ ውጪ የሚጠቀሱ የሀሰት ንግግሮች ናቸው።ቁርአን ኢየሱስ ከመወለዱ በፊት የተወሰኑ ክስተቶችን ስለ ኢየሱስ በምዕራፍ 19 ላይ ይናገራል።ለመሀመድ ልደት ግን ይህን ያህል ቦታ አልሰጠውም።እና እንደቁርአን ትርክት እንኳን ታላቁ ነቢይ ሊባል የሚችለው ማነው? 📜 መጽሐፍ ቅዱስ የኢየሱስ እና ስለ ኢየሱስ የሚናገር እንጂ የመሀመድ እና ስለ መሀመድ አይደለም። 📜ኢየሱስም እንዲህ ብሏል:-“እናንተ በመጻሕፍት የዘላለም ሕይወት እንዳላችሁ ይመስላችኋልና እነርሱን ትመረምራላችሁ፤ እነርሱም ስለ እኔ የሚመሰክሩ ናቸው፤”
— ዮሐንስ 5፥39

የየትኛው ልደት አስደናቂ ነው?

Address

Churchil Avenue
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Tổng đại lý vé máy bay 247 posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Tổng đại lý vé máy bay 247:

Share