የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ አገልግሎት/Addis Ababa Diocese Media Service

  • Home
  • የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ አገልግሎት/Addis Ababa Diocese Media Service

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ አገልግሎት/Addis Ababa Diocese Media Service ይህ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ የፌስቡክ ገጽ ነው።
መንፈሳዊ አገልግሎትና ሰሞነኛ ጉዳዮች ይቀርቡበታል።
(4)

ከ14,000በላይ ለሚሆኑ የሰንበት ት/ ቤት ተማሪዎች በሀገረ ስብከት ደረጃ የብሔራዊ ፈተና ምዘና ማከናወኑን የአንድነቱ  ተቀዳሚ ምክትል ሰብሳቢ ገለጹ። ሐምሌ ፲፬/፳፻፲፯ ዓ/ሜ የአዲስ አበ...
21/07/2025

ከ14,000በላይ ለሚሆኑ የሰንበት ት/ ቤት ተማሪዎች በሀገረ ስብከት ደረጃ የብሔራዊ ፈተና ምዘና ማከናወኑን የአንድነቱ ተቀዳሚ ምክትል ሰብሳቢ ገለጹ።

ሐምሌ ፲፬/፳፻፲፯ ዓ/ሜ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ

ከ14,000በላይ ለሚሆኑ የሰንበት ት/ ቤት ተማሪዎች በሀገረ ስብከት ደረጃ የብሔራዊ ፈተና ምዘና ማከናወኑን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ተቀዳሚ ምከትል ሰብሳቢ ላእከ ኄራን ገለጹ።

ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የአዲስ አበባና የሀድያ ስልጤ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በቡራኬ ያስጀመሩት የደብረ ምጥማቅ ሰዓሊተ ምሕረት ቅድስት ማርያም ወቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ካቴድራል የምዘናው ማከናወኛ ሰንበት ትምህርት ቤት ጨምሮ በሁሉም ክፍላተ ከተማ ቤተ ክህነት በሚገኙ 160 የምዘና መውሰጃ ሰንበት ትምህርት ቤቶች በተሳካ ሁኔታ የምዘና መርሐ ግብሩ መጠናቀቁን የአንድነቱ ተቀዳሚ ምክትል ሰብሳቢ ላእከ ኄራን መንክር ግርማ ገልጸዋል።

ላእከ ኄራን መንክር ግርማ አክለውም ተመዛኞች ዓመቱን ሙሉ በሰንበት ት/ቤቶች ሲማሩ መቆየታቸውን አስታውሰው በትናትናው ዕለት ከ168 ሰንበት ት/ቤቶች የተውጣጡ 14,800 የሚሆኑ ተመዛኞች የተፈተኑ ሲሆን፤ በሁሉም የመፈተኛ ጣብያዎች ፈተናዎቹ መሰጠታቸውን እንዲሁም የቋንቋ እና ልዩ ፍላጎት ላላቸው ተማሪዎች አስተርጓሚ እና አንባቢ ተመድቦላቸው የተፈተኑ መሆናቸውን አብራርተዋል።

በተጨማሪም ከሀገረ ስብከቱ ጀምሮ የሁሉም ክፍላተ ከተማ ቤተ ክህነት አንድነት ጽ/ቤት እና ትምህርት ክፍሎች በየክፍላተ ከተሞቻቸው ያሉ ተፈታኞችን የክትትል ጣቢያዎች አዘጋጅተው በጥሩ መልኩ ያስተባበሩ መሆናቸውን የክፍለከተማ ቤተክህነት ሓላፊዎችም በተመደቡበት ጣቢያ በመገኘት በጸሎት በመክፈት እና ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን፤ የገዳማት እና አድባራት አስተዳዳሪዎችም በጸሎት በመክፈት እና አስፈላጊ ድጋፍ በመስጠት ለመርሐ ግብሩ መሳካት ሁሉም የበኩላቸውን ተወጥተዋል ብለዋል።

ዘገባው የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሰንበት ትምህርት ቤት አንድነት ነው።

ቤተ ክርስቲያን ቅርሶቿን በመንከባከብ የቅድመ ጥንቅቃቄ ሥራዎችን አጠናክራ መቀጠል እንዳለባት  ፕሮፌሰር አበባው አያሌው ገለጹ።ሐምሌ ፲፬/፳፻፲፯ ዓ/ም የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያየኢት...
21/07/2025

ቤተ ክርስቲያን ቅርሶቿን በመንከባከብ የቅድመ ጥንቅቃቄ ሥራዎችን አጠናክራ መቀጠል እንዳለባት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው ገለጹ።

ሐምሌ ፲፬/፳፻፲፯ ዓ/ም የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ

የኢትዮጵያ ቅርስ ጥበቃ ባለ ስልጣን ዋና ዳይሬክተር ፕሮፌሰር አበባው አያሌው እና የሥራ ባልደረቦቻቸው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ መጻሕፍት ወመዘክር ሙዚየምን ገበኙ። ጉብኝቱ በቅርሶች ደኅንነትና ጥበቃ ላይ በጋራ ለመሥራት ዓላማ ያደረገ መሆኑ በጉብኝቱ ወቅት ተገልጿል፡፡

ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በመርሐ ግብሩ ላይ እንደተናገሩት፤ ቤተክርስቲያን ያሏትን ቅርሶች ለመጠበቅ ከምትከተለው ጽኑ አቋም የተነሳ ቅርሶችን በልዩ እንክብካቤ ለመያዝ እያደረገች ያለችው ጥረት የሚመሰገን ነው ብለዋል።

‹‹ቅርስና ሕይወት አንድ ናቸው›› ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ ‹‹ሁለቱንም ካጣናቸው መልሰን ስለማናገኛቸው ቅድመ ጥንቅቃቄ ማድረግ ይገባናል›› ሲሉም አሳስበዋል። አያይዘውም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን እና የቅርስ ጥበቃ ባለስልጣን እስካሁን በቅርስ ጥበቃ ረገድ አያሌ ሥራዎችን በጋራ ሲያከናውኑ መቆየታቸውን አስታውሰው፤ ወደፊትም በጋራ የሚያሠሩ የመግባቢያ ሰነዶችን በመፈራረም የጋራ ቅርሶቻችን በጋራ እንጠብቃለን ሲሉ የሁለትዮሽ ግንኙነትን ስለማጠናከር አስፈላጊነት ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የቅርስ ጥበቃ ቤተ መጻሕፍት ወመዘክር መምሪያ ዋና ኃላፊ በኩረ ትጉሃን ምትኩ ከንቲባ በበኩላቸው የባለሥልጣኑ የሥራ ኀላፊዎች ስላደረጉት ጉብኝት አመስግነው፤ ቤተ ክርስቲያን ከባለ ሥልጣን መ/ቤቱ ጋር በጋራ ለመሥራት ያላትን ፍላጎት አሳውቀዋል፡፡

© የመንበረ ፓትርያርክ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

የሚዲያችን   በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑን!https://www.youtube.com/የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ አገልግሎትስለአንዲት ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን ሁሉ ነገር እንዳርሳለን።
20/07/2025

የሚዲያችን በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑን!

https://www.youtube.com/

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ አገልግሎት
ስለአንዲት ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን ሁሉ ነገር እንዳርሳለን።

ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የአዲስ አበባና ሀዲያ ስልጤ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የ5ኛው ዙር ሀገረ ስብከት አቀፍ የሰንበት ተማሪዎች ብሔራዊ ምዘና መርሐ ግብር አስመልክተው በሰአሊተ ምሕረ.....

በደብረ ብርሃን ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን የብሉይ ኪዳን እና የሐዲስ ኪዳን 28 ደቀ መዛሙርት በብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ የሰሜን ሸዋ ሀገረስብከት ሊቀ ጳጳስ ቡራኬ ተመረቁ።ሐምሌ ፲፫/፳፻፲፯...
20/07/2025

በደብረ ብርሃን ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን የብሉይ ኪዳን እና የሐዲስ ኪዳን 28 ደቀ መዛሙርት በብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ የሰሜን ሸዋ ሀገረስብከት ሊቀ ጳጳስ ቡራኬ ተመረቁ።

ሐምሌ ፲፫/፳፻፲፯ ዓ/ም የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ

በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት በደብረ ብርሃን ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን እና በአንሳስ መንበረ ብርሃን ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን ሲማሩ የነበሩ 6 የብሉይ ኪዳን እና 22 የሐዲስ ኪዳን ደቀ መዛሙርት በብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ እና የሰሜን ሽዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ አባታዊ ቡራኬ ተመርቀዋል።

በምርቃት መርሐ ግብሩ መጋቤ ሐዲስ የኔታ ወልደ ሚካኤል በየነ በደብረ ብርሃን ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን የአንሳስ መንበረ ብርሃን ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን ሐዲስ ኪዳን ትርጓሜ መምህር ሪፖርት ያቀረቡ ሲሆን ይህ ትምህርት ቤት በቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን በ1994 ዓም በብፁዕ አቡነ ኤፍሬም አማካኝነት እንደተመሰረተ እና አሁንም በሰፊው እያስተማረ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

በሪፖርቱም ላይ 6 የብሉይ ኪዳን እና 22 የሐዲስ ኪዳን ደቀ መዛሙርት በአጠቃላይ 28 ደቀመዛሙርት በብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ መመሪያ ሰጪነት ጥብቅ ክትትልን በማድረግ ለምረቃት እንደበቁ ተናግረዋል።

ይህ ትምህርት ቤት ለተለያዩ 24 ዓመታት ልዩ ልዩ ደቀመዛሙርትን ያፈራ ሲሆን ደቀመዛሙርቱ ትምህርታቸውን እንዳይከታተሉ የምግብ እና የልብስ እጥረት እንዲሁም የመጸሐፍ ዋጋ መወደድ ለደቀመዛሙርቱ ፈተና እንደሆነባቸው ይህ ነገርም እንዲፈታ ማንኛውም የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አማኝ እንዲተባበራቸው ጥሪ አቅርበዋል።

ለዚህ ትምህርት ቤት አዳራሽ መስሪያ እገዛ ያደረጉ የሰሜን ሀገረ ስብከትን እና የተለያዩ ድጋፍ ሰጪ ምእምናንን አመስግነዋል።

የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ክቡር መጋቤ ሐዲስ ነቅዐጥበብ አባቡ “ወደ ዓለም ሁሉ ሂዱ ወንጌልንም ለፍጥረት ሁሉ ስበኩ።” በሚል መነሻ ኃይለ ቃል ለተመራቂ ደቀመዛሙርቱ መልዕክታዊ ትምህርት አስተምረዋል።

በትምህርታቸውም ይሀን ቃል የተናገረው የፍጥረት ሁሉ ባለቤት መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሲሆን የተናገረውም በሄደበት ለሚከተሉት ባደረበት ለሚያድሩት 3ዓመት ከ 3 ወር ከእግሩ ሥር ለተማሩ ለደቀመዛሙርቱ እንደሆነና ወንጌል ለዓለም መድኃኒት፣ ሰላም እና ፈውስ እንደሆነ ገልጸዋል።

ክቡር ሥራ አስኪያጁ ዛሬ የተመረቃችሁ ደቀመዛሙርት በብፁዕነታቸው ተመርቃችሁ ወደ ዓለም ሔዳችሁ ወንጌልን የምታስተምሩበት ቀን ስለሆነ እንኳን ደስ አላችሁም በማለት መምህራኑንም አመስግነዋል።

ደቀ መዛሙርቱንም እስከዛሬ የታገላችሁት ከረሃብ እና ከጥም ጋር ነው ነገር ግን ከዚህ በኃላ ትግላችሁ ከዓለም ፈተናዎች ጋር ስለሆነ መጠንከር ይገባል፤ በሐይማኖት እና በምግባር ጸንታችሁ እንደ እርግብ የዋህ እንደ እባብ ብልህ በመሆን እንድታገለግሉ ፈጣሪ ይርዳችሁ ብለዋል።

የሰሜን ሽዋ ሀገረ ስብከት ይህንን ትምህርት ቤት ወደ ፊት በተቻለው አቅም በመደገፍ እና በብፁዕታቸው መልካም ፈቃድ ወደ አዳሪ ትምህርት ቤት ለማሳደግ እቅድ እንዳለው ገልጸዋል።

ብፁዕ አብነ ቀሌምንጦስ የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ዛሬ ላይ የተመረቃችሁ ደቀመዛሙርት በሐዲስ ኪዳን 5 ዓመት በብሉይ ኪዳን 6 ዓመት በውጣውረድ ውስጥ በማለፍ ለዛሬው የደስታችሁ ቀን በመድረሳችሁ እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል።

ብፁዕነታቸው ትምህርት ቤት ውጣ ውረድ አለው የሚሰራውም በሰው አእምሮ ነው በዚህም አእምሮ የሚራቀቅበት፣ ለአዲስ ነገር የሚዘጋጅበት ፣ጥልቅ ነገሮች የሚታወቅበት፣ ደቀመዛሙርት የሚፈልቅበት የእውቀት መገኛ ነው ይህንንም ያገኛችሁ ተመራቂዎች ዛሬ የኃላፊነት ሹመት ተሰጥቷችኃልና በዓለም ያለውን ፈተና በማለፍ በእውቀት እንደታገለግሉ እግዚአብሔር ይርዳችሁ በማለት ቃለ በረከት አስተላልፈዋል።

ተመራቂ ደቀመዛሙርት የምስክር ወረቀት ከብፁዕነታቸው ተቀብለዋል።

መርሐ ግብሩ መልአከ ብርሃናት አባ ይትባረክ መኰንን የደብረ ብርሃን ቅድስት ሥላሴ እና በሥሩ ያሉ አብያተክርስቲያናት አስተዳዳሪ፣ መልአከ ምሕረት አባ ሙሴ መካሻ የሣሪያ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል እና በሥሩ ያሉ አድባራት አስተዳዳሪ፣ መራሔ ሊቃውንት ያዕቆብ ተክለ አረጋዊ የጠባሴ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም እና በሥሩ የሚገኙ አብያተ ክርስቲያናት የአራቱ ጉባኤያት መምህር፣ የሀገረስብከቱ ልዩ ልዩ ክፍል ሓላፊዎች፣ሊቃውንተ ቤተክርስቲያ፣ የሰንበት ትምህርት ቤት መዘምራን እና ምእመናን በተገኙበት በተመራቂ ደቀመዛሙርት ወረብ እና ቅኔ ቀርቦ በብፁዕነታቸው ቃለበረከት ተጠናቅቋል።

©አቡቀለምሲስ ሚዲያ

20/07/2025
ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ ሊቀ ጳጳስ በሰአሊተ ምሕረት ተገኝተው የ5ኛው ዙር ሀገረ ስብከት አቀፍ ብሔራዊ ምዘና የሚወስዱ ሰንበት ተማሪዎች ጎበኙ።ሐምሌ ፲፫/፳፻፲፯ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚ...
20/07/2025

ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ ሊቀ ጳጳስ በሰአሊተ ምሕረት ተገኝተው የ5ኛው ዙር ሀገረ ስብከት አቀፍ ብሔራዊ ምዘና የሚወስዱ ሰንበት ተማሪዎች ጎበኙ።

ሐምሌ ፲፫/፳፻፲፯ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ

ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የአዲስ አበባና የሀዲያ ስልጤ እፈአህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በሰአሊተ ምሕረት ተገኝተው የ5ኛው ዙር ሀገረ ስብከት አቀፍ ብሔራዊ ምዘና የሚወስዱ ሰንበት ተማሪዎች ጎበኙ።

ከብፁዕነታቸው የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ምሕረት አባ ገብረ መድኅን ንግሤ፣ የብፁዕ ሊቀ ጳጳስ ልዩ ጸሐፊ መጋቤ ስብሐት ዐቢይ ዘለቀ፣የደብረ ምጥማቅ ሰአሊተ ምሕረት ቅድስት ማርያምና ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ካቴድራል አስተዳዳሪ መልአከ ኃይል ተክለ ብርሃን ደስታና የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት አመራሮች ተገኝተዋል።

በዛሬው ዕለት ምዘናውን የሚወስዱት ብዛታቸው 14 ሺህ በላይ ሰንበት ተማሪዎች ሲሆኑ በደብረ ምጥማቅ ሰአሊተ ምሕረት ቅድስት ማርያም ካቴድራል አደራሽ ላይ የሚፈተኑት ደግሞ 600 ተማሪዎች እንደሆኑ ተገልጿል።

ምዘናው የ4ኛ፣ የ8ኛና የ10ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ተፈታኞች እንደሆኑም ተብራርቷል።

ብፁዕነታቸው እንዳሉት የነገ ቤተ ክርስቲያን ተረካቢ ትውልድ የሚገኝበት ተቋም ሰንበት ትምህርት ቤት እንደመሆኑ መጠን ተፈትነው ያለፉ በዕውቀት የተሻሉ ወጣቶች በእጅጉ ያስፈልጉናል ብለዋል።

በመጨረሻ ብፁዕነታቸው ለተፈታኞች መልካም ውጤት የተመኙ ሲሆን አያይዘውም የደብረ ምጥማቅ ሰአሊተ ምሕረት ቅድስት ማርያምና ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ካቴድራል ሰንበት ትምህርት የሚያስተምራቸውን ተማሪዎች ጎብኝተው ቡራኬ ሰጥተዋል።

🔵የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ
ስለ አንዲት ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን

🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚 https://www.facebook.com/AddisAbabaDiocese?mibextid=2JQ9oc

ከዚህ በተጨማሪ በሌሎች የበይነ መረብ አማራጮች ለመከታታል
በቴሌግራም: https://t.me/AddisAbabaDiocese

በዩቱዩብ: http://www.youtube.com/

በቲውተር: https://twitter.com/AADioceseMedia/media
በቲክቶክ:http://tiktok.com/
መጠቀም ይችላሉ።

"ለሰው ሁሉ መድኃኒት የሆነውን ወንጌል ይዛችሁ በመሄድ  አስተምሩ"ብፁዕ አቡነ ማርቆስ የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልእኮ መምሪያ ሊቀ ጳጳስሐምሌ ፲፪/፳፻፲፯ ዓ/ም የአዲስ አበባ ሀገረ ስብ...
19/07/2025

"ለሰው ሁሉ መድኃኒት የሆነውን ወንጌል ይዛችሁ በመሄድ አስተምሩ"
ብፁዕ አቡነ ማርቆስ የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልእኮ መምሪያ ሊቀ ጳጳስ

ሐምሌ ፲፪/፳፻፲፯ ዓ/ም የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ

ለሰው ሁሉ መድኃኒት የሆነውን ወንጌል ይዘው በሁሉ አቅጣጫ እንዲያስተምሩ ብፁዕ አቡነ ማርቆስ የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልእኮ መምሪያ ሊቀ ጳጳስ ለተመራቂዎች አባታዊ መልእክት አስተላለፉ።

ብፁዕነታቸው ይህን ያሉት የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ ታዕካ ነግሥት በአታ ለማርያም ገዳም የመምህራንና የቀሳውስት ማሰልጠኛ መንፈሳዊ ትምህርት ቤት በ2017 ዓ.ም ትምህርታቸውን ያጠናቀቁ ደቀ መዛሙርትን ባስመረቀበት ወቅት ነው።

በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ጽርሐ ተዋሕዶ አዳራሽ በተከናወነው መርሐ ግብር ትምህርት ቤቱ በሐዲሳት ትርጓሜ 11፣ በብሉይ ትርጓሜ 13 ፣ በሊቃዉንት ትርጓሜ 33 ፣ በቅኔ 11፣ በቅዳሴ 5 ፣ በኆኅተ : ስብከት 244 በአጠቃላይ 317 ደቀ መዛሙርት አስመርቋል።

በምረቃው ላይ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት፣ የአዲስ አበባ ሀገረስብከት የሥራ ኃላፊዎች የገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እና የተመራቂ ቤተሰቦች ተገኝተዋል ።
የታዕካ ነገስት በአታ ለማርያም ገዳም አስተዳዳሪ ሊቀ ሊቃውንት ቆሞስ አባ ተክለ ሃይማኖት ወልዱ ለተመራቂዎች የእንኳን ደስ አላችሁ መልእክት አስተላልፈዋል ።

በምረቃ መርሐ ግብሩ ወቅት አጠቃላይ የመማር ማስተማር ሂደትን በተመለከተ ሊቀጉባኤ አባ ኪዳነማርያም ደርበው ሪፖርት አቅርበዋል። በሪፖርቱ መምህራንና ቀሳውስት በማሰልጠን ቀዳሚና አንጋፋ የሆነው መንፈሳዊ ትምህርት ቤቱ የጎደሉትን በሟሟላት በበለጠ ማሳደግ እንደሚያስፈልግ ተጠቁሟል ።

በተያያዘም በትምህርት ቤቱ የተለያየ አስተዋጽኦ የነበራቸው የመጽሐፈ ሊቃውንት፣ መምህራን፣ ደቀመዛሙርት እና ሌሎች አካላት የምስጋና ሥጦታ ተበርክቶላቸዋል ።

ብፁዕ አቡነ ማርቆስ የስብከተ ወንጌል ሐዋርያዊ ተልዕኮ መምርያ የበላይ ኃላፊ "ደቀመዛሙርቱ በፍርሐት ተቀምጠው ሳሉ ሰላም አላቸው በሚስማር የተቸነከረው እጁ አሳያቸው" የሚለውን ኃይለቃል መነሻ በማድረግ በዘመናችን ጎናቸው በረሀብ ችንካር ተቸንክረው ለሚሰቃዩ ወገኖች እናንተም የተማራችሁት መድኃኒት የሆነውን ወንጌል አሳይዋቸው ሲሉ ሲሉ አባታዊ መመሪያ አስተላልፈዋል ።

በምረቃው ላይ ከደቀ መዛሙርቱ መካከል የ80 ዓመት ዕድሜ ባለጸጋ መኖራቸው ለጉባኤው ልዩ ስሜት ፈጥሯል።

በመጨረሻም የገዳሙ ካህናት ሊቃውንት ወረብ፣ ተመራቂ ደቀመዛሙርት ቅኔ አቅርበው መርሐግብሩ በጸሎተ ቡራኬ ተጠናቋል ።

©EOTC TV

የደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ክርስቲያን ሰበካ ጉባኤ ምክትል ሊቀ መንበር መጋቤ ሠናያት ኢ/ር አያሌው መሸሻ ለሀዲያና ስልጤ ሀገረ ስብከትና ለሆሳዕና መንበረ ጵጵስና ደብረ ገነት ቅድስት ማ...
19/07/2025

የደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ክርስቲያን ሰበካ ጉባኤ ምክትል ሊቀ መንበር መጋቤ ሠናያት ኢ/ር አያሌው መሸሻ ለሀዲያና ስልጤ ሀገረ ስብከትና ለሆሳዕና መንበረ ጵጵስና ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን ግንባታ የገንዘብ ድጋፍ አደረጉ።

ሐምሌ ፲፪/፳፻፲፯ ዓ/ም የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ

የደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ክርስቲያን ሰበካ ጉባኤ ምክትል ሊቀ መንበር መጋቤ ሠናያት ኢ/ር አያሌው መሸሻ ለሀዲያና ስልጤ ሀገረ ስብከትና ለሆሳዕና መንበረ ጵጵስና ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን ግንባታ የገንዘብ ድጋፍ አደረጉ።

በዛሬው ዕለት በተከናወነው በደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ሁሉን አቀፍ የልማት ሥራዎች ምርቃት ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅ አቡነ ሳዊሮስ ፣ ብፁዕ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ አቡነ ዲዮስቆሮስ እንዲሁም ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የአዲስ አበባና የሀዲያ ስልጤ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የተገኙ ሲሆን በተለይም ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ ለተወሰኑ ቀናት በሀዲያ ስልጤ ሀገረ ስብከታቸው የነበራቸውን ሐዋርያዊ አገሎግሎት አጠናቀው ለዚሁ መርሐ ግብር ሲባል ከሆሳዕና በሌሊት ተጉዘው መገኘታተው ታውቋል።

በምርቃት መርሐ ግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት የደብሩ ሰበካ ጉባኤ ምክትል ሊቀ መንበር መጋቤ ሠናያት ኢ/ር አያሌው መሸሻ በደብሩ የሰበካ ጉባኤ ምክልት ሊቀ መንበር ሆነው ከተመረጡበት ጊዜ ጀምሮ እንደእግዚአብሔር ፈቃድ የሚችሉት ለማድረግ እየተሯሯጡ እንደሚገኙ ገልጸዋል።

በዚህም ቀደም ባለው ጊዜ የደብሩ ዋና የፊት ለፊት በር አካባቢ የነበረው ገጽታ በማስታወስ የሥርዐት ባለቤት ለሆነች ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን የሚመጥን አልበረም ብለዋል።

በመሆኑም ከተማው ከሚከተለው የኮሪደር ልማት መነሻነት ለደብሩ ሁለንተናዊ ለውጥ ለማምጣት ምክንያት የሚሆን መደላድል መፈጠሩን አስተውሰው በዚህ መነሻነት በርካታ ሥራዎች መሠራታቸውን አብራርተዋል።

በዚህም ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት መጥተዉ የተሠሩ ሥራዎችን ጎብኝተው ስለባረኩልን እጅግ እናመሰግናለን ቡራኬያችሁም ትድረሰን ብለዋል።

አያይዘውም ብፁዓን አባቶች ለሚመሯቸው አህጉረ ስብከት በተለያዩ ሁለንተናዊ ድጋፎች ለማገልገል ዝግጁ መሆናቸውን የገለጹ ሲሆን ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ ለሚመሩት ለሀዲያ ስልጤ ሀገረ ስብከት ገጠር አብያተ ክርስቲያናት ድጋፍ የሚሆን የ500,000 ብር ቼክ ለብፁዕነታቸው አስረክበዋል ።

መጋቤ ሠናያት አክለውም ቀደም ባለው ጊዜ በብዙ ሕይወታዊ እድገታቸው በሆሳዕና ከተማ መሆኑን ያሳታወሱ ሲሆን በተለይም ጥንታዊቷ የሆሳዕና መንበረ ጵጵስና ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን በእሳት በተቃጠለ ጊዜ በእጅጉ አዝነው በወቅቱ ድጋፍ ማድረጋቸውን አውሰተዋል።

ይሁን እንጂ በብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ ያልተቋረጠ ትጋት በዓይነቱ ልዩ የሆነ ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን እየተሠራ በመሆኑ ደስታየ ወደር የለውም ብለዋል።

በመሆኑም በሆሳዕና መንበረ ጵጵስና ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ሕንጻ ቤተ ክርስቲያ ግንባታ በትናንሽ ድጋፎች ከመሳተፍ ባለፍ ብዙ አልሠራሁም የሚሉት መጋቤ ሠናያት ኢ/ር አያሌው ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ በደቡብና ምዕራብ አፍሪካ ሀገረ ስብከት የነበራቸው ሐዋርያዊ አገልግሎት ማጠናቀቃቸውን ተከትሎ በነበረው የምስጋና መርሐ ግብር ለግል የተሰጣቸውን ከ1 ሚሊዮን ብር በላይ ለሆሳዕና መንበረ ጵጵስና ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ይሆንልኝ ብለው ሲሰጡ በእጅጉ ልቤ ወደ ትናንቱ ተመለሰ ለማገዝም ወሰንኩ ይላሉ።

ስለሆነም ለሆሳዕና መንበረ ጵጵስና ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን ግንባታ ድጋፍ
#1 ሚሊዮን ብር፣
#3,000 ኩንታል ሲሚንቶ ኩንታል ሲሚንቶ
#ከዋናው መንገድ ጀምሮ ሙሉ ቤተ ክርስቲያኑን አስፓልት ንጣፍ እንደሚያደርጉ እንዲሁም በሞያ በጉልበትና በገንዘብ በሁሉን ዓይነት ድጋፍ ከዚህ በኋላ ከብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ ጎን እንደማይለዩ በብፁዓን አባቶችና በገዳማትና አድባራት እንዲሁም ማኅበረ ካህናት ፊት ቃል ገብተዋል።

ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና ሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ለገጠሪቱ ቤተ ክርስቲያንና ለጥንታዊታ ሆሳዕና መንበረ ጵጵስና ቅድስት ማርያም ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን ግንባታ ከፍተኛ ድጋፍ ያደረጉትን መጋቤ ሠናያት ኢ/ር አያሌው መሸሻን በእጅጉ አድንቀዋል።

ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅ አቡነ ሳዊሮስ አክለውም ጥንታዊቷን የሆሳዕና ማርያም ቤተ ክርስቲያን አደጋ በደረሰበት ጊዜም በቦታው ተገኝተው ድጋፍ እንዳደረጉ አስተውሰው ለገጠሪቱ ቤተ ክርስቲያን በብርቱ ማሰብና ድገፍ ማድረግ ምእመናንንም አይዟችሁ ማለት ከእውነተኛ ክርስቲያን የሚገኝ ተግባር የሚነበብ ሕይወት መሆኑን ገልጸዋል።

ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የአዲስ አበባና የሀዲያ ስልጤ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የተደረገውን ድጋፍ በምስጋና ተቀብለዋል።

🔵የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ
ስለ አንዲት ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን

🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚 https://www.facebook.com/AddisAbabaDiocese?mibextid=2JQ9oc

ከዚህ በተጨማሪ በሌሎች የበይነ መረብ አማራጮች ለመከታታል
በቴሌግራም: https://t.me/AddisAbabaDiocese

በዩቱዩብ: http://www.youtube.com/

በቲውተር: https://twitter.com/AADioceseMedia/media
በቲክቶክ:http://tiktok.com/
መጠቀም ይችላሉ።

  ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸው የደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን  የተለያዩ የራስ አገዝ ልማቶች በብፁዓን አባቶች ቡራኬ ተመረቁ።ሐምሌ ፲፪/፳ ፻ ፲ ፯ ዓ/ም የአዲስ አበባ ሀ...
19/07/2025

ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸው የደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን የተለያዩ የራስ አገዝ ልማቶች በብፁዓን አባቶች ቡራኬ ተመረቁ።

ሐምሌ ፲፪/፳ ፻ ፲ ፯ ዓ/ም የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ

ከ70 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸው የደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን የተለያዩ የራስ አገዝ ልማቶች ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅና ብፁዕ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ እንዲሁም ብፁዕ የአዲስ አበባና ሀዲያ ስልጤ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በተገኙበት ተባርከው ተመረቁ።

በምርቃት መርሐ ግብሩ ላይ ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የደቡብ ምሥራቅ ትግራይና ራያ አህገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመ/ፓ/ጠ/ቤ/ክ ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የአዲስ አበባና የሐድያ ስልጤ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ መልአከ ምሕረት ቆሞስ አባ ገ/መድኅን ንጉሤ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ ኢንጅነር ወንድሙ ሴታ በም/ከንቲባ ማዕርግ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የአ/አ/ሀ/ስ/ የዋና ክፍል ኃላፊዎች፣ ሊቀ ኅሩያን ዳዊት ታደሰ የን/ስልክ ላፍቶ ክ/ከ/ቤ/ክ ሥራ አስኪያጅ፣ መጋቤ ሠናያት የቻለው ለማ የአራዳ ጉሌ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ፣ የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት የሥራ ሐላፊዎች፣ መልአከ ገነት መዝገቡ ላቀው የደብሩ አስተዳዳሪ፣ መጋቤ ሠናይ ኢንጅነር አያሌው መሸሻ የደብሩ ሰበካ ጉባኤ ም/ሊቀ መንበር፣ የገዳማትና የአድባራት አስተዳዳሪዎች፣ የመንግሥታዊና የልዩ ልዩ ድርጅት ኃላፊዎች፣ የሰበካ ጉባኤ አባላት፣ ሊቃውንተ ቤ/ክ አባቶች የደብሩ ሰንበት ትምህርት ቤት አባላት፣ የአካባቢውና በጎ አድራጊ ምእመናንና ምዕመናት ተገኝተዋል።

በአጭር ወራት ተሠርተው ለዛሬው ምርቃት የበቁት የተለያዩ የራስ አገዝ ልማት ሥራዎች በዋናናነት ለመንግሥተ ሰማይ ዓላማ ከማይጠፋው ዘር ለተወለድንበት ሕያው ተልእኮና አገልግሎት ቅጥረ ግቢውን ምቹ ከማድረግ ባለፈ የደብሩን የራስ አገዝ ልማት ከማሳደግ አኳያ ብዙ ጥቅም ያላቸው መሆናቸውን መሆኑ ብፁዓን አባቶችን ያስጎበኙት መጋቤ ሠናያት ኢ/ር አያሌው መሸሻ ገልጸዋል።

ብፁዓን አባቶች የተሠሩ ሥራዎችን በአካል በሁሉም ቦታዎች ከጎበኙ በኋላ በቤተ ክርስቲያኑ ቅጥር ግቢ ውስጥ የተለያዩ ዕጽዋትን ተክለዋል።

ከዚያም ወደ አዲስ መልክ ታድሶ አገልግሎት ወደ ሚሰጠው ሁለገብ አዳራሽ በማምራት የተለያዩ መርሐ ግብሮች ተከናውነዋል።

የእንኳን ደህና መጣችሁ መልእክት ያስተላለፉት የደብሩ አስተዳዳሪ መልአከ ገነት መዝገቡ ላቀው "ቤተ ክርስቲያናችን የሰጠችንን ኃላፊነት በአግባቡ መወጣት ስለአለብን ሰበካ ጉባኤውን፣ ካህናቱን፣ ምዕመናኑንና የሰንበት ት/ቤት ወጣቱን በጥበብና በብልሃት በመያዝ ምዕመናን ገንዘባቸውን በትክክለኛው ቦታ ላይ ለታቀደለትና ለታለመለት ዓላማ እንዲውል
በመደረጉ ዛሬ የተጎበኘው የሁላችንም የሥራ ውጤት ተባብሮ በመሥራት የተገኘ በመሆኑ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በዚህ ታሪካዊና ደማቅ በዓላችን ላይ ተገኝታችሁ እኛን ልጆቻችሁን ስለባረካችሁን ቅድስት ቡራኬያችሁ ትድረሰን" ብለዋል።

በደብሩ የተከናወኑትን ሁሉን አቀፍ ልማቶችን በሪፖርት መልክ ያቀረቡት የደብሩ ዋና ጸሐፊ ሊቀ ብርሃናት መዐዛ ተክለ ወልድ "የመንሳዊ ልማቱን በማስቀደም የእግዚአብሔርን መንግሥት ለመወረስ እንደሚገባ ሆነው ይኖሩ ዘንድ ምእምናን በመንፈሳዊ ዕውቀት እንዲጎለምሱ፣ በምግባር በሃይማኖት ፀንተው በክርስቲያናዊ ሕይወት ተግተው መኖርን እንዲያጠናክር ይቻል ዘንድ ስም ያላቸው የተለያዩ የቅዱስ ወንጌል ጉባኤያት በማከናወን ያመኑት እንዲጸኑና የኮበለሉም እንዲመለሱ ማድረግ ተችሏል ብለዋል።

አክለውም የተሠሩት የልዩ ልዩ ለልማቶችን ያብራሩ ሲሆን ከ2011 ዓ/ም ጀምሮ የነበረ የሊዝ ውዝፍ ዕዳ ተክፍሎ መጠናቀቁን፤የቅጽረ ግቢው አስፓልት ንጣፍ እንዲሁም አጽድ፤ ደረጃቸውን የጠበቁ መጠለያዎችና ወንበሮች፣ አጥርና የመኪና ማቆሚያ፣ አገልግሎቱን ተደራሽ ማድረጊያ ስክሪን ፣ ነአዳራሽ፣የክርስትና ቤትና የተለያዩ ቢሮዎች በአዲስ መልክ ታድሰው በምርቃት መብቃታቸውን አብራርተዋል።

አክለውም ወደፊት ሊሠሩ ስለታሰቡ ሥራዎች የተቀሱ ሲሆን በዋናናነት አሁን አገልግቶት እየሰጠ የሚገኘው ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን ጠባብ በመሆኑ በአዲስ ወይም ባለበት የማስፋፋት ሥራና የካህናት ማረፊያ ቤት ግንባታ ይገኙበታትል ብለዋል።

በደብሩ ለተሠሩት ሁሉን አቀፍ ልማቶች ትልቁን የሁሉም ልርብርብና ድጋፍ እንዳለ ሆኖ በተለይም አገልጋዮችንና ምእመናኑን በመፍቅር አስተባብረው እየመሩ ለሚገኙት መልአከ ገነት መዝገቡ ላቀው እንዲሁም በደብሩ ሰበካ ጉባኤ ምክትል ሊቀ መንበርነትና እግዚአብሔር በባረከላቸው ገንዘብም እያገለገሉ የሚገኙትን መጋቤ ሠናያት ኢ/ር አያሌው መሸሻ በብፁዓን አባቶች ፊት አመስግነዋል።

ቀጥሎም የምስጋና ምስክር ወረቀትና የወርቅ ወንጌል ለመጋቤ ሠናያት ኢ/ር አያሌው የምስጋና ምስክር ወረቀት ለደብሩ አስዳዳሪ እንዲሁም በልማቱ ላይ የሚነበብ ድርሻ ለነበራቸው በጎ አገልጋዮች ካህናትና ምዕምናን የምስጋና ምስክር ወረቀት ከብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት እጅ ተቀብለዋል።

የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ኅሩያን ዳዊት ታደሰ በበኩላቸው ደብሩ መዋቅሩን አክብረው የሚሠረቱ የሥራ መሪዎችና በበጎ ነገር ሁሉ ዋጋ የሚከፍሉ የሰበካ ጉባኤ አባላትና ምእምናን ያሉበት መሆኑ ጠቅሰው ለሥራቸውም ምስጋና አቅርበዋል።

አክለውም ክብርት ወ/ሮ አዳነች አቤቤ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ በተለያዩ የቤተ ክርስቲያን ልማቶች በብዙ አገልገልቶት እንዳልተለዩ ገልጸው ለሚያደርጉት መልካም ሥራ ምስጋና ይገባቸዋል ብለዋል።

ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የአዲስ አበባና ሀዲያ ስልጤ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ባዩትና በጎበኙት ተጨባጭ የልማት ሥራ አድንቀው በተለይም በቤተ ክርስቲያኑ በር አካባቢ የተሠራው ገላጭ ሥራ ለሌሎች አብያተ ክርስቲያናት አርአያነቱ የጎላ ነው ብለዋል።

በዚህም ከቤተ ክርስቲያን የንጽሕና ባሕርይና የአዲስ አበባ ከተማ ከሚከተለው የውበትና የጽዱነት መርሐ አኳያ የአብያተ ክርስቲያናት ቅጥር ግቢ ማሳመርና ለመንፈሳዊ አገልግሎት ምቹ ለማድረግ ይቻል ዘንድ የክፍላተ ከተማ ቤተ ክህነት ሥራ አስኪያጆችና የገዳማትና የአድባራት አስተዳዳሪዎች ጠንክረው መሥራት እንዳለባቸው ጥብቅ መመሪያ አስተላልፈዋል።

አያይዘውም የአቋቋሙ ሊቅ መልአከ ገነት መዝገቡ ላቀው እጃቸው መቋሚያና ጸናጽል ብቻ ሳይሆን የልማት መሳሪያዎችን ይዘው ልማትን ማሳመር እንደሚችሉ አረጋግጠዋል በዚህም እሳቸውንና መጋቤ ሠናያት እንዲሁም በዚሁ አገልግሎት የተሳተፉትን ሁሉ እናመሰግናለን እግአዚአብሔር በብዙ ይባርካችሁ ያላችሁንም ይጠብቅላችሁ በማለት ቡራኬ ሰጥተዋል።

ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በበኩላቸው ባዩት ልማት በእጅጉ መደነቃቸውን ገልጸው በዚህ መልካም ተግባር በብዙ የደከሙ እውነተኛ አገልጋዮችና ምእምናን ያመሰገኑ ሲሆን በተለይም የደብሩን አስተዳዳሪና መጋቤ ሠናያት ኢ/ር አያሌው መሸሻ በደብሩ ልማት ላደረጉት አስተዋጽኦና በጎ ሥራ አመስግነዋል።

በመጨረሻም ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ በሰጡት ቃለ ምዕዳን " ያሉ ሲሆን በገንዘባቸው ላይ አለቃ የሆኑ፤ ስላላቸው ብቻ ሳይሆን እንዲሰጡ እግዚአብሔር ያገዛቸውን መጋቤ ሠናያትን እዚአብሔር ይባርክህ ያለህን እንዲሁ ለመልካም ይበልልህ በማለት ባርከዋል።

ብፁዕነታቸው እንዳሉት ሁሉም ከእግዚአብሔር መሆኑን አምኖ የሚሰጥ ሰው በብርቱ ያተርፋል የእሱ የሆነው ነገር ሁሉ ይባረክለታል የሚለው በተግባር የታየው የአባቶቻችን ሕይወት በመሆኑ በሁሉም መንገድ ያገለገላችሁ ሁሉ እግዚአብሔር ይቅደምላችሁ በማለት መርቀዋል።

አያይዘውም መርሐ ግብሩን በጸሎት አጠናቀዋል።

🔵የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ
ስለ አንዲት ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን

🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚 https://www.facebook.com/AddisAbabaDiocese?mibextid=2JQ9oc

ከዚህ በተጨማሪ በሌሎች የበይነ መረብ አማራጮች ለመከታታል
በቴሌግራም: https://t.me/AddisAbabaDiocese

በዩቱዩብ: http://www.youtube.com/

በቲውተር: https://twitter.com/AADioceseMedia/media
በቲክቶክ:http://tiktok.com/
መጠቀም ይችላሉ።

የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ  ታዕካ ነገሥት በአታ ለማርያም ገዳም የመምህራንና የቀሳውስት ማሰልጠኛ መንፈሳዊ ትምህርት ቤት  በ2017 ዓ.ም ትምህርታቸውን  ያጠናቀቁ ደቀ መዛሙርትን  ብፁዓን ...
19/07/2025

የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ ታዕካ ነገሥት በአታ ለማርያም ገዳም የመምህራንና የቀሳውስት ማሰልጠኛ መንፈሳዊ ትምህርት ቤት በ2017 ዓ.ም ትምህርታቸውን ያጠናቀቁ ደቀ መዛሙርትን ብፁዓን አበው ሊቃነጳጳሳት በተገኙበት በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ጽርሐ ተዋሕዶ አዳራሽ በማስመረቅ ላይ ይገኛል።
©EOTCTV

ሐምሌ ፲፪/፳፻፲፯ ዓ/ም የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ

 #ቀጥታ ሥርጭት /በደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ከ70 ሚሊዮን በላይ ወጪ የተደረገባቸው የተለያዩ የራስ አገዝ ልማቶች ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅና ብፁዕ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋ...
19/07/2025

#ቀጥታ ሥርጭት /በደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ከ70 ሚሊዮን በላይ ወጪ የተደረገባቸው የተለያዩ የራስ አገዝ ልማቶች ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅና ብፁዕ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ እንዲሁም ብፁዕ የአዲስ አበባና ሀዲያ ስልጤ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በተገኙበት የምርቃት መርሐ ግብር እየተከናወነ ነው፡፡
ሐምሌ ፲፪/፳ ፻ ፲ ፯ ዓ/ም የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ

EOTC AAD LIVE

Address


Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ አገልግሎት/Addis Ababa Diocese Media Service posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ አገልግሎት/Addis Ababa Diocese Media Service:

Shortcuts

  • Address
  • Telephone
  • Alerts
  • Contact The Business
  • Claim ownership or report listing
  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share