Ras Becky Satenaw ራስ ቤኪ ሳተናው

Ras Becky Satenaw ራስ ቤኪ ሳተናው የምፈራው ውሸትን ብቻ ነው።

እንደ ATM ያለ ገንዘብ የማይንቀሳቀሱት የዘመኑ ዘማሪዎች ፣ በክፍያ የሚገባው የመዝሙር ኮንሰርትና የሆቴል ቤት ዝንቦች።=========================================ከሶስ...
23/07/2024

እንደ ATM ያለ ገንዘብ የማይንቀሳቀሱት የዘመኑ ዘማሪዎች ፣ በክፍያ የሚገባው የመዝሙር ኮንሰርትና የሆቴል ቤት ዝንቦች።
=========================================

ከሶስት ሳምንት በፊት ሊደረግ የነበረዉ የመዝሙር ኮንሰርት ( የሙዚቃ ብንለዉ ይቀላል ) ይህ ዝግጅት ሊደረግ ታስቦ የነበረዉ በጊዮን ሆቴል ነበረ። ችግሩ በጊዮን ሆቴል መደረጉ አይደለም ፤ በእርዳታ ስም … በስመ ክርስትና እግዚአብሄርን ለማምለክ በክፍያ የሚገባበት ኮንሰርት ማዘጋጀት አንድም እግዚአብሄርን አለመፍራትና ህዝበ ክርስቲያኑን መናቅ ነው። የሆኑ ግሩፖች እንደፈለጉ እየተነሱ ህዝቡንስ እስከመቼ ነዉ የሚያሞኙት?

ለእኔ እነዚህና መሰሎቻቸው የATM ማሽኖች ናቸው ያለ ብር የማይጮሁ ያለ ብር የማይተነብዩ ናቸው። ከጅምሩም Gion ሆቴል ላይ ለምን ማዘጋጀት ተፈለገ? የዘፈን ኮንሰርት አይደል or festivals። በጣም ያልጠበኲትና ያስደነገጠኝ ደግሞ በጣም የማከብራቸዉና ብዙ ምእመን የተባረከባቸዉ እንደ ዘማሪ ወርቅነህ አላሮና ዘማሪ እንዳለን መመልከቴ ነዉ 🥹

First of all በእርዳታ አስታኮ ሆቴል አዳራሽ ተከራይቶ ከምእመኑ የመግብያ ማስከፈል ምን ይሉታል? የተሰበሰበውን ገንዘብ ገቢና ወጪውን የትኛው አካል ነው የሚቆጣጠረው? ይህንን ፕሮግራም በአብያተ-ክርስቲያናት እንደ መካነ-ኢየሱስ ፣ ቃለ-ህይወት ፣ ሙሉ-ወንጌል ባሉ ሰፋፊ Church ውስጥ ለምን ማድረግ አልተፈለገም? የፕሮቴስታንት አብያተ ክርስቲያናትስ ይህንን ተግባር ከማውገዝ ስለምን ተቆጠቡ?

ዘመን አፈላሽና የሀሰተኛ ነብያት ቸርች አዳማቂዎች እንደ ይሳቅ ሰዲቅ ፣ አቤኔዘር ፣ ይትባረክ እና መሰሎቻቸዉ ያለ ብር የማይንቀሳቀሱ የATM ማሽኖች ፣ ከትልልቅ ሆቴሎች ወንበሮች ላይ የማይጠፉ የሆቴል ቤት ዝንቦች ……… ናቸወ። ታርጌታቸዉ በትላልቅ ሆቴሎች ላይ የሚያገኙትን ባለ ሀብቶች ና ዲያስፖራዎችን ነው ፤ በተለይ ደግሞ ሴቶችን ታርጌት ያደርጋሉ። እንደ Sheraton, Kaleb, Saro Maria, Harmony, Haile Grand እና Mado ሆቴሎች ላይ አታጣቸውም።

ከሴቶች በላይ ይኳኳላሉ። ትክክለኛ መንፈሳውያን ቢሆኑ ኖሮ ከሰኞ-ከሰኞ ቸርች ላይ ይገኙ ነበር ነገር ግን they are money 💰 💵 minded ! ታርጌታቸው በሀብታም ሰርጐች ላይ ከ50 ሺ የማያንስ ገንዘብ እየተቀበሉ የሰርግ ስራ መስራት ነው ፤ እሱንም የተመረጡ ሆቴሎች ካልሆነ በስተቀር ቀጥረውም አይመጡም። በጣም የሚገርመው አብዛኛው የዘመኑ ዘማሪዎች ሁለተኛ ትዳራቸው ላይ ያሉና ከትዳራቸዉም ውጪ በዉስልትና የወለዱ ናቸው።

ብዙ ሰዉ ስላላወቀ ቀኑ ተራዝሟል የተባለለትን በክፍያ የሚገባበትን የመዝሙር ኮንሰርት ቢደረግ እንኳን ባለመግባት አጉል ልምምድን እናስቀር። ቅልጥም ባገኙበት የሚጮሁ ዘማሪ ተብዬዎችን አደብ እናሲዝ። ተጨማሪ ሚስጥራቸዉን ደግሞ በYouTube በቪዲዮ ከሰሞኑ እከሰታለው። ዝም ያልነዉ ስለማናውቅ አይደለም 🙈🙉🙊

ማንችስተር ዩናይትድ በጥር የዝውውር መስኮት ሶስት ተጫዋቾች እነ ካዝሜሮን እና ቫራንን ጭምር ለመሸጥ ይፈልጋል።ቀያይ ሴጣኖቹ ተጫዋቾቻቸው ራፋኤል ቫራን፣ ጄደን ሳንቾ እና ካዜሚሮን በጥር የዝ...
09/12/2023

ማንችስተር ዩናይትድ በጥር የዝውውር መስኮት ሶስት ተጫዋቾች እነ ካዝሜሮን እና ቫራንን ጭምር ለመሸጥ ይፈልጋል።
ቀያይ ሴጣኖቹ ተጫዋቾቻቸው ራፋኤል ቫራን፣ ጄደን ሳንቾ እና ካዜሚሮን በጥር የዝውውር መስኮት ለመሸጥ የዝውውር ሂሳብ ለመስማት እያሰቡ ነው። እንደ The independent ዘገባ ከሆነ ከአሰልጣኝ ኤሪክ ቴን ሀግ ጋር ግጭት ውስጥ የገባው ጄደን ሳንቾ፣ ቋሚ ቦታውን ያጣው ራፋኤል ቫራንን ሸጠው በካዜሚሮ ቦታ በኩል ደሞ እንደሱ ተመሳሳይ አጨዋወት ያለው አማካይ ማስፈረም ፈልገዋል።
አሰልጣኝ ኤሪክ ቴን ሀግ እነዚህን ተጫዋቾች መሸጥ የሚፈልጉት በጥሩ የዝውውር መስኮት እንደሆነ የተገለፀ ሲሆን በመልበሻ ክፍል ውስጥ ከተለያዩ ተጫዋቾች ድጋፍ እያጡ ስለሚገኙም እንደሆነ ዘገባው አክሏል።

🚨 19 ግንቦት 2014 ማንቸስተር ዩናይትድ ልዊስ ቫንሀልን ዋና አሰልጣኝ አድርጎ ሾመ። ሉዊስ ቫንሀል ኤሪክ ቴን ሃግ አሁን እየገጠመው ያለውን ተመሳሳይ ችግር ገጥሞት እንደነበረ መቼም አትር...
05/12/2023

🚨 19 ግንቦት 2014 ማንቸስተር ዩናይትድ ልዊስ ቫንሀልን ዋና አሰልጣኝ አድርጎ ሾመ። ሉዊስ ቫንሀል ኤሪክ ቴን ሃግ አሁን እየገጠመው ያለውን ተመሳሳይ ችግር ገጥሞት እንደነበረ መቼም አትርሱ ከዚያም በጆዜ ሞሪንሆ ተተክተዋል። ግንቦት 27 ቀን 2016 ማንቸስተር ዩናይትዶች ጆዜ ሞሪንሆ ዋና አሰልጣኝ አድርገው ሾሙ፣ ተመሳሳይ ችግር አጋጥሞታል እና በኦሌ ጉናር ሶልሻየር ተተካ። ነገር ግን ጆዜ ከመሄዱ በፊት ግን ችግሩ ምን እንደሆነ ፍንጭ ሰጥቷል።

እ.ኤ.አ. ማርች 28 ፣ 2019 ማንቸስተር ዩናይትድ ኦሌ ጉናር ሶልሻየርን ዋና አሰልጣኝ አድርገው ሾሙ ፣ OGS ተመሳሳይ ችግር አጋጥሞታል እና በ Ralf Rangnic ተተክቷል። ህዳር 29 ቀን 2021 ማንቸስተር ዩናይትድ ራልፍ ራንኒክን በጊዜያዊ አሰልጣኝነት ሾሙ። ራልፍ ተመሳሳይ ችግር አጋጥሞታል, ራልፍ ችግሩን ተረድቶ ምን መደረግ እንዳለበት መፍትሄ ሰጥቶ የነበረ ቢሆንም ቦርዱ ራልፍ የሰጠውን መፍትሄ ችላ ብሎታል ነገር ግን እሱን በማሰናበት በኤሪክ ቴን ሃግ ለመተካት መረጡ።

ኤፕሪል 22 ቀን 2022 ማንቸስተር ዩናይትድ ኤሪክ ቴን ሀግን ዋና አሰልጣኝ አድርጎ ሾመ። በኤሪክ ቴን ሃግ ጊዜ ተመሳሳይ ችግር እንደገና ታይቷል እናም በዚህ ጊዜ ሁላችንም ወደ ታሪክ ተመልሰን ይህንን ችግር በትክክል መተንተን አለብን። ⛳ በመጀመሪያ ችግሩ ምንድን ነው? አዲስ ሥራ አስኪያጅ ሲቀጠር እነዚህ ሁለት የታወቁ ትልልቅ ልጆች በጥቂት ጨዋታዎች ላይ ንፁህ ሆነው ይጫወታሉ እና በኋላም ከአሰልጣኙ ጋር ይላመዳሉና ከእነሱ ሀሳብና እቅድ ውጪ የሆነውን አሰልጣኝ blackmail በማድረግ ያስባርራሉ።

አሰልጣኙ ጉዳዩን ወደ ሚዲያ ለማቅረብ ሲሞክር ንፁህ ሆነው በደጋፊና በሚዲያ ፊት በመቅረብ ማናጀሩ ተጫዋቾቹን በደል እየፈፀመ ያለ መጥፎ አሰልጣኝ አድርገው እንዲመለከቱት በማድረግ የስም ማጥፋት ይፈፅማሉ። አሁንስ ይበቃል! MUTD ለራሽፎርድ እና አንቶኒ ማርሻል ይበቃል ሊባሉ ይገባል አመለካከታቸው የማይረባ እና ሙያዊ ብቃት የጎደላቸው ስለሆኑ የመውጫውን በር በአስቸኳይ ሊያሳዩዋቸው ይገባል!

አሰልጣኙን ማባረር እና ሌላ አሰለሰጣኝ መቅጠር የዚህ ጥፋት ፍጻሜ ላይሆን ይችላል ነገር ግን በማንቸስተር ዩናይትድ ውስጥ የመወሰጫውን በር ሊያሳዪዋቸው የሚገቡ የተለመዱ ፊቶች አሉ። መጀመሪያ እነዚህን ሁለት ፊቶች ማሸሽ! የናፈቀኝ ነገር አለ?😎

ድኃ በፍፁም ሊያደርጋቸው የማይገቡ 5  ነገሮች1, ምንም አይነት ጦርነት ቢነሳ የሚወድምብህ ንብረት የምታጣው መሬት ወይም ቤት ስለሌለ በጦርነት አትሳተፍ። የቻልከውን ያህል ሸሽተህ ጦርነት የ...
28/07/2023

ድኃ በፍፁም ሊያደርጋቸው የማይገቡ 5 ነገሮች

1, ምንም አይነት ጦርነት ቢነሳ የሚወድምብህ ንብረት የምታጣው መሬት ወይም ቤት ስለሌለ በጦርነት አትሳተፍ። የቻልከውን ያህል ሸሽተህ ጦርነት የሌለበት አካባቢ ኑር። ኢትዮጵያም ኖርክ ቻድ ድኃ እስከሆንክ ድረስ መብትም ሀገር የለህምና ራስህ ላይ አተኩር። ንብረትና ሀገር ያላቸው እንዲዋጉ ተውላቸው።

2, በፍፁም ጆሮህንና ሃሳብህን በየትኛውም ወገን ለተሰለፈ ፖለቲከኛ አትስጥ። በአንተ ላይ ተንጠልጥሎ ከርሱን መሙላትና ነገ ስልጣን ሲይዝ ሊግጥህ ለሚፈልግ የዚህ ሀገር እከካም ፖለቲከኛ አይደለም ደምህን አይነምድርህንም ልትሰጠው አይገባም።

3, ለኃይማኖት ተቋማት መገንቢያ፤ ለኃይማኖት መምህራን ድጋፍ በሚል ሰበብ ካለኝ ላይ ብሰጥ ይባረክልኛል እያልክ ለፍተህ ያገኘኸውን ትንሽ ገንዘብ በፍፁም አትስጣቸው። ፈለጣቸው ካስጨነቀህ የምታመልከው አምላክ ይስጥህ እንጂ እኔ ከየት አመጣለሁ በላቸው

4, ተቃውመህ የምትቀይረው መንግስት ደግፈህ የምታነግሰው ፖለቲከኛ የለምና ከድጋፍም ሆነ ከተቃውሞ ፖለቲካ በቻልከው አቅም ራቅ። ፖለቲካዊ ወሬዎች ሲነሱብህ መልስህ ምን አገባኝ ብቻ መሆን አለበት። ወዳጄ ፖለቲካ ለፖለቲከኛው መተዳደሪያ ነው። እስኪ አእምሯቹህ ውስጥ ያለውን ፖለቲከኛ አስቡት፤ ፖለቲካ በቃኝ ቢል ሌላ መተዳደሪያ ሙያ አለው?

5, ገንዘብ ባይኖረኝም ጤና አለኝ ጲሪሪም ጳራራም እያልክ ድህነትህን አትኩራበት። ድህነትህን ጥረህ ግረህ ያገኘኸው የልፋትህ ውጤት አስመስለህ አትመፃደቅበት። ድኃ እስከሆንክ ድረስ የምታጣው ነገር የለምና ውሳኔዎችን ለመወሰን አትፍራ፤ ከዚህ በላይ ኪሳራ አይደርስብህም፤ ለመለወጥ ጣር፤ አጋጣሚዎችን ሁሉ ተጠቀም።

ዳዊት ድሪምስ 🤝 የብልፅግና ወንጌል ፕሮማክስ or High Copy ነው።የስነ-ልቦና ችግር ግዜ የሚወስድና ህክምና የሚፈልግ የጤና እክል ነው፤ ትታከመዋለህ እንጂ ዳዊትና ዳግማዊት ፣ ወዳጀረነ...
05/07/2023

ዳዊት ድሪምስ 🤝 የብልፅግና ወንጌል ፕሮማክስ or High Copy ነው።

የስነ-ልቦና ችግር ግዜ የሚወስድና ህክምና የሚፈልግ የጤና እክል ነው፤ ትታከመዋለህ እንጂ ዳዊትና ዳግማዊት ፣ ወዳጀረነህና ማንያዘዋል እሸቱ በሚገነቡልህ የውሸት ማንነትና የቃላት ጋጋታ አትፈታውም... በነሱ ቅቤ ምላስም ድህነትህን ትተህ በሮኬት ፍጥነት ከበርቴ አትሆንም! እነሱ ራሱ ሀብታም የሆኑት አንተ እነሱን ለማየት በምትከፍለው ብርና የዩትዩብ ቪው ነው! አለቀ ደቀቀው ... መራራ እውነት ነው ዋጠው።

ወዳጄ ነገርየው በገዛ ብርህ አንተን የማደንዘዝና በሂደት የምትከተለውን እምነት የመሸርሸር ቢዝነስ ነው።

የአንዳንድ አነቃቂዎች ነገር ይገርማል። ዳዊት ድሪምስ ችግርህን ለሰው አትንገር ምክያንቱም እነሱ የራሳቸው ችግር አለባቸው ይላል።

"እንደ ኢትዮጵያ ባለ የዳበረ ማህበራዊ ኑሮ ያለበት ሀገር፣ በእቁብ፣ በእድር እና በደቦ የሚረዳዳ ማህበረሰብ ውስጥ፣ የሰውን ችግር እህ ብሎ የሚሰማ ማህበረሰብ ውስጥ ችግርህን ለሰው አትንገር ብሎ ምክር ምን ይሉታል? ማለት ያለብህ ችግርህን ለማን እንደምትነግር ምረጥ ነው። ያለዚያማ ላንተስ ለምን ችግር አለብኝ ብሎ ለስልጠና ይከፍለሃል? ...... ችግሩን አውጥቶ ሳይናገር የሚብሰለሰል ሰው ወይ ራሱን ያንቃል አሊያም ያብዳል።"

የአዲሱ ዘመን እንቅስቃሴ የሃይማኖትነት መስፈርትን ያሟላል፤ አያሟላም የሚል ካለ የ15 ልዩ ዲሲፒሊኖች ባለቤት የሆኑ የሃይማኖት ፍልስፍናና የማህበረሰብ ሳይንስ ምሁራን እኤአ በ2014 ዓ ም በሕብረት የፃፉትን "NEW AGE SPIRITUALITY: Rethinking Religion" መፅሐፍን ማንበብ ይችላል...እንቅስቃሴው ሃይማኖታዊ መሆኑን ይበልጥ ለመረዳት ሌሎች የአንትሮፖሎጂ እና Philisophy of Religion ምሁራንም የደረሱትንና በጥናት ላይ የተመሠረቱ መፅሐፍትን ጭምር በዋቢነት ማቅረብ ይቻላል።

እንግዲህ የአዲሱ ዘመን እንቅስቃሴ በሃይማኖትነት ከተፈረጀ፤ የኢትዮጵያ ሕገመንግሥት በአንቀፅ 11 ንዑስ አንቀፅ 1 እና 2 ላይ በተከታታይ "መንግስትና ሃይማኖት እንደሚለያዩ" እና "መንግስታዊ ሃይማኖት" የሚባል ነገር እንደሌለ በግልፅ ያሰምራል።

በተቃራኒው በታዋቂው ካናዳዊዉ የስበት ሕግ አስተማሪ ቦብ ፕሮክተር አማካይነት አያሌ ሥልጠናዎችን እንደወሰደ የነገረን ዳዊት ድሪምስ የተባለ ግለሰብ ሃይማኖታዊ አስተምህሮውን "በመንግስታዊ ቢሮዎች፣ በሚኒስትር መስሪያ ቤቶች፣ በከንቲባ ፅ/ቤቶች፣ በክፍለከተማና በወረዳ መንግስታዊ መዋቅሮች ውስጥ በሴሚናርና በሥልጠና መልክ (በስመ-ሞቲቬሽን ጭምብል ሸፍኖት) እንደሚያሰራጭ በ"ትልቅ ሕልም አለኝ" መፅሐፉ ውስጥ ይፋ ማድረጉ ይታወሳል።

ከዚህም በላይ ዳዊት ድሪምስ ባሰለጠናቸው ተከታዮቹ አማካይነት ሃይማኖቱን ወደፊት በሀገር አቀፍ(መንግስታዊ ሃይማኖት ሊሆን ማለት ነው) ደረጃና በአፍሪካ አህጉርም ጭምር እንደሚያስፋፋ በመፅሐፉ አስቀምጧል።

ሆኖም የአዲሱ ዘመን ሃይማኖታዊ አስተምህሮን በመንግስታዊ ተቋማት ማሰራጨትና አልፎ ተርፎም መንግስታዊ ሃይማኖት ለማድረግ የሚደረገው እንቅሰቃሴ የኢትዮጵያን ሕገመንግሥት ሙሉ በሙሉ የሚፃረር ድርጊት በመሆኑ ሊኮነን የሚገባው አካሄድ ነው።

እንደሚታወቀው የአዲሱ ዘመን ሃይማኖታዊ እንቅስቃሴን ዳዊት ድሪምስ በመፅሐፉ በአፍሪካ አህጉር ደረጃ ቢገድበውም የሃይማኖቱ ዋና ግቡ የተባበሩት መንግስታትን ድርጅትንና አሜሪካንን በመጠቀም የዓለም መንግስትን ማቋቋም(World Government) እንደሆነ የአደባባይ ምስጢር ከሆነ ሰነባብቷል።

እነዚህ ሰዎች የተደራጁ ማፊያዎች ናቸው! Brain wash እያደረጉና እያደነዘዙህ የሚበሉ ሞላጫ ሌቦች ናቸው። በሞቲቬሽን ሰበብ ሊዘርፉ የቋመጡ ሌቦች ናቸው። እስካሁንም ብዙ ዘርፈዋል። በቃችሁ የሚላቸው የህግ አካል እስካሁን አለመኖሩ በጣም ይገርመኛል። ዳዊት ድሪምስ፣ ማንያዘዋል፣ ዳግማዊት እና ሌሎቹም የሞቲቬሽን ማፊያዎች በሞቲቬሽን ሽፋን እቅዳቸው ሌላ ነው። ህዝቡን መዝረፍ ነው የተያያዙት። ይሄንን ለመፃፍ ያነሳሳኝ ብዙ ምክንያት አለኝ። ከምክንያቶቼ አንዱ ደግሞ የሚያስከፍሉትን የገንዘብ መጠን ከሰሞኑ መስማቴ ነው። እነ ዳዊት ድሪምስ ለቀናት ብቻ በሚቆየው ስልጠናቸው ለ 1 ሰው ከ 5,000 እስከ 25,000 ብር ነው የሚያስከፍሉት። የኑሮ ውድነት፣ የኢኮኖሚ መዋዠቅ የሚያንከራትተውን ወገኔን ሊበሉ ያሰፈሰፉ ጅቦች ናቸው። ሲጀመር መርሀግብራቸው ይሄን ያህል ክፍያ ሊከፈል አይገባውም። የነሱን ስልጠና ለመሰልጠን 100 ብርም ሲበዛበት ነው። ለ 100 ብር ራሱ የማይመጥን ስልጠና ነው የሚሰጡት። ስልጠናቸውና የሚያስከፍሉት ገንዘብ አይመጣጠንም። በቀጥታ ህዝቡን መዝረፍ ነው የተያያዙት። በተለይ ይሄ ዳዊት ድሪምስ የሚባለው ሰውዬ ምኑም አይጥመኝም። እንዲሁ አይቼው አጭበርባሪ እንደሆነ መገመት እችላለሁ። በነገራችን ላይ እነዚህ ሰዎች ደላሎች አሏቸው። ወጣቶችን እንዲያመጡና እንዲመለምሉ የሚያሰማሯቸው ደላሎች አሉ። በእነዚህ አማካኝነት YouTube ላይ በቀላሉ የሚገኝን ነገር ሞቲቬሽን እያሉ ለ 1 ሰው እስከ 25,000 ብር ያስከፍላሉ። ለዛውም ለሳምንት ብቻ ለሚቆይ ስልጠና። ሌቦች ናቸው! እነዚህን ስርዓት የሚያሲዝልን አንድ የህግ አካል አለመኖሩ በጣም ይገርማል።

ዳዊት ድሪምስ አዲስ ባሳተመው መፅሐፉ ገፅ 312 ላይ .....መንገድ ላይ ወድቆ ያገኘኸውን ገንዘብም ሆነ ማንኛውንም ነገር ልክ አንተ በትኩረት ስለፈለክና ስላገኘህ በስበት-ህግ እንዳገኘኸውና የራስህ ንብረት እንደሆነ አድርጎ ማስተማር .... ከሐይማኖታዊም ሆነ ማህበራዊ እሴቶች ውጭ የሆነ the new world ሀይማኖት ነው። ወንድሜ ለአንተ ለኢትዮጵያዊው 5 ሺ ብር ደሞዝ ተከፋይ ሆነህ ፣ 10 ሺ ብር የቤት ኪራይ ከፍለህ ፣ ምግብ ቀለብህን ወሩን ሙሉ ችለህ ፣ የትራንስፖርትና የአንዳንድ ወጪዎችህን ሸፍነህ ፣ ድንገት ቢያምህ የህክምና ከፍለህ ፣ ቤተሰብ ረድተህ ለምትኖረው ለአንተ ለታታሪው ኢትዮጵያዊ ወንድሜ የዳዊት ድሪምስም ሆነ የእነዚህ ሞጭላፋ ሌቦች ምክር ቀልድና ማላዘን ነው የሚሆንብህ። እንደ እውነቱ ከሆነ አንተ ከወር ወር በ5ሺ ብር ይሄንን ሁሉ ወጪ አውጥተህ የምትኖረው አስማተኛው ልጅ ነበርክ ለእነሱ ምክር መምከር ያለብህ።

ወዳጄ ራስህን ከዘመናዊ ሌቦች ጠብቅ።

  😢😢😢(እጅግ አሳዛኝ እውነተኛ ታሪክ) አንድ የሞላለት ባለጠጋና ልጁ ቅንጡና ውድ እቃዎች ወደሚሸጡበት ሞል ሄዱ። የሚሸምቱትን ሸማምተው ወደ መኪናቸው ሲመለሱ አንድ የተቀዳደደ ልብስ የለበሰ...
22/06/2023

😢😢😢

(እጅግ አሳዛኝ እውነተኛ ታሪክ)

አንድ የሞላለት ባለጠጋና ልጁ ቅንጡና ውድ እቃዎች ወደሚሸጡበት ሞል ሄዱ። የሚሸምቱትን ሸማምተው ወደ መኪናቸው ሲመለሱ አንድ የተቀዳደደ ልብስ የለበሰ ልጅ ወደነሱ ቀረብ ብሎ.....

"አባባዬ እርዳኝ፣ የምለብሰው ልብስ ሰውነቴ ላይ አለቀ...ሃሩርና ቁር ተፈራረቁብኝ" አለው።

ሀብታሙ ሰው ልጁን መልከት ሲለው ደነገጠ። እውነትም በጣም የታረዘ መሆኑን አለባበሱ ይናገራል።

"ስንት አመትህ ነው የኔ ልጅ?" ሲል በርህራሄ ጠየቀው።

"አስር ዓመቴ ነው።"

"እንደዛ ከሆነ ጥሩ ነው፤ የኔም ልጅ አስር አመቱ ነው። አሁን የተገዙለት አዳዲስ ልብሶች ልክህ ይሆናሉ ማለት ነው።" አለና...........

ወደራሱ ልጅ ዘወር ብሎ
"የኔ ልጅ ለዚህ ብላቴና ዛሬ የተገዙልህን ልብሶችህን በመስጠት ደግነትህን ታሳየኛለህ አይደል? ነገ መጥተን ላንተ ሌላ እንገዛለን" አለው።

"ደስ ይለኛል!" ሲል ልጁም ተስማማ።

አባትም የገዟቸውን ልብሶች እያወጣ ለዛ ደሃ ልጅ ሲሰጠው በልጁ ፊት ላይ የደስታ ብርሃን ፍንትው ብሎ ሲበራ አየና.....
"የት ነው የምትኖረው ግን?" ሲል ጠየቀው።

ደሃው ህፃንም "ከፊት ለፊት ካለው ድልድይ ስር በስተቀኝ በኩል ባለው ፕላስቲክ ቤት ውስጥ" ሲል መለሰ።

ቃለ-ምልልሳቸው በዚሁ አብቅቶ ሃብታሙ ለጋስና ልጁ ወደ መኪናቸው ገብተው እስኪሄዱ ያምስኪን የተሰጠውን ልብስ በደረቱ አጣብቆ አቅፎ በደስታ እያያቸው ነበር.......

ከሶስት ወር በኋላ ያ ሃብታም ያንን የጎዳና ህፃን ፈልጎት መጣና ወደ መኪናው በመውሰድ በትልቅ ሻንጣ የታጨቁ ልዩ ልዩ አልባሳትና ጫማዎችን ሲሰጠው እንዲህ አለው......

"እነዚህ ልብሶችና ጫማዎች የልጄ ነበሩ አሁን ግን ያንተ ናቸው" ሲል ሃዘን ባደበዘዘው ፈገግታ ታጅቦ ነገረው።

ደሃው ህፃን የደስታ እንባ እያነባ

"አባባ ያንተ ልጅስ? ምን ይለብሳል?" ጠየቀ።

"አንተ ትንሽ ልጅ አትጨነቅ። የኔ ልጅ እነዚህን አልባሳት አሁን አይፈልጋቸውም....ምክንያቱም አሁን እሱ በገነት ውስጥ ነውና፤ የኔ ጣፋጭ ትንሹ ልጅ ከሳምንታት በፊት በካንሰር ህመም ህይወቱ አልፋለች። ከካንሰር ጋር እየታገለ ሶስት አመት ኑሯል....እናም ከኛ ጋር እንደሚለያይና ትቶን እንደሚሄድ እናውቅ ነበር። የኔ ጣፋጭ ልጅ በመጨረሻው የመለያያ ጊዜያችን እንዲህ አለኝ 'አባ አንተንና እማዬን የምለይበት ጊዜ በጣም ቀርቧል....ከንግዲህ ዳግም የምንገናኘው በገነት ብቻ ነው። አባ የኔ የሆኑ ነገሮችን በሙሉ ለዛ በድልድዩ ስር ለሚኖረው የጎዳናው ልጅ ስጥልኝ' ብሎኝ ተለየኝ።

አባት ለተወሰነ ጊዜ እንባውን እያፈሰሰ ንግግሩን ገታ።

" የኔ ልጅ ምናልባት ደሃ ስለሆንክ ታዝን ይሆናል። ግን አስታውስ ጤናን እና ህይወትን የታደልክ ሃብታም መሆንህን እንዳትረሳ። እኔ ያለኝ ገንዘብና ቁሳዊ ሃብት ልጄ ከገጠመው የጤና ድህነትና በመጨረሻም ከሞት አልታደገውም...እናም እልሃለሁ እያንዳንዳችን ያጣናቸው ነገሮች ቢኖሩም በጃችን ያሉና ምንም ያልመሰሉን ግን ሌላው ያጣቸው፣ የተቸገረባቸው፣ የተሰቃየባቸው ብዙ ድልብ ሃብቶች አሉ...እነሱን በደንብ ተንከባክበን እና እያመሰገንን በመጠበቅ የጎደሉንን ደግሞ መፈለግ ነው ያለብን...." ሲል በተሰበረ ልብ መከረው።
ልጀ ደስ ካለህ ከኔ ጋር ብትሆንና የልጀ ማስታወሻ ብትሆነኝ ደስ ይለኛል አለ አባት እንባ እየተናነቀው

ልጅም በአውንታ ግንባሩን ነቀነቀው

ሁለቱም ደስታና ሃዘን ተደራርበው ያመነጬባቸውን የንባ ዘለላዎች እየጠረጉ ወደ ቤት አመሩ ......😢
________________________________________
መልካም ቀን ለሁላችሁም❤❤❤❤

  ።የሰሞኑ የ12ተኛ ክፍል ውጤት አነጋጋሪነቱ እንደቀጠለ ነው። በኢትዮጵያ ታሪክም እንደዚህ አይነት ስርዓት ያለው የፈተና አሰጣጥና የፈተና ውጤት ተመዝግቦ አያውቅም። እኔ በበኩሌ በተገኘው ...
30/01/2023




የሰሞኑ የ12ተኛ ክፍል ውጤት አነጋጋሪነቱ እንደቀጠለ ነው። በኢትዮጵያ ታሪክም እንደዚህ አይነት ስርዓት ያለው የፈተና አሰጣጥና የፈተና ውጤት ተመዝግቦ አያውቅም። እኔ በበኩሌ በተገኘው ውጤት እጅግ በጣም ተደስቻለው ፤ ምክንያቱም ጊዜውንና ሰዓቱን በsocial media ላይ ሲቧልት የነበረ ይመነጠራል ፤ በትክክል የሰራ ደግሞ ያልፋል ..... አለቀ ደቀቀ።

ከዛሬ 5 አመት በፊት በአአ ውስጥ በሚገኝ በአንድ ታዋቂ ት/ቤት ውስጥ በአስተማሪነት ከelementary - high school ድረስ የማስተማር እድሉን አግኝቼ ሰርቻለው። ይህም ት/ቤት Gjbson Youth Academy ይባላል ፤ የባለ ስልጣንና የባለሀብት ልጆች የሚማሩበት ት/ቤት ነው። በስነምግባርና ተማሪዎችን በማነፅ ደረጃ በጣም ተመራጭ የሆነ ት/ቤት ነው። በትምህርት ጥራትና አሰጣጥ ግን ጥያቄ ያለበት ነበረ።

በኢትዮጵያ ውስጥ ተማሪዎቻቸውን ካሳለፉ ት/ት ቤቶች ከ1-20 ካሉት ውስጥ አለመካተቱን ሳይ ሳቄ አመለጠኝ። "አለባብሰው ቢያርሱ በአረም ይመለሱ ነው ተረቱም።" በዚህ ት/ቤት ውስጥ የባለ ስልጣንና የባለሀብት ልጆች ከመማራቸው የተነሳ መምህራን የጣሏቸውን ተማሪዎች ት/ት ቤቱ በራሱ ስልጣን ያሳልፋቸው ነበር። ሆን ተብሎ የክረምት ት/ት በማለት 10 ወር ሙሉ ተምሮ ያላለፈን ተማሪ በ1ወር ትምህርት ተምሮ እንዲልፍ ይደረግ ነበር። ይኸው ዛሬ በዘመነ ፕ/ር ብርሐኑ ነጋ ጊዜ ነገሩ በሙሉ ተዘርግፎ ወጥቷል።

በመጨረሻም እንደ አንድ መምህር እንደነበረ ሰው ምን ይሰማሃል ካላቹኝ? ደስታ ..... እላቹሃለው .... እንኳን ወደቁ ፣ እሰይ ወደቁ እላቹሃለው። የመውደቅን ህመም የማያውቅ ውድቀትን ከይፈራም ፤ ሰርቶ እንጂ ሰርቆ የሚያልፍ ትውልድ ለሀገርም ለቤተሰብም ሸክም ነውና ይህ የወደቀውን የትምህርት ስርዓታችንን የምናነሳበት ወቅት ነው። ነገ ተመርቆ የሚወጣ ተማሪ ራሳቸውን የሚፈጥሩና ሀገራቸውን የሚሰሩ መሆን አለባቸው።

 ? ፍፁም አምላክ ... ፍፁም ሰው የሆነው ክርስቶስስ ስለምን ተጠመቀ? ይሄ ጥያቄ ብዙ ጊዜ ሚነሳው የጥምቀትን purpose ካለማወቅ ይመስለኛል ምክንያቱም ብዙ ሰዎች ጥምቀትን እንደ ስርዓት...
19/01/2023

?
ፍፁም አምላክ ... ፍፁም ሰው የሆነው ክርስቶስስ ስለምን ተጠመቀ?

ይሄ ጥያቄ ብዙ ጊዜ ሚነሳው የጥምቀትን purpose ካለማወቅ ይመስለኛል ምክንያቱም ብዙ ሰዎች ጥምቀትን እንደ ስርዓት ብቻ ስለሚያዩ... ወደ መልሱ ስገባ ኢየሱስ የተጠመቀው ሕግን ሁሉ መፈፀም ስለነበረበት ነው ሁለተኛ ደግሞ ለኛ ምሳሌ ሊሆን ነው " የተጠራችሁለት ለዚህ ነውና፤ ክርስቶስ ደግሞ ፍለጋውን እንድትከተሉ ምሳሌ ትቶላችሁ ስለ እናንተ መከራን ተቀብሎአልና።"
(1ኛ የጴጥሮስ መልእክት 2:21)

በሐዋሪያት ስርዓት ላይ የክርስቶስ የሆኑትን የሚያሳድደው ሳውል በብርሐን ተገልጦለት አንድ ሐናኒያ ወደሚባል በፀሎት የተጋ አንድ ሰው ጋር እንዲሄድ አድርጎት ሐናኒያም እንዲህ አለው። “ባየኸውና በሰማኸው በሰው ሁሉ ፊት ምስክር ትሆንለታለህና። አሁንስ ለምን ትዘገያለህ? ተነሣና ስሙን እየጠራህ ተጠመቅ ከኃጢአትህም ታጠብ።"
(የሐዋርያት ሥራ 22:16)...

ይህም ክፍል የሚገልፀው የምንጠመቀው ጥምቀት ከሐጢአታችን የምንነፃበት እንደሆነ በግልፅ አማርኛ ይገልፅልናል። ክርስቶስ በአካል የተገለፀለት ሳውል ካየው ብርሐን መጠን አይነ-ስውር ሆኖ ነበር። ይህንንም ያየውን ተዓምር የክርስቶስን ስም እየጠራ እንዲጠመቅና ከሐጢአቱም እንዲታጠብ ሳውል ነግሮታል ስለዚህ የውሃ ጥምቀት ከሐጢያት ያነፃል ማለት ነው።

" ነገር ግን የመድኃኒታችን የእግዚአብሔር ቸርነትና ሰውን መውደዱ በተገለጠ ጊዜ ፥
እንደ ምሕረቱ መጠን ለአዲስ ልደት በሚሆነው መታጠብና በመንፈስ ቅዱስ በመታደስ አዳነን እንጂ፥ እኛ ስላደረግነው በጽድቅ ስለ ነበረው ሥራ አይደለም። (ወደ ቲቶ 3: 4-5).....

ያልተጠመቀ ዳግመኛ አልተወለደም ማለት ነው! ጥምቀት ከክርስቶስ ጋር ሞተን በአዲስ ህይወት ዳግም መነሳታችንን symbolically ምናሳይበት ነው።

ወደ ሮሜ ሰዎች 6፥2-3 እንደዚህ ይላል ..........
"ለኃጢአት የሞትን እኛ ወደ ፊት እንዴት አድርገን በእርሱ እንኖራለን? ወይስ ከክርስቶስ ኢየሱስ ጋር አንድ እንሆን ዘንድ የተጠመቅን ሁላችን ከሞቱ ጋር አንድ እንሆን ዘንድ እንደ ተጠመቅን አታውቁምን?" ይላል።
በዚህ ክፍል ደግሞ ጥምቀት ከክርስቶስ ሞትና ህይወት ጋር አንድ የምንሆንበት እንዲሁም እኛ ለሀጢአት የሞትን ሰዎች ከክርስቶስ ጋር እንዴት መኖር እንዳለብን ፤ እንዲሁም የምንጠመቀው ከክርስቶስ ጋር እና ከሞቱም ጋር አንድ ለመሆን ነው የምንጠመቀው። ስለዚህ ጥምቀት ስርዓት ብቻ ፣ የውሃ እጥበት ብቻ ወይም መደረግ አለመደረግም የሚችል ሳይሆን የክርስትና ግዴታችንና በክርስቶስ ሞትና ህይወት አንድ የምንሆንበት ነው። በሌላ አገላለፅ እየሱስ ስራችንን ሲሰራ መተባበራችንን እናሳያለን። ልክ በእምነት ብንድንም ማመናችንን በስራ በመግለጥ መዳናችንን እንደምናፀና እና እንደምናሳይ ማለት ነው።

“ኢየሱስ ግን መልሶ፦ የምትለምኑትን አታውቁም። እኔ ልጠጣው ያለውን ጽዋ ልትጠጡ እኔም የምጠመቀውን ጥምቀት ልትጠመቁ ትችላላችሁን? አለ። እንችላለን አሉት።”
— ማቴዎስ 20፥22

“የዮሐንስ ጥምቀት ከወዴት ነበረች? ከሰማይን ወይስ ከሰው? አላቸው። እነርሱም እርስ በርሳቸው ሲነጋገሩ፦ ከሰማይ ብንል፦ እንኪያስ ስለ ምን አላመናችሁበትም? ይለናል፤”
— ማቴዎስ 21፥25

በማርቆስ ወንጌልም እንዲሁ ዮሐንስ በምድረበዳ የንስሐንም ጥምቀት እያጠመቀ እንደነበረ ያስረዳናል።
"ዮሐንስ በምድረ በዳ እያጠመቀ የንስሐንም ጥምቀት ለኃጢአት ስርየት እየሰበከ መጣ።
የይሁዳም አገር ሁሉ የኢየሩሳሌምም ሰዎች ሁሉ ወደ እርሱ ይወጡ ነበር፥ ኃጢአታቸውንም እየተናዘዙ በዮርዳኖስ ወንዝ ከእርሱ ይጠመቁ ነበር።"
— ማርቆስ 1፥4-5

ሉቃስ 7፥29-30 .... እንደዚህ ይላል
"የሰሙትም ሕዝብ ሁሉ ቀራጮች እንኳ ሳይቀሩ በዮሐንስ ጥምቀት ተጠምቀው እግዚአብሔርን አጸደቁ ፤ ፈሪሳውያንና ሕግ አዋቂዎች ግን በእርሱ ስለ አልተጠመቁ የእግዚአብሔርን ምክር ከራሳቸው ጣሉ።" በዚህ ምዕራፍ ላይ ደግሞ ጥምቀት የእግዚአብሔርን ክብር የምንገልፅበት ፣ አብ አምላካችንን የምናፀድቅበት እንደሆነ ይገልፅልናል። በተቃራኒውም ደግሞ ሳይጠመቁ የሚቀሩት የእግዚአብሔር ምክር ከእኘሱ እንደራቀ እንደራቀ ይገልፃል።

ክርስቶስ ደቀ-መዝሙሩንና ህዝቡን ሲያስተምር ስለ ጥምቀት ትልቅ ቦታነትና ግዴታነት እንደዚህም ብሎ አስተምሯቸዋል።
“ነገር ግን የምጠመቃት ጥምቀት አለችኝ፥ እስክትፈጸምም ድረስ እንዴት እጨነቃለሁ?”
— ሉቃስ 12፥50

በሐዋርያት ሥራ 1፥1-7 ሲነገር ..........
- "አጵሎስም በቆሮንቶስ ሳለ ጳውሎስ በላይኛው አገር አልፎ ወደ ኤፌሶን መጣ ፥ አንዳንድ ደቀ መዛሙርትንም አገኘ፦ ባመናችሁ ጊዜ መንፈስ ቅዱስን ተቀበላችሁን? አላቸው።
- እነርሱም፦ አልተቀበልንም መንፈስ ቅዱስ እንዳለ ስንኳ አልሰማንም አሉት። እንኪያ በምን ተጠመቃችሁ? አላቸው።
- እነርሱም፦ በዮሐንስ ጥምቀት አሉት።
- ጳውሎስም፦ ዮሐንስስ ከእርሱ በኋላ በሚመጣው በኢየሱስ ክርስቶስ ያምኑ ዘንድ ለሕዝብ እየተናገረ በንስሐ ጥምቀት አጠመቀ አላቸው። ይህንም በሰሙ ጊዜ በጌታ በኢየሱስ ስም ተጠመቁ ፤ ጳውሎስም እጁን በጫነባቸው ጊዜ መንፈስ ቅዱስ ወረደባቸው በልሳኖችም ተናገሩ፥ ትንቢትም ተናገሩ። ሰዎቹም ሁሉ አሥራ ሁለት ያህሉ ነበር።" በእነዚህ ክፍሎች ውስጥ የምንረዳው ነገር የውሃ ጥምቀት ስርዓትን መፈፀም ብቻ እንዳልሆነና ውሃ በመንፈስ ቅዱስ ተምሳሌትነት የሚገለፅ እንደሆነና ዝም ተብሎ የሚፈፀም እንዳልሆነ እንረዳለን። ይህም ማለት በስሙ በአብ ፣ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ አምነን አዳኝነቱን ተቀብለን በመንፈስ ቅዱስ የምንሞላበትም ጭምር ነው።

ኤፌሶን 4፥4-6
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
"በመጠራታችሁ በአንድ ተስፋ እንደ ተጠራችሁ አንድ አካልና አንድ መንፈስ አለ፤አንድ ጌታ አንድ ሃይማኖት አንዲት ጥምቀት፤ከሁሉ በላይ የሚሆን በሁሉም የሚሠራ በሁሉም የሚኖር አንድ አምላክ የሁሉም አባት አለ።"
በዚህ ክፍል እንደሚያስረዳን አንድ አካል ፣ አንድ መንፈስ ፣ አንድ ጌታ ፣ አንድ ሀይማኖት አንድ ጥምቀት እንዳለ ያስረዳናል። አንዱን አጉድለን አንዱን ብቻ የምንይዝበት ስርዓትም ሆነ አምልኮት የለም። አንድ ሀይማኖት ክርስትናችን ነው ፤ አንድ ጥምቀት በአብ ፣ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ አምነን የምንጠመቀውና በመንፈስ ቅዱስ የምንሞላበት እንጂ ስርዓት ብቻ ወይም የውሃ እጥበት አይደለም።

ቆላስይስ 2፥11-12 ላይ ደስ በሚል ግልፅ ቋንቋ ያስቀምጥልናል።
" የሥጋንም ሰውነት በመገፈፍ ፥ በክርስቶስ መገረዝ ፥ በእጅ ባልተደረገ መገረዝ በእርሱ ሆናችሁ ደግሞ ተገረዛችሁ ፤ በጥምቀትም ከእርሱ ጋር ተቀብራችሁ ፥ በጥምቀት ደግሞ ፥ ከሙታን ባስነሣው በእግዚአብሔር አሠራር በማመናችሁ፥ ከእርሱ ጋር ተነሣችሁ።" ይህም የሚያሳየን መገረዝ በስጋዊ ሳይሆን በስራና በምግባር ክርስቶስን መምሰልን ፤ በጥምቀት ከእርሱ ጋር መቀበራችንን እንዲሁም በጥምቀቱ ደግሞ ከሙታን ባስነሳው በእግዚአብሔር ስራ ማመናችንን የምንገልፅበትና መነሳታችንን የምናሳይበት የመንፈስ ቅዱስ አሰራር ነው።

በ1ኛ ጴጥሮስ 3፥21 .....ጥምቀት ውሃ ውስጥ መነከርና እድፍን ማስወገድ እንዳልሆነና ለአምላካችን ለእግዚአብሐር የበጎ ህሊና ልመናን የምናቀርብበትና የኢየሱስን ትንሳኤ የምናበስርበት መሆኑን ደስ በሚል ቃል ይገልፅልናል።
“ይህም ውኃ ደግሞ ማለት ጥምቀት ምሳሌው ሆኖ አሁን ያድነናል፥የሰውነትን እድፍ ማስወገድ አይደለም፥ ለእግዚአብሔር የበጎ ሕሊና ልመና ነው እንጂ፥ ይህም በኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ ነው።" 1ኛ ጴጥሮስ 3፥21

ማርቆስ 16፥15-18
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
"እንዲህም አላቸው፦ ወደ ዓለም ሁሉ ሂዱ ወንጌልንም ለፍጥረት ሁሉ ስበኩ። ያመነ የተጠመቀም ይድናል፥ ያላመነ ግን ይፈረድበታል።ያመኑትንም እነዚህ ምልክቶች ይከተሉአቸዋል፤ በስሜ አጋንንትን ያወጣሉ፤ በአዲስ ቋንቋ ይናገራሉ፤ እባቦችን ይይዛሉ፥ የሚገድልም ነገር ቢጠጡ አይጎዳቸውም፤ እጃቸውን በድውዮች ላይ ይጭናሉ እነርሱም ይድናሉ።" ብዙውን ጊዜ በዚህ ክፍል ውስጥ ያለውን ቃለት በመለያየት አጉል ለሆነ ስህተት ሰዎች እንዲሄዱ ያደርጋቸዋል። "ያመነ የተጠመቀም ይድናል ፤ ያላመነ ግን ይፈረድበታል" የሚለውን ክፍል በማንሳት ያልተጠመቀ አይፈረድበትም .... ያላመነ ነው የሚለው በማለት የክርክር ሀሳብ ያነሱበታል። እዚህ ጋር መረዳት ያለብን ... በ1ኛ ጴጥሮስ እንደተገለፀው ጥምቀት እድፍ ማስወገጃ አይደለም ፤ ስንጠመቅ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ማመናችንን የምንገልፅበት ስለሆነ ነው። ስለዚህ እነዚህ ቃላቶች ተነጣጥለው ብቻቸውን የሚቆሙ አይደሉም። አለማመንም አለመጠመቅም ያስፈርድብናል ማለት ነው !!

በመጨረሻም ሐዋርያት 8፥35-39 ፊሊጶስ ኢትዮጵያዊ ጃንደረባን አግኝቶ ስለ ጥምቀት ያስተማረውን ቦታ ጠቅሼ ሀሳቤን ልቋጨው።

"ፊልጶስም አፉን ከፈተ፥ ከዚህም መጽሐፍ ጀምሮ ስለ ኢየሱስ ወንጌልን ሰበከለት።
በመንገድም ሲሄዱ ወደ ውኃ ደረሱ፤
- ጃንደረባውም፦ እነሆ ውኃ ፤ እንዳልጠመቅ የሚከለክለኝ ምንድር ነው? አለው።
- ፊልጶስም፦ በፍጹም ልብህ ብታምን ፥ ተፈቅዶአል አለው። መልሶም፦ ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ አምናለሁ አለ።
ሰረገላውም ይቆም ዘንድ አዘዘ፥ ፊልጶስና ጃንደረባው ሁለቱም ወደ ውኃ ወረዱ፥ አጠመቀውም። ከውኃውም ከወጡ በኋላ የጌታ መንፈስ ፊልጶስን ነጠቀው፤ ጃንደረባውም ሁለተኛ አላየውም፥ ደስ ብሎት መንገዱን ይሄድ ነበርና። " ሐዋርያት 8፥35-39

ኢትዮጵያዊው ጃንደረባ የውሃ ጥምቀትን ማድረግ ፈልጎ በዚህ ውሃ እንዳልጠመቅ የሚከለክለኝ ማነው? ሲለው ፊሊጶስም ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ መሆኑን ካመነ እንደሚችል ነገረው ፤ ጃንደረባውም የተባለውን ፈፀመ። ጥምቀት በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ከማመን ጋር የሚደረግ ነው እንጂ የውሃ እጥበት አለመሆኑን ያስረዳናል።

ሰላማቹ ይብዛልኝ። ሀሳብ አስታየታቹን አስፍሩ። Shallom 🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏

 እውነቱ ይህ ነው ፣ ፍቅር የሚለካው በልባችን ላይ በተወው ቊስል ልክ ነው። እጅግ የምንወዳቸው ሰዎች አሳምመውን ይሆናል። እኛም እጅግ የሚወዱንን ሰዎች አሳምመን ይሆናል። ምክንያቱም ፍቅር ...
18/01/2023



እውነቱ ይህ ነው ፣ ፍቅር የሚለካው በልባችን ላይ በተወው ቊስል ልክ ነው። እጅግ የምንወዳቸው ሰዎች አሳምመውን ይሆናል።
እኛም እጅግ የሚወዱንን ሰዎች አሳምመን ይሆናል። ምክንያቱም ፍቅር የሚታየው በታገስነው ቊስል ውስጥ ስለሆነ።

ፍቅር የሚታወቀው የተለዋወጥናቸውን ቃላት ሳይሆን በምንታገሠው ቊስል ፣ በተሰማን የውስጥ ሕመም ፣ በከፈልነውን መሥዋዕትነትና በተካፈልነውን ብርሃን ነው።

ከትንሣኤው በኋላ በሐዋርያቱ ፊት የተገለጠው ክርስቶስ እርሱ የሚወዱት ጌታ እንደሆነ ለማስረዳት ያሳያቸው የትንሣኤው ድል ማብሠሪያ መለከት አይደለም ፣ የፍቅሩ ማስረጃ ቊስሉ ነበር። "ወደ እኔ ኑ ቊስሌን ዳስሱ ፣ እጃችሁንም ስለ እናንተ ፍቀር በቆሰልሁት ቊስል አስገቡ" ነበር ያላቸው። አታስታውሱኝም? አላወቃችሁኝም? እስከ ሞት ድረስ የወደድኳችሁ እኔ ነኝ። ለፍቅሬ ማረስጃ እንዲሆናችሁ ደግሞ ቊስሌን ተመልከቱ! ነው ያላቸው።

ፍቅር ቊስል ነው።
በእግዚአብሔር መንግሥት ክብርና ምስጋና የምናገኘውም በምድር ሳለን በነበሩ ስኬቶቻችንና ባስገኘናቸው ውጤቶቻችን ሳይሆን በታገሥናቸው መከራዎችና በተሰቃየንባቸው ሕመሞች ልክ ነው።

ለዚህም ነው በአበው መጽሐፍ አንድ አባት ለረጅም ዓመት በሰውነትዋ ላይ ቆስሎ የምትሰቃይን ሴት ሊጠይቁ ሲሔዱ "እዩት ቊስሌን አጎንብሰው ቢያዩት አጥንቴ ይታይዎታል" አለቻቸው። እርሳቸውም ጎንበስ ብለው "ብዙ ዓመት በታገስሽው በቊስልሽ ውስጥ የሚታየኝ አጥንት ሳይሆን ገነት ነው" አሏት።

12/01/2023

በSocial Media ካሉ ሰዎች ሁሉ የሰውነት ልክ የሆነ ድንቅ ሰው። እግዚአብሔር ዘመንህን ይባርከው።

09/01/2023

እግዚአብሔር ዘመንህን ይባርክ ወንድሜ 🙏🙏

ለካስ ሂፕ ሆፕም ይሰማሉ 😂😂😂ድምፃዊ ቴዲ ዮ ታሰረበሂፖፕ እና ራፕ ሙዚቃዎቹ የሚታወቀው ቴዲ ዮ "ወንበርሽ" የተሰኘውን እና ፖለቲካዊ ይዘት ያለውን ሙዚቃ ቪዲዮ ከለቀቀ ከሁለት ቀናት በኋላ ...
30/12/2022

ለካስ ሂፕ ሆፕም ይሰማሉ 😂😂😂

ድምፃዊ ቴዲ ዮ ታሰረ

በሂፖፕ እና ራፕ ሙዚቃዎቹ የሚታወቀው ቴዲ ዮ "ወንበርሽ" የተሰኘውን እና ፖለቲካዊ ይዘት ያለውን ሙዚቃ ቪዲዮ ከለቀቀ ከሁለት ቀናት በኋላ መታሰሩ ታውቋል። ቴዲዮ በዚህ ሙዚቃ ከቋጠራቸው ስንኞች መካከል

የወንዜ የወንዜ የወንዜ ትርምስ
ጥያቄ ብቻ ነው መልሱ ላይመለስ
የወንዜ የወንዜ የወንዜ 4 ኪሎ
ወንበርሽ ይፋጃል ጠፋ ሁሉን ጥሎ

ልዩነሽ አዎ አማላይ
በውበትሽ ሰው ገዳይ
የኔ ያሉሽ ያለ ከልካይ
ስንቱን አየን ባንቺ ጉዳይ
እውነት እውነቱን እስቲ ልናገር
ሁሉም ይበል ባንቺ ጥንቅር
ተወልደናል እኛ ሸገር እንደሌለው ሆነን አገር ..
ያራዳ ልጅ እድለኛ
የፀዳ ነው ከዘረኛ
ለመጣው ለተረኛ
ማጨብጨብ ነው ለቀማኛ
ሸገር ተወልዶ ማደጉ የቱ ጋ ነው እስቲ ጥቅሙ
በስጋት ቤት ማጉረምረሙ መኖር አፈር እየቃሙ

የሚሉት ይገኙበታል።

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ras Becky Satenaw ራስ ቤኪ ሳተናው posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share