የኢኦተቤ መገናኛ ብዙኀን አገልግሎት ሥርጭት ድርጅት/ EOTC Broadcasting Service Agency/

  • Home
  • Ethiopia
  • Addis Ababa
  • የኢኦተቤ መገናኛ ብዙኀን አገልግሎት ሥርጭት ድርጅት/ EOTC Broadcasting Service Agency/

የኢኦተቤ መገናኛ ብዙኀን አገልግሎት ሥርጭት ድርጅት/ EOTC Broadcasting Service Agency/ is a Facebook social networking site based on the Doctrine and Canon of the EOTC.
(2)

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የመገናኛ ብዙኃን ሥርጭት አገልግሎት ድርጅት
/ Ethiopian Orthodox Tewahedo Church Broadcasting Service Agency/

ብብፁዕ ወቅዱስ ኣቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ብምኽንያት ዕረፍቲ ንቡረ እድ በላይ መረሳ ገብረዮሐንስ ...
24/08/2025

ብብፁዕ ወቅዱስ ኣቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ብምኽንያት ዕረፍቲ ንቡረ እድ በላይ መረሳ ገብረዮሐንስ አመልኪቱ ዝተውሃበ ናይ ሓዘን መግለጺ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

"ዘጻመወ በዓለም የሐዩ ለዝሉፉ፤ እስመ ኢይሬኢ ሙስና፤ እቲ ኣብ ዓለም ዝደኸመ ንዘልዓለም ክድሕን እዩ: ጥፍኣት/መከራውን ኣይክረኽቦን እዩ (መዝ. 48፥9)።

ንቡረ እድ በላይ መረሳ ሃይማኖት ዘለዎም፤ ንሃይማኖት ዝመስከሩ፣ ሃይማኖትውን ዝመስከረትሎም ኣቦ ኣሽሓት፣ ናይ ብዙሓት መምህር፣ ፍቕሪ እግዚኣብሔርን ፍቕሪ ብጻይን ዝጸንዓሎም ሙሉእ ጊዚኦም ዝመሃሩ፣ ንኹሉ ብማዕረ ዓይኒ ዝርእዩ፣ ኣብ ልቢ ኣመንቲ ቃል ወንጌል ዝዘርኡ ዓብይ ሓረስታይ ወንጌል፣ ኣብ ብዙሓት ደቆም ፍሬኦም ዝረኣዩ፣ ኣቦ ኣሽሓት፣ ኣንደበቶም ከቶ ዘይትዕንቀፍ፣ ጋሻ ውሕጅ/ዘመን ዘየሽንፎም፣ ኣብ ቦትኦም ዝተረኽቡ፣ ብትኽክል ዝፈለጡ/ዝተረድኡ፣ ብነጻ ዝተዋህቦም/ዝተቐበልዎ ብነጻ ዝሃቡ፣ ተንቀሳቓሲ ቤተ መጻሕፍቲ ነይሮም።

እዞም መዘና ኵላትና፣ ብጻይ ትምህርት ቤት፣ ናይ ቤተ ክርስቲያን መብራህቲ ዝኾኑ ኣቦ ካብዚ ዓለም ድኻም ምዕራፎም ክንሰምዕ ብዓቢይ ሓዘን እዩ።

የሕዝባቸውን መከራ በልባቸው ተሸክመው ለኖሩት ለእርሳቸው ይህ ዕረፍት ቢሆንም ለቤተ ክርስቲያን አባቶችና ለምእመናን ግን ትልቅ ጉዳት ነው።

እዙይ ዋላኳ ነዞም መከራ ህዝቦም ኣብ ልቦም ጸይሮም ዝነበሩ ኣቦ ዕረፍቲ/እፎይታ እንተኾነ ንቤተ ክርስቲያን ኣቦታትን ምእመናንን ግን ዓብይ ጉድኣት/ክሳራ እዩ።

ስለዚ ንሶም ናይ ቅድስቲ ቤተ ክርስቲያን ቅርሲ ከምኻኖም መጠን ናሃቶም ሕልፈት ከም ናይ ሓደ ሰብ ሕልፈት ዝርአ ስለዘይኮነ ብስም ቅዱስ ሲኖዶስን ብስም መላእ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ኢትዮጵያን ዝተሰምዓና ሓዘን ንገልጽ!

ብዕረፍቲ እዞም ዓቢይ ሊቅ ዝሓዘንኩም ኩልኻትኩም በቲ ንሶም ዝዝከርሉ ሠናይ ተግባራቶምን ብደቀ መዛሙርቶምን/ተምሃሩኦምን ህያው/ህልዊ ስለዝኾኑ በዚኦም ኽትጽናዕንዑ ይግባኣኩም።

እግዚኣብሔር ኣምላኽና ንሊቃውንቲ ቤተ ክርስቲያን ይሓልወልና፤ ብዕረፍቲ ሥጋ ንዝተፈለዩና ዕረፍቲ ነፍሲ፣ ኣብዚ ንዝተረፍና ድማ ምጽንናዕ ይልኣኸልና/ይሃበና!

እግዚአብሔር አምላኽ ኢትዮጵያን ህዝባን ይባርኽ! አሜን።

ኣባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት

ነሓሰ 16/2017 ዓ.ም
ዋሽንግተን ዲሲ፡ ኣመሪካ
©ፍሉይ ቤት ጽሕፈት ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ

ትርጉም፡ በመምህር ኪደ ዜናዊ

በሸገር ሀገረ ስብከት የወይብላ ማኅደረ መለኮት ቅድስት ማርያምና  ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል የስብከተ ወንጌል ክፍልና  አክሊለ ምክሕነ ሰንበት ትምህርት ቤት ያስተማራቸውን ተማሪዎች አስመረቀ።መ...
24/08/2025

በሸገር ሀገረ ስብከት የወይብላ ማኅደረ መለኮት ቅድስት ማርያምና ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል የስብከተ ወንጌል ክፍልና አክሊለ ምክሕነ ሰንበት ትምህርት ቤት ያስተማራቸውን ተማሪዎች አስመረቀ።
መምህር ጌታቸው በቀለ
( ነሐሴ 18 ቀን 2017 ዓ.ም)
በሸገር ሀገረ ስብከት የወይብላ ማኅደረ መለኮት ቅድስት ማርያምና ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል በተሰናዳው የምርቃት መርሐ ግብር ላይ በካቴድራሉ ስብከተ ወንጌል በኦሮምኛ ቋንቋ ክፍል የተማሩ 75 ተማሪዎችና በሰንበት ትምህርት ቤቱ በተከታታይ ትምህርት የተማሩ 570 ተማሪዎች ተመርቀዋል።
ሰንበት ትምህርት ቤቱ በአጥቢያው ለሚገኙ ወጣቶች በአርአያነት የሚጠቀስ ሥራ እየሠራ ይገኛል። በአብነት ትምህርት፣ በኦሮምኛ ቋንቋ ሰፊ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል።

ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ የምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በምርቃቱ ላይ ባስተላለፋት መልእክት በቋንቋ ማስተማር ይገባል፣ ዛሬ በኦሮምኛ ቋንቋ የተመረቃችሁም የተማራችሁትን ለሌላ እንድታሳውቁ፣ እንድታስተምሩ ነው። ቤተክርስቲያን አስተምራችኋለች፣ የቤተክርስቲያን ውለታ መርሳት አይገባም ሲሉ አባታዊ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።

በመርሐ ግብሩ ላይቆሞስ አባ አፈወርቅ ዮሐንስ የሦስቱ የክፍላተ ከተማ ዋና ሥራ አስኪያጅ የአጥቢያው ምእመናንና የተመራቂ ቤተሰቦች ተገኝተዋል።
ሙሉ ዘገባውን ይዘን እንቀርባለን።

የሊቃውንት ጉባኤ ሰብሳቢ፣ የድጓ ምስክር፣ መምህርና የታሪክ ምሁር ክቡር  ንቡረእድ በላይ መረሳ ገብረዮሐንስ  አጭር የሕይወት ታሪክ፦ 1/ ክቡር ንቡረእድ በላይ መረሳ• ከአባታቸው ከዲያቆን ...
23/08/2025

የሊቃውንት ጉባኤ ሰብሳቢ፣ የድጓ ምስክር፣ መምህርና የታሪክ ምሁር ክቡር ንቡረእድ በላይ መረሳ ገብረዮሐንስ አጭር የሕይወት ታሪክ፦

1/ ክቡር ንቡረእድ በላይ መረሳ
• ከአባታቸው ከዲያቆን መረሳ ገብረዮሃንስ እና ከእናታቸው ከአመተጽዮን ረዳ በመስከረም 1931 ዓ.ም በአክሱም ከተማ ተወለዱ። በቤተሰቡ ውስጥ ሁለተኛ ልጅ ሲሆኑ 3 ዓመት ሲሞላቸው አባታቸው እና እናታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ስለተለዩአቸው የልጅነት ጊዜአቸውን ከክስታቸው ጋር አሳለፈዋል።

ይህ ገና በለጋ ዕድሜያቸው የወላጆች እጦት ሳይገድባቸው በነበራቸው ብሩህ አእምሮ በአራት ዓመታቸው ትምህርት ጀምረው መዝሙረ ዳዊት፣ ቅዳሴ፣ ሰዓታትንና ሌሎች መጻሕፍትን ጨርሰው ቤተ ክርስቲያንን ማገልገል የጀመሩት ገና በ12 ዐመታቸው ነበር።

2/ ትምህርት እና የተማሩባቸው ቦታዎች
ክቡር ንቡረእድ በላይ መረሳ ከፍተኛ የትምህርት ፍላጎት ስለነበረባቸው
በጊዜው ከነበሩ ሊቅ ከመሪጌታ ስቡህ ተላ
- ምዕራፍ - ፆመ ድጓ እና አቋቋም በሚገባ ተምረው ያጠናቀቁ ሲሆን ከዚህ በተጨማሪም፥
• በወቅቱ ከነበሩ ሊቅ ከመሪጌታ ገሱ ገ/ማርያም ዝማሬና ምዕራፍ ተምረው የተመረቁ ሲሆን በተለያዩ የወገራ አካባቢዎች ሄደው ቅኔ ተቀኝቷል።
• ከዚህ በኋላ ወደ ትውልድ አገራቸው አክሱም ተመልሰው ከቄሰ ገበዝ ገብረአብ ማሩ
ሰላም ለኪ ብለው በመጀመር ሁሉን ዘልቀው የድጓ ትምህርትም አጠናቀዋል።
• በ1954 ዓ.ም ወደ ቤተልሔም በመሄድ ድጓ አመስክረው እንዲሁም ከየኔታ ዘርአዳዊ ጎንደር አዘዞ ዝማሬ መዋስእትን ቅንዋትን ተምረዋል።
• የአቋቋም ትምህርት ከየኔታ ይትባረክ ጎንደር አዘዞ በሚገባ የተማሩ ሲሆን።
• ትርጓሜ መጻሕፍት ወደ አክሱም ተመልሰው በወቅቱ ሊቅ ከነበሩ ከየታ ገብረጊዮርጊስ ተምረዋል።

3/ የሥራ መደባቸውን በተመለከተ
ክቡር ንቡረእድ በላይ መረሳ በር/አ/ወገ/አክ/ጽዮን ቤተ ክርስቲያን፦
• ከ1956 -1960 ዐ/ም በግራጌታ ማዕረግ
• ከ1960-1979 ዐ/ም በመሪጌታ ማዕረግ
• ከ1979-1993 በንቡረ እድ ማዕረግ ሲያገለግሉ ይህን ታላቅ ማዕረግ/ሹመት ቤተ ክርስቲያን ይዘው ቤተ ክርስቲያንን በሚገባ በሙሉ ልብ አገልግሏል።
በ2003 ዓ.ም ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም በጎንደር ብቻ ይሰጥ የነበረውን የድጓ ምስክርነት የንቡረ እድ በላይ መረሳ ሁኔታና እና ብቃት ከተረዱ በኋላ የድጓ ምስክርነት የድጓ ደራሲ የቅዱስ ያሬድ ጥንተ መንበር በሆነችው በአክሱም በንቡረ እድ በላይ መረሳ እንዲሰጥ አድርገዋል።

4/ የመምህርነት የሥራ መደብ
ከ1957 ዓ.ም ጀምረው በአክሱም በሚገኘው የቅዱስ ያሬድ መንፈሳዊ ትምህርት ቤት ወንበር ተክለው ለ60 ዓመታት ደከመኝ ሰለቸኝ ልረፍ ሳይሉ ቅዱስ ያሬድ የጻፋቸው መጻሕፍትና የደረሳቸው ዜማታት ሳይበረዙ ከትውልድ ወደ ትውልድ እንዲተላለፉ ትልቅ አስተዋጽኦ አድርገዋል።

ከ1945 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ዕለተ ዕረፍታቸው ለ72 ዓመታት ያህል በፍጹም ትዕግስት፣ በትሕትና፣ በፍፁም ልብ እግዚአብሔርን በመፍራት የተለየ መብትን ሳይጠይቁ ቤተ ክርስቲያን በቅኔ ማህሌት፣ በቅዳሴ እና በስብከተ ወንጌል አገልግለዋል።

ከዚህ በተጨማሪም የር/አድ/ወገ/ኣክ/ጽዮን ቤተ ክርስቲያን የሊቃውንት ጉባኤ ሰብሳቢ
በመሆን በ2012 ዐ/ም በተደረገ ጉባኤ ትክክለኛ የቅዱስ ያሬድ ዜማ የአክሱም ቀለም በመለየትና በሥርዓት በመጽሐፍ ተጽፎና ተሰንዶ በሳቸው ልሳን ተቀርጾ እንዲደመጽ ያደረጉ ሲሆን አንዱ የሊቅነታቸው ምስክር መጽሐፈ ዚቅ ዘአክሱም የሚል ከሌሎች ሊቃውንት ጋር በመተባበር እንዲታተም ተደርጓል። እንዲሁም በሕትመት ላይ ያለው ድምጸ ያሬድ የሚል መጽሐፍ እንዲጻፍ ያደረጉ አባት ናቸው።

5/በሕይወት ጉዟቸው የገጠሟቸው ክስተቶች
ክቡር ንቡረ እድ በላይ መረሳ በአስመራ እንዲሁም በአዲስ አበባ በተሻለ ደመወዝ እንቅጠርዎት ሲባሉ ከታቦተ ጽዮን አልወጣም ብለው ከአክሱም ከተማ ሳይወጡ ታቦተ ጽዮንን አገልግለዋል። ለዚህም ነው በታማኝነት በቅንነት ያገለገላትን ዋጋ የምትሰጥ ታቦተ ጽዮን የእናታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ወላዲተ አምላክ ፆመ ፍልሰታ ሱባኤ እንዳለቀ የዕረፍታቸው ዜና የተሰማ።

በተጨማሪም የክርስትና ስማቸው ተክለገሪማ ሲሆን የቀብር ሥነ ስርዓታቸውም በነሐሴ 17/12/2017 ዓ/ም በጻድቁ አቡነ ገሪማ ወርሐዊ በዓላቸው መፈጸሙ ልዩ ያደርገዋል።

➢ በመላ ሀገሪቱ ብዙ ሊቃውንት ያፈሩ ሲሆኑ የድጓ ምስክርነት ከመቀበላቸው በኋላ ግን ከ100 በላይ መምህራን አስመርቀዋል።

➢ በዘንድሮም ከ2 ዓመት በላይ ያስተማሯቸው፣ ነሐሴ 30 እና ጳጉሜን 5 ሊመረቁ መርሐ ግብር ለወጣላቸው ተመራቂ ተማሪዎች ዕረፍታቸው የማይቀር መሆኑን ተረድተው ፣ ከመሞታቸው ከአንድ ሳምንት በፊት ነሐሴ 30 እና ጳጉሜን 5:2017 ዐ/ም የሚል የምስክር ወረቀት ተሰጧቸዋል።

6/ ምሥጢር ዕውቀታቸው/ሊቅነታቸው
ክቡር ንቡረ እድ በላይ መረሳ በልጅነታቸው የወላጆቻቸውን እጦት/ሞት ታግሰው
በሚገባ አቅደው በጉዟቸው ወቅት ያጋጠሟቸውን ፈተናዎች በርጋታና ጸሎት እየፈቱ በንቃት የሃይማኖትና የታሪክ መጻሕፍትን እያነበቡ፣ እያገናዘቡና እየተማሩ ለዚህ የክብር ደረጃ የደረሱ አባት ናቸው።

7/ ለሀገራቸው ያበረከቱት አስተዋፅኦ
ክቡር ንቡረእድ በላይ መረሳ
❖ በመጥፋት ላይ የነበረውን የግእዝ ቋንቋ እንዲነሣ ር/አድ/ወገ/አክ/ጽዮን ቤተ ክርስቲያን ከግእዝ ቋንቋ ውጪ በሌላ እንዳትገለገል ሕግ በማውጣት እስካሁን ግእዝ ቋንቋ እንዲጠበቅ ያደረጉ አባት ናቸው።

❖ ለተለያዩ ተመራማሪዎች ትክክለኛውን የግእዝ ቋንቋ እውቀት በመስጠት ቋንቋው እንዲጠበቅ ሲያደረጉ የነበሩ አባት ናቸው።
❖ በተጨማሪም የአክሱም ዩኒቨርሲቲ የግእዝ ቋንቋን በማስተዋወቅ ረገድ መሪ ተዋናይ በመሆን የዩኒቨርሲቲው መምህራን እና ተማሪዎች ስለ ግእዝ ቋንቋ፣ ስለ ቅዱስ ያሬድ፣ ስለ አክሱም ጥንታዊ ታሪክ ያላቸውን እውቀትን በማካፈል እንደ ታላቅ ቤተ-መጽሐፍት እና ሙዚየም ሆነው ያለፉ አባት ናቸው።
❖ በተለያዩ ህዝባዊ ኮንፈረንሶች እና ሲምፖዚየሞች በአካል በመገኘት የአክሱም ትክክለኛ ታሪክ ሲያስረዱ የነበሩ አባት ናቸው።
❖ የአክሱም ጥንታዊ ሥልጣኔ እና የግእዝ ቋንቋ በዓለም እንዲታወቅ ከበርካታ የታሪክ ተመራማሪዎች፣ መገናኛ ብዙኃን
- በዜና
- በዶክመንተሪ እና
- በመጽሓፍ ትክክለኛውን ታሪክ እያካፈሉ መረጃና ማስረጃ በማቅረብ የማይተካ የአንበሳውን ድርሻ ያበረከቱ ሊቅ አባት ነበሩ።

ክቡር ንቡረእድ በላይ መረሳ
➢ በክርስቲያኑ ማሕበረሰብ ዓለም ዘንድ እንደ ሙዚየም እና ቤተ መጻሕፍት ተደርገው የሚወሰዱ ታላቅ ክብርና ተቀባይነት ነበራቸው።
➢ በአክሱም ከተማ ህዝብና አስተዳደር
በአክሱም ጽዮን ቤተ ክርስቲያን እንደ ጉልላት የሚታዩ ትልቅ ክብር የተበራቸው ክቡር ንቡረ እድ በላይ መረሳ ያሉት ይሁን የሚባሉ ሊቅ አባት ነበሩ።

➢ በተለያዩ ገዳማትና አድባራት እየተገኙ ለህዝባቸው ሰላም እና ሃይማኖታዊ
አንድነትን የሚያስተምሩ የተከበሩ አባት ነበሩ።
➢ ከተለያዩ የሃይማኖት አባቶች እና የመንግሥት አካላት ጋር ምክክር በማድረግ መቻቻል እንዲያድግ ህዝበ ክርስቲያኑ ሃይማኖቱን ጠብቆ እንዲኖር ያደረጉ አባት ናቸው።
9/ ያገኝዋቸው ክብርታት እና ሽልማቶች
ክቡር ንቡረእድ በላይ መረሳ፦
✓ በነበራቸው ሊቅነትና አገልግሎት በመስጠት ባደረጉት አበርክቶ ከህዝቡ ከአክሱም ጽዮን ቤተ ክርስቲያን አብያተ ክርስቲያናት እና ገዳማት አገልጋዮች ታላቅ ክብርና ምስጋና ያገኙ ልዩ አባት ናቸው።

✓ በግራጌታ ማዕረግ ላይ እያሉ ከንቡረ እድ መኩሪያ እጅ አፈ ንቡረ ኤድ ኃይለ ሥላሴ ተክለን ቀሸ ገበዝ ተክለሃይማኖት ወልደሥላሴን
- ካባ
- ቁፍጣን እና
- ቁፍጣን የሚባሉ በወቅቱ ትልቅ ሽልማት አግኝተዋል።
✓ በመሪጌታ ማዕረግ ላይ እያሉ፦
- የነበራቸው እውቀትና አገልግሎት ግምት ውስጥ በማሳየት በቀዳማዊ አፄ ኃይለ ሥላሴ
- ካባ
- መርገፍ እና
- ቁፍጣን ተሸልመዋል። በዚያን ጊዜ የቤተ ክርስቲያን ሕግ በሽልማት ካልተሰጠው በስተቀር አንድ አገልጋይ በራሱ ካባ ገዝቶ እንዲለብስ አይፈቅድም ነበር።
✓ የድጓ ምስክር ሰጪ ተብለው በተሾሙ ወቅትም፦
• አዲስ አበባ ከሚኖሩ የአክሱም እና አካባቢው ተወላጆች፦
- የወርቅ ካባ
- የብር ራስወርቅ
- የብር መቋሚያ እና
-የብር ጸናጽል በሽልማት የተሰጣቸው አባት ናቸው።

- ክቡር ንቡረእድ በላይ መረሳ ባለትዳር የ3 ወንድ እና የ4 ሴት ልጆች አባት ሲሆኑ ልጆቻቸውን የእሳቸውን ፈለግ እንዲከተሉ ያስተማሩ እና ለትልቅ ቁምነገር ያደረሱ አርአያ የሆኑ አባት ነበሩ።
• ክቡር ንቡረ እድ በላይ መረሳ ባደረባቸው ሕመም በ87 ዓመታቸው ነሐሴ15/2017 ዓ/ም 0ርፈው የቀብራቸው ሥነ በሥርዓት አበው ከተለያዩ አካባቢዎች የመጡ ሊቃውንት፣ መነኮሳ፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የር/አድ/ወገ/አክ/ጽዮን ቤተ ክርስቲያን ካህናት፣
ያቆናትና ተማሪዎቻቸው፣ የአክሱም ከተማና አካባቢው ማሕበረሰብ፣ ልጆቻቸው፣ ቤተሰቦቻቸውና ወዳጆቻቸው በተገኙበት ነሐሴ 17/2017 ዓ/ም በር/አድ/ወገ/አክ/ጽዮን ቤተ ክርስቲያን ተፈጽሟል።

• የር/አድ/ወገ/አክ/ጽዮን ቤተ ክርስቲያን ለመላው ሕዝብ ክርስቲያን፣ ለሊቃውንት እና አገልጋዮች ር/አድ/ወገ/አክ/ጽዮን፣ ለክቡርት ባለቤታቸው፣ ለልጆቻቸው፣ ለተማሪዎቻቸውና ጓደኞቻቸው መፅናናትን ተመኝታ የክቡር ንቡረ እድ ተክለገሪማ ነፍስ በአብርሃም፣ በይስሐቅ እና በያዕቆብ እቅፍ እንድትኖር ተመኝታለች። አሜን!!!

ምንጭ፦ ርእሰ አድባራት ወገዳማት አክሱም ጽዮን ቤተ ክርስቲያን

ትርጉም፦ መምህር ኪደ ዜናዊ

ለብፁዕ አቡነ ቄርሎስ ሊቀ ጳጳስ የምስጋና መርሐ ግብር ተካሄደ። (  ነሐሴ 17 ቀን 2017 ዓ.ም )በሰሜን ወሎ መንበረ ጵጵስና ሀገረ ስብከት የወልድያ ከተማ አስተዳደር ቤተክህነት መንበረ ...
23/08/2025

ለብፁዕ አቡነ ቄርሎስ ሊቀ ጳጳስ የምስጋና መርሐ ግብር ተካሄደ።

( ነሐሴ 17 ቀን 2017 ዓ.ም )

በሰሜን ወሎ መንበረ ጵጵስና ሀገረ ስብከት የወልድያ ከተማ አስተዳደር ቤተክህነት መንበረ ንግሥት ኪዳነ ምሕረት ቤተክርስቲያን ሰበካ ጉባኤ ከደብሩ ሰንበት ትምህርት ቤት ጋር በመተባበር ለብፁዕ አቡነ ቄርሎስ የምስጋና መርሐ ግብር አካሄዷ።

በሰንበት ትምህርት ቤቱ ሀሳብ አመንጭነት ትናንት ነሐሴ 16 ቀን 2017 ዓ.ም በተደረገው በዚሁ የምስጋናና የእውቅና መርሐ ግብር ብፁዕ አቡነ ኤርምያስን ጨምሮ ተጋባዥ እንግዶች፣ የሀገረ ስብከት፣ የወረዳ አብያተክህነት የሥራ ኅላፊች፣ የአድባራት አስተዳዳሪዎች፣ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያንና በርካታ ምእመናን/ት ተገኝተዋል።

በእውቅና መርሐ ግብሩ ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ ሊቀ ጳጳስ ባስተላለፉት ቃለ ምእዳን ብፁዕ አቡነ ቄርሎስ ከልጅነታቸው ጀምሮ ለቤተክርስቲያን አገልግሎት ዋጋ መክፈላቸውን ገልጸዋል።

ከመቅደላ እስከ ብልባላ፣ ከወሎ እስከ ጎንደር፣ ከሸዋ እስከ ወላይታና ሲዳሞ ክፍላተ ሀገር በእግር እየተጓዙ ያሳለፉትን ውጣ ውረድ፣ የቀሰሙትን የቤተክርስቲያን እውቀት፣ በተለያየ የአገልግሎት ደረጃ ያደረጉትን ሃይማኖታዊ ተጋድሎም አስታውሰዋል።

ብፁዕነታቸው ኹሉን ተምረው የተሾሙ በመሆናቸው በቤተክርስቲያኗ አገልግሎት ያስቀመጡት ታሪካዊ አሻራ ሳይደበዝዝ ሕያው ሁኖ እንደሚኖርም ተናግረዋል።

የመሠረ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት የብፁዕነታቸውን የማይረሳ አገልግሎት ኹልጊዜ ለማውሳትና ለሕፃናትና ማእከላውያን የነበራቸው፤ አሁንም ድረስ ያልነጠፈው ፍቅራቸውና ጸሎታቸው እንዲበዛላቸው የሰንበት ትምህርት ቤቱን ባለ ሁለት ወለል ኹለገብ ሕንጻ "ብፁዕ አቡነ ቄርሎስ ኹለገብ ሕንጻ" ተብሎ እንዲጠራ የስም ስጦታ አበርከቷል፡፡

የብፁዕነታቸውን ዐለም አቀፍ ሐዋርያዊ አገልግሎት የሚያወሱ ቅኔ፣ ያሬዳዊ ዝማሬና ሌሎች ዝግጅቶች የቀረቡ ሲሆን ሰንበት ትምህርት ቤቱና ሰበካ ጉባኤው ምእመናንን በማስተባብር ለብፁዕነታቸው ያዘጋጀውን ልዩ ስጦታ በብፁዕ አቡነ ኤርምያስ በኩል አበርክቷል።

ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ ሊቀ ጳጳስ ሰንበት ትምህርት ቤቱ ሀሳቡን በማመንጨት መርሐ ግብሩን በማዘጋጀታቸው አመስግነው ብፁዕ አቡነ ቄርሎስ ከምሥረታ ጀምሮ ሕጻናቱን በመንፈሳዊ ሕይወት ኮትኩተው ለማሳደግ ብዙ የደከሙ በመሆኑና ውለታቸውን ለማስታወስ ሰንበት ትምህርት ቤቱ ተክለ ቄርሎስ ተብሎ እንድጠራ ሰይመውታል።
© የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት

22/08/2025
የንቡረ ዕድ በላይ መረሳ ዕረፍት በማስመልከት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም የኃዘን መልዕክት አስተላለፉ።የቅዱስነታቸው የ...
22/08/2025

የንቡረ ዕድ በላይ መረሳ ዕረፍት በማስመልከት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም የኃዘን መልዕክት አስተላለፉ።

የቅዱስነታቸው የኃዘን መግለጫ እንደሚከተለው ይነበባል።

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

"ዘጻመወ በዓለም የሐዩ ለዝሉፉ፤ እስመ ኢይሬኢ ሙስና፦ በዓለም የደከመ ለዘለዓለም ይድናል፤ ጥፋትን አያይምና። መዝሙር 48፥9

ንቡረ ዕድ በላይ መረሳ ሃይማኖት ያላቸው፣ ሃይማኖትን የመሰከሩ፣ ሃይማኖትም የመሰከረችላቸው፣ ወላዴ አእላፍ፣ መምህረ አሕዛብ፣ ፍቅረ እግዚአብሔርና ፍቅር ቢጽ የጸናላቸው፣ ዘመናቸውን በሙሉ ያስተማሩ፣ ሁሉን በእኩል ዓይን የተመለከቱ፣ ቃለ ወንጌልን በምእመናን ልብ ላይ የዘሩ ታላቅ ገበሬ፣ ፍሬአቸውን በብዙኃን ልጆቻቸው ላይ ያዩ፣ አበ ብዙኃን፣ አንደበታቸው ድንቅፍ የማይልባቸው፣ የዘመን ጎርፍ የማይወስዳቸው፣ በስፍራቸው የተገኙ፣ በትክክል ያወቁ፣ በነጻ የተቀበሉትን በነጻ የሰጡ፣ ተንቀሳቃሽ ቤተ መጻሕፍት ነበሩ።

እኒህ የሁላችን የዘመን እኩያ፣ የትምህርት ቤት ባልንጀራ፣ ማኅቶተ ቤተ ክርስቲያን የሆኑት አባት ከዚህ ዓለም ድካም ማረፋቸውን የሰማነው በከፍተኛ ኀዘን ውስጥ ነው።

የሕዝባቸውን መከራ በልባቸው ተሸክመው ለኖሩት ለእርሳቸው ይህ ዕረፍት ቢሆንም ለቤተ ክርስቲያን አባቶችና ለምእመናን ግን ትልቅ ጉዳት ነው።

ስለሆነም የቅድስት ቤተ ክርስቲያን ቅርስ ከመሆናቸው አንጻር የእርሳቸው ኅልፈት እንደ አንድ ሰው ኅልፈት የሚታይ ባለመሆኑ በቅዱስ ሲኖዶስና በመላው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ስም የተሰማንን ኀዘን እንገልጻለን!

በታላቁ ሊቅ ዕረፍት ያዘናችሁ ሁሉ እርሳቸው በሚታወሱበት መልካም ተግባራቸው እና በደቀ መዛሙርቶቻቸው ሕያው ናቸውና ልትጽናኑ ይገባችኋል።

እግዚአብሔር አምላካችን ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንን ይጠብቅልን። በሕይወተ ሥጋ ለተለዩን ዕረፍተ ነፍስን ፣ በዚህ ለቆየነውም መጽናናትን ይላክልን!

እግዚአብሔር አምላክ ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!!
አሜን።

አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃን ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም
ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት

ነሐሴ 16 ቀን 2017 ዓ.ም

ዋሽንግተን ዲሲ አሜሪካ
©የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽሕፈት ቤት

በቤተ ክርስቲያኗ ስም የሚደረግ የጎዳና ላይ የገንዘብ ልመና ሕገ ወጥ መሆኑ በድጋሚ ተገለጸ።  በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የአዳዲስ አብያተ ክርስቲያናት አተካከልና የነባርና...
22/08/2025

በቤተ ክርስቲያኗ ስም የሚደረግ የጎዳና ላይ የገንዘብ ልመና ሕገ ወጥ መሆኑ በድጋሚ ተገለጸ።

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የአዳዲስ አብያተ ክርስቲያናት አተካከልና የነባርና የጥንታዊያን አብያተ ክርስቲያናት እድሳት እንዲሁም በአብያተ ክርስቲያናት ዙሪያ የሚታነፁ ሁለገብ የልማት ሕንፃዎች የገንዘብ አሰባሰብ (የልግስና) መጠየቂያ ፈቃድ ሕግና ደንብን የተከተለ መሆኑ ይታወቃል፡፡

ይሁን እንጂ ከሕግና ደንብ ውጭ በየጊዜው የሚደረገው የጎዳና ላይ ልመና በቤተ ክርስቲያኗ እውቅና የሌለው ሕገ ወጥ ድርጊት ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያኗ አዲስ ለሚተከሉ ለሕንፃ አብያተ ክርስቲያናም ሆነ እድሳት ለሚደረግላቸው እንዲሁም በአብያተ ክርስቲያናት ዙሪያ ለሚታነፁ ሁልገብ የልማት ሥራዎች ሁሉ መተግበሪያ የሚሆን በቅዱስ ሲኖዶስ ፀድቆ የወጣ ደንብና ሥርዓት አላት፡፡
ይህን ውሳኔ በማስፈፀም የአሰራር ሂደቱን ተከታትሎ ፈቃድ የሚሰጠው የጠቅላይ ቤተ ክህነት የዕቅድና ልማት መምሪያ አዲስ ለሚተከሉም ሆነ በአገልግሎትና በአደጋ ለተጎዱ አብያተ ክርስቲያናት እንዲሁም በቤተ ክርስቲያን ዙሪያ ላሉ የልማት ሥራዎች የገንዘብ ልመና ፈቃድ የሚሰጥበት አግባብን ስንመለከት፤ በሀገረ ስብከቱ ጽ/ቤት በሊቀ ጳጳሱ ታምኖበት ለሥራው የተዋቀሩ የኮሚቴዎችን ዝርዝር የያዘ ደብዳቤ በተፈርሞ ሲቀርብ እና የሚሰራው ግንባታ የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ ወይም ቅድመ ካርታ ሕጋዊ ሰነድ ግንባታው የሚሠራበት ፕላን የሚፈጀው የዋጋ በዝርዝር ና ጥቅል ዋጋ ተገልፆ በባለሞያ የተረጋገጠ ሆኖ ሲቀርብ ነው፡፡
የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዕቅድና ልማት መምሪያ ይህን መሠረት አድርጎ ከአረጋገጠ በኋላ የገንዘብ አሰባሰቡን በተመለከተ ከአካባቢው ተወላጆች ከባለ ሀብትና ከበጎ አድራጊዎች እንዲያሰባስቡ ነገር ግን በጎዳና ላይ መለመን በጥብቅ የተከለከለ መሆኑን ተገልጾ ለሁለት ዓመት የሚቆይ የገንዘብ መሰብሰቢያ ፈቃድ ከአሰራር ደንብ ጋር ፈቃድ ይሰጣል፡፡ ይሁን እንጂ ከዚህ አግባብነት ካለው መሰረታዊ አሰራር ውጭ በመንቀሳቀስ
• የቤተ ክርስቲያኗን ነዋያተ ቅድሳት በመጠቀም በተለይም ሥዕለ አድህኖ በፀሐይና በአቧራ በዝናብ ይዘው የቤተ ክርስቲያኗን ገጽታ ማበላሸታቸው፤
• በአብዛኛው ተመሳሳይ ፎርጅድ የልመና ፈቃድ በመያዝ ሕዝቡን በማታለል ማጭበርበራቸው በርካታ ሕገወጥ ፎርጅድ ፈቃድ በየፖሊስ ጣቢያውን ፍ/ቤት በምርመራ ላይ መሆኑ፤
• በልመና የተሰማሩት ሕገ ወጥ አካላት ካህን ሳይሆኑ ጠምጥመውና ካባ ለብሰው መስቀል ይዘው በሕገ ወጥ መንገድ ገንዘብ እየሰበሰቡ ሕብረተሰቡን መዝረፋቸው በማስረጃ ተረጋግጧል፡፡
ስለሆነም የቤተ ክርስቲያኒቱ አባላት ምዕመናንም ሆኑ በጎ አድራጊ ረጂ ኢትዮጵያዊያን ሕጋዊ መሠረት የሌለውን የእግረኛና የትራፊክ መንገድ በመዝጋት በጎዳና ላይ እየተካሄደ ያለውን በቤተ ክርስቲያኗ ስም የሚደረገው ልመናን ሕጋዊ ሥርዓት ለማስያዝ በድጋሚ ግንዛቤ መስጠቱ አስፈልጓል፡፡ በተጨማሪም የምትለግሱት ገንዘብም ሆነ ማቴሪያል በትክክል ሕጋዊ እውቅና ኖሮት ከላይ በተገለጸው አግባብ ሲሆን ብቻ መሆኑንን መገንዘብ ያስፈልጋል፡፡
በአጠቃላይ የጎዳና ላይ ልመና ከቤተ ክርስቲያኗ እውቅና ውጭ መሆኑ ታውቆ እንዳትታለሉ እያስገነዘብን የሕግ አስከባሪ አካላት በቤተ ክርስቲያኗ ስም የሚደረግ የጎዳና ላይ ልመናን ለማስቆም ጠንካራ የሥራ ትብብር እንዲያደርግልን በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ስም እንጠይቃለን፡፡
© የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዕርገት መታሰቢያ በዓል አከባበር በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት በአንጎለላ ጽርሐ አርያም ሰሚነሽ ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ቤተ ክርስቲያን የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብ...
22/08/2025

የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዕርገት መታሰቢያ በዓል አከባበር በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት በአንጎለላ ጽርሐ አርያም ሰሚነሽ ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ቤተ ክርስቲያን የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ መጋቤ ሐዲስ ነቅዐጥበብ አባቡ በርካታ ምእመናን በተገኙበት ተከብሯል። አከባበሩን ቅዳሜ ምሽት 2 ሰዓት በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት አቡቀለምሲስ ሚዲያ መርሐ ግብር በ ይከታተሉ ።

የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም የዕረፍቷና የዕርገቷ መታሰቢያ  በጀሞ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም እና ቅ/ኪዳነ ምሕረት ቤተ ክርስቲያን ተከበረ።ሪፖርተር መ/ር ኪዱ ዜናዊ(  ነሐሴ 16 ቀ...
22/08/2025

የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም የዕረፍቷና የዕርገቷ መታሰቢያ በጀሞ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም እና ቅ/ኪዳነ ምሕረት ቤተ ክርስቲያን ተከበረ።
ሪፖርተር መ/ር ኪዱ ዜናዊ
( ነሐሴ 16 ቀን 2017 ዓ.ም)

የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም የእረፍቷና የዕርገቷ መታሰቢያ ክብረ በዓል በዐዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ጽ/ቤት ሥር በሚገኘው በጀሞ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም እና ቅ/ኪዳነ ምሕረት ቤተ ክርስቲያን ተከበረ።
በክብረ በዓሉ የኢኦተቤ መገናኛ ብዙኀን አገልግሎት ሥርጭት ድርጅት/ EOTC Broadcasting Service Agency/ ዋና ሥራ አስኪያጅ መ/ር አካለወልድ ተሰማ (ዶ/ር) ፣ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንና በርካታ ምእመናን በተገኙበት በደምቀት ተከብሮ ውሏል።

የእመቤታችን  የቅድስት ድንግል ማርያም በዓለ ዕርገት በራቡ ሀርቡ ደብረ ሲና  ቅድስት ኪዳነምሕረት   ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ በተገኙበ...
22/08/2025

የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም በዓለ ዕርገት በራቡ ሀርቡ ደብረ ሲና ቅድስት ኪዳነምሕረት ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ በተገኙበት በድምቀት ተከበረ።
ብፁዕነታቸው የሱባኤው ማሰርያ ቅዱስ ሥጋውና ክቡር ደሙ ነው ሲሉ አባታዊ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።
ሪፖርተር ሰላም አምባዬ
( ነሐሴ 16 ቀን 2017 ዓ.ም)

ነሓሴ 16 ቀን ቅድስት ቤተክርስቲያናችን የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ያረገችበትን በዓል በታላቅ መንፈሳዊ ሥነ ሥርዓት ታከብራለች።
የዘንድሮው የዕርገትዋ በዓል በሸገር ከተማ ሀገረ ስብከት ላይ በሚገኘው በዓለም ገና ከራቡ ደብረ ሲና ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ቤተክርስቲያን ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅ የደቡብ ምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት እና የሸገር ከተማ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የሸገር ከተማ ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ እና የሀገረ ስብከቱ የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት በታላቅ ድምቀት ተከብሮ ውሏል።

በሸገር ሀገረ ስብከት የስብከተ ወንጌል ማደራጃ ኃላፊ በሆኑት በመጋቤ ወንጌል መምህር ሄኖክ ታየ በራእይ ዮሐ.3፥21 ላይ ተጽፎ የምናገኘው :- እኔም ድል እንደ ነሣሁ፥ ከአባቴም ጋር በዙፋኑ ላይ እንደተቀመጥሁ፥ ድል ለነሣው ከእኔ ጋር በዙፋኔ ላይ ይቀመጥ ዘንድ እሰጠዋለሁ ። በሚል ኃይለ ቃል መነሻ በማድረግ የዕለቱ ትምህርተ ወንጌል ሰጥተዋል ።

በዕለቱ በደብሩ የተለያየ የልማት እንቅስቃሴዎች እየተከናወነ እንደሆነ በደብሩ አስተዳዳሪው በመልአከ ገነት ቀሲስ ልዑል የገለጹ ሲሆን ምእመናን የተጀመሩ የልማት ሥራዎች እንዲደግፉና የበኩላቸው አስትዋጽኦ ልያደርጉ እንደሚገባ ጠቁመዋል ።

ሀገራችን ኢትዮጵያ በአባቶቻችን ጸሎት ነው የምትጠበቀው በእግዚአብሔር ቤት ተገኝቶ መጸለይ መባረክ መታደል ነው።
ያለፈው የሱባኤ ልዩ ጊዜ ነው ያሰለፍንበት ሱባኤው አስጀምሮ ላስፈጸመን ለእግዚአብሔር ክብር ምስጋና ይድረሰው በማለት የጀመሩ ብፁዕነታቸው የሱባኤው ማሰርያው ቅዱስ ሥጋውና ክበር ደሙ ነው ሲሉ አባታዊ መልእክት ቃለምዕዳን እና ቡራኬው በመስጠት መርሐግብሩ ተጠናቋል።

በዕለቱም በደብሩ ሊቃውንት ወረብ እንዲሁም በደብረ ሰንበት ትምህርት ቤት ያሬዳዊ ዝማሬ ቀርቧል።

"የሻደይ ቄጤማ የምህረት፣ የደስታ እና የሰላም  ተምሳሌት ናት" ብፁዕ አቡነ በርናባስ(  ነሐሴ 16/2017 ዓ.ም የሻደይ በዓል ሃይማኖታዊ ሥርዓቱን ጠብቆ በሰቆጣ ከተማ ደብረ ፀሐይ ወይብላ...
22/08/2025

"የሻደይ ቄጤማ የምህረት፣ የደስታ እና የሰላም ተምሳሌት ናት" ብፁዕ አቡነ በርናባስ
( ነሐሴ 16/2017 ዓ.ም
የሻደይ በዓል ሃይማኖታዊ ሥርዓቱን ጠብቆ በሰቆጣ ከተማ ደብረ ፀሐይ ወይብላ ቅድስት ማርያም ካቴድራል እየተከበረ ነው።
በበዓሉ ላይ መልእክት ያስተላለፉት የዋግ ኽምራ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል ብፁዕ አቡነ በርናባስ ሻደይ የሰላም እና የፍቅር ምልክት ነው ብለዋል።

በኖኅ ዘመን የነበረው የውኃ ሙላት መጉደሉን ለማብሰር እርግብ የሰላም ቄጤማ እንዳመጣች ሁሉ ዛሬም ደናግል ዘማርያን የሻደይ ቄጤማ ይዘው እየዘመሩ ይውላሉ ነው ያሉት።

በኖኅ ዘመን ቄጤማ ሰላምን፣ ደስታን፣ ፍቅርን እንዳበሰረ ሁሉ ዛሬም የሻደይ ቄጤማ የምህረት የደስታ፣ የሰላም ተምሳሌት ኾኖ በቤተክርስትያኗ እየተከበረ መምጣቱን አንስተዋል።

ዛሬም ሀገራችን ሰላም እና ፍቅር ያስፈልጋታል ያሉት ብፁዕነታቸው በዓሉን ስናከብር ለሀገር ሰላም በመስበክ እና በመተባበር ሊኾን ይገባል ብለዋል። የተቸገሩትን ወገኖች በመርዳትና በመደገፍ በዓሉን ማክበር እንደሚገባም አሳስበዋል።
© አሚኮ

Address

Sahle Selassie Street
Addis Ababa
1000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የኢኦተቤ መገናኛ ብዙኀን አገልግሎት ሥርጭት ድርጅት/ EOTC Broadcasting Service Agency/ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to የኢኦተቤ መገናኛ ብዙኀን አገልግሎት ሥርጭት ድርጅት/ EOTC Broadcasting Service Agency/:

Share

EOTC BROADCASTING SERVICE AGENCY

የኢኦተቤ መገናኛ ብዙኃን አገልግሎት ስርጭት ድርጅት