Ethio Athletics

Ethio Athletics Providing Athletics news & information.

አትሌት ጉዳፍ ጸጋይ እውነቱን ይፋ አደረገች!"ስለእኔ ከዶፒንግ ጋር በተያያዘ በቀረቡ ዜናዎች ላይ አንድ መረጃ ላካፍላችሁ እወዳለሁ። በሐኪሜ ትዕዛዝ መሠረት የመውለድ አቅሜን (ፈርቲሊቲ) ለማ...
12/06/2026

አትሌት ጉዳፍ ጸጋይ እውነቱን ይፋ አደረገች!
"ስለእኔ ከዶፒንግ ጋር በተያያዘ በቀረቡ ዜናዎች ላይ አንድ መረጃ ላካፍላችሁ እወዳለሁ። በሐኪሜ ትዕዛዝ መሠረት የመውለድ አቅሜን (ፈርቲሊቲ) ለማሻሻል ሌትሮዞል (letrozole) የተባለውን ተጨማሪ መድኃኒት ወስጄ ነበር።

በአሁኑ ወቅት እርግዝናዬ በጥሩ ሁኔታ ላይ ይገኛል፤ ልጄ እንደተወለደም በፍጥነት ወደ ስፖርቱ እመለሳለሁ ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ።

ለአድናቂዎቼ በሙሉ ለምትሰጡኝ ፍቅር አመሰግናለሁ፣ ሁላችሁንም ናፍቄአችኋለሁ።

በተጨማሪም የአትሌቲክስ ኢንተግሪቲ ዩኒት (AIU) ላሳየኝ መረዳትና ድጋፍ አድናቆቴን እገልጻለሁ።"

ጉዳፍ ፀጋይ ደስታ

ብርቄ ሀየሎም በሻንግሀይ ዳይመንድ ሊግ ነገሰች!ዛሬ በቻይና ሻንግሀይ የ2026 የዳይመንድ ሊግ ውድድር በታላቅ ድምቀት ተካሂዷል። 🥇 በ1500 ሜትር የሴቶች ውድድር፦ አትሌት ብርቄ ሓየሎም 3...
16/05/2026

ብርቄ ሀየሎም በሻንግሀይ ዳይመንድ ሊግ ነገሰች!

ዛሬ በቻይና ሻንግሀይ የ2026 የዳይመንድ ሊግ ውድድር በታላቅ ድምቀት ተካሂዷል።

🥇 በ1500 ሜትር የሴቶች ውድድር፦ አትሌት ብርቄ ሓየሎም 3:55.56 በሆነ አስደናቂ ሰዓት ቀድማ በመግባት የውድድሩን ክብረወሰን (Meet Record) አሻሽላለች! የወቅቱን የዓለም ፈጣን ሰዓት (World Lead) አስመዝግባለች!
በዚሁ ርቀት የፓሪስ ኦሎምፒክ የ800 ሜትር የብር ባለቤቷ አትሌት ፅጌ ዱጉማ ሁለተኛ ሆና ስትገባ 3፡55.71 በሆነ ሰዓት የግል ምርጥ ሰዓቷን (PB) በማሻሻል ድንቅ ብቃቷን አሳይታለች። ሌላኛዋ አትሌት ወርቅነሽ መሰለ በ3:57.56 የዓመቱ ምርጥ ሰዓቷን (SB) በማስመዝገብ 4ኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች።

ትዕግስት አሰፋ በድጋሚ የራሷን የአለም ክብረወሰን በማሻሻል አሸነፈች!ትግስት ባለፈው አመት በለንደን ማራቶን ያስመዘገበችውን የሴቶች ብቻ የአለም ክብረወሰን በ9 ሰከንዶች በማሻሻል ነው ያሸነ...
26/04/2026

ትዕግስት አሰፋ በድጋሚ የራሷን የአለም ክብረወሰን በማሻሻል አሸነፈች!
ትግስት ባለፈው አመት በለንደን ማራቶን ያስመዘገበችውን የሴቶች ብቻ የአለም ክብረወሰን በ9 ሰከንዶች በማሻሻል ነው ያሸነፈችው

🇪🇹’s Tigst Assefa defends her TCS London Marathon crown, breaking her own women’s-only marathon world record once again with 2:15:41 👑

She lowers the very mark she set here last year by 9 seconds 😤

ዮሚፍ ቀጀልቻ ታሪክ ሰራ!ዮሚፍ ቀጀልቻ በመጀመሪያው የለንደን ማራቶን ርቀቱን ከሁለት ሰአት በታች 1:59:41 በማጠናቀቅ አዲስ ታሪክ ሰርቷል።ዮሚፍ በዛሬው የለንደን ማራቶን ውድድሩን አዲስ ...
26/04/2026

ዮሚፍ ቀጀልቻ ታሪክ ሰራ!
ዮሚፍ ቀጀልቻ በመጀመሪያው የለንደን ማራቶን ርቀቱን ከሁለት ሰአት በታች 1:59:41 በማጠናቀቅ አዲስ ታሪክ ሰርቷል።

ዮሚፍ በዛሬው የለንደን ማራቶን ውድድሩን አዲስ ክብረወሰን በማስመዝገብ ያሸነፈው ኬንያዊው ሴባስቲያን ሳዌን ተከትሎ በመግባት ሁለተኛ ደረጃን አግኝቷል።

አስደናቂ የማራቶን ሰአት ተመዘገበ!ኬንያዊው አትሌት ሴባስቲያን ሳዌ በዛሬው የለንደን ማራቶን ውድድር ርቀቀቱን 1:59:39 በማጠናቀቅ አዲስ የአለም ክብረወሰን አስመዘገበ።SABASTIAN SA...
26/04/2026

አስደናቂ የማራቶን ሰአት ተመዘገበ!
ኬንያዊው አትሌት ሴባስቲያን ሳዌ በዛሬው የለንደን ማራቶን ውድድር ርቀቀቱን 1:59:39 በማጠናቀቅ አዲስ የአለም ክብረወሰን አስመዘገበ።

SABASTIAN SAWE IS THE FIRST PERSON EVER TO RUN A SUB-TWO Abbott World Marathon Majors MARATHON!

A NEW ERA FOR MARATHON RUNNING!

የአፍሪካ ፈጣኑ ሯጭ ፈርዲናንድ ኦማንያላ በአዲስ አበባ ስታዲየም አሸነፈ!***በአዲስ አበባ ግራንድ ፕሪ የወንዶች የ100 ሜትር ፉክክር የአፍሪካ የመቶ ሜትር ፈጣኑ አትሌት ኬንያዊው ፈርዲናን...
18/04/2026

የአፍሪካ ፈጣኑ ሯጭ ፈርዲናንድ ኦማንያላ በአዲስ አበባ ስታዲየም አሸነፈ!
***
በአዲስ አበባ ግራንድ ፕሪ የወንዶች የ100 ሜትር ፉክክር የአፍሪካ የመቶ ሜትር ፈጣኑ አትሌት ኬንያዊው ፈርዲናንድ ኦማንያላ ርቀቱን በ9.98 በማጠናቀቅ ድል አድርጓል።

አሜሪካዊቷ ጋቢ ቶማስ  #በአዲስ አበባ ግራንድ ፕሪ በሁለት ርቀቶች አሸነፈች!****በዛሬው የአዲስ አበባ ግራንድ ፕሪ የአንድ ቀን ውድድር  በሴቶች 100 ሜትር እና 200 ሜትር አሜሪካዊቷ ...
18/04/2026

አሜሪካዊቷ ጋቢ ቶማስ #በአዲስ አበባ ግራንድ ፕሪ በሁለት ርቀቶች አሸነፈች!
****
በዛሬው የአዲስ አበባ ግራንድ ፕሪ የአንድ ቀን ውድድር በሴቶች 100 ሜትር እና 200 ሜትር አሜሪካዊቷ አትሌት ጋቢ ቶማስ አሸንፋለች። በ100 ሜትር ርቀቱን 11.13 ሰከንዶች ነው ያጠናቀቀችው።

በተጨማሪም ጋቢ ቶማስ 200 ሜትሩን ስታሸንፍ፣ ርቀቱን ለማጠናቀቅ 22.42 ፈጅቶባታል።

አትሌት ምስጋና ዋቁማ በዓለም አትሌቲክስ የርምጃ ሻምፒና ታሪክ ለኢትዮጵያ የመጀመሪያውን ሜዳሊያ አስገኘበብራዚል ብራዚሊያ ከተማ 31ኛው የዓለም አትሌቲክስ የርምጃ ሻምፒዮና ኢትዮጵያውያን አት...
12/04/2026

አትሌት ምስጋና ዋቁማ በዓለም አትሌቲክስ የርምጃ ሻምፒና ታሪክ ለኢትዮጵያ የመጀመሪያውን ሜዳሊያ አስገኘ
በብራዚል ብራዚሊያ ከተማ 31ኛው የዓለም አትሌቲክስ የርምጃ ሻምፒዮና ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የተሳተፉባቸው የፍጻሜ ውድድሮች ተደርገዋል።

በወንዶች የግማሽ ማራቶን የርምጃ ፍጻሜ ውድድር አትሌት ምስጋና ዋቁማ 1 ሰዓት ከ27 ደቂቃ ከ33 ሴኮንድ ሁለተኛ ደረጃን በመያዝ የብር ሜዳሊያ አግኝቷል።

አትሌት ምስጋና በኢትዮጵያ ስድስተኛ የሻምፒዮናው ተሳትፎ የመጀመሪያውን ሜዳሊያ አስገኝቷል።

ከ20 ዓመት በታች የ10 ኪሎ ሜትር ሴቶች የፍጻሜ ውድድር ህይወት አምባው በ48 ደቂቃ ከ52 ሴኮንድ ዘጠነኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች። በርቀቱ የግል ምርጥ ሰዓቷን አስመዝግባለች።

ቻይናዊቷ አትሌት ዩቶንግ ያንግ አንደኛ ወጥታለች።

እንዲሁም ጣልያናዊቷ ሴሬና ዲ ፋቢዮ ሁለተኛ፣ ቻይናዊቷ ሊሁዋ ኒ ሶስተኛ ደረጃን ይዘው አጠናቀዋል።

በ10 ኪሎ ሜትር ከ20 ዓመት በታች ወንዶች ፍጻሜ አብዱሰላም አብዱልወሀብ 42 ደቂቃ ከ21 ሴኮንድ 11ኛ ደረጃን ይዞ ጨርሷል። በርቀቱ የግል ምርጥ ሰዓቱን አስመዝግቧል።

ኢትዮጵያ በተሳተፈችባቸው ሶስት የፍጻሜ ውድድሮች አንድ የብር ሜዳሊያ በማግኘት አጠናቃለች።

በሻምፒዮናው ተሳትፎ ታሪኳ የመጀመሪያ ሜዳሊያ አግኝታለች

Athlete Kenenisa Bekele's 17 years daughter Elnata published a book.Ethiopian legend express his feeling as follows."Tod...
14/06/2025

Athlete Kenenisa Bekele's 17 years daughter Elnata published a book.

Ethiopian legend express his feeling as follows.

"Today, our first daughter Elnata Kenenisa published her very first book — and we couldn't be prouder! At just 17 years old, she has poured her heart into a collection of 17 beautiful poems, titled "Fragments of Emotion." Such a perfect title for the heartfelt words she’s shared.

We are all so proud of her incredible achievement and the talent she’s already showing at such a young age. Elnata, your dedication and creativity inspire us every day. Keep shining and chasing your dreams — this is just the beginning!

We love you so much, and we can't wait to see what you accomplish next. Stay blessed and keep writing your amazing story! "

.

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethio Athletics posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share