
30/06/2025
ዱባይ የአየር ላይ ታክሲ የሙከራ በረራ አደረገች
ዱባይ በመካከለኛው ምሥራቅ የመጀመሪያውን በኤሌክትሪክ የሚሰራ የአየር ላይ ታክሲ ሙከራ አደረገች፡፡
ሙከራው የኢሚሬትስ መንገዶች ባለ ስልጣን መቀመጫውን አሜሪካ ካደረገው ጆቢ ኤቪየሸን ጋር በመተባበር ለዚሁ ዓለማ በተመረጠ በርሃማ አካባቢ መደረጉን ዥንዋ የዜና አውታር ዛሬ አስነብቧል፡፡
የአየር ላይ ታክሲ ሙከራው ዱባይ መጭውን ዘመን የሚመጥን የትራንስፖርት አግልግሎት ለማስተዋወቅ ያላትን ቁርጠኝነት ያሳያል ሲሉ ፤ ሸህ ሃምዳን ቢን ሞሃመድ ቢን ራሽድ አል ማክቱም ተናረዋል፡፡
ታክሲዎቹ በሰዓት እስከ 320 ኪሜ መብራር ይችላሉ የተባለ ሲሆን፤ እሰከ 360 ኪሎ ሜትር ድረስ የማካለል አቅም አንዳለቸውም ተዘግቧል፡፡
መንደርድር ሳያስፈልጋቸው በቀጥታ ብድግ ብሎው እንደሚበሩ የተነገረላቸው በራሪ ታክሲዎች ፣ ሲየስፈልግም ያለምንም ማንዣብብ ፌርማታቸው ላይ ያርፋሉ ተብሏል፡፡
ፓይለቱን ሳይጨምር እያዳንዳቸው አራት ሰዎችን የመጫን አቅም ያላቸው በራሪ ታከሶዎቹ ህዝብ ለሚበዛበቸውና ለሚጨናነቁ ከተሞች ፈቱን መድሃኒት ናቸው ተብሏል፡፡
በዱባይ ዓለም ዓቀፍ ኤርፖርት አቅራቢያ በ2026 የአየር ላይ ፌርማታ ለመክፈት መታቀዱንም ፤ የኤሜሬትስ መንገዶችን ባለ ሰልጣንን ጠቅሶ የቻይናው የዜና አውታር ዥንዋ አስነብቧል፡፡
በአህመድ መሃመድ