FM Addis 97.1 /ኤፍ ኤም አዲስ 97.1 ሬዲዮ/

FM Addis 97.1 /ኤፍ ኤም አዲስ 97.1 ሬዲዮ/ Ethiopian Broadcasting Corporation is a 24 hour working public media.
(274)

Ethiopian Broadcasting Corporation is a national media which disseminates its news and programs world wide via Television,Radio and Website.

ዱባይ  የአየር ላይ ታክሲ የሙከራ በረራ   አደረገችዱባይ በመካከለኛው ምሥራቅ የመጀመሪያውን  በኤሌክትሪክ የሚሰራ   የአየር ላይ ታክሲ ሙከራ አደረገች፡፡ሙከራው የኢሚሬትስ መንገዶች ባለ ስ...
30/06/2025

ዱባይ የአየር ላይ ታክሲ የሙከራ በረራ አደረገች

ዱባይ በመካከለኛው ምሥራቅ የመጀመሪያውን በኤሌክትሪክ የሚሰራ የአየር ላይ ታክሲ ሙከራ አደረገች፡፡

ሙከራው የኢሚሬትስ መንገዶች ባለ ስልጣን መቀመጫውን አሜሪካ ካደረገው ጆቢ ኤቪየሸን ጋር በመተባበር ለዚሁ ዓለማ በተመረጠ በርሃማ አካባቢ መደረጉን ዥንዋ የዜና አውታር ዛሬ አስነብቧል፡፡

የአየር ላይ ታክሲ ሙከራው ዱባይ መጭውን ዘመን የሚመጥን የትራንስፖርት አግልግሎት ለማስተዋወቅ ያላትን ቁርጠኝነት ያሳያል ሲሉ ፤ ሸህ ሃምዳን ቢን ሞሃመድ ቢን ራሽድ አል ማክቱም ተናረዋል፡፡

ታክሲዎቹ በሰዓት እስከ 320 ኪሜ መብራር ይችላሉ የተባለ ሲሆን፤ እሰከ 360 ኪሎ ሜትር ድረስ የማካለል አቅም አንዳለቸውም ተዘግቧል፡፡

መንደርድር ሳያስፈልጋቸው በቀጥታ ብድግ ብሎው እንደሚበሩ የተነገረላቸው በራሪ ታክሲዎች ፣ ሲየስፈልግም ያለምንም ማንዣብብ ፌርማታቸው ላይ ያርፋሉ ተብሏል፡፡

ፓይለቱን ሳይጨምር እያዳንዳቸው አራት ሰዎችን የመጫን አቅም ያላቸው በራሪ ታከሶዎቹ ህዝብ ለሚበዛበቸውና ለሚጨናነቁ ከተሞች ፈቱን መድሃኒት ናቸው ተብሏል፡፡

በዱባይ ዓለም ዓቀፍ ኤርፖርት አቅራቢያ በ2026 የአየር ላይ ፌርማታ ለመክፈት መታቀዱንም ፤ የኤሜሬትስ መንገዶችን ባለ ሰልጣንን ጠቅሶ የቻይናው የዜና አውታር ዥንዋ አስነብቧል፡፡

በአህመድ መሃመድ

አፍሪካ የአፈር ማዳበሪያ ከውጭ ማስገባት ሙሉ በሙሉ ልታቆም ነው አሊኮ ዳንጎቴ የአፍሪካዊው ባለጸጋ አሊኮ ዳንጎቴ አፍሪካ በ40 ወራት ውስጥ የማዳበሪያ ሉዓላዊነቷን ታጋግጣለች ብለዋል ፡፡ይህ...
30/06/2025

አፍሪካ የአፈር ማዳበሪያ ከውጭ ማስገባት ሙሉ በሙሉ ልታቆም ነው

አሊኮ ዳንጎቴ

የአፍሪካዊው ባለጸጋ አሊኮ ዳንጎቴ አፍሪካ በ40 ወራት ውስጥ የማዳበሪያ ሉዓላዊነቷን ታጋግጣለች ብለዋል ፡፡

ይህን ግብ ለማሳካት ደግሞ “የዳንጎቴ የማዳበሪያ ፋብሪካን” የማስፋፋት ስራ እንደሚከናወን ገልፀዋል ፡፡

የማስፋፊያው ስራው አሁን ላይ ያለውን የፋብሪካውን ዓመታዊ የማምረት አቅም 3 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን ማዳበሪያን በሶስት እጥፍ ለማሳደግ እንደሚያስችል አስረድተዋል ፡፡

የሚሰፋፋው ፋብሪካ በአለም ትልቁ ፋብሪካ ለመሆን ያለመ ሲሆን፣ የአሁኑን የኳታር የማምረት አቅም ይበልጣል።

ይህ እንቅስቃሴ ዓለም አቀፍ የማዳበሪያ ገበያን የሚቀይር፣ የአፍሪካን ሉዓላዊ የሚያደርግና አህጉሪቱ የማዳበሪያ ላኪ ያደርጋታል ተብሎ ይጠበቃል።

እንደ ቲቪ ኒውስ ናይጄሪያ ዘገባ
ይህ የአሊኮ ዳንጎቴ ጥረት
የአፍሪካ የግብርና ምርታማነትን ለመጨመር እና የምግብ ዋስትናን ይበልጥ ለማሳደግ ወሳኝ መሆኑ ተገልጿል ።

በሰላምን ገዳ

30/06/2025

ዶትስትሪም

ነገ ምሽት 3 ሰዓት ይጠብቁን!

#ዶትስትሪም

ኤፍ ኤም አዲስ የዕለቱ የዝውውር ዜና‎ # ባርሴሎና(ኒኮ ዊሊያምስ)‎ስፔናዊው የክንፍ መስመር ተጫዋች ኒኮ ዊሊያምስ ወደ ባርሴሎና የሚያደርገው ዝው  0 nውር መስተጓጎሉን የስፔኑ ማርካ ዘግቧ...
30/06/2025

ኤፍ ኤም አዲስ የዕለቱ የዝውውር ዜና

‎ # ባርሴሎና(ኒኮ ዊሊያምስ)

‎ስፔናዊው የክንፍ መስመር ተጫዋች ኒኮ ዊሊያምስ ወደ ባርሴሎና የሚያደርገው ዝው 0 nውር መስተጓጎሉን የስፔኑ ማርካ ዘግቧል።

ባርሴሎናዎች ተጫዋቹን በላ ሊጋው እንደሚያስመዘግቡ እርገጠኛ አለመሆናቸው ተገልጿል።ተጫዋቹ አስቀድሞ ስለምዝገባው መተማመኛ ይፈልጋል።

‎የተጫወቹ ክለብ ቢልባኦ ዊሊያምስ ከባርሳ ይልቅ ወደ ባየር ሙኒክ እንዲዛወር ይፈልጋል።

‎ # አርሴናል(በኤቢሪቼ ኢዜ)

‎አርሴናል በኤቢሪቼ ኢዜ ዝውውር ጉዳይ በይፋ ንግግሮች ጀምሯል።
‎መድፈኞቹ የተጫዋቹን የውል ማፍረሻ ዋጋ ለመክፈል ፍቃደኛ ናቸው።ሆኖም ከጎረቤታቸው ቶተንሀም ብርቱ ፉክክር ይጠብቃቸዋል።

የቶማስ ፍራንክ ቡድን መሀመድ ኩዱስንም ከዌስትሀም ይፈልጋል።

‎ # ባየርሊቨርኩሰን

‎የቡንደስሊጋው ክለብ ማሊክ ቲልማንን ከፒኤስቪ ለማስፈረም ተስማማ።
‎በሁለቱ ክለቦች መካከል በተደረሰው ስምምነት ዝውውሩ ከ35 -40 ሚሊየን ዩሮ አጠቃላይ ፓኬጅ ይኖረዋል።

‎ሊቨርኩሰኖች ቲልማንን የፍሎሪያን ቪርዝ የረዥም ጊዜ ተተኪ ለማድረግ ተማምነዋል።

‎ # ማንቸስተር ዩናይትድ (ጆኒ ኤቫንስ)

‎የ37 ዓመቱ የማንቸስተር ዩናይትድ ተከላካይ ጆኒ ኤቫንስ ከፕሮፌሽናል እግርኳስ ተጫዋችነት እራሱን ካገለለ በኋላ በሌላ ሚና ብቅ ብሏል።

‎ተጫዋቹ ከሀያ ዓመት በላይ በዘለቀው የእግርኳስ ተጫዋችነት ህይወቱ 536 ጨዋታዎችን አድርጓል።
‎ኤቫንስ አሁን በማንችስተር ዩናይትድ የአካዳሚ ተጫዋቾችን ብቃት የማሳደግ ሚና ተሰጥቶታል።

ሃላፊነቱ ከክለቡ ስፖርቲንግ ዳይሬክተርና አካዳሚ ዳይሬክተሩ ጋር በጋራ በመስራት ታዳጊዎችን ለዋናው ቡድን የመመገብ ሃላፊነትን የሚወጣ ይሆናል።

በፍቃዱ ተስፋዬ

የፕሮግራም ጥቆማከ "ዛሬ" አዘጋጆች #ዛሬ በኤፍ ኤም አዲስ 97.1 የሚተላለፈው የመዝናኛ ፕሮግራም ከድምፃዊት የሺ ደምመላሽ ጋር ቆይታ ያደርጋል::"ውብ ሰው" የተሰኝውን አዲስ አልበም ለአድ...
30/06/2025

የፕሮግራም ጥቆማ
ከ "ዛሬ" አዘጋጆች

#ዛሬ በኤፍ ኤም አዲስ 97.1 የሚተላለፈው የመዝናኛ ፕሮግራም ከድምፃዊት የሺ ደምመላሽ ጋር ቆይታ ያደርጋል::

"ውብ ሰው" የተሰኝውን አዲስ አልበም ለአድማጭ ያቀረበችው ድምፃዊቷ ከአዳዲስ ስራዎቿ ጋር ቆይታ ታደርጋለች::

ማክሰኞ ሰኔ 24/2017ዓ.ም ከቀኑ 8:00 እስከ 10:00 ይጠብቁን::

30/06/2025

አዲስ መረጃ … ሰኔ 23/2017 ዓ.ም
#አዲስመረጃ

የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና መሰጠት ጀመረ******************የመጀመሪያው ዙር የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና በመላ ሀገሪቱ መሰጠት ጀምሯል፡፡በዛሬው ዕለት በሁሉም የመፈተኛ ጣ...
30/06/2025

የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና መሰጠት ጀመረ
******************

የመጀመሪያው ዙር የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና በመላ ሀገሪቱ መሰጠት ጀምሯል፡፡

በዛሬው ዕለት በሁሉም የመፈተኛ ጣቢያዎች ለተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ነው ፈተናው መሰጠት የጀመረው።

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር ኢ/ር) የ2017 ትምህርት ዘመን የ 12ኛ ክፍል ማጠቃለያ ፈተናን በቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ተገኝተው አስጀምረዋል።

የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ አየለች እሸቴ፤ ለዘንድሮዉ የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና በቂ ዝግጅት መደረጉን ለኢቲቪ ገልጸዋል፡፡

ኩረጃን ሙሉ ለሙሉ ለማስቀረት ትምህርት ሚኒስቴር ከባለድርሻ አካላት ጋር ጠንካራ ስራ መስራቱንም ተናግረዋል።

በሀገር አቀፍ ደረጃ የ 2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ከ608 ሺህ በላይ ተማሪዎች ይወስዳሉ።

በአዲስ አበባ 51 ሺህ 259 ተማሪዎች በተፈጥሮ ሳይንስ እና በማህበራዊ ሳይንስ በሁለት ዙር በበይነ መረብ እና በወረቀት ይፈተናሉ።

ፈተናዉ ለተፈጥሮ ሳይንስ እና ለማሕበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች በወረቀት እና በበይነ መረብ ከሰኔ 23 እስከ ሐምሌ 8 በፈተና መስጫ ማዕከላት ይሰጣል።

በምንተስኖት ይልማ

30/06/2025

ብርቱ ወግ 🔥🔥

በኢቲቪ ዜና ቻናል - በቅርብ ቀን ይጠብቁን!

#ብርቱወግ

አፍሪካዊቷን ጋዜጠኛ “ ቆንጆ ነሽ” በማለት ያደነቁት ዶናልድ ትራምፕ መነጋገሪያ ሆነዋል።በነጩ ቤተ -መንግስት  ለዘገባ  የተገኘችውን አፍሪካዊት ጋዜጠኛ ቆንጆ ነሽ በማለት አድናቆታቸውን የገ...
30/06/2025

አፍሪካዊቷን ጋዜጠኛ “ ቆንጆ ነሽ” በማለት ያደነቁት ዶናልድ ትራምፕ መነጋገሪያ ሆነዋል።

በነጩ ቤተ -መንግስት ለዘገባ የተገኘችውን አፍሪካዊት ጋዜጠኛ ቆንጆ ነሽ በማለት አድናቆታቸውን የገለጹት የአሜሪካው ፕሬዝዳንት መነጋሪያ ሆነዋል፡፡

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ትራምፕ ዴሞክራቲከ ሪፐብሊክ ኮንጎንና ረዋንዳን ለማስታረቅ በተሰናዳው ስነ-ስርዓት ላይ በነጩ- ቤተ መንግሰት ለዘገባ የተገኘችውን አንጎላዊት ጋዜጠኛ ሃርያና ቬራስን ነው ቆንጆ ነሽ ሲሉ ያደነቋት፡፡


እንዳንች ያሉ ቆነጃጀት ጋዜጠኞች ቢበዙ እንዴት መልክም ነበር ሲሉም ምኞታቸውን ገልጸዋል፡፡

"ይህን ማለቴ ትክክል ላይሆን ይችላል” ቢሆንም “በጣም ውብ ናት: ሲሉ ተደምጠዋል፡፡

በአህመድ መሃመድ

30/06/2025

አዲስ ስፖርት

30/06/2025

የኢትዮጵያ ጊዜ … ሰኔ 23/2017 ዓ.ም #አዲስመረጃ

Address

Addis Ababa

Telephone

+2515172516

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when FM Addis 97.1 /ኤፍ ኤም አዲስ 97.1 ሬዲዮ/ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to FM Addis 97.1 /ኤፍ ኤም አዲስ 97.1 ሬዲዮ/:

Share

Our Story

FM Addis 97.1 is the First FM radio station in Ethiopia . On air since 2000. You can listen our station for 24 hours throughout the country and outside Ethiopia.

በ1992 ዓ.ም የተመሰረተውና በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ኤፍ ኤም አዲስ 97.1 ሬዲዮ በተለያዩ የማሰራጫ አማራጮች በመላ ሀገሪቱና በባህርማዶ ለሚገኙ አድማጮቹ ለ24 ሰአታት የተለያዩ ዝግጅቶች ይቀርቡበታል፡፡ የፌስ ቡክ ትስስራችን ቤተሰብ በመሆንዎም እናመሰግናለን፡፡