FM Addis 97.1 /ኤፍ ኤም አዲስ 97.1 ሬዲዮ/

FM Addis 97.1 /ኤፍ ኤም አዲስ 97.1 ሬዲዮ/ Ethiopian Broadcasting Corporation is a 24 hour working public media.
(297)

Ethiopian Broadcasting Corporation is a national media which disseminates its news and programs world wide via Television,Radio and Website.

07/11/2025
የማንቸስተር ዩናይትዱ አሰልጣኝ ሩበን አሞሪም የጥቅምት ወር የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ኮከብ አሰልጣኝ ሆኗል።ዩናይትድ በተጫወችም አሰልጣኝም ሽልማቱን አሸንፏል።
07/11/2025

የማንቸስተር ዩናይትዱ አሰልጣኝ ሩበን አሞሪም የጥቅምት ወር የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ኮከብ አሰልጣኝ ሆኗል።

ዩናይትድ በተጫወችም አሰልጣኝም ሽልማቱን አሸንፏል።

የብልፅግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች በኦሮሚያ ክልል የተለያዩ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ ************ስልጠና ሲወስዱ የነበሩ የብልፅግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ሸዋ ...
07/11/2025

የብልፅግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች በኦሮሚያ ክልል የተለያዩ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ
************

ስልጠና ሲወስዱ የነበሩ የብልፅግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ሸዋ ዞን እየተከናወኑ የሚገኙ የግብርና ክላስተሮችንና ሌሎች የልማት እንቅስቃሴዎችን ጎብኝተዋል፡፡

ከሁሉም ክልሎች የተውጣጡ የብልፅግና ፓርቲ አመራሮች ባለፉት 10 ቀናት በአዳማ ከተማ ስልጠና ሲወስዱ ቆይተዋል።

ሰልጣኞቹ በዛሬው ዕለት በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሸዋ ዞን ቦራ ወረዳ በክላስተር እየለማ ያለውን የፓፓያ ማሳ ተመልክተዋል፡፡

በክላስተር እየለማ ያለው እና “red ready" የሚባለው የፓፓያ ዝርያ ከአንድ ዛፍ ላይ እስከ አንድ ኩንታል ምርት ሊያስገኝ እንሚችል በምሥራቅ ሸዋ ግብርና ቢሮ ማብራሪያ ተሰጥቷል፡፡

አመራሮቹ በዞኑ ሉሜ ወረዳ በክላስተር እየለማ ያለውን የዓሣ ምርትም የጎበኙ ሲሆን፣ በክላስተር እየለማ ያለው ዓሣ አመራረት ትምህርት የሚወሰድበት እንደሆነ ተጠቅሷል፡፡

በሉሜ ወረዳ ቆቃ ባና ቀበሌ ለ80 ወጣቶች የሥራ ዕድል የፈጠረው የዓሣ ማርቢያ ኩሬም ሌሎች ክልሎች ጥሩ ተሞክሮ ያዩበት መሆኑ ተገልጿል።

በጉብኝቱ የተሳተፉት የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ(ዶ/ር)፤ ኢትዮጵያ ብዝኃ ኢኮኖሚ አካሄድን መጀመሯ ብልፅግናን ለማሳካት ትክክለኛው መንገድ ላይ መሆኗን ማሳያ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡

በብልፅግና ሂደት ውስጥ ገጠሩን ማሸጋገር እና ማዘመን ትኩረት የተሰጠው ጉዳይ መሆኑን ያነሱት ዶ/ር ኤርጎጌ፤ አርሶ አደሩ ለፍጆታ ከማምረት በዘለለ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ በሚደረገው ሂደት ሚናው የጎላ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡

በገጠር ትራንስፎርሜሽን ከማምረት ለውጪ ገበያ እስከማቅረብ የዘለቀ መሆኑንም ያስገነዘቡት ሚኒስትሯ፣ ገጠሩን ለኑሮ ምቹ ለማድረግ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ገጠሩን እና ከተማውን ለማስተሳሰር የተሄደበት ርቀት በጎ ጅምሮች መኖራቸውን ያመላከተ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

በአስማረ ብርሀኑ

07/11/2025
የፋሲል ግቢ ለዳግም ውልደት በቅቷል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)***************** የፋሲል ግቢ ተውቦ እና አምሮ ለዳግም ውልደት መብቃቱን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕ...
07/11/2025

የፋሲል ግቢ ለዳግም ውልደት በቅቷል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
*****************

የፋሲል ግቢ ተውቦ እና አምሮ ለዳግም ውልደት መብቃቱን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተናገሩ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ የፋሲል ግንብ የትም የማናገኘው ውድ ሀብት መሆኑን ጠቅሰው፣ "በእጃችን ስላለ ግን የሚገባውን ዋጋ አልሰጠነውም" ብለዋል።

"ይህን አባቶቻችን ያስረከቡንን ወርቅ ሀብት ይዘን ሀገር ብናለማ ኢትዮጵያ ዛሬ ተረጂ እና ለማኝ አትሆንም ነበር" ሲሉ ቁጭታቸውን ገልጸዋል።

"ዋናው ችግራችን እኛ እናንስና ታላላቆቹን ጎትተን መተካከል መፈለጋችን ነው”፤ ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ከእነዚያ ታላላቅ መሪዎች በኋላ ኢትዮጵያ ውስጥ የተከሰተው አንሰው ትላልቁን ጎትተው የሚያሳንሱ በመበራከታቸው እንደሆነ ገልጸዋል።

ታላቆችን ማድነቅ እና ማክበር፣ የታላላቆችን ሥራ መመርመር ሲጀመር በእነሱ ሥራ ላይ ጡብ በመጨመር የተደመረ ዕድገት ሊያመጣ እንደሚችል ነው የተናገሩት።

ታላላቆችን ማሳነስ እና ሥራቸውን ማኮሰስ ግን የሚያቀጭጭ መሆኑን ጠቅሰው፣ "ትላንትናችን መታወቂያችን እና መታወሻችን በመሆኑ ትላንትናችንን መርሳት የለብንም" ብለዋል።

ኋላውን ማስታወስ የሰው ተፈጥሮ መሆኑን እና ኋላውን ማስታወስ የቻለ ደግሞ ወደ ፊት ለመራመድ አቅም እንደሚኖረው ጠቅሰዋል።

ጎንደር በትላንቷ ታሪክ ላይ ውበት መጨመሯን ጠቅሰው፣ ታዳጊዎች የነገ ብሩህ ተስፋቸው እዚህ ውስጥ ስለሚገኝ ራሳቸውን ማዘጋጀት እንዳለባቸው ጥሪ አቅርበዋል።

በለሚ ታደሰ

07/11/2025
ብርያን ምቡሞ የጥቅምት ወር ኮከብ ተጫወች ሆነ።የማንቸስተር ዩናይትዱ የአጥቂ አማካኝ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የወሩ ኮከብ ተመርጧል። ምቡሞ በወሩ 3 ግቦችን ሲያስቆጥር 1 አመቻችቶ ማቀበል ...
07/11/2025

ብርያን ምቡሞ የጥቅምት ወር ኮከብ ተጫወች ሆነ።

የማንቸስተር ዩናይትዱ የአጥቂ አማካኝ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የወሩ ኮከብ ተመርጧል።

ምቡሞ በወሩ 3 ግቦችን ሲያስቆጥር 1 አመቻችቶ ማቀበል ችሏል።

ዩናይትድ በ11ኛ ሳምንት ነገ ከቶተነሀም በሚያደርገው ጨዋታ የሚጠበቅ ተጫዎች ነው

07/11/2025

ከማንችስተር ዩናይትድ vs ከሊቨርፑል ደጋፊዎች ጋር የሚደረግ ቆይታ

07/11/2025

የኢትዮጵያ ጊዜ…ጥቅምት 28/2018 ዓ.ም
#የኢትዮጵያጊዜ

07/11/2025

የመገጭ የመስኖ ልማት ፕሮጀክት ቁልፍ የሆነው የወንዝ ቅልበሳ ሥራ በተሳካ መልኩ ተጠናቋል

የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ

የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በጎንደር በነበራቸው ጉብኝት የመገጭ የመስኖ ልማት ፕሮጀክት የሥራ ሁኔታን መገምገማቸውን በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ፅፈዋል::

ፕሮጀክቱ 870 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ 17 ሽህ ሄክታር በመስኖ አቅርቦት ይሸፍናል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተናግረዋል፡፡

የፕሮጀክቱ ቁልፍ የሆነው የወንዝ ቅልበሳ ሥራ በተሳካ መልኩ ተጠናቋል ነውያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፡፡

የቀሩት ሥራዎችም በተያዘላቸው የጊዜ ሰሌዳ እየተካሄዱ ይገኛሉ ብለዋል ።

የመገጭ ግድብ ሲጠናቀቅ የአካባቢውን የግብርና ምርታማነት የሚያሳድግ እንደሚሆንም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አመላክተዋል።

የተመኙሽ አያሌው

07/11/2025

ወቅታዊ ውይይት - ብሔራዊ ጥቅምና ዘላቂ ሰላም ፣ ሀገራዊና ቀጠናዊ እንቅስቃሴዎች

የኮሪደር ልማቱ አዲስ አበባን ከሰለጠኑ የአለም ሀገራት ከተሞች ጋር ተወዳዳሪ የሚያደርጋት ነው         አርክቴክት ዮሐንስ መኮንንበአዲስ አበባ እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማት መዲናዋን...
07/11/2025

የኮሪደር ልማቱ አዲስ አበባን ከሰለጠኑ የአለም ሀገራት ከተሞች ጋር ተወዳዳሪ የሚያደርጋት ነው

አርክቴክት ዮሐንስ መኮንን

በአዲስ አበባ እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማት መዲናዋን ከሰለጠኑ የአለም ሀገራት ከተሞች ጋር ተወዳዳሪ የሚያደርጋት ነው ሲሉ አርክቴክት ዮሐንስ መኮንን ከኢቢሲ ኤፍ ኤም አዲስ 97.1 ጋር ባደረጉት ቆይታ ተናግረዋል፡፡

ሰዎች ከተማ ውስጥ ሲንቀሳቀሱ ደህንነታቸውና ምቾታቸው የተጠበቀ ነው ወይ የሚለው በኪነ ህንፃ ሳይንስ አንድ ከተማ ለነዋሪዎቿ ምቹ መሆኗ ሲጠና ከሚታዩት ዋና ዋና ነገሮች አንዱ ነው ብለዋል አርክቴክት ዮሐንስ፡፡

የትራንስፖርት አማራጭ፤ የእግረኛና የብስክሌት መንገዶች መኖር፤ ከተማዋ ለአካል ጉዳተኞች፣ ለህፃናት ተማሪዎችና ለተሸከርካሪዎች ምቹ ናት ወይ የሚሉት ደግሞ ከመመዘኛ መስፈርቶቹ መካከል ተጠቃሽ መሆናቸውን ባለሙያው አንስተዋል፡፡

አዲስ አበባ ለበርካታ ዓመታት መስፈርቱን ሳታሟላ ቆይታለች ያሉት ባለሙያው የኮሪደር ልማቱ ለከተማዋ ሰፊ እድል ይዞ የመጣ ነው ብለዋል፡፡

አሁን በኮሪደር ልማቱ ክፍት ቦታዎች በመኖራቸው የልጆች መጫወቻ፣ አረንጓዴ ስፍራዎች፣ የእግረኛና የብስክሌት መንገዶች እንዲሁም የስፖርት ማዘውተሪያ ቦታዎችን በመስራት የህዝቡ ደህንነትና ጤንነት እንዲጠበቅ በማድረግ የተረጋጋ ከተማ እንድትሆን አስተዋፅኦ እንደሚያበረክት ገልፀዋል፡፡

ከከተማ እቅድ እና ከኪነ ህንጻ አንፃርም ብዙ ጉድለቶችን እየሞላ የሚሄድ ፕሮጀክት መሆኑን ጠቁመዋል፡፡

በክልል ከተሞች የተጀመረው የኮሪደር ልማት ይበል የሚያሰኝ ነው ያሉት ባለሙያው ልክ እንደ አዲስ አበባ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አመላክተዋል፡፡

የተመኙሽ አያሌው

Address

Shegole, Addisu Gebeya
Addis Ababa
1000

Telephone

+2515172516

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when FM Addis 97.1 /ኤፍ ኤም አዲስ 97.1 ሬዲዮ/ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to FM Addis 97.1 /ኤፍ ኤም አዲስ 97.1 ሬዲዮ/:

Share

Our Story

FM Addis 97.1 is the First FM radio station in Ethiopia . On air since 2000. You can listen our station for 24 hours throughout the country and outside Ethiopia.

በ1992 ዓ.ም የተመሰረተውና በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ኤፍ ኤም አዲስ 97.1 ሬዲዮ በተለያዩ የማሰራጫ አማራጮች በመላ ሀገሪቱና በባህርማዶ ለሚገኙ አድማጮቹ ለ24 ሰአታት የተለያዩ ዝግጅቶች ይቀርቡበታል፡፡ የፌስ ቡክ ትስስራችን ቤተሰብ በመሆንዎም እናመሰግናለን፡፡