FM Addis 97.1 /ኤፍ ኤም አዲስ 97.1 ሬዲዮ/

FM Addis 97.1 /ኤፍ ኤም አዲስ 97.1 ሬዲዮ/ Ethiopian Broadcasting Corporation is a 24 hour working public media.
(288)

Ethiopian Broadcasting Corporation is a national media which disseminates its news and programs world wide via Television,Radio and Website.

ታላቁ የህዳሴ ግድብ ቀጠናዊ ትስስርን  ይፈጥራል ---ደይሊ ሳባህ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የኢትዮጵያን ሀገራዊ ልማት ከማፋጠኑም ባሻገር ቀጠናውን  ይበልጥ ያስተሳስራል ሲል ደይሊ ሳባህ...
15/09/2025

ታላቁ የህዳሴ ግድብ ቀጠናዊ ትስስርን ይፈጥራል ---ደይሊ ሳባህ

ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የኢትዮጵያን ሀገራዊ ልማት ከማፋጠኑም ባሻገር ቀጠናውን ይበልጥ ያስተሳስራል ሲል ደይሊ ሳባህ ጽፏል፡

" ግድቡ የተራቀቀ የምህንድስና ውጤት ብቻ ሳይሆን ብሄራዊ ምልክት ነው ፤ ከፍ ሲልም ምስራቅ አፍሪካን አንድ የማድረግ እምቅ አቅም ያለው የባንዲራ ፕሮጀክት ፡፡ "

ቀጠናዊ ውህደትን በማቀጣጠል በአባይ ተፋሰስ ሀገራት ዘንድ የትብብርና የመተማመን በርን ይከፍታልም ነው ያለው ጋዜጣው፡፡

ኢትዮጵያዊያን የማንንም እርዳታ ሳይጠይቁ በራስ አቅም የገነቡት ታላቁ የህዳሴ ግድብ መላው አፈሪካን ይበልጥ አንድ ያደርጋልም ብሏል ፤ደይሊ ሳባህ፡፡

ግድቡ የኢትዮጵያዊያንን በተፈጥሮ ሀብታቸው የመጠቀም የዘመናት ጥያቄ የመለሰ ግዙፍ ፕሮጀክት ነው ያለው ደይሊ ሳባህ ፤ኢትዮጵያዊያን አንድ ሲሆኑ የሚሳናቸው ምንም ነገር እንደሌለም አስነብቧል።

"ደይሊ ሳባህ" በሀገረ -ቱርክየ በእንግሊዘኛ ቋንቋ እየታተመ የሚሰራጭ ዕለታዊ ጋዜጣ ነው።

አህመድ መሀመድ

የኢትዮጵያን ትርክት ከሕዳሴ ግድብ በፊትና በኋላ ብለን መክፈል የምንችልበት ደረጃ ላይ ነን ፡- ዲያቆን ዳንኤል ክብረትየኢትዮጵያ ስንክሳር ከሁለቱ ውሀዎች  ከአባይ ወንዝና ቀይ ባህር ጋር የ...
15/09/2025

የኢትዮጵያን ትርክት ከሕዳሴ ግድብ በፊትና በኋላ ብለን መክፈል የምንችልበት ደረጃ ላይ ነን ፡-

ዲያቆን ዳንኤል ክብረት

የኢትዮጵያ ስንክሳር ከሁለቱ ውሀዎች ከአባይ ወንዝና ቀይ ባህር ጋር የሚያያዙ እንደሆኑ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የማህበራዊ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር ሙአዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ገልጸዋል ፡፡

ከ17ኛው ክፍለዘመን የቅኝ ገዢዎች አፍሪካን የመቀራመት ተግባር ጀምሮ የኢትዮጵያ መንግስታት አባይን ለተለያየ ጥቅም የማዋል የሀገሪቱን ተፈጥሯዊ መብት ለማስጠበቅ ሲታገሉ እንደነበር ተናግረዋል ፡፡

የጠቅላይ ሚኒስትሩ የማህበራዊ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር ሙአዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ከኢቢሲ ኤፍ ኤም ኢዲስ 97.1 ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደገለጹት ኢትዮጵያ በአባይ ወንዝ ተጠቃሚ እንድትሆን መንግስታት ብቻ ሳይሆኑ ህዝቡ እና ልሒቃንም ሲሞግቱ ኖረዋል ፡፡

ኢትዮጵያን ከአባይ ውጭ ለማድረግ ቅኝ ገዢዎች ብዙ ለፍተዋል ያሉት ሚኒስትሩ የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ መጠናቀቅ ኢትዮጵያውያን በአባይ ወንዝ የመጠቀም መብታቸውን መልሰው ያገኙበት ታሪካዊ ድል ነው ብለዋል ፡፡

ዲያቆን ዳንኤል የኢትዮጵያ ትርክት አሁን ከሕዳሴ ግድብ በፊት እና በኋላ ተብሎ መከፈል የሚችልበት ደረጃ ላይ ይገኛል ብለዋል ፡፡ ከግድቡ በፊት እኛም አንችልም ብለን ሌሎችም አትችሉም ብለውን ፤ የዓለም የገንዘብ ተቋማት ካልደገፉን መስራት አንችልም በሚል ትርክት ታስረን ነበር ሲሉ ያስረዳሉ ፡፡

ከሕዳሴ ግድብ መጠናቀቅ በኋላ ግን እኛም እንችላለን ብለን እነሱም ትችላላችሁ ያሉበት ፤ በራሳችን አቅም የምንፈልገውን ፖሊሲ መፈጸም እንዲሁም በራሳችን ጉዳይ ራሳችን መወሰን እንደምንችል እና ለዚህም የማንንም ፈቃድ መጠየቅ እይገባንም የሚል ትርክት የገነባንበት ነው ብለዋል ፡፡

ዲያቆን ዳንኤል እንደሚሉት ኢትዮጵያ በተፈጥሮ ሀብቷ እንዳትጠቀም ለማድረግ የሚሰነዘሩ ጫናዎች የጥቁር ሕዝብ አካል በመሆኗም ጭምር የመጡ ናቸው ፡፡ ጥቁሮች ለመልማት የሌላ አካል ፈቃድ እና እርዳታ ያስፈልጋቸዋል የሚል ትርክት ሰፍኖ እንደነበር አስታውሰዋል ፡፡

ይህን በጥቁር ሕዝቦች ላይ የተሰነዘረ የአይችሉም ትርክት ለመቀየር ኢትዮጵያ እንደ አድዋ ባሉ ተምሳሌታዊ ድሎች ስትቀለብስ መኖሯን ሚኒስትሩ አውስተዋል ፡፡

አሁን በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ መጠናቀቅ እንደ ፓንአፍሪካኒስት ሀገር የኢትዮጵያን ብቻ ሳይሆን የጥቁር ሕዝቦችን የመቻል አቅም ያሳየ እና አዲስ ትርክት የፈጠረ መሆኑን ሙአዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ተናግረዋል ፡፡

በቤተልሔም ገረመው

የሕዳሴ ግድብ ግንባታ በስኬት መጠናቀቁን አስመልክቶ የጋሞ  እና የጎፋ ዞን ነዋሪዎች ደስታቸውን ገለጹ*************የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ በስኬት  መጠናቀቁን አስመልክ...
15/09/2025

የሕዳሴ ግድብ ግንባታ በስኬት መጠናቀቁን አስመልክቶ የጋሞ እና የጎፋ ዞን ነዋሪዎች ደስታቸውን ገለጹ
*************

የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ በስኬት መጠናቀቁን አስመልክቶ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የጋሞ እና የጎፋ ዞን ነዋሪዎች የተሰማቸውን ደስታ በአደባባይ ገልፀዋል፡፡

በዞኖቹ ባሉ ሁሉም መዋቅሮች 'በህብረት ችለናል!' በሚል መሪ ሀሳብ የሕዳሴ ግድብ በድል በመጠናቀቁ ህዝባዊ ድጋፍ ሰልፍ ተካሂዷል።

ነዋሪዎች የግድቡ ግንባታ የሁሉም ኢትዮጵያዊ የልፋት ውጤት መሆኑን በመጥቀስ ገልጸዋል፡፡

‎በህዝባዊ ድጋፍ ሰልፉ ከተስተጋቡ መፈክሮች መካከል፤ ግድባችን የዓባይ ዘመን ትውልድ የተጋድሎ ሰንደቅ ፣ በራስ አቅም በአፍሪካዊነት ኩራት የተገነባ ሐውልት፣ ግድባችን ለተፋሰሱ ሀገራት በረከት እንጂ ጉዳት አይደለም፣ ግድባችን የመቻል ማሳያ የማንሰራራት ጅማሮ ምልክት፣ የውጭ ተፅዕኖ ያልበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነት ላይ የቆመ ግድብ የሚሉት ይገኙበታል።

የምስጋና እና የደስታ አገላለጽ መርሐ ግብር በክልሉ ባሉ 12 ዞኖች ቀጥሎ የሚካሄድ ሲሆን፣ ክልላዊ የድጋፍ ሰልፍ መስከረም 8 ቀን 2017 ዓ.ም ይካሄዳል።

በተመስገን ተስፋዬ

#ሕዳሴ #ደቡብኢትዮጵያ

15/09/2025

አዲስ መረጃ ... መስከረም 05/2018 ዓ.ም

ትምህርት ከተጀመረ በኋላ የሚባክን ጊዜ አይኖርም - ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ************************ከትምህርት ሥርዓቱ ሪፎርም ጋር ተያይዞ ትምህርት ከተጀመረ በኋላ የሚባክን ጊዜ ...
15/09/2025

ትምህርት ከተጀመረ በኋላ የሚባክን ጊዜ አይኖርም - ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ
************************

ከትምህርት ሥርዓቱ ሪፎርም ጋር ተያይዞ ትምህርት ከተጀመረ በኋላ የሚባክን ጊዜ እንደማይኖር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ገለጹ።

ሚኒስትሩ አክለውም ተማሪዎችም ሆኑ መምህራን የጊዜ አጠቃቀማቸውን ማስተካከል እንዳለባቸው ገልጸዋል።

የትምህርት ሥርዓቱ ሪፎርም አንዱ የትኩረት አቅጣጫ የጊዜ አጠቃቀም መሆኑንም ነው ሚኒስትሩ ያነሱት።

ቀደም ሲል ወጥ ያልነበረው የትምህርት ማስጀመሪያና ማጠናቀቂያ ጊዜን መስተካከሉንም ጠቅሰው፤ ተማሪዎች መማር ያለባቸውን የትምህርት ሰዓት በአግባቡ ሊማሩ እንደሚገባ ተናግረዋል።

ይህን ለማድረግም ተማሪዎች ትምህርት ቤት ከተከፈተ ጀምሮ በትምህርት ገበታቸው ላይ ተገኝተው ትምህርት በመከታተል ዕውቀት መቅሰም እንዳለባቸው ነው የገለጹት።

እንደ ሚኒስትሩ ገለጻ፤ ከ12ኛ ክፍል የማትሪክ ውጤት መዘግየት ጋር ተያይዞ ዩኒቨርሲቲዎች ዛሬ ትምህርት አልጀመሩም።

ይሁንና ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ ሁሉም የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች የመማር ማስተማር ሥራቸውን ይጀምራሉ ብለዋል።

በ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና
15/09/2025

በ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና

በ17 የኢትዮጵያ ቋንቋዎች የተዜመው የሕዳሴ ግድብ ኅብረ ዜማ - “ዋሴ፣ ዋሴ” **************** “ዋሴ፣ ዋሴ” በርካታ አርቲስቶች የተሳተፉበት እና በ17 የኢትዮጵያ ቋንቋዎች ለታላቁ...
15/09/2025

በ17 የኢትዮጵያ ቋንቋዎች የተዜመው የሕዳሴ ግድብ ኅብረ ዜማ - “ዋሴ፣ ዋሴ”
****************

“ዋሴ፣ ዋሴ” በርካታ አርቲስቶች የተሳተፉበት እና በ17 የኢትዮጵያ ቋንቋዎች ለታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የተዜመ ኅብረ ዜማ ነው።

“ዜማው ሕዳሴ ግድብ መላ ኢትዮጵያውያንን በአንድነት ያስተሳሰረ ሰንደቅ ዓለማ ፕሮጀክት መሆኑን በሚያንፀባርቅ መልኩ የተሠራ በመሆኑ ተወዳጅ ሊሆን ችሏል” ይላል የዜማው ደራሲ አርቲስት ወንድዬ አበበ።

“ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በአንድነት ያስተሳሰረን ዋስትናችን ነው፤ እኔም ይህንኑ ለማመላከት ኅብረ ዜማውን ሠርላችሁ ሲል ለኢቢሲ ዶትስትሪም ተናግሯል።

ከዚህ ቀደም የመከላከያ ሠራዊት አባል የነበረው አርቲስቱ፣ “በእኔ እና በተወለድከበት አፈር መካከል የሀገር ፍቅር ያበራልኝ መከላከያ ነው” ይላል።

“ሀገርህን ስትወድ ትልልቅ ነገሮችን ታስባለህ፤ መልካም እና በጎ ሐሳብ ከውስጥህ ይመነጫል፤ ፍቅር ትልልቅ ቁም ነገሮችን እንዳስብ እና እንድንቀሳቀስ አድርጎኛል” ሲልም አክሏል።

በዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ዘንድ ብዙ ጊዜ ለኢትዮጵያዊነት የሚሰጠው ስም የድህነት፣ ስደት እና ረሃብ ነው የሚለው አርቲስት ወንድዬ፣ በመሰባሰባችን ውስጥ በዓባይ ውኃ ላይ በራሳችን አቅም ሕዳሴን መገንባት እና እውን ማድረግ ችለናል፤ ማቻልንን በሕደሴ ያረጋገጥንበት ነው ብሏል።

‘ዋሴ ዋሴ’ የኅብር ዜማ በጥበብ የተሠራውም ዓባይ ዋሳችን፣ ጠበቃችን፣ ምልክታችን ነው የሚለው እሳቤን መሠረት አድርጎ እንደሆነ ጠቅሷል።

“ዓባይ ዘረ-ብዙ ነው፤ ሁሉም ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ባላቸው አቅም በጉልበት፣ በገንዘብ ደግፈዋል፤ በእውቀት ያለ ልዩነት ከሕዳሴ ጎን ቆመው በመከራከር የደርሻቸውን ተወጥተዋል፤ እኔም ጥበብን ተጠቅሜ የበኩሌን አድርጌያለሁ፤ በዚህም ደስ ይለኛል” ብሏል።

“እኛ እናልፋለን፣ ሀገር ትኖራለች፤ ሀገር ስትሠራ በቅብብሎሽ ነው። የሆነ አካል ብቻውን ሀገር ሠርቶ አይጨርስም” የሚለው አርቲስት ወንድዬ፣ የኢትዮጵያ መሪዎች የሕዳሴ ግድብን በሐሳብ ከመጠንሰስ እስከ መፈፀም በቅብብሎሽ እዚህ ማድረሳቸው እንደሚያኮራው ነግሮናል።

‘ዋሴ ዋሴ’ ኅብረ ዜማ የዓባይ ውኃ ሙሌት ጀምሮ እስከ ፍፃሜው ባለው ሂደት በፍቅር እየተደመጠ ብዙዎች ጋር መድረስ የቻለ፤ ሕዝቡ ጋር ሳላወራ ለመግባባት ያደረሰኝ፤ ሕዝቡ ሳይነግረኝ ፍላጎቱን መረዳት የቻልኩበት፤ የላቀ ፍቅር እና ደስታ ያገኘሁበት ዜማ ነው ይላል።

የሕዳሴን ከፍታ በ‘ዋሴ ዋሴ’ ኅብረ ዜማ ለመግለጽ የተሞከረበት መንገድ የጥበብ ኃይል አለው።

እግዚአብሔር ሳምሶንን “በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ‘ኃይልህ ያለው በፀጉርህ ላይ ነው፤ ፀጉርህን ጠብቅ’ ብሎታል” የሚለው ወንድዬ፣ የእኛም ትልቁ ኃይላችን ያለው ኅብረታችን እና አንድነታችን ላይ ነው ሲል ይገልጻል።

‘ዋሴ ዋሴ’ የኅብር ዜማ ይህንን ኅብረት እና አንድነት በመጠበቅ የተሠራ በመሆኑ ነው በፍቅር እየተደመጠ ያለው ብሏል።

ዕድር፣ ዕቁብ፣ ጽዋ፣ ቅርጫ፣ ቡና ጠጡ የሚል ማንነት ባለው ማኅበረሰብ ውስጥ በማደጉ ኅብረ ገብነትን እንዲላበስ እንዳስቻለው ይናገራል።

“እነዚህ የኢትዮጵያዊነት እሴቶች መገለጫዎች እኔን የቀረጹኝ ይመስለኛል” ሲልም ምስክርነቱን ሰጥቷል።

የጋራ የሆነችው ሀገርን ማስቀደም እና ከነጠላ ማንነት ወደ ብዘኃ ማንነት መግባት በሚጠይቀው ወታደር ቤት ማሳለፉም በእርሱ ማንነት ላይ ትልቅ አሻራ ማሳረፉንም ነው የሚገልጸው።

ሕዳሴ እንደ አየር መንገዳችን እና እንደ መከላከያ ሠራዊታችን ሁሉ ሁሉንም ኢትዮጵያዊ አንድ ያደረገ የጋራ መገለጫችን ነው ሲል ይናገራል።

ፍፁም አንድነት እና ኅብረት ካለ፣ ምንም ማድረግ እንደሚቻል የሕዳሴው ግድብ ማሳያ መሆኑን ጠቁሞ፣ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ተገንቶ ለዚህ ፍፃሜ በመድረሱ ደስታዬ እጥፍ ድርብ ነው ብሏል አርቲስት ወንድዬ አበበ።

በመሐመድ ፊጣሞ

ኢትዮጵያ ዓመተ ምሕረት ሳይሆን ታሪክ ነው የቀየረችው ፦ ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ኢትዮጵያ የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታን በማጠናቀቅ የአይቻልም መንፈስን በመስበሯ 2017ን በ2018...
15/09/2025

ኢትዮጵያ ዓመተ ምሕረት ሳይሆን ታሪክ ነው የቀየረችው ፦ ዲያቆን ዳንኤል ክብረት

ኢትዮጵያ የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታን በማጠናቀቅ የአይቻልም መንፈስን በመስበሯ 2017ን በ2018 ሳይሆን ታሪክ ነው የቀየረችው ሲሉ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የማህበራዊ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር ሙአዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ከኢቢሲ ኤፍ ኤም አዲስ 97.1 ጋር በነበራቸው ቆይታ ተናግረዋል ።

2018 የኢትዮጵያ ማንሰራራት መሰረት የሚይዝበት ፤ ብልፅግናዋ ይበልጥ የሚታይበት መሆኑን ተናግረዋል ። የዚህ መነሻው የሺህ ዘመናት የኢትዮጵያውያን መሻት ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ መጠናቀቁ እንደሆነ አስረድተዋል ።

በዚህ አመት 7ቱ የጉባ ላይ ብስራቶች የተባሉት ግዙፍ ሀገራዊ ፕሮጀክቶች መካከል የተወሰኑት የሚመረቁበት ፤ የተቀሩት የሚጀመሩበት መሆኑን ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ጠቁመዋል ።

በቤተልሔም ገረመው

15/09/2025

የሀገር ውስጥ እና የውጭ ስፖርታዊ ጉዳዮች

15/09/2025

የኢትዮጵያ ጊዜ ... 05/01/2018 ዓ.ም

የ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤት መመልከቻ ገፅ ይፋ ሆኗል********************የ2017 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ውጤትን ተፈታኞች የሚያገኙበት አድራሻዎችም  ይፋ ተ...
15/09/2025

የ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤት መመልከቻ ገፅ ይፋ ሆኗል
********************

የ2017 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ውጤትን ተፈታኞች የሚያገኙበት አድራሻዎችም ይፋ ተደርጓል፡፡

ዌብ ሳይትና ቴሌግራም አድራሻ የሚጠቀሙ ተፈታኞች ጊዜያዊ ሰርቲፊኬታቸውን ወዲያውኑ አውርደው (download አድርገው) መውሰድና መጠቀም ይችላሉ፡፡
ተብሏል::

ውጤት ለመመልከት አድራሻዎች:-

1. በዌብ ሳይት፡ https://result.eaes.et
2. በቴሌገራም፡ https://t.me/EAESbot
3. በአጭር የጽሑፍ መልዕክት (SMS)፡ 6284 ላይ ተማሪዎች ውጤታቸውን ማየት እንደሚችሉ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ይፋ አድርጓል::

የለሜቻ ግርማ የፓሪስ ኦሎምፒክ አስደንጋጭ ክስተት እና ዛሬ የሚጠበቀው ፍጻሜ*********** ይሄ ብዙዎችን ያስደነገጠ ክስተት ከተፈጠረ አንድ ዓመት ሆኖታል፡፡ ጊዜው እና ቦታው ደግሞ 202...
15/09/2025

የለሜቻ ግርማ የፓሪስ ኦሎምፒክ አስደንጋጭ ክስተት እና ዛሬ የሚጠበቀው ፍጻሜ
***********

ይሄ ብዙዎችን ያስደነገጠ ክስተት ከተፈጠረ አንድ ዓመት ሆኖታል፡፡ ጊዜው እና ቦታው ደግሞ 2024 ፓሪስ ኦሎምፒክ ነው፡፡ ኢትዮጵያ የወርቅ ሜዳልያ ከምትጠብቅባቸው ርቀቶች አንደኛው በነበረው የወንዶች 3ሺ ሜትር መሰናክል ሀገራቸውን የወከሉት አትሌት ለሜቻ ግርማ፣ ጌትነት ዋለ እና ሳሙኤል ፍሬው ማጣሪያውን በማለፍ ለፍጻሜ ደርሰዋል፡፡

አትሌት ለሜቻ ግርማ ከ2019 የዶሃ ዓለም ሻምፒዮና ጀምሮ ኢትዮጵያ ብዙም በማትታወቅበት 3ሺ ሜትር መሰናክል ልዩነት ፈጣሪ መሆኑን ለዓለም አሳይቷል፡፡ አሁን ላይ የርቀቱ የዓለም ክብረ ወሰን ባለቤት ጭምር ነው፡፡

ለሜቻ የዛሬ ዓመት በተደረገው የፓሪስ ኦሎምፒክ ከነበረው ዝግጅት እና ካለው ወቅታዊ ብቃት አንጻር የአሸናፊነት ቅድሚያ ግምቱን አግኝቷል፡፡ የፍጻሜው ውድድር ተጀመረ ለሜቻ ግርማ ከሀገሩ ልጆች ጋር በመናበብ በርቀቱ ለኢትዮጵያ መጀመርያ የሆነውን የወርቅ ሜዳልያ ለመውሰድ በጥንቃቄ መሮጡን እና መሰናክሉን መዝለል ቀጥሏል፡፡

ነገር ግን ውድድሩ ሊጠናቀቅ 300 ሜትር ሲቀረ ትልቅ ግምት ያገኝው አትሌት ፍጥነቱን በሚጨምርበት ሰዓት በመሰናክሉ ተደናቅፎ ወደቀ፡፡ በገጠመው የጭንቅላት ጉዳትም በፍጥነት ወደ ሆስፒታል ተወሰደ፡፡ በወቅቱ አሜሪካዊው ኮሜንታተር ሌይ ዲፊ የጉዳቱን ክብደት ሲገልጽ በ40 ዓመታት የአትሌቲክስ ኮሜንታሪነት ስራዬ እንዲህ አይነት ክስተት አልተመለከትኩም ብሎ ነበር፡፡ብዙዎች ቁመተ መለሎው ለሜቻ በፍጥነት እንዲያገግም እና ወደ ቀደመ ጥንካሬው እንዲመለስ ምኞታቸውን ገልጸዋል፡፡ አስደንጋጭ የነበረው ሁነት መፈጠሩን ተከትሎ ኢትዮጵያም የርቀቱን ወርቅ ለማግኝት ሌላ ጊዜን እንድትጠብቅ ግድ ሆነ፡፡

የ24 ዓመቱ አትሌት ከዚያ ክስተት ተመልሶ ሀገሩን በትልቅ መድረክ የሚወክልበት ሌላ ዕድል አግኝቷል፡፡ የ3 ጊዜ የዓለም አትሌቲከስ ሻምፒዮና የብር ሜዳልያ ባለቤቱ እና የአንድ ኦሎምፒክ የብር ሜዳልያ ባለ ክብሩ ለሜቻ ግርማ ዛሬ በሚደረገው የ3ሺ ሜትር መሰናከል ፍጻሜ ኢትዮጵያን ከሚወክሉት አንዱ ነው፡፡

ማጣሪያውን 2ኛ ሆኖ ያለፈው የዓለም ከብረ ወሰን ባለቤቱ ለሜቻ ግርማ ቀን 9 ሰዓት ከ55 ላይ ለሌላ ክብር ይፋለማል፡፡ 16 አትሌቶች በፍጻሜው በሚሳተፉበት 3ሺ ሜትር መሰናከል በፓሪስ አብረውት የነበሩት አትሌት ጌትነት ዋለ እና ሳሙኤል ፍሬውም ይጠበቃሉ፡፡

ለሜቻ ግርማ በቡዳፔስት እና በኢውጂን ዓለም ሻምፒዮና እንዲሁም በቶኪዮ ኦሎምፒክ የብር ሜዳልያውን ሲወስድ በሦስቱም አጋጣሚዎች የቀመደው ሞሮኮአዊው አትሌት ሶፊያን ኤል ባካሊ ዛሬም ትልቅ ፈተና እንደሚሆን ይጠበቃል፡፡

በአንተነህ ሲሳይ

Address

Shegole, Addisu Gebeya
Addis Ababa
1000

Telephone

+2515172516

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when FM Addis 97.1 /ኤፍ ኤም አዲስ 97.1 ሬዲዮ/ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to FM Addis 97.1 /ኤፍ ኤም አዲስ 97.1 ሬዲዮ/:

Share

Our Story

FM Addis 97.1 is the First FM radio station in Ethiopia . On air since 2000. You can listen our station for 24 hours throughout the country and outside Ethiopia.

በ1992 ዓ.ም የተመሰረተውና በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ኤፍ ኤም አዲስ 97.1 ሬዲዮ በተለያዩ የማሰራጫ አማራጮች በመላ ሀገሪቱና በባህርማዶ ለሚገኙ አድማጮቹ ለ24 ሰአታት የተለያዩ ዝግጅቶች ይቀርቡበታል፡፡ የፌስ ቡክ ትስስራችን ቤተሰብ በመሆንዎም እናመሰግናለን፡፡