FM Addis 97.1 /ኤፍ ኤም አዲስ 97.1 ሬዲዮ/

FM Addis 97.1 /ኤፍ ኤም አዲስ 97.1 ሬዲዮ/ Ethiopian Broadcasting Corporation is a 24 hour working public media.
(292)

Ethiopian Broadcasting Corporation is a national media which disseminates its news and programs world wide via Television,Radio and Website.

13/10/2025

አዲስ መረጃ … ጥቅምት 03/2018 ዓ.ም
#ኤፍኤምአዲስ97.1 .1

የአንድነት ምልክትሃይሌ ለምን እምባ አወጣሰንደቁ ስትወጣደራርቱ ለምን አለቀሰችሰንደቅ ዓላማዋን እያየችጥልቅ ነው የሲቃቸው ቅኔወየው ቋጠሮ ላልገባኝ እኔእነሱ በዕግራቸው ሮጠው በፈሰሰው ላባቸው...
12/10/2025

የአንድነት ምልክት

ሃይሌ ለምን እምባ አወጣ
ሰንደቁ ስትወጣ

ደራርቱ ለምን አለቀሰች
ሰንደቅ ዓላማዋን እያየች

ጥልቅ ነው የሲቃቸው ቅኔ
ወየው ቋጠሮ ላልገባኝ እኔ

እነሱ በዕግራቸው ሮጠው በፈሰሰው ላባቸው
በአንድነት የሚሰበሰብ ድፍን አገር አላቸው

ተዳክማ የኖራቸ አገር የደበዘዘች ባንዲራ
ካዘመመችበት ተነስታ ስትቆም ስታንሰራራ
ከናቋት ሃያላን በላይ ከፍ ብላ ስታበራ
ኢትዮጵያ የሚለው ስሟ በከብር ደምቆ ሲጠራ

እሱ ነው ያስለቀሳቸው አንጀታቸውን አላውሶ
አገር ባንድ ላይ ሲቆም የልዩነትን ግንብ አፍርሶ!

ሰንደቅ ዓላማችን ለኢትዮጵያ ማንሠራራት፤ የአዲስ ዘመን ድል ብስራት!
12/10/2025

ሰንደቅ ዓላማችን ለኢትዮጵያ ማንሠራራት፤ የአዲስ ዘመን ድል ብስራት!

12/10/2025
"ገጠር ግባ" ገጠርን ያስናፈቀው አንጋጋሪ ሙዚቃ ሙሉ የመዝገብ ስሙ እዮኤል ዮሴፍ ማርዮሲሆን  ለመድረክ መጠሪያ እንዲሆነው "ዮ ማርዮስ" የሚለውን መርጧል::ትውልድ እና እድገቱ በባህር ዳር ...
12/10/2025

"ገጠር ግባ" ገጠርን ያስናፈቀው አንጋጋሪ ሙዚቃ

ሙሉ የመዝገብ ስሙ እዮኤል ዮሴፍ ማርዮ
ሲሆን ለመድረክ መጠሪያ እንዲሆነው "ዮ ማርዮስ" የሚለውን መርጧል::

ትውልድ እና እድገቱ በባህር ዳር ከተማ እንደሆነ የሚናገረው ሙዚቀኛው ከሰሞኑ በበርካቶች የተወደደለት "ገጠር ግባ" ሙዚቃው በእውነተኛ ታሪክ ላይ የተመሰረተ እንደሆነ ከኤፍ ኤም አዲስ 97.1 መሰንበቻ ፕሮግራም ጋር በነበረው ቆይታ ገልፇል::

የታሪኩ መነሻ ወላጅ እናቱ መሆናቸውን የሚናገረው ዮ ማርዮስ "እኔ ከተማ ለመኖር ልቤ ሲሸፍት እናቴ ወደገጠር ሄጄ እያረስኩ እና እያለብኩ እንድኖር የነገረችኝን ሃሳብ ሙዚቃ አደረኩት"ሲል ይናገራል::

በአጋጣሚ ወደ ሙዚቃ ያደገው "ገጠር ግባ" ዜማን ወላጅ እናቱም እንደወደዱት እና ምክራቸውን በዚህ ልክ ፈጠራ ጨምረው የሰሩበት መንገድ እንዳስደነቃቸው ተናግሯል::

ሙዚቃው ከወጣ በኃላ ከህዝብ ያገኛቸው አስተያየቶች ያልጠበቀው መሆኑን የሚገልፀው ዮ ማርዮስ በቀጣይም መሰል ፈጠራ ያላቸው የሂ ፖፕ ሙዚቃዎች እንደሚኖሩትም ገልጿል::

"ገጠር ግባ" ሙዚቃ በስቱዲዮ ከተሰራው ከፍ ባለ መንገድ ስመጥር ባለሞያ የተሳተፈበት የቪዲዮ ምስል(ክሊፕ) እየተሰራለት እንደሚገኝ ኤፍኤም አዲስ 97.1 መሰንበቻ ፕሮግራም ከፕሮዲዮሰሩ ብሊክ ሰምቷል::

ሙሉ ቆይታውን በተከታዩ ሊንክ ይከታተሉ::

https://youtu.be/9wLkGJHG_ZU?si=9N1FndvnPgOjKOGo

"ማዕበሉ እና ወጀቡ ሲበረታብን እንኳን ሰንደቃችንን ስናይ እንበረታለን"ፒቲ ኦፊሰር  ሳሙኤል አረጋየኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ ከሚውለበለብባቸው ቦታዎች አንዱ የኢትዮጵያ መርከቦች ተጠቃሾች ናቸው...
12/10/2025

"ማዕበሉ እና ወጀቡ ሲበረታብን እንኳን ሰንደቃችንን ስናይ እንበረታለን"

ፒቲ ኦፊሰር ሳሙኤል አረጋ

የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ ከሚውለበለብባቸው ቦታዎች አንዱ የኢትዮጵያ መርከቦች ተጠቃሾች ናቸው።

የሀገር ገቢ እና ወጪ ንግድ ስርአትን ጨምሮ ታላላቅ ተልዕኮዎች አንግበው ከሚሰማሩት የኢትዮጵያ መርከቦች ፊት ሁሌም የኢትዮጵያ ሰንደቅዓላማ ይውለበለባል::

መርከበኛ እና ሰንደቅ ዓላማ የአንድ ሳንቲም ሁለት ገፅታ ናቸው የሚሉት መርከበኛ ፒቲ ኦፊሰር ሳሙኤል አረጋ ሰንደቅ አላማ ለመርከበኛ መፅናኛ እና ብርታቱ እንደሆነ ይገልፃሉ::

"በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ በሚያልፍ የባህር ጉዞ ውስጥ ወጀብ እና ማዕበሉ ሲበረታብን እንኳን ሰንደቅ አላማችንን ስናይ እንበረታለን። ሰንደቃችን የተዳከመ ስሜታችንን ወደአሸናፊነት የምትቀይር ናት" ሲሉ ይናገራሉ::

የዓለም ሀገራትን ማቆራረጥን በሚጠይቀው የባህር ጉዞ ውስጥ ሁሌም ማለዳ እና ምሽት የኢትዮጵያን ሰንደቅ አላማ የማውጣት ስነ ስርዓት ይከወናል የሚሉት ፒቲ ኦፊሰር ሳሙኤል አረጋ ይህም በተለየ ትዕይንት የታጀበ መሆኑን ይገልፃሉ::

"ሁሌም ጠዋት 2:00 ጉዟችን የሚጀምረው ሰንደቅ አላማን ሰቅለን የኢትዮጵያ ብሔራዊ መዝሙርን ዘምረን ነውሁሉም በመርከብ ውስጥ ያሉ ባልደረቦችም በክብር ዘብ ታጅበው ይህን ያደርጋሉ በተመሳሳይ ጀንበር ስትጠልቅም ሰንደቃችንን ዘምረን እናወርዳለን" የሚሉት ፒቲ ኦፊሰርን የሀገር ሰንደቅ ሲሰቀል በመርከበኞቹ አባላት የሚኖረው መረበሽ እና ልብ መራድ ለቀጣይ ተልዕኮ የሚያዘጋጅ እንደሆነ ገልፀዋል::

ከኤፍ ኤም አዲስ 97.1 እሁድ አራዳ ዝግጅት ጋር ቆይታ ያደረጉት ፒቲ ኦፊሰር ሳሙኤል አረጋ ኢትዮጵያውያን ባስተሳሰረን ሰንደቅ አላማችን ፊት ሆነን በተሰማራንበት መስክ ሀገራችንን እንደሰንደቋ ከፍ እናድርግ ሲሉ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል::

ሙሉ ቆይታውን በተከታይ ሊንክ ይከታተሉ::

https://youtu.be/5nkrfEVimCM?si=N2RMgq0ZYWQpSTYh

ቅዱስ ጊዮርጊስ ሻምፒዮን ሆነ************ቅዱስ ጊዮርጊስ መቻልን 2 ለ 1 በማሸነፍ የአዲስ አበባ ከተማ ህዳሴ ዋንጫ አሸናፊ ሆኗል፡፡በአዲስ አበባ ስቴዲየም በተደረገው ፍጻሜ አሸናፊ ጌ...
12/10/2025

ቅዱስ ጊዮርጊስ ሻምፒዮን ሆነ
************

ቅዱስ ጊዮርጊስ መቻልን 2 ለ 1 በማሸነፍ የአዲስ አበባ ከተማ ህዳሴ ዋንጫ አሸናፊ ሆኗል፡፡

በአዲስ አበባ ስቴዲየም በተደረገው ፍጻሜ አሸናፊ ጌታቸው እና አዲሱ አቱላ የፈረሰኞቹን ግቦች አስቆጥረዋል፡፡

ቻርለስ ሙሴጌ ደግሞ የመቻልን አንድ ግብ ያስቆጠረ ተጫዋች ሆኗል፡፡

በርካታ ደጋፊዎች በታደሙበት ፍጻሜ ፈረሶቹ የአዲስ አበባ ከተማ ዋንጫን ለ8ኛ ጊዜ ያሸነፉበትም ሆኗል፡፡

ሃዊ ፈይሳ የቺካጎ ማራቶንን አሸነፈች************ለ47ኛ በተደረገው የቺካጎ ማራቶን  አትሌት ሀዊ ፈይሳ አሸናፊ ሆናለች፡፡በዓለም አትሌቲክስ የፕላቲኒየም ደረጃ በተሰጠው ማራቶን አትሌት...
12/10/2025

ሃዊ ፈይሳ የቺካጎ ማራቶንን አሸነፈች
************
ለ47ኛ በተደረገው የቺካጎ ማራቶን አትሌት ሀዊ ፈይሳ አሸናፊ ሆናለች፡፡

በዓለም አትሌቲክስ የፕላቲኒየም ደረጃ በተሰጠው ማራቶን አትሌት ሀዊ ፈይሳ 2 ሰዓት 14 ደቂቃ 56 ሰከንድ ርቀቱን ለማጠናቀቅ የወሰደባት ሰዓት ሆኖ ተመዝግቧል፡፡

ሌላኛዋ ኢትዮጵያዊት አትሌት መገርቱ አለሙ 2ኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች፡፡

2 ሰዓት 17 ደቂቃ 18 ሰከንድ መገርቱ አለሙ ርቀቱን ለማጠናቀቅ የወሰደባት ሰዓት ነው፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ለስልጤ ዞን እና ለሀዲያ ዞን አመራሮች ተልዕኮ ሰጡ******************ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በስልጤ እና በሀዲያ ዞኖች ከወረዳ ጀምሮ ላሉ ...
12/10/2025

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ለስልጤ ዞን እና ለሀዲያ ዞን አመራሮች ተልዕኮ ሰጡ
******************

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በስልጤ እና በሀዲያ ዞኖች ከወረዳ ጀምሮ ላሉ አመራሮች ተልዕኮ ሰጥተዋል።

ተልዕኮው አመራሮቹ በመጪዎቹ ወራት ዞኖቹ ያላቸውን ሀብት በመጠቀም ብሎም የአካባቢዎቹን ተወላጆች በማስተባበር በእያንዳንዱ ዞን 1 ሺህ ሞዴል የገጠር መኖሪያ ቤቶች እንዲገነቡ የሚጠይቅ ነው።

መንግሥት የዜጎችን የመኖሪያ ቤት ችግር ለመቅረፍ 1.5 ሚሊዮን መኖሪያ ቤቶችን ለመገንባት የቀረጸው ፕሮጀክት ከተሞችን ብቻ የሚመለከት እንዳልሆነ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ገልጸዋል።

በመጪው ምርጫ ለወረዳ፣ ለዞን፣ ለክልል እና ለፌደራል ምክር ቤቶች የሚወዳደሩ የስልጤ ዞን እና የሀዲያ ዞን እጩዎች ይህን ካልተገበሩ መመረጥ የለባቸውም ሲሉ ጠቁመዋል።

ተመራጮች ሠርተው ባሳዩት እንጂ እንሠራለን ብለው ቃል በሚገቡት ኃላፊነት ላይ ሊቀመጡ እንደማይገባም ነው ጠቅላይ ሚኒስትሩ ያመላከቱት።

ከትናንት በስቲያ ርክክባቸው የተፈጸመ የሀዲያ ዞን እና የስልጤ ዞን ሞዴል የገጠር መንደሮች ግንባታ 3 ወራት ብቻ መውሰዱን ጠቅሰው፤ እስከ ምርጫው ያለው ጊዜ የእስከአሁኑን እጥፍ ውጤት ለማስመዝገብ በቂ መሆኑን ገልጸዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ተልዕኮውን በሰጡበት መልዕክታቸው ይህ ተግባር ሳይፈጸም አካባቢዎቹን ተመልሰው እንደማይጎበኙም ተናግረዋል።

በአፎሚያ ክበበው

በቻይና በዩንቨርስቲዎች መካከል የሚደረገው የአውሮፕላን ዲዛይን ፈጠራ ውድድር **********************በቻይና በሚገኙ ዩንቨርስቲዎች ውስጥ የሚማሩ የአቬሽን ዘርፍ ተማሪዎች ትምህርታ...
12/10/2025

በቻይና በዩንቨርስቲዎች መካከል የሚደረገው የአውሮፕላን ዲዛይን ፈጠራ ውድድር
**********************

በቻይና በሚገኙ ዩንቨርስቲዎች ውስጥ የሚማሩ የአቬሽን ዘርፍ ተማሪዎች ትምህርታቸውን ካጠናቀቁ በኋላ በተግባር እና በንድፈ ሐሳብ የቀሰሙትን የአቬሽን ዘርፍ እውቀት ወደ ተግባር አውርደው የዘመናዊ አውሮፕላኖች ዲዛይን በሚታይ መንገድ አዘጋጅተው በውድድር ይፎካከራሉ፡፡

በዚህ አመትም ከ150 ዩንቨርስቲዎች የተወጣጡ ከ4000 በላይ ተማሪዎች የራሳቸውን የአውሮፕላን ዲዛይን ይዘው በምስራቅ ቻይና በምትገኘው ሺጂያንግ ግዛት ተገኝተዋል፡፡

ተማሪዎቹ የሚያቀርቡት የአውሮፕላን ዲዛይን ፈጠራ ምን ያሕል የካርቦን ልቀት አለው፣ በሰው ሰራሽ አስተውሎት ፈጠራ ምን ያህል የበቃ ነው እና ከቻይና የአየር ንብረት ፖሊሲ ጋር አንዴት አብሮ ይጓዛል የሚለው ዋንኛ የውድድሩ መስፈርቶች ናቸው፡፡

በውድድሩ ላይ በርካታ የሐገር ውስጥ እና የውጭ ጎብኚዎች የሚገኙ ሲሆን የውድድሩ ዓላማ ተማሪዎቹ አሁን ካለው የአቬሽን ዘርፍ ጋር ምን ያህል እየተጓዙ ነው የሚለውን ለማስተዋወቅ ያለመ መሆኑን ሲጂቲኤን ዘግቧል፡፡

በሰው አልባ አውሮፕላን እና በአየር ላይ የታክሲ አገልግሎት ከዓለም ቀዳሚ አምራች ለመሆን እሰራች ያለችው ቻይና፤ ብቁ እና የሰለጠኑ ወጣቶችን ለመለየት ውድድሩን እየተጠቀመችበት እንደምትገኝም ተነግሯል፡፡

በሀብተሚካኤል ክፍሉ

"ሜዳሊያ ውስጥ ገብቼ  የሀገሬ መዝሙር ሲዘመር ኩራት ይሰማኛል"የብስክሌት ሻምፒዮኗ  ፅጌ ካህሳይ በቅርቡ ሩዋንዳ ኪጋሊ በተደረገው  የዓለም የብስክሌት ሻምፒዮና ላይ በሁለት የውድድር ዓይነቶ...
12/10/2025

"ሜዳሊያ ውስጥ ገብቼ የሀገሬ መዝሙር ሲዘመር ኩራት ይሰማኛል"

የብስክሌት ሻምፒዮኗ ፅጌ ካህሳይ

በቅርቡ ሩዋንዳ ኪጋሊ በተደረገው የዓለም የብስክሌት ሻምፒዮና ላይ በሁለት የውድድር ዓይነቶች ተሳትፋ ከአፍሪካ ቀዳሚ በመሆን ያጠናቀቀችው ፅጌ ካህሳይ ከኤፍ ኤም አዲስ 97.1 መሰንበቻ ዝግጅት ጋር ቆይታ አድርጋለች።

በወጣቶች ዘርፍ ከአለም አንደኛ ሆነሻል ደስታሽ እንዴት ነበር?

👉"በመጀመሪያ አመሰግናለሁ። ውድድሩ አለም ሻምፒዮና ስለሆነ ደስ ይላል በማሸነፌም ደስ ብሎኛል።

በወጣቶች በ18.6 እና በሌላኛው በ74 ኪ.ሜ ተሳታፊ ነበርሽ እና በሀገር ውስጡም አንፃር በውድድሩ ፈታኙ ምን ነበር??

👉"ኪሎ ሜትሩ ተመሳሳይ ነው የተለየው ነገር እነሱ ፕሮፌሽናል ስለሆኑ ነው። እኔ ደግሞ የጠቀመኝ
የ አይዩሲ ስልጠና ወስጄ ስለነበር ነው ።እዛ በአቅርቦት ወይም በማቴሪያልም የተሻሉ ናቸው በአፍሪካ አንፃር ሲታይ የጎደለን ነገር አለ ግን አሪፍ ነበር።"

በዚህ አይነት ባልተመቸ እና በስልጠና ረገድ ልዩነት ባለበት ሁኔታ ይሄን ተቋቁሞ ማሸነፍ ቀላል አይደለም....

👉"አንድ አቋም አለኝ ከሰራሁ እንደማሸንፍ እርግጠኛ ነኝ እና በደንብ ተዘጋጅቼ ነበር ከአይዩሲ ጋር ሶስት ወር ቆይቻለሁ። ምርጥ 10 ውስጥ እንደምገባ እርግጠኛ ነበርኩ የተሻለም ይገባ ነበር ከዛ በላይ ባመጣ ደስ ይለኝ ነበር። ደስታውን አልችለውም ነበር አሁንም በመጣው ደስተኛ ነኝ። በቀጣይ አመት አመጣለሁ ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ።"

ከአፍሪካ ቀዳሚ ከአለም ሰባተኛ ሆነሽ ነው ያጠናቀቅሽው ቀላል የሚባል አይደለም።ለኢትዮጵያውያን ትልቅ ኩራት አለው ለእያንዳንዳችን ትርጉሙ ከፍ ያለ ነው። በቀጣይ ህልምሽ ምንድነው?

👉"ቀጣይ እቅዴ አውሮፓ ክለብ ገብቼ ቱርደንፍራንስ ላይ መገኘት ነው ።የመጀመሪያ አፍሪካዊት መሆንም ህልሜ ነው። ከፈጣሪ እና ከኢትዮጵያ ህዝብ ጋር እንደማደርገው ተስፋ አደርጋለሁ። "

ሀገርን መወከል ሰንደቅን ከፍ ማድረግ ትልቅ ትርጉም አለው እና ይሄን ስሜት ባንቺ ውስጥባውቀው ደስ ይለኛል

👉"በጣም ደስ ይላል የሆነ ስሜት አለው ሰንደቅ ያደረኩበትን ቪዲዮ ሳየው የተለየ ነገር አለው። መግለፅ አልችልም አሸንፌ ወደ ሜዳሊያ ስገባ የሀገር ብሄራዊ መዝሙር ሲዘመር በጣም ኩራት ይሰማኛል። "

ኑራ ኢማም

ሙሉ ቆይታውን በተከታዩ ሊንክ ይከታተሉ::

https://youtu.be/lVczA2odnLk?si=BdxdmHy-224mJTNr

የፕሮግራም ጥቆማ ለሀገር ልጆችከቅኝት ስፖርት አዘጋጆች ቡርኪናፋሶ ከ ኢትዮጵያ ለ2026ቱ የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ የመጨረሻ የምድብ ጨዋታ በ4 ኦውት ዋጋዱጉ ስቴዲየም ቡርኪና ፋሶ ከኢትዮጵያ ጋ...
12/10/2025

የፕሮግራም ጥቆማ ለሀገር ልጆች
ከቅኝት ስፖርት አዘጋጆች
ቡርኪናፋሶ ከ ኢትዮጵያ

ለ2026ቱ የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ የመጨረሻ የምድብ ጨዋታ በ4 ኦውት ዋጋዱጉ ስቴዲየም ቡርኪና ፋሶ ከኢትዮጵያ ጋር ዛሬ እሁድ ምሽት 4:00 ላይ የሚያደርጉትን ጨዋታ ከ3:00 ጀምሮ በኤፍኤም አዲስ 97.1 ላይ በአገር አቀፍ ስርጭት ቅኝት ስፖርቶች በቀጥታ ወደናንተ ያደርሳሉ።

ጨዋታውን ማን ያሸንፋል? ግምትዎን ያስቀምጡ!

ፕሮግራሙን በኤፍኤም አዲስ 97.1 ላይ በሬዲዮ፣ በሳተላይት ቴሌቪዥን(በተንቀሳቃሽ ምስል)፣በዩቲዩብና በፌስቡክ ገጾቻችን በፈለጉት አማራጭ መከታተል ይችላሉ!!

ማን ያሸንፋል?

ፕሮግራሙን ቅኝት ሚዲያና ኮሚኒኬሽን ከኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ጋር በመተባበር በኤፍኤም አዲስ 97.1 ላይ ያቀርቡታል።

ቅኝት ስፖርት

Address

Shegole, Addisu Gebeya
Addis Ababa
1000

Telephone

+2515172516

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when FM Addis 97.1 /ኤፍ ኤም አዲስ 97.1 ሬዲዮ/ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to FM Addis 97.1 /ኤፍ ኤም አዲስ 97.1 ሬዲዮ/:

Share

Our Story

FM Addis 97.1 is the First FM radio station in Ethiopia . On air since 2000. You can listen our station for 24 hours throughout the country and outside Ethiopia.

በ1992 ዓ.ም የተመሰረተውና በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ኤፍ ኤም አዲስ 97.1 ሬዲዮ በተለያዩ የማሰራጫ አማራጮች በመላ ሀገሪቱና በባህርማዶ ለሚገኙ አድማጮቹ ለ24 ሰአታት የተለያዩ ዝግጅቶች ይቀርቡበታል፡፡ የፌስ ቡክ ትስስራችን ቤተሰብ በመሆንዎም እናመሰግናለን፡፡