DireTube

DireTube DireTube.com is the #1 Ethiopian Video Sharing Site. DireTube is an Ethiopian media and entertainment website founded on October 26, 2008.

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለአርሶ አደሮች የግብርና ብድር አገልግሎት አስጀመረ ‎የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለባለአነስተኛ ይዞታና ለተደራጁ አርሶ አደሮች የሚሰጥ የግብርና ብድር አገልግሎት በዛሬው ...
18/12/2025

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለአርሶ አደሮች የግብርና ብድር አገልግሎት አስጀመረ

‎የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለባለአነስተኛ ይዞታና ለተደራጁ አርሶ አደሮች የሚሰጥ የግብርና ብድር አገልግሎት በዛሬው ዕለት አስጀምሯል።

በማስጀመሪያ መርሐ ግብሩ የግብርና ሚኒስትር ዴዔታ መለስ መኮንን (ዶ/ር)፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ አቤ ሳኖ ተወካይ እና የኮርፖሬት አገልግሎቶች ኤክስኪውቲቭ ም/ፕሬዚዳንት አቶ አፍሬም መኩሪያ እና የሌሎች ተቋማት ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።

አቶ ኤፍሬም በወቅቱ እንዳሉት፥ ንግድ ባንክ አዳዲስ አገልግሎቶችን በመተግበር ቀልጣፋና አስተማማኝ አገልግሎት እየሰጠ ነው።

የፋይናንስ አገልግሎት ተደራሽነትና አካታችነትን ይበልጥ ለማሳደግም በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልጸው፤ በተለይም ለግብርና ዘርፍ የሚሰጠውን የብድር አገልግሎት ለማስፋትና ለማጠናከር ትኩረት ተደርጓል ብለዋል።

ባንኩ ለአርሶ አደሮች የግብርና ስራዎችን ለማሳደግ ልዩ የብድር አገልግሎት ማስጀመሩ የገጠር ኢኮኖሚ ዕድገትን ለማሳደግ ያስችላል ነው ያሉት።

በአገልግሎቱ የእርሻ መሬት ያላቸው፣ በኩታገጠም በቡድን የተደራጁ፣ በባንኩ 6 ወርና ከዚያ በላይ የቆጠቡ፣ በሰብል ልማት፣ በአትክልትና ፍራፍሬ፣ በወተትና ወተት ተዋጽኦ እንዲሁም በእንስሳት ሀብት ልማት የተሰማሩ አርሶ አደሮች ተጠቃሚ ይሆናሉ።

የብድር አገልግሎቶቹ የሰብል ምርት፣ የግብርና ማሽነሪና መሳሪያዎች፣ የእንስሳት እርባታ፣ የመጋዘን ደረሰኝ እና የፕሮጀክት ፋይናንስ አቅርቦት የተሰኙ ናቸው።

መለስ መኮንን (ዶ/ር) በበኩላቸው፥ የብድር አገልግሎቱ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት በማረጋገጥ የዘርፉን ምርታማነት ለማሳደግ እንደሚያስችል ተናግረዋል።

(መላኩ ገድፍ - ኤፍ ኤም ሲ)

ኢዜማ የጸጥታ ችግር ባለባቸው አካባቢዎች ምርጫን ለማካሄድ መንግስት ልዩ ትኩረት እንዲሰጥ ጠየቀየኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) በመጪው ሀገራዊ ምርጫ ወቅት የጸጥታ ችግር ባለባቸው...
18/12/2025

ኢዜማ የጸጥታ ችግር ባለባቸው አካባቢዎች ምርጫን ለማካሄድ መንግስት ልዩ ትኩረት እንዲሰጥ ጠየቀ

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) በመጪው ሀገራዊ ምርጫ ወቅት የጸጥታ ችግር ባለባቸው አካባቢዎች ዜጎች የመምረጥ መብታቸውን በነጻነት እንዲጠቀሙ መንግስት ዋስትና ሊሰጥ እንደሚገባ አሳስቧል።

የፓርቲው አመራር እዮብ ብርሀኑ፤ ሰላምና መረጋጋት ለዲሞክራሲያዊ ምርጫ ቀዳሚው ወይንም “አስቻይ ሁኔታ” መሆኑን ተናግረዋል።

ፓርቲው በሀገሪቱ አንዳንድ ክፍሎች የሚታየው አለመረጋጋት በምርጫው ዝግጅትና አፈጻጸም ላይ ጥላ ሊያጠላ እንደሚችል ስጋቱን ገልጿል።

በተለይም ተፈናቃዮች ያሉባቸው እና ግጭቶች ባልበረዱባቸው ስፍራዎች የምርጫ ጣቢያዎችን መክፈትና የዕጩዎች ምዝገባ ማካሄድ ፈታኝ እንደሚሆን ተመልክቷል።

አመራሩ ከዚህ በተጨማሪም መራጮች ያለምንም ስጋት ወደ ምርጫ ጣቢያዎች ወጥተው ድምጻቸውን መስጠት የሚችሉበት አስተማማኝ ሰላም ሊሰፍን ይገባል ብለዋል።

የፖለቲካ ፓርቲ ዕጩዎች የጸጥታ ስጋት ሳይኖርባቸው በሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች ተንቀሳቅሰው የምርጫ ቅስቀሳ ማድረግ እንዲችሉ መንግስት ጥበቃ ሊያደርግላቸው ይገባል ሲልም ነግረዉናል።

የጸጥታ ችግር ባለባቸው መንገዶች ላይ የምርጫ ቁሳቁሶች በሰላም ተንቀሳቅሰው መድረስ በሚችሉበት ሁኔታ ላይ ብሄራዊ የምርጫ ቦርድ ከጸጥታ አካላት ጋር በቅንጅት እንዲሰራ ተጠይቋል።

ኢዜማ አያይዞም፤መንግስት የጸጥታ ችግር ባለባቸው አካባቢዎች ያለውን ሁኔታ በዝርዝር በመገምገም፣ አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ ልዩ የጸጥታ ጥበቃ ስምሪት እንዲያደርግና የምርጫው ሂደት ፍትሃዊነት እንዳይጓደል ጥረት እንዲያደርግ ጠይቋል።

ኢትዮ ኤፍ ኤም (ለአለም አሰፋ)

ይመለከተኛል 3!ዛሬ አለም አቀፍ የፍልሰተኞች ቀን ነው!ይህ ጉዳይ የማይመለከተው ማን አለ?አለም አቀፍ የፍልሰተኖኞች ቀንን ስናከብር፣ለህጋዊ ፍልሰተኞች ፤ ለህገወጥ የሰዎች ዝውውር ሰለባዎች ...
18/12/2025

ይመለከተኛል 3!

ዛሬ አለም አቀፍ የፍልሰተኞች ቀን ነው!

ይህ ጉዳይ የማይመለከተው ማን አለ?

አለም አቀፍ የፍልሰተኖኞች ቀንን ስናከብር፣ለህጋዊ ፍልሰተኞች ፤ ለህገወጥ የሰዎች ዝውውር ሰለባዎች እና ተጎጅዎች፣ወገኖቻችንን ለመደገፍ ብልዩነት እንዘጋጅ።

ይህ ፕሮግራም ህገወጥ ስደት የሚያስከትለውን ተጽእኖ፣ የተስፋ ታሪኮችን እና የሰብዓዊነት ጥሪን በአንድነት የሚያቀርብ ነው።

እኛ ሁላችንም በአንድነት ቆመን
👉ግንዛቤ እንፍጠር
👉ክብርን እንስጥ
👉 ድጋፍን እንጨምር
👉 ተስፋን እንከፍት
👉ህገወጥ ስደትን እንጠየፍ

አብረን በትብብር፤እና በቅንጅታዊ አሰራራር ለፍልሰተኞች ሁላችንም ድጋፍ እናድርግ።

ይመለከተኛል 3!

ስዊት ላይፍ ፎር ኦል ከሲግማ ኢስት አፍሪካ ጋር በቲኤች ግሩፕ የተዘጋጀ

አንዳንድ አትሌቶች የተከለከሉ ጸረ-አበረታች መድሃኒቶችን መጠቀማቸው ትልቅ ፈተና ሆኗል ተባለ-  በፀረ አበረታች ቅመሞች ህግና ደንብ ዙሪያ ስልጠና እየሰጠ ነው፣የኢትዮጵያ ብሔራዊ ፀረ አበረታ...
18/12/2025

አንዳንድ አትሌቶች የተከለከሉ ጸረ-አበረታች መድሃኒቶችን መጠቀማቸው ትልቅ ፈተና ሆኗል ተባለ

- በፀረ አበረታች ቅመሞች ህግና ደንብ ዙሪያ ስልጠና እየሰጠ ነው፣

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ፀረ አበረታች ቅመሞች ባለስልጣን አትሌቶች ከፀረ አበረታች ቅመሞች ነፃ በመሆን ፍትሀዊ ውድድር እንዲያካሄዱ ስልጠና እየሰጠ ነው።

ባለስልጣን መሰሪያ ቤቱ ሁሉም ስፖርታዊ ውድድሮች ከአበረታች ቅመሞች የጸዱ እና ነፃ ውድድርን መሠረት ያደረጉ እንዲሆኑ በማናጀር ለታቀፉ አትሌቶች፣ አሰልጣኞችና ማናጀሮች ስልጠና እየሰጠ ያለው።

ኢትዮጵያ በዓለምአቀፍ ደረጃ የምትታወቅበትን አትሌቲክስ ጨምሮ በበርካታ አይነት ስፖርታዊ ውድድሮች እንዳሉ ይታወቃል።

በአትሌቶች የሚስተዋሉ አልፎ አልፎ የተከለከሉ ጸረ-አበረታች መድሃኒቶችን መጠቀም አሁንም የዘርፉ ትልቅ ፈተና ሆኖ ቀጥሏል።

ኢትዮጵያ የዓለምአቀፍ ፀረ ዶፒንግ ስምምነትን የተቀበለች መሆኗን የገለፁት የባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ምክትል ዳሬይክተር ወ/ሮ ፋንታዬ ገዛኸኝ የተፈረሙ የስምምነት ሰነዶች በሙሉ ተፈፃሚ እንዲሆኑ ባለስልጣን መስሪያቤቱ በእቅድ እየሰራ ነው ብለዋል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ፀረ አበረታች ቅመሞች ባለስልጣን ስምምነቱን ለማስፈፀም የተቋቋመ ባለስልጣን እንደሆነም ነው የገለፁት ምክትል ዳይሬክተሩ።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ፀረ አበረታች ቅመሞች ባለስልጣን ከተቋቋመበት ስልጣንና ተግባር አንፃር አትሌቶችን ከፀረ አበረታች ቅመሞች ነፃ በማድረግ እንደሆነ በስልጠናው ተመላክቷል።

ይህን መነሻ ያደረገ ስልጠና በዶፒንግ ምንነት፣ በሚያስቀጡ የሕግ ጥሰትና ተግባራት፣ የወንጀል ተጠያቂነት እንዲሁም አስተዳደራዊ ቅጣን ጨምሮ በተለያዩ ህጎች ዙሪያ ስልጠና እየሰጠ ይገኛል።

አትሌቶችን የተከለከሉ ፀረ አበረታች መዳሃኒቶችን ተጠቅመው ከተገኙ ከውድድር ማራቅ እስከ የእድሜ ዘመን እገዳ የሚደርስ ቅጣት እንደሚጣልባቸው የስልጠና ሰነዱ ያስረዳል።

ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ባዘጋጀው ስልጠና በማናጀሮች የታቀፍ አትሌቶችና አሰልጣኞች ስልጠናቸውን እየተከታተሉ ነው።(ባህልና ስፖርት ሚ/ር)

ከጋምቤላ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በወቅታዊ የክልሉ ሰላምና ፀጥታ ሁኔታ የተሰጠ መግለጫ።ውድ የክልላችን ሕዝቦች:- ባለፉት የለውጥ ዓመታት እንደ ክልልም ሆነ እንደሀገር እየተከናወኑ ባሉ የል...
18/12/2025

ከጋምቤላ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በወቅታዊ የክልሉ ሰላምና ፀጥታ ሁኔታ የተሰጠ መግለጫ።

ውድ የክልላችን ሕዝቦች:-
ባለፉት የለውጥ ዓመታት እንደ ክልልም ሆነ እንደሀገር እየተከናወኑ ባሉ የልማት ስራዎች የሚታዩና የሚዳሰሱ በርካታ ስኬቶች ተመዝግበዋል።

በክልሉም የአመራር ለውጡ ከተደረገ ወዲህ በሰላም ግንባታ ዘርፍ እምርታዊ ለውጥ መመዝገቡ የሚታወስ ነው።

በዚህም የክልላችን ሕዝቦች በልማት ተጠቃሚ መሆን የሚችሉበት ሰፊ እድል እና መደላድል ተፈጥሮ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ሲሰሩ ቆይተዋል።

ከጥቂት ዓመታት በፊት በክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች ሲከሰት በነበረው የፀጥታ መደፍረስ እና ግጭት መንግስት የዜጎችን በሰላም የመኖር መብት ለማረጋገጥ የአመራር ለውጥ መደረጉ የሚታወስ ነው።

በዚሁ መሰረት አዲስ የመጡት አመራሮች የነበረውን የፀጥታ ችግር በመፍታት ሕዝቦች በሰላም እና በመቻቻል አብሮ የመኖር እሴቶቻቸው እንዲዳብርና የክልሉን ልማት ከመንግስት ጋር በመቀናጀት እየተከናወኑ ባሉ የልማትና የሰላም ግንባታ ስራዎች በርካታ ውጤቶች እንዲመዘገቡ ጥረቶች እየተደረጉ ይገኛሉ።

ነገር ግን የክልሉ ህዝብ ሰላም መሆን እንቅልፍ የሚነሳቸው እና ግጭት እና የሰው ሞት የሚያስደስታቸው ኃይሎች በሰሞኑ የጋምቤላ ከተማን ጨምሮ በሌሎች ወረዳዎች ትርምስ ፈጥረዋል።

የክልሉ መንግስት ከህዝቡ ጋር ተባብሮ ያመጣውን ሰላም እና ልማት ወደ ኋላ ለመመለስ እየሰሩ ያሉ እነዚህ በእኩይ ተግባራት ላይ የተሰማሩ ኃይሎች በየቦታው ሰዎችን በመግደል፣ ተሽከርካሪዎች ላይ ጥቃት በማድረስ እና ህይወት እንዲጠፋ በማድረግ፣ የፀጥታ አካላትን እና አመራርን ኢላማ በማድረግ ወደ ለየለት የሕዝቦች እልቂት ለማስገባት የተለያዩ ሙከራዎችን ሲያደርጉ ተስተውሏል።

መንግስት ቅድሚያ የዜጎችን ሰላምና ደህንነት ማስከበር ላይ ትኩረት በማድረግ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመቀናጀት ተጠርጣሪዎችን አድኖ በመያዝ ላይ ሲሆን በርካቶችንም በቁጥጥር ስር አውሏል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ የፌደራል እና የክልሉ የፀጥታ አካላት አሁን ላይ ወንጀለኞችን በቁጥጥር ስር ለማዋል ሰፊ ስራዎችን እየሰሩ በመሆኑ ሕዝቡ በመሰል ጥፋት ላይ የተሰማሩ አካላትን ሲመለከት ጥቆማ እንዲሰጥ የክልሉ መንግስት ያሳስባል።

በተጨማሪም ለፀጥታ ስራ ተመድበው ከሚሰሩ የሰራዊት አባላት ውጪ የትኛውንም የጦር መሳሪያ ይዞ የሚገኝ እና የሚንቀሳቀስ ግለሰብ ወይም ቡድን ላይ የፀጥታ አካላቱ አስፈላጊውን እርምጃ የሚወስድ መሆኑን መንግስት ያስገነዝባል።

መላው የክልሉ ማህበረሰብም የፀጥታ መዋቅሩ የአካባቢውን ሰላም በማጽናት የሚያደርገው ጥረትና አጥፊዎችን ለህግ ለማቅረብ እየሰራ ያለውን የህግ ማስከበር ስራ እንዲደግፍ ጥሪ ቀርቧል።

በተከሰተው የፀጥታ ችግር ሳቢያ በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋትና ጉዳት የክልሉ መንግስት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን እየገለፀ ለተጎጂ ቤተሰቦች መጽናናትን ተመኝቷል።

የጋምቤላ ህዝቦች ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት

 #ሹመትየድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት ታህሳስ 8/2018 ዓ.ም ባካሄደው 3ኛ የስራ ዘመን 5 ዓመት 3ኛ አስቸኳይ ጉባኤ፥ በፈቃዳቸው ከኃላፊነታቸው በተነሱት አፈ-ጉባኤ ወ/ሮ ፈቲህያ አደን ...
18/12/2025

#ሹመት

የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት ታህሳስ 8/2018 ዓ.ም ባካሄደው 3ኛ የስራ ዘመን 5 ዓመት 3ኛ አስቸኳይ ጉባኤ፥ በፈቃዳቸው ከኃላፊነታቸው በተነሱት አፈ-ጉባኤ ወ/ሮ ፈቲህያ አደን ምትክ አቶ አብዲ ሙክታርን የምክር ቤቱ አፈ-ጉባኤ በማድረግ ሾሟል።

በተጨማሪም አቶ ብሩክ ወርቅነህ የድሬዳዋ የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ እና ወ/ሮ ሌሊሴ አህመድ የሴቶች ህጻናት እና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ እንዲሁም አቶ ፉአድ መሀመድ የምክር ቤቱ ጽ/ቤት ኃላፊ እንዲሆኑ የቀረበለትን ሹመት በሙሉ ድምፅ አፅድቋል።(ድሬደዋ ከንቲባ ቢሮ)

የማህበራዊ ሚዲያን በመጠቀም ሙያዊ ክብርን ያዋረዱ፣ ከህብረተሰቡ ባህልና ሞራል ተቃራኒ የሆኑ መልዕክቶችን ሲያሰራጩ የነበሩ ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር በማዋል ምርመራ እያጣራ መሆኑን የአዲስ አ...
17/12/2025

የማህበራዊ ሚዲያን በመጠቀም ሙያዊ ክብርን ያዋረዱ፣ ከህብረተሰቡ ባህልና ሞራል ተቃራኒ የሆኑ መልዕክቶችን ሲያሰራጩ የነበሩ ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር በማዋል ምርመራ እያጣራ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አስታወቀ፡፡
***
የማህበራዊ ሚዲያን በኃላፊነት በመጠቀም ትውልድን ማነፅ እንደሚገባ የበርካቶች ሀሳብና አስተያየት ከመሆኑም አልፎ ዜጎች ያልተገራ የማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም እንዲገታ በተለያዩ የሚዲያ አማራጮች ሀሳቦቻቸውን እየሰጡም ይገኛሉ፡፡

የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያም የማህበራዊ ሚዲያን በመጠቀም ሙያዊ ክብርን የሚያዋርዱ፣ ከህብረተሰቡ ባህል፣ እምነትና ሞራል ተቃራኒ የሆኑ መልዕክቶችን ሲያስተላልፉ የነበሩ " የማህበራዊ ሚዲያ አንቂ ወይም ይዘት ፈጣሪዎች ነን " (Social Media Influencers and Content Creators) የሚሉ አራት ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራ ይገኛል፡፡

የመጀመሪያዎቹ ተጠርጣሪዎች ዛሀራ መሀመድና ፈቲያ ኤልያስ የተባሉ ነዋሪነታቸው በቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 12 ልዩ ቦታው ቦሌ ቡልቡላ ሲሆን የቲክቶክ ፕላትፎርምን በመጠቀም የሀገሪቱን ባህል፣ ወግ፣ እምነትና ሞራል በማይመጥን መልኩ "Illuminant" ወይም " የሠይጣን ማህበርተኞች አባላት ነን እኛን ምሰሉ፤ በርካታ ገንዘብ ታገኛላችሁ" የሚሉ መልዕክቶችን ሲያስተላልፉ በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡

ሦስተኛው ተጠርጣሪ ደግሞ ለታ ደረጄ ተረፋ የተባለ ነዋሪነቱ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከተማ ወረዳ 04 ልዩ ቦታው ጀሞ ሦስት የሆነ " የተከበረውን የመምህርነት ሙያና የመምህራንን ክብር በሚያንቋሽሽ መልኩ" ተንቀሳቃሽ ምስሎችን እየሰራ በቲክቶክ ፕላትፎርም ሲያሰራጭ በቁጥጥር ስር ሊውል ችሏል፤ ተጠርጣሪው በሚለቃቸው ተንቀሳቃሽ ምስሎች የተማሪ የደንብ ልብስ ለብሶ የመማሪያ ወንበሮች ላይ ቆሞ መጨፈር፣ በመምህራን ላይ የማሾፍ፣ ከተማሪ ኪስ ገንዘብ የመስረቅና የመሳሰሉ ይዘቶችንም ይሰራ እንደነበር ፖሊስ አረጋግጧል፡፡

አራተኛው ተጠርጣሪ ኤዶም ሚሊዮን ሲሆን ነዋሪነቱ በቂርቆስ ክ/ከተማ ወረዳ 10 ልዩ ቦታው ካምቦሎጆ እንዲሁም የሽመልስ ሀብቴ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪ ሲሆን እርሱም የቲክቶክ ፕላትፎርምን በመጠቀም ከወገቡ በላይ ልብሱን በማውለቅና ራቁቱን በመሆን "ሰግጥ ፈምስ" በማለት በየመንገዱ ህብረተሰቡን የማስደንገጥ፣ ራቁቱን ምግብ በትሪ በመያዝ ህብረተሰቡን ካላጎረስኳችሁ የማለትና የማስደንገጥ ይዘቶችን ሲሰራ በቁጥጥር ስር ውሏል፡፡

ፖሊስ በቁጥጥር ስር በዋሉ ግለሰቦች ወይም "የማህበራዊ ሚዲያ አንቂ ወይም ይዘት ፈጣሪዎች ነን" (Social Media Influencers and Content Creators) በሚሉ ግለሰቦች ላይ ተገቢውን የወንጀል ምርመራ ስራ የጀመረ ሲሆን በቀጣይም ተመሳሳይ ድርጊት ውስጥ የሚገቡ የማህበራዊ ሚዲያ "አንቂ ነን" ባዮችን እንደማይታገስም የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ያሳስባል፡፡
*
(ዘገባ፦ ረ/ኢንስፔክተር ዳዊት እርገጤ - አ/አ ፖሊስ)

ጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ሆስፒታል ዘመናዊ የህክምና መመርመሪያ መሳሪያ ተበረከተለት***"አይካፕ" ኢትዮጵያ "ፔፕፋር ሰፖርት" ከተሰኘው ግብረ ሰናይ ድርጅት ጋር በመተባበር ለጎንደር ዩኒቨር...
17/12/2025

ጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ሆስፒታል ዘመናዊ የህክምና መመርመሪያ መሳሪያ ተበረከተለት
***
"አይካፕ" ኢትዮጵያ "ፔፕፋር ሰፖርት" ከተሰኘው ግብረ ሰናይ ድርጅት ጋር በመተባበር ለጎንደር ዩኒቨርሲቲ ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሪፈራል ሆስፒታል "ቪዲዮ ኮልፖስኮፕ" የተሰኘ ዘመናዊ የማህጸን ጫፍ ካንሰር የህክምና መመርመሪያ መሳሪያ በድጋፍ መልክ አበርክተዋል፡፡

ይህ የመርመሪያ መሳሪያ ከሶስት ሚሊየን ብር በላይ ወጪ እንደተደረገበት በርክክቡ ወቅት የገለጹት ዶ/ር ንጋት አምሳሉ (የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የማሕጸን ካንሰር ሰብ ስፔሻሊስት) ፣ መሳሪያው የሰው ሰራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂን (AI) ማካተት የሚችል ከመሆኑም በላይ ለማህጸን ጫፍ ቅድመ ካንሰር ልየታ ጉልህ ሚና እንደሚኖረው አያይዘው ተናግረዋል፡፡

ለጋሽ ድርጅቶቹን በመወከል የመመርመሪያ መሳሪያውን ያስረከቡት የአይካፕ ኢትዮጵያ ፕሮግራም ማኔጀር ዶ/ር ህዝቅየል ጴጥሮስ ናቸው፡፡ በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሆሲፒታል በኩል ርክክቡን የፈጸሙት የዩኒቨርሲቲ ሆስፒታሉ ቺፍ ክሊኒካል ዳይሬክተር ዶ/ር ምንአርጋቸው አጣናው ሲሆኑ፣ ዳይሬክተሩ የዩኒቨርሲቲ ሆሲፒታሉን የህክምና ባለሙያዎች በዕውቀት፣ በአመለካከትና በክህሎት ብቁ እንዲሆኑ ማድረግ ብቻውን ለውጤት እንደማያበቃ ገልጸው ይልቁንም የበቁ ባለሙያዎች ዘመኑን የዋጀ የህክምና መመርመሪያ መሳሪያዎች ግብዓት ሊሟሉላቸው እንደሚገባ አያይዘው ተናግረዋል፡፡

ዶ/ር ምንአርጋቸው ከአስር ሚሊየን ህዝብ በላይ ግልጋሎት ለሚሰጠው ለጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል በየጊዜው ድጋፍ ለሚያደርጉ ግብረ ሰናይ ድርጅቶችና ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን በሙሉ ልባዊ ምስጋናቸውንም አቅርበዋል፡፡
***
(የህዝብ ግንኙነት ዳሬክቶሬት)

ህንድ እና ህንዳውያን:- የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ወዳጆች!!በተረፈ ወርቁ (ዲ/ን)"... የጥንታዊት ታሪክና ገናና ሥልጣኔ ባለቤት፤ የአፍሪካና የጥቁር ሕዝብ ታላቅ የነጻነት ተጋድሎ ምልክት ከ...
17/12/2025

ህንድ እና ህንዳውያን:- የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ወዳጆች!!

በተረፈ ወርቁ (ዲ/ን)

"... የጥንታዊት ታሪክና ገናና ሥልጣኔ ባለቤት፤ የአፍሪካና የጥቁር ሕዝብ ታላቅ የነጻነት ተጋድሎ ምልክት ከሆነች አገር- ኢትዮጵያ ይሄ የክብር ኒሻን ስለተበረከተልኝ ደስታዬ እጥፍ ድርብ ነው፤ በ1.4 ቢሊዮን በሚሆነው የአገሬ የህንድ ሕዝብ ስም ምስጋናዬን ለመግለጽ እወዳለሁኝ...፤"

በአገራችን ኢትዮጵያ ይፋዊ ጉብኝት በማድረግ ላይ የሚገኙት የህንዱ ጠቅላይ ሚ/ር ናኔድራ ሞዲ- በጠቅላይ ሚ/ር ዐብይ አሕመድ የኢትዮጵያ ከፍተኛ ኒሻን በተበረከተላቸው ጊዜ ከላይ በመግቢያዬ ላይ ከጠቀስኩት ንግግራቸው ባሻገር በንግግራቸው - ህንድና ህንዳውያን አገራችን ኢትዮጵያ በፋስሽት በተወረረች ወቅት ከጎናችን መቆማቸውን ታሪክ አጣቅስው ተናግረዋል።

ህንድ እና ህንዳውያን:- የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ወዳጆች!!

የቅኝ ገዥዎችን ቅስም ካነካከተውና መላው አውሮፓንና ነጮችን በድንጋጤ እጃቸውን በአፋቸው ላይ እንዲጭኑ ያደረጋቸውን፤ አንፀባራቂውን የዐድዋውን ድል- ለመበቀል ፋሽስት ኢጣልያ ከ40 ዓመታት ዝግጅት በኋላ በአየርና በምድር የጦር መሳሪያ እስከ አፍንጫው ታጥቆና እንዲሁም በዓለም አቀፍ የሕግ የተከለከለ የመርዝ ቦምብ ሳይቀር ተሽክሞ ነበር የመጣው።

"... ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያውያን በዓለም ፊት የሚኮሩበት ነጻነታችውና ሉዓላዊነታቸው በቅኝ ግዛት ቀምበር ስር እንዲወድቅና ኢትዮጵያውያን ዳግመኛ አንገታቸውን ቀና አድርገው እንዳይሄዱ ለአፍሪካና ለመላው ጥቁር ሕዝብ መቀጣጫ ሊሆኑ ይገባል!!" በሚል እብሪትና ትእቢት ፋስሽቱ ቤኒቶ ሞሶሎኒ የበቀልና የጭካኔ ሰይፉን በኢትዮጵያውያን ላይ መዘዘብን።

በዛ የመከራና የጭንቅ ዘመን ህንድና ህንዳውያን ከኢትዮጵያ ጋር ቆመዋል፤ በዓለም መድረክ ድምፅ ሆነውናል። ታሪክን ምስክር እናድርግ፤ በወቅቱ የህንድ ጠቅላይ ሚ/ር የነበሩት ጃኋራል ኔህሩ በህንድ ፓርላማ ባሰሙት ንግግራቸው እንዲህ ነበር ያሉት፤

"We in India can do nothing to help our brethren in distress in Ethiopia… But we can at least send them sympathy… in the hour of their trial. We stand with them today in their sorrow…" (quoted in Indian government records and MEA speeches).

"... ምንም እንኳን ለኢትዮጵያና ለኢትዮጵያውያን ለጊዜው ምንም ማድረግ ባንችልም- ለነጻነታቸው በሚያደርጉት ተጋድሎአቸው ከጎናቸው መሆናችን የሚገልጽ ልባዊ መልእክታችንን ልንልክላቸው እንወዳለን፤ በዓለም አቀፍ መድረክ ለኢትዮጵያውያን የፀረ-ፋሽስት እና የፀረ-ቅኝ ግዛት ተጋድሎ የጋራ ድምፅ እንሆናቸዋለን...፤"

ኢትዮጵያ እና ህንድ በቀደመው ዘመን

ጥንታዊት፤ የገናና ታሪክና የግዙፍ የሥልጣኔ ባለቤት የሆነችው አገራችን ኢትዮጵያ- እንደ አገራችን ሁሉ የሺህ ዘመናት ታሪክና የሥልጣኔ ባለቤት ከሆነችው ህንድ ጋር ለ2000 ሺህ ዓመታት በፊት በህንድ ውቅያኖስ እና በቀይ ባሕር አማካኝነት የአፍሪካን ድንበር የተሻገረ የንግድ ግንኙነት/Martime Trade እንደነበረን የታሪክ ድርሳናት የአርኪዮሎጂ ሳይንስ ግኝቶች ይመሰክራሉ።

ወጌን ፈር ለማስያዝ ይረዳኝ ዘንድ ከታሪክ ድርሳናት በጥቂቱ ላጣቅስ፤

Neville Chittick, የተባለ ምሁር፤ "Indian Relations with East Africa before the Arrival of the Portuguese" በሚል በጻፈው መጽሐፍ በህንድ በኩሻን ሥርወ-መንግሥት ዘመን መገበያያ የነበሩ የወርቅ ሳንቲሞች በአርኪዮሎጂ ጥናት በአክሱምና በደብረዳሞ መገኘታቸውን ተጽፏል። ይኸው ምሁር፤ የህንድ የጉፕታ ዘመነ መንግሥት አሻራ የሆኑ ቁሳቁሶች፤ የከበሩ ጌጣጌጦችና ጨሌዎች በጥንታዊቷ አክሱም ከተማና የኢትዮጵያ ወደብ በሆነችው አዶሊስ መገኘቱን አትቷል።

በተጨማሪም በኢትዮጵያ/በአክሱም ታሪክና ሥልጣኔ ላይ የተጻፉ በርካታ የታሪክ ድርሳናትና የጉዞ ማስታወሻዎች እንደሚጠቁሙት፤ አክሱማውያን የዝሆን ጥርስ፣ ወርቅ፣ ዕንቁ፣ ሃርና የከበሩ ማዕድናትን... ወዘተ. በቀይ ባሕርና በህንድ ውቅያኖስ አማካኝነት ከህንድና ከመካከለኛው ምሥራቅ አጋራት ጋር የንግድ ልውውጥ ያደርጉ ነበር።

የግሪክ የኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን መነኩሴና ተጓዥ የነበሩት አባ ኮስሞስ ኢንዲክሎፕተስ፤ "the Periplus of Eritrean Sea" በሚል አርእስት ከ 1500 ዓመታት ገደማ በፊት በጻፉት የጉዞ ማስታወሻቸው፤

"... ኢትዮጵያውያን/አክሱማውያን በጥንት ዘመን በቀይ ባሕር በኩል- ከመካከለኛው ምሥራቅ፣ ከዐረቢያ፣ ከቻይና ከህንድ ጋር የጠበቀ የባሕር ላይ የንግድ ግንኙነት እንደነበርን፤" ጽፈዋል።

እንደ ማጠቃለያ፤

የህንድና የኢትዮጵያ ግንኙነት ሺሕ ዘመንን የተሻገረ ጠንካራ የታሪክና የሥልጣኔን እሤቶችን የሚጋራ ነው። በግርማዊ ቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ዘመነ መንግሥት የኢትዮጵያና የህንድ ዲፕሎማሲ ግንኙነት ጠንካራ መሠረትን ይዞ ተጀመረ። በደርግም ሆነ በዘመነ ኢሕአዴግ መንግሥታት ቢቀያየሩም የሁለቱ አገራት ግንኙነት ተጠናክሮ እንደቀጠለ ነው።

ኢትዮጵያና ህንድ በትምህርት፣ በጤና፣ በግብርና፣ በኢንቨስትመንት፣ በቴክኖሎጂ... ወዘተ. ረገድ የጠበቀ ትስስር አላቸው። በዓለም ዙሪያ በሰላም ማስከበር ዘመቻ ሁለቱ አገራት- ኢትዮጵያና ህንድ በግንባር ቀደምትነት የሚጠቀሱ አገራት ናቸው። በብሪክስ አገራትና በደቡብ ደቡብ ትብብር መድረክ ህንድና ኢትዮጵያ የጎላ ሚናን እየተጫወቱ የሚገኙ ሀገራት ናቸው።

የዛሬውን ኢትዮጵያንና ህንድን የተመለከተውን ወጌን- በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ ሳይንስና የዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህር/ፕሮፌሰር፤ በአንድ ወቅትም በህንድ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሆነው ያገለገሉት አምባሳደር ዶ/ር ትዝታ ሙሉጌታ አባባል ለመቋጨት ወደድኹ፤

"የኢትዮጵያና የህንድ ግንኙነት በማይናወጽ ጠንካራ የታሪክ መሠረትና የእርስበርስ ትብብር ላይ የቆመ ነው፤"

የኢትዮጵያና የህንድ ግንኙነት ይለምልም!!

በኢትዮጵያ ለሚገኙ አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች የፋይናንስ ተደራሽነትን የሚመለከት ዓለምዓቀፍ ሲምፖዚየም ተከፈተየSNV ሊዌይ (LIWAY) ፕሮጀከት፣ በኢትዮጵያ ለሚገኙ አነስተኛና መካ...
17/12/2025

በኢትዮጵያ ለሚገኙ አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች የፋይናንስ ተደራሽነትን የሚመለከት ዓለምዓቀፍ ሲምፖዚየም ተከፈተ

የSNV ሊዌይ (LIWAY) ፕሮጀከት፣ በኢትዮጵያ ለሚገኙ አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች (MSMEs) የፋይናንስ ተደራሽነትን የሚመለከት ዓለምዓቀፍ ሲምፖዚየም በዛሬው እለት በሃያት ሬጀንሲ በይፋ መጀመሩን አስታውቋል።

ጉባዔው "ለ MSMEs የፋይናንስ በሮችን መክፈት፡ በኢትዮጵያ ለሴቶች፣ ወጣቶችና አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች (MSMEs) ያሉ ተግዳሮቶችና ዕድሎች" በሚል መሪ ሃሳብ እየተካሄደ ይገኛል።

ይህ መድረክ ቁልፍ የፋይናንስ ዘርፍ ባለድርሻ አካላትን (ባንኮችን፣ የማይከሮ ፋይናንስ ተቋማትን፣ ፊንቴከ ኩባንያዎችን፣ የመንግሥት አካላትን እና አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞችን) በአንድነት በማሰባሰብ የዘርፉን ተግዳሮቶችና ዘላቂ መፍትሄዎች ላይ ለመወያየት ያለመ እንደሆነ ተገልጿል።

የፕሮጀከቱ ዋና ዓላማ 400,000 ዝቅተኛ ገቢ ያላቸውን ሰዎች (50% ሴቶች እና 75% ወጣቶች) ገቢ እንዲያድግና የኢኮኖሚ ተሳትፎአቸው እንዲጨምር ማስቻል እንደሆነ ተጠቁሟል።

የሊዌይ ፕሮጀክት (LIWAY Project) በዋነኝነት የዜጎችን ኑሮ በማሻሻል ረገድ ሰፊ ስራ እየሰራ እንደሚገኝ የተገለፀ ሲሆን፣ በዚህም ከ 276,500 በላይ ሴቶችና ወጣቶች የኑሮ ደረጃቸው እንዲሻሻል ለማድረግ ተችሏል ተብሏል፡፡ በተለይም የፋይናንስ ተደራሽነትን በማዘመን ረገድ የዲጂታል የብድር አገልግሎትን ውጤታማ በሆነ መንገድ ተግባራዊ ማድረጉም ተነግሯል፡፡

በዚህም መሰረት፣ ተደጋጋሚ ብድሮችን ጨምሮ ከ 1,700 በላይ ዲጂታል ብድሮች ለተጠቃሚዎች የቀረቡ ሲሆን፣ በገንዘብ መጠንም ከ 161 ሚሊዮን ብር በላይ የሥራ ማስኬጃ ካፒታል በዲጂታል ዘዴ መሰራጨቱ በመርሀገብሩ ተገልጿል፡፡

በተጨማሪም አነስተኛና ጥቃቅን ኢንተርፕራይዞችን (MSMEs) በማጠናከር ረገድ፣ ወደ 300 ለሚጠጉ ድርጅቶች የጥሬ ገንዘብ ፍሰትን መሰረት ያደረጉ 768 ብድሮች በመስጠት የኢኮኖሚ እንቅስቃሴያቸው እንዲቀላጠፍ ከፍተኛ እገዛ አድርጓል፡፡

SNV ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ፣ ከልማት አጋሮች እና ከግል የፋይናንስ ተቋማት ጋር በመሆን የፖሊሲ ዘርፎች ላይ እየሰራ እንደሚገኝ የትገለፀ ሲሆን ይህም ለሴቶች አመቺ የሆኑ የብድር አይነቶችን (ለምሳሌ የጥሬ ገንዘብ ፍሰትን የተከተለ የክፍያ ጊዜ፣ ምትክ ዋስትና) መሞከርና ማስፋፋት ፣ በጥሬ ገንዘብ ፍሰት ላይ ለተመሠረተ ብድር ግልጽ የአበዳሪ መስፈርቶችን፣ የሸማቾች ጥበቃ ዘዴዎችን እና የሪፖርት አቀራረቦችን መወሰን ናቸው

SNV ዓለም አቀፍ የልማት ድርጅት ሲሆን በድህነት የሚኖሩ ሰዎችን ኑሮ ዘላቂ በሆነ መንገድ በማሻሻል ይታወቃል፡፡ በዋናነት በሦስት ዘርፎች ግብርና ፣ ምግብ፣ ኢነርጂ እና ውሃ ላይ ያተኩራል

SNV ከ 20 በላይ በሆኑ አገሮች የሚሰራ ሲሆን፣ በኢትዮጵያ ውስጥ ደግሞ ከ 1974 ዓ.ም. ጀምሮ በመሥራት ላይ ይገኛል፡፡
#ድሬትዩብ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሼባ ማይልስ እና አኮያ ፕሮፐርቲስ ስምምነት ተፈራረሙ።📌 አርቲስት እፀህይወት አበበ የድርጅቱ ብራንድ አምባሳደር ሆነች።​የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሼባ ማይልስ እና አ...
17/12/2025

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሼባ ማይልስ እና አኮያ ፕሮፐርቲስ ስምምነት ተፈራረሙ።

📌 አርቲስት እፀህይወት አበበ የድርጅቱ ብራንድ አምባሳደር ሆነች።

​የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሼባ ማይልስ እና አኮያ ፕሮፐርቲስ የደንበኞቻቸውን ተጠቃሚነት የሚያሳድግ የስትራቴጂካዊ አጋርነት ስምምነት ተፈራርመዋል።

​ታህሳስ 7 ቀን 2018 ዓ.ም በኢትዮጵያ ስካይ ላይት ሆቴል በተከናወነው የፊርማ ስነ-ስርዓት፣ የአየር መንገዱን የሽልማት መርሃ-ግብር (ShebaMiles) ከሪል እስቴት ግብይት ጋር የሚያስተሳስር ስምምነት ተደርጓል።

​​በዚህ ስምምነት መሰረት በአኮያ ፕሮፐርቲስ እየተገነቡ ያሉ ዘመናዊ መኖሪያ ቤቶችን እና የንግድ ሱቆችን የሚገዙ ደንበኞች፣ የስታር አሊያንስ (Star Alliance) አባል ከሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሼባ ማይልስ የጎልድ አባልነት ሽልማት በክብር ያገኛሉ። ይህም ደንበኞች በኢንቨስትመንታቸው ልክ የአየር መንገዱን ጥቅማጥቅሞች እንዲያገኙ ያስችላቸዋል።

ይህ ስምምነት በኢትዮጵያ አየር መንገድ ሼባ ማይልስ እና የሪል እስቴት ዘርፍ መካከል ያለውን ትብብር ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር መሆኑ ተመልክቷል።

​በዚሁ መርሃ-ግብር ላይ አኮያ ፕሮፐርቲስ በተለያዩ ፊልሞችና የጥበብ ስራዎቿ ከፍተኛ ተወዳጅነትን ያተረፈችውን አርቲስት እፀህይወት አበበን የድርጅቱ የብራንድ አምባሳደር አድርጎ በይፋ አስተዋውቋል። አርቲስቷ የድርጅቱን ገፅታ በመገንባትና የምርት ስሞቹን ለህዝብ በማስተዋወቅ ረገድ ግንባር ቀደም ስራዎችን እንደምትሰራ ተገልጿል።

​​ከ230 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ እድል የፈጠረው አኮያ ግሩፕ፣ በውስጡ የተለያዩ ታላላቅ ድርጅቶችን አቅፎ የያዘ ግዙፍ ተቋም ነው። ከእነዚህም መካከል፦
📍​አኮያ ፕሮፐርቲስ፦ በሪል እስቴት ዘርፍ ዘመናዊ ቤቶችን የሚያቀርብ፣
📍​አኮያ ኮፊ፦ በቡና ምርትና ኤክስፖርት ላይ የተሰማራ፣
📍​አኮያ ሞተርስ፦ በተሽከርካሪ ግብይት ዘርፍ የሚንቀሳቀሱ ይገኙበታል።

“የኢትዮጵያ ጤፍ ከፍተኛ ፋይበር ያለውና ተስማሚ የምግብ ዓይነት ነው” - ናሬንድራ ሞዲየኢትዮጵያ ጤፍ ከፍተኛ ፋይበር ያለውና እጅግ ተስማሚ የምግብ ዓይነት መሆኑን የሕንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ...
17/12/2025

“የኢትዮጵያ ጤፍ ከፍተኛ ፋይበር ያለውና ተስማሚ የምግብ ዓይነት ነው” - ናሬንድራ ሞዲ

የኢትዮጵያ ጤፍ ከፍተኛ ፋይበር ያለውና እጅግ ተስማሚ የምግብ ዓይነት መሆኑን የሕንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ገለጹ።

የሕንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በኢፌዴሪ 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች እና የፌዴሬሽን ምክር ቤቶች 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን የጋራ ስብሰባ ላይ ተገኝተው ንግግር አድርገዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በኢፌዴሪ 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች እና የፌዴሬሽን ምክር ቤቶች 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን የጋራ ስብሰባ ላይ ባደረጉት ንግግር፤ በሕንድ ሦስት ዋና ዋና ምግቦች ቢኖሩም የኢትዮጵያ ጤፍ ግን ከፍተኛ ፋይበር ያለውና ለጤና ተስማሚ የሆነ የምግብ ዓይነት መሆኑን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ምግቦች በተለይም "በየዓይነቱ" በሕንድም ሆነ በአውሮፓ በስፋት እየተለመደ መምጣቱን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጠቁመዋል።

አገራቱ በጋራ ለመሥራት የሚያደርጉት ትብብር የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነቱን ይበልጥ ለማጠናከር የሚረዳ መሆኑንም ናሬንድራ ሞዲ አብራርተዋል።

ጋዜጣ ፕላስ

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when DireTube posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to DireTube:

Share

Our Story

DireTube is the Largest Ethiopian News & Video Platform. It has particularly proven its value when it comes to keeping the worldwide Ethiopian Diaspora connected to their home country.

In many parts of the world Ethiopians do not have direct access to Ethiopian news and entertainment, therefore, DireTube becomes their primary source for these. For this reason DireTube is now one of the most popular Ethiopian websites on the internet.