DireTube

DireTube DireTube.com is the #1 Ethiopian Video Sharing Site. DireTube is an Ethiopian media and entertainment website founded on October 26, 2008.

ሴቶች ለእናንተ ነው።የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሕክምና ኮሌጅ ከበልሻ ፋውንዴሽን ጋር በመተባበር  ነጻ የጡት ካንሰር ምርመራ እና ግንዛቤ መስጫ መርሐ ግብር አዘጋጅቷል። ሁላችሁም በዚ...
29/10/2025

ሴቶች ለእናንተ ነው።

የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሕክምና ኮሌጅ ከበልሻ ፋውንዴሽን ጋር በመተባበር ነጻ የጡት ካንሰር ምርመራ እና ግንዛቤ መስጫ መርሐ ግብር አዘጋጅቷል።

ሁላችሁም በዚህ እድል እንድትጠቀሙ ተጋብዛችዋል።

ከጥቅምት 17/2018-ጥቅምት 21/2018 ዓ.ም
በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሕክምና ኮሌጅ

የካንሰር ሕክምና ማዕከል
በመገኘት የዚህ እድል ተጠቃሚ ይሁኑ
ከጠዋቱ 2፡30-10፡00 እንጠብቅዎታለን።
የጡት ካንሰር በሽታ ስር ሳይሰድ ከታወቀ
ሙሉ ለሙሉ ሊድን የሚችል በሽታ ነው።

ፋንታ ሲኒማ ቱር በዩኒቨርሲቲዎች ሊጀመር ነው!ፋንታ ሲኒማ ቱር በዩኒቨርሲቲዎች ተማሪዎችን ለአዲሱ የትምህርት ዘመን እንኳን ደህና መጣችሁ በማለት ከአስር በላይ በሆኑ ዩኒቨርሲቲዎች ማለትም  ...
29/10/2025

ፋንታ ሲኒማ ቱር በዩኒቨርሲቲዎች ሊጀመር ነው!

ፋንታ ሲኒማ ቱር በዩኒቨርሲቲዎች ተማሪዎችን ለአዲሱ የትምህርት ዘመን እንኳን ደህና መጣችሁ በማለት ከአስር በላይ በሆኑ ዩኒቨርሲቲዎች ማለትም ( በጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ፣ ሀረማያ ዩኒቨርሲቲ፣ ሀረር ጤና ሳይንስ ዩኒቨርሲቲ፣ ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ፣ ጅማ ዩኒቨርሲቲ፣ ሆሳዕና ዋቻሞ ዩኒቨርሲቲ፣ ወላይታ ዩኒቨርሲቲ፣ አርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ፣ ዲላ ዩኒቨርስቲ እና ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ) ተወዳጁን “ አል-ሞቷል “ ፊልም በመያዝ ለተማሪዎች ከፋንታ ተወዳጅ ጣእም ጋር አሪፍ ጊዜ እንድታሳልፉ ይዞላችሁ መጥቷል።

ከጥቅምት 20 - ህዳር 03 ድረስ ከላይ በተጠቀሱት ዩኒቨርሲቲዎች የሚታይ ይሆናል::

ደስ የሚል ጣፋጭ ስሜት ከፋንታ ጋር!
ፈታ በፋንታ ሲኒማ

በባህር በር ጉዳይማ እኛም እንደህዝብ አልሰማንም፤ጎበዝ አጀንዳው የልጆቻችንን ሀገር የመስራት ጉዳይ ነው።***(ተስፋዬ ዘ ሸገር - ለድሬ ቲዩብ)ስለ ወደብ የምናወራው እኮ ስለቸገረን እንንጠቅ...
29/10/2025

በባህር በር ጉዳይማ እኛም እንደህዝብ አልሰማንም፤
ጎበዝ አጀንዳው የልጆቻችንን ሀገር የመስራት ጉዳይ ነው።
***
(ተስፋዬ ዘ ሸገር - ለድሬ ቲዩብ)

ስለ ወደብ የምናወራው እኮ ስለቸገረን እንንጠቅ በሚል አይደለም፤ ንብረታችን ነጣቂያችን ያደርግበት አጥቶ እጁ ላይ ነውና እናስመልስ እያልን ነው። እንኳንን አሰብን ማስመለስ አሰብን ማጣትንም ችለን ኖረናል። ከኬኒያና ከኡጋንዳ ከሱማሊያ እና ከሱዳን ጭምር ኮንትሮባንድ የሚገባባት ትልቅ ሀገር ዜጎች የሆንበት ምስጢር እኮ ባህር አልባነት ነው።
መቶ ምናምን ሚሊዮን ቁጥር ያለው ህዝብ ሆነን በአናቱ ስለ አድዋ እየዘፈንን በአናቱ ደግሞ "ጥንት እኮ ኢትዮጵያ በስሟ የሚጠራ ውቅያኖስ ነበራት" እያልን እየተረክን፣ ታሪክ ደቡብ አረቢያ ባህሩ ዳር አስቀምጦን እኛ ግን ሌላ ቦታ ያለን ህዝቦች ነን።
የኢትዮጵያ ህዝብ በባህር በር ጉዳይ የወል መሻት አለው። እርግጥ ነው ባህር ስንቀማ ዓይናችንን የሸፈኑ፣ ጆሯችንን የደፈኑ የመሰላቸው ሰዎች ዛሬም እዚያ ማዶ ምን እንደሚሰፈርላቸው አላውቅም "ለአሰብ ብንዋጋ ከሻዕቢያ ጎን እንቆማለን" ይሉናል።

ጎበዝ ባህሩ ብሎ ስም ለሚያወጣ ህዝብ የባህር በር ጉዳይ ምኑም የማይመስለው የሚመስለው የማዶ ሰው አይገባኝም ይልቁንም የእኛ ሰው የእናቱን ጡት ከመንከስ ወደ መቁረጥ ከፍ ያደረገበት የባንዳነት መንፈስ ይደንቀኛል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ትናንት ፓርላማ ላይ ስለ ባህር በሩ ሲናገሩ እኛ "አልሰማንም" ያሏት ነገር ትልቁን የትውልድ እንቆቅልሽ ለመፍታት ዋናዋ መሳሪያ ናት።

ልንስማማ የሚገባን የባህር በር ያስፈልገናል በሚለው ላይ ነው። እንዴት የሚለው ሌላ ጥያቄ ሌላ መልስ አለው። ከምንም በላይ ግን የልጆቻችንን ሀገር የምንሰራው ባህሩ በእጃችን ስናስገባ ነው። ባህር ሸጦ መብላት አንድ ነገር ነው ባህር ሰጥቶ መሞት ግን ምን የሚሉት ጨካኔ እንደሆነ ትውልድ ሊማር የሚችለው ዳግም ወደ ባህር ዳርቻችን ስንጠጋ ነው።

ዛሬ የምናየው አፋር ትልቁን እርስቱን ያጣበት ታሪክ አሁን ያለችዋ ኢትዮጵያ ወደ ነገ እንዳትሄድ እንቅፋት የሆነ ጉዳይ የወደብ ዕዳ ነው። ወደብ ስሙ በምን ቋንቋ ጦርነት እንደሆነ አይገባኝም። የባህር በር ያስፈልገናል ማለት ውጊያ አማረን ማለት አይደለም።

ግን ደግሞ የባህር በር ፍላጎታችሁ እንድወጋችሁ ያስገድደኛል የሚል ከመጣ ወደ የትም አንሸሽም።

በባህር በር እጦት ያልደረሰብን ነገር የለም። አሁን ለወደብ አብረን ስንቆም ቃታ የሚስብ ቢመጣ ወደ ወደቡ ያስጠጋናል እንጂ ወደ ኋላ አያሸሸንም።

29/10/2025

መኖር በጊፍት መንደር!
***
ጊፍት ሪል ስቴት በለገሃር፣ በተ/ሃይማኖት፣ በ22 ማዞሪያ፣ በሲኤምሲ እና በፈረስ ቤት በሚገኙ መንደሮቹ ቅንጡ አፓርትመንቶችንና የንግድ ሱቆችን በተመጣጣኝ ዋጋ ለሽያጭ አቅርቧል፡፡

ይምጡ! ከጊፍት ጋር ቤተሰብ ይሆኑ!

መኖር በጊፍት መንደር!

ጊፍት ሪል ስቴት
ማህበረሰብን እንገነባለን!

ለበለጠ መረጃ:-
Website: https://www.giftrealestate.com.et
+251984 65 65 65/+251979 65 65 65

ኢትዮጵያ ለደቡብ ሱዳን ሰላም አስፈላጊውን ድጋፍ ታደርጋለች- የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር)ኢትዮጵያ ለደቡብ ሱዳን ሰላም እና መረጋጋት የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደም...
29/10/2025

ኢትዮጵያ ለደቡብ ሱዳን ሰላም አስፈላጊውን ድጋፍ ታደርጋለች- የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር)

ኢትዮጵያ ለደቡብ ሱዳን ሰላም እና መረጋጋት የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ገለጹ።

ኢትዮጵያ ከደቡብ ሱዳን ጋር በመሰረተ ልማት ያላትን ትስስር ለማጠናከር ፍላጎት እንዳላትም ተናግረዋል።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) በደቡብ ሱዳን የምስራቅ አፍሪካ ጉዳዮች ሚኒስቴር ፒዬንግ ዴንግ ኩኦል የተመራ ከፍተኛ ልዑክ ዛሬ በጽህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።

ልዑካን ቡድኑ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ በደቡብ ሱዳን በተለይም በአቢዬ ግዛት ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ አስመልክቶ ገለጻ አድርጓል።

ኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብን አጠናቃ በስኬት በማስመረቋ ደስታቸውን በመግለጽ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) የደቡብ ሱዳን ፕሬዝዳንት ሳልቫ ኪር ማያርዲት በህዳሴ ግድብ ምርቃት ላይ በመሳተፋቸውም ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ ለደቡብ ሱዳን ሰላም እና መረጋጋት ያላትን ጽኑ ቁርጠኝነት አረጋግጠዋል።

ሁለቱ ሀገራት በመሰረተ ልማት የበለጠ በመተሳሰር ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ትብብርን ለማጎልበት ሊሰሩ እንደሚገባም ገልጸዋል።

AMN

የመልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ምልጃ እና ረድኤት አይለየን🙏ገብርኤል ማለት የእግዚአብሔር ኃይል ነው ማለት ነው። መልአኩ ገብርኤል በቅድስናው ቅዱስ ይባላል፡፡ የዙፋን መልእክተኛ ነውና መልአክ ወይ...
29/10/2025

የመልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ምልጃ እና ረድኤት አይለየን🙏

ገብርኤል ማለት የእግዚአብሔር ኃይል ነው ማለት ነው። መልአኩ ገብርኤል በቅድስናው ቅዱስ ይባላል፡፡ የዙፋን መልእክተኛ ነውና መልአክ ወይም መልእክተኛ ይባላል፡፡

የሠራዊት አዛዥ ነውና ሊቀ መላእክት ይባላል፡፡ በቅዱስ መጽሐፍ ስማቸው ከገነኑ መላእክት ከቅዱስ ሚካኤል ቀጥሎ የሚጠራው ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ነው፡፡ ቅዱስ ገብርኤል ድንቅ መልእክቶችን በማድረስና የተረበሹትን በማረጋጋት ይታወቃል፡፡ ነገደ መላክት በሰማይ አምላካቸው ተሰውሮባቸው ማን ፈጠረን ብለው በተጨነቁ ጊዜ ያረጋጋቸው እርሱ ነው፡፡ በክብሩ ከፍ ብሎ በመፈጠሩ መላዕክትን እኔ ነኝ የፈጠርኳችሁ ብሎ ሊያስት የሞከረውን የሀሰት አባት የያኔው (ሳጥናኤል) ጠላት ዲያብሎስ ተከራክሮ የረታው እርሱ ቅዱስ ገብርኤል ነው፡፡ እግዚአብሔርን የሚያመለኩና የሚገዙ እንዲሁም ለእርሱ ከብርን የሚሰጡ ሁሉ ከነገር እንኳን አንዳች እንደማይጎድላቸው በዘመናት መካከል ተመልክተናል፡፡

ደግሞም እግዚአብሔር ለሚወዱት የሚሆን ጠባቂ በዙሪያቸው ያቆማል። ይህም ደግሞ እውነት ነው፡፡ በሉቃስ 1÷19 “እኔ በእግዚአብሔር ፊት የምቆመው ገብርኤል ነኝ” ብሎ መገኛ ስፍራውንና እግዚአብሔር የሰጠውን ክብር በይፋ ያወጀ መልአክ ነው፡፡ ቅዱስ ገብርኤል አብሳሬ ትስብዕት፤ እመቤታችን አምላክን እንደምትወልድ ታላቁን የምሥራች ይዞ የደረሰው ቅዱስ ገብርኤል ነው፡፡ የሰው ልጆችን መዳን ታላቁን የምሥራች ይዞ በመምጣቱና በሀዲስ ኪዳን ስሙ ተደጋግሞ በመጠቀሱ መጋቤ ሐዲስ ይባላል፡፡ ሊቀ ካህናት ዘካርያስ መጥምቁ ዮሐንስን እንደሚወልድ የዘመናትን የጸሎት ምላሽ ይዞ የመጣ እርሱ ነው፡፡ በባቢሎን ምርኮ ሆኖ ስለሕዝቡ የሚያለቅሰውን የነቢዩ ዳንኤልን የጸሎት መልስ ይዞ የመጣው፣ ራእዩንም ያብራራለት ቅዱስ ገብርኤል ነው፡፡ ቅዱስ ገብርኤል የአምላክና የሰው ልጆች ወዳጅ ነው፡፡

ቅዱስ ገብርኤል በእግዚአብሔር ፊት ታላቅ የሚቆም የአምላክ ባለሟል ነው፡፡ መላእክት የሰው ልጆች አፍቃሪና ወዳጅ ናቸው፡፡ ከእነዚህ ወዳጆቻችን አንዱ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ነው፡፡ ይህንም ህጻኑ ቅዱስ ቂርቆስንና እናቱ ቅድስት ኢየሉጣን ከእሳት አድኗል፡፡ የፋርስ ንጉሥ የነበረው ናቡከደነፆር እግዚአብሔር አምላክ ምድሪቱንና ሕዝቡን እንዲያስተዳድር ቢፈቅድለት በትዕቢት ተሞላ፡፡ በኢሳይያስ 10÷13-14፤ እና በዳንኤል 3÷1 እንደተጻፈው “ሁሉን በኃይሌ አደርጋለሁ፣ በማስተዋል ጥበቤም የአሕዛብን ድንበሮች አርቃለሁ፣ ሀብታቸውንም እዘርፋለሁ፣ የሚኖሩባቸውንም ከተሞች አናውጣለሁ፣ በእጄም ዓለምን ሁሉ እንደ ወፍ ቤት እሰበስባለሁ፣ እንደ ተተወ እንቁላልም እወስዳቸዋለሁ፤ ከእኔም የሚያመልጥ የለም፤ የሚቃወመኝም የለም” ብሎ ቁመቱ ስድሳ ክንድ፣ ወርዱም ስድስት ክንድ የወርቅ ጣዖትን አሠርቶ በባቢሎን አውራጃ በዱራ ሜዳ ላይ አቁሞ ስገዱለት አለ፡፡

ሦስቱ እግዚአብሔር የመረጣቸው ጠቢባን ሕጻናት አናንያ፣ አዛርያ፣ ሚሳኤል በንጉሡ ፊት ቆመው “ንጉሥ ሆይ እኛ የምናመልከው አምላክ በሰማይ አለ፡፡ ከሚነድደው ከእቶኑ እሳት ያድነን ዘንድ ይችላል፤ ከእጅህም ያድነናል፡፡ ንጉሥ ሆይ! ይህም ባይሆን አማልክትህን እንዳናመልክ ላቆምኸውም ለወርቁ ምስል እንዳንሰግድ ዕወቅ” ባሉ ጊዜ ወደ እቶን እሳት ተጣሉ፡፡ ሊቀ መላዕክት ቅዱስ ገብርኤልም ደርሶ አዳናቸው፡፡ ዛሬም ገዳማውያን እናቶችና አባቶቻችን የኃጢአት እቶን፣ የስጋ ፈተና፣ የዲያብሎስ ውጊያ በበረታቸው ጊዜ የሚረዳቸው በመከራቸው ሁሉ ጽናት የሚሰጣቸው እርሱ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ነው፡፡ እነርሱም በጸሎታቸው ሰዓት ሁሉ ተግተው ይጠሩታል፡፡ የጸሎታቸው በረከት ተካፋይ እንድንሆን ገዳማቸውን እንደግፍ በዓታቸውን እናጽና፡፡

ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444

የጥገና ሥራ ለማከናወን የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዛሬ ጥቅምት  19 ቀን 2018 ዓ.ም የጥገና ስራ ለማከናወን በአዲስ አበባ እና ሸገር ከተማ አንዳንድ አካ...
29/10/2025

የጥገና ሥራ ለማከናወን የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዛሬ ጥቅምት 19 ቀን 2018 ዓ.ም የጥገና ስራ ለማከናወን በአዲስ አበባ እና ሸገር ከተማ አንዳንድ አካባቢዎች ላይ ኃይል የሚቋረጥባቸው አካባቢዎችን ይፋ አድርጓል

👉ከጠዋቱ 2፡30 እስከ ቀኑ 9፡30 በመሳለሚያ፣አማኑኤል ቤተክርስትያን እስከ ኮካ፣ ፍሊንት ስቶን አካባቢ፣ ጎሮ ሚካኤል፣ ቡልቡላ ሙሉውን፣ ሳሪስ አቦ አካባቢ፣ ቡልቡላ ማርያም ማዞሪያ፣ በቦሌ ሚካኤል፣ ሩዋንዳ፣ ቦሌ ሚኪ ካፌ፣ ቡልቡላ ሸክላ ቤቶች፣ አየር ማረፊያ ራዳር፣ ጊዮርጊስ ቤ/ክ፣ የቻይናዎች ከሬሸር፣ ገስላ ሰፈር አካባቢ

👉ከጠዋቱ 3፡00 እስከ ቀኑ 9፡30 በለገጣፎ ከተማ፣ ለገዳዲ፣ ኤሞሌስ ፋብሪካ፣ ካሰዴ፣ ጣፎ፣ 44 ማዞሪያ ፣ ሰንዳፋ ጫፍ እና አካባቢው ላይ የኃይል አቅርቦት ይቋረጣል፡፡

ስለሆነም በጠቀሱት አካባቢዎች የሚገኙ ደንበኞች የጥገና ሥራው ተጠናቆ የኃይል አቅርቦቱ እስኪመለስ ድረስ በትዕግስት እንድትጠብቁ አሳስቧል

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት

ዶክተር ጌታቸው ተድላ ሁለት መፅሐፍትን ቅዳሜ ያስመርቃሉጥቅምት 22 ቀን 2018 ዓ.ም በዶክተር ጌታቸው ተድላ አበበ የተጻፉ 2 መጽሐፍት ይመረቃሉ፡፡ በዓለም ሲኒማ ከጠዋቱ 2:00 ሰዓት ጀም...
29/10/2025

ዶክተር ጌታቸው ተድላ ሁለት መፅሐፍትን ቅዳሜ ያስመርቃሉ

ጥቅምት 22 ቀን 2018 ዓ.ም በዶክተር ጌታቸው ተድላ አበበ የተጻፉ 2 መጽሐፍት ይመረቃሉ፡፡ በዓለም ሲኒማ ከጠዋቱ 2:00 ሰዓት ጀምሮ በሚደረገው የምረቃ መርሀ- ግብር ልዩ ልዩ እንግዶች ይታደማሉ።

የመጀመሪያው መጽሐፍ የወይዘሮ “አበበች” ቶላ ሲሆን፣ ይህች በጎ አድራጊ ሴት በየቀኑ ከ60 እስከ 80 የሚደርሱ የጎዳና ተዳዳሪዎች ትመግባለች፡፡ የምትመግበውም ልዩ ልዩ የአዲስ አበባ ጎዳናዎች እየተዘዋወረች ነው፡፡ ዝክር በሚሆንበት ወቅት፣ ከ100 እስከ 200 ሰዎችን ታበላለች፡፡ በሽተኞችን ከየጎዳናውና ከየጎጆው እያነሳች ሐኪም ቤት በመውሰድ ታሳክማቸዋለች፡፡ የጎዳና ኑሮ አስመርሯቸው ወደ ቤተሰቦቻቸው ለመመለስ የሚፈልጉትን አጥባና አልብሳ፣ የኪስ ገንዘብ ሰጥታ በአውቶቡስ ወደየመጡበት ክፍለ ሀገር ትሸኛቸዋለች፡፡ የእዚህች በጎ አድራጊ ሴት ታሪክ ታፍኖ እንዳይቀር፣ ደራሲ ዶክተር ጌታቸው ተድላ መነበብ ያለበትን የሕይወቷን ታሪክ ዘክረውልናል፡፡

ይህን መፅሐፍ ከዶክተር ጌታቸው ተድላ ጋር በመሆን ያዘጋጀችው ጋዜጠኛ ቤርሳቤህ ጌቴ ስትሆን እርሷም ከዚህ ቀደም 4 መፅሐፍትን ለአንባቢያን ያቀረበች ናት።

በጋዜጠኝነት ላለፉት 14 ዓመታት ያገለገለችው ቤርሳቤህ ጌቴ የቴሌቪዥን ፣የሬድዮ ፕሮዳክሽን እንዲሁም መፅሔቶች በማዘጋጀት የምትታወቅ ባለሙያ ነች።

ሁለተኛው መጽሐፍ - “እጅ የማትሰጥ ነፍስ” ተብሎ የተሰየመ ግለ- ታሪክ ሲሆን፣ አንድ ወጣት በደርግ ዘመነ መንግሥት፣ ከ11ኛ ክፍል ታፍሶ የብሔራዊ ውትድርና ምልምል ሆኖ ወደ ደዴሳ ተወሰደ፡፡ ሦስት ዓመት ሠልጥኖ ሊመረቅና ሊሠናበት ሲደርስ፣ ወደ ጦርነት እንደሚላኩ ሲነገር፣ ከሁለት ጓደኞቹ ጋር ጠፍተው በእግራቸው አዲስ አበባ መመለሳቸውን ያወሳል፡፡ እዚያም ያልተስማማው ወጣት በሚያስገርምና በማያዳፍር ሁኔታ ወደ አሜሪካን መጓዙን ያወጋል፡፡ አሜሪካን ሀገርም እንዳሰበው ሳይሆን ብዙ ጭንቀት፣ ብዙ ጊዜ ዘብጥያ መውረድ አጋጥሞት፣ ያንን ሁሉ ትግል፣ ያንን ሁሉ ጭንቀት እጅ አልሰጥም ብሎ እንዳመጣጡ አሳልፎ፣ ከፍተኛ ከሚባል ኑሮ እንደደረሰ ዶክተር ጌታቸው ተድላ ይህንን ልብ አንጠልጣይ ታሪክ አውግተውናል፡፡

ይህን መፅሐፍ ከዶክተር ጌታቸው ተድላ ጋር በመሆን ያዘጋጀው ታምሩ ጎንቼ ቢልልኝ ሲሆን ባለፉት 30 ዓመታት በሥነ-ፅሑፍ እና በሚድያ ሥራ ላይ ያሳለፈ ነው።

የመፅሀፉ ዋና ደራሲና አሳታሚ በመሆን ትልቁን ሚና የተጫወቱት ዶክተር ጌታቸው ተድላ አበበ ባለፉት 18 ዓመታት ከ 17 በላይ መፅሐፍትን አዘጋጅተው ለህትመት ያበቁ ሲሆን በሙያም የግብርና ኢኮኖሚስትና ደራሲ ናቸው።

ለረጅም ዓመታት በስዊድን አገር የኖሩት ዶክተር ጌታቸው ተድላ ከ2000 ሚሊኒየም በኃላ ሙሉ ጊዜያቸውን ለድርሰት ሥራ በመስጠት ፣የራሳቸውንም ግለ-ታሪክ በሁለት መፅሐፍ ማስነበብ የቻሉ ሰው ናቸው።

ቅዳሜ መፅሐፎቹ ሲመረቁ የባለታሪኮቹ ቤተሰቦች እና ተጋባዥ እንግዶች እንደሚታደሙ ለማወቅ ተችሏል።

ኮኬት ኢንቨስትመንት ኢንተርናሸ‍ናል ሞዴል ሌንሳ ጥላሁንን ከአሜሪካን ሃገር በማስመጣት ብራንድ አምባሳደር አድርጎ ሾመ ። ‎‎ሞዴል ሌንሳ ጥላሁን ነዋሪነቷን በአሜሪካን ሃገር ያደረገች ትውልደ...
28/10/2025

ኮኬት ኢንቨስትመንት ኢንተርናሸ‍ናል ሞዴል ሌንሳ ጥላሁንን ከአሜሪካን ሃገር በማስመጣት ብራንድ አምባሳደር አድርጎ ሾመ ።

‎ሞዴል ሌንሳ ጥላሁን ነዋሪነቷን በአሜሪካን ሃገር ያደረገች ትውልደ ኢትዮጵያዊት የቢዝነስ ሰው ስትሆን ከዚህ ቀደም በሚስ ኢትዮጵያ ውድድር ሶስተኛ ደረጃን ይዛ ያጠናቀቀች ሲሆን የሚስ ኦሮሚያ የቁንጂና ውድድርን ደግሞ በአንደኝነት በማሸነፍ ሃገሯን በአለም አደባባይ ያስጠራች ኢንተርናሽናል ሞዴል ናት ።

‎ ኮኬት ኢንቨስትመንት እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር በ2020 የተቋቋመ ሲሆን በዋነኛነት በሶፍት ዌር ኢንጂነሪንግ ፣ በሶፍት ዌር ማበልፀግና ለተቋማት ማቅረብ ፣ በኮንስትራክሽን እና በኢንቴሪየር ዲዛይ ስራ ላይ የተሰማራ ሃገር በቀል ድርጂት ነው ።

‎ ኮኬት ኢንቨስትመንት ኢንተርናሽናል ሞዴል ሌንሳ ጥላሁንን ብራንድ አምባሳደር አድርጎ የሾማት ድርጂቱ የሚሰጠውን አገልግሎት በአለም አቀፍ ደረጃ ለማስተዋወቅና ተደራሽ ለማድረግ ሞዴል ሌንሳ አሜሪካንን ጨምሮ በተለያዮ የአለም ሃገራት ካካበተችው አለም አቀፍ እውቅናና የስራ ተነሳሽነት እንደዚሁም ኮኬት በቀጣይ አለማቀፍ የቢዝነስ ሰዎች ጋር ለሚያደርገው ግንኙነት ራዕዮን እውን ከማድረግ አኳያ ስኬታማ ተግባራትን እንደምታከናውን በማመን መሆኑን የኮኬት ኢንቨስትመንት ዋና ስራ አስፈፃሚ ዋሲሁን ተፈራ ገልፀዋል ።

‎ ኢንተርናሽናል ሞዴል ሌንሳ ጥላሁን የኮኬት ብራንድ አምባሳደር ለመሆን 15 ሚሊየን ብር የተከፈላት ሲሆን ኮኬት ኢንቨስትመንት ከሃገር አልፎ በተለያዮ የአለም ሃገራት ለሚያደርገው የንግድ እና የተለያዮ አገልግሎቶች እንቅስቃሴ የተቋሙን ርዕይ እውን ለማድረግ እንደምትሰራ ቃል ገብታለች ።

ብሔራዊ የቲቢ ጥምረት ተመሰረተበአለማችን ላይ በገዳይነታቸው ከፍተኛ ከሚባሉ በሽታዎች አንዱ የሆነው የቲቢ በሽታ በየጊዜው ስርጭቱን እየጨመረ አሳሳቢነቱም ከዕለት ዕለት እያደገ ይገኛል። እንደ...
28/10/2025

ብሔራዊ የቲቢ ጥምረት ተመሰረተ

በአለማችን ላይ በገዳይነታቸው ከፍተኛ ከሚባሉ በሽታዎች አንዱ የሆነው የቲቢ በሽታ በየጊዜው ስርጭቱን እየጨመረ አሳሳቢነቱም ከዕለት ዕለት እያደገ ይገኛል። እንደ አለም አቀፉ የጤና ድርጅት በኢትዮጵያ በዜጎች ላይ እስከ ሞት ከሚያደርሱ በሽታዎች ዝርዝር ውስጥ በቀዳሚነት ካስቀመጣቸው ተላላፊ በሽታዎች መካከል አንዱ የቲቢ በሽታ ነው። በአሁኑ ወቅት ባለው ሪፖርት በኢትዮጵያ ከ19ሺህ በላይ ዜጎች በቲቢ በሽታ ይሞታሉ ስለሆነም ይህንን በዜጎች ላይ ከፍተኛ ጉዳት በማድረስ ላይ የሚገኘውን በሽታ ከተቻለ ከሀገራችን ማጥፋት ካልተቻለም የሚያደርሰውን ጉዳት መቀነስ ይቻል ዘንድ የሁሉንም ርብርብ ይፈልጋል። ይህንንም ጥረት ማሳካት የሚችል ብሔራዊ የቲቢ ጥምረት በላቭ ኢን አክሽን ኢትዮጵያ እና በጤና ሚንስቴር ትብብር በግሎባል ፈንድ ደጋፊነት በአዲስ አበባ ሳሬም ሆቴል የተለያዩ በቲቢ በሽታ ላይ በሀገራችን የሚሰሩ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች በተገኙበት ተመስርቷል።

ጥምረቱ በሽታው በሀገራችን በሚገኙ ዜጎች ላይ የሚያደርሰውን ጉዳት ከመከላከል ባሻገር በጋራ በትብብር ለመስራት መደላድልን የሚፈጥር መሆኑን የገለፁት በጤና ሚኒስቴር የቲቢ የስጋ ደዌና የሳንባ በሽታ መከላከልና መቆጣጠር ዴስክ ኃላፊ የሆኑት አቶ ታዬ ለታ ለጥምረቱ ምስረታ መሳካት አስተዋፅኦ ለነበራቸው አካላት ምስጋናቸውን አቅርበው በቀጣይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከጥምረቱ ጎን በመሆን አስፈላጊውን ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል።

ላቭ ኢን አክሽን ኢትዮጵያ ከግሎባል ፈንድ በተገኘ ድጋፍ ከጤና ሚንስቴር ጋር በመተባበር የቲቢ በሽታን በመከላከል ረገድ የማህበረሰቡን ግንዛቤ ማሳደግ የሚችሉ የተለያዩ ስራዎችን እየሰራ የሚገኝ ሲሆን ይህን ጥምረት ለማሳካት ከዚህ ቀደም በርካታ ጥረቶች ቢደረጉም ባለመሳካቱ ከፍተኛ ቁጭት ውስጥ መሆናቸውን የገለፁት የምስረታው ተሳታፊዎችና መስራቾች ዛሬ ምስረታው እውን ሆኖ በማየታቸው፤ በሽታው እያደረሰ ያለውን ጉዳት ለመከላከል ያላቸውን እምነትና ተስፋ እንደጨመረላቸው ተናግረዋል።

ከንቲባ አዳነች አቤቤ - ስለሰቃዮቹ ተማሪዎች!..ዛሬ በ2017 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከ500 በላይ ውጤት ካስመዘገቡ 1321 ተማሪዎች መካከል ከፍተኛ ውጤት ላመጡ 3...
28/10/2025

ከንቲባ አዳነች አቤቤ - ስለሰቃዮቹ ተማሪዎች!..

ዛሬ በ2017 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከ500 በላይ ውጤት ካስመዘገቡ 1321 ተማሪዎች መካከል ከፍተኛ ውጤት ላመጡ 336 ተማሪዎች እውቅና ሰጥተን አበረታተናል።

በ2016 የትምህት ዘመን የ12ኛ መልቀቂያ ፈተና ከወሰዱት ውስጥ ያለፋት 21.3 በመቶ ሲሆኑ በ2017 ወደ 31 በመቶ አድጓል፤ እንዲሁም እንደ ሀገር 100 ፐርሰንት ካሳለፉ 50 ትምህርት ቤቶች መካከል 17ቱ በከተማ አስተዳደራችን ስር የሚገኙ ትምህርት ቤቶች ናቸው።

በተጨማሪም ሁለት አዳሪ ትምህርት ቤቶች 100 ፐርሰንት ማሳለፍ መቻላቸው የስራችን ውጤታማነት ማሳያ ነው።

በተለይም ዛሬ የማበረታቻ ሽልማት ከሰጠናቸው መካከል አይነ ስውራን እና መስማት የተሳናቸው ተማሪዎቻችን ለገጠማቸው የአካል ጉዳት ፈተና እጅ ሳይሰጡ ላስመዘገቡት ከፍተኛ ውጤት ትልቅ ክብር አለኝ ።

የዩኒቨርስቲ መግቢያ ውጤት ያስመዘገባችሁ ውድ ተማሪዎቻችን በዩኒቨርሲቲዎቹ የሚኖራችሁ ቆይታ የበለጠ እውቀት የምትቀስሙበት፣ ለአገር ለወገን የሚጠቅም ክህሎት ይዛችሁ የምትወጡበት እንዲሆን እመኛለሁ።

ፈጣሪ ኢትዮዽያን እና ሕዝቦቿን ይባርክ

ኢንፊኒክስ ኢትዮጵያ እና የአዲስ አበባ ተግባረ ዕድ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በጋራ ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙኢንፊኒክስ ኢትዮጵያ እና የአዲስ አበባ ተግባረ ዕድ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ወጣቱን...
28/10/2025

ኢንፊኒክስ ኢትዮጵያ እና የአዲስ አበባ ተግባረ ዕድ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በጋራ ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ

ኢንፊኒክስ ኢትዮጵያ እና የአዲስ አበባ ተግባረ ዕድ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ወጣቱን በቴከኖሎጂ ዘርፍ ለመደገፍ እና አብሮ ለመስራት የሚያስችለውን የመግባቢያ ስምምነት በዛሬው እለት ተፈራርመዋል።

ስምምነቱ የኢንፊኒከስ ኢትዮጵያ ወላጅ ኩባንያ የሆነው ትራንስሽን ማኑፋክቸሪንግ ኃ.የተ.የግ.ማ እና የአዲስ አበባ ተግባረ ዕድ ፖሊ ቴከኒክ ኮሌጅ በኢትዮጵያ የቴከኖሎጂ ትምህርት፣ ፈጠራ እና የወጣቶችን ማጎልበት ትብብርን ለማሳደግ እንደሆነ ተገልጿል

ከስምምነቱ ጎን ለጎን ደንበኞችን ከተለያዩ የኢንፊኒክስ ምርቶች ጋር ለማስተዋወቅ እና በአዲሶቹ ቴከኖሎጂዎች የተግባር ልምድ ለማቅረብ ያለመው 6ኛውን የኢንፊኒክስ ቀንን አክብሯል።

በዚህም በብራንዱ ዲጂታል መድረኮች ላይ ለተደረጉ ለተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ ውድድሮች አሸናፊዎችም ሽልማቶችን አበርከቷል።

የመግባቢያ ስምምነቱ የኢንፊኒክስ ከለብን በተግባረ ዕድ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የሚያቋቁም ሲሆን ይህም ለተማሪዎች ለተግባራዊ የኢንዱስትሪ ልምድ፣ ለክህሎት ግንባታ እና ለፈጠራ ፍለጋ እድሎችን ይፈጥራል ተብሏል።

ስምምነቱ ለተማሪዎች ከሚሰጠው ጥቅም ውስጥ ተማሪዎች በግል እና ሙያዊ እድገት ላይ ያተኮሩ ወርክሾፖች እና የማማከር ፕሮግራሞች ውስጥ ይሳተፉሉ ፣ በኢንፊኒከስ እና ትራንሽን ባለሙያዎች መምሪያ የፈጠራ ተነሳሽ ትምህርት ይሳተፉሉ ፣በትራንሽን እና ኢንፊኒክስ ውስጥ የስራ ዕድል ወይም ስራ በተማሪ መልኩ እድል ማግኘት ይችላሉ እንዲሁም መምህራን የቴክኖሎጂ ስልጠና ያገኛሉ፣ ይህም ትምህርታቸው ከአዳዲስ የኢንዱስትሪ አዝማሚያዎች እና ልምዶች ጋር ወቅታዊ መሆኑን እንደሚያረጋግጥ ተገልጿል።

የአዲስ አበባ ተግባረ ዕድ ፖሊ ቴከኒከ ኮሌጅ ዲን አቶ ተስፋዬ አድማሱ ይህ የመግባቢያ ስምምነት ወጣቶችን በትምህርት፣ በፈጠራ እና በቴክኖሎጂ የማበረታታት የጋራ ግብን ያካትታል ብለዋል፡፡

ትራንሽን ማኑፋክቸሪንግ ኃ.የተ.የግ.ማ በመወከል የፕላትፎርም ዳይሬክተር የሆኑት Mር Guo ZhongLei ኩባንያው በችሎታ እና በትምህርት ላይ ኢንቨስት ለማድረግ ያለውን ቁርጠኝነት አጉልቶ እያሳየ እንደሚገኝ ገለጸዋል

በትራንስሽን ማኑፋክቸሪንግ ኃ.የተ.የግ.ማ ባለቤትነት የተያዘው ኢንፊኒክስ የስማርትፎን ብራንድ እ.ኤ.አ. በ 2011 በኢትዮጵያ ከተመሰረተበት ጊዜ አንስቶ በሺዎች የሚቆጠሩ የስራ እድሎችን መፍጠሩ ተነግሯል
#ድሬትዩብ

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when DireTube posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to DireTube:

Share

Our Story

DireTube is the Largest Ethiopian News & Video Platform. It has particularly proven its value when it comes to keeping the worldwide Ethiopian Diaspora connected to their home country.

In many parts of the world Ethiopians do not have direct access to Ethiopian news and entertainment, therefore, DireTube becomes their primary source for these. For this reason DireTube is now one of the most popular Ethiopian websites on the internet.