DireTube

DireTube DireTube.com is the #1 Ethiopian Video Sharing Site. DireTube is an Ethiopian media and entertainment website founded on October 26, 2008.

 #ላለው ሁሉ ይሰጡታልና፤ ይጨምሩለታልም፤ ለሌለው ግንየዐቢይ ጾም ስድስተኛ ሰንበት ገብር ሔር ወይም ቸር አገልጋይ የተሰኘው ሲሆን ይህንን ስያሜ ያገኘበትም ምክንያት ከዋዜማው ጀምሮ የሚዘመረ...
30/03/2025

#ላለው ሁሉ ይሰጡታልና፤ ይጨምሩለታልም፤ ለሌለው ግን

የዐቢይ ጾም ስድስተኛ ሰንበት ገብር ሔር ወይም ቸር አገልጋይ የተሰኘው ሲሆን ይህንን ስያሜ ያገኘበትም ምክንያት ከዋዜማው ጀምሮ የሚዘመረው ጾመ ድጓ “ጌታውን ያስደሰተው አገልጋይ ታማኝና ቸር አገልጋይ ነው፡፡” ገብር ሔር በጎ አገልጋይ ማለት ሲሆን የስያሜውን መነሻ የምናገኘው በዕለቱ ሥርዓተ ቅዳሴ ከሚነበበው የወንጌል ክፍል ማቴ.25-14-30 ነው፡፡ በዚህ ሳምንት ለሰው ሁሉ የማገልገያ ጸጋ መሰጠቱን፣ ሰጪው እግዚአብሔር አምላክ መሆኑን፣ ቅን አገልጋዮች ስለሚቀበሉት ዋጋ፣ ሰነፍ አገልጋዮች ስለሚጠብቃቸው ፍርድ ይሰበካል፡፡ መዝሙረ 39÷8 “አምላኬ ሆይ፣ ፈቃድህን ለማድረግ መከርሁ ሕግህም በልቤ ውስጥ ነው። በታላቅ ጉባኤ ጽድቅህን አወራሁ። በዜማ ይባላል፡፡

መንገድ እንደሚሄድ አገልጋዮቹንም ጠርቶ ሊያተርፉበት ገንዘቡን እንደ ሰጣቸው ሰው እንዲሁ ይሆናልና፡፡ ለእያንዳንዱ እንደ ችሎታው ለአንዱ አምስት÷ ለአንዱ ሁለት÷ ለአንዱም አንድ ሰጠና ወዲያውኑ ሄደ፡፡ ያ አምስት መክሊት የተቀበለውም ሄደ፤ ነግዶም ሌላ አምስት መክሊት አተረፈ፡፡ ሁለት የተቀበለውም ሌላ ሁለት አተረፈ፡፡ አንድ መክሊት የተቀበለው ግን ሄዶ ምድርን ቈፈረና የጌታዉን ወርቅ ቀበረ፡፡ ከብዙ ጊዜም በኋላ የእነዚያ አገልጋዮች ጌታ ተመልሶ ተቈጣጠራቸው፡፡ አምስት መክሊት የተቀበለውም ቀረበና አቤቱ አምስት መክሊት ሰጥተኸኝ ነበር፤ እነሆ ሌላ አምስት አተረፍሁ ብሎ አምስት መክሊት አስረከበ፡፡ ጌታውም አንተ የታመንህ በጎ አገልጋይ በጥቂት የታመንህ ስለ ሆንህ በብዙ እሾምሃለሁ፤ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ አለው፡፡ ሁለት መክሊት የተቀበለውም አቤቱ ሁለት መክሊትን ሰጥተኸኝ አልነበረምን? እነሆ ሌላ ሁለት መክሊትን አተረፈሁ አለ፡፡ ጌታውም አንተ የታመንህ በጎ አገልጋይ በጥቂቱ የታመንህ ስለ ሆንህ በብዙ አሾምሃለሁ፤ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ አለው፡፡

አንድ መክሊት የተቀበለውም መጣና እንዲህ አለ፡- አቤቱ÷ አንተ ካልዘራህበት የምታጭድ÷ ካልበተንህበትም የምትሰበስብ ጨካኝ ሰው እንደ ሆንህ አውቃለሁ፤ ስለ ፈራሁም ሄድሁና መክሊትህን በምድር ውስጥ ቀበርሁ፤ እንግዲህ እነሆ÷ መክሊትህ፡፡ ጌታውም መልሶ አለው፡- አንተ ክፉና ሰነፍ አገልጋይ÷ እኔ ካልዘራሁበት የማጭድ÷ ካልበተንሁበትም የምሰበስብ ጨካኝ ሰው እንደ ሆንሁ ታውቃለህን? ገንዘቤን ለለዋጮች መስጠት በተገባህ ነበር፤ እኔም ራሴ መጥቼ ገንዘቤን ከትርፉ ጋር በወሰድሁ ነበር፡፡ ከዚያ የቆሙትንም እንዲህ አላቸው፤ ይህን መክሊት ከእርሱ ተቀብላችሁ ዐሥር መክሊት ላለው ስጡት፡፡ ላለው ሁሉ ይሰጡታልና፤ ይጨምሩለታልም፤ ለሌለው ግን ያንኑ ያለውን ይወስዱበታል፡፡

ክፉውን አገልጋይ ግን÷ ልቅሶና ጥርስ ማፋጨት ወዳለበት በውጭ ወደ አለ ጨለማ አውጡት፡፡ የመክሊቱ ባለቤት አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፤ ባለ አምስት፤ ባለ ሁለትና ባለ አንድ መክሊት የተቀበሉት በጥምቀት ጸጋ መንፈስ ቅዱስን የተቀበሉ፤ተምረው የሚያስተምሩ መምህራን ናቸው፡፡ የስጦታው መለያየት መበላለጥን ለማሳየት ሳይሆን የአንዱ ጸጋ ከሌላው እንደሚለይ የሚያጠይቅ ነው፡፡ ባለ አንድ መክሊት የተባለው ዐላውያን ነገሥታት፤ ዐላውያን መኳንንት እሳት ስለት አሳይተው ቢያስክዱኝ፣መናፍቃን ተከራክረው ቢረቱኝ፣ ምላሽ ቢያሳጡኝ፣ ሃይማኖቴን ቢያስቱኝ ብሎ ከማገልገል ይልቅ ሃይማኖቱን የማያስተምርና የማይመሰክር ነው፡፡ ትልቁ ጥያቄ የኛ መክሊት የተሰጠን ጸጋ ምን ተሰራበት የሚለው ነው፡፡

በገዳማዊ ኑሮ ያሉትን እየረዳንና በዓታቸውን እያጸናን የበረከታቸው ተሳታፊ እንሁን፡፡

ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444

30/03/2025

በብሩህ እናት ሀገር አቀፍ የሴቶች የቢዝነስ ሥራ ፈጠራ ውድድር የ 500 ሺ ብር ተሸላሚ የሆነችው ሉሊት ሰሙንጉስ ስለ ውድድሩ ሂደት፣ ስለ ፈጠራ ስራዋ፣ ስለ እናት ባንክና አጋሮቹ እንዲሁም ስለ ቀጣይ ዕቅዷ ይህን ብላለች።

ቪዲዮውን ይመልከቱ!...

1 ሺህ 446ኛው የዒድ አልፈጥር በዓል አከባበር በአዲስ አበባ ከተማ!..
30/03/2025

1 ሺህ 446ኛው የዒድ አልፈጥር በዓል አከባበር በአዲስ አበባ ከተማ!..

30/03/2025

"መዝገበ አእምሮ" - በቅርብ ቀን!...

ውድ ደንበኞቻችን!..እንኳን ለ1446ኛው የኢድ አል-ፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁኢድ ሙባረክ!..በፋስትፔይ 1 ዶላር በ 136 ብር ወደሀገር ቤት በነፃ ይላኩ!!!ፋስትፔይ ኢቲፈጣን የመላኪያ...
30/03/2025

ውድ ደንበኞቻችን!..

እንኳን ለ1446ኛው የኢድ አል-ፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ
ኢድ ሙባረክ!..

በፋስትፔይ 1 ዶላር በ 136 ብር ወደሀገር ቤት በነፃ ይላኩ!!!

ፋስትፔይ ኢቲ
ፈጣን የመላኪያ መንገድ

የድሬደዋ ከንቲባ ከድር ጁሃር ለመላ የእስልምና እምነት ተከታዮች የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ***ከወራቶች ሁሉ ቅዱስ የሆነው የኢባዳ፥ የመተዛዘን እና የአብሮነት ታላቅ ወር ረመዷ...
29/03/2025

የድሬደዋ ከንቲባ ከድር ጁሃር ለመላ የእስልምና እምነት ተከታዮች የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ

***

ከወራቶች ሁሉ ቅዱስ የሆነው የኢባዳ፥ የመተዛዘን እና የአብሮነት ታላቅ ወር ረመዷን ተጠናቆ የሸዋል ወር አንድ ሲል፥ በጾም እና በፀሎት ወሩን ያሳለፍን ሁሉ የተቸገሩ ወገኖችን በማሰብ የዒደል ፊጥር በዓልን በደስታ ልናሳልፍ፥ በአላህ ፈቃድ ለዋዜማው ስለደረስን እንኳን ደስ አለን ብለዋል።

ባሳለፍነው ወር የተቸገሩ ወገኖችን በማሰብ፣ በመጠየቅ እና በመዘየር፥ በተለይ ደግሞ ከክርስትና እምነት ተከታይ ወገኖቻችን ጋር በነበረን የአብሮነት ኢፍጣር፥ የእኛ የድሬዎችን የፍቅር ውብ እሴቶች አድምቀን ባሳለፍንባቸው ቀናት ያገኘነው ደስታ ወደር የለውም ሲሉም መልዐክት አስተላልፈዋል።

በረመዳን ጾም ያገኘነውን ይህንን ደስታ፥ በነገዋ የኢደል ወሳኝ ቀን ለተቸገሩ ወገኖች በመድረስ መድገም እና አብሮነታችንን በተግባር ማሳየት ይገባናል እያልኩኝ፥ 1446ኛው የዒደል ፊጥር በዓል የሰላም፥ የፍቅርና የመተሳሰብ እንዲሆንልን ከልብ እመኛለሁ ብለዋል።

መጋቢት 20/2017
(ኢ ፕ ድ)

29/03/2025

የሰውን ልጅ ለማዳን በደካማ ስጋ ቢወለድ 40 ቀንና 40 ሌሊት ከጾመ በኋላ ተራበ፣ በእጅጉም ተፈተነ።

በዚህ ውስጥ ጾምና ፀሎት የጠላታችን ድል መንሻ መሆኑን አሳዬን፤ ትህትና፣ ፍቅርን ፣የበዛ ፍቅረ- ንዋይን ቀንሶ ለተቸገሩት ማካፈልን በተግባር አስተማረን።

እኛም በተለይም በዚህ የአብይ ጾም ወቅት የተቸገሩ ገዳማዊያንን በማገዝ የበረከት ስራን እንድንሰራ ጥሪ ቀርቦልናል፤

እርስዎም የበረከቱ ተካፋይ ይሁኑ።
ገዳማዊያኑን እንደግፍ ለነፍሳችንም ስንቅን እንያዝ!

ድጋፍ ለማድረግ:-የቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ለበለጠ መረጃ:-0938644444

ለተሽከርካሪ ዝግ የሚኾኑ መንገዶች!..1446ኛው የኢድ አልፈጥር ረመዳን ክብረ በዓል ጋር ተያይዞ የኢድ ሶላት ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ በአዲስ አበባ ከተማ የተወሰኑ መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ ...
29/03/2025

ለተሽከርካሪ ዝግ የሚኾኑ መንገዶች!..

1446ኛው የኢድ አልፈጥር ረመዳን ክብረ በዓል ጋር ተያይዞ የኢድ ሶላት ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ በአዲስ አበባ ከተማ የተወሰኑ መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ እንደሚሆኑ የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ፡፡
***
ነገ መጋቢት 21 ቀን 2017 ዓ/ም የሚከበረውን 1446ኛውን የኢድ አልፈጥር ረመዳን በዓል ያለ ምንም የጸጥታ ችግር እንዲከበር የጸጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል ቅድመ ዝግጅቱን አጠናቆ ወደ ስራ መግባቱ የሚታወስ ሲሆን በዓሉን ምክንያት በማድረግ በአዲስ አበባ የሚከናወነው የኢድ ሶላት ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ የተወሰኑ መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ ይሆናሉ፡፡

በመሆኑም የትራፊክ መጨናነቅ እንዳይፈጠር አሽከርካሪዎች ከዚህ በታች የተገለፁት መንገዶች ዝግ መሆናቸውን ተገንዝበው ሌሎች አማራጮችን እንዲጠቀሙም የአዲስ አበባ ፖሊስ አሳስቧል፡፡

በዚህም መሰረት፡-
👉 ከመገናኛ በ22 አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ ለሚመጡ ተሽከርካሪዎች ቅዱስ ዑራኤል አደባባይ በተመሳሳይ ከቦሌ አካባቢ በአትላስ መብራት ወደ ቅዱስ ዑራኤል አደባባይ ለሚሄዱ አትላስ መብራት እና ፒኮኪ መብራት ላይ፣
👉 ከቦሌ ወሎ ሠፈር መታጠፊያ ወደ ኦሎምፒያ አደባባይ ለሚሔዱ አሽከርካሪዎች ኦሎምፒያ አደባባይ ላይ፣
👉 ከወሎ ሠፈር ጀምሮ እስከ ጋዜቦ አደባባይ ውስጥ ውስጡን ወደ ዋናው መንገድ የሚያስወጡት መንገዶች ዝግ የሚደረጉ ይሆናል፣
👉 ከአጎና መስቀለኛ ወደ ጥላሁን አደባባይ -ሳንጆሴፍ መብራት አጎና ሲኒማ መስቀለኛ ላይ፣
👉 ከቡልጋሪያ መብራት ወደ ገነት ሆቴል ሜክሲኮ አደባባይ ለሚሄዱ አሽከርካሪዎች ቡልጋሪያ መብራት ላይ፣
👉 ከቅድስት ልደታ ፀበል በAU ቅዱስ ሚካኤል መታጠፊያ ወደ ወደ ሜክሲኮ አደባባይ AU ሚካኤል መታጠፊያ፣
👉 ከጦር ኃይሎች በከፍተኛ ፍ/ቤት ወደ ሜክሲኮ አደባባይ ለሚሔዱ ከፍተኛ ፍ/ቤት አደባባይ ላይ፣
👉 ከአብነት አካባቢ በፈረሰኛ ፖሊስ መብራት ወደ ጨፌ ሜዳ መብራት ፈረሰኛ መብራት ላይ፣
👉 ከሞላ ማሩ መስቀለኛ ወደ ጌጃ ሰፈር መውረጃ ሞላ ማሩ መታጠፊያ ላይ፣
👉 ከመርካቶ አካባቢ በአቡነ ተክለ ኃይማኖት አደባባይ ወደ ጥቁር አንበሳ ለሚሄዱ አቡነ ተክለ ኃይማኖት አደባባይ ላይ ዝግ ይደረጋል።
👉 ከፒያሳ በባንኮዲሮማ መብራት ወደ ቴዎድሮስ አደባባይ ባንኮዲሮማ መብራት ላይ፣
👉 ከሲግናል አካባቢ በሴቶች አደባባይ ወደ ካዛንቺስ ለሚሄዱ ተሽከርካሪዎች ሴቶች አደባባይ ላይ ከንጋቱ 11:00 ሰዓት ጀምሮ ፕሮግራሙ እስከሚጠናቀቅ ድረስ መንገዶቹ ዝግ ይሆናሉ።

ከዚህ በተጨማሪም ዛሬ ከበዓሉ ዋዜማ ምሽት ጀምሮ በተጠቀሱት ቦታዎች ላይ ተሽከርካሪዎችን ለአጭርም ይሁን ለረጅም ሠዓት ማቆም የተከለከለ ሲሆን ህብረተሰቡም ከፖሊስ የሚሰጠውን መረጃ ተገንዝቦ የትራፊክ ፖሊስ አባላት በሚጠቁሙት አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀም እና ለትራፊክ ፖሊስ አባላት ትዕዛዝ አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርግ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጥሪውን እያስተላለፈ ለእምነቱ ተከታዮች በሙሉ በዓሉ የፍቅርና የሠላም እንዲሆን መልካም ምኞቱን ይገልፃል፡፡
ኢድ ሙባረክ

"እንኳን ለ1446ኛው የዒድ አል ፈጥር በዓል አደረሳችሁ!!" - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ “ዒድ አል ፈጥር” የረመዳን ጾምን የማጠናቀቂያ በዓል ነው፡፡ ዒድ አል ፈጥር “የምስጋና፣ የበ...
29/03/2025

"እንኳን ለ1446ኛው የዒድ አል ፈጥር በዓል አደረሳችሁ!!"
- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ

“ዒድ አል ፈጥር” የረመዳን ጾምን የማጠናቀቂያ በዓል ነው፡፡ ዒድ አል ፈጥር “የምስጋና፣ የበጎ አድራጎት እና የወንድማማችነት/እኅትማማችነት” በዓል ነው፡፡ ዒድ አል ፈጥር ከአንድ ወር የጾም ጊዜ በኋላ የሚመጣ በዓል ነው፡፡ ጾሙ የሰውን ድካም፣ ዐቅም ማነስ እና ልክ የሚያሳይ ነው፡፡ ፈጣሪ ካልደገፈው በቀር የሰው ልጅ ዐቅም ውሱን መሆኑን ያሳያል፡፡ ትዕቢት፣ ጥጋብ እና ክፋት በዚህ ደካማ ሰው ላይ መብቀላቸውን ለተመለከተ፣ የሰው ጠላቱ የገዛ ጠባዩ መሆኑን ይማራል፡፡ ሰው በዘመናት ውስጥ ሌሎችን ለመግዛት የታገለውን ያህል ራሱን ለመግዛት አልታገለም፡፡ ዛሬም በሀገራችን የምናየው ፈተና በዋናነት ራስን ካለመግዛት የሚመጣ ፈተና ነው፡፡ ራሱን የማይገዛ ሰው ዐቅሙን አያውቀውም፡፡ ወደ ውስጡ አያይም፡፡ ጠላቱን ከገዛ ጠባዩ ውስጥ ከመፈለግ ይልቅ፣ ጠላቱን ከጎረቤቱ ይፈልገዋል፡፡ በዚህ የተነሣ ከገዛ ወገኑ ጋር ሲቃረን ይኖራል፡፡ እንደ ረመዳን ዓይነት ወቅቶች ውስጥን ለመመልከት የሚጠቅሙ ናቸው፡፡

ውስጣቸውን የተመለከቱ ሰዎች ምስጋና ገንዘባቸው ነው፡፡ ሰው የራሱን ልክ ካላወቀ ሌላውን አያደንቅም፤ ሌላውን አያመሰግንም፡፡ የሌለውን ካልተረዳ ያለውን አያውቅም፤ አያደንቅም፡፡ የራሱ ጠላት የገዛ ጠባዩ መሆኑ ካልገባው፣ ሌላውን ወገኑን አያፈቅርም፡፡ ለዚህ ነው የጾሙ መጨረሻ፣ ዒድ አል ፈጥር የምስጋና በዓል የሆነው፡፡ ጾሙ ከቤተሰብ ጀምሮ እስከ ማኅበረሰብ ድረስ ራስን ገዝቶ ለመሰባሰብ ይጠቅማል፡፡ መሰባሰቡም ከስሜት የወጣ፣ ስክነትና ራስን መግዛት ያለበት ነው፡፡ ሀገራዊ ምክክራችን ይሄን ዕሴት ቢላበስ እንጠቀማለን፡፡ መነጋገሩ ብቻ አይጠቅምም፡፡ ከስሜት ወርዶ፤ በስክነት ተሞርዶ፤ ነገን ተመልክቶ - መመካከር፡፡ ያ ከሆነ እንደ ዒድ ሁሉ፣ የምክክራችን ፍጻሜው ምስጋና ይሆናል፡፡

የዒድ ሌላው ዕሴት በጎ አድራጎት ነው፡፡ ዐቅም ለሌላቸው፤ ሁኔታው ላልተሟላላቸው ወገኖች መልካምን ነገር ማድረግ፡፡ ዝምድናን፣ ዘርን ወይም እምነትን ሳይመለከቱ ሰውን በሰውነቱ ብቻ መርዳት፡፡ የጾም ምንዳዕ ሙሉ የሚሆነው በጎ አድራጎት ከተጨመረበት ነው፡፡ በጎ አድራጎት ማለት ከራስ አጉድሎ ሌላውን መሙላት ነው፡፡ እንደ ሀገር ለመቀጠልና እንደ ሕዝብ ለመተሣሠር በጎ አድራጎት እጅግ አስፈላጊ ዕሴት ነው፡፡ ራስን በሌላው ጫማ ላይ አስገብቶ ማየት፡፡ የሌላው ጉድለት ለመሙላት ሲባል የራስን ማጣት፡፡ ለምን ወገኔ ያዝናል? ለምን ወገኔ ይከፋል? ብሎ መንገብገብ፡፡

ሁላችንም የየራሳችንን ወገን ጥቅምና መብት በማስከበር ብቻ ሀገር ልንገነባ አንችልም፡፡ ትሥሥራችን ወገን ዘለል ሆኖ፣ የሌላውን ወገን ጉዳትና ፈተና መጋራት ይገባናል እንጂ፡፡ የእኔ ቤት ሲሟላ አይደለም የእርሱ ቤት የሚሟላው፡፡ የእርሱ ቤት ሲሟላ ነው የእኔ ቤት የሚሟላው፡፡ የፖለቲካ ምኅዳራችን በዚህ ነባር ዕሴታችን ላይ ካልተመሠረተ ፍትሐዊነትን እና እኩልነትን ለማስፈን እንቸገራለን፡፡

እነዚህን ሁለቱን ዕሴቶች የሚያስተሣሥረው የዒድ ዕሴት “ወንድማማችነት/እኅትማማችነት” ነው፡፡ ወንድማማችነት/ እኅትማማችነት ማለት በጋራ ዕሴቶች፣ በመተባበር እና በጋራ ግብ ላይ የተመሠረተ ወዳጅነት ነው፡፡ ይሄ ወዳጅነት በሥነ ምግባር የተገራ፣ ፍቅርንና አንዱ ለሌላው መቆምን መሠረት ያደርጋል፡፡ የጋራ ኃላፊነትን ይወስዳል፡፡ በሀገራችን የፖለቲካ ሕይወት እጅግ አስፈላጊው/ግን እጅግ የተረሳው ዕሴት ነው፡፡ መብትንም ሆነ ግዴታን በወንድማማችነት/እኅትማማችነት መነጽር መመልከት ነገሩን ለሰውነት ቅርብ ያደርገዋል፡፡ ለእኔ ከሚለው አውጥቶ ለእኛ፤ ለእኛ ከሚለውም ጭምር አውጥቶ “ለእነርሱ እና ለእኛ”፤ ለእነርሱ እና ለእኛ ከሚለውም አውጦቶ “ለእኛ ይቅርብን፤ ለእነርሱ ይደረግ “ወደሚለው የላቀ ሰብእና ያደርሰዋል፡፡

በእምነቶች፣ በፖለቲካ ፓርቲዎች፣ በማኅበረሰቦች እና በልሂቃን መካከል የተሻለውን አብሮነት የሚፈጠረው ወንድማማችነት/እኅትማማችነት ነው፡፡ የተሻለ መረዳዳት፣ የተሻለ መተዋወቅ እና የተሻለ መግባባት ይፈጥራል፡፡ ለሌላው ሲል መተዉን፤ ለሌላው ሲል መቀበልን እና ለሌላው ሲል ለበደሎች ዕውቅና መስጠትን የሚያስገኘው ዕሴት - ወንድማማችነት/እኅትማማችነት ነው፡፡ የዒድ በዓል አንዱ ዕሴት የሆነውም በዚህ የተነሣ ነው፡፡ የዒድን በዓል እነዚህን የበዓሉ ዕሴቶች እያሰብን፣ እያዳበርንና ለሀገር ግንባታ እየተጠቀም እንድናከበረው ጥሪ አቀርባለሁ፡፡ ቤተሰቦች፣ ጎረቤታሞች፣ ማኅበረሰቦች እና የእምነት አባቶች ሲሰባሰቡ እነዚህ ሦስት የዒድ ዕሴቶች ጎልተው እንዲወጡና ማኅበረሰባችን እንዲገነባባቸው እንዲያደርጉ አደራ እላለሁ፡፡
ኢድ ሙባረክ!

ኢትዮጵያ በልጆቿ ጥረት ታፍራና ተከብራ ለዘላለም ትኑር!
ፈጣሪ ኢትዮጵያና ሕዝቦቿን ይባርክ!
መጋቢት 20፣ 2017 ዓ.ም

ለ1446ኛው ዓ.ሒ የዒድ አል-ፊጥር ሶላት ወደ ዒድ-አደባባይ ሲመጡ ምዕመናን ሊከተሏቸው የሚገቡ ደንቦች🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹‼️ የዒድ ሶላት የሚሰገደው ከጠዋቱ 2:30 በአዲስ አበባ ስቴድየም በመሆኑ...
29/03/2025

ለ1446ኛው ዓ.ሒ የዒድ አል-ፊጥር ሶላት ወደ ዒድ-አደባባይ ሲመጡ ምዕመናን ሊከተሏቸው የሚገቡ ደንቦች
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
‼️ የዒድ ሶላት የሚሰገደው ከጠዋቱ 2:30 በአዲስ አበባ ስቴድየም በመሆኑ ቀደም ብሎ በቦታው መድረስ።

‼️ ከቤት ሲወጣ አፍጥሮና ካሉን አልባሳት የተሻለውን በመልበስ እንዲሁም በጀማዓ እየተኮነ ተከቢራ ማለት።

‼️ወደ ዒዱ ቦታ ሲመጣ የተወደዱ ሱና ተግባራትን መከወንና በተቻለ አቅም በመጡበት ላለመመለስ መሞከር

‼️ ለጸጥታ አካላት እና ለበጎ ፈቃደኛ አስተባባሪዎች የፍተሻ ትብብር ማድረግ።

‼️ ወደ ዒድ መስገጃ ቦታ ከመስገጃ እና ተንቀሳቃሽ ስልክ ውጪ ያሉ ቁሳቁሶችን (እስክሪብቶ፣ የጆሮ ማዳመጫ፣ ሽቶ፣ የሴቶች መዋብያ፣ ዣንጥላ፣ ወዘተ) ይዞ መግባት ስለማይቻል እነዚህን እና መሰል ንብረቶችን ይዞ አለመምጣት።

‼️ ማንኛውም ለሰጋጆቾ ደህንነት አጠራጣሪ ሁኔታዎች ከተመለከቱ ለበጎ ፈቃደኛ አስተባባሪዎችና ለጸጥታ አካላት በአፋጣኝ ማሳወቅ።

‼️ ከኢፌዴሪ ሰንደቅ አላማ ውጪ ማንኛውም አይነት ባነር፣ ህትመት ያለው ቲሸርት፣ መፈክር እና ባንዲራ ከኢዱ ጋር ተያያዥነት ስለማይኖረው አለመያዝ።

‼️ የ CAR PASS ያላቸው ተሽከርካሪ ይዘው የሚመጡ ጊዮን ሆቴል ጊቢ ውስጥ ተሽከርካሪያቸውን እንዲያቆሙ::

‼️ የ CAR PASS ካላቸው ምዕመናን ውጭ ተሽከርካሪ ይዘው የሚመጡ በአቅራቢያ ባሉ በኮሪደር ልማቱ በተሰሩ አልያም ሌሎች ምቹ በሆኑ ስፍራዎች መኪና እንዲያቆሙ::

‼️ በእለቱ ከሚከናወኑ የተክቢራ፣ የዒድ ሶላት እና ኹጥባ ውጪ ማንኛውም የዒዱን ድባብ እና ከተማችንን ሰላም ከሚያውኩ ተግባር መቆጠብ።

‼️በከተማችን የትራንስፖርት ችግር መኖሩ የሚታወቅ በመሆኑ የግል ተሽከርካሪ ይዘው የሚመጡ ለሌሎች የትራንስፖርት አገልግሎት በመስጠት ትብብር ማድረግ።

‼️ በምንጓዝበት ጎዳና እና በምንሰግድበት ቦታ ሁሉ የከተማችን የኮሪደር ልማት ውጤቶችን እና የመዲናችንን ንፅህና መጠበቅ።

ኢድ ሙባረክ
- የአዲስ አበባ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት

የኢድ አል ፈጥር በዓል ነገ ይከበራልየ1446ኛው የኢድ አል ፈጥር በዓል የሸዋል ጨረቃ በመታየቷ በነገው ዕለት እሁድ መጋቢት 21/2017 የሚውል መሆኑ ተገልጿል።- ቀደም ሲል ሀሩን ሚድያን ...
29/03/2025

የኢድ አል ፈጥር በዓል ነገ ይከበራል

የ1446ኛው የኢድ አል ፈጥር በዓል የሸዋል ጨረቃ በመታየቷ በነገው ዕለት እሁድ መጋቢት 21/2017 የሚውል መሆኑ ተገልጿል።

- ቀደም ሲል ሀሩን ሚድያን ጠቅሰን ሰኞ እንደሚውል የገለፅነው ከከፍተኛ ይቅርታ ጋር በዚህ እንዲታረም እየጠየቅን ለመላው ሙስሊም ማህበረሰብ እንኳን ለ1446ኛው የኢድ አል ፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ እንላለን።

ኢድ ሙባረክ!!

ህዝበ ሙስሊሙ የኢድ- አልፊጥር በዓልን ሲያከበር ለተቸገሩ ወገኖችን በመርዳት ሊያሳልፈው ይገባል።🔖 የጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዝዳንት ሸይኽ ሀጂ ኢብራሂም ቱፋየኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ...
29/03/2025

ህዝበ ሙስሊሙ የኢድ- አልፊጥር በዓልን ሲያከበር ለተቸገሩ ወገኖችን በመርዳት ሊያሳልፈው ይገባል።

🔖 የጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዝዳንት ሸይኽ ሀጂ ኢብራሂም ቱፋ

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የ1446ኛውን ዓ.ሂ የኢድ አል ፈጥር በዓልን አስመልክቶ ዛሬ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፏል።

የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክቱን ያስተላለፉት የጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዝዳንት ሸይኽ ሀጂ ኢብራሂም ቱፋ እንዳሉት የ1446 ኛው ዓ.ሂ የረመዳን ፆም ህዝበ ሙስሊም የተለያዩ በጎ ተግባራትን በመስራት ማሳለፉን ተናግረዋል።

የዘንድሮ የረመዳን ፆም በተለይ የአፋርና የሱማሌ ወንድም ህዝብ ከዚህ በፊት የነበረውን ቁርሾ በመተው በጋራ በህብረት ያሳለፉበት በመሆኑ የተለየ እንደሚያደርገው አንስተዋል።

በመጨረሻም ህዝበ ሙስሊሙ የኢድ አልፊጥር በዓልን ሲያከበር የተቸገሩ ወገኖችን በመርዳት እንዲሁም ፍፁም ሰለማዊ በሆነ መልኩ በዓሉ እንዲያልፍ ሁሉም ባለድርሻ አካላት የበኩላቸውን አስተዋፅኦ እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።

© ሀሩን ሚዲያ

የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ዛሬ በለነገዋ የሴቶች የተሃድሶ እና ክህሎት ማበልጸጊያ ማዕከል በ 2ኛ ዙር ስልጠና ሲወስዱ የነበሩ 380 ሰልጣኞችን አስመርቀው ወደ ስራ ማሰማራታቸ...
29/03/2025

የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ዛሬ በለነገዋ የሴቶች የተሃድሶ እና ክህሎት ማበልጸጊያ ማዕከል በ 2ኛ ዙር ስልጠና ሲወስዱ የነበሩ 380 ሰልጣኞችን አስመርቀው ወደ ስራ ማሰማራታቸውን ገለፁ።

ከንቲባዋ በማኀበራዊ ድረገፃቸው ባጋሩት መልዕክት ከአስከፊ ህይወት ወጥታችሁ ስልጠናችሁን በብቃት በማጠናቀቅ ለምርቃት የበቃችሁ እንዲሁም ወደ ስራ ለመሰማራት የተዘጋጃችሁ ልጆቻችን እና እህቶቻችን እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል።

ለነገዋ የሴቶች የተሃድሶ እና ክህሎት ማበልጸጊያ ማዕከል ለማህበራዊ፣ ለኢኮኖሚያዊ እና ለስነ ልቦና ስብራት የተጋለጡ ሴቶችን ካሉበት የህይወት ውጣ ውረድ እንዲወጡ በማድረግ፣ የስነ ልቦና ድጋፍ እና የሙያ ስልጠና በመስጠት ወደ ስራ በማሰማራት ላይ የሚገኝ ማዕከል ሲሆን በሁለተኛው ዙርም በ17 የሞያ አይነቶች የብቃት ምዘና ያለፉ 380 ሰልጣኞችን አስመርቀን የስራ እድልም እንደተፈጠረላቸውም ገልፀዋል።

አያይዘውም "ለማዕከሉ ድጋፍ በማድረግ እና የስራ እድል በመፍጠር ላይ የምትገኙ ባለሀብቶች እንዲሁም ሰልጣኞቹ በማዕከሉ በነበራቸው ቆይታ እናትም አባትም ሆናችሁ ከስልጠና በላይ የሆነ እንክብካቤ እና ፍቅር በመስጠት ከልብ ያሰለጠናችሁ፣ የተንከባከባችሁ እና ወደ ስራ ያሰማራችሁ አመራሮች እና መምህራንን በሰልጣኞቹ እና በራሴ ስም አመሰግናለሁ ማለታቸው ተዘግቧል።
(ከንቲባ ፅ/ቤት)

በመጪው እሁድ መጋቢት 21 በቴክኖ ኢትዮጵያ የቲክቶክ ገፅ የኳስ አፍቃሪያን በጉጉት የሚጠብቁት የላይቭ ስርጭት ከGhost እና Abi Eyuel ጋር እጅግ አነጋጋሪ የሆኑ የፕሪሚየር ሊግ  እና...
29/03/2025

በመጪው እሁድ መጋቢት 21 በቴክኖ ኢትዮጵያ የቲክቶክ ገፅ የኳስ አፍቃሪያን በጉጉት የሚጠብቁት የላይቭ ስርጭት ከGhost እና Abi Eyuel ጋር እጅግ አነጋጋሪ የሆኑ የፕሪሚየር ሊግ እና የቻፒያንስ ሊግ ወሬዎች፣ ባለፉት 5 አምታት ነግሶ የቆየው ክለብ ማነው?፣ ከፈርጉሰን እና ዌንገር በኋላ የድል ማማ ላይ መቆየት የቻለውስ ቡድን የትኛው ነው? በዝርዝር እናወራበታለን፡፡ በማልያ እና ሌሎች አጓጊ ሽልማቶች የሚንበሸበሹበት እሁድ ጠዋት ከ5ሰዓት ጀምሮ ከታች ያለውን ሊንክ በመጫን የቴክኖ ኢትዮጵያን ቲክ ቶክ ፔጅን ፎሎው አርገው ይጠብቁን፡

https://www.tiktok.com/?_t=ZS-8v5DAPXWGS9&_r=1

 #ሕዝቡም ሁሉ እየተመለከቱት ዘንዶውን በጦሩ ወግቶ ገደለው አባቱ ዮሐንስ ግብፃዊ ሲሆን ወደ አንጾኪያ ከሠራዊት ጋር ሄዶ አንዲት ጣዖት አምላኪ አገባ፡፡ ቅዱስ ቴዎድሮስ ከተወለደም በኋላ ወደ...
29/03/2025

#ሕዝቡም ሁሉ እየተመለከቱት ዘንዶውን በጦሩ ወግቶ ገደለው

አባቱ ዮሐንስ ግብፃዊ ሲሆን ወደ አንጾኪያ ከሠራዊት ጋር ሄዶ አንዲት ጣዖት አምላኪ አገባ፡፡ ቅዱስ ቴዎድሮስ ከተወለደም በኋላ ወደ ጣዖቷ አቅርባ አምኮቷን ልታስተምረው በፈለገች ጊዜ አባቱ ክርስትናን አስተማረው፡፡ በዚህም ምክንያት አባረረችውና ልጇን አስቀረች፡፡ ቅዱስ ቴዎድሮስም ባደገ ጊዜ ወደ እውነተኛው መንገድ ይመራው ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ዘወትር ይጸልይ ነበር፡፡ በእግዚአብሔር ፈቃድም የክርስትና ጥምቀት ሲጠመቅ እናቱ አዘነች፡፡ ሲጎለምስም ንጉሡ ዲዮቅልጥያኖስ የሠራዊቱ አለቃ አድርጎ ሾመው፡፡ ከምሥራቃዊው ቴዎድሮስ ጋር ሆነውም የፋርስን ሰዎች ወግተው ድል አደረጓቸው፡፡ የፋርስና የበርበር ሰዎችም በሮማውያን ላይ ተነሡባቸውና ብዙ ከተሞችን አጠፉ፡፡ ንጉሡ ዲዮቅልጥያኖስም በዚህ ጊዜ ፈራ፡፡ ቅዱስ ቴዎድሮስንም ጠርቶ ብሎ አዘዘው፡፡

ቴዎድሮስም የአንተን ሠራዊትና የጦር መሣርያ ይዤ አልገጥማቸውም፣ በጌታዬ በክርስቶስ ስም አሸንፋቸዋለሁ፣ አንድ የራሴ ጦርና ፈረስ ብቻ ስጠኝ አለው፡፡ ንጉሡም ጨንቆት ነበርና የወደድከውን አድርግ አለው፡፡ በማግሥቱም ቴዎድሮስ ወደ ጦርነቱ ሲወጣ ንጉሡ ዲዮቅልጥያኖስን ሠራዊቱን ይዘህ እዚሁ ቆመህ ጠብቅ እኔ በጌታዬ ኃይል የምሠራውን ታያለህ ብሎት ሄደና ከጸለየ በኋላ ጦርነቱን ብቻውን ጀመረ፡፡ ንጉሡም ከሠራዊቱ ጋር ከሩቅ ሆኖ ያየው ነበር፡፡ ቴዎድሮስ የበርበርን ሰዎች ፈረሰኛም ሆነ እግረኛ ምንም ሳያስቀር በእግዚአብሔር ኃይል አጠፋቸው፡፡ የመኳንንቶቻቸውንም ቸብቸቦ ቆርጦ ለንጉሡ አቀረበለት፡፡ የአንጾኪያ ሰዎችም የበርበርን አገር ማረኩ፡፡

አውኪስጦስ የሚባል አገር ሰዎች የሚያመልኩት፣ ርዝመቱም 24 ክንድ ለሚደርስ ታላቅ ዘንዶ በየዕለቱ ሁለት ሁለት ሴቶች ልጆችን እንዲበላቸው ይሰጡት ነበር፡፡፡ የአንዲት ክርስቲያን ሁለት ልጆችንም ወስደው ለዘንዶው አቀረቧቸው፡፡ ቅዱስ ቴዎድሮስ ወደዚያች አገር ሲደርስም እናታቸው አልቅሳ ነገረችው፡፡ ከፈረሱም ወርዶ ወደ ምሥራቅ ዞሮ ከጸለየ በኋላ ሕዝቡም ሁሉ እየተመለከቱት ዘንዶውን በጦሩ ወግቶ ገደለውና ለልጆቹን አዳናቸው፡፡ ከዚህ በኋላ ወደ ግብፅ ሄዶ አባቱን አገኘውና ተመልሶ ወደ አንጾኪያ ሲመጣ ንጉሡ ዲዮቅልጥያኖስ በክርስቶስ ማመኑን ክዶ ይልቁንም ክርስቲያኖችን ሲያሰቃይ አገኘው፡፡ የአውኪስጦስ ሰዎች ዘንዶውን ስለገደለው ከሰውት በንጉሡ ፊት አቆሙት፡፡ ንጉሡንም ስለ ባዕድ አምልኮው እጅግ አድርጎ ዘለፈው፡፡ ንጉሡም በንዴት ጽኑ ሥቃይ አሠቃየው፡፡እጆቹንና እግሮቹን ከግንድ ጋር ቸነከሩት፡፡

ቅዱስ ሚካኤልም ተገልጦለት ከቁስሉ ፈውሶት ሰማዕትነቱን በትዕግስት እንዲፈጽም በመንገር አረጋጋው፡፡ ሕዝቡም ተሰብስቦ ንጉሡን አወገዘው፡፡ ከጠላቶቻችን እጅ ያዳነንን ቴዎድሮስን የምታሰቃይ አንተ ከሀዲ ርጉም ነህ፣ በቴዎድሮስም አምላክ አምነናል ሲሉት ሁሉንም ሰየፋቸው፡፡ የብረት አልጋም አምጥቶ ቅዱስ ቴዎድሮስን በላዩ አስተኝቶ ከሥር እሳት አነደደበት፡፡ ጌታችንም ፈወሰውና በሚቀጥለው ቀን ሄዶ በንጉሡ ፊት ስለአምላኩ ክብር ሲመሰክር የጦር ሠራዊቱም ሁሉ በእግዚአብሔር አመኑ፡፡ ንጉሡም ብዙ ካሠቃየው በኋላ በመጨረሻ ሐምሌ 20 ቀን አንገቱን በሰይፍ ቆረጠውና የሰማዕትነቱ ፍጻሜ ሆነ፡፡ ሥጋውንም በእሳት አቃጥላለሁ ቢል እሳቱ ከቶ ሥጋውን አላቃጥል ብሎ እምቢ ብሎታል፡፡ በአገራችን በስሙ የተሠሩ አብያተክርስቲያናት አሉ፡፡ ቢሾፍቱ መስመር የረር በዓታ ጽላቱ ይገኛል፡፡

በገዳማዊ ኑሮ ያሉትን እየረዳንና በዓታቸውን እያጸናን የበረከታቸው ተሳታፊ እንሁን፡፡

ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444

ልዩ የትምህርት ወንጌል መርሃ ግብር በቃጥላ የተወደዳችሁ ኦርቶዶክሳውያን የዓቢይ ጾምን 6ኛ ሳምንት «ገብርኄር» ተአምሯ በማይነጥፍበት፣ የብዙዎች እምባ በሚታበስበት፣ የፈተናዎቻችን ቋጠሮ በሚ...
29/03/2025

ልዩ የትምህርት ወንጌል መርሃ ግብር በቃጥላ

የተወደዳችሁ ኦርቶዶክሳውያን የዓቢይ ጾምን 6ኛ ሳምንት «ገብርኄር» ተአምሯ በማይነጥፍበት፣ የብዙዎች እምባ በሚታበስበት፣ የፈተናዎቻችን ቋጠሮ በሚፈታበት የቃጥላ ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን እናሳልፍ።

በዕለቱ ብፁዕ አቡነ ቀውስጦስ የሰሜን ሸዋ ሰላሌ ሀገረስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል፣ ተጋባዥ ሰባኪያን፣ ዘማሪያን፣ መምህራንና ሊቃውንት ይገኛሉ። ከአጋንንት እስራት የተፈቱ፣ ከተለያዩ ደዌዎች የተፈውሱ እና የተደረገላቸው ምዕምናን ምስክርነት ይሰጣሉ።

መጋቢት 21 ከቃጥላ አይቀርም

“ቴሌብር አዲስ ነገር እስከ ፋሲካ ኤክስፖ 2017 ተዘጋጀ“ቴሌብር አዲስ ነገር እስከ ፋሲካ ኤክስፖ 2017 በአዲስ አበባ ኤግዚቢሽን ማዕከል ከመጋቢት 19 እስከ ሚያዚያ 11/2017 ዓ.ም ተ...
29/03/2025

“ቴሌብር አዲስ ነገር እስከ ፋሲካ ኤክስፖ 2017 ተዘጋጀ

“ቴሌብር አዲስ ነገር እስከ ፋሲካ ኤክስፖ 2017 በአዲስ አበባ ኤግዚቢሽን ማዕከል ከመጋቢት 19 እስከ ሚያዚያ 11/2017 ዓ.ም ተዘጋጅቷል።

ይህ ቴሌብር አዲስ ነገር እስከ ፋሲካ ኤክስፖ 2017 ታሜሶል ኮሙዩኒኬሽን ከታምኮን ሶፍትዌር ሶሉሽን እና ከሊያን ቢዝነስ ግሩኘ ጋር በመሆን እንዳዘጋጁት ተገልጿል፡፡

የ “ቴሌብር አዲስ ነገር እስከ ፋሲካ ኤክስፖ 2017“ በአዲስ አበባ ኤግዚቢሽን ማዕከል መጋቢት 19 ቀንየሚካሄድ ሲሆን እስከ ሚያዝያ 11 ቀን 2017 ዓ.ም ይቆያል ተብሏል።

ታሜሶል ኮሙዩኒኬሽን በዛሬው እለት በሀያት ሪጀንሲ ሆቴል በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንደገለጸው፣ ይህ ኤክስፖ ከዚህ ቀደም ከተደረጉ የንግድ ትርኢቶች የተለየ እና ልዩ የሚያደርጉት በርካታ ዝግጅቶች እንዳሉት ገልጿል::

በቴሌብር አዲስ ነገር እስከ ፋሲካ ኤክስፖ ላይ
ከ300 በላይ የሀገር ውስጥ እና የውጭ ንግድ ተቋማት ምርት እና አገልግሎቶቻቸውን በተመጣጣኝ ዋጋ ለማህበረሰቡ እንደሚያቀርቡ የተገለፀ ሲሆን ከንግድ ተቋማት በተጨማሪ ለበጎ አድራጎት ድርጅቶች እና በልዩ ትኩረት ለአካል ጉዳተኞች በመስጠት የአካል ጉዳተኞች መንደር ተካቷል ተብሏል።

በዚህ መንደር በአካል ጉዳተኞች የተመረቱ ምርቶች ለሽያጭ የሚቀርቡ ሲሆን ከዚህም በተጨማሪ አካል ጉዳተኞች በኪነጥበብ ዘርፍ የተለያዩ የመድረክ ስራዎችን የሚያቀርቡ ይሆናል።

እንዲሁም ከኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት ጋር በመተባበር የ50 ሚሊዮን ብር ሎተሪ በኤክስፖ ላይ በልዩ ሁኔታ ይተዋወቃል።

ለጎብኚዎችም ልዩ ልዩ አዝናኛ እና አስተማሪ እንዲሁም የሚያሸልሙ ጨዋታዎች የተዘጋጁ ሲሆን የመግቢያ ዋጋውም 100 ብር እንደሆነ ተነግሯል ።
(በድሬቲዩብ ሪፖርተር)

“ግዛት” የተሰኘ ልብ አንጠልጣይ ቴሌኖቬላ በዲኤስቲቪ-አቦል ቴሌቪዥን ለተመልካቾች መቅረብ ሊጀምር ነው፡፡ አዲሱን ልብ አንጠልጣይ ተከታታይ ድራማ ግዛትን የመጀመሪያ ክፍሎች በአቦል ቲቪ ድረገ...
29/03/2025

“ግዛት” የተሰኘ ልብ አንጠልጣይ ቴሌኖቬላ በዲኤስቲቪ-አቦል ቴሌቪዥን ለተመልካቾች መቅረብ ሊጀምር ነው፡፡

አዲሱን ልብ አንጠልጣይ ተከታታይ ድራማ ግዛትን የመጀመሪያ ክፍሎች በአቦል ቲቪ ድረገፅ ይመልከቱ!

http://bit.ly/gizat

ከኢትዮጵያውያን ዕውቅ የፊልም ባለሙያዎች ጋር በድንቅ ጥምረት ስራዎችን እያቀረበ የሚገኘው አቦል ቴሌቪዥን ለተመልካቾች እጅግ አስደሳችና ለደንበኞች የሚመጥኑ አዳዲስ ይዘቶችን በብዛት እያደረስ ነው፡፡

ላለፉት ዓመታት ግዙፍ፣ አዳዲስና እውቅ ኢትዮጵያውያን ባለሙያዎችን በማሳተፍ በኢትዮጵያ የቴሌቪዥን ተከታታይ ድራማዎች ታሪክ ፋና ወጊ የሚያድርጉትን ተወዳጅና እለታዊ የሆኑ ተከታታይ ቴሌኖቬላዎችን ማቅረቡና እያቀረበ መሆኑም ይታወቃል፡፡ አሁን ደግሞ አነጋጋሪ፣ ልብ አንጠልጣይና በላቀ ጥራትና ሙያዊ ብስለት የተዘጋጀውን “ግዛት” የተሰኘ አዲስ ቴሌኖቬላ ለተመልካቾች ለማቅረብ ዝግጅቱን አጠናቋል፡፡

“ግዛት”በታዋቂዋ የፊልም ባለሙያ ኤደን ጌታቸው ፕሮዲዩስ የተደረገ ሲሆን በቴሌቪዥን ድራማዎች ትወና አንቱታን ያተረፉ ድንቅ ተዋንያን ተሳትፈውበታል። ከእነዚህም መካከል ታምሩ ብርሃኑ፣ ቢኒያም ወርቁ እና ሜሮን እንግዳ ይገኙበታል።

“ግዛት” ሌሎችም በማራኪ ትወናቸው ገፀ-ባህሪያትን ሆነው የሚተውኑበትና በአቦል ቴሌቪዥን ለረጅም ጊዜያት በየዕለቱ ከሰኞ እስከ አርብ የሚተላለፍ ቴሌኖቬላ ነው፡፡
ግዛት ልብ እያንጠለጠለ የሁለት ቤተሰቦችን የግዛት ሽኩቻ፣ የገንዘብ ፍቅርና ጥቅም ፍለጋ ብሎም በተለያየ አጋጣሚ በሚፈጠሩ ክስተቶች የቤተሰብ ፍቅር በገንዘብ ሲፈተን የሚያሳይ ሲሆን በየክፍሉ ቀጥሎ ምን ሊፈጠር ነው በሚያስብሉ ድርጊቶች የተሞላ ድንቅ ተከታታይ ድራማ ነው።

“ግዛት” ቴሌኖቬላ ‘The Queen’ከተሰኘው የኤምኔት ተወዳጅ የደቡብ አፍሪካ ተከታታይ የቴሌቪዥን ድራማ ታሪክ በመነሳት የኢትዮጵያን ወግ፣ ባህል፣ እሴትና የአኗኗር ይትባሃል በጠበቀ ሁኔታ የተዘጋጀ ድራማ ነው፡፡

በ“ግዛት” የሀረግ ገፀ-ባህሪን ተላብሳ የምትጫወተው ሜሮን እንግዳ ሙሉ ጊዜዋን ለድራማው በማዋል ገፀ-ባህሪዋን ልዩ ውበትና ጉልበት በመስጠት የትወና ብቃቷን ያሳየችበት ሲሆን በሌላ በኩል ታምራት በለጠ ወይም ሰመረ ደግሞ አዲስ ችሎታና ብቃት ለፊልም ኢንዱስትሪው ይዞ የመጣበት ነው። ይህ ተዋናይ ለድራማው እንዲተውን እጩ የሆኖ የቀረበው የቀረፃ ወይም የፕሮዳክሽን አባል ሆኖ እያሰራ ባለበት ወቅት የግዛት ዳይሬክተር ኤደን ጌታቸው እምቅ ችሎታውን ተገንዝባ ሰመረን ወክሎ እንዲጫወት መርጣዋለች።

ዲኤስቲቪ ለሀገር በቀል ይዘቶች መጎልበት ግንባር ቀደም አካል እንደመሆኑ መጠን በሀገር ውስጥ መዝናኛዎች ለደንበኞ ምርጥ ምርጡን እያቀረበ ነው። ተመልካቾችንን የሚማርኩና ከዕለተ ዕለት ህይወታቸው ጋር ቀረቤታ ያላቸውን ታሪኮችን በላቀ ጥራት ሲያቀርብ ቆይቷል፡፡ አሁን ደግሞ የፕሮዳክሽን ቡድን አባላትም ሆኑ የአቦል ቴሌቪዥን ተመልካቾች አስደሳችና ልዩ የመዝናኛ ጊዜን በ“ግዛት” እለታዊና ተከታታይ ቴሌኖቬላ እንደሚያጣጥሙ እምነታችን የጸና ነው ብለዋል አዘጋጆቹ፡፡

“ግዛት” ከሰኞ መጋቢት 22 ቀን 2017 ዓ/ም ጀምሮ በጎጆ ፓኬጅ ዲኤስቲቪ-አቦል ቻናል 465 ከምሽቱ 2:30 መተላለፍ የሚጀምር ሲሆን ተመልካቾች ሊያመልጣቸው የማይገባ ድንቅ ተከታታይ የቴሌቪዥን ድራማ መሆኑም ተገልጿል፡፡

#ሁሉምያለውእኛጋርነው #ግዛት #አቦልቲቪ

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when DireTube posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to DireTube:

Videos

Share

Our Story

DireTube is the Largest Ethiopian News & Video Platform. It has particularly proven its value when it comes to keeping the worldwide Ethiopian Diaspora connected to their home country.

In many parts of the world Ethiopians do not have direct access to Ethiopian news and entertainment, therefore, DireTube becomes their primary source for these. For this reason DireTube is now one of the most popular Ethiopian websites on the internet.