DireTube

DireTube DireTube.com is the #1 Ethiopian Video Sharing Site. DireTube is an Ethiopian media and entertainment website founded on October 26, 2008.

♦️የዳይመንድ ሊግ አሸናፊዋ አትሌት ፋንታዬ በላይነህ ብ/ቡድኑን ተቀላቅላ ሆቴል ገባች✍️በጋዜጠኛ ይስሀቅ በላይ(ሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል)ባለፈው ሐሙስ ምሽት  ዙሪክ ላይ በተካሄደው የ2025...
01/09/2025

♦️የዳይመንድ ሊግ አሸናፊዋ አትሌት ፋንታዬ በላይነህ ብ/ቡድኑን ተቀላቅላ ሆቴል ገባች

✍️በጋዜጠኛ ይስሀቅ በላይ(ሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል)

ባለፈው ሐሙስ ምሽት ዙሪክ ላይ በተካሄደው የ2025 የዳይመንድ ሊግ ፍፃሜ ክስተት ሆና ያሸነፈችው የ24 ዓመትዋ አትሌት ፋንታዬ በላይነህ የቶኪዮ አለም ሻምፒዮና ተሳታፊ የሆነው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ብ/ቡድን ተቀላቅላ ሆቴል መግባቷ ተረጋግጧል

አመለሸጋው፣ልታይ ልታይ የማይለውና ተደብቆ ድምፁን አጥፍቶ በመስራት ውጤታማ በመሆን ተለይቶ በሚታወቀው ወጣቱ አሠልጣኝ ቴዎድሮስ ኃይሉ የምትሠለጥነው አትሌት ፋንታዬ በላይነህ የብዙዎቹን ቀልብ የሳበውን የ3000 ሜትር ውድድር በማሸነፍዋ ወደ ቶኪዮ አለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ተሳታፊ የሚያደርጋትን ትኬት መቁረጧን መዘገባችን ይታወሳል።

አትሌት ፋንታዬ በላይነህ በዙሪኩ የ2025 የዳይመንድ ሊግ ፍፃሜ በ3000 ሜትር 8:40.56 በሆነ ሠዓት በመግባት በማሸነፏ በዓለም አትሌቲክስ አዲሱ ህግ መሰረት በWild Card በቀጥታ በማለፍ በቶኪዮ ጃፓን ከሴፕቴምበር 13-21/2025 የሚካሄደው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ሀገርዋን ወክላ የምትሳተፍበትን ወርቃማ ዕድል አግኝታለች።

የአለም አትሌቲክስ ያወጣውን አዲስ ህግ ተከትሎ በWild Card በቀጥታ ተሳታፊ መሆኗን ያረጋገጠችው አትሌት ፋንታዬ በላይነህ ባለፈው ቅዳሜ ከዙሪክ አዲስ አበባ ገብታ ዛሬ(እሁድ) ቤልቪው ሆቴል በመግባት ለቶኪዮው የአለም ሻምፒዮና በዝግጅት ላይ የሚገኘውን የአትሌቲክስ ብ/ቡድን ተቀላቅላለች።

በአፍሪካ የአትሌቲክስ ሻምፒዮና በ5000ሜትር በ2022 የብርና በ2024 የወርቅ ሜዳልያ ባለቤት የሆነችው ወጣቷ አትሌት በቶኪዮው የአለም ሻምፒዮና በርቀቱ የመሳተፍ ዕድል ማግኘቷ ለኢትዮጵያ እንደመልካም አጋጣሚ የተወሠደ ሲሆን ሜዳልያ የማግኘት ዕድላችንን ከፍ እንደሚያደርገውም ባለሙያዎች አስተያየት እየሠጡበት ይገኛሉ።

ከአትሌቷ ስኬት ጀርባ የሚገኘውና ድምፁን አጥፍቶ ተደብቆ ስራውን ብቻ የሚሰራውና የነገ የአትሌቲክሱ አልጋወራሽ ይሆናል ተብሎ የሚጠበቀው ወጣቱ አስልጣኝ ቴዎድሮስ ሀይሉ በቶኪዮ የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና አትሌት መዲና ዒሳ፣አትሌት ሳሙኤል ፍሬው፣ አትሌት አለሽኝ ባወቀንና አሁን ደግሞ ፋንታዬ በላይነህን በማስመረጥ ከፍተኛ አትሌቶችን ካስመረጡ አሰልጣኞች ተርታ እንዲሠለፍም አድርጎታል ።

አሠልጣኝ ቴዎድሮስ ኃይሉ የጀግናዋና የአመለሸጋዋ አትሌት መሠረት ደፋር ባለቤትም ነው።

የመጽሐፍ ቀበኛው ፍርድ እያነጋገረ ነው!...እርስዎ በፍርዱ ላይ ያልዎትን አስተያየት ቢያጋሩን?***መጽሐፍ ሲሰርቅ የተያዘው  በ6 ወር እስራት ተቀጣ!ነሀሴ 13 ቀን 2017 ዓ.ም አለህልኝ ...
01/09/2025

የመጽሐፍ ቀበኛው ፍርድ እያነጋገረ ነው!...እርስዎ በፍርዱ ላይ ያልዎትን አስተያየት ቢያጋሩን?
***

መጽሐፍ ሲሰርቅ የተያዘው በ6 ወር እስራት ተቀጣ!

ነሀሴ 13 ቀን 2017 ዓ.ም አለህልኝ አንዷለም የተባለ ግለሰብ በአዲስ አበባ ቤተ መጻሕፍ አንባቢ መስሎ ገብቶ ሊገመት በማይቻል መልኩ መጽሐፍ ሰርቆ ሲወጣ፣ በቤተ መጻህፍቱ ፈታሾች በቁጥጥር ስር ውሎ፣ ፖሊስ ጉዳዩን ሲከታተል ከቆየ በኋላ ነሀሴ 22 ቀን 2017 ዓ.ም በዋለው ችሎት የስድስት ወር እስራት ተፈርዶበታል።

(ምንጭ፡ አዲስ አድማስ)

🎉🎉 Mastercard 🎉🎉Your Key to Hassle-Free Travel!Accepted Worldwide | Safe & Secure | Easy to Use***ይሠሯል ከልብ፣ እንደ ንብ!Commi...
31/08/2025

🎉🎉 Mastercard 🎉🎉

Your Key to Hassle-Free Travel!
Accepted Worldwide | Safe & Secure | Easy to Use

***
ይሠሯል ከልብ፣ እንደ ንብ!
Committed to Service Excellence!



Facebook / Instagram / linkedin / X / Youtube / Tiktok / Website

ጌጅ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ከ2400 በላይ ተማሪዎችን አስመረቀ ጌጅ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ በ2017 የትምህርት ዘመን በቀንና በማታ ያስተማራቸው ከ2400 በላይ ተማሪዎችን ማስመረቁን አስታውቋል ።ጌጅ ...
31/08/2025

ጌጅ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ከ2400 በላይ ተማሪዎችን አስመረቀ

ጌጅ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ በ2017 የትምህርት ዘመን በቀንና በማታ ያስተማራቸው ከ2400 በላይ ተማሪዎችን ማስመረቁን አስታውቋል ።

ጌጅ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ በመማር ማስተማር ከፍተኛ ልምድ ያለው የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋም ሲሆን በመጀመሪያ ዲግሪና በቴክኒክን ሙያ ስልጠና የመግቢያ መስፈርቱን ያሟሉ ተማሪዎችን በማስተማር ትናንት ነሐሴ 24 ቀን 2017 ዓ.ም ማስመረቁን ሰምተናል።

ዩኒቨርሲቲ ኮሌጁ አጠቃላይ 2465 ተማሪዎችን ያስመረቀ ሲሆን የመጀመሪያ ዲግሪ በቀና በማታ የትምህርት መርሀግብር እንዲሁም በቴክኒክና ሙያ የትምህርት ዘርፎች በአዲስአበባ ዩኒቨርስቲ 6ኪሎ ካምፓስ ጊቢ ውስጥ ማስመረቁ አስታውቋል።

በምረቃ መርሃግብሩ፣ በትምህርት ሚኒስቴር የኢትዮጵያ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አገለግሎት ኃላፊን ጨምሮ የኢትዮጵያ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ስራ አስኪያጅ በተገኙበት የተከናወነ ሲሆን ለተመራቂዎች የሕይወት ልምድ መልእክት በማስተላለፍ መከናወኑን ታውቋል።

የዕለቱን ምረቃ በዓል ለየት የሚያደርገው የአውራምባ ማኅበረሰብ መሥራች የሆኑት ክቡር ዶ/ር ዙምራ ኑሩ እና ባለቤታቸው ወ/ሮ እናነይ ክብረት በክብር እንግድነት ተገኝተው ተመራቂ ተማሪዎች ሥራን ሳይንቁ ጠንክሮ በመሥራት ራሳቸውን እንዴት መለወጥ እንዳለባቸው ከአውራምባን ማኅበረሰብ መማር አለባቸው ሲሉ ምክራቸውን ለግሰዋል።
ወ/ሮ እናነይ ክብረት
"መነሻችን ሰው ነው መድረሻችን ሰዉ ነዉ!"በማለት ጠንካራ መልዕክት አስተላለፈዋል።

ጌጅ ዩኒቨርስቲ ኮሌጅ በትምህርት ዘርፍ ከተሰማሩ ከፍተኛ የትምህርት መስጫ ተቋማት እድሜ ጠገብ ከሚባሉት ተርታ የሚመደቡ መካከል አንዱ ሲሆን የመማር ማስተማር አገልግሎት መስጠት ከጀመረ 23 አመታት ያስቆጠረ ተቋም ሲሆን በከፍተኛ አኳኋን ማህበራዊ ሀላፊነትን በመወጣት የሚነገርለት መሆኑን የተገኘው መረጃ ያሳያል።

በአዲሱ በጀት አመት አዳዲስ የትምህርት አይነቶች ለመጨመር ውጥን እንዳለው የተገለፀ ሲሆን ከተለያዩ አለማቀፍ የትምህርት ተቋማት ጋር በመተባበር ሁለተኛ እና ሶስተኛ ዲግሪ ፕሮግራሞች በትብብር ለመስራት እየተንቀሳቀሰ መሆኑን ዩኒቨርስቲ ኮሌጁ ገልጿል ።

በተጨማሪም በበይነመረብ የትምህርት አገልግሎት ለመስጠት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር እየሰራ መሆኑንና ፍቃድ ለማግኘትም በብርቱ እየሰራ እንደሚገኝ የትምህርት ተቋሙ በመርሀግብሩ ላይ አስታውቋል።

የትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን እንዲሁም ከአዲስ አበባ የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለሥልጣን የሚሰጠውን እውቅና ፈቃድ በመውሰድ በአዲስአበባ የተለያዩ አካባቢዎች ቅርንጫፎች ከፍቶ እየሰራ እንደሚገኝ ከዩኒቨርስቲ ኮሌጁ ያገኘነውን መግለጫ ላይ ተመልክተናል።

በተያያዘ ዜና ጌጅ ሰርቪስ ትሬዲንግ ሐውስ ፒኤልሲ በስሩ የሚተዳደሩ የትምህርት ተቋማት እና ሌሎች ያሉት ሲሆንጌጅ ሰርቪስ ትሬዲንግ ሐውስ በስሩ ከያዛቸው ተቋማት መካከል:- ጌጅ ዩኒቨርስቲ ኮሌጅ፣ ኩዊንስ ኮሌጅ፣ ሶፍትኔት የሥልጠና ማዕከል፣ ኤል ኤም ኢንተርናሽናል ሆቴል ስኩል፣ ግሬስ ኮሌጅ፣ ጌጅ አካዳሚ፣ ኤምጂኬ(MGK printing enterprise )AGET (African Global education & Technology )፣ AIHD (African international humanitarian development )፣ (ኤስኤም ኤስትሬዲንግ )SMS trading plc የሚባሉ ተቋማት እንዳሉና ከ2000 ዜጎች የስራ እድል መፍጠር የቻለ አርዓያ ተቋም ነዉ።

(ጋዜጠኛ ሲሳይ መንግስቴ እንደዘገበው)

የያቤሎ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የዘመናት የልማት ጥያቄ ምላሽ የሰጠ ነው - አቶ ሽመልስ አብዲሳ የያቤሎ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የዘመናት የልማት ጥያቄ ምላሽ የሰ...
31/08/2025

የያቤሎ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የዘመናት የልማት ጥያቄ ምላሽ የሰጠ ነው - አቶ ሽመልስ አብዲሳ

የያቤሎ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የዘመናት የልማት ጥያቄ ምላሽ የሰጠ ነው አሉ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ፡፡

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በኦሮሚያ ክልል ቦረና ዞን የያቤሎ አውሮፕላን ማረፊያን አገልግሎት በዛሬው ዕለት አስጀመሯል።

በዚሁ ወቅት አቶ ሽመልስ አብዲሳ እንዳሉት፥ መንግስት የመሰራተ ልማት ዝርጋታን በማፋጠን የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ከምንጊዜውም በላይ በቁርጠኝነት እየሰራ ነው።

ከመሃል ሀገር ርቀው የሚገኙ አካባቢዎችን በመሠረተ ልማት ተጠቃሚ በማድረግ በማህበራዊ፣ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ዘርፎች እኩል ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

በቦረና አካባቢ የያቤሎ አየር ማረፊያ ተገንብቶ አገልግሎት መጀመሩ ቦረና ከአዲስ አበባ የነበረውን ረጅም መንገድ ያሳጠረ ነው ማለታቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡

መንግሥት የህዝቡን የመሠረተ ልማት ጥያቄዎች በተግባር ምላሽ እየሰጠ መሆኑንም ጠቁመዋል።
(ኤፍ ኤም ሲ)

የሁሉ የገንዘብ ቁጠባ እና ብድር ማህበር 4ተኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውን አካሄደ የሁሉ የገንዘብ ቁጠባ እና ብድር ማህበር 4ተኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውንና ሁለተኛ አመት የምስረታ በዓሉን በዛ...
31/08/2025

የሁሉ የገንዘብ ቁጠባ እና ብድር ማህበር 4ተኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውን አካሄደ

የሁሉ የገንዘብ ቁጠባ እና ብድር ማህበር 4ተኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውንና ሁለተኛ አመት የምስረታ በዓሉን በዛሬው እለት የማህበሩ አባላትና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በስካይ ላይት ሆቴል አካሄዷል

በቀን ከ10 ብር ጀምሮ መቆጠብ የሚችል ዜጋ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ የማህበሩ አባል በመሆን ብድር ማግኘት የሚችልበትን አሰራር የዘረጋው ማህበሩ አባላቱ በየቀኑ መቆጠብ እስከቻሉ ድረስ የብድር አገልግሎት ተጠቃሚ መሆን እንደሚችሉ ተገልጿል፡፡

ማህበሩ ከ2 ሺህ ብር ጀምሮ እስከ አምስት ሚሊዮን ብር ድረስ ብድር እንደሚሰጥ ተገልጾ የሞባይል አፕሊኬሽን በመጠቀም አባላት የብድር አገልግሎት መጠቀም የሚያስችላቸውን አገልግሎትም ዘርግቷል፡፡

የሁሉ ገንዘብ ቁጠባ እና ብድር ኅብረት ሥራ ማኅበር የቦርድ ሠብሣቢ መሳፍንት ደበበ የሁሉ ገንዘብ ቁጠባ እና ብድር ኅብረት ሥራ ማኅበር ባለፉት ሁለት ዓመታት ከ920 ሚሊዮን ብር በላይ ብድር በማሰራጨት 60 በመቶ የሚኾኑ አባላቱን ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን ገልጸዋል።

ማኅበሩ በአጭር ጊዜ ውስጥ የአባላቱን ቁጥር ወደ 22 ሺ በላይ ከፍ ማድረግ ችሏል ያሉት ሳብሳቢው የካፒታል መጠኑንም ወደ 1 .65 ቢሊየን ብር በላይ በማሳደግ በርካታ የብድር አማራጮችን ለኅብረተሰቡ እያቀረበ ይገኛልም ነው ያሉት።

በመድረኩ የተገኙት የኢትዮጵያ ኅብረት ሥራ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጌትነት ታደሰ ኮሚሽኑ በአሁን ሰአት ሁሉን አቀፍ መሻሻል እያደረገ እንዳለ ገልፀው የሁሉ ገንዘብ ቁጠባ እና ብድር ኅብረት ሥራ ማኅበር በአጭር ጊዜ ውስጥ ላስመዘገበው ስኬት ምሥጋናቸውን አቅርበዋል።

ኮሚሽነር አክለውም የገንዘብ ቁጠባ እና ብድር ማህበራት ግልፀኝነትና ታማኘነትን ላይ ተመስርተው መስራት እንዳለባቸው አሳስበዋል

ማህበሩ የዘመናዊ ኮር ባንኪንግ ተጠቃሚም እንደሆነ የተገለፀ ሲሆን ይህም ኮርባንኪንግ ከሁሉም ባንኮች ጋር በትብብር ለመስራት የሚያስችል በመሆኑ እና ሁሉንም የአገራችንን ባንኮች እንደቅርንጫፍ አድርጎ መጠቀም ስላስቻላቸው፣ የማህበሩ አባላት ከየትኛውም ባንክ ገንዘባቸውን ገቢ ወጪ ማድረግ ይችላሉ ተብሏል፡፡

ማኅበሩ ከተመሠረተበት ባለፉት ሁለት ዓመታት በርካታ ሥራዎችን ያከናወነ ነው። በተለይም የፋይናንስ አገልግሎትን በቀላሉ ማግኘት ለማይችሉ ዝቅተኛ የኅብረተሰብ ክፍሎች ተደራሽ የኾነ አገልግሎት በመስጠት ተጨባጭ ውጤቶችን እያስመዘገበ እንደሚገኝ ተገልጿል።

በ2015 ዓ.ም በ126 ሺ ብር ካፒታል በሃዋሳ ከተማ የተመሰረተው ኅብረት ሥራ ማህበሩ ሲመሰረት 114 ወንድ 28 ሴት በድምሩ 142 አባላት የነበሩት ሲሆን ዛሬ ላይ ከ22 ሺ በላይ አባላት እንዳለው ተነግሯል፡፡

810 ሰልጣኞች ተመረቁዛሬ በለነገዋ የሴቶች ተሀድሶና ክህሎት ማበልፀጊያ ማዕከል በተለያዩ ሞያዎች ያሰለጠንናቸውን 810 የ3ኛ ዙር ሰልጣኞች አስመርቆ ወደ ስራ አሰማራ።  ማዕከሉ ለተለያዩ ማ...
31/08/2025

810 ሰልጣኞች ተመረቁ

ዛሬ በለነገዋ የሴቶች ተሀድሶና ክህሎት ማበልፀጊያ ማዕከል በተለያዩ ሞያዎች ያሰለጠንናቸውን 810 የ3ኛ ዙር ሰልጣኞች አስመርቆ ወደ ስራ አሰማራ።

ማዕከሉ ለተለያዩ ማህበራዊ ችግሮች ተጋልጠው ጎዳና የወደቁ፣ ለሴተኛ አዳሪነት የተጋለጡ ሴቶችን ከጎዳና በማንሳት በተለያዩ ክህሎቶች እያሰለጠነ ወደ ስራ እያሰማራ ይገኛል ።

የዛሬውን ጨምሮ ከዚህ ቀደም በተለያዩ ዙሮች አሰልጥነን ወደ ስራ ያሰማራናቸው ሴቶች አጠቃላይ ቁጥር 1 ሺ 692 ደርሷል ።ይህ ስራ ከተማችን ውስጥ ሌት ተቀን ከምንከውናቸው ሌሎች የልማት ስራዎች አልቀን የምናየዉ አንዱና ዋነኛ ስራችን ነው። ሴት እህቶቻችን እነሱ ባልፈጠሩት ችግር ለመራር የህይወት ፈተና ሲጋፈጡ፣ ሲወገዙ፣ ሲገፉ፣ በረንዳ ሲወድቁ፣ ለአስከፊው የሴተኛ አዳሪነት ህይወት ሲጋለጡ ይስተዋላል። የችግሩ ዋነኛ ምንጭ እነሱ ሳይሆኑ በዋናነት ድህነት እና ኋላቀርነት ነው ።

ይህን ችግር ከስሩ የሚነቅለው ብቸኛዉ መንገድ ደግሞ የጀመርነው የኢትዮዽያ ሁለንተናዊ ብልፅግና እውን መሆን ነው። ለዚህም ሌት ተቀን መስራታችን ይቀጥላል ።

ከንቲባ አዳነች አቤቤ እንዳሉት የዛሬ ተመራቂ ተማሪዎች ትናንት ከነበሩበት የጎዳና ላይ ህይወት ወጥተው፣ ከአስከፊ ህይወት ተላቀው፣ ከሱስ ተጋላጭነታቸው እና ከጤና ችግሮች ወጥተው በአዲስ ህይወት ጅማሮ ላይ ሆነው በማየታችን እጅግ ደስተኞች ነን።

ተመራቂዎች በቀጣይ ዳግም ላይመለስ በተቀየረው የትላንት ማንነታችሁ ሳትሸማቀቁ ፣ በማዕከሉ ቆይታ ያካበታችሁትን እውቀት፣ ክህሎት፣ መልካም ስነ ምግባር በስራ ላይ እንድታውሉ። በየእለቱ ራሳችሁን በእውቀትና ቴክኖሎጂ ከጊዜዉ ጋር እያሳደጋችሁ ለሌሎች እህቶቻችሁ ምሳሌ እንድትሆኑ አደራ እላለሁ ብለዋል ።

ከንቲባዋ አያይዘውም ለዚህ በርካቶችን ከጨለማ ህይወት ታድጎ በቀሪ ህይወታቸው ብርሃን እንዲፈነጥቅ ላደረገ በጎ ስራ በእውቀት፣ በሞያ ፣ በሀብት ድጋፍ ያደረጋችሁ ባለድርሻ አካላት፤ ባለሀብቶች፣ የከተማችን አመራሮች በተለይም አጠቃላይ የተቋሙን አመራሮችና ባለሙያዎች በተመራቂዎቹ ስም እጅግ በጣም አመሰግናለሁ ።

ለየዋኁ እንድረስለት?!ተፈጥሮ እና ሰው በፍፁም የተዋደዱበት ያ ምድር ተፈጥሮ ጨከነችበት። አረንጓዴው መንደር ድንገት ማቅ ለበሰ።ከጓሮዋም ከጓዳዋም ለመስጠት የማትሰስተው ያች የዋህ የጌዴኦ እ...
31/08/2025

ለየዋኁ እንድረስለት?!

ተፈጥሮ እና ሰው በፍፁም የተዋደዱበት ያ ምድር ተፈጥሮ ጨከነችበት። አረንጓዴው መንደር ድንገት ማቅ ለበሰ።ከጓሮዋም ከጓዳዋም ለመስጠት የማትሰስተው ያች የዋህ የጌዴኦ እናት አንገቷን ደፍታ ስቅስቅ ብላ አለቀሰች።ሀገር አማን ብላ ጎጆዋን በምታሞቅበት ማለዳ ዱብ ዕዳ መጣባት።የእኔ የምትለው ሁሉ በቅፅበት ከመሬት በታች ተቀበረ። የማህፀኗ ፍሬ እና የቤት እንስሳት ከአፈር በታች ተቀበሩ።እናም ሀዘኑ መሪር ህይወትም መራራ ሆነችባት።

ወትሮ በሥራ ትጋቱ፣ በጥምር እርሻ ጥበቡ የሚታወቀው ፣እንግዳ ሆኖ የመጣን ሁሉ "ነጋን ጌ"፣ "ፋያን ጌ"ብሎ በፈገግታ የሚቀበለው #የጌዴኦ አርሶ አደር ድንገት ቀዬው ፣መንደሩ፣መሬቱ ከዳውና ከመሬት በታች ከነቤተሰቡ ተቀበረ።

የተንከባከባት ተፈጥሮ ጨከነችበት። ስንት ነገር ያደረገው፣ስንት ታሪክ የሠራው ያ ጀግና አርሶ አደር ምንም ነገር ማድረግ የማይችል ፣የሰው እጅ የሚያይ ሆኗል። ዘወትር በስስት የሚያያቸውን ልጆቹን እና የምንከባከባቸውን ከብቶቹን በጎዶሎ ቀን አጥቷል።ጰየሞቀ ሰፈሩን ለቆ ተሰዷል።ለነገ ዕጣ ፈንታው ፈጣሪውን እየለመነ ፣ለዛሬ ውሎ የለጋሶችን እጅ እያየ ነው።

እናም አሁን ኢትዮጵያዊ ፍቅር፣ የለጋስ ሰው እጅ ፣የኢትዮጵያዊ ወገን ድጋፍ፣የአፅናኞች አብሮነት በእጅጉ ያስፈልገዋል። #አብነት የሚሆኑን ልበ ቀናዎች ከቀዬው ዘልቀው ችግሩን እየተጋሩ ከጎኑ ሆነዋል። በአካል መገኘት የማንችል ግን በፀሎትና በገንዘብ ድጋፍ ከጎናቸው እንሁን።

ፈጣሪ ሆይ በምህረትህ እና በማፅናናትህ ከጌዴኦ ወገኖቻችን ጋር ሁን‼️

(ጋዜጠኛ ደስታ ወልደሰንበት)

31/08/2025

ይኸው! የወንዶች ጉዳይ እጅግ ማራኪ ከሆነው የቴክኖ ካሞን 40 ጋር፡፡ ዛሬውኑ የራስዎት ያድርጉት!

የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል በአመራርነት ዘርፍ የዕውቅና ሽልማት አገኙ፨፨፨የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል በአመራርነት ዘርፍ የ...
31/08/2025

የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል በአመራርነት ዘርፍ የዕውቅና ሽልማት አገኙ
፨፨፨

የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል በአመራርነት ዘርፍ የዕውቅና ሽልማት የተበረከተው የስታር ዋይድ አዋርድ ኢንተርናሽናል የተበለ ድርጅት ነሐሴ 24/2017 ዓ.ም በስካይ ላይት ሆቴል ባዘጋጀው የስታር ዋይድ አዋርድ ላይ ነው።

ለኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል በአመራርነት ዘርፍ የዕውቅና ሽልማት የተበረከተላቸው ወንጀልን በብቃት መከላከል የሚያስችል በኢትዮጵያ የመጀመርያ የሆነውን የዜጎች ተሳትፎ መተግበሪያ (EFPApp) በማበልፀግ ኅብረተሰቡ ወንጀል በመከላከል ውስጥ የሚያደርገው ተሳትፎ በከፍተኛ ደረጃ በማሳደጋቸው እንደሆነ ተገልጿል።

ማንኛውም ሰው ያለ ምንም እንግልት ወደ ፖሊስ ጣቢያ መሄድ ሳይጠበቅበት እቤቱ ወይም በሥራ ቦታ ሆኖ መተግበርያውን ብቻ በመጠቀም የወንጀል ድርጊቶችን በተመለከተ ለፖሊስ መረጀ የሚያደርስበት ዘመናዊ ሀገር በቀል ቴክኖሎጂ መሆኑ በሽልማት ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ተገልጿል።
(ኢ.ፌ.ፖ.ሚ)

በክርስትናው ዓለም በዓለም አቀፍ ደረጃ ታሪካቸው ከሚነገርላቸው ሰማዕታት አንዱ በሀገራችን በኢትዮጵያም በአማላጅነቱ የሚታወቀው ታላቁ ሰማዕት ቅዱስ መርቆሬዎስ፡፡መርቆሬዎስ ማለት የአብ ወዳጅ ...
31/08/2025

በክርስትናው ዓለም በዓለም አቀፍ ደረጃ ታሪካቸው ከሚነገርላቸው ሰማዕታት አንዱ በሀገራችን በኢትዮጵያም በአማላጅነቱ የሚታወቀው ታላቁ ሰማዕት ቅዱስ መርቆሬዎስ፡፡

መርቆሬዎስ ማለት የአብ ወዳጅ ማለት ነው። በሁለተኛ ትርጉሙ የኢየሱስ ክርስቶስ አገልጋይ ማለት ነው። በሀገራችን በኢትዮጵያም በበርካቶች ዘንድ በፍጣን ተራዲኢነቱ ይታወቃል፡፡ በትውልዱ ሮማዊ ሲሆን አረማውያን የነበሩት ቤተሰቦቹ ከአምልኮተ ጣኦት ወደ አምልኮተ እግዚአብሔር የተመለሱ ናቸው፡፡ አባቱ ፊታቸው የውሻ የሆነ፣ የአውሬነት ጸባይ ያላቸው በእግዚአብሔር ኃይል የሚታዘዙት ሁለት አገልጋዮች ነበሩት፡፡ በመርዶሳውያን ሀገር ተማርኮ የሔደው አባቱ ጸጋ እግዚአብሔር በዝቶለት በዚያ ሹመት አጊኝቷል፡፡ አባትና እናቱ ሲያርፉም ልጃቸው ስልጣኑን ተረክቧል፡፡

በእምነቱ የጸናው ፍጹም ክርስቲያናዊ ቅዱስ መርቆሬዎስም የአባቱን ስልጣን ወርሶ በንጉስ ዳኪዮስ ስር በመርዶሳውያን አገር ላይ ተሾመ፡፡ መርቆሬዎስ መኰንንነት በተሾመም ጊዜ ገጸ ከለባት የሚባሉት የውሻ ፊት ያላቸው የአባቱ አገልጋዮች አብረውት ነበሩ፤ ለመዋጋትም በወጣ ጊዜ የቀድሞው የአራዊት የሆነ ተፈጥሯቸውን እግዚአብሔር ይመልስላቸው ስለነበር ማንም አይቋቋመውም ነበር፡፡ ለቅዱስ መርቆሬዎስ ታላቅ የድል አድራጊነት ኃይል ተሰጠው፡ ዜናውም በሁሉም ሀገሮች ተሰማ፤ በሀገረ ሮሜ ጣዖት የሚያመልከው ዳኬዎስ የተባለውም ንጉሥ ከበርበር ሰዎች ጋር ጦርነት ሊገጥም በወጣ ጊዜ እጅግ ሲበዙበት ፈራ፡፡ ቅዱስ መርቆሬዎስ ግን በጦሩ መካከል የተሳለ ሰይፍ የያዘ የእግዚአብሔርን መልአክ ስላየ ንጉሡን “እግዚአብሔር ያጠፋቸዋልና አትፍራ” አለው፤ ከዚያም ሰይፉን ለቅዱስ መርቆሬዎስ ሰጠውና “ጦርነቱን ድል ባደረግህ ጊዜ እግዚአብሔርን አስበው” አለው፡፡

የመልአኩ ተራዳኢነት፣ የቅዱስ መርቆሬዎስ ጀግንነት ትልቅ ድርሻ አበርክቶበት ድል አድርጉ፡፡ መልአኩም ዳግም ተገልጦለት “ለምን የፈጣሪህን ስም መጥራት ረሳህ” አለው፡፡ ጦርነቱ በንጉሱ ዳኪዮስ ወገን አሸናፊነት ሲጠናቀቀ ንጉሡ ከጦርነቱ በኋላ ለጣዖታቱ ዕጣን በማሳረግ በዓልን አደረገ፡፡ የእግዚአብሔር መልአክ በጠላቶቹ ፊት ድል ያጎናጸፈው ቅዱስ መርቆሬዎስ ግን በዚህ ድርጊት በማዘኑ በበዓሉ ላይ አልተገኘም፡፡ ንጉሡ ዳኪዮስ ይህንን ሲያውቅ መልእክተኞችን ልኮ አስጠራውና “ከእኔ ጋር ለምን አታጥንም?” አለው፡፡ ቅዱስ መርቆሬዎስ ትጥቁንና ልብሱን አውልቆ ከወረወረለት በኋላ “ክብር ይግባውና እኔ አምላኬ ኢየሱስ ክርስቶስን ፈጽሞ አልክደውም፤ ለረከሱ ጣዖቶችህም አልሰግድም” አለው፡፡ ከዚህ በኋላ ነበር ሰማዕቱ ቅዱስ መርቆሬዎስ በክርስትናው የተፈተነው፡፡

ቅዱስ መርቆሬዎስ ግን በጽናት በሃይማኖት ቆመ፡፡ በዚህ የተናደደው ንጉሡ ዳክዮስ አብሮት በጣኦት አምልኮው ስላልተሳተፈ በልዩ ልዩ ሥቃዮችም እጅግ አሠቃየው፡፡ በኋላም ስለ መርቆሬዎስ ብለው የሀገሩ ሰዎች እንዳይነሡበት ፈርቶ በብረት ችንካር ቸንክሮ የቀጵዶቅያና የእስያ ክፍል ወደ ሆነች ወደ ቂሳርያ ከደብዳቤ ጋር ላከው፡፡ በዚያም እጅግ ካሠቃዩት በኋላ በንጉሥ ዳኬዎስ ትዕዛዝ አንገቱን በሰይፍ ቆረጡትና የሰማዕትነት ተጋድሎውን ፈጸመ፤ የሕይወትንም አክሊል ተቀዳጀ፤ በዓለሙ ሁሉ አብያተ ክርስቲያናት ታነጹለት፡፡ እግዚአብሔርም ድንቅ ድንቅ የሆኑ ተአምራትን በቅዱስ መርቆሬዎስ ስም አደረገ፡፡ በየቀሩ በ25 ቀንም መታሰቢያው ነው፡፡ የሰማዕታቱን አሰረ ፍኖት የሚከተሉት ገዳማውያንም ዓለም የምትሰጣቸውን ተድላና ደስታ ንቀው ክርስቶስን ብለው ወጥተዋልና ጸሎታቸው ኃይልን ታደርጋለች፡፡ ገዳማቸውን እንደግፍ በዓታቸውን እናጸና ከበረከታቸውን እንሳተፍ፡፡

ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444

♦️ኢትዮጵያዊው ኃይለማሪያም ኪሮስና ሲፋን ሀሰን የሲዲኒ ማራቶንን አሸነፉ♦️ኤሊዩድ ኪፕቾግ በዘጠነኛነት ውድድሩን አጠናቋል፣✍️በጋዜጠኛ ይስሀቅ በላይ(ሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል)ከ35ሺ በላይ ...
31/08/2025

♦️ኢትዮጵያዊው ኃይለማሪያም ኪሮስና ሲፋን ሀሰን የሲዲኒ ማራቶንን አሸነፉ

♦️ኤሊዩድ ኪፕቾግ በዘጠነኛነት ውድድሩን አጠናቋል፣

✍️በጋዜጠኛ ይስሀቅ በላይ(ሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል)

ከ35ሺ በላይ ሠዎች በተሳተፉበት የ2025 TCL SYDNEY MARATHON በኤሊት አትሌቶች ኢትዮጵያዊው ኃይለማርያም ኪሮስና ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ ሲፋን ሀሰን አሸናፊነታቸውን ሲያውጁ በውድድሩ ብዙ የተወራለት ኬንያዊው ኤሊዩድ ኪፕቾጌ ዘጠነኛ በመሆን አጠናቋል።

ኃይለማርያም ኪሮስና ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ ሲፋን ሐሠን ውድድሩን 2:06:06 እና 2:18:22 በሆነ ሠዓት በመግባት የውድድሩን ሪከርድ በማሻሻል ጭምር አሸንፈዋል።

ከ2024 ጀምሮ ቦስተን፣ ቶኪዮ፣ በርሊን፣ ቺካጎ፣ ለንደንና ኒውዮርክ ሲቲ ቀጥሎ ወርልድ ሜጀር ማራቶን ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ ተካቶ የተካሄደው የሲዲኒ ማራቶን በወንዶች የ28 ዓመቱ ኢትዮጵያዊ ኃይለማርያም ኪሮስ በአንደኝነት ሲያጠናቅቅ ሌላኛው ኢትዮጵያዊ አዲሱ ጎቦና በ10 ሠከንዶች ዘግይቶ የቦታው ሪከርድ የሆነ 2:06:16 በማስመዝገብ በሁለተኛነት አጠናቋል።

በኤሊት ሴቶች አይበገሬዋ ሲፋን ሀሰን ታሪክ መስራቷን ባሳየችበት ውድድር በሲዲኒ ምድር ከ2:18:22 በታች በመግባት የመጀመሪያዋ ሴት አትሌት ሆና ተመዝግባለች።

የወቅቱ የአለም የማራቶን አሸናፈነቷንና በ5ሺ እና 10ሺ ሜትር የነሐስ ሜዳልያ አሸናፊነቷን በማወጅ በሶስት ውድድር ሜዳሊስት በመሆን አዲስ ታሪክ ያፃፈችው ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ ኔዘርላንዳዊ ሲፋን ሀሰን የአለም አትሌቲክስ ክስተት መሆኗን በሲዲኒ ጎዳና ላይም አሳይታለች።

የአለማችን አስገራሚዋ አትሌት ሲፋን ሀሰን በአፕሪል ወር በለንደን ማራቶን 2:19:00 በመግባት በሶስተኝነት ካጠናቀቀች በኃላ ያስመዘገበችው የማራቶን የመጀመሪያ ድሏም ሆኗል።

በሴቶች ምድብ ሲፋን ሀሰንን ተከትላ ኬንያዊቷ ብሪጅድ ኮስጊ በሁለተኝነት ስታጠናቅቅ ኢትዮጵያዊያኖቹ ወርቅነሽ ኢዶሳና ኩሜሺ ሲቻላ ሶስተኛና አራተኛ በመሆን አጠናቀዋል።

♦️የሲዲኒ ማራቶንን በማሸነፍና ሪከርድ በመስበር የሚገኝ ሽልማት

👉በወንድም በሴትም አንደኛ ለሚወጡ ለእያንዳንዳቸው 30ሺ ዶላር

👉በወንድም በሴትም ሁለተኛ ለሚወጡ ለእያንዳንዳቸው 20ሺ ዶላር

👉በወንድም በሴትም ሶስተኛ ለሚወጡ ለእያንዳንዳቸው 10ሺ ዶላር

👉በወንድም በሴትም አራተኛ ለሚወጡ ለእያንዳንዳቸው 5ሺ ዶላር

♦️የቦታውን ሪከርድ ለሚያሻሽሉ ደግሞ ተጨማሪ 10ሺ ዶላር

በወንድም በሴትም አምስተኛ ለሚወጡ ለእያንዳንዳቸው 2500ሺ ዶላር ያገኛሉ። አውስትራሊያ ለመጀመሪያ ጊዜ ለአሸናፊዎች 135ሺ የአውስትራሊያ ዶላር መድባለች።
***
Sydney Marathon 2025 ኤሊት ወንዶች ውጤቶች

ሀይለማሪያም ኪሮስ 🇪🇹 2:06:06 CR

አዲሱ ጎበና 🇪🇹 2:06:16

ቲቤሎ ራማኮንጎአና 🇱🇸 2:06:47

ሙስጠፋ ሆዳድ 🇲🇦 2:07:17

ኤድዋርድ ቼሴሬክ 🇰🇪 2:07:38

አራኦ ማሳቶ Arao (JPN) 2:07:42

ላባን ኮሪዮር 🇰🇪 2:08:06

ፍሊክስ ኪፕቱ 🇰🇪 2:08:18

ኤሊዩድ ኪፕቾጌ 🇰🇪 2:08:31

ቪክቶር ኪፕቺርቺር 🇰🇪 2:09:01

♦️ኤሊት ሴቶች ውጤቶች

ሲፋን ሀሠን (NLD) 2:18:22 CR

ብሪጅድ ኮስጌይ 🇰🇪 2:18:56

ወርቅነሽ ኢዴሳ 🇪🇹 2:22:15

ኩሜሺ ሲቻላ 🇪🇹 2:22:50

ኢቫሊን ቺርቺር 🇰🇪 2:23:13

ሆሶዳ አይ 👺 2:23:27

ሊኔ ፖምፒአኒ 🇦🇺 2:24:47

ጄሲካ ስቴንሠን 🇦🇺 2:28:56

ሊሳ ዌይትማን 🇦🇺 2:29:34

አቢጋሊ ኖርድበርግ 🇦🇺 2:35:43

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when DireTube posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to DireTube:

Share

Our Story

DireTube is the Largest Ethiopian News & Video Platform. It has particularly proven its value when it comes to keeping the worldwide Ethiopian Diaspora connected to their home country.

In many parts of the world Ethiopians do not have direct access to Ethiopian news and entertainment, therefore, DireTube becomes their primary source for these. For this reason DireTube is now one of the most popular Ethiopian websites on the internet.