DireTube

DireTube DireTube.com is the #1 Ethiopian Video Sharing Site. DireTube is an Ethiopian media and entertainment website founded on October 26, 2008.

በ8 የአጀንዳ ርዕሰ ጉዳዮች መግባባት ተደርሷልከሁለት ቀናት በፊት በሰላም ግንባታ፣ በሃይማኖት ጉዳዮች፣ በሙስና እና መልካም አስተዳደር እንዲሁም በመንግስት አደረጃጀት እና የፖለቲካ ስርዓት ...
13/08/2026

በ8 የአጀንዳ ርዕሰ ጉዳዮች መግባባት ተደርሷል

ከሁለት ቀናት በፊት በሰላም ግንባታ፣ በሃይማኖት ጉዳዮች፣ በሙስና እና መልካም አስተዳደር እንዲሁም በመንግስት አደረጃጀት እና የፖለቲካ ስርዓት ሲመካከሩ የነበሩ ቡድኖች መግባባት ላይ እንደደረሱ መገለፁ የሚታወስ ነው፡፡

በዛሬው ዕለትም የተቀሩት ማለትም
• በሀገር ግንባታ
• በፌዴራል ከተሞች ጉዳይ
• ተቋማት ግንባታ፣ የሕግ የበላይነት እና ሰብዓዊ መብት
• ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ላይ ተመካካሪዎች ስምምነት ላይ ደርሰዋል፡፡
(ኮምሽኑ)

አንሳር ያደርሳል — ከ1.25 ቢልዮን ብር በላይ በስኬት መንገድ!እውነትም አንሳር ወደ ህልምዎ ያደርሳል!በአንድ አመት ተኩል የሥራ ዘመን ውስጥ፣ ንግድዎን ወደ አዲስ ከፍታ ለማድረስ ከወለድ ...
13/08/2026

አንሳር ያደርሳል — ከ1.25 ቢልዮን ብር በላይ በስኬት መንገድ!
እውነትም አንሳር ወደ ህልምዎ ያደርሳል!

በአንድ አመት ተኩል የሥራ ዘመን ውስጥ፣ ንግድዎን ወደ አዲስ ከፍታ ለማድረስ ከወለድ ነፃ የሆነው የዲጂታል ፋይናንሲንግ መተግበሪያችን «አንሳር» ያለ ምንም መያዣ ከ1.25 ቢሊዮን ብር በላይ ፋይናንሲንግ አድርጓል!

አንሳር በቁጥሮች፡
• አጠቃላይ ፋይናንሲንግ፡ 1.25 ቢሊዮን ብር በላይ
• የተመዘገቡ ደንበኞች፡ 20,000 በላይ
• ተጠቃሚዎች፡ 14,500 በላይ የፋይናንሲንግ ተጠቃሚዎች
• የንግድ ትስስር፡ 3,615 አቅራቢዎች ከ7,400 በላይ ምርቶች ጋር
በዘመናዊ የዲጂታል ፋይናንሲንግ መፍትሄዎች፣ የወጣት ስራ ፈጣሪዎችን በተለይም የሴቶችን የልማት ጉዞ እያፋጠንን ነው።

አንሳር የሴት ስራ ፈጣሪዎችን በመደገፍ አስደናቂ ውጤት አስመዝግቧል፡፡

• ከአጠቃላይ ተጠቃሚዎች 85% የሚሆኑት ሴቶች ናቸው!
• ከአጠቃላይ የፋይናንሲንግ ብር 94% የሚሆነው ለሴቶች የዋለ ነው!

የዓለማችን ምርጥ ዲጅታል ፋይናንሲንጎች ተርታ በመሰለፍ ሁለት ዓለም አቀፍ እውቅናዎችንና ሽልማቶችን ተቀዳጅቷል።

እርስዎስ፣ ወደ ህልምዎ ለመድረስ ዝግጁ ነዎት?

እንግዲያውስ ዛሬውኑ የአንሳር ዲጂታል ፋይናንሲንግ መተግበሪያን ከፕሌይ ስቶር (Play Store) ወይም ከአፕ ስቶር (App Store) በስልክዎ ላይ አውርደው መጠቀም ይጀምሩ!

መተግበሪያውን ለማውረድ፡- https://play.google.com/store/apps/details?id=com.halal.gebeya.halal

ዘምዘም ባንክ - የማይነጥፍ የእድገት ምንጭ!

ድሬዳዋ የኢንቨስትመንት ወጪን የመሸፈን አቅሟ ከ70 በመቶ በላይ ደርሷልየምስራቁ የሀገሪቱ ክፍል የንግድና የኢንዱስትሪ ማዕከል በሆነችው ድሬዳዋ በርካታ የልማት ስራዎች መሰራታቸውን የድሬዳዋ ...
13/08/2026

ድሬዳዋ የኢንቨስትመንት ወጪን የመሸፈን አቅሟ ከ70 በመቶ በላይ ደርሷል

የምስራቁ የሀገሪቱ ክፍል የንግድና የኢንዱስትሪ ማዕከል በሆነችው ድሬዳዋ በርካታ የልማት ስራዎች መሰራታቸውን የድሬዳዋ አስተዳደር ገቢዎች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አብዱሰላም ሙሀመድ ገልጸዋል፡፡

የነዋሪዎችን የመልካም አስተዳደር እና የመልማት ፍላጎት ለማሟላት የከተማዋን ገቢ በሙሉ አቅም የመሰብሰብ ስልጣን አለው - የድሬዳዋ አስተዳደር ገቢዎች ባለስልጣን፡፡

ከለውጡ አመራር በፊት እንደድሬዳዋ በዓመት የሚሰበሰብ ገቢ 1 ቢሊየን ብር አይሞላም ነበር ያሉት ዶ/ር አብዱሰላም፣ የከተማዋ ግብር ከፋዮች የመክፈል ባህላቸው ከጊዜ ወደ ጊዜ እየዳበረ ስለመጣ፣ አመራሩና ፈጻሚው ልዩ ትኩረት በመስጠቱ፣ ዘርፉን ለማዘመን በትኩረት በመሰራቱ እንዲሁም የባለስልጣኑ የመፈጸም አቅም ከፍ በማለቱ የድሬዳዋ አስተዳደር ገቢዎች ባለስልጣን በ2018 በጀት ዓመት ቀጥተኛ፣ቀጥተኛ ካልሆኑና ከማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎቶች ከ7 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን አስረድተዋል፡፡

በድሬዳዋ ከተማ ያሉ ከፍተኛ ግብር ከፋዮች ለብቻ ቅድሚያ ተሰጥቷቸው የሚገለገሉበት ክፍል አላቸው፡፡

እንደዶ/ር አብዱሰላም ገለጻ፣ግብር ከፋዮች ከእንግልት የጸዳ አገልግሎት ማግኘት እንዲችሉ በገቢዎች ሚኒስቴር በኩል የለሙ ቴክኖሎጂዎች ስራ ላይ ውለዋል፡፡ የአመራር እና የፈጻሚውን አቅም ለመገንባትና የታክስ ተገዢነትን ለማረጋገጥ ከገቢዎች ሚኒስቴር ጋር በቅንጅት እየተሰራ ነው፡፡
የዜጎች የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች የሚመለሱት ግብርን በወቅቱና በታማኝነት መክፈል ሲቻል ነው ያሉት ዶ/ር አብዱሰላም፣ ደሬዳዋን ለነዋሪዎች ምቹ፣ ጽዱ፣ውብ እና አረንጓዴ ለማድረግ የኮሪደር ልማት ስራዎች ተሰርተዋል፡፡የንፁህ መጠጥ ውሃ ተደራሽነትንም ለማሳደግ ከፍተኛ ርብርብ ተደርጓል ብለዋል፡፡

በድሬዳዋ አስተዳደር በገቢ ግብር እየተከናወኑ ካሉ የልማት ፕሮጀክቶች መካከል በሶስት ምዕራፍ እየተገነባ የሚገኘው የውሃ ማጠራቀሚያ ታንከር ተገንብቷል፡፡12 ጥልቅ ጉድጓዶችም በአቅራቢያው ተቆፍረዋል፡፡

በከተማው አጠራር ከአሮጌው ኬላ እስከ ጅቡቲ መንገድ መገንጠያ 4.2 ኪሎሜትር ርዝመት ያለው እንዲሁም፣ከመስቀለኛ ወደ ገንደ ተስፋ የሚወስደው የ1.65 ኪሎሜትር የአስፋልት መንገዶች የተገነቡት ከከተማዋ ግብር ከፋዮች በተሰበሰበ ገቢ ነው፡፡

የገጠር ቀበሌዎችን እርስ በርስ እንዲሁም ከዋና ዋና መንገዶች ጋር ለማገናኘት እየተገነቡ ካሉ የገጠር መንገዶች መካከል ከሀርላ ቀበሌ እስከ አዳዳ2 ያለው የ13 ኪሎ ሜትር መንገድ አንዱ ሲሆን፣ፕሮጀክቱ 74 በመቶው ተጠናቋል፡፡

የድሬዳዋ ዓለማቀፍ ስታዲየም ዓለማቀፍ ደረጃውን ለማሻሻል በራስ አቅም የተለያዩ ስራዎች ተከናውነዋል፡፡የነዋሪዎችን የቤት ጥያቄ ለመመለስም የጋራ መኖሪያ ቤቶች በራስ አቅም ተገንብተዋል ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ፣ከተማዋ ኢንቨስትመንት ላይ የምታውለው ወጪን የመሸፈን አቅሟ ከለውጡ አመራር በፊት 50 በመቶ በታች የነበረ ሲሆን፣ዛሬ ላይ ከ70 በመቶ በላይ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
የድሬዳዋ አስተዳደር ገቢዎች ባለስልጣን ከነዋሪው እና ከንግዱ ማህበረሰብ ገቢን በመሰብሰብ ለከተማዋ ኢኮኖሚያዊ እድገት መሳካት ዘርፈ-ብዙ ስራዎችን እያከናወነ ይገኛል ።
#ድሬቲዩብ

የቡሄ በዓልን በዩኔስኮ ለማስመዝገብ የሚደረገው ጥናት ሂደት ላይ መሆኑ ተገለፀበኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን እምነት ተከታዮች ዘንድ በየዓመቱ ነሐሴ 13 ቀን በድምቀት የሚከበረው...
13/08/2026

የቡሄ በዓልን በዩኔስኮ ለማስመዝገብ የሚደረገው ጥናት ሂደት ላይ መሆኑ ተገለፀ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን እምነት ተከታዮች ዘንድ በየዓመቱ ነሐሴ 13 ቀን በድምቀት የሚከበረውን የቡሄ (ደብረታቦር) በዓልን በተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ የሳይንስ እና የባህል ተቋም (ዩኒስኮ) በማይዳሰስ የአለም ቅርስነት ለማስመዝገብ ሂደቱ በጥናት ላይ መሆኑን የቱሪዝም ሚኒስቴር ለአሐዱ አስታውቋል።

ኢትዮጵያ የብዙሃ ባህል፣ ቅርስና እሴት ባለቤት እንደመሆኗ ያሏትን ቅርሶች በዩኒስኮ ለማስመዝገብ በጥናት ላይ የሚገኙ ብዙ ቅርሶች መኖራቸውን የገለፁት በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የቱሪዝም ማስታወቂያ መሪ ስራ አስፈፃሚ አቶ ተሾመ ተክሉ ናቸው።

ቡሄ በኢትዮጵያ በስፋት ከሚታወቁ በዓላት መካከል አንዱ መሆኑን ያነሱት ስራ አስፈፃሚው በዓሉም በብዛት ልጆች የሚሳተፉበትና የተለያዩ ሀይማኖታዊ ስርዓቶች የሚ ከናወኑበት እንደሆነ ገልፀዋል።

የሀገር ውስጥ ጎብኝዎች ተሳትፎ የማሳደግ እና ለቀጣዩ ትውልድ የማስተላለፋ ሀላፊነት እንደሚጠይቅ አስገንዝበዋል።

በዚህ ረገድም ሚኒስቴሩ በዓላት ስላላቸው ታሪክና ጠቀሜታ እንዲሁም እንዴት ማስቀጠል እንደሚገባ እና ከማን ምን ይጠበቃል በሚሉ ጉዳዮች ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጥ ስራን እንደሚሰራ ተናግረዋል።

በተጨማሪም በበዓሉ ወቅት ህዝቡ ተሳታፊ እንዲሆን የእርስ በእርስ ትስስሩን እንዲ
ጠናከር የማድረግ ስራን እንደሚያከናውን አመላክተዋል።

በስፍራሽ ደመላሽ (አሐዱ ሬዲዮ)

የተሽከርካሪ መለዋወጫዎችን ጥራት ለማሻሻል እና ወደ ኤሌክትሪክ የሚደረገውን ሽግግር ለማፋጠን እየተሰራ መሆኑ ተገለጸየኢትዮጵያ ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ በርኦ ሃሰን ቀደም...
13/08/2026

የተሽከርካሪ መለዋወጫዎችን ጥራት ለማሻሻል እና ወደ ኤሌክትሪክ የሚደረገውን ሽግግር ለማፋጠን እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ

የኢትዮጵያ ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ በርኦ ሃሰን ቀደም ሲል በነዳጅ ተሽከርካሪዎች መለዋወጫዎች ላይ ይስተዋል የነበረውን የጥራት ማነስ እና ህገወጥ አሠራር ለመቅረፍ ሰፊ ሥራዎች መከናወናቸውን አስታወቁ።

ሚኒስትር ዴኤታው እንደገለጹት፤ የዘርፉ አቅርቦት ከዚህ ቀደም ጥራት የጎደለው፣ ለሐሰተኛ ምርቶች የተጋለጠ እና ለተለያዩ ማጭበርበሮች ክፍት ሆኖ ቆይቷል። ይህንን ችግር ለመቅረፍም ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ጠንካራ የአቅርቦት ሰንሰለት ለመዘርጋት ጥረት እያደረገ ይገኛል።

በተጨማሪም ዓለም አቀፍ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪና የመለዋወጫ አምራች ኩባንያዎች በኢትዮጵያ የሽያጭ ማዕከላትንና የማገጣጠሚያ ተቋማትን እንዲመሠርቱ ሁኔታዎች እየተመቻቹ መሆናቸውን ጠቁመዋል።

ነዳጅ የሚጠቀሙ ተሽከርካሪዎችን ወደ ኤሌክትሪክ፣ ሃይብሪድ እና የተፈጥሮ ጋዝ ለመቀየር የሚያስችሉ መሣሪያዎችና መለዋወጫዎች ከቀረጥ ነጻ እንዲገቡ የፖሊሲ ድጋፍ መደረጉንም ተናግረዋል።

በሌላ በኩል የሀገር ውስጥ አምራቾች፣ ተሽከርካሪ ገጣሚዎችና አከፋፋዮች የፋይናንስ አቅም እንዲጠናከር እና ጥራቱን የጠበቀ አሠራር እንዲከተሉ ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ አስገንዝበዋል።

የከተማ እና የሀገር አቋራጭ ታክሲዎችን ወደ ኤሌክትሪክና ሌሎች ጽዱ የኃይል አማራጮች ለማሸጋገር የሚያስችል ስትራቴጂ ተቀርጾ ወደ ሥራ መገባቱንም ሚኒስትር ዴኤታው አክለው ገልጸዋል።

ኢትዮ ኤፍ ኤም

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን ውጤታማ የሚዲያ ሬጉላቶሪ ስርዓትን ለማጠናከር እንዲረዳው ከ11 የመንግስት ተቋማት ጋር የመግባቢያ ስምምነት ፊርማ ስነስርዓት አከናወነ።ዛሬ ነሐሴ 7/20...
13/08/2026

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን ውጤታማ የሚዲያ ሬጉላቶሪ ስርዓትን ለማጠናከር እንዲረዳው ከ11 የመንግስት ተቋማት ጋር የመግባቢያ ስምምነት ፊርማ ስነስርዓት አከናወነ።

ዛሬ ነሐሴ 7/2018 ዓ.ም በስካይላይት ሆቴል በተከናወነው የመግባቢያ ስምምነት መርሐግብር ላይ የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ሃይማኖት ዘለቀ እንደተናገሩት
የመገናኛ ብዙኃን ዘርፍ ቴክኖሎጂ መቀበያና ማሰራጫ አውታር በከፍተኛ ሁኔታ እየዘመነ እንደሚገኝ፣
የዘርፉ ተሳታፊዎችና የሚዲያ ተቋማት ቁጥር በየጊዜው እያደገ ከመምጣቱ አንፃር የሬጉላቶሪ ስራው ውስብስብና ፈታኝ እየሆነ ስለመምጣቱ፣ የቴክኖሎጂ ልማትና ሕግ የማስፈጸም ስራዎችን በተናጠል መስራት ውጤታማ እንዳይሆን አድርጎታል። አያይዘውም የፈቃድ፣ የምዝገባ፣ የክትትልና ቁጥጥር ስራዎች ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ባለመተሳሰራቸው በተናጠል የሚወሰድ ድጋፍና እርምጃ ውጤቱ አጥጋቢ አይደለም ብለዋል።

በመሆኑም በሀገር ደረጃ የመገናኛ ብዙኃን የክትትል፣ የአቅም ግንባታና የቴክኖሎጂ ልማት ስራዎችን ከሕግ አስፈፃሚና የቴክኖሎጂ ቁጥጥር ተቋማት ጋር በቅንጅት መስራት አስፈላጊ መኾኑን ጠቅሰዋል።

በፊርማ ስነስርዓቱ የታቀፉት በድምሩ 16 ተቋማት ሲኾኑ በአካል ተገኝተው በዛሬው ዕለት ስምምነት የፈረሙት 11 ተቋማት ናቸው። በተለያየ ምክንያት በዛሬው ዕለት ያልተገኙ ተቋማትን ጨምሮ ከሌሎችም ጋር መሰል ትብብር እንደሚቀጥል ዋና ዳይሬክተሯ ሃይማኖት ዘለቀ ተናግረዋል።

በስምምነቱ የታቀፉ ተቋማት የብሔራዊ መረጃና ደህንነት፣ የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ የፍትሕ ሚኒስቴር፣ የመከላከያ ሚኒስቴር፣ ንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር፣ ኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት፣ የፋይናንስ ደህንነት አገልግሎት፣ አርተፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት፣ የኢምግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት፣
የጉምሩክ ኮሚሽን፣ የኮሚኒኬሽን ባለሥልጣን፣
መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት፣
የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለሥልጣን፣ የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ ናቸው።

በአሁን ሰዓት በጠቅላላ 329 የመገናኛ ብዙሃን ፈቃድ አግኝተው እየተንቀሳቀሱ መኾኑ ተጠቁሟል።
📷 ከበደ መክብብ

#ድሬቲዩብ

በመኰንን ሸገኔ ስም ሽልማት ሊሰጥ ነው በርካታ ተማሪዎችን ባፈሩት ፣ ከ 50 አመት በፊት ሕይወታቸው ባለፈው በመምህር መኮንን ሸገኔ ስም ሽልማት ሊሰጥ ነው። የአርአያ ሰው ሽልማት  ፋውንዴሽ...
13/08/2026

በመኰንን ሸገኔ ስም ሽልማት ሊሰጥ ነው

በርካታ ተማሪዎችን ባፈሩት ፣ ከ 50 አመት በፊት ሕይወታቸው ባለፈው በመምህር መኮንን ሸገኔ ስም ሽልማት ሊሰጥ ነው።

የአርአያ ሰው ሽልማት ፋውንዴሽን ፕሬዚዳንት ዲያቆን ፍሬው ሰይፉ ለተወዳጅ ሚድያ እንደተናገሩት በየዓመቱ በሚሰጠው የአርአያ ሰው ሽልማት ላይ ዘንድሮ ነሐሴ 16 2018 ዓ.ም በሚደረገው ሥነ ሥርዓት ሽልማቱ መታሰቢያ የተደረገው ለመምህር መኮንን ሸገኔ ነው ብለዋል። በተጨማሪም በየአመቱ 'የመኮንን ሸገኔ ሽልማት' በሚል ዘርፍ ለተለያዩ ሰዎች እውቅና እንደሚሰጥ ታውቋል።

የአባቷን ታሪክ በማፃፍና ለቁምነገር እንዲበቃ በማድረግ የአንበሳውን ድርሻ የተወጣችው ልጃቸው ካቢው መኮንን ሸገኔ ስትሆን የዛሬ አመት በሰኔ 2017 መኮንን ሸገኔ የሀገር ባለውለታ" የሚል መጽሐፍ በዕዝራ እጅጉ ተፅፎ መመረቁ ይታወቃል።

ኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለማሪያምን ጨምሮ በርካታ ምሁራንን ለወግ ማዕረግ ያበቁት መምህር መኮንን በአገር ውስጥ እና በባህር ማዶ በሚገኙ ተማሪዎቻቸው ዘንድ የሚወደዱ እና የሚከበሩ እንደሆኑ ይታወቃል።

መኰንን ሸገኔ፣ የዛሬ 49 ዓመት ሕይወታቸው ያለፈ የዳግማዊ ምኒሊክ፣የድሬደዋ ልዑል መኰንን ፣እና የአዲስ አበባ ልዑል መኰንን ትምህርት ቤቶች ርዕሰ- መምህር የነበሩ ሲሆን በሥራ ላይ ሳሉ በተተኮሰባቸው ጥይት ህይወታቸው ማለፉ ይታወቃል።

ህይወታቸው ሲያልፍ ገና የ5 ዓመት ልጅ የነበረችው ካቢው መኮንንም አባቴ የእኔ ብቻ ሳይሆን የመላ ኢትዮጵያዊያን አባት ነው ብላ በማመን ስለ አባቷ ለትውልዱ አንድ አሻራ ለማኖር መነሳቷን ትናገራለች። የአርአያ ሰው ሽልማትም ለመኮንን ሸገኔ ለሰጠው ዕውቅና ምስጋናዋን አቅርባለች።

በዳላስ በሚደረገው የእውቅና ሥነ -ሥርዓት የመኮንን ሸገኔ ቤተሰቦችን ጨምሮ ከተለያዩ ክፍለ -ግዛቶች የመጡ የቀድሞ ተማሪዎች ይታደማሉ ተብሎ ይጠበቃል።

በዳላስ የሚሰጠው የአርአያ ሰው ሽልማት ከተመሠረተ 10 ዓመት ያስቆጠረ ሲሆን' እናቀዳድማለን እንጂ አናወዳድርም' የሚለውን መርህ አንግቦ ዘንድሮ ለአገር ባለውለታዎች እውቅና ይሰጣል።

ግርማ ሰይፉ፤ በሀገራዊ ምክክሩ ጉዳይ አንዳንድ ሚዲያዎችን ወቀሱሀገራዊ ምክክር  መጀመር ትልቅ ዜና ነው። ምክንያቱም ኢትዮጵያዊያን በተለያየ አጀንዳዎች ልዩነቶች አሉን። ልዩነት የምንፈታው ደ...
13/08/2026

ግርማ ሰይፉ፤ በሀገራዊ ምክክሩ ጉዳይ አንዳንድ ሚዲያዎችን ወቀሱ

ሀገራዊ ምክክር መጀመር ትልቅ ዜና ነው። ምክንያቱም ኢትዮጵያዊያን በተለያየ አጀንዳዎች ልዩነቶች አሉን። ልዩነት የምንፈታው ደግሞ በጉልበት/በጠብመንጃ ነው። ከዚህ የተለየ አማራጭ ሲጀመር ትልቅ ዜና ነው። ሀገራችንን "እንወዳለን" የሚሉ በውጭ ያሉ የተለያዩ "ሚዲያዎች" ይህ ዜና አልሆን ብሏቸው ስንብቷል። እንወዳታለን የሚሉትን ሀገር እየነከሱ ፍቅር አልገባ ብሎኛል።

እነዚሁ አካላት አሁን ደግሞ መግባባት የተደረስባቸው ሳይሆኑ፣ ቀድሞም የልዩነት ነጥብ የነበሩ ጉዳዮች ልዩነት ሆን ብለው ዜና እና ሰበር ዜና እያደረጉት ይገኛል። ጎበዝ በዚህ ዘመን ዜና ምንድነው? ብሎ ጎግል መጠየቅ እንዴት ይከብዳል?

ጎበዝ ቀድሞም ለምክክር የተቀመጥነው ልዩነት ስላለን ነው። ይህ ዜና አይሆንም። ዜና የሚሆነው፣ ልዩነት ያላቸው ሃሳቦች በስለጠነ መንገድ ውይይት ማድረግ መቻሉ ነው። ከታገሳችሁ የስነስርዓት ጉዳይ ሆኖብን እንጂ ዜና የሚሆኑ፣ እንደ ጉድ የሚተረኩ ጉዳዮች አሉ።

ጨዋነት ይዞን፣ ሀገር ብለን ዋጥ ያደረግነው፣ የምክክር ሂደቶች አሉ። ዱብ እዳ አይደሉም። ግርምት የሚፈጥሩ፣ ዋው! የሚያስብሉ ናቸው። ጥሩ ዜና መዋል ካለ በቅጡ ይሰንዳቸዋል። በነገራችሁ ላይ ሁሉም እንቅስቃሴ በኮምሽኑ ሪከርድ የሚደረግ ነው። ያልሆነ ሆነ ብሎ ተረት ተረት ማቅረብ ወደፊትም አይቻልም። ይህ ታሪክ ነው። ጎበዝ ዜናውን በአግባቡ ካልስራችሁ የታሪኩ አካል አትሆኑም።

አትክልተኛው፣ የደሴቲቱ ነዋሪ!!
ከምክክር ደጃፍ!!

የአውሮፓ ሰማይ ተከደነ! አስደናቂው የፀሐይ ግርዶሽ አህጉሪቱን ወደ ሌሊት ጨለማ ቀየራት በአውሮፓ አህጉር ከ27 ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ የታየውና የብዙዎችን ቀልብ የሳበው ታላቁ የሙሉ ...
13/08/2026

የአውሮፓ ሰማይ ተከደነ! አስደናቂው የፀሐይ ግርዶሽ አህጉሪቱን ወደ ሌሊት ጨለማ ቀየራት

በአውሮፓ አህጉር ከ27 ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ የታየውና የብዙዎችን ቀልብ የሳበው ታላቁ የሙሉ ፀሐይ ግርዶሽ የተከሰተ ሲሆን፣ የስፔን፣ አይስላንድ እና ግሪንላንድን ክፍሎች ለአጭር ደቂቃዎች ወደ ሙሉ ጨለማ ለውጧቸዋል።

ጨረቃ በፀሐይ እና በምድር መካከል ሙሉ በሙሉ በመጋረዷ ምክንያት፣ ድንገተኛ የሌሊት ጨለማ በሰማይ ላይ ሰፍኖ የነበረ ሲሆን፣ በተመሳሳይ ሰዓትም ከዋክብት እና ፕላኔቶች በግልጽ ይታዩ ነበር።

በስፔን በሚገኙ ከተሞችና የባህር ዳርቻዎች ከተሰበሰቡት በመቶ ሺዎች ከሚቆጠሩ ጎብኚዎች መካከል አንዱ እንደገለጹት፣ ከሰዓታት በፊት የነበረው ሞቃታማ የፀሐይ ብርሃን በቅጽበት ጠፍቶ አየሩ ሲቀዘቅዝ እና አካባቢው ሲጨልም የሚፈጥረው ስሜት ከአንደበት በላይ እንደሆነ ተናግረዋል።

በአይስላንድና በስፔን ሰማይ ላይ የታየው ይህ አስደናቂ ክስተት፣ ከፊል የፀሐይ ግርዶሽ ሆኖ በሌሎች የምዕራብ አውሮፓና ሰሜን አፍሪካ አገራትም ሊታይ ችሏል።
(መናኸሪያ ራዲዮ)

አጋዝእተ ዓለም ሥላሴ ከክፉ ነገር ሁሉ ይከልሉን፤ የልባችንን መልካም መሻትም ይሙሉልን🙏በኦሪት ዘፍጥረት ምዕራፍ 11፥1-9 እና በቅዱሳት አዋልድ መጻሕፍት ተጽፎ እንደምናገኘው ከጥፋት ውሃ በ...
13/08/2026

አጋዝእተ ዓለም ሥላሴ ከክፉ ነገር ሁሉ ይከልሉን፤ የልባችንን መልካም መሻትም ይሙሉልን🙏

በኦሪት ዘፍጥረት ምዕራፍ 11፥1-9 እና በቅዱሳት አዋልድ መጻሕፍት ተጽፎ እንደምናገኘው ከጥፋት ውሃ በኋላ የኖኅ የትውልድ ነገዶች ከምሥራቅ ተነሥተው በሄዱ ጊዜ በሰናዖር ምድር አንድ ሜዳ አገኙ፤ በዚያም ተቀመጡ፤ ወልደው ተዋልደው ብዙዎች ሆኑ፡፡ በኋላም “ሳንሞት ስም ማስጠሪያ ግንብ እንገንባ” ብለው መከሩ፡፡ አለቃቸው ናምሩድም “ሞትን የሚያመጡብን ሥላሴ ናቸውና እነርሱን ወግተን ሞትን እናርቅ” አላቸው፡፡ ይህንም ለማድረግ ሰማይ ጠቀስ ግንብ ይገነቡ ጀመር፡፡ እግዚአብሔርም አለ “ኑ እንውረድ አንዱ አንዱን እንዳይሰማው በዚያ ቋንቋቸውን እንገለባብጠው”፡፡ ቅድስት ሥላሴ ምሕረታቸው የበዛ ቢሆንም በሕዝቡ ላይ ዲያብሎስ ስለሠለጠነባቸውና ለሌሎች ከሀድያን ትምህርት ይሆን ዘንድ ቋንቋቸውን ደበላለቁባቸው፡፡

እነርሱም የማይግባቡ፣ የማይደማመጡ፣ ሆነው ተበታትነዋል፡፡ ባለማስተዋል የሠሩትንም ሕንፃ ዓመጻ ነፋስ ጠራርጎ አጥፍቶታል፡፡ ያም ስፍራ ባቢሎን ተባለ። እነርሱንም በምድር ሁሉ ላይ በትኖአቸዋል። ይህን ያደረጉ ሥላሴ በመሆናቸው በዓሉ ጥር 7 ይከበራል፡፡ በዚህ የመጽሐፍ ክፍል ውስጥ “እግዚአብሔርም አለ” ብሎ አንድነቱን ከነገረን በኋላ “ኑ እንውረድ፤ አንዱ የአንዱን ነገር እንዳይሰማው ቋንቋቸውን በዚያ እንደባልቀው።” የሚል ከአንድ በላይ መሆንን የሚያመለክት ዓረፍተ ነገር ያስቀምጥልናል፡፡ ይህም በበርካታ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች የተገለጸ ሦስትነት እንደሆነ እንረዳለን፡፡ በዘፍ 1÷26 “እግዚአብሔርም አለ ሰውን በመልካችን እንደ ምሳሌያችን እንፍጠር” የሚለው ቃል “እግዚአብሔርም አለ” ብሎ አንድነቱን “ሰውን በመልካችን እንፍጠር” ብሎ ልዩ ሦስትነትን ይገልጻል፡፡

ቅድስት ሥላሴ ተብለው በሴት አንቀጽ የሚጠሩት አጋእዝተ ዓለም ሥላሴ፣ በሴት መጠራታቸው የፍጹም ርህራሄያቸው፣ የቸርነታቸው ማሳያ ነው፡፡ አንድም ሦስትም ብላ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ታስተምረናለች፡፡ ይህ አንድነትና ሦስትነት እደምን ነው ቢሉ… በስልጣን፣ በአገዛዝ፣ በመለኮት፣ በሕልውና፣ በመፍጠር በመሳሰሉት አንድ ናቸው እንላለን፡፡ ልዩ ሦስትነታቸውም በስም “አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ” ብለን፣ በግብር “አብ ወላዲ ወይም አባት፣ ወልድ ተወላዲ ወይም ልጅ፣ መንፈስ ቅዱስ ሰራጺ፣ ከአብ የሰረጸ የወጣ” ማለት ነው፡፡ በአካል “ለአብ ፍጹም አካል ፍጹም ገጽ ፍጹም መልክ አለው ነው፤ ለወልድም ፍጹም አካል ፍጹም ገጽ ፍጹም መልክ አለው፤ ለመንፈስ ቅዱስም ፍጹም አካል ፍጹም ገጽ ፍጹም መልክ አለው” ብለን እናምናለን፡፡

የሥላሴ ገጽ አካልና ፊት እንደ ሰው ነውን? የሚል ጥይቄ ቢነሣ መልሱ “አዎ፤ እንደ ሰው ነው” የሚል ነው፡፡ ነገር ግን የሰው ገጽ አካልና ፊት ውሱን፣ ጠባብ፣ ፈራሽና በስባሽ ነው፤ የሥላሴ ግን እንዲህ አይደለም፤ በሰማይና በምድር፣ በአየርና በእመቅ የመላ ረቂቅ ሕያው ባሕርይ ነው፡፡ ታላቁ ነቢየ እግዚአብሔር ቅዱስ ኢሳይያስ በምዕራፍ 86÷1-2 እንደጻፈው “ሰማይ ዙፋኔ ነው፤ ምድርም የእግሬ መረገጫ ናት፤ የምትሠሩልኝ ቤት ምን ዓይነት ነው? የማርፍበትስ ስፍራ ምንድን ነው? ይህ ሁሉ የእጄ ሥራ ነው፤ ይህም ሁሉ የእኔ ነው” ይለናል በአንድነት በሦስትነት የሚመሰገን የሚመሰጠር ቅዱስ እግዚአብሔር፡፡

በዚህ ልዩ ሦስትነት አምነን የተጠመቅንና እኛ ክርስቲያኖች የሥላሴን በረከት ለመቋደስ በበረከት ስራ እንሳተፍ፡፡ የትምህርቱ ምንጭ የሆኑትን ገዳማት እንርዳ፣ የገዳማውያኑን በዓት እናጽና፡፡

ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

ለበለጠ መረጃ:- 09 38 64 44 44/0918077957

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when DireTube posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to DireTube:

Shortcuts

Share