
15/04/2025
አርቲስት ሰላም ተስፋዬ የፖፕላር ኤሌክትሮኒክስ ትሬዲንግ ብራንድ አምባሳደር ሆነች
አርቲስት ሰላም ተስፋዬ ከፖፕላር ኤሌክትሮኒክስ ትሬዲንግ ጋር የብራንድ አምባሳደርነት የስራ ውል ስምምነት ዛሬ ሚያዝያ 7/2017 ዓ.ም ተፈራርማለች።
አርቲስት ሰላም ተስፋዬ በፖፕላር ኤሌክትሮኒክስ ትሬዲንግ ለቴሌቪዥን፤ ቢል ቦርድ እና ሶሻል ሚዲያዎች ላይ ማስታወቂያዎችን የምትሰራ ይሆናል።
ፖፕላር ኤሌክትሮኒክስ ትሬዲንግ የተለያዩ የኤሌክትሮኒክስ ምርቶችን ከውጭ በማስመጣት የሚታወቅ ድርጅት ሲሆን በዛሬው እለትም አዲስ በከፈተው ሾው ሩም አርቲስት ሰላም ተስፋዬን ብራንድ አምባሳደር አድርጎ ሾሟል።
የአርቲስቷ የአምባሳደርነት ስምምነት ለአንድ ዓመት የሚቆይ ይሆናል።
Telegram: https://t.me/FirtunaMedia
Facebook: https://www.facebook.com/firtunamedia/
Instagram: https://www.instagram.com/firtunamedia/
Tiktok : https://www.tiktok.com/
Stay with us.
አብራችሁን ቆዩ