Firtuna

Firtuna Firtuna is an Ethiopian-based entertainment news company

Firtuna is a media and production company that provides Art Related news Daily which has a vision of Transforming the Ethiopian art industry to the next level.

አርቲስት ሰላም ተስፋዬ የፖፕላር ኤሌክትሮኒክስ ትሬዲንግ ብራንድ አምባሳደር ሆነችአርቲስት ሰላም ተስፋዬ ከፖፕላር ኤሌክትሮኒክስ ትሬዲንግ ጋር የብራንድ አምባሳደርነት የስራ ውል ስምምነት ዛሬ...
15/04/2025

አርቲስት ሰላም ተስፋዬ የፖፕላር ኤሌክትሮኒክስ ትሬዲንግ ብራንድ አምባሳደር ሆነች

አርቲስት ሰላም ተስፋዬ ከፖፕላር ኤሌክትሮኒክስ ትሬዲንግ ጋር የብራንድ አምባሳደርነት የስራ ውል ስምምነት ዛሬ ሚያዝያ 7/2017 ዓ.ም ተፈራርማለች።

አርቲስት ሰላም ተስፋዬ በፖፕላር ኤሌክትሮኒክስ ትሬዲንግ ለቴሌቪዥን፤ ቢል ቦርድ እና ሶሻል ሚዲያዎች ላይ ማስታወቂያዎችን የምትሰራ ይሆናል።

ፖፕላር ኤሌክትሮኒክስ ትሬዲንግ የተለያዩ የኤሌክትሮኒክስ ምርቶችን ከውጭ በማስመጣት የሚታወቅ ድርጅት ሲሆን በዛሬው እለትም አዲስ በከፈተው ሾው ሩም አርቲስት ሰላም ተስፋዬን ብራንድ አምባሳደር አድርጎ ሾሟል።

የአርቲስቷ የአምባሳደርነት ስምምነት ለአንድ ዓመት የሚቆይ ይሆናል።



Telegram: https://t.me/FirtunaMedia
Facebook: https://www.facebook.com/firtunamedia/
Instagram: https://www.instagram.com/firtunamedia/
Tiktok : https://www.tiktok.com/

Stay with us.
አብራችሁን ቆዩ

ሙዚቀኛው ሞቶ ተገኘ!የቀድሞ ሮሀ ባንድ ሳክስፎኒስቱ በመኖሪያ ቤቱ ሞቶ ተገኘከቀደምት ሮሀ ባንድ አባላት መካከል ተጠቃሹ አርቲስት ስምኦን ሊባኖስ በመኖሪያ ቤቱ ሕይወቱ አልፎ እንደተገኘ ጋዜጠ...
14/04/2025

ሙዚቀኛው ሞቶ ተገኘ!

የቀድሞ ሮሀ ባንድ ሳክስፎኒስቱ በመኖሪያ ቤቱ ሞቶ ተገኘ

ከቀደምት ሮሀ ባንድ አባላት መካከል ተጠቃሹ አርቲስት ስምኦን ሊባኖስ በመኖሪያ ቤቱ ሕይወቱ አልፎ እንደተገኘ ጋዜጠኛ ግርማ ፍስሃ የአርቲስቱን የቀድሞ ስራ ባልደረባና ጓደኛ ሙዚቀኛ ዳዊት ይፍሩን ዋቢ አድርጎ ዘግቧል።

" ከደቂቃዎች በፊት ጋሽ ዳዊት ይፍሩ እንዲህ አለኝ.. "እጅግ አሳዛኝ ሁኔታ ውስጥ ነን። የዛን ዘመን የሮሃ ባንድ ሳክስፎኒስት የቀድሞ የስራ ባልደረባዬና ጓደኛዬ የነበረው አርቲስት ስሞኦን ሊባኖስ ( ዮናስ ደገፉ) ዛሬ ህንድ ኢንባሲ አካባቢ በሚገኘው መኖሪያ ቤት ህይወቱ አልፎ ተገኝቷል።
ለምርመራው የአዲስ አበባ ፖሊስ አስክሬኑን ወስዷል"አለኝ።

ግን ሌላው የሚያሳዝነው ቤተሰቦቹን ማግኘት አልተቻለም ። እና ቤተሰቡ ወይም ወዳጆቹ አዲስ አበባ ፖሊስ መጠየቅ ትችላላችሁ። " ሲል መረጃውን አጋርቷል።

ባሉበት ሆነው ትኩስ እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኝት ቤተሰብ ይሁኑ።

"""""""""""***""""""""""


Telegram: https://t.me/FirtunaMedia
Facebook: https://www.facebook.com/firtunamedia/
Instagram: https://www.instagram.com/firtunamedia/
Tiktok : https://www.tiktok.com/

Stay with us.
አብራችሁን ቆዩ

ሰይፍ ፋንታሁን ህመም ገጥሞት እንደነበረ ተናገረ ዝነኛው የቴሌቪዥን እና ሬድዮ ፕሮግራሞች አቅራቢ ሰይፉ ፋንታሁን ትንሽ ህመም ገጥሞት እንደነበረ  በማህበራዊ ትስስር ገፁ አስታወቀ።ሰይፉ ፋን...
12/04/2025

ሰይፍ ፋንታሁን ህመም ገጥሞት እንደነበረ ተናገረ

ዝነኛው የቴሌቪዥን እና ሬድዮ ፕሮግራሞች አቅራቢ ሰይፉ ፋንታሁን ትንሽ ህመም ገጥሞት እንደነበረ በማህበራዊ ትስስር ገፁ አስታወቀ።

ሰይፉ ፋንታሁን በማህበራዊ ትስስር ገፁ"ቀለል ያለውን አድርጎልኛል።እግዚአብሔር ይመስገን።በዚህ ሳምንት ወደ ስራ እመለሳለሁ" ብሏል።

በሙዚቀኛ ኤልያስ መልካ ስም የተሰየመው የሮያሊቲ ክፍያ ማስገኛ ሥርዓት ይፋ ሆነበተወዳጁ የሙዚቃ ባለሙያ ኤልያስ መልካ ስም የተዘጋጀው የሙዚቃ ሮያሊቲ መሰብሰቢያ ሥርዓት በዛሬው ዕለት በይፋ ...
01/04/2025

በሙዚቀኛ ኤልያስ መልካ ስም የተሰየመው የሮያሊቲ ክፍያ ማስገኛ ሥርዓት ይፋ ሆነ

በተወዳጁ የሙዚቃ ባለሙያ ኤልያስ መልካ ስም የተዘጋጀው የሙዚቃ ሮያሊቲ መሰብሰቢያ ሥርዓት በዛሬው ዕለት በይፋ ተዋውቋል።

ሥርዓቱ ኤልያስ መልካ የኢትዮጵያ ሙዚቃ ሮያሊቲ መሰብሰቢያ ወይም (EMEMRC) የሚል መጠሪያ የተሰጠው ነው።

የኢትዮጵያ የቅጅና ተዛማጅ መብቶች የጋራ አስተዳደር እና የኢትዮጵያ የሙዚቃ ቅጅና ተዛማጅ መብቶች የጋራ አስተዳደር የሮያሊቲ ክፍያ አሰባሰብን አስመልክቶ በጋራ ያዘጋጁትን የሮያሊቲ ክፍያ ቀመር ለማፅደቅ ውይይት እየተካሄደ ይገኛል።

የኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ባለስልጣን የቀረበለትን ቀመር ለማፅደቅ ከሚዲያ አመራሮችና ከፈጠራ ባለሙዎች ጋር እየተወያየ ሲሆን፥ ተቋማት የሚከፍሉት የሮያሊቲ ክፍያ የገቢ አቅማቸውን መሰረት በማድረግ 24 ሠአት የሙዚቃ ውጤቶችን ይጠቀማሉ ተብሏል።

የሙዚቃ ተጠቃሚዎች በዓመትና በጊዜያዊነት ክፍያ መፈፀም እንደሚችሉም ተሰምቷል።

ለአዕምሯዊ ንብረት ባለስልጣን በቀረበው ቀመር መሰረት ተቋማቱ በ24 ሠአት ውስጥ 360 እነዲሁም በዓመት ደግሞ 131 ሺህ 400 ሙዚቃዎችን እንደሚያጫውቱ ተመላክቷል።

የሙዚቃ ባለሙያውም በተጫወተለት የሙዚቃ መጠን የሚከፈለው ሲሆን፥ ባለስልጣኑና ሁለቱ ማህበራት በዛሬው ዕለት የሮያሊቲ ክፍያ ቀመርን ያፀድቃሉ ተብሎ ይጠበቃል ሲል አራዳ ኤፍ ኤም 95.1 ዘግቧል።

Firtuna

📌ከድምጻዊ አንዱዓለም ጎሳ እጮኛ ቀነኒ አዱኛ ህልፈት ጋር በተያያዘ እስካሁን ያሉ መረጃዎች የድምጻዊ አንዱዓለም ጎሳ እጮኛ ሞትን በተመለከተ በርካታ መረጃዎች እየወጡ ይገኛሉ። ከመሞቷ አንድ ...
11/03/2025

📌ከድምጻዊ አንዱዓለም ጎሳ እጮኛ ቀነኒ አዱኛ ህልፈት ጋር በተያያዘ እስካሁን ያሉ መረጃዎች

የድምጻዊ አንዱዓለም ጎሳ እጮኛ ሞትን በተመለከተ በርካታ መረጃዎች እየወጡ ይገኛሉ።

ከመሞቷ አንድ ቀን በፊት የት ነበረች? የድምጻዊው ማናጀር ስለልጅቷ ተናግሯል።

በኢንጂነሪንግ ድግሪ ከአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ የተመረቀችው ቀነኒ በሞዴሊንግ በማስታወቂያ ሥራዎች በማኅበራዊ ሚድያ ዝናን አትርፋለች።

በሚቀጥለው ቅዳሜ ልደቷን ለማክበር በሚል ፎቶዎች እየተነሳች እንደነበር ከቅርብ ሰዎቿ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

ልጅቱ ከመሞቷ አንድ ቀን በፊት የት ነበረች?

ልጅቱ ከመሞቷ አንድ ቀን በፊት ለልደቷ ፎቶ ስትነሳ እንደነበር በወቅቱ ፎቶ ያነሳት የነበረው የወንዴክስ ስቱዲዮ ባለቤት ወንድወሰን ጋሻው ተናግሯል ።

ፎቶግራፈሩም "በፎቶግራፍ ስራዎች ካፈራዋቸው ወዳጆቼ መካከል የቀኝ እጄ የምላት እህቴ ቀነኒ አዱኛ መካሪዬ ጎደኛዬ የክፉ ቀን ወዳጄ ነበረች።

ትላንት መጋቢት 1 2017 ዓ.ም ከቀኑ 10:00 ጀምሮ የልደት ፎቶዎች ሳነሳት ነበር ማታ 1:00 በሰላም ተለያየትን ዛሬ ጠዋት መጋቢት 2 2017 ዓ.ም ጠዋት ማረፏን አረዱኝ" ብሏል።

በተጨማሪም ትላንትና መጋቢት 1 2017 ዓ.ም አመሻሹን ቀነኒ አዱኛ ከእጮኛዋ ድምጻዊ አንዱዓለም ጎሳ ጋር በመዝናኛ ስፍራ አብረው እንዳሳለፉም ከተለያዩ ምንጮች ኤቨንት አዲስ ሚዲያ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።

የድምፃዊ አንዱአለም ጎሳ ማናጀር የሆነው ለሊሣ እንድሪስ የተፈጠረውን ለቢቢሲ አፋን ኦሮሞ ተናግሯል።

"ንጋት 11:00 ሰዓት ስልክ ተደውሎ «ቀነኒ ተጎድታ ሆስፒታል ገብታለች ቶሎ ድረስ» እንደተባለ የሚናገረው ለሊሳ እሱ ሩቅ በመሆኑ በሰዓቱ መድረስ እንዳልቻለ ይናገራል።

ቦሌ አራብሳ ከዓመት በላይ በጋራ ከሚኖሩበት መኖሪያ ቤታቸው ከአምስተኛ ፎቅ እንደወደቀች እና ምን እንደተፈጠረ ፖሊስ እያጣራ መሆኑ ተነግሯል።

ክስተቱ ከተፈጠረ በኋላ በቅርብ በሚገኘው ያኔት ሆስፒታል ከገባች በኋላ ጠዋት ፖሊስ መጥቶ ሬሳዋን ወደ ሚኒሊክ ሆስፒታል ለምርመራ ከወሰደ በኋላ የምርመራ ውጤት እስኪወጣ አስክሬኗ ወደ ቤተሰቦቿ ሱሉልታ መሄዱ ነው የተገለፀው።

ድምፃዊ አንዱዓለም ጎሳ ለጥያቄ ትፈለጋለህ ተብሎ ከሆስፒታል ወደ ፖሊስ ጣቢያ ተወስዶ እዛ የሚገኝ ሲሆን እኛ የምናውቀው እስካሁን አለመታሰሩን ነው ምርመራ እናድርግ ብሎ ነው ፖሊስ የወሰደው ሲል ማናጀሩ ይናገራል።

ለሁለት አመታት በፍቅር ከቆዩ በኋላ በቅርቡ ጋብቻቸውን ለመፈፀም እየተዘጋጁ እንደሆነ አውቃለሁ ሲል ለሊሳ ይናገራል።

ፖሊስም ምን አለ?

የልጅቱ አሟሟት ምን እንደሆነ የምርመራ ስራ ተሰርቶ እስኪገለጹ ድረስ ህብረተሰብ በትዕግሥት ይጠብቅ።አንዳንድ ግለሰቦች ተገቢ ካልሆነ ትንታኔ ይታቀቡ ብሏል።

📸ፎቶው ትላንት ለልደቷ ተነሳችው ፎቶ ነበር።

የአንዱዓለም ጎሳ ባለቤት ህልፈት የድምፃዊ አንዷለም ጎሳ ባለቤት ቀነኒ አዱኛ በድንገት ሕይወቷ ማለፉ ተሰምቷል፡፡ የቀነኒን አሟሟት በተመለከተ ፖሊስ ምርመራ ላይ እንዳለ አሳውቋል ።ቀነኒ አዱ...
11/03/2025

የአንዱዓለም ጎሳ ባለቤት ህልፈት

የድምፃዊ አንዷለም ጎሳ ባለቤት ቀነኒ አዱኛ በድንገት ሕይወቷ ማለፉ ተሰምቷል፡፡ የቀነኒን አሟሟት በተመለከተ ፖሊስ ምርመራ ላይ እንዳለ አሳውቋል ።

ቀነኒ አዱኛ ፤ ከመሞቷ ከ12 ሰዓታት በፊት በቲክቶክ የማኀበራዊ የመገናኛ ድረገጽ ላይ ደስተኛ ሆና በመጨፈር ቪዲዮ ለቃ ነበር ።

ለድምፃዊ አንዷለም ጎሳ፣ ለቤተሰቦቿ እንዲሁም ለወዳጅ ዘመዶች ፈጣሪ መፅናናቱን ይስጥልን ።


Telegram: https://t.me/FirtunaMedia
Facebook: https://www.facebook.com/firtunamedia/
Instagram: https://www.instagram.com/firtunamedia/
Tiktok : https://www.tiktok.com/

Stay with us.
አብራችሁን ቆዩ

ድምጻዊ ዘሩባቤል ሞላ በፕሪስቴጅ አዲስ ዝግጅት ላይ እንግዳ በመሆን ይቀርባል።(መግቢያው በነፃ ነው)የተለያዩ የጥበብ ባለሞያዎችን እየጋበዝ ልምዶቻቸውን እንዲያጋሩ እያደረገ ያለው ፕሪስቴጅ አ...
01/02/2025

ድምጻዊ ዘሩባቤል ሞላ በፕሪስቴጅ አዲስ ዝግጅት ላይ እንግዳ በመሆን ይቀርባል።

(መግቢያው በነፃ ነው)

የተለያዩ የጥበብ ባለሞያዎችን እየጋበዝ ልምዶቻቸውን እንዲያጋሩ እያደረገ ያለው ፕሪስቴጅ አዲስ መርሐግብር ዘሩባቤል ሞላን ጋብዟል::

የፕሪስቴጅ አዲስ አዘጋጆች"ከድምጻዊ ዘሩባቤል ሞላ ጋራ በሚኖረን ቆይታ የሥራ፣ የህይወት ልምድ እና ተሞክሮውን የሚያካፍለን ሲሆን ከእናንተ ከወዳጅ እና አድናቂዎቹ የሚቀርቡለትን ጥያቄዎች ደግሞ የፊታችን ማክሰኞ ጥር 27 2017 ዓ.ም መልስ ለመስጠት ቀጠሮ ይዘናል" ሲሉ ለኤቨንት አዲስ ሚዲያ ገለጸዋል።

በዕለቱ ከአርቲስቱ ጋር የፎቶግራፍ መነሳትና አውቶግራፍ የማስፈረም መርሃግብር ይኖራል ተብሏል::

ፕሪስቴጅ አዲስ ከዘሩባቤል ሞላ ጋር የሚያደረገው አዝናኝ እና አስተማሪ ቆይታ ማክሰኞ ጥር 27 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 8:00 ጀምሮ አሜሪካን ኢምባሲ ቅጥር ግቢ ውስጥ ( ከስድስት ኪሎ ወደ ሽሮሜዳ መሄጃ ) ይካሄዳል።በዝግጅቱ ላይ ለመታደም ከታች ያለውን ሊንክ በመንካት ይመዝገቡ:
https://bit.ly/SatchmoCenterMembership

መታወቂያ መያዝ እንዳይረሳ፣ማርፈድ ወደ ውስጥ እንዳትገቡ ያደርጋል ፕሮግራሙ ከመጀመሩ ቀደም ብላችሁ ለመገኘት ሞክሩም ተብላችኋል።

ለተጨማሪው:

Telegram: https://t.me/FirtunaMedia
Facebook: https://www.facebook.com/firtunamedia/
Instagram: https://www.instagram.com/firtunamedia/
Tiktok : https://www.tiktok.com/

Stay with us.
አብራችሁን ቆዩ

የሙዚቃ ባለሞያ ተፈሪ አሰፋ አረፈ የድራም የሙዚቃ መሳሪያ ተጫዋቹ እና የነጋሪት ባንድ መስራች የሆነው ተፈሪ አሰፋ ከዚህ ዓለም በሞት እንደተለየ ተሰምቷል።ተፈሪ አሰፋ የኢትዮጵይ ሙዚቃ ካለበ...
24/01/2025

የሙዚቃ ባለሞያ ተፈሪ አሰፋ አረፈ

የድራም የሙዚቃ መሳሪያ ተጫዋቹ እና የነጋሪት ባንድ መስራች የሆነው ተፈሪ አሰፋ ከዚህ ዓለም በሞት እንደተለየ ተሰምቷል።

ተፈሪ አሰፋ የኢትዮጵይ ሙዚቃ ካለበት ደረጃ ከፍ ለማድረግ የያዘውን ሞያ በውጭ ሃገር ተምሮ እና በሚገባ አጠናቆ ወደ ሃገሩ ኢትዮጵያ በመመለስ የድራም አጨዋወት ሞያ በሃገራችን በብዙ ሰው እንዲወደድ ያደረገ ታታሪ የሙዚቃ ሰው ነበር።

የሃገራችንን ሙዚቃ ድምበር ተሻጋሪ እንዲሆን እና በመላው ዓለም ተድማጭ እንዲሆን ጥናት አድርጎ የሙዚቃ አልበም በማስቀረፅ በዓለም ገበያ ላይ እንዲውል ያስቻለ ፣የድርሻውን የተወጣ እና እየተውጣ የሚገኝ ትጉህ፣ ታታሪ፣እውቀቱን ለሌሎች አሳልፎ መስጠትን የማይሰስት፣ ብዙ የድራም ተጫዋቾችን ያፈራ፣የድራም አጨዋወት ጥበብን በሚገባ በተማሪዋቹ አዕምሮ ውስጥ ያፅነሰ፣ ቀና ፣ልበ እሩሩህ እና ከሁሉም ሰው ጋር ተግባቢ እና መልካም ሰው ነበር።

ለተጨማሪው:

Telegram: https://t.me/FirtunaMedia
Facebook: https://www.facebook.com/firtunamedia/
Instagram: https://www.instagram.com/firtunamedia/
Tiktok : https://www.tiktok.com/

Stay with us.
አብራችሁን ቆዩ

አርቲስት እንቁስላሴ ወርቅአገኘሁ አረፈአንጋፋው አርቲስት እንቁስላሴ ወርቅአገኘሁ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል፡፡አርቲስት እንቁስላሴ ባደረበት ሕመም በሕክምና ሲረዳ ቆይቶ ሕይወቱ ማለፉን የአር...
19/01/2025

አርቲስት እንቁስላሴ ወርቅአገኘሁ አረፈ

አንጋፋው አርቲስት እንቁስላሴ ወርቅአገኘሁ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል፡፡አርቲስት እንቁስላሴ ባደረበት ሕመም በሕክምና ሲረዳ ቆይቶ ሕይወቱ ማለፉን የአርቲስቱ ቤተሰቦች ለፋና ዲጂታል ተናግረዋል፡፡

አርቲስት እንቁስላሴ 30 በሚሆኑ ፊልሞች እና ቴአትሮች ላይ በትወና በመሳተፍ በብዙዎች ዘንድ አድናቆትን አገኝቷል፡፡

ለተጨማሪው:

Telegram: https://t.me/FirtunaMedia
Facebook: https://www.facebook.com/firtunamedia/
Instagram: https://www.instagram.com/firtunamedia/
Tiktok : https://www.tiktok.com/

Stay with us.
አብራችሁን ቆዩ

ተወዳጇ አርቲስት ሙሉዓለም ታደሰ በሲትኮም ድራማ እየመጣች ነውበተለያዩ የቴሌቪዥንና ሬድዮ ድራማዎች እንዲሁም ፊልሞችና ተውኔቶች ላይ የምናውቃትና ከቴሌቪዥን ድራማዎች ጠፍታ የቆየችው አንጋፋው...
02/12/2024

ተወዳጇ አርቲስት ሙሉዓለም ታደሰ በሲትኮም ድራማ እየመጣች ነው

በተለያዩ የቴሌቪዥንና ሬድዮ ድራማዎች እንዲሁም ፊልሞችና ተውኔቶች ላይ የምናውቃትና ከቴሌቪዥን ድራማዎች ጠፍታ የቆየችው አንጋፋው አርቲስት ሙሉዓለም ታደሰ በአዲስ የቴሌቪዥን ሲትኮም ድራማ እየመጣች እንደሆነ ተሰምቷል።

አርቲስት ሙሉዓለም ታደሰ የምትሳተፍበት ሲትኮም ድራማ "ዞሮ መውጫዬ"የተሰኘ ርዕስ ያለው እንደሆነም ተገልጿል።

ይህ ሲትኮም ድራማ አርቲስት ሙሉዓለም ታደስ እና አርቲስት ሚካኤል ታምሬ የተጣምሩበት እንደሆነም ተነግሯል። ድራማው በኢቢሲ ቴሌቪዥን እንደሚተላለፍም ተሰምቷል።


Telegram: https://t.me/FirtunaMedia
Facebook: https://www.facebook.com/firtunamedia/
Instagram: https://www.instagram.com/firtunamedia/
Tiktok : https://www.tiktok.com/

Stay with us.
አብራችሁን ቆዩ

28/11/2024
አርቲስት አስቴር አወቀ እና ሜትሮፖሊታን ሪል እስቴት በጋራ ለመስራት ተስማሙአርቲስት አስቴር አወቀ እና ሜትሮፖሊታን ሪል እስቴት በጋራ ለመስራት መስማማታቸውን ዛሬ ህዳር 19/2017 ዓ.ም ...
28/11/2024

አርቲስት አስቴር አወቀ እና ሜትሮፖሊታን ሪል እስቴት በጋራ ለመስራት ተስማሙ

አርቲስት አስቴር አወቀ እና ሜትሮፖሊታን ሪል እስቴት በጋራ ለመስራት መስማማታቸውን ዛሬ ህዳር 19/2017 ዓ.ም ይፋ አድርጓል።

የተለያዩ አለም አቀፍ ሽልማቶችን እና የሚዲያ ሽፋኖችን በማግኘት እና የሀገሯን ሙዚቃ በድምቀት በማስተዋወቅ የምትታወቀው የሙዚቃ ንግስት አሁን ደግሞ ከሜትሮፖሊታን ሪል እስቴት ጋር በህብረት በመሆን የተለያዩ የስነ ጥበብ፣ የበጎ አድራጎት እንዲሁም የሚዲያ ስራዎችን ለህዝብ እንደምታደርስ የአስቴር አወቀ ማናጀር ወ/ሮ አዳነች ወርቁ ገልጻለች።

የሜትሮፖሊታን ሪል እስቴት የሽያጭ እና የማርኬቲንግ ዳይሬክተር አቶ አለማየሁ ተሬሳ እንደገለጹት በዚህም ስምምነት ለህዝብ መልካም ነገር የማድረስ እቅድ እንዳላቸው አሳውቀዋል።

ሜትሮፖሊታን ሪል እስቴት በአሜሪካውያንና እና ቱርካውያን ባለ ሀብቶች የተቋቋመ ሪል እስቴት ሲሆን ከ 1000 በላይ ለሆኑ ኢትዮጵያውን የስራ ዕድል ፈጥሯል። ላለፉት 3 አስርት አመታት በአሜሪካ እና በቱርከ እንዲሁም ለ9 ዓመታት በሀገራችን ኢትዮጵያ ስኬታማ የሆኑ እጅግ ዘመናዊ የሪል እስቴት ፕሮጀከቶችን በመስራት ላይ ይገኛል::


Telegram: https://t.me/FirtunaMedia
Facebook: https://www.facebook.com/firtunamedia/
Instagram: https://www.instagram.com/firtunamedia/
Tiktok : https://www.tiktok.com/

Stay with us.
አብራችሁን ቆዩ

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Firtuna posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Firtuna:

Share