03/02/2023
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ጥሪ
***********,,,*******
ቤተክርስቲያን ለልጆቿ ከፊታችን ባለው የነነዌ ጾም እየደረሰባት ላለው እና በአገራችን ኢትዮጵያ እንዲሁም በሕዝቡ እና በአገልጋዮቿ ላይ ስለሚደርሰው መከራ እና ሰቆቃ ሁሉ በጾምና በጸሎት እግዚአብሔርን የነነዌ ሕዝቦ ማቅ ለብሶ አመድ ነስንሶ እግዚአብሔርን እንደለመኑት ልጇቿም ጥቁር ለብሰው ሱባኤውን እንዲያሳልፉ ጥሪዋን አቅርባለች።
እኛም ልጆቿ የቤተክርስቲያንን ጥሪ ተቀብለን በነዚህ ሶስት ቀና አበዝተን በመጾም እና በመጸለይ እግዚአብሔር ጥያቄያችንን እንዲመልስልን፣ አገራችንን ጽኑ ሠላም እንዲያደርግልን፣ ሕዝቦቿን ዘር ሃይማኖት ብሔር ሳይለይ ከመከራ ሥጋ ከመከራ ነፍስ እንዲጠብቅልን፣ አማጽያንን ወደ ልባቸው እንዲመለሱ እንዲያደርግልን፣ ወዘተ በቤተክርስቲያን በመገኘት ከእግዚአብሔር ጋር እንድንነጋገር እግዚአብሔር የሚለንን እንድንሰማ ይሁን።
አንዳንዶች በይሉኝታ ተመሳስለው ለማደር ፍርሐትም አርዷቸው ላያደርጉ ይችሎ ይሆናል፤ ነገር ግን አብዛኞች እንደሚያደርጉት የቤተክርስቲያንን ጥሪም እንደሚሰሙ ተስፋ አደርጋለሁ።
እግዚአብሔርን በጸሎት መለመን የአንዲት እምነት ተግባር ብቻ አይደለምና እግዚአብሔርን የምታመልኩ እግዚአብሔር እንደሚሰራ የምታምኑ የእግዚአብሔርን ሥራ ታዩ ዘንድ በጾም በጸሎት አገር ላይ የተቃጣው ነገር እንዲመለስ፣ በኢትዮጵያ ሰማይ ላይ እያንዣበበ ያለው ነገር እንዲረግብ ሁላችንም አብረን በመቆም ጥቁር ለብሰን እንጹም እንጸልይ።
ከጾም እና ከጸሎት በቀር ማሸነፍ አይቻልም።
ይቆየን።