Addis24ቀዳሚ

Addis24ቀዳሚ ሁሉንም መረጃ በአንድ ድረ ገፅ ያግኙ
አዲስ24 ቀዳሚ👈

አትሌት ገለቴ ቡርቃ ከመጀመርያው አንስቶ የገጠማት ችግር ተነግሮ የሚያልቅ አይደለም፦ አትሌት መሠረት ደፋርለሀገሯ ይህን ያክል ዋጋ የከፈለችው አትሌት ከ2010 ዓ.ም ጀምሮ የገጠማትን ችግር ...
10/06/2025

አትሌት ገለቴ ቡርቃ ከመጀመርያው አንስቶ የገጠማት ችግር ተነግሮ የሚያልቅ አይደለም፦ አትሌት መሠረት ደፋር

ለሀገሯ ይህን ያክል ዋጋ የከፈለችው አትሌት ከ2010 ዓ.ም ጀምሮ የገጠማትን ችግር ለመፍታት በፍርድ ቤት ስለመንከራተቷ በቅርበት አውቃለሁ ያለችው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌደሬሽን ምክትል ፕሬዚዳንት አትሌት መሠረት ደፋር፤ ሕግ ለዚህች የሀገር ባለውለታ ትክክለኛውን ፍትህ እንዲሰጣት እጠይቃለሁ ብላለች።

መንግሥትም ለጉዳዩ ትኩረት እንዲሰጠው የኦሎምፒክ ሻምፒዮኗ መሠረት ደፋር ጠይቃለች።

Via EBC

ከጉራጌና ጉራጊኛ የኪነ-ጥበብ ባለውለታዎች መካከል አንዱ የሆነው የ10 አልበሞች ባለቤቱ አርቲስት ጋሽ ደምሴ ተካ የኦዳ አዋርድ የሕይወት ዘመን ልዩ ተሸላሚ ሆኗል።እንኳን ደስ አለህ! እንኳ ...
08/12/2024

ከጉራጌና ጉራጊኛ የኪነ-ጥበብ ባለውለታዎች መካከል አንዱ የሆነው የ10 አልበሞች ባለቤቱ አርቲስት ጋሽ ደምሴ ተካ የኦዳ አዋርድ የሕይወት ዘመን ልዩ ተሸላሚ ሆኗል።

እንኳን ደስ አለህ! እንኳ ደስ ባረናኽም!

የልደት በዓል ወደ እስራኤል ጉዞ  እንደሚደረግ ተገለጸ Ethiopia | ኤማሁስ የመንፈሳዊ ጉዞ ወኪል የገናን በአል አስመልክቶ ወደ እስራኤል ጉዞ ማዘጋጀቱን ዛሬ በተሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ተ...
06/12/2024

የልደት በዓል ወደ እስራኤል ጉዞ እንደሚደረግ ተገለጸ

Ethiopia | ኤማሁስ የመንፈሳዊ ጉዞ ወኪል የገናን በአል አስመልክቶ ወደ እስራኤል ጉዞ ማዘጋጀቱን ዛሬ በተሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ተገለጸ።

መስከረም 22 ቀን በሊቃነ ጳጳሳት ተባርኮ ስራ መጀመሩ የሚታወሰው ኤማሁስ የመንፈሳዊ ጉዞ ወኪል በኢትዮጵያ የሚገኙ ገዳማትን እና አድባራትን ለዓለም ከማስተዋወቅ በተጨማሪም ምዕመናን ከኢትዮጵያ ውጪ የሚገኙ ታሪካዊ ገዳማትንና አድባራትን እንዲጎበኙ አላማ አድርጎ ወደ ሥራ መግባቱን የኤማሁስ መንፈሳዊ ጉዞ ወኪል መስራች እና ባለቤት የሆኑት መልአከ ሕይወት ቆሞስ አባ ወ/ኢየሱስ ሰይፉ ገልጸዋል።

ከታህሳስ 25 እስከ ጥር 7 ቀን 2017 ዓ.ም ለ10 ቀናት ወደ እስራኤል የእየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል አስመልክቶ በተዘጋጀው መንፈሳዊ ጉዞ ላይ በርካታ ኢትዮጵያውያን እና የበቁ አባቶች በጉዞ ላይ ተሳታፊ እንደሚሆኑ እና በቀሩት ቀናቶችም በምዝገባ ላይ እንደሚገኙ መልአከ ሕይወት ቆሞስ አባ ወ/ኢየሱስ ሰይፉ በጋዜጣዊ መግለጫ መርሐግብሩ ላይ ተናግረዋል።

መንፈሳዊ የጉዞ ማኅበሩ የተቋቋመው ለትርፍ ሳይሆን ምእመናንን ለማገልገል ፣ የተዘጉ አብያተ ክርስቲያናትን ለማስከፈት ፣ የአብነት ትምህርት ቤቶችንም ለመደገፍ እና መሰል መንፈሳዊ አገልግሎቶችን ለማከናወን ነው በማለት የገለጹ ሲሆን በሌሎች የጉዞ ማኅበራት ላይ የምናያቸውን ክፍተቶች ለመሸፈን ዕቅዶችን ይዞም እንደሚሰራም አሳውቀዋል።

ኤማሁስ የመንፈሳዊ ጉዞ ወኪል ከሌሎች መንፈሳዊ ጉዞ ማኅበራት የሚለይበት በዋናነት ከአብነት ትምህርት ቤት ጀምሮ የሚማሩ ተማሪዎችን አቅም እንኳን ባይኖራቸው በስፖንሰር ሊቃውንቱም ቢሆኑ በቃል የተማሩትን በገጽ እንዲመለከቱ የሚያግዝ መንፈሳዊ ጉዞ ማኅበር ነው በማለት ገልጸዋል።

ኢትዮ ቻይና የፊልም እና የ ቴሌቪዥን ፌስቲቫል በኢትዮጰያ ሊካሄድ ነው።በቻይና እና በኢትዮጰያ ለሚገኙ የፊልም ት/ት ተቋማት የፊልም እውቀት ሽግግር ማምጣት ያለመ እንደሆነ ተመልክቷል።በፊልሙ...
06/12/2024

ኢትዮ ቻይና የፊልም እና የ ቴሌቪዥን ፌስቲቫል በኢትዮጰያ ሊካሄድ ነው።
በቻይና እና በኢትዮጰያ ለሚገኙ የፊልም ት/ት ተቋማት የፊልም እውቀት ሽግግር ማምጣት ያለመ እንደሆነ ተመልክቷል።
በፊልሙ ዘርፍ እውቀትና ልምድ ልውውጥ ለማድረግ ይህ ኢትዮ ቻይና የፊልም እና የቴሌቪዥን ፌስቲቫል የሚጫወተው ሚና ከፍተኛ መሆኑን ተገልጿል።
በኢትዮጵያ የቻይና አምባሲ የባህል አማካሪ ዣንግ ያዋይ " የኢትዮጵያ የፈጠራ ዘርፍ ለማጠናከር ችሎታን ለማዳበር የስልጠና እና የቍሳቁስ ድጋፍ አያደረገች ያለውን ቁርጠኝነትን የሚያሳይ ትልቅ ፌስቲቫል መሆኑን አመላክተዋል ።
በተጨማሪም በሁለቱ ሀገራት መካከል የባህል፣ ታሪክና የፈጠራ ትብብርን የሚያጠናክር ፌስቲቫል እንደሆነ አክለዋል።
ፈስቲቫሉ የጎፍ ኢንተርቴይመንት፣ ከኢፌዴሪ ዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ፣ ከኢፌደሪ ባህልና ስፖርት ሚኒስቴር እና ከቻይና ኤምባሲ በኢትዮጵያ ጋር በጋራ መተባበር ያዘጋጀው ነው።
ሪፖርተር ትርሲት ሀብቴ

የባህል ምሽት ቤቷ በእሳት ቃጠሎ ወድሟል!Support Amsal Mitke: Rebuild a Beloved Cultural Landmarkhttps://gofund.me/6f56ec7c  | በኢትዮጵያ የ...
05/12/2024

የባህል ምሽት ቤቷ በእሳት ቃጠሎ ወድሟል!
Support Amsal Mitke: Rebuild a Beloved Cultural Landmark

https://gofund.me/6f56ec7c

| በኢትዮጵያ የሙዚቃ ታሪክ የራሷን አሻራ ያሳፈረችው አርቲስት አምሳል ምትኬ ከልጅነት ዕድሜዋ ጀምሮ ለምትወደው የሙዚቃ ሞያ የተጋች፣ የአንገፋ የሙዚቃ ተምሳሌቶቿን ምክርና ልምድ ተቀብላ ሕልሟን ያሳካች ታታሪ የኪነጥበብ ሰው ናት፡፡ በሙዚቃ ሥራዎቿ የኢትዮጵያን ባህልና ታሪክ ያስተዋወቀች፣ በአገር ውስጥም ሆነ በባህርማዶ በተዘጋጁ ኮንሰርቶችና ባዛሮች ተወዳጅ ሥራዎቿን ለሚወዷት አድናቂዎቿ በማቅረብ ከፍ ያለ ዝና እና ክብር አትርፋለች፡፡

አርቲስት አምሳል ምትኬ ለተቸገረ ደራሽ፣ አረጋዊያንን ደጋፊ፣ አዛኝና እና ሩህሩህ ስብዕና ያላት ኢትዮጵያዊ መሆኗን በተግባር አሳይታለች፡፡ የእሷን ፈለግ ተከተለው ለመጡ ወጣቶች በሃሳብ ይምታበረታ፣ በማቴሪያልና በገንዘብ የምትደግፍ ቅን ሰው ናት፡፡ በጤና፣ በዕድሜ መግፋት ለተቸገሩ አንጋፋ የኪነጥበብ ሰዎችን በማጽናናት፣ በመድረስ ትታወቃለች፡፡

በተለያየ ጊዜ በአገራችን በተፈጠሩ ሰው ሰራሽና የተፈጥሮ አደጋዎች በገቢ ማስገኛ መድረኮች በሞያዋ ከመሳተፍ በተጨማሪ በገንዘብ ስትደግፍ የኖረች አገርና ወገኗን ወዳድ ኢትዮጵያዊ ናት፡፡

ከ10 ዓመት በፊት በባህርዳር ከተማ ደረጃው በጠበቀ መልኩ በከፈተቸው የምሽት ክለብ ለሞያ አጋሮቿና ለወጣት ሙዚቀኞች እንዲሁም በተለያየ ሞያ ለተቀጠሩ በአጠቃላይ ለ60 ወገኖች የሥራ ዕድል በመፍጠር ጥቂት ለማይባሉ ቤተሰቦች የሕይወት ለውጥ አለኝታ ሆናለች፡፡

በዚህ የምሽት ክለብ ይሰሩ የነበሩ ወጣት የሙዚቃ መሣሪያ ተጫዋቾና ድምጻዊያን ሞያቸውን እንዲያሳድጉ አስችሏቸዋል፡፡ በሕዝብ ዘንድ ታዋቂ መሆን ችለዋል፡፡ ራሳቸውን ችለው እንዲሰሩና እንዲለወጡ የበኩሏን አስተዋጽዖ አድርጋለች፡፡

ዛሬ ያ ለሥራ አጥ ወገኖቿ አለኝታ የሆነችበት፣ የባህር ዳር ከተማ ድምቀትና መዳረሻ የነበረው፣ በርካታ የሙዚቃ ባለሞያዎች የወጡበት፣ በሞያቸው እውቅና ያተረፉበት፣ ቤተሰብ የሚያስተዳድሩበት የባህል ምሽት ቤት ከምሽቱ 12 ሰዓት አካባቢ ምክንያቱ ባልታወቀ የእሳት ቃጠሎ ወድሟል፡፡

ለዓመታት ሰርታ ያፈራችው በውስጡ የነበሩ በውድ ዋጋ የተገዙ የሙዚቃ መሳሪያዎችና ሌሎች የባህል ሬስቶራንቱ መገልገያ ዕቃዎች ባሉበት አመድ ሆነዋል፡፡

ይህን መጎዳቷን የሰሙ በአገር ውስጥና በተለያየ የዓለም ክፍል የሚኖሩ አድናቂዎቿ "ጉዳትሽ ጉዳታችን" ነው በማለት አፅናንተዋታል፡፡ .

ለሀገር ለወገን ደራሽ በመሆን ካላት አካፍላ የኖረችው አርቲስት አምሳል ምትኬ የህዝብ ልጅ ናት፡፡ ይህን ሁሉ ንብረት ለማፍራት ደክማለች፡፡

ውድ ኢትዮጵያዊያን ወገኖችና የአርቲስት አምሳል ምትኬ አድናቂዎች!....ለአገርና ለወገን አለሁ በማለት በሞያዋ ስታግዝ ለኖረችው ተወዳጅ አርቲሰት "ጉዳትሽ ጉዳታችን" እንዳልናት ሁሉ በተግባር ልንደርስላት ይገባል፡፡ በመሆኑም የባህል ምሽት ቤቷ በተሻለ ሁኔታ ተግንብቶ ወደሥራ እንድትገባ በማድረግ ይህን የጎፈንድ ሚ ከፍተናል፡፡

https://gofund.me/6f56ec7c

We are heartbroken to share the devastating news of the fire that destroyed Amsal Mitke’s cherished cultural restaurant. For over 20 years, Amsal has been a passionate cultural ambassador for Ethiopia, sharing her country’s rich heritage, traditions, and cuisine wit

የኢሳት ቴሌቪዥን መጨረሻ....ለሚድያ ኢንዱስትሪ እምብዛም ክፍት ኣልነበረም የሚባልለት የኢህአዴግ መንግስት የሃገሪቱ ሥልጣን በተቆጣጠረ ሰሞን ለሚድያ ነፃነት ምሳሌ መሆን የሚችል ተብሎ በ ባ...
03/12/2024

የኢሳት ቴሌቪዥን መጨረሻ....

ለሚድያ ኢንዱስትሪ እምብዛም ክፍት ኣልነበረም የሚባልለት የኢህአዴግ መንግስት የሃገሪቱ ሥልጣን በተቆጣጠረ ሰሞን ለሚድያ ነፃነት ምሳሌ መሆን የሚችል ተብሎ በ ባለሙያዎች የተመሰከረለት ህግ ሲያወጣ በፊት የነበረ የሳንሱር ስርዓት በመነሳቱ በሃገሪቱ ታይቶ በማይታወቅ መልኩ ሚዲያዎች እንደ አሸን ፈሉ።
የመረጃ ፉክክሩ ጦዞ በሚዲያዎች በኩል የሃገሪቱ የወቅቱ ቁንጮ ባለስልጣናትን ሳይቀር ያለፍርሃት አበጥረው እስከ መስደብ የደረሱ ዘገባዎች ፣ እርቃናቸው የሚያወጡ ደፋር ዘገባዎች በመዘገብ የወቅቱ መንግስት አቅሉን እስኪስት ተፈታተኑት።
የሚድያዎቹ ጭሆት ና ተፅእኖ መቋቋም ያቃተው ገዢው መንግስት የሰጣቸውን ነፃነት መልሶ በመንሳት አብዛኞቹ እንዲዘጉ ሆነ።
ኢህአዴግ ሰጠ ኢህአዴግ ነሳ በማለትም የነበረውን ፈጣን የሚድያ ኢንዱስትሪ እድገት አንድም በፈጠሩት ተፅዕኖ አንድም በነበራቸው ያልተገረዘ የአዘጋገብ ስርዓት መልሶ አቀጨጨው ። አጠፋቸውም ::
በ 2010 ዓ.ም የለውጥ ሀይሉ ከመጣ ወዲህ ሚዲያዎች እንዳያድጉ ስቅለ የያዙ ህግ ሸረናል ያለዉ የብልፅግና መንግስት እንደውም ለአንዱስትሪው እድገት አማራጭ ይሆን ዘንድ Ethiosat ን እንካችሁ አለ።
በዚህም እልል ተባለ፣ ዘዘመረ፣ የዘርፉ ባለሙያዎችም " እሰይ ቀን ወጣልን ከመሽ" በማለት አሞካሹት ።
የጠፋት ሚዲያዎችም ከጠፉበት መብቀል ጀመሩ ። ፈሉ ።
በዚህም በመቶዎች የሚቆጠሩ (main Stream ) ሚዲያዎች ተከፈቱ። ከ 30 በላይ የቲቪ ጣብያዎች ተከፍተዋል።
ይሁን እንጂ ከቅርብ ግዚያት ወዲህ በተለይም ከ 2016 መጨረሻ ጀምሮ ብዙ የቲቪ ጣብያዎች በሳተላይት ተንጋግተው የመውረዳቸው ጉዳይ ብዙዎችን እያነጋገረ ይገኛል ።
የአብዛኛቹ ምክንያት ደግሞ የዓቅም (የፋይናንስ ) እጥረት ነው ተብሏል።
ከወረዱ በጥቂቱ ነው፣ የኛ፣ KTV ፣ እና ሌሎች በተለያዩ ብሄረሰቦች የተቋቋሙ ሚዲያዎች የሚጠቀሱ ሲሆኑ ሌሎችም በፋይናንስ ትንቅንቅ ውስጥ ገብተው በጣር እንዳሉ ተገልጿል፡ በቅርቡ በውስጡ በተፈጠረው የአስተዳደር አለመግባባት እና የኢዲቶሪያል ፖሊሲ መንሸዋረር ሲያነጋግረ የቆየው ኢሳት ቲቪ ም ተመሳሳይ እጣ ገጣሞታል ተብሏል። በዚህም ከዛሬ ጀምሮ ከሳተላይት መውረዱ አዲስ 24 አረጋግጧል :: የህዝብ አይንና ጆሮ እሆናለሁ ብሎ ከሃገር ዉጭ ሁኖ የኢህአዴግ መንግስትን በመገልበጥ ሲሰራ የቆየው ታጋይ የህዝብ ልጅ ኢሳት ወደ ሃገር ገብቶ በሃገር ውስጥ ገብቶ የመንግስት አፍና ፈረስ ሆኜ እስራለሁ በማለት 6 ዓመታትን የተጓዘው ኢሳት የመንግስት በለሟልነት ሳያዋጣው ፣ ከሰራተኞቹ ተሰማምቶ መስራት ሳይሆንለት እንዲሁም የነቃ ፡ የበቃና የበራለት ማህበረሰብ ሳይፈጥር እነሆ ሌሎች ወገኖቹ የደረሳቸው እጣ ደርሶት በዓቅም እጦት ጓዙን ሸክፎ ወርዷል፡፡
አዲስ 24
ቀዳሚ

ሚለርስ ፎር ኒውትሪሽን ኢኒሼቲቭ በኢትዮጵያ የተመጣጠነ ምግብ እጥረትን ለመቅረፍ ስራ ጀመረ   | ሚለርስ ፎር ኒውትሪሽን ቴክኖ ሰርቭ ከተሰኘ የበጎ አድራጎት ድርጅት ጋር በጋራ በመሆን በኢት...
03/12/2024

ሚለርስ ፎር ኒውትሪሽን ኢኒሼቲቭ በኢትዮጵያ የተመጣጠነ ምግብ እጥረትን ለመቅረፍ ስራ ጀመረ

| ሚለርስ ፎር ኒውትሪሽን ቴክኖ ሰርቭ ከተሰኘ የበጎ አድራጎት ድርጅት ጋር በጋራ በመሆን በኢትዮጵያ የተመጣጠነ ምግብ እጥረትን ለመቅረፍ ስራ በኢትዮጵያ በዛሬው እለት አስጀምረዋል ።

በስራ ማስጀመሪያ ፕሮግራሙ ላይ እንደተገለፀው ጥምረቱ የስንዴ ዱቄት አምራች እና የምግብ ዘይት ፋብሪካዎችን በቫይታሚን በማበልፀግ የተመጣጠነ ምግብ ዕጥረትን ለመቀነስ እንደሚሰራ ተገልጿል።

ሚለርስ ፎር ኒውትሪሽን ባለፈው አንድ አመት ጊዜ ውስጥ ለ140 ፋብሪካዎች የቴክኒካል ድጋፍ እና ለተጨማሪ 40 ፋብሪካዎች ደግሞ ስልጠና መስጠቱንም የሚለርስ ፎር ኒውትሪሽን የኢትዮጵያ ፕሮግራም ስራ አስኪያጅ አቶ እያቄም አምሳሉ ገልጸዋል።

ይሁን እና በሀገር አቀፍ ደረጃ አሁንም አሳሳቢ የሆኑ የአመጋገብ ችግሮች እያጋጠሟት መሆኑን የሚለርስ ፕሮግራም ስራ አስኪያጅ የሆኑት ኢያኬም አምሳሉ ተናግረዋል።

የማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት የምግብና መጠጥ ኢንዱስትሪ ምርምርና ልማት ማዕከል በቅርቡ ባወጣው መረጃ መሠረት ከአምስት ዓመት በታች ላሉ ሕፃናት 22በመቶ ከክብደታቸው በታች መሆኑም ተነግሯል።

እነዚህ አኃዛዊ መረጃዎች የተመጣጠነ ምግብ እጥረትን ለመቅረፍ እና ሁሉም ህጻናት ለጤናማ እድገት የሚያስፈልጉትን ንጥረ ነገሮች እንዲያገኙ ለማድረግ ቀጣይ ጥረቶች አስፈላጊ መሆኑን የሚያሳዩ ናቸው ተብሏል።

ከዚህ በተጨማሪ አገራችን ከተመጣጠነ ምግብ ዕጥረት ጋር በተያያዘ 16.5 በመቶ አመታዊ ጂዲፒ ወጪ እንደምታደርግ የተገለፀ ሲሆን ይህንን ለማስቀረት በማሰብ በየዕለቱ ልንመገባቸው የምንችላቸው የምግብ ግብዓቶችን በቫይታሚኖች በማበልጸግ እንደሚሰራ ነው አቶ እያቄም የገለፁት።

ሚለርስ ፎር ኒውትሪሽን በአፍሪካ እና እስያ በሚገኙ ስምንት ሀገራት በባንግላዲሽ፣ ህንድ፣ ኢንዶኔዥያ፣ ኬንያ፣ ናይጄሪያ፣ ፓኪስታን፣ ታንዛኒያ እና አሁን ኢትዮጵያን ጨምሮ እንደሚሰራ ተነግሯል።

በእነዚህም ሀገራት የሚገኙ የስንዴ፣ በቆሎ፣ ሩዝ እና የምግብ ዘይት ምርቶችን በቫይታሚን የሚያበለፅግ ነው።

ለቡ አካባቢ ያሉ ስጋ ቤቶች ስጋ ቤት ብቻ ሳይሆኑ   .  .   .በቪዲዬ እና በድምፅ የታገዘ መረጃ በውስጥ መስመር ለቡ አካባቢ ካሉ ስጋ ቤቶች ተላከልኝ ። ይህውም በአስተናጋጅነት የተቀጠሩ...
02/12/2024

ለቡ አካባቢ ያሉ ስጋ ቤቶች ስጋ ቤት ብቻ ሳይሆኑ . . .

በቪዲዬ እና በድምፅ የታገዘ መረጃ በውስጥ መስመር ለቡ አካባቢ ካሉ ስጋ ቤቶች ተላከልኝ ።
ይህውም በአስተናጋጅነት የተቀጠሩ ሴቶች የመጣውን ተገላጋይ ስጋ ለመብላት ብቻ ሳይሆን ለፆታዊ ግንኙነት ፍላጎት እንዲኖረው በማድረግ እየተደራደሩ እንደሚወጡ በተላከልኝ በድብቅ የተቀረፀ ቪዲዬ እና ድምፅ ለማወቅ ችያለሁ ።

ከተላከልኝ መረጃ እንደተረዳሁት በአስተናጋጅነት የሚከፈላቸው ክፍያ በቂ ባለመሆኑ የቤቶቹ ባለቤቶች በተደራቢነት ይሄን በመስራት ኑሮዎቸውን መደጎም ገቢያቸውን ማሳደግ እንደሚችሉ በሚኖራቸው የስራ ቅጥር የቃል ንግግር ላይ ከባለቤቶቹ እንደሚነገራቸው ። ይህንም በማድረጋቸው ቤቱ በርከት ያለ ደንበኛ እንዲኖረው ከማድረግም ባሻገር እነሱም ተጠቃሚ እንደሚሆኑ አለበዚያ ግን ደሞዛቸው ለታክሲ በቂ አለመሆኑ ተነግሯቸው በተዘዋዋሪ ይሄን መስራትም አንዱ ያልተፃፈ የቤቱ የውስጥ ህግ መሆኑ አስረግጠው ነግረዋቸው እንደቀጠሯቸው ትናገራለች ።

ወንድ ልጅ ሊስተናገድ ሲመጣ ፍላጎት እንዲኖረው" Flirt" ማሽኮርመም እንዳለባቸው በቀጣሪዎቻቸው ተደጋግሞ የሚገለፅላቸው ሲሆን በየ ቀኑ ከአንድ ደንበኛ ጋር በድርድር አብረው የማደርም ግዴታ እንዳለባቸው በተላከልኝ መረጃ ማወቅ ችያለሁ ።

ይህ ጉዳይ በቀጥታ የሚመለከተው የአዲስ አበባ ከተማ ባህል ኪነጥበብና ቱሪዝም ቢሮ ከፍተኛ ክትትል አድርጎ የመፍትሄ አቅጣጫ እና እርምጃ መውሰድ ያለበት ይመስለኛል ።

አንዲት ሴት ያለ ተፅዕኖ የማስተናገድ ስራ ብቻ እየሰራች የመኖር መብቷ ሊረጋገጥላት ይገባል ። ሴት ልጅ ገላዋን እየሸጠች የግለሰብ ኪስ የምታደልበበት እና ህይወቷን አደጋ ላይ የምትጥልበት ጊዜ ሊያበቃ ግድ ይላል ።

50 ሺ ብር ቅጣቱ ከሰው ልጅ ህይወት አንፃር ለኔ ምንም ነው ።

ሼር በማድረግ እህቶቻችንን ከሚደርስባቸው ተፅዕኖ እንታደጋቸው ።

ግልባጭ :—
ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር
ለአዲስ አበባ ሴቶችና ህፃናት ቢሮ
ለአዲስ አበባ ከተማ ባህል ኪነጥበብና ቱሪዝም ቢሮ ለወይዘሮ ገነት ይመር
(ምንጭ Tariku zewdu)

ነጻነት የሰዕል አውደ ርዕይና የስዕል ጨረታ በሸራተን አዲሰ ሆቴል  ሊዘጋጅ ነው።ህዳር 23 ቀን 2016 ዓ/ም ሐሙስ አመሻሸ 12:00 የሚጀመረው ይህ የሰዕል አውደ ርዕይና የስዕል ጨረታ አላ...
02/12/2024

ነጻነት የሰዕል አውደ ርዕይና የስዕል ጨረታ በሸራተን አዲሰ ሆቴል ሊዘጋጅ ነው።
ህዳር 23 ቀን 2016 ዓ/ም ሐሙስ አመሻሸ 12:00 የሚጀመረው ይህ የሰዕል አውደ ርዕይና የስዕል ጨረታ አላማው የሰዓሊ ብሩክ የሺጥላ የጉልበት ንቅለ ተከላ ህክምና ይረዳ ዘንድ መሆኑን ተገልጿል::
የሰዕል አውደ ርዕይና የስዕል ጨረታውን ኪነ ጥበብን ባከበረ መልኩ ለማዘጋጀት መታቀዱን ያብራራው ሰዓሊ ብሩክ የሺጥላ በዚህ ዝግጅት ላይ በርካቶች እንደሚሳተፉበት ጠቁሟል።
በተጨማሪም ስዕልን በማክበርና በመውደድ አሁን ካለሁበት የጤና ሁኔታ የተሻለ ለመንቀሳቀስ ይረዳ ዘንድ ህክምናውን የራሴን ስዕሎች ለጨረታ በማቅረብ ወጪዬን ለመሸፈን አቅጃለሁ ያለዉ ሰዓሊው ለሌሎች የኪነ ጥበብ ባለሙያዎችም አስተማሪ እንደሆነ ተናግሯል፡፡
በመጨረሻም የሰዕል አውደ ርዕይና የስዕል ጨረታ ተካፋይ በመሆን ህክምናው የተሰካ እንዲሆን በዝግጅቱ ተገባዣች እንዲገኙ ሰዓሊ ብሩክ ጥሪ አቅርቧል።
ይህ የጉልበት ንቅለ ተከላ ህክምና በስዊድን ሀገር የሚደረግ ሲሆን ከ3ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ እንደሚጠይቅ ተገልጿል።
(ዘገባዉን ያደረሰችን ትርሲት ሀብቴ ናት)

🇪🇹  💟🥇🥉
25/07/2022

🇪🇹 💟🥇🥉

Address

Addis Ababa

Telephone

+251713285960

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Addis24ቀዳሚ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Addis24ቀዳሚ:

Share