
23/08/2025
የጋምቤላ ክልልን በማር ምርት ማስጠራት እፈልጋለሁ - አቶ ቲቶ ሐዋርያት
***************
የቀድሞው ፖለቲካኛ የአሁን የግብርና ኢንቨስተር አቶ ቲቶ ሐዋርያት ወደ ግብርና ሥራ በመግባት በጋምቤላ ክልል በግብርና ኢንቨስትመንት ላይ ተሰማርተዉ ስኬታማ ሆነዋል።
አሁን ላይ ከ300 በላይ የንብ ቀፎ አንዳላቸዉ እና የጋምቤላ ክልልን በማር ምርት ለማስጠራት እየሰሩ መሆኑን አንስተዋል።
ከባህላዊ የንብ ቀፎ በመጀመር ወደ ዘመናዊ የንብ ቀፎ መሸጋገራቸውን የሚያነሱት አቶ ቲቶ፤ በዓመት ከ2000 ኪሎ ግራም በላይ የተጣራ ማር እንደሚያገኙም ይገልፃሉ።
ከራሳቸዉ እና በአከባቢው ማር ከሚያመርቱ ገበሬዎች ማር በመግዛት በተመጣጠኝ ዋጋ ገዝተዉ በማቅረብ በፊት በሶስት ወር ደሞዝ የሚያገኙትን አሁን ላይ በሶስት ቀን ማግኘት መቻላቸዉን ተናግረዋል።
አቶ ኦኮሞ ጅዋቶ ኦኮክ እንዲሁ በተለያዩ የቅጥር ስራዎች ያሳለፉ ሲሆን አሁን ላይ በግብርና ስራ ተሰማርተው ውጤት ማስመዘግብ ችለዋል።
ከመንግሥት የመስሪያ መሬት ተሰጥቷቸው መሬቱን በማልማት ሰሊጥ እና በቆሎ በማምረት ውጤታማ መሆናቸውንም ገልጸዋል።
በቢታንያ ሲሳይ