Ethiopian Broadcasting Corporation

Ethiopian Broadcasting Corporation Ethiopian Broadcasting Corporation is a 24 hour working public media.

In addition to this Meta Page, we have other social media accounts:
Twitter
https://twitter.com/ebczena
Telegram
https://t.me/EBCNEWSNOW
Youtube
https://www.youtube.com/c/EBCworld
Instagram
https://www.instagram.com/ebcnews1/
Tiktok
https://www.tiktok.com/?lang=en



Ethiopian Broadcasting Corporation is a national media that disseminates its news and programs world wide via Television, Radio, and Website.

 "በሀገራችንም አንድ ለእናቱ የሆነው ባቡር በከተሞች ምሥረታ፣ ዕድገትና ትሥሥር ላይ ያለውን በጎ ተጽዕኖ ስናስብ በአንድ መቅረቱ በእጅጉ የሚያስቆጭ ነው። ሀገር አቋራጭ የባቡር መሥመሮች ካላ...
17/10/2025



"በሀገራችንም አንድ ለእናቱ የሆነው ባቡር በከተሞች ምሥረታ፣ ዕድገትና ትሥሥር ላይ ያለውን በጎ ተጽዕኖ ስናስብ በአንድ መቅረቱ በእጅጉ የሚያስቆጭ ነው።
ሀገር አቋራጭ የባቡር መሥመሮች ካላቸው ፍጥነትና የማጓጓዝ ዐቅም አንጻር ምርቶችን በተሻለ ክብካቤና ፍጥነት ለተለያዩ ገበያዎች ማድረስ ይችላሉ፡፡ በመላው ሀገራችን ብቻ ሳይሆን ከጎረቤት ሀገራትም ጭምር የሚያገናኙን መሆን ይገባቸው ነበር፡፡"

(የመደመር መንግሥት ገጽ 57)

17/10/2025

አዲስ ቀን … ጥቅምት 07/2018 ዓ.ም
#አዲስቀን

የባንግላዴሽ ኑክሌር የመገንባት ሀሳብ እንደተሰማ  ተቺዎች "ከምኞት የማይዘል የድሀ ሀገር ህልም "  በማለት አጣጥለው ነበር። ይሁን እንጂ  የባንግላዴሽ መሪዎች መጪውን ዘመን ተመልክተው  ዘ...
17/10/2025

የባንግላዴሽ ኑክሌር የመገንባት ሀሳብ እንደተሰማ ተቺዎች "ከምኞት የማይዘል የድሀ ሀገር ህልም " በማለት አጣጥለው ነበር።

ይሁን እንጂ የባንግላዴሽ መሪዎች መጪውን ዘመን ተመልክተው ዘላቂ እና ርካሽ የኃይል ምንጭ ከሌለ ሀገሪቱ ከድህነት ለመውጣትም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለመወዳደር እንደማትችል በማመናቸው ሀገሪቱን ለዘመናት ከነበረችበት የጨለማ ታሪክ ያወጣል ያሉትን ታላቁን የሩፑር ፕሮጀክት አስጀመሩ።

በዚህ ውሳኔ መሰረት ባንግላዴሽ ይህንን በሀገሪቱ ታሪክ ታይቶ የማይታወቅ ታላቅ ፕሮጀክት ስትጀምር በወቅቱ የነበረው የባንግላዴሽ አጠቃላይ አመታዊ የሀገር ውስጥ ምርት ከ100 ቢሊዮን ዶላር ብዙም የማይበልጥ ነበር።

ሆኖም ውሳኔው የሀብታምነት ሳይሆን የረጅም ጊዜ የህልውና ጥያቄ ነበርና የነበሩበትን ሁኔታ ወደጎን በማድረግ በይቻላል መንፈስ ታላቁን ፕሮጀክት እውን ለማድረግ መረባረብ ጀመሩ።

በዚህ መልኩ የተጀመረው የባንግላዴሽ የሩፑር የኑክሌር ሀይል ማመንጫ ግንባታ ታዲያ ያጋጠመው የገንዘብ እጥረት ብቻ አልነበረም።

በተለይ የፕሮጀክቱ ስራ ተጀምሮ ግማሽ ላይ እንደደረሰ በዓለም አቀፍ ደረጃ አጋጥሞ የነበረው የኮቪድ 19 ወረርሽኝን ፕሮጀክቱን ለመጨረስ ፈተና ሆነ።

በአካባቢው የተፈጠረው ጂኦ ፖለቲካዊ ውጥረት እና የተፈጥሮ አደጋ ይህ ግዙፍ ፕሮጀክት አደጋ ውስጥ እንዲወድቅ አድርጓል።

ይህን አደጋ እንዴት አለፈችው? ትልቁ ህልም እንዴት ተፈታ? ሊንኩን ተጭነው ያንብቡ:-

በድህነት ውስጥ የተወለደው የኒውክሌር ህልም፦ ሩፑር

ህዳሴን ለፍጻሜ ያበቃ ትውልድ የመልማት ቁጭቱን በባህር በር ሊደግም ይገባል -  የቀድሞ የባህር ኃይል አባላት*********************የህዳሴ ግድብን ለፍጻሜ ያበቃው ትውልድ የመልማት...
16/10/2025

ህዳሴን ለፍጻሜ ያበቃ ትውልድ የመልማት ቁጭቱን በባህር በር ሊደግም ይገባል - የቀድሞ የባህር ኃይል አባላት
*********************

የህዳሴ ግድብን ለፍጻሜ ያበቃው ትውልድ የመልማት ቁጭቱን በባህር በር ሊደግመው ይገባል ሲሉ ከኢቲቪ ጋር ቆይታ ያደረጉ የቀድሞ የባህር ኃይል አባላት ገለፁ፡፡

የቀድሞ የባህር ሀይል አባል ማስተር ቺፍ ዘሩሁን ወዬሳ፤ ኢትዮጵያ የባህር በር በነበራት ወቅት የንግድ እንቅስቃሴው በጥሩ ደረጃ ላይ እንደነበር አስታውሰዋል፡፡

በጊዜው የአሰብ ወደብ ሁል ጊዜ ስራ ይበዛበት ነበር የሚሉት ማስተር ቺፍ ዘሩሁን፤ በዛን ወቅት በነበረው እንቅስቃሴ ላይ አሁን ያለው የተሳለጠ የንግድ እንቅስቃሴ ቢታከልበት ኖሮ ኢትዮጵያ ጠንካራ ኢኮኖሚ የምትገነባ ሀገር እንደምትሆን ምንም ጥርጥር የለውም ሲሉ ጠቅሰዋል፡፡

ኢትዮጵያ አሁን እያነሳች ያለችው የባህር በር ይገባኛል ጥያቄ ወደብን ከማግኘት የዘለለ እና ሁለንተናዊ የመልማት ፍላጎትን የያዘ እንደሆነ አንስተዋል፡፡

የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ለሀገሪቱ ደህንነትና ህልውና ወሳኝ ጉዳይ መሆኑንም ተናግረዋል፡

ኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብን በራሷ አቅም ሰርታ መጨረስ እንደምትችል ለዓለም አሳይታለች ያሉት ማስተር ቺፍ ዘሩሁን፤ አሁን ደግሞ የምታነሳውን ግልፅ የባህር በር ጥያቄ ከግብ ለማድረስ ትውልዱ በጋራ ሊቆም እንደሚገባ ገልፀዋል፡፡

የቀድሞ የባህር ኃይል አባል ሊዲንግሲማን ጥበቡ ተፈራ በበኩላቸው፤ የባህር በር ጥያቄ የንግድ መስመር ጥያቄ ብቻ ሳይሆን የሉዓላዊነትም ጥያቄ ነው ይላሉ፡፡

የህዳሴ ግድብ ለፍፃሜ መብቃት የዘመናት ቁጭትን የመለሰ እንደመሆኑ አሁንም ትውልዱ በኢኮኖሚ የማደግ ፍላጎቱን በባህር በር ሊደግመው እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡

በሐይማኖት ከበደ

በታማኝ ግብር ከፋዮች ገንዘብ አዲስ አበባ ተመራጭና ተወዳዳሪ እየሆነች ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ   ******************ከታማኝ ግብር ከፋዮች የሚሰበሰበው ገቢ አዲስ አበባን ለን...
16/10/2025

በታማኝ ግብር ከፋዮች ገንዘብ አዲስ አበባ ተመራጭና ተወዳዳሪ እየሆነች ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ
******************

ከታማኝ ግብር ከፋዮች የሚሰበሰበው ገቢ አዲስ አበባን ለንግድ እና ለመኖር የተመቸች እና በአለም አቀፍ ደረጃም ተመራጭና ተወዳዳሪ እያደረጋት ይገኛል ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለፁ፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለታማኝ ግብር ከፋዮች የእውቅና መርሐ ግብር አካሂዷል።

ከንቲባ አዳነች አቤቤ ይህን አስመልክቶ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ባጋሩት መልእክት፤ ዛሬ የከተማችንን ታማኝ ግብር ከፋዮች በታላቅ ድምቀት ሸልመናል፤ ተሸላሚ ግብር ከፋዮቻችን እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል፡፡

አዲስ አበባ ከታማኝ ግብር ከፋዮች በምትሰበስበዉ ገቢ በከተማዋ በአስደናቂ ሁኔታ ሜጋ ፕሮጀክቶች፣ የወንዝ ዳርቻና የኮሪደር ልማት፣ የተማሪዎች ምገባ እና ሌሎች የህዝቡን የኑሮ ጫና ያቀለሉ ስራዎች መሰራታቸውን ገልፀዋል፡፡

ይህም ከተማዋን ለንግድ እና ለመኖር የተመቸች እንዲሁም በአለም አቀፍ ደረጃም ተመራጭና ተወዳዳሪ እያደረጋት እንደሚገኝ ጠቁመዋል፡፡

ይህ ለዉጥ ለግብር ከፋዮች ተጨማሪ አሴት፣ ለቢዝነስ ማህበረሰቡ ተጨማሪ የሀብት መፍጠሪያ ምንጭ ነዉ ሲሉም ጠቅሰዋል።

በቀጣይ በግብር አሰባሰብ ዙሪያ የአገልግሎት አሰጣጥን ይበልጥ ዲጂታላይዝ በማድረግ፣ በማዘመን እና ተጠያቂነትን በማስፈንና ክፍተቶችን በመሙላት የሁለንተናዊ ብልፅግና ተምሳሌት የሆነች ከተማን እንገነባለን ብለዋል።

16/10/2025

በኋይት ሐውስ ውስጥ ግዙፍ አዳራሽ እንዲገነባ እና መንግሥታቸው ለያዘው አካባቢን የማስዋብ ሥራ ከፍተኛ ገንዘብ ድጋፍ ላደረጉ አሜሪካውያን ባለሃብቶች የእራት ግብዣ በማድረግ ምስጋና አቅርበዋል።

16/10/2025

የሀገር ጉዳይ
በቅርብ ቀን ይጠብቁን !

16/10/2025

FoodS Futures: Conversations for a Better World
Explore the future of food and agriculture through FAO’s Four Betters in a fast-paced, Davos-style talk series featuring a dynamic mix of FAO’s Core Leaders, chefs, activists, policymakers, and thought leaders.

ታማኝ ግብር ከፋዮች አዲስ አበባ እንደገና እንድትሰራ አድርገዋል - አቶ አገኘሁ ተሻገር**********************ታማኝ ግብር ከፋዮች አዲስ አበባ ለአፍሪካ ከተሞች ምሳሌ እንድትሆንና...
16/10/2025

ታማኝ ግብር ከፋዮች አዲስ አበባ እንደገና እንድትሰራ አድርገዋል - አቶ አገኘሁ ተሻገር
**********************

ታማኝ ግብር ከፋዮች አዲስ አበባ ለአፍሪካ ከተሞች ምሳሌ እንድትሆንና እንደገና እንድትሰራ በማድረግ የላቀ ሚና መወጣታቸውን የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር ገለጹ።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለታማኝ ግብር ከፋዮች የእውቅና መርሐ ግብር አካሂዷል።

የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር በዚሁ ወቅት፤ መንግሥት ኢትዮጵያን መካከለኛ ገቢ ካላቸው ሀገራት ተርታ ለማሰለፍ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያዎችን በጥራት እየተገበረ ይገኛል ብለዋል።

ለዚህም የገቢ ሰብሳቢ ተቋማት ኢኮኖሚው ከሚያመነጨው ሀብት በቂ ገቢ ለመሰብሰብና ሀገራዊ የልማት ዕቅዶችን ለማሳካት እየሰሩ መሆኑን ገልጸዋል።

የፌደራል መንግሥትም ሆነ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢ የመሰብሰብ አቅማቸው እያደገ ነው ያሉት አቶ አገኘሁ፤ በዚህም የማህበረሰቡን ፍትሐዊ የልማት ተጠቃሚነት እያረጋገጡ እንደሚገኙ ተናግረዋል።

ለዚህ ደግሞ የታማኝ ግብር ከፋዮች ሚና ወሳኝ መሆኑን በማንሳት፤ በከተሞች እድገት፣ በወጣቶች ስራ ዕድል ፈጠራና የዜጎችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት በሚያረጋግጡ ሌሎች ዘርፎች ጉልህ ስኬቶች መመዝገባቸውን አንስተዋል።

የአዲስ አበባን አዳጊ ፍላጎት በበቂ ደረጃ ለማሟላት የገቢ ሰብሳቢ ተቋማትና ግብር ከፋዮች ይበልጥ ተቀናጅቶ መስራትና ገቢ የመሰብሰብ አቅምን ማሳደግ አስፈላጊ መሆኑን መጥቀሳቸውን ኢዜአ ዘግቧል።

በገቢ ዘርፍ ሪፎርሙ የታክስ አሰባሰብና አስተዳደር ስርዓትን በማሻሻል የሚሰበሰበው ገቢ እያደገ መምጣቱን ገልጸው፤ ታማኝ ግብር ከፋዮች ለሀገርና ለከተማዋ ልማት ላበረከቱት አስተዋፅኦ አመስግነዋል።

16/10/2025

የምሽት 2 ሰዓት አማርኛ ዜና ... ጥቅምት 06/2018 ዓ.ም
#ኢቲቪ57

የኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ከፋኦ የእውቅና ሽልማት ተበረከተለት*********************የኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ከዓለም የምግብና እርሻ ድር...
16/10/2025

የኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ከፋኦ የእውቅና ሽልማት ተበረከተለት
*********************

የኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ከዓለም የምግብና እርሻ ድርጅት (ፋኦ) የእውቅና ሽልማት ተበርክቶለታል፡፡

ኢንስቲትዩቱ የተበረከተለት የእውቅና ሽልማት የፋኦ መርሐ ግብሮችን በብቃት በመተግበር በተለይም ዘላቂ የግብርና እና የገጠር ልማትን፣ የምግብ ዋስትናን እና ፈጠራን ለማሳደግ ባሳየው የላቀ አፈፃፀም መሆኑ ተመላክቷል፡፡

የኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ዋና ስራ አስፈጻሚ ማንደፍሮ ንጉሴ (ዶ/ር) በጣሊያን ሮም በሚገኘው የፋኦ ዋና መስሪያ ቤት ተገኝተው ከድርጅቱ የተበረከተውን ዓለም አቀፉን የስኬታማ ተቋም ሽልማት ተቀብለዋል፡፡

የዓለም የምግብና እርሻ ድርጅት በጣሊያን ሮም ባካሄደው የዓለም የምግብ ጉባኤ ላይ ለኢትዮጵያ አረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ምርጥ የዘላቂ የደን ልማት አያያዝና አጠቃቀም በሚል ዘርፍ ዕወቅና መስጠቱ ይታወሳል፡፡

Address

Shegole, Addisu Gebeya
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian Broadcasting Corporation posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Ethiopian Broadcasting Corporation:

Share

Our Story

Ethiopian Broadcasting Corporation is a national media which disseminates its news and programs world wide via Television,Radio and Website.