17/10/2025
"በሀገራችንም አንድ ለእናቱ የሆነው ባቡር በከተሞች ምሥረታ፣ ዕድገትና ትሥሥር ላይ ያለውን በጎ ተጽዕኖ ስናስብ በአንድ መቅረቱ በእጅጉ የሚያስቆጭ ነው።
ሀገር አቋራጭ የባቡር መሥመሮች ካላቸው ፍጥነትና የማጓጓዝ ዐቅም አንጻር ምርቶችን በተሻለ ክብካቤና ፍጥነት ለተለያዩ ገበያዎች ማድረስ ይችላሉ፡፡ በመላው ሀገራችን ብቻ ሳይሆን ከጎረቤት ሀገራትም ጭምር የሚያገናኙን መሆን ይገባቸው ነበር፡፡"
(የመደመር መንግሥት ገጽ 57)