Ethiopian Broadcasting Corporation

  • Home
  • Ethiopian Broadcasting Corporation

Ethiopian Broadcasting Corporation Ethiopian Broadcasting Corporation is a 24 hour working public media.

In addition to this Meta Page, we have other social media accounts:
Twitter
https://twitter.com/ebczena
Telegram
https://t.me/EBCNEWSNOW
Youtube
https://www.youtube.com/c/EBCworld
Instagram
https://www.instagram.com/ebcnews1/
Tiktok
https://www.tiktok.com/?lang=en



Ethiopian Broadcasting Corporation is a national media that disseminates its news and programs world wide via Television, Radio, and Website.

4 ቀን ቀረው***አረንጓዴ አሻራ "በመትከል ማንሰራራት" በ7ኛ ዓመት 700 ሚሊዮን ችግኞች በአንድ ጀምበር! ሐሙስ - ሐምሌ 24 ቀን 2017 ዓ.ም ኢትዮጵያውያን በጋራ ይተክላሉ።  #አረንጓ...
27/07/2025

4 ቀን ቀረው
***

አረንጓዴ አሻራ "በመትከል ማንሰራራት" በ7ኛ ዓመት 700 ሚሊዮን ችግኞች በአንድ ጀምበር!

ሐሙስ - ሐምሌ 24 ቀን 2017 ዓ.ም ኢትዮጵያውያን በጋራ ይተክላሉ።

#አረንጓዴዐሻራ #ኢቢሲ

ያገኘነው ነጻ የህግ አገልግሎት እንባችንን አብሷል፡- ተገልጋዮች*********************ወ/ሮ ደግነሽ ዳልጋ ከድሃ ቤተሰብ የተወለደች ስትሆን በትዳር አጋሯ ክህደት ተፈጽሞባት ስትቸገ...
26/07/2025

ያገኘነው ነጻ የህግ አገልግሎት እንባችንን አብሷል፡- ተገልጋዮች
*********************

ወ/ሮ ደግነሽ ዳልጋ ከድሃ ቤተሰብ የተወለደች ስትሆን በትዳር አጋሯ ክህደት ተፈጽሞባት ስትቸገር ቆይታ አሁን ባገኘችው ነጻ የህግ አገልግሎት ፍትህ ማግኘቷን ትናገራለች።

ክህደት የፈጸመባት የትዳር አጋሯ በራሱ የህግ ባለሙያ መሆኑ ሂደቱን አስቸጋሪ ቢያደርገውም በነጻ ከጎኗ በቆመላት የህግ ባለሙያ አማካኝነት እንባዋ መታበሱን አስረድታለች።

በተመሳሳይ አቅመ ደካሞች እና ህመምተኞች የሆኑት ወ/ሮ አየለች ቡና እና አቶ ዳንኤል ኩታፎ በኢኮኖሚ አቅም ውስንነት ምክንያት መሄጃ ባጡበት ጊዜ የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ነጻ የህግ አገልግሎት ክፍል ምንም ዓይነት ወጪ ሳያስወጣ ፍትህ እንዲያገኙ ማስቻሉን ተናግረዋል።

የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ከመንግስታዊ አካላት ጋር በመቀናጀት እስከአሁን የተሰጠውን ነጻ የህግ አገልግሎት አፈጻጸም ከባለድርሻዎች ጋር ገምግሟል።

ተቋሙ ነጻ የህግ አገልግሎት መስጠት ከጀመረ ወዲህ የህሊና እርካታ የሚሰጡ ሥራዎች መከናወናቸውን የሚናገሩት የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ጉዳዮች ም/ፕሬዚዳንት ዘውድነህ ቶማስ (ዶ/ር)፤ በወላይታ ዞን በ5 ማዕከላት የተሰጠው አገልግሎት ውጤታማ መሆኑን አስረድተዋል።

በዩኒቨርሲቲው የህግ ትምህርት ክፍል ዲን ረዳት ፕሮፌሰር ታመነ ኤና በበኩላቸው፥ በ2017 በጀት ዓመት 364 ዜጎች ነጻ የህግ አገልግሎት ማግኘታቸውን ጠቅሰው፤ በአዲሱ በጀት ዓመት ተደራሽነትን ለማስፋት የአገልግሎት ማዕከላትን ቁጥር ወደ 8 ለማሳደግ እንሰራለን ብለዋል።

የሚሰጠው አገልግሎት የፍትህ ተደራሽነትን ከማስፋት ረገድ ያለው አበርክቶ የላቀ በመሆኑ የባለድርሻዎች እገዛ ሊጎለብት እንደሚገባ ተመላክቷል።

በተመስገን ተስፋዬ

#ወላይታሶዶዩኒቨርሲቲ #ነጻየህግአገልግሎት

በረሮዎችን ለወታደራዊ ስለላ********************በረሮዎችን ለወታደራዊ ስለላ ለማሰማራት ምርምር እያደረገ ያለው የጀርመን ኩባንያ ምርምሩን ወደማጠናቀቁ መቃረቡን ይፋ አድርጓል።ስዋር...
26/07/2025

በረሮዎችን ለወታደራዊ ስለላ
********************

በረሮዎችን ለወታደራዊ ስለላ ለማሰማራት ምርምር እያደረገ ያለው የጀርመን ኩባንያ ምርምሩን ወደማጠናቀቁ መቃረቡን ይፋ አድርጓል።

ስዋርም ባዮታክቲክ የተባለውና ከጀርመን መንግሥት ወታደራዊ የቴክኖሎጂ ተቋም ጋር በቅርበት የሚሰራው ኩባንያ በበረሮዎች ላይ ጥቃቅን ካሜራዎች በመግጠምና ወደ ወታደራዊ ስፍራዎች በህብረት ወይም በተናጠል አስርጎ በማስገባት ወቅታዊ መረጃዎችን እንዲልኩ ለማድረግ መቻሉን አስታውቋል።

ከፍተኛ ወጪ ተመድቦ ሲካሄድ የነበረው ይህ ምርምር በበረሮዎች ላይ ምስጢራዊና ደህንነቱ የተጠበቀ ሊጠለፍ የማይችል መገናኛ መሳሪያ እንዲሁም ትናንሽ ዘመናዊ ካሜራ በመግጠም በርቀት ሆኖ በመቆጣጠርና በመምራት የስለላ ድሮን ማሰማራት ከማይቻልባቸው ቦታዎች መረጃዎችን ለማግኘት ያስችላል ተብሏል።

በቅርቡም ምርምሩ ሙሉ ለሙሉ ተጠናቅቆ ወደ ተግባር እንደሚገባ የኩባንያውን ምንጮች ዋቢ በማድረግ ሮይተርስ ዘግቧል።

ጤናማ ምግብ እና አመጋገብ እንዴት ያለ ነው?  *****************"የቅዳሜ መልክ" ፕሮግራም በ"ኑሮ በዘዴ" ዝግጅቱ "የተመጣጠነ አመጋገብ ለጤና" በሚል ርዕስ የሥነ-ምግብ ባለሙያዎች...
26/07/2025

ጤናማ ምግብ እና አመጋገብ እንዴት ያለ ነው?
*****************

"የቅዳሜ መልክ" ፕሮግራም በ"ኑሮ በዘዴ" ዝግጅቱ "የተመጣጠነ አመጋገብ ለጤና" በሚል ርዕስ የሥነ-ምግብ ባለሙያዎችን አቅርቦ አወያይቷል።

የማኅበረሰብ ሥነ-ምግብ ባለሙያው አብደላ አብዱለጢፍ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ በተለያዩ አካባቢዎች በርካታ ተፈጥሮአዊ የሆኑ የምግብ ዓይነቶች እንዳሏት፣ ነገር ግን እንዳልተጠቀምንባቸው ይገልፃሉ።

የአመጋገብ ሥርዓታችን በሁለት መንገድ አደገኛ ሁኔታ ውስጥ መግባቱንም ይናገራሉ።

ጥሩ ተመጋቢ ናቸው ብለን የምናስባቸው ሰዎች ምግባቸው ወደ ዘመናዊነት የተጠጋ እየመሰላቸው የተጠባበሱ ነገሮችን ማዘውተር ጀምረዋል ነው ያሉት።

በተዛባው የአመጋገብ ሥርዓት ምክንያት ያደጉ ሀገራት በርካታ የጤና ችግሮችን እያስተናገዱ መሆናቸውን ጠቅሰው፤ በነዚህ ሀገራት ካንሰር፣ ኩላሊት፣ የደም ግፊት፣ ስኳር፣ ከመጠን ያለፈ ውፍረት እና መሰል የጤና ችግሮች እየተንሰራፉ መምጣታቸውን ጠቅሰዋል።

ዝቅተኛ ገቢ ያለው ማኅበረሰብ አመጣጥኖ የሚመገበውን ማግኘት የማይችል መሆኑ ደግሞ ሌላ ችግር ነው ይላሉ ዶ/ር አብደላ።

በዚህኛው ወገን ደግሞ እንደ ወባ፣ ታይፎድ እና ታይፈስ የመሳሰሉት በሽታዎች እየተከሰቱ በመሆናቸው ጫናው እንደ ሀገር ከባድ መሆኑን አመላክተዋል።

"ይህን ጫና ለመቀነሳ የአያቶቻችንን ዓይነት ተፈጥሮአዊ አመጋገብ ብንከተል ረጅም ዕድሜ ከመኖር ባሻገር በሽታ የመከላከል አቅማችን የዳበረ ይሆናል ነው" ያሉት።

ለዚህ ደግሞ የሥነ-ምግብ ዕውቀትን ማስፋፋት እና የአንዱን ማህበረሰብ የአመጋገብ ባህል ወደ ሌላው ማሻገር እንደሚገባ ባለሙያው ምክረ ሀሳብ አቅርበዋል።

በአፍሪካ የምግብ ሉዓላዊነት ሕብረት ዳሬክተር የሆኑት ዶ/ር ሚሊዮን በላይ በበኩላቸው የኢትዮጵያ ባህላዊ ምግብ በመላው ዓለም በልዩነት እንደሚታወቅ ገልፀዋል።

የኢትዮጵያ ምግቦች በውስጣቸው የያዟቸውን ለሰውነት አስፈላጊ የሆኑ ንጥረ ነገሮች አብዛኛው ህብረተሰብ እንደማያውቅ አንስተው፤ ለጤናማ አመጋገብ ይህን የምግብ ሀብታችንን ማወቅ እንደሚያስፈልግ አመላክተዋል።

በንፍታሌም እንግዳወርቅ

#የቅዳሜመልክ

እሑድ ቤት - የእልፍኝ ጨዋታ ከማትያስ አንበርብር ጋርነገ ከ 8:00 ሰዓት ጀምሮ #እሑድቤት        #ሙሉዓለምታደሰ  #ሚካኤልታምሬ  #የእልፍኝገበታ    #የእልፍኝጨዋታ  #ዚያራ  #ቤት...
26/07/2025

እሑድ ቤት - የእልፍኝ ጨዋታ

ከማትያስ አንበርብር ጋር

ነገ ከ 8:00 ሰዓት ጀምሮ

#እሑድቤት #ሙሉዓለምታደሰ #ሚካኤልታምሬ #የእልፍኝገበታ #የእልፍኝጨዋታ #ዚያራ #ቤትለእንግዳ #ብታዩት #ሄሎኢትዮጵያ #ደርሶመልስ

የጋምቢያ ግብርና ሚኒስትር በተመድ የምግብ ሥርዓት ጉባኤ ለመካፈል አዲስ አበባ ገቡ*******************በሁለተኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የምግብ ሥርዓት ጉባኤ ላይ ለመሣተፍ ...
26/07/2025

የጋምቢያ ግብርና ሚኒስትር በተመድ የምግብ ሥርዓት ጉባኤ ለመካፈል አዲስ አበባ ገቡ
*******************

በሁለተኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የምግብ ሥርዓት ጉባኤ ላይ ለመሣተፍ የተለያዩ ሀገራት መሪዎችና እንግዶች አዲስ አበባ በመግባት ላይ ያገኛሉ።

የጋምቢያ ግብርና ሚኒስትር ዶክተር ዲንባ ሳባሊ ዛሬ ምሽት ላይ አዲስ አብ ገብተዋል።

ሚኒስትሩ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ፕሮፌሰር እያሱ ኤሊያስ እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች አቀባበል አድርገውላቸዋል።

በእንቻለው አያሌው

አርሰናል ጊዮኬሬሽን ማስፈረሙን ይፋ አደረገ*********************አርሰናል ቪክቶር ጊዮኬሬሽን ከስፖርቲንግ ሊዝበን ማስፈረሙን ይፋ አድርጓል።ዜናውን አስተያየት መስጫው ላይ ባለው ሊ...
26/07/2025

አርሰናል ጊዮኬሬሽን ማስፈረሙን ይፋ አደረገ
*********************

አርሰናል ቪክቶር ጊዮኬሬሽን ከስፖርቲንግ ሊዝበን ማስፈረሙን ይፋ አድርጓል።

ዜናውን አስተያየት መስጫው ላይ ባለው ሊንክ ያገኙታል።

የዛምቢያና ማሊ ግብርና ሚኒስትሮች በተመድ የምግብ ሥርዓት ጉባዔ ላይ ለመካፈል አዲስ አበባ ገቡ****************የዛምቢያ ግብርና ሚኒስትር ሪዩበን ፊሪ ምቶሎና የማሊ ግብርና ሚኒስትር...
26/07/2025

የዛምቢያና ማሊ ግብርና ሚኒስትሮች በተመድ የምግብ ሥርዓት ጉባዔ ላይ ለመካፈል አዲስ አበባ ገቡ
****************

የዛምቢያ ግብርና ሚኒስትር ሪዩበን ፊሪ ምቶሎና የማሊ ግብርና ሚኒስትር ዳንኤል ሲሚዮን ከሊማ ቦሌ አየር ማረፊያ ሲደርሱ፤ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ሳህረላ አብዱላሂና የፍትህ ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ኤርሚያስ የማነብርሃን አቀባበል አድርገውላቸዋል።

በኢትዮጵያ ከሐምሌ 20 እስከ ሐምሌ 22 ቀን 2017 ዓ.ም በሚካሄደው ዓለም አቀፍ ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ ከተለያዩ ሀገራት እንግዶች አዲስ አበባ እየገቡ ይገኛሉ።

በእንቻለው አያሌው

እሑድ ቤት - የእልፍኝ ጨዋታ ከአበባው ጌታቸው ጋርነገ ከ 8:00 ሰዓት ጀምሮ #እሑድቤት        #ሙሉዓለምታደሰ  #ሚካኤልታምሬ  #የእልፍኝገበታ    #የእልፍኝጨዋታ  #ዚያራ  #ቤትለእ...
26/07/2025

እሑድ ቤት - የእልፍኝ ጨዋታ

ከአበባው ጌታቸው ጋር

ነገ ከ 8:00 ሰዓት ጀምሮ

#እሑድቤት #ሙሉዓለምታደሰ #ሚካኤልታምሬ #የእልፍኝገበታ #የእልፍኝጨዋታ #ዚያራ #ቤትለእንግዳ #ብታዩት #ሄሎኢትዮጵያ #ደርሶመልስ

የኬኒያ ቀዳማዊት እመቤት ሬቸል ሩቶ በተመድ የምግብ ሥርዓት ጉባኤ ለመካፈል አዲስ አበባ ገቡ*****************የኬኒያ ቀዳማዊት እመቤት ሬቸል ሩቶ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የምግ...
26/07/2025

የኬኒያ ቀዳማዊት እመቤት ሬቸል ሩቶ በተመድ የምግብ ሥርዓት ጉባኤ ለመካፈል አዲስ አበባ ገቡ
*****************

የኬኒያ ቀዳማዊት እመቤት ሬቸል ሩቶ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የምግብ ሥርዓት ጉባኤ ለመካፈል አዲስ አበባ ገብተዋል።

ቀዳማዊት እመቤቷ አዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ሲደርሱ የሴቶች እና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ሁሪያ አሊ ተቀብለዋቸዋል።

ከሐምሌ 20 እስከ 22/2017 ዓ.ም ኢትዮጵያ የምታስተናግደው 2ኛው የተመድ የምግብ ሥርዓት ጉባኤ ትኩረቱን በዋናነት በሥርዓተ ምግብ ሽግግር ላይ አድርጎ ይካሄዳል።

26/07/2025

እድሜ ያልበገራቸው ብርቱዋ እናት እቴነሽ ፈለቀ ዛሬም ሥራ ላይ ናቸው |ብርቱ መዳፍ

የኬኒያ የግብርናና እንስሳት ሀብት ሚኒስትር በ2ኛው የተመድ የምግብ ሥርዓ ጉባኤ ለመካፈል አዲስ አበባ ገቡ******************የኬኒያ የግብርናና እንስሳት ሀብት ሚኒስትር ሙታሂ ካግዌ...
26/07/2025

የኬኒያ የግብርናና እንስሳት ሀብት ሚኒስትር በ2ኛው የተመድ የምግብ ሥርዓ ጉባኤ ለመካፈል አዲስ አበባ ገቡ
******************

የኬኒያ የግብርናና እንስሳት ሀብት ሚኒስትር ሙታሂ ካግዌ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የምግብ ሥርዓት ጉባኤ ለመካፈል አዲስ አበባ ገቡ።

ሚኒስትሩ አዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የኢንዱስትሪ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ታረቀኝ ቡሉልታ፣ የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር መለስ መኮነን እንዲሁም ሌሎች ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች አቀባበል አድርገውላቸዋል።

ኢትዮጵያ ከሐምሌ 20 እስከ 22/2017 ዓ.ም የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የምግብ ሥርዓት ጉባኤን በአዲስ አበባ ታስተናግዳለች።

የምግብ ሥርዓት ጉባኤው በሐምሌ ወር 2015 ዓ.ም በጣልያን ሮም የተካሄደው የመጀመሪያ የተመድ የምግብ ሥርዓት ጉባኤ ላይ የተገቡ ቃሎች ትግበራ ሂደትን መነሻ በማድረግ የሚካሄድ ነው።

በእንቻለው አያሌው

Address


Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian Broadcasting Corporation posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Ethiopian Broadcasting Corporation:

Shortcuts

  • Address
  • Alerts
  • Contact The Business
  • Claim ownership or report listing
  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share

Our Story

Ethiopian Broadcasting Corporation is a national media which disseminates its news and programs world wide via Television,Radio and Website.