Ethiopian Broadcasting Corporation

Ethiopian Broadcasting Corporation Ethiopian Broadcasting Corporation is a 24 hour working public media.

In addition to this Meta Page, we have other social media accounts:
Twitter
https://twitter.com/ebczena
Telegram
https://t.me/EBCNEWSNOW
Youtube
https://www.youtube.com/c/EBCworld
Instagram
https://www.instagram.com/ebcnews1/
Tiktok
https://www.tiktok.com/?lang=en



Ethiopian Broadcasting Corporation is a national media that disseminates its news and programs world wide via Television, Radio, and Website.

10/06/2026

የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መግለጫ

የ5ቱ ዓመታት ገፆች፡ በመደመር ትውልድ ያበበችውና ነዋሪዎቿን ያከበረችው አዲሲቱ ከተማ******************የከተሜነት እውነተኛ ትርጉም በሰማይ ጠቀስ ህንፃዎች መደርደር ወይም በኮንክሪ...
10/06/2026

የ5ቱ ዓመታት ገፆች፡ በመደመር ትውልድ ያበበችውና ነዋሪዎቿን ያከበረችው አዲሲቱ ከተማ
******************

የከተሜነት እውነተኛ ትርጉም በሰማይ ጠቀስ ህንፃዎች መደርደር ወይም በኮንክሪት ክምችት ብቻ ሳይሆን፣ ነዋሪዎች በክብር፣ በምቾትና በደህንነት በሚኖሩበት ዘመናዊ ሥርዓት ይለካል።

ካለፈው 6ኛው ሀገራዊ ምርጫ እስከ 7ኛው ምርጫ ዋዜማ በተዘረጉት አምስት ዓመታት፣ የመደመር ትውልድ የከተሞቻችንን የትላንት ገፅታ በመቀየር፣ ከተሞችን ከድህነትና ከጥግግት አውጥቶ ለነዋሪዎቻቸው የተመቹ የብልፅግና ማዕከላት እንዲሆኑ አስደናቂ ስራዎችን በመንግሥት መሪነት አከናውኗል።

በእነዚህ የ5ቱ ዓመታት ገፆች ጎልቶ ከሚታየው ስኬት አንዱ የቤት ልማት አብዮት ነው። ቀደም ሲል ዘላቂና ውጤታማ ያልነበረውን የቤት ልማት ፕሮግራም በአዲስ መልክ በመቃኘት ታላቅ የቤት አቅርቦት ንቅናቄ ተደርጓል።

መንግሥት በዋነኝነት ሲያከናውነው የነበረውን ልማት ከግል ዘርፉ እንዲሁም ከመንግሥትና የግል አጋርነት (PPP) ጋር በማስተሳሰር የቤቶች ልማት በከፍተኛ ፍጥነት እንዲከናወን ተደርጓል። በዚህም ከ2013 እስከ 2017 በጀት ዓመት ባሉት ጊዜያት ብቻ ከመንግሥት፣ ከሪል ስቴት አልሚዎችና ከግል ቤት ሠሪዎች አቅም ጋር ተደምሮ ከ1.1 ሚሊዮን በላይ ቤቶች ተገንብተዋል። ከዚህ ጎን ለጎንም፣ ዐቅማቸው ዝቅተኛ ለሆኑ ቤት ፈላጊዎች በመንግሥት በኩል የሚከናወኑ የቤት ልማት ፕሮግራሞች ሳይቋረጡ ቀጥለዋል።

የመደመር ከተሜነት ሰውን ማዕከል ያደረገ በመሆኑ፣ ማኅበረሰብን በማስተባበር ዐቅመ ደካማ ለሆኑ ወገኖች 166,207 ደረጃቸውን የጠበቁ ቤቶች ተገንብተው ተላልፈዋል። ከተሞችን ከእርጅናና ከድህነት ገፅታ ለማላቀቅ፣ በዝቅተኛ ደረጃ ላይ የሚገኙ ቤቶችን ደረጃ የማሳደግ ሥራ በስፋት ተከናውኗል። በ2013 ዓ.ም ከ75 በመቶ በላይ የነበረውን ከደረጃ በታች የሆኑ (substandard) ቤቶች ድርሻ፣ በ2017 ዓ.ም ወደ 52 በመቶ ዝቅ ማድረግ ተችሏል። ይህ ዜጎችን ከማይመችና ኋላቀር አኗኗር ወደ ዘመናዊ የኑሮ ሁኔታ በፈቃደኝነት ያሸጋገረ የክብር ጉዞ ነው።

ይህ ታላቅ የከተማ ትራንስፎርሜሽን የሲቪል ሰርቪሱንና የከተሞችን አገልግሎት ከማዘመን ጋር ተጣምሮ የተጓዘ ነው። ከተሞች ዘመኑን የዋጀ አደረጃጀትና የአስተዳደር ሥርዓት እንዲኖራቸው በማድረግ፣ የማዘጋጃ ቤት አገልግሎቶች ለዜጎች በተሻለ ቅልጥፍና እንዲቀርቡ ተደርጓል።

ይሁን እንጂ፣ መንግሥት ከተሞችን በተቀናጀ አግባብ ሲያለማ፣ አንዳንድ ኃይሎች ይህንን የልማት አቅጣጫ ባለመረዳት የተዛባ አመለካከት ሲያራምዱ ቆይተዋል። ዜጎችን ወደ ተሻለ የኑሮ ሁኔታ ለማሸጋገር የሚሰሩትን የመልሶ ማልማት ስራዎች "ማፈናቀልና ማህበራዊ ኢንጂነሪንግ" ብለው ሲስሉ፣ የከተማን ይዞታ ስርዓት ለማስያዝና አረንጓዴ ቦታዎችን ለመጠበቅ የሚወሰዱ ህጋዊ እርምጃዎችን በሌላ ስም ለማጠልሸት ሞክረዋል። አልፎ ተርፎም ከተሞቻችን ባህላችንንና ታሪካችንን እንዲያንፀባርቁ ለማድረግ የተሰሩትን የውበት ሥራዎች "ታሪክን እንደ ማውደም" አድርገው አቅርበዋል።

ሆኖም እውነታው በተግባር ሊደበቅ አይችልም። ዜጎቻችን የስራዎቹን ፋይዳ አውቀው ምስክርነታቸውን ሲሰጡ፣ የውጭ ሀገራት ሚዲያዎችና ዜጎች ሳይቀሩ በከተሞቻችን ላይ የተመዘገቡትን አስደናቂ ለውጦች እያደነቁ ይገኛሉ። የአገልግሎት አሰጣጥን ለማዘመንና የሲቪል ሰርቪሱን ውጤታማ ለማድረግ የሚከናወኑ ሪፎርሞችንም አሉታዊ ስም በመስጠት ለውጡን ለማደናቀፍ የተሞከሩ ሙከራዎች ከሽፈዋል። በአጠቃላይ እነዚህ የ5ቱ ዓመታት ገፆች፣ መንግሥት ከተሞችን የነገው ዘመን የሥልጣኔ ማዕከላት ለማድረግ ያለውን ግልጽ አቋምና የማድረግ አቅም በተግባር ያረጋገጡ፣ እንዲሁም ለነዋሪዎቻቸው ምቹና ዘመናዊ ከተሞችን የፈጠሩ ደማቅ ታሪካዊ ምዕራፎች ናቸው።

በአዶኒያስ ወልደአረጋይ

Ethiopian Broadcasting Corporation #አዲስአበባ #ከተማ #አሻራ #ኢትዮጵያ #የመደመርትውልድ #ምገባ #የተማሪዎችምገባ

10/06/2026

የ5 ዓመታቱ ገፆች

የዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የአጀንዳ ቀረፃ ዝግጅት መጨረሻ ምዕራፍ ላይ ደርሷል-ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ****************የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ዋናው ሀገራዊ ጉባ...
10/06/2026

የዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የአጀንዳ ቀረፃ ዝግጅት መጨረሻ ምዕራፍ ላይ ደርሷል-ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ
****************

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ዋናው ሀገራዊ ጉባኤ የአጀንዳ ቀረፃ ዝግጅት መጨረሻ ምዕራፍ ላይ መድረሱን የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ አስታወቁ።

የአጀንዳ ማሰባሰብና ተሳታፊ ልየታ የምክክር ሂደት ስኬት በዜጎች መካከል ብሔራዊ መግባባትን ማስፈን የሚያስችል ተምሳሌታዊ አቅምና ተቋም መፈጠሩን እንደሚያሳይም ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከሀገር አቀፍና የክልል ፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር የሀገራዊ ምክክር አጀንዳ ቀረጻ ግብዓት ማሰባሰቢያ የውይይት መርሃ ግብር እያካሄደ ይገኛል።

የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ፤ኮሚሽኑ ያከናወናቸውን ተግባራትና የእስካሁን ሂደቶችን በማስመልከት ማብራሪያ ሰጥተዋል።

በሀገራዊ ምክክር የአጀንዳ ማሰባሰብ፣የተሳታፊ ልየታና ዋናውን የምክክር ጉባኤ የማካሄድ ዝግጅት ስኬታማ ሥራ መሰራቱን ገልጸዋል።

ኢትዮጵያውያንና ባለድርሻ አካላት በእስካሁኑ ሂደት የነበራቸው ንቁ ተሳትፎም ነጻና ገለልተኛ ሀገራዊ ምክክርን ማስተባበር የሚያስችል አቅምና ተቋም መፈጠሩን እንደሚያሳይ ተናግረዋል።
የአጀንዳ ማሰባሰብ ሥራውም በታላላቅ ህዝባዊ መድረኮች በቀጥታና በጥናት ለኮሚሽኑ ቀርበው የማሰባሰብ ሥራ በስፋት መከናወኑን አብራርተዋል።

በአጀንዳ ማሰባሰብና ተሳታፊ ልየታ የነበረው የህዝብና የባለድርሻ አካላት ተሳትፎም ለሚሰሩ ሥራዎች ጥልቅ መነሻ የሚሆኑ የሀገር ሃብቶች መሆናቸውን አስረድተዋል።

በዋናው ሀገራዊ ጉባኤ የአጀንዳ ሃሳብ የሚሰጡና የሚሳተፉ ተወካዮች በሁሉም ወረዳዎችና ከተሞች የማስመረጥ ስራ 93 በመቶ መፈጸም እንደተቻለ አስገንዝበዋል።

የአጀንዳ ማሰባሰብና ተሳታፊ ልየታ አካታችነት፣ነጻና ዴሞክራሲያዊ ተሳትፎም ለሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ወሳኝ ምዕራፍ መሰረት መጣሉን ማንሳታቸውን ኢዜአ ዘግቧል።

የዋናው ሀገራዊ ጉባኤ የአጀንዳ ቀረጻ ዝግጅት የማጠቃለያ ምዕራፍ ላይ ደርሷል ያሉት ፕሮፌሰር መስፍን፤የፖለቲካ ፓርቲዎችም የእስካሁኑ ሂደት ጉልህ ተሳትፏቸውን እንዲያስቀጥሉ ጠይቀዋል።

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር የእስካሁኑ ሂደት አካታች፣ነጻና ዴሞክራሲያዊነትም ተምሳሌታዊ የምክክር አቅምና ተቋም መፈጠሩን እንደሚያሳይ አስገንዝበዋል።

የ5ቱ ዓመታት ገፆች፡ የሚያጎርሱ ሩህሩህ እጆች*************ካለፈው 6ኛው ሀገራዊ ምርጫ አንስቶ ወደ 7ኛው ምርጫ ዋዜማ ስንሸጋገር፣ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ በወርቅ ቀለም ደምቀው ከሚታ...
10/06/2026

የ5ቱ ዓመታት ገፆች፡ የሚያጎርሱ ሩህሩህ እጆች
*************

ካለፈው 6ኛው ሀገራዊ ምርጫ አንስቶ ወደ 7ኛው ምርጫ ዋዜማ ስንሸጋገር፣ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ በወርቅ ቀለም ደምቀው ከሚታዩት ገፆች መካከል አንዱና ዋነኛው ሰውን ማዕከል ያደረገው ታላቅ የልማት ስራ ነው።

የመደመር ትውልድ "ሰውን የዘነጋ ልማት የጥፋት ያህል ነው" በሚል ጽኑ የሞራል እሳቤ፣ የልማት ትርጓሜን ከረዣዥም ኮንክሪትና ከአስፋልት ንጣፍ ባሻገር ወደ ዜጎች ማዕድ ላይ አምጥቶታል። ልማት ትርጉም የሚኖረው የነዋሪውን በተለይም የነገ ሀገር ተረካቢ ህፃናትን ህይወት ሲታደግ ነው በሚል መርህ፣ የመንግስት የትኩረት ማዕከል ወደ ሰው ተመልሷል።

የዚህ ሰው-ተኮር እሳቤ ቁንጮና አስደናቂ ስኬት የተማሪዎች ምገባ ፕሮግራም ነው። ትላንት በባዶ ሆዳቸው ትምህርት ቤት እየዋሉ አዕምሯቸው በረሃብ ይዝል የነበሩ፣ በርሀብ ይወድቁ የነበሩ ህፃናትን ታሪክ የመደመር ትውልድ ቀልብሶታል።

ትናንት ከቤታቸው ሲወጡ አንጀታቸው እየተላወሰ፣ ትምህርት ገበታ ላይ በድካም ይወድቁ የነበሩ ህፃናትን የሰቆቃ ታሪክ ዛሬ ታሪክ ሆኗል፡፡ "መጪው ትውልድ የኔ ነው" ብሎ በሃላፊነት መንፈስ የተነሳው ይህ ትውልድ፣ ቢያንስ ለመማር ተማሪው ምግቡንና የትምህርት ቁሳቁሱን እንዳይቸገር በሚል ርኅራኄ በተሞላበት አቋም ይህን የተቀደሰ ዘመቻ ጀመረ። በዚህም በሚሊዮን የሚቆጠሩ ተማሪዎች በቀን ሁለት ጊዜ ትኩስና የተመጣጠነ ምግብ በትምህርት ቤታቸው እንዲያገኙ ተደርጓል።

ይህ ፕሮግራም የመንግስትን የልማት አቅጣጫ ከማሳየት ባለፈ፣ ኢትዮጵያዊውን የመረዳዳት እሴት በላቀ ደረጃ ያነቃቃ ሆኗል። ሚሊዮኖችን ተጠቃሚ ያደረጉት የተማሪዎች ምገባ ርኅራኄን ተቋማዊ በማድረግ፣ ዜጎች እርስ በእርሳቸው እንዲተጋገዙና የሚያስችል የእሳቤ መሰረት ተጥሏል።

ከምገባው ጎን ለጎንም የትምህርት ቁሳቁሶችን፣ ደብተሮችን እና የደንብ ልብሶችን በነፃ በማቅረብ፣ ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው ቤተሰብ ልጆች የኑሮ ጫና ሳይበግራቸው ከሌሎች እኩዮቻቸው ጋር በእኩልነት እንዲማሩ ታላቅ መደላድል ተፈጥሯል።

በዚህም በጠዋት ተነስተው "ልጄ ምን በልቶ ይውላል?" የሚለው የድሃ እናቶች የዘወትር ጭንቀት ቀልሏል። የልጆች የስነ-ልቦና ስብራት ተጠግኖ፣ የሀብታምም ሆነ የድሃ ልጅ አንድ አይነት የደንብ ልብስ ለብሰው፣ ከአንድ ማዕድ እየተመገቡ የመደመርን ትክክለኛ ትርጉም በትምህርት ቤታቸው ግቢ ውስጥ መኖር ችለዋል።

የተማሪዎች ምገባ ስራ ፋይዳው ዛሬ ሆድን ከመሙላትም እጅግ የዘለለ ነው። ይህ ተግባር የነገዋን ኢትዮጵያ የሚረከብ፣ በአካልና በአእምሮ የዳበረ፣ ጤናማና ብቁ ትውልድ የመፍጠር ጥልቅ ሀገራዊ ራዕይ ያለው ተግባር ነው።

በልጅነት ዕድሜ የተመጣጠነ ምግብ ማግኘት ለአእምሮ እድገት ወሳኝ በመሆኑ፣ የዛሬው ምገባ የነገውን የምርምር፣ የፈጠራና የአመራር አቅም ማጎልበት ማለት ነው። በርሃብ ምክንያት ከትምህርት ገበታ የሚቀሩ ተማሪዎች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ የቀነሰ ሲሆን፣ የትምህርት አቀባበላቸውና ውጤታቸውም የዚያኑ ያህል ሊሻሻል ችሏል።

በአጠቃላይ፣ እነዚህ የ5ቱ ዓመታት ገፆች የመደመር ትውልድ ፖለቲካን ከሰብዓዊነት ጋር ያዋሀደበት፣ የነገን ትውልድ በዛሬ ርኅራኄ ያነፀበት ደማቅ የታሪክ ምዕራፍ ናቸው። ፖለቲካ ማለት የስልጣን ሽኩቻ ብቻ ሳይሆን የዜጎችን እንባ ማበስና የተራቡትን ማጉረስ መሆኑን በተግባር አሳይቷል።

በአዶኒያስ ወልደአረጋይ

Ethiopian Broadcasting Corporation #አዲስአበባ #ከተማ #አሻራ #ኢትዮጵያ #የመደመርትውልድ #ምገባ #የተማሪዎችምገባ

2.3 ትሪሊዮን ብር ለላቀ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ሽግግር***************የላቀ የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ሽግግር ለማምጣትና የተጀመሩ ሀገራዊ የለውጥ ጥረቶችን ለማሳካት፣ የሚኒስትሮች ምክ...
10/06/2026

2.3 ትሪሊዮን ብር ለላቀ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ሽግግር
***************

የላቀ የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ሽግግር ለማምጣትና የተጀመሩ ሀገራዊ የለውጥ ጥረቶችን ለማሳካት፣ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ባካሄደው 56ኛ መደበኛ ስብሰባ የ2019 በጀት ዓመት የፌደራል መንግሥት በጀት 2.3 ትሪሊዮን ብር ሆኖ እንዲጸድቅ ረቂቅ ሰነዱን ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መርቷል።

ይህ የተመደበው በጀት ባለፉት አምስት ዓመታት ከተመዘገቡት ስኬቶች መነሻነት፣ እንዲሁም የአስር ዓመቱ መሪ የልማት እቅድ አካል በሆነው የልማትና ኢንቨስትመንት ግቦች ላይ ተመስርቶ የተዘጋጀ መሆኑ ተገልጿል።

የምጣኔ ሀብት ባለሙያው ቆስጠንጢኖስ በርኸተስፋ (ዶ/ር) እንደገለጹት፣ ይህ የበጀት መጠን ማደግ መንግሥት ካለው የማስፈጸም አቅምና የፊስካል ፖሊሲ ጥንካሬ ጋር የተያያዘ ነው።

መንግሥት በአንድ በኩል ያለው ገቢ በከፍተኛ ደረጃ እየጨመረ መምጣቱን ያሳየ ሲሆን፣ ይህም ገቢ ከታክስ የሚሰበስበውን፣ ከተለያዩ ዓለም አቀፍ ብድሮችና እርዳታዎች፣ እንዲሁም በኤክስፖርት እና ከዲያስፖራ የሚገኘውን ገቢ እንደሚጨምር አስገንዝበዋል።

ባለፉት ጊዜያት የተጀመሩ እና የተጠናቀቁ ግዙፍ ሀገራዊ ፕሮጀክቶች የኢትዮጵያን የመፈጸም አቅም በተግባር ያሳዩ መሆናቸውን አመላክተዋል። በዚህ መነሻነትም ካለፈው በተሻለ የ2019 በጀትም ለተለያዩ ፕሮጀክቶችና ማህበራዊ አገልግሎቶች ሊውል የሚችል በጀት መሆኑን ጠቅሰዋል።

ዶ/ር ቆስጠንጢኖስ አያይዘውም የ2019 በጀት ከ2018 ብልጫ ማሳየቱ በትምህርት፣ በጤና፣ በመሰረተ ልማት እና በስራ እድል ፈጠራ ዙሪያ ሰፊ መሻሻሎችን ለማምጣት ትልቅ ትርጉም እንዳለው ጠቅሰዋል። ሆኖም የታሰበውን የኢኮኖሚ እድገት በዘላቂነት ለማስቀጠል ሰላምና ደህንነትን ማረጋገጥ ወሳኝ መሆኑን ባለሙያው ጠቁመዋል።

ሀገራችን ያላትን የሰው ኃይል፣ የውኃ፣ የግብርና እና የማዕድን ሀብት በአግባቡ ለመጠቀም የጸጥታ ችግሮችን በዘላቂነት መፍታት፣ ሕገወጥ የገንዘብ ዝውውርንና ሕገወጥ ንግድን በቁርጠኝነት መግታት እንደሚገባ ዶ/ር ቆስጠንጢኖስ ገልጸዋል።

ለዚህም የሲቪል ማህበረሰቡ እና የሚዲያ ተቋማት በንቃት በመሳተፍ ሕገወጥ አሰራሮችን እንዲያጋልጡና የሕግ የበላይነት እንዲከበር ማድረግ እንደሚገባ ገልጸው፣ የዘንድሮው የ2.3 ትሪሊዮን ብር ረቂቅ በጀት የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ አቅምና የገቢ አሰባሰብ ሥርዓት በከፍተኛ ሁኔታ እያደገ ስለመሆኑ ግልጽ ማሳያ ነው ብለዋል።

በቤተልሔም ገረመው

10/06/2026

አዲስ አበባ ስሟን መኖር ጀመረች

በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን በበጋ መስኖ የለማው የስንዴ ሰብል በኮምባይነር እየተሰበሰበ ነው****************በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ቅምብቢት ወረዳ በበጋ መስኖ የለማው የ...
10/06/2026

በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን በበጋ መስኖ የለማው የስንዴ ሰብል በኮምባይነር እየተሰበሰበ ነው
****************

በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ቅምብቢት ወረዳ በበጋ መስኖ የለማው የስንዴ ሰብል ዘመናዊ የግብርና መሣሪያዎችን (ኮምባይነር) በመጠቀም የመሰብሰብ ሥራ በስፋት እየተከናወነ ይገኛል።

የኦሮሚያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አወሉ አብዲን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችም በወረዳው በመገኘት ይህንን የሰብል አሰባሰብ ንቅናቄ በአካል ተመልክተዋል።

የአካባቢው አርሶ አደሮች ቀደም ሲል በነበረው ልማድ በዓመት አንድ ጊዜ ብቻ ያመርቱ እንደነበር አስታውሰው፣ በአሁኑ ወቅት ግን በበጋ መስኖ ልማት አማካኝነት በዓመት ሁለትና ከዚያ በላይ ማምረት መቻላቸውን ገልጸዋል።

ይህ የሥራ ንቅናቄ የምርት መጠንን ከማሳደጉም በላይ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነታቸውን ይበልጥ እንዳጎናጸፋቸው አርሶ አደሮቹ ተናግረዋል።

የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አወሉ አብዲ በበኩላቸው፣ እንደ ሀገር በምግብ ራስን ለመቻልና የሀገርን ሉዓላዊነት ለማረጋገጥ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

በኦሮሚያ ክልልም ሁሉንም ወቅቶች በመጠቀም ለማምረት ሰፊ ስትራቴጂ መዘርጋቱን የጠቀሱት አቶ አወሉ፣ በተለይም በበጋ ወቅት ስንዴን ጨምሮ ሌሎች ጠቃሚ ሰብሎች እንዲመረቱ በቁርጠኝነት እየተሠራ መሆኑን አስገንዝበዋል።

በዚህም መሠረት በተለያዩ የክልሉ አካባቢዎች በበጋ ስንዴ አማካኝነት በዓመት ሁለትና ከዚያ በላይ ምርት እንዲገኝ እየተደረገ መሆኑን ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ ጠቁመዋል።

የአሁኑ የምርት አሰባሰብ ሂደትም ይበልጥ በቴክኖሎጂና በመካናይዜሽን የታገዘ እንዲሆን እየተደረገ መሆኑን ያነሱት አቶ አወሉ፣ የክልሉ መንግሥት የአርሶ አደሩን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ይበልጥ ለማረጋገጥ በትኩረት እየሠራ እንደሚገኝም አረጋግጠዋል።

በአባዲ ወይና

10/06/2026

قوات الدفاع الوطني الإثيوبية.. الحصن المنيع لسيادة الوطن

Address

Shegole, Addisu Gebeya
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian Broadcasting Corporation posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Ethiopian Broadcasting Corporation:

Share