Ethiopian Broadcasting Corporation

Ethiopian Broadcasting Corporation Ethiopian Broadcasting Corporation is a 24 hour working public media.

In addition to this Meta Page, we have other social media accounts:
Twitter
https://twitter.com/ebczena
Telegram
https://t.me/EBCNEWSNOW
Youtube
https://www.youtube.com/c/EBCworld
Instagram
https://www.instagram.com/ebcnews1/
Tiktok
https://www.tiktok.com/?lang=en



Ethiopian Broadcasting Corporation is a national media that disseminates its news and programs world wide via Television, Radio, and Website.

የጋምቤላ ክልልን በማር ምርት ማስጠራት እፈልጋለሁ - አቶ ቲቶ ሐዋርያት***************የቀድሞው ፖለቲካኛ የአሁን የግብርና ኢንቨስተር አቶ ቲቶ ሐዋርያት ወደ ግብርና ሥራ በመግባት በ...
23/08/2025

የጋምቤላ ክልልን በማር ምርት ማስጠራት እፈልጋለሁ - አቶ ቲቶ ሐዋርያት
***************

የቀድሞው ፖለቲካኛ የአሁን የግብርና ኢንቨስተር አቶ ቲቶ ሐዋርያት ወደ ግብርና ሥራ በመግባት በጋምቤላ ክልል በግብርና ኢንቨስትመንት ላይ ተሰማርተዉ ስኬታማ ሆነዋል።

አሁን ላይ ከ300 በላይ የንብ ቀፎ አንዳላቸዉ እና የጋምቤላ ክልልን በማር ምርት ለማስጠራት እየሰሩ መሆኑን አንስተዋል።

ከባህላዊ የንብ ቀፎ በመጀመር ወደ ዘመናዊ የንብ ቀፎ መሸጋገራቸውን የሚያነሱት አቶ ቲቶ፤ በዓመት ከ2000 ኪሎ ግራም በላይ የተጣራ ማር እንደሚያገኙም ይገልፃሉ።

ከራሳቸዉ እና በአከባቢው ማር ከሚያመርቱ ገበሬዎች ማር በመግዛት በተመጣጠኝ ዋጋ ገዝተዉ በማቅረብ በፊት በሶስት ወር ደሞዝ የሚያገኙትን አሁን ላይ በሶስት ቀን ማግኘት መቻላቸዉን ተናግረዋል።

አቶ ኦኮሞ ጅዋቶ ኦኮክ እንዲሁ በተለያዩ የቅጥር ስራዎች ያሳለፉ ሲሆን አሁን ላይ በግብርና ስራ ተሰማርተው ውጤት ማስመዘግብ ችለዋል።

ከመንግሥት የመስሪያ መሬት ተሰጥቷቸው መሬቱን በማልማት ሰሊጥ እና በቆሎ በማምረት ውጤታማ መሆናቸውንም ገልጸዋል።

በቢታንያ ሲሳይ

የአካል ጉዳት ሳይበግራቸው ኑሮን ለማሸነፍ የሚተጉት ብርቱ አባት****************ኩሻ ጉርሙ ይባላሉ፤ ተወልደው ያደጉት በአዲስ አበባ በልደታ ክፍለ ከተማ ሲሆን በልጅነታቸው ኳስ ሲጫወ...
23/08/2025

የአካል ጉዳት ሳይበግራቸው ኑሮን ለማሸነፍ የሚተጉት ብርቱ አባት
****************

ኩሻ ጉርሙ ይባላሉ፤ ተወልደው ያደጉት በአዲስ አበባ በልደታ ክፍለ ከተማ ሲሆን በልጅነታቸው ኳስ ሲጫወቱ ባጋጠማቸው አደጋ ለአካል ጉዳት እንደተዳረጉ ያስታውሳሉ።

አቶ ኩሻ ጉርሙ ከዚህ በፊት በጥበቃ ስራ ላይ ተሰማርተው ይሰሩ የነበረ ቢሆንም አሁን ግን የመንገድ ፅዳት ስራ ላይ ተሰማርተው ይገኛሉ።

የአካል ጉዳተኛ የሆኑት አቶ ኩሻ ጉርሙ ኦቲዝም ታማሚ የሆነው ልጃቸውን እና ቤተሰባቸውን ለማስተዳደር የአካል ጉዳታቸው ሳይበግራቸው በመንገድ ፅዳት ስራ ላይ ተሰማርተው እየሰሩ ነው።

ከለሊቱ 10 ሰዓት ጀምሮ የመንገድ ፅዳት ስራቸውን የሚያከናውኑ ሲሆን በቀን 3 ኪሎ ሜትር መንገድ ያፀዳሉ።

ስራው በጣም ከባድ ቢሆንም ፈተናዎችን ተቋቁሜ እየሰራሁ፤ ፅዱ ሆኖ ሳየው በጣም ደስተኛ እሆናለሁ ይላሉ።

አቶ ኩሻ ጉርሙ የኦቲዝም ታማሚ ልጅ ያላቸው ሲሆን ከስራ መልስ ልጃቸውን ወደ ት/ቤት ያደርሳሉ ከሰዓት ደግሞ ባለቤታቸው ወደ ቤት ታመጣዋለች።

ታድያ ልጃቸውን ለማድረስ ትራንስፖርት ስለማይገኝ ከመንገድ ፅዳት መልስ ልጃቸውን ወደ ት/ቤት ማድረስ ፈተና እንደሆነባቸው ይናገራሉ።

እኚህ ብርቱ አባት የኦቲዝም ታማሚ የሆነው ልጃቸውን ፍላጎት ባለቤታቸው ጋር በመሆን የሚያሟሉ ቢሆንም፤ አሁንም የልጃቸው ጤና ፈተና እንደሆነባቸው ይገልፃሉ።

አቶ ኩሻ ጉርሙ የህይወትን ፈተና ተቋቁመው በፅናት ቤተሰባቸውን የዕለት ጉርሻ ላለማሳጣት የሚታትሩ ትጉ አባት ናቸው።

የኝህን ባለታሪክ ሙሉ ቪዲዮ ለማግኘት በኮሜንት ሴክሽን ላይ ያለውን ሊንክ ይጫኑ

በሔለን ተስፋዬ

በሐዋሳ ዩኒቨርስቲ የተሰሩት የላብራቶሪ ማስተማሪያ መሳሪያዎች*********************የሀዋሳ ዩኒቨርስቲ መምህራን ችግር ፈቺ ቴክኖሎጂዎችን እየሰሩ መሆናቸውን ይገልጻሉ።በሀዋሳ ዩኒቨር...
23/08/2025

በሐዋሳ ዩኒቨርስቲ የተሰሩት የላብራቶሪ ማስተማሪያ መሳሪያዎች
*********************

የሀዋሳ ዩኒቨርስቲ መምህራን ችግር ፈቺ ቴክኖሎጂዎችን እየሰሩ መሆናቸውን ይገልጻሉ።

በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂ እንስቲትዩት መምህርና ተመራማሪ ፍሬው ስለሺ፤ የዉሃ ፍሰትን በተመለከተ የሚቀርቡ የንድፈ ሀሳብ ትምህርቶች በተግባር ሳይታዩ መሉ ግንዛቤ ማግኘት አስቸጋሪ እንደሚሆን ይናገራሉ።

ይህን ችግር በማየት በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት መምህራን የላብራቶሪ መሳሪያ መስራታቸዉን ጠቅሰዋል።

እነዚህ የላብራቶሪ ማስተማሪያ መሳሪያዎች ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ሲሆን፤ በዋናነት የስነ ዉሃ ባህሪያትን ለመመርመር እንደሚያስችሉ ገልጸዋል።

ይህ ቴክኖሎጂ በሀገር ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ ሀዋሳ ላይ እየተመረተ ሲሆን ለከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ችግር ፈቺ መሆኑንም በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት መምህርና ተመራማሪ መኮንን በቀለ አመልክተዋል።

በፊት መሳሪያዉ ከዉጭ ስለሚመጣ ከፍተኛ ወጭ ይወጣ እንደነበር ያነሱት ተመራማሪው፤ የዩንቨርሲቲው ተማሪዎችም በተግባር ለመማር መሳሪያዎቹ በሰፊዉ ስለማይገኙ ወደተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ይጓዙ እንደነበር ተናግረዋል።

ይህ ቴክኖሎጂ የዉጭ ምንዛሬ ወጭን በመቀነስ እንዲሁም ጊዜ በመቆጠብ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አንዳለዉም አንስተዋል።

ከትምህርት ባለፈም ለምርምር እንደሚያገለግሉ እና መንግስት ትኩረቱን ቴክኖሎጂ ላይ አድርጎ ፈጠራን በማበረታታቱ ውጤታማ እንዲሆኑ ማስቻሉን ገልጸዋል።

መምህራኑ በዘጠኝ አመት ውስጥ ዘጠኝ የፈጠራ ስራ መስራታቸዉን እና ያመረቱትን ምርት ለተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች እንደሚሰጡ አክለዋል።

በቢታንያ ሲሳይ

ግንባታ ላይ ያለ ሕንፃን ለአገልግሎት ማዋል ይቻላል?***********በኢትዮጵያ የተለያዩ ከተሞች ግንባታቸው እየተከናወነ የሚገኙ ሕንፃዎች ከታች ደግሞ ለግለሰቦችና ለድርጅቶች ተከራይተው አገ...
23/08/2025

ግንባታ ላይ ያለ ሕንፃን ለአገልግሎት ማዋል ይቻላል?
***********

በኢትዮጵያ የተለያዩ ከተሞች ግንባታቸው እየተከናወነ የሚገኙ ሕንፃዎች ከታች ደግሞ ለግለሰቦችና ለድርጅቶች ተከራይተው አገልግሎት ሲሰጡ ማየት የተለመድ ተግባር ሆኗል፡፡

በጉዳዩ ላይ የሕንፃ አጠቃቃም አዋጅ ቁጥር 624 እና በሚኒስትሮች ምክር ቤት የፀደቀው 243/2003 መመሪያ መኖሩን የሚናገሩት ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ አዲስ መሀመድ፤ ከሚመለከተው የመንግስት ተቋም የህንፃ ሹም ፍቃድ ማግኘት አለበት ይላሉ፡፡

በግንባታ ላይ ያለ ሕንፃ ከታች አገልግሎት እንዲሰጥ ፍቃድ መስጠት በሕንፃዎች አጠቃቀም አዋጁም ሆነ በመመሪያው አይቻልም ሲሉም የሕግ አማካሪዋ ለኢቢሲ ተናግረዋል።

ያላለቀ ሕንፃን ወደአገልግሎት ለማስገባት በቅድሚያ የሕንፃው ባለቤት መስፈርቶችን ካሟላ መሰረታዊ መረጃዎችን በመያዝ ሕንፃው ለአገልግሎት ብቁ ነው ለመጠቀም ፍቃድ ይሰጠኝ ብሎ ለሕንፃ ሹም አካል ማመልከት እንዳለበት አስረድተዋል።

የሚመለከተው የሕንፃ ሹም ደግሞ ጥያቄው በደረሰው በአስር ቀናት ውስጥ የሕንፃውን ሁኔታ በማየት ለመገልገያነት እንደሚውል ወይም ማስተካከያ እንደሚያስፈልገው መልስ መስጠት እንዳለበት ሕጉ ያስገድደዋል ይላሉ።

ሕንፃው ያላሟላቸው ቅድም ሁኔታዎች ካሉም በመግለፅ ለአገልግሎት ብቁ አለመሆኑን መልሰ መስጠት ይጠበቅታል ነው ያሉት የሕግ አማካሪዋ፡፡ የሕንፃ ባለቤቶች በዚህ መንገድ ግንባታው ያልተጠናቀቀን ሕንፃ እንደሚያከራዩም ተናግረዋል፡፡

በግንባታ ላይ ያለ ሕንፃን ግን አገልግሎት መስጠት እንዳይችል የሚያዝ አዋጅ መኖሩን አስታውቀዋል፡፡

ሕንፃዎች ግንባታቸው ሳይጠናቀቅ በልዩ ሁኔታ አገልግሎት እንዲሰጡ ከተፈለገ ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ ተገቢ ስለመሆኑም አንስተዋል፡፡

በግንባታ ላይ ያለው ሕንፃ ከታች አገልግሎት እየሰጠ ከላይ በግንባታ ላይ መሆኑ በማንኛውም ሁኔታ ጉዳት ማያደርስ መሆኑን ማረጋገጥ ይገባል ብለዋል፡፡

ተቆጣጣሪ እና ፍቃድ ሰጪ አካላትም ኃላፊነታቸውን ካልተወጡ በወንጀልም በፍትሐብሄርም ተጠያቂ እንደሚሆኑ በሕግ መቀመጡን ጠበቃና የህግ አማካሪዋ ተናግረዋል፡፡

በላሉ ኢታላ

አርሰናል ሊድስ ዩናይትድን 5 ለ 0 አሸነፈ***************በ2ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ በሜዳው ከሊድስ ዩናይትድ የተጫወተው አርሰናል 5 ለ 0 አሸንፏል፡፡በኢምሬትስ በተደረ...
23/08/2025

አርሰናል ሊድስ ዩናይትድን 5 ለ 0 አሸነፈ
***************

በ2ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ በሜዳው ከሊድስ ዩናይትድ የተጫወተው አርሰናል 5 ለ 0 አሸንፏል፡፡

በኢምሬትስ በተደረገው ጨዋታ ዩሪያን ቲምበር ሁለት ግቦችን ሲያስቆጥር ቪክቶር ጊዮኬሬሽም በጨዋታ እና በፍጹም ቅጣት ምት ሁለት ግቦችን አስቆጥሯል፡፡ ቡካዮ ሳካ ቀሪዋን ግብ ያስቆጠረ ተጫዋች ነው፡፡

ሁለት ግብ አስቆጥሮ አንድ ለግብ የሚሆን ኳስ ያመቻቸው ቲምበር ከናቾ ሞንሪያል በኋላ ለሦስት ግቦች መገኝት ምክንያት የሆነ ተከላካይ ሆኗል፡፡

60 ሺ ተመልካቾች በታደሙበተ ጨዋታ አምበሉ ማርቲን ኦዴጋርድ እና ቡካዮ ሳካ ጉዳት አጋጥሟቸው ከሜዳ ለመውጣት ተገደዋል፡፡

እንግሊዛዊው አማካይ ማክስ ዶውማን ተቀይሮ በመግባት የመጀመርያ የፕሪሚየር ሊግ ጨዋታውን ያደረገ ሲሆን ከኢታን ንዋኔሪ እና ጀርሚ ሞንጋ በመቀጠል 16 አመት ሳይሞላው በሊጉ የመሰለፍ እድል ያገኝ በእድሜ ትንሹ 3ኛው ተጫዋች ሆኗል፡፡

በአንተነህ ሲሳይ

የኩርሙክ ወርቅ ፋብሪካ አስደናቂ የሥራ ውጤት ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)*********************ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክል...
23/08/2025

የኩርሙክ ወርቅ ፋብሪካ አስደናቂ የሥራ ውጤት ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
*********************

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኘውን የኩርሙክ ዘመናዊ የወርቅ ፋብሪካ የግንባታ ሂደት ተመልክተዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚሁ ወቅትም፤ የኩርሙክ ወርቅ ፋብሪካ አስደናቂ የሥራ ውጤት ነው ብለዋል፡፡

መጀመር በቂ አይደለም ክትትል እና ድጋፍ ያስፈልጋል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልልም ሆነ የአሶሳ ከተማ እየተለወጡ ያለበት መንገድ የሚታይ መሆኑን ገልፀዋል።

ባለፈዉ ዓመት ክልሉን ለመጎብኘት ሲመጡ የነበረዉ የከተማው ገፅታ በእጅጉ መቀየሩንና የኮሪደር ልማት ከከተማ ወጥቶ በክልል መታየቱ አስደሳች መሆኑን ተናግረዋል።

ከአሶሳ የተወሰኑ መቶ ኪሎሜትሮች ርቀት የሚገኘውና በማሽን የታገዘው ዘመናዊ የኩርሙክ ወርቅ ፋብሪካ አስደናቂ የሥራ ውጤት መሆኑንም ገልጸዋል።

ፋብሪካው የክልሉን ሰፊ የወርቅ አቅም ያሳያል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በምስራቅ አፍሪካ ትልቁ ፋብሪካ እንደሚሆንም ጠቅሰዋል፡፡

ፋብሪካው በሚቀጥለው አመት በግማሽ አቅሙ ማምረት እንደሚጀምር ገልጸዋል።

መሰል ፕሮጀክቶች የኢትዮጵያን ብልጽግና ለማረጋገጥ ወሳኝ መሆናቸዉን ያነሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ይህም ከሌሎች ፕሮጀክቶች ጋር ተደምሮ የኢትዮጵያን ብልጽግና አዉን እንደሚያደረግ ተናግረዋል።

ኢትዮጵያ የብዝሀ ዘርፍ ኢኮኖሚ በመከተሏ በተለያዩ ዘርፎች ወጤት መታየቱንም አንስተዋል።

በቢታንያ ሲሳይ

ጊዮኬሬሽ በሊጉ የመጀመርያ ግቡን አስቆጠረ***************አርሰናል ሊድስ ዩናይትድን 4 ለ 0 እየመራ ሲሆን ቪክቶር ጊዮኬሬሽ በሊጉ ኢምሬትስ ላይ የመጀመርያ ግቡን አስቆጥሯል፡፡በጨዋታ...
23/08/2025

ጊዮኬሬሽ በሊጉ የመጀመርያ ግቡን አስቆጠረ
***************

አርሰናል ሊድስ ዩናይትድን 4 ለ 0 እየመራ ሲሆን ቪክቶር ጊዮኬሬሽ በሊጉ ኢምሬትስ ላይ የመጀመርያ ግቡን አስቆጥሯል፡፡

በጨዋታው ሌላኛው ግብ አስቆጣሪ ቡካዩ ሳካ በጉዳት ከሜዳ ወጥቷል፡፡

በመጀመርያው ግማሽ አምበሉ ማርቲን ኦዴጋርድ በተመሳሳይ ተጎድቶ ለመውጣት ተገዷል፡፡

ዩሪያን ቲምበር ሁለት ግቦችን ያስቆጠረ ተጫዋች ሆኗል፡፡

በአንተነህ ሲሳይ

በኢሉአባቦር ዞን ከ 500 ሺህ ኪሎግራም በላይ የአቮካዶ ምርት ለገበያ ለማቅረብ እየተሰራ ነው ****************በኢሉአባቦር ዞን በተያዘው የምርት ዘመን ከ500 ሺህ ኪሎግራም በላይ ...
23/08/2025

በኢሉአባቦር ዞን ከ 500 ሺህ ኪሎግራም በላይ የአቮካዶ ምርት ለገበያ ለማቅረብ እየተሰራ ነው
****************

በኢሉአባቦር ዞን በተያዘው የምርት ዘመን ከ500 ሺህ ኪሎግራም በላይ የአቮካዶ ምርት ለአለም ገበያ ለማቅረብ መታቀዱን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ፡፡

የኤክስፖርት ምርቶችን በስፋት በማምረት የውጭ ምንዛሪን ለማሳደግ የተያዘውን አገራዊ ግብ ለማሳካት በዞኑ ለመጀመርያ ጊዜ 500 ሺህ ኪሎግራም የአቮካዶ ምርት ለአለም ገበያ ለማቅረብ እየተሰራ መሆኑም ተገልጿል፡፡

የኢሉአባቦር ዞን ምክትል አስተዳዳሪ አቶ መሀመድጠሀ አባፊጣ፤ በዞኑ ከቡና እና ማር ቀጥሎ ለመጀመርያ ጊዜ አቮካዶን ለአለም ገበያ ለማቅረብ የሚያስችል ቅድመ ዝግጅት ተደርጎ አሁን ላይ በይፋ መጀመሩን ገልፀዋል፡፡

በዞኑ የምግብ ሉአላዊነትን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን የኤክስፖርት ምርቶችን በማስፋት የውጭ ምንዛሪን ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑንም የዞኑ ምክትል አስተዳዳሪ ተናግረዋል፡፡

የመርሀግብሩ አንድ አካል የሆነውና ተግባራዊ በመደረግ ላይ በሚገኘው የአቮካዶ ልማት ኢኒሼቲቭ የተያዘውን ግብ ለማሳካት አርሶአደሩ የተሻሻሉ ምርታማ ዝርያዎችን እንዲጠቀም የሚያግዝ ድጋፍና ክትትል እየተደረገ እንደሚገኝም አቶ መሀመድጠሀ ገልፀዋል፡፡

በዞኑ የበቾ ወረዳ አርሶአደሮች ከአሁን በፊት አቮካዶን በጓሮ በማልማት በአካባቢው ገበያ ተገድበው ሲያቀርቡ በመቆየታቸው በድካማቸው ልክ ተጠቃሚ እንዳልነበሩ ገልፀዋል፡፡

አሁን ላይ ግን ምርጥ የአቮካዶ ዝርያን ማልማት በመጀመራቸው ለአለም ገበያ ለማቅረብ በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር የበለጠ ተጠቃሚ መሆን መጀመራቸውን ተናግረዋል፡፡

በሚፍታህ አብዱልቃድር

ጃፓን ከአፍሪካ ሀገራት ጋር 300 የትብብር ስምምነቶችን ተፈራረመች ******* በጃፓን ዮኮሃማ 9ኛው የቶኪዮ ዓለም አቀፍ የአፍሪካ ልማት ኮንፈረንስ (ቲአይሲኤዲ) ተካሂዷል። በዚህ ጉባዔ ላ...
23/08/2025

ጃፓን ከአፍሪካ ሀገራት ጋር 300 የትብብር ስምምነቶችን ተፈራረመች
*******

በጃፓን ዮኮሃማ 9ኛው የቶኪዮ ዓለም አቀፍ የአፍሪካ ልማት ኮንፈረንስ (ቲአይሲኤዲ) ተካሂዷል።

በዚህ ጉባዔ ላይ በጃፓን እና በአፍሪካ ሀገራት መካከል 300 አዳዲስ የትብብር ስምምነቶች ተፈርመዋል።

ይህም የአፍሪካ እና ጃፓንን በተለያዩ ዘርፎች ያሉ ትብብሮች እንደሚያጠናክር አፍሪካ ኒውስ ዘግቧል።

ስምምነቶቹ ለአፍሪካ ልማት ወሳኝ የሆኑት እንደ መሠረተ ልማት፣ ጤና ፣ ቴክኖሎጂ፣ ትምህርት እና ግብርና ያሉ ዘርፎችን ያካተተ ነው።

ስምምነቶቹ ጃፓን ከአፍሪካ ሀገራት ጋር ለመስራት ያላትን ቁርጠኝነት የሚያጎላ ነው ተብሏል።

በቢታኒያ ሲሳይ

23/08/2025

"መጀመር በቂ አይደለም ክትትል እና ድጋፍ ያስፈልጋል። የቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልልም ሆነ የአሶሳ ከተማ እየተለወጡ ያለበት መንገድ የሚታይ ነው።" - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

አርሰናል ኤቤሬቺ ኤዜን አስፈረመ *******************አርሰናል ኤቤሬቺ ኤዜን ከክሪስታል ፓላስ ማስፈረሙን አስታውቋል፡፡ኤቤሪቺ ኤዜ በመድፈኞቹ ቤት 10 ቁጥር መለያ የሚለብስ ሲሆን፤...
23/08/2025

አርሰናል ኤቤሬቺ ኤዜን አስፈረመ
*******************

አርሰናል ኤቤሬቺ ኤዜን ከክሪስታል ፓላስ ማስፈረሙን አስታውቋል፡፡

ኤቤሪቺ ኤዜ በመድፈኞቹ ቤት 10 ቁጥር መለያ የሚለብስ ሲሆን፤ ከክለቡ ጋርም የአምስት ዓመት ውል ተፈራርሟል፡፡

ከካይ ሀቨርዝ ጉዳት በኋላ የኤዜን ዝውውር በፍጥነት ያከናወነው አርሰናል፤ ለእንግሊዛዊው ተጫዋች 67 ሚሊዮን ፓውንድ መክፈሉ ተነግሯል፡፡

ኤቤሬቺ ኤዜ በክረምቱ የዝውውር መስኮት የአሰልጣኝ ሚካኤል አርቴታ 7ኛው ፈራሚም ሆኗል፡፡

አርሰናል ምሽት 1:30 ላይ በኤምሬትስ ስታዲየም ከሊድስ ዩናይትድ ጋር የሚያደርግው ጨዋታ ይጠበቃል፡፡

በአንተነህ ሲሳይ

23/08/2025

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአሶሳ ከተማ ያደረጉት ጉብኝት

Address

Shegole, Addisu Gebeya
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian Broadcasting Corporation posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Ethiopian Broadcasting Corporation:

Share

Our Story

Ethiopian Broadcasting Corporation is a national media which disseminates its news and programs world wide via Television,Radio and Website.