Obright News

Obright News Obright Media is a Media Production & News Company based in Addis Ababa,Ethiopia Obright is a privately owned Media and Production Company based in Addis Ababa

Faawundeeshiniin Hacaaluu Hundeessaa Beekamtii Artistiifi Shakkamaa yakkaa Abdualam Gosaatiif kenne kaasuu ibsee akkasum...
05/07/2025

Faawundeeshiniin Hacaaluu Hundeessaa Beekamtii Artistiifi Shakkamaa yakkaa Abdualam Gosaatiif kenne kaasuu ibsee akkasumas uummat hunda dhiifama gaafatee jira

አዋጅ አዋጅ አዋጅ ! ያልሰማ ይስማ፤ የሰማ ያሰማ!በዓድዋ ድል መታሰቢያ የሚገኙት ሁለቱም ሲኒማ ቤቶችና የ3ዲ ቴክኖሎጂ የተገጠመላቸዉ ድል እና ጋሻ ሲኒማ ቤቶች  ሥራ ጀምረዋል፡፡ሁላችሁም እ...
02/07/2025

አዋጅ አዋጅ አዋጅ ! ያልሰማ ይስማ፤ የሰማ ያሰማ!
በዓድዋ ድል መታሰቢያ የሚገኙት ሁለቱም ሲኒማ ቤቶችና የ3ዲ ቴክኖሎጂ የተገጠመላቸዉ ድል እና ጋሻ ሲኒማ ቤቶች ሥራ ጀምረዋል፡፡
ሁላችሁም እየመጣችሁ ከሚትወዱዋቸዉ ጋር በመሆን እንድትዝናኑ በክብር ተጋብዛችኋል፡፡

26/06/2025
17/06/2025

ተከፈተ 😮

የብሔራዊ ቤተ-መንግስት
ሙዚየም ለሕዝብ ክፍት ሆነ::

ብሔራዊ ቤተ-መንግስት ሙዚየም
ከዛሬ ጀምሮ ለሕዝብ ክፍት ሆኗል።

የመግቢያ ዋጋዎች:

* መደበኛ ቲኬት: 300 ብር
* ልዩ ቲኬት: 1,000 ብር

የሥራ ሰዓታት: ሙዚየሙ ከማክሰኞ በስተቀር በየቀኑ ከጥዋቱ 3 ሰዓት እስከ ምሽቱ 11 ሰዓት ክፍት ይሆናል።

በሙዚየሙ ውስጥ የሚገኙት:

* የመኪና ሙዚየም፣
* እዮቤ ልዩ ቤተ-መንግስት ሙዚየም፣
* የቤተ-መንግስት ቅርሶች እና
* የተለያዩ ሀገራት ስጦታዎች ለጎብኚዎች ቀርበዋል።

መዝናኛዎችም ይገኛሉ።

Friends
17/06/2025

Friends

Ethnic Derashe people of Ethiopia dressed with beautiful culural costume visiting the Adwa Victory Memorial

12/06/2025

በብርቱዎች ትጋት ተጠናክሮ የሚቀጥል እንጅ በዋዘኞች ከንቱ ቅዠት የሚቆም ልማት የለንም !

የለውጡ መንግስት ሲከማቹ የቆዩና አዳዲስ የህዝብ የልማት ጥያቄዎችን በመመለስ ሁለንተናዊ ብልፅግናን ለማረጋገጥ የያዘው የጠራ እሳቤ እና ቁርጠኛ አቋም የሚታይና የሚጨበጥ ውጤት አስመዝግቧል።

ለህዝባችን እና ለሀገራችን የሚበጅ ዘመኑን የሚመጥን አዲስ የፖለቲካ ባህል ለመገንባት የሚደረገው ርብርብ አሁንም ይበልጥ ተጠናክሮ ቀጥሏል።

የህዝብን ችግር የሚያቃልሉ አዳዲስ ሀሳቦችን የማፍለቅ ብቻም ሳይሆን የመተግበር ችግርም ከለውጡ በኋላ ብዙም የለም።

የአሻጋሪ እሳቤዎች ውጤት የሆኑት አስደማሚ ፕሮጀክቶች ተጠናቅቀው ለመመልከት ዓመታትን መጠበቅ በከተማችንም በሀገራችንም ታሪክ እየሆነ መጥቷል ፤ ከለውጡ በፊት በነበረው የስራ ባህል በዓመታት ውስጥ እውን ይሆናሉ ተብለው የማይታሰቡ የነበሩ ግዙፍ ፕሮጀክቶች አሁን ላይ በጥቂት ወራት አንዳንዴም በሳምንታት ውስጥ ተጠናቀው ለህዝብ አገልግሎት መስጠት የሚጀምሩበት አዲስ ታሪክ መመዝገብ መጀመሩ የማይታበል ሀቅ ነው።

ለረጅም ዘመናት ዳብሮ ከቆየው ኋላቀር የፖለቲካ ባህል አስተሳሰብ መውጣት ያልቻሉ ተቸካይ ግለሰቦች ደግሞ የሚቃወሙትን እና የሚደግፉትን በቅጡ መለየት ተስኗቸው ተደናግረው ሲያደናግሩ ፣ ተሳስተው ለማሳሳት ሲሞክሩ ይስተዋላሉ።

ምን ተሰራ ብሎ የተሰራውን ልማት ከመጠየቅ ፣ ያልተሰራውንም እንዲሰራ ከመጠየቅና የራስን አሻራ ከማሳረፍ ይልቅ ማን ሰራው እያሉ ልማትን ለማጥላላት
የሚሞክሩ ሀይሎች በሀገራችን ለረጅም ዘመን የቆየው የፖለቲካ ስብራት ነፀብራቅ ናቸው።

የሀሳብ ድርቀት ያለባቸው ግለሰቦችና ቡድኖች የህዝብን ህይወት የሚያሻሽሉ፣ ሀገርን ወደ ፊት የሚያሻግሩ አዳዲስ እሳቤዎችን ማፍለቅ አይችሉም። በትጉህ እጆች የተሰሩ ልማቶችን ማሽሟጠጥ ፣ ማጥላላት ፣ ከቻሉም ልማትን ማደናቀፍ ግን የሀሳብ አልባዎች መለያ ነው።

የሚቃወሙት ሲጠፋ የህዝብን ልማት ህዝብ እንዲጠላውና እንዲቃወመው የሚደረግ ከንቱ ቅዥት የዘመናችን ትልቁ ድንቁርና ነው ቢባል ማጋነን አይሆንም።

የከተማችንን ንፅህና ፣ የከተማችንን ውበት ፣ የከተማችንን ተወዳዳሪነት በማሳደግ ለነዋሪዎቿም ለጎብኝዎቿም ምቹ ለማድረግ የሚደረግን ርብርብ ማጥላላትን የትግል ስልቱ የሚያደርግ አካሄድ የፖለቲካ ንቅዘት መገለጫ እንጅ ሌላ ምንም ሊሆን አይችልም።

ከአዲስ አበባ በብዙ መመዘኛዎች የተሻሉ ከተሞች ያሏቸው ሀገራት መሪዎች ጭምር ተሞክሮውን ለመውሰድ በአደባባይ የመሰከሩለትን የኮሪደር ልማት " ብልጭልጭ " በሚል ቃል ለማንኳሰስ መሞከር የአስተሳሰብ መቀንጨርን ያሳያል እንጅ የሰው ተኮር ልማታችንን ግዝፈት ሊያሳንስ አይችልም።

ለመጪው ትውልድ ጭምር የሚሻገር ጥቅም እንዳለው በመረዳት ተደራሽ ባልሆነባቸው አካባቢዎች የሚኖሩ የከተማችን ነዋሪዎች "ከእኛ ጋ መቼ ይደርሳል ? " እያሉ በጉጉት የሚጠባበቁትን የኮሪደር ልማት በህዝባችን ዘንድ እንዲጠላ ማሰብ በራሱ የጤነኛ አስተሳሰብ ማሳያ አይደለም።

ተሞክሯቸው እንደ ሀገር እየሰፋ የሚገኘውን አንፀባራዊ ፕሮጀክቶች መገንባት እንጅ ማጥላላት እውቀትም ጉልበትም ስለማይጠይቅ አንዳንዶች የዘወትር ስራቸው አድርገውታል።

በጥላቻ የተሞሉ ግለሰቦችና ቡድኖች ፍቅርን ሊሰብኩ ፣ ልማትን ሊያሳኩ አይችሉም ፤ በኋላቀር አመለካከቶች ምክንያት ወደ ኋላ የሚመለስ ወይም ባለበት የሚቆም ልማት አለመኖሩን ግን የተግባር ምላሽ ያገኛሉ።

በተንሸዋረረ እይታ ፣ በጭፍን አመለካከት ልማትን በማጥላላት ፖለቲካዊ ትርፍ ለማግኘት መሞከር ፖለቲካዊ ዝቅተት ሲሆን ወደ ሌሎችም ለማስተጋባት የሚደረግ መፍጨርጨር ደግሞ የአዋቂነን ባዮች ድንቁርና ነው።

ከሀገራዊ ለውጡ በኋላ ኢትዮጵያ ላይ አዲስ እና አሻጋሪ እሳቤዎች እንደማያቋርጥ ጅረት እየመነጩ የህዝባችንን የኑሮ ደረጃ በሚያሻሽሉ መልኩ ተግባራዊ እየተደረጉ ይገኛሉ።

በትናንት የመቆዘም፣ በትናንት ብቻ የመኩራራት እሳቤ የትም እንደማያደርስ ስለታመነበት በላብ መስዋዕትነት ነገን ዛሬ የመገንባት የተለወጠ የስራ ባህል እየተገነባ ነው።

በመጠላለፍ ፖለቲካ ሀገርን እንደ ሀገር ለማስቀጠል ጭምር ከባድ በሚሆንበት በምንገኝበት ዓለም አቀፍ ፖለቲካዊ አውድ ከትብብርና ፉክክር ውጪ ያሉ የሴራ እንቅስቃሴዎች ዘመኑን ያልዋጁ ናቸው።

በሀገራችን ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ በተካሄደው ፍትሀዊና ዴሞክራሲያዊ የህዝብ ምርጫ የህዝብን ይሁንታ ማግኘት ያልቻሉ ተፎካካሪ የፖለቲካ ሀይሎች በየደረጃው በሚገኙ የኃላፊነት እርከኖች አሻራቸውን ማሳረፍ የሚችሉበት ዕድል የተፈጠረውም መጠላለፍን በማስወገድ ትብብርን ለማጠናከር ነው።

ሁለንተናዊ ብልፅግናን ዕውን ለማድረግ እየተደረ የሚገኘው ብርቱ ጥረት ሂደቱም ጭምር ፍትሀዊ አሳታፊ እንዲሆን የተሰጠው ልዩ ትኩረትም ሰው ተኮር እሳቤዎች በስፋት ተግባራዊ የሚደረጉበትን ሁኔታ አሳድጓል።

በለውጡ መንግስት መተግበር የጀመረው ልማት የማይቆም ፣ ወደ ኋላም ሊመለስ የማይችል ፣ የዛሬውን እና የነገውን ትውልድ ዘላቂ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ መሆኑን ከታለፉ ውስብስብ ፈተናዎች ፣ ከተመዘገቡ ተጨባጭ ውጤቶች ማረጋገጥ ተችሏል::

ሁለንተናዊ ብልፅግናን ዕውን ማድረግ በሀገራችን የነበሩና አሁንም ያልተቀረፉ ውስብስብ ችግሮች መፍትሄ መስጠት እንደሚያስችል ጠንቅቀው የሚረዱት የሀገራችን ታሪካዊ ጠላቶች እና በህዝብ ስም የሚነግዱ ቁማርተኞች ዋነኛ የጥፋት ዒላማቸውን በሀገራችን ፈጣን ዕድገትን እያስመዘገቡ የህዝባችንን የኑሮ ደረጃ እያሻሻሉ በሚገኙ ሰው ተኮር ልማቶች ላይ ማድረግ ከጀመሩ ሰነባብተዋል።

ፈጣን ዕድገት ማስመዝገብ ወንጀል እንደሆነ አድርገው ሌት እና ቀን የሚያወሩ ግለሰቦች በልማቱ ስም የህዝብ ሀብት ተበላ የሚል ጥያቄ የላቸውም ፤ የህዝብ ሀብት ለህዝብ ልማት የሚውልበት ግልፅ አሰራር ስለተዘረጋ።

ፕሮጀክቶች እየተጓተቱ ነው እንዳይሉም ፕሮጀክቶችን በጥራትና በፍጥነት ጀምሮ በመጨረስ በኩል የለውጡ መንግስት የሚታማ አልሆነላቸውም።

ልማቱ የጥቂቶችን ህይወት ብቻ የሚያሻሽል ነው ብለው እንዳያወሩም የልማት ተነሽዎችንም ሆነ አጠቃላይ የከተማችንን ነዋሪዎች ህይወት በተጨባጭ እያሻሻለ መሆኑ ከማንም የተሰወረ አልሆነላቸውም።

የከተማችንን ፈጣን ዕድገት የሚያጥላሉበት ምክንያት ፈልገው ሲያጡ ህዝባችንን እና ከተማችንን ከጥልቅ ጉስቁልና እያወጣ የድህነት አቧራን እያራገፈ የሚገኘውን ልማት " አብለጭላጭ ልማት " ብለው የሚጠሩ ግለሰቦች መንግስትንም ሆነ ህዝባችንን ከልማት የመነጠል ዓላማቸው አልተሳካም ፤ ወደፊትም አይሳካም።
የመንግስት አቋምም ሆነ የህዝባችን ፍላጎት ልማትና ብልፅግና በመሆኑ የኮሪደር ልማቱን ጨምሮ ሌሎችም ሰው ተኮር ፕሮጀክቶች ልቀውና ሰፍተው እየተተገበሩ ይገኛል።

የተቀናጁ መሰረተ ልማቶች እየተገነቡ ፣ እንኳንስ ለመኖር አልፎ ለመሄድ ጭምር የጤና ጠንቅ ሆነው የቆዩ አካባቢዎች አምረውና ተውበው ለህዝባችን የጋራ መገልገያ መዋላቸው የሚያስመሰግን እንጅ በምንም መመዘኛ የሚያስወቅስ አይደለም።

የህዝባችንን ፍትሀዊ ተሳታፊነት እና ተጠቃሚነት እያረጋገጠ የሚገኘው ሰው ተኮር ልማታችን በእኛ ትውልድ ብቻም ሳይሆን በመጪው ትውልድ ጭምር ምስጋና የሚቸረው የመደመር ትውልድ አሻራ መሆኑን ጠንቅቆ በመረዳት ርብርብን ማጠናከር ከሁላችንም ይጠበቃል።

በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅ/ጽ/ቤት

Fake News Alert                    እንግዲህ የፓለቲካው ሊቅ የሚባለው 2.9 ሚሊየን ተከታይ ያለው ጃዋር መሀመድእንዲህ ሳያጣራና የሀላፊነት ስሜት ሳይሰማው ከ2ተኛ ክፍል ...
09/06/2025

Fake News Alert

እንግዲህ የፓለቲካው ሊቅ የሚባለው 2.9 ሚሊየን ተከታይ ያለው ጃዋር መሀመድ

እንዲህ ሳያጣራና የሀላፊነት ስሜት ሳይሰማው ከ2ተኛ ክፍል ተማሪ በማይተናነስ መልኩ ለሚከተሉት 2.9 ተከታዮች ያገኜውን የሀሰት ዜና እየለጠፈ ህዝብ የሚያባላው !

መንግሥትን መገልበጥ በፌስቡክ ሼርና ላይክ የሚመስለው ኬንያ ሆኖ ኢትዮጵያ ትግል ለመምራት የሚያስብ የዋህ ነው

ሊቅ ያለው መሪጌታ ጋ ነው ! ጃዋር የገነነው ባለው ፓለቲካ እውቀትና ብስለት ሳይሆን ሳያቁ በሚከተሉት 2.9 ተከታዮቹ የገነነ ሰው ነው !!

ጃዋር ትግል ሊጠልፍ ነው የመጣው የምንለው በምክንያት ነው
HagereTube Oromia ProspHagereTubey@followersOromia Prosperity Party / OPP /

ዛሬ በ Fb popular የሆነው ጉዳይ  "አፈትልኮ የወጣው የአሥመራው መፈንቅለ- መንግሥት" የሚለው ቀደዳ ሲሆን በጣም ብዙዎች ተቀባብለውታል ።"መረጃውን ከየት አገኛችሁት" ለሚለው ምላሹ "...
02/06/2025

ዛሬ በ Fb popular የሆነው ጉዳይ "አፈትልኮ የወጣው የአሥመራው መፈንቅለ- መንግሥት" የሚለው ቀደዳ ሲሆን በጣም ብዙዎች ተቀባብለውታል ።"መረጃውን ከየት አገኛችሁት" ለሚለው ምላሹ " ከ ሚስጥር አፈንፋኙ "Francis Global Voice" ማሕበራዊ ድሕረ-ገፅ " የሚል ነው።

ወገኖቼ ያልተረጋገጠ ወሬ ከማሯሯጥ ራሱ "አፈንፋኙ" የተባለለት "Francis Global Voice" የሚባል ድረገጽ አለ ወይ?" በማለት ገጹን ፈልጎ መፈተሽ ይቀላል።
ለማንኛውም የተባለው ድረገጽ ጭምር የለም🤔‼️
Gumaa Saqqataa Gem

Address

Addis Ababa

Telephone

+251944550155

Website

https://obright.net/

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Obright News posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Obright News:

Share