Addis Gize - አዲስ ጊዜ

Addis Gize - አዲስ ጊዜ Providing latest News. Providing latest News and Information.

ታግተናል በማለት ወላጆቻቸውን 500ሺህ ብር የጠየቁ ታዳጊዎቸ በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተጣራባቸው መሆኑን የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ ገለፀ፡፡***የወንጀል ድርጊቱ የተፈፀመው...
01/08/2025

ታግተናል በማለት ወላጆቻቸውን 500ሺህ ብር የጠየቁ ታዳጊዎቸ በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተጣራባቸው መሆኑን የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ ገለፀ፡፡
***
የወንጀል ድርጊቱ የተፈፀመው በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ወረዳ 9 ልዩ ቦታው ኳስ ሜዳ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ ነው።

አጋችና ታጋች በመምሰል የማታለል ወንጀሉን የፈፀሙት አራቱ ተጠርጣሪዎች ዕድሜያቸው ከ18 ዓመት በታች የሆኑ ሁለት ወንዶችና ሁለት ሴቶች ሲሆኑ ለሁለት ቀናት ከቤተሰቦቻቸው ወጥተው ሲዝናኑ ቆይተው ገንዘብ ሲያጥራቸው በመመካከር ለቤተሰብ ስልክ ደውለዋል፡፡

ወንዶቹ አጋች ሴቶቹ ደግሞ ታጋቾች በመሆን ለሴቶቹ ቤተሰቦች በደወሉት ስልክ 5 መቶ ሺ ብር የጠየቁ ሲሆን የሴት ወላጆች አቅራቢያቸው ወደሚገኝ ፖሊስ ጣቢያ ቀርበው ጥቆማ ሠጥተዋል።

ፖሊስም ለቀረበው ጥቆማ ተገቢውን ትኩረት በመስጠት መረጃዎችን በማሰባሰብ አራቱንም ተጠርጣሪዎች ካሉበት ቦታ በቁጥጥር ስር ሊያውላቸው ችሏል፡፡

የታዳጊዎቹ ቤተሰቦች በወቅቱ ሴት ልጆቻቸው መታገታቸውን ሲሰሙ ከፍተኛ ድንጋጤ ውስጥ ገብተው እንደነበር ተናግረው ፖሊስ ላከናወነው ተግባርም ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡

በልጆች አስተዳደግ ዙርያ የቤተሰብ ኃላፊነት ከፍተኛ ሲሆን በአንዳንድ ታዳጊ ወጣቶች ላይ የሚስተዋለው ባህሪ የነገ ተስፋቸውን ሊያጨልም የሚችል በመሆኑ ሊታረምና በወላጆች ዘንድም ከፍተኛ ጥንቃቄና ትኩረት ሊደረግበት እንደሚገባም የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ጥሪውን ያቀርባል።

ሚሊኒየም አዳራሽ ሊፈርስ ነው!***በሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ስር የሚገኘው ሚሊኒየም አዳራሽ በመባል የሚታወቀው አዲስ ፓርክ እና ማኔጅመንት ከታህሳስ 2018 ጀምሮ ሙሉ በሙሉ ፈርሶ በአዲ...
23/07/2025

ሚሊኒየም አዳራሽ ሊፈርስ ነው!
***
በሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ስር የሚገኘው ሚሊኒየም አዳራሽ በመባል የሚታወቀው አዲስ ፓርክ እና ማኔጅመንት ከታህሳስ 2018 ጀምሮ ሙሉ በሙሉ ፈርሶ በአዲስ መልኩ እንደሚገነባ መገለጹን ካፒታል ጋዜጣ ዘግቧል።

በ2000 ዓ.ም. አገልግሎት መስጠት የጀመረው ይህ ግዙፍ አዳራሽ በኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገኙ ታላላቅ አዳራሾች ግንባር ቀደሙ ነው።

አዲሱ ግንባታ የአዳራሹን አቅም እና ዘመናዊነት ይበልጥ ያሳድጋል የተባለ ሲሆን ለግንባታው የሚወጣው ኢንቨስትመንት መጠን እና የስራ ተቋራጩ ማንነት በቀጣይ ይፋ ይደረጋል ተብሏል።

ሚሊኒየም አዳራሽ በ20 ሺህ ስኩዌር ሜትር ስፋት ላይ ያረፈ ሲሆን በአንድ ጊዜ እስከ 25,000 ሰዎችን የማስተናገድ አቅም አለው።

ይህ አዳራሽ ከትልልቅ ብሔራዊ ፕሮግራሞች፣ ዓለም አቀፍ ስብሰባዎች፣ ኤግዚቢሽኖች፣ ኃይማኖታዊ ፕሮግራሞች፣ የምርቃት ስነስርዓቶች በተጨማሪ፣ ታላላቅ ሰዎች ህይወታቸው ሲያልፍ ለሽኝት ስነስርዓቶች ጭምር ሚናውን ሲጫወት ቆይቷል።

በሰኔ ወር 2017 ምሽት ላይ ሚሊኒየም አዳራሽ የተለመደውን አገልግሎት እየሰጠ በነበረበት ወቅት ድንገተኛ የእሳት አደጋ እንደገጠመው ታውቋል። የዚህ ችግር ምንጭ ለጊዜው በሚመለከተው አካል እየተጣራ በመሆኑ ጊዜው ሲደርስ ይፋ እንደሚደረግ ተገልጿል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ ከ17 ዓመታት በኃላ አዳራሹ ሙሉ በሙሉ ፈርሶ በአዲስ መልኩ መገንባት ለወደፊቱ ለተለያዩ ዝግጅቶች የተሻለ እና ዘመናዊ የመስተንግዶ አማራጭ እንደሚሰጥ ይጠበቃል ተብሏል።

"ክለቡ ጥያቄዬን ከመለሰ በኢትዮጵያ መድን መቀጠል እፈልጋለሁ"     ገብረመድህን ሃይሌ ከኢትዮጵያ መድን ጋር ታሪካዊ ድል ያስመዘገበው አሰልጣኝ ገብረመድህን ሃይሌ በክለቡ የመቆየት ፍላጎት ...
27/06/2025

"ክለቡ ጥያቄዬን ከመለሰ በኢትዮጵያ መድን መቀጠል እፈልጋለሁ"
ገብረመድህን ሃይሌ

ከኢትዮጵያ መድን ጋር ታሪካዊ ድል ያስመዘገበው አሰልጣኝ ገብረመድህን ሃይሌ በክለቡ የመቆየት ፍላጎት እንዳለው ገልጿል፡፡ ጅማ አባጅፋር እና መቐለ 70 እንደርታ በታሪካቸው ለመጀመሪያ ጊዜ የፕሪምየር ሊጉን ዋንጫ እንዲያነሱ የረዳው አሰልጣኙ ድሎቹን ማበላለጥ እንደሚከብደው ተናግሯል፡፡

‹‹ሁሉም የዋንጫ ድሎች የራሳቸው መልክ አላቸው፡፡ አንዱን መምረጥ ይከብደኛል ፤ ዋንጫ ያነሳሁባቸው ሦስቱም ክለቦች አዲስ ታሪክ በማስመዝገባቸው ኩራት ይሰማኛል፡፡›› ብሏል።

ከአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ ( AMN) ጋር ቆይታ ያደረገው ገብረመድህን ሃይሌ ኢትዮጵያ መድንን በማሰልጠን ቢቀጥል ደስተኛ እንደሆነ ገልጿል።

በክለቡ ለመቀጠል ግን እንዲሟሉ የሚፈልጋቸው ነገሮች እንደሉ ጠቁሟል፡፡ ‹‹በቀጣይ ኢንተርናሽናል ውድድር ላይ እንሳተፋለን፡፡ ክለቡ ይህን ታሳቢ ያደረገ አደረጃጀት ሊከተል ይገባል፡፡›› ብሏል፡፡

‹‹ለክለቡ ሃላፊዎች ምን እንደምፈልግ ነግሬያቸዋለሁ፡፡ እስካሁን ምላሽ አልሰጡኝም፡፡ በዚሁ የሚቀጥሉ ከሆነ ምንም ማድረግ አልችልም፡፡ ነገሮች ከተስተካከሉ እና ቡድኑ ከተደራጀ በመድን እስከመጨረሻ ብቆይ ደስ ይለኛል፡፡›› በማለት ፍላጎቱን አብራርቷል፡፡

በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ የኢዮጵያ ፕሪምየር ሊግን ያሸነፈው ኢትዮጵያ መድን በቀጣይ ዓመት ኢትዮጵያን ወክሎ የአፍሪካ ቻምፒየንስ ሊግ ላይ ይሳተፋል፡፡

"ታገቢኛለሽ?"  በምርቃቷ ቀን የጋብቻ ጥያቄ የቀረበላት ተመራቂ!*******ከወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ በእንስሳት ሕክምና ዶክትሬትዋን የያዘችው ሀና አለማየሁ ከዩኒቨርሲቲው እና ከእጮኛዋ 2 ወ...
24/06/2025

"ታገቢኛለሽ?" በምርቃቷ ቀን የጋብቻ ጥያቄ የቀረበላት ተመራቂ!
*******
ከወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ በእንስሳት ሕክምና ዶክትሬትዋን የያዘችው ሀና አለማየሁ ከዩኒቨርሲቲው እና ከእጮኛዋ 2 ወርቅ በአንድ ጊዜ አግኝታለች።

በትምህርት ክፍሏ የላቀ ውጤት በማምጣት የወርቅ ሜዳልያ የተሸለመችው ዶ/ር ሀና፣ በምረቃዋ ላይ የተገኘው እጮኛዋ በድንገት የወርቅ ቀለበት እና የታገቢኛለሽ ጥያቄ አቅርቦላታል።

ለጥያቄው እሺታዋን የገለጸችው ተመራቂዋ "በትምህርት ቆይታዬ ወቅት እጮኛዬ ሲያበረታታኝ ነበር" ስትል ለኢቢሲ ተናግራለች።

"ይሁንና በእንዲህ አይነት አጋጣሚ በድንገት የታገቢኛለሽ ጥያቄ አቅርቦ ያስደንቀኛል ብዬ አላሰብኩም" ነበር ብላለች።

"ከእግዚአብሔር ጋር በመሆኔ ሁሌም አሸንፋለሁ! እንጦጦ ኪዳነ ምህረት በየወሩ አልቀርም! "             ኃይሌ ገ/ሥላሴበማኅበረ ቅዱሳን የሕዝብ ግንኙነትና ትብብር አገልግሎት ማስተባበሪ...
23/06/2025

"ከእግዚአብሔር ጋር በመሆኔ ሁሌም አሸንፋለሁ! እንጦጦ ኪዳነ ምህረት በየወሩ አልቀርም! "
ኃይሌ ገ/ሥላሴ

በማኅበረ ቅዱሳን የሕዝብ ግንኙነትና ትብብር አገልግሎት ማስተባበሪያ ትናንት ሰኔ 15 2017 ዓ.ም በተዘጋጀው የድህረ ግቢ ጉባኤ ምሩቃን መርሐ ግብር ላይ አትሌት ኃይሌ ገብረ ሥላሴ ተገኝተው ያላቸውን ልምድ እና ተሞክሯቸውን ለወጣቶች አጋርተዋል።

“ከልጅነቴ ጀምሮ በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ በፈሪሐ እግዚአብሔር ያደግሁ መሆኔ ለስኬቴ መሰረት ነው" ብለዋል።

"የሁለት ኦሎምፒክ የድል ወርቆቼን የሰጠሁት ለእንጦጦ ኪዳነ ምህረት ነው። በየወሩም አልቀርም። እሷ ለእኔ ብዙ ነገሬ ናት፤ ከእግዚአብሔር ጋር ያለ ሰው ሁሌም አሸናፊ እና ጠንካራ ነው" ያሉት አትሌት ኃይሌ "በተለይም ዛሬ ለደረስኩበት ደረጃ ያገዘኝ በእግዚአብሔር ላይ ባለኝ ከፍተኛ እምነት እንዲሁም ጠንክሬ በመሥራቴ ነው" ሲሉ ተናግረዋል፡፡

"እኔ በሰከንድ ሚሊዮኖችን እንዳገኘሁ ሁሉ በሰከንድም ብዙ ሚሊዮን የሚያወጣ ሀብት አጥቻለሁ! ነገር ግን ከእግዚአብሔር ጋር በመሆኔ ሁሌም አሸንፋለሁ!" ሲሉም አክለዋል።

አክለውም “እናንተ ወጣቶች በውስጣችሁ ባለው አቅም እና ኃይል ልተሠሩበት ይገባል፤ ለዚህም በመጀመሪያ ራሳችሁን ማሸነፍ ይጠበቅባችኋል፤ ለሥራችሁ ዲሲፕሊንም መታመንና መታገል አለባችሁ። ይህም በሕይወቴ ላሳካኋቸው ስኬቶችና ላስመዘገብኳቸው ተጨባጭ ውጤቶች ጠቅሞኛል" በማለት ተሞክሯቸውን አጋርተዋል፡፡

"ሁላችንም በሕይወታችን ውስጥ የእግዚአብሔርን 10ቱ ትእዛዛትን በማክበር እንዲሁም ራሳችንን በማወቅ የምንፈልገውን ስኬት እና ዓላማ ማሳካት እንችላለን" በማለት ገልጸዋል፡፡

በመጨረሻም ከማኅበረ ቅዱሳን የተበረከተላቸውን የፍቅርና አክብሮት ማስታወሻ ከማኅበሩ ዋና ሥራ አስፈጻሚ መ/ር ዋሲሁን በላይ ተቀብለዋል፡፡

(ማህበረ ቅዱሳን)

100 ሺ ብር ቅጣት!***በብስክሌት መንገድ በመኪና የሄደችው ግለሰብ 100 ሺህ ብር  ተቀጣች።በዛሬው እለት በአዲስ አበባ ከተማ በለሚኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ሲኤምሲ ሚካኤል ቤተክርስቲያን...
21/06/2025

100 ሺ ብር ቅጣት!
***
በብስክሌት መንገድ በመኪና የሄደችው ግለሰብ 100 ሺህ ብር ተቀጣች።
በዛሬው እለት በአዲስ አበባ ከተማ በለሚኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ሲኤምሲ ሚካኤል ቤተክርስቲያን አካባቢ በልማት ኮሪደር በተሰራው በብስክሌት መንገድ ላይ መኪና በማሽከርከር ደንብ የተላለፈችው ግለሰብ 100 ሺ ብር መቀጣቷ ታውቋል።

አሽከርካሪዋ በቸልተኝነት ደንብ ተላልፋ የባለስልጣኑ ኦፊሰሮች ክትትልና በህብረተሰቡ ጥቆማ መሠረት ከነተሽከርካሪዋ በቁጥጥር ስር በማዋል መቀጣቷን የከተማዋ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ገልጿል።

የአጋርነት ስምምነት! አብርሃም ግዛው ኢንተርቴይመንት እና ካቦድ ማርኬቲንግ ሶሉሽን የአጋርነት ስምምነት ተፈራረሙ!***ካቦድ ማርኬቲንግ ሶሉሽን በአይነቱ ለየት ያለ በቅርብ የሚደረግ ካቦድ ሪ...
11/06/2025

የአጋርነት ስምምነት!
አብርሃም ግዛው ኢንተርቴይመንት እና ካቦድ ማርኬቲንግ ሶሉሽን የአጋርነት ስምምነት ተፈራረሙ!
***
ካቦድ ማርኬቲንግ ሶሉሽን በአይነቱ ለየት ያለ በቅርብ የሚደረግ ካቦድ ሪል እስቴት ኤክስፖ 2025 ጋር በተያያዘ የተለያዩ የማስታወቂያ ኤቨንቱን ሁነቱን ሙሉ ሥራዎችን ለማከናወን ከአብርሃም ግዛው ኢንተርቴይንመንት ጋር ስምምነት በዛሬዉ እለት አድርገዋል።

Partnership Announcement

Kabod Marketing Solutions has officially signed an agreement with Abrham Gizaw Entertainment for media mobilization and promotional activities for the upcoming Kabod Real Estate Expo.

Abraham Gizaw

ደብዳቤው ይኸውና!አትሌት ገለቴ ቡርቃ ቅሬታ ያቀረበችበት የቀድሞ ባለቤቷ ጽፎላት የነበረው ደብዳቤ!
10/06/2025

ደብዳቤው ይኸውና!
አትሌት ገለቴ ቡርቃ ቅሬታ ያቀረበችበት የቀድሞ ባለቤቷ ጽፎላት የነበረው ደብዳቤ!

08/06/2025

Cristiano Ronaldo, Legend!
Nations League Winner.

"ባለቤቴ ዘረፈኝ! ጎዳና ልወጣ ነው ድረሱልኝ" አትሌት ገለቴ ቡርቃአትሌቷ በሩጫ ዘመኗ ያገኘችውን ሀብትና ንብረት ባለቤቷ መውሰዱን ገልጻ፣ "ጎዳና ልወጣ ነው መንግስት ይድረስልኝ" ብላለች።መ...
08/06/2025

"ባለቤቴ ዘረፈኝ! ጎዳና ልወጣ ነው ድረሱልኝ" አትሌት ገለቴ ቡርቃ
አትሌቷ በሩጫ ዘመኗ ያገኘችውን ሀብትና ንብረት ባለቤቷ መውሰዱን ገልጻ፣ "ጎዳና ልወጣ ነው መንግስት ይድረስልኝ" ብላለች።

መኖሪያ ቤት እና መንግስት በተለያየ ጊዜ የሸለማት 11 መሬቶች ውስጥ አስሩ ባለቤቷ መሸጡን እና አሁን ካለችበት ቤት ለማስወጣት በፍርድ ቤት ጉዳዩን እየጨረሰ ነው ብላለች።

ካሏት 5 መኪናዎች 4 መኪኖችን ባለቤቷ መሸጡንም ገልጻለች።

በአሁኑ ወቅት ልምምድ አቁማ በፍርሃት ለአንድ አመት ከቤት ሳትወጣ መቀመጧን ተናግራለች።

"ፍርድ ቤት ሁሉንም ነገር እኔ ላይ እየፈረደ ነው የእኔን ጉዳይ እየተመለከተ አይደለም" በማለት በገመዳ ሾው ላይ ቀርባ ተናግራለች።

Address

Africa Ave
Addis Ababa

Telephone

+251-115-540404

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Addis Gize - አዲስ ጊዜ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Addis Gize - አዲስ ጊዜ:

Share