05/06/2026
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በአርሲ ዞን በንጹሐን ዜጎችና በሃይማኖት ተቋማት ላይ በደረሰው ጥቃት የተሰማቸውን ጥልቅ ኀዘን ገለጹ
የጠቅላይ ሚኒስትር ፅሕፈት ቤት በሰጠው ወቅታዊ መግለጫ፥ ጥቃቱ የሀገሪቱን ዕድገትና 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ለማስተጓጎል ከውጭ ኃይሎችና ከአማራ ክልል አማፅያን ጋር በጥምረት የተከናወነ የጥፋት ውጥን አካል መሆኑን አስታውቋል።
የሽብር ቡድኖቹ በአማራ ክልል ከተሞች፣ በደቡባዊ ትግራይ አዋሳኝ አካባቢዎችና በአዲስ አበባ ጥቃት ለመፈጸም እንዲሁም በኦሮሚያ መንገዶችን ለመዝጋት ያደረጉት ሙከራ በፀጥታ ኃይሎች መክሸፉ ተገልጿል።
ቡድኑ ይህንን መቋቋም ሲያቅተው የብሔርና ሃይማኖት ግጭት ለመቀስቀስ በአርሲ አሰኮ ላይ ጥቃት ማድረሱንና አሁን ላይ የተቀናጀ እርምጃ እየተወሰደበት መሆኑን ፅሕፈት ቤቱ አብራርቷል።
መንግሥት መሰል እኩይ ተግባራትን በቁርጠኝነት እንደሚመክትና የፖለቲካ ቅሬታዎች በብሔራዊ ምክክር ሊፈቱ እንደሚገባ አሳስቧል።