Tirita Media

Tirita Media News provider. Providing latest News and Information.

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በአርሲ ዞን በንጹሐን ዜጎችና በሃይማኖት ተቋማት ላይ በደረሰው ጥቃት የተሰማቸውን ጥልቅ ኀዘን ገለጹ የጠቅላይ ሚኒስትር ፅሕፈት ቤት በሰጠው ወቅታዊ መግለጫ፥ ...
05/06/2026

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በአርሲ ዞን በንጹሐን ዜጎችና በሃይማኖት ተቋማት ላይ በደረሰው ጥቃት የተሰማቸውን ጥልቅ ኀዘን ገለጹ

የጠቅላይ ሚኒስትር ፅሕፈት ቤት በሰጠው ወቅታዊ መግለጫ፥ ጥቃቱ የሀገሪቱን ዕድገትና 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ለማስተጓጎል ከውጭ ኃይሎችና ከአማራ ክልል አማፅያን ጋር በጥምረት የተከናወነ የጥፋት ውጥን አካል መሆኑን አስታውቋል።

​የሽብር ቡድኖቹ በአማራ ክልል ከተሞች፣ በደቡባዊ ትግራይ አዋሳኝ አካባቢዎችና በአዲስ አበባ ጥቃት ለመፈጸም እንዲሁም በኦሮሚያ መንገዶችን ለመዝጋት ያደረጉት ሙከራ በፀጥታ ኃይሎች መክሸፉ ተገልጿል።

ቡድኑ ይህንን መቋቋም ሲያቅተው የብሔርና ሃይማኖት ግጭት ለመቀስቀስ በአርሲ አሰኮ ላይ ጥቃት ማድረሱንና አሁን ላይ የተቀናጀ እርምጃ እየተወሰደበት መሆኑን ፅሕፈት ቤቱ አብራርቷል።

መንግሥት መሰል እኩይ ተግባራትን በቁርጠኝነት እንደሚመክትና የፖለቲካ ቅሬታዎች በብሔራዊ ምክክር ሊፈቱ እንደሚገባ አሳስቧል።

የቀድሞ የኬንያ ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ እና የስራ ባልደረቦችን በማግኘቴ ታላቅ ደስታ ይሰማኛል" ጠ/ሚ አብይ አህመድ"ኡሁሩ ኬንያታ የሚመሩትና 73 አባላት የያዘውን የአፍሪካ ህብረት የምርጫ...
03/06/2026

የቀድሞ የኬንያ ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ እና የስራ ባልደረቦችን በማግኘቴ ታላቅ ደስታ ይሰማኛል" ጠ/ሚ አብይ አህመድ

"ኡሁሩ ኬንያታ የሚመሩትና 73 አባላት የያዘውን የአፍሪካ ህብረት የምርጫ ታዛቢ ልዑክ፤ ለዲሞክራሲ ግንባታ ሂደታችን ላበረከቱት አገልግሎትና አስተዋጽኦ የላቀ ምስጋናችንን እናቀርባለን"።

"‎ዲሞክራሲያዊ ሂደቶች ከአኅጉራችን ነባራዊ ሁኔታና ተሞክሮ ጋር የተጣጣሙ እንዲሆኑ ለማድረግ አፍሪካዊ ተቋማት ቁልፍ ሚና ይጫወታሉ።

የምርጫ ሂደታችንን ለመደገፍ በመላው ሀገሪቱ ታዛቢዎችን በማሰማራት የምርጫ ታዛቢ ልዑኩ ላደረገው ያልተቆጠበ ጥረት እውቅና እና አድናቆት እየሰጠን፣ የምልከታውን የተሟላ ውጤት እንጠብቃለን።

የቁጫ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ቁህዴፓ) በሰባተኛው አገራዊ ምርጫ ሂደት ላይ ከፍተኛ ቅሬታ እንዳለው አስታወቀ።ፓርቲው ዛሬ በአዲስ አበባ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ፤ በምርጫው እለት ደጋፊዎቹ ...
03/06/2026

የቁጫ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ቁህዴፓ) በሰባተኛው አገራዊ ምርጫ ሂደት ላይ ከፍተኛ ቅሬታ እንዳለው አስታወቀ።

ፓርቲው ዛሬ በአዲስ አበባ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ፤ በምርጫው እለት ደጋፊዎቹ እንዳይመርጡ መከልከላቸውንና የምርጫ ካርዳቸው በሃይል ተነጥቆ ለሌላ ፓርቲ እንዲሰጥ መደረጉን ገልጿል።

ከምርጫው አስቀድሞም ሆነ በምርጫው እለት የአካባቢው ባለስልጣናት እና የጸጥታ ሀይሎች
በፓርቲው አመራሮች እና አባላት ላይ ሰብአዊ መብት ጥሰቶች ፈጽመውብናል ሲልም ፓርቲው ገልጿል።

የቁህዴፓ ፕሬዝዳት ረዳት ፕሮፌስር ገነነ ገደቡ
እንዳሉት፤ የፓርቲው ከፍተኛ አመራሮች ጭምር በድምጽ መስጫ ክልላቸው ድምጽ እንዳይሰጡ በመንግስት አካላት እገዳ ተጥሎባቸዋል።

ፓርቲው የተፈጸሙትን የመብት ጥሰቶች ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፣ ለሰብአዊ መብት እና ለፍትህ አካላት ማሳወቁን ገልጾ፣ በአሁኑ ወቅት ምላሽ እየጠበቀ እንደሚገኝ አስታውቋል።

ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ እና ዓለም አቀፍ መስፈርቱን የጠበቀ ሆኖ መጠናቀቁን ኢሰመኮ አስታወቀ!የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ባወጣው መግለጫ፤ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የ...
02/06/2026

ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ እና ዓለም አቀፍ መስፈርቱን የጠበቀ ሆኖ መጠናቀቁን ኢሰመኮ አስታወቀ!

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ባወጣው መግለጫ፤ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የተረጋጋ፣ ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊ እና በዓለም አቀፍ መስፈርቶች መሰረት ደረጃውን የጠበቀ ሆኖ መጠናቀቁን በምልከታው ማረጋገጡን ገልጿል።

📌 ከኮሚሽኑ መግለጫ የተገኙ ዋና ዋና ነጥቦች፡

🔎 የቅርብ ክትትል፡ ኮሚሽኑ በምርጫው ሂደት ላይ ታዛቢ ባለሙያዎችን በማሰማራት ሂደቱን በቅርበት ሲከታተል ቆይቷል።

📦 የቁሳቁስ አቅርቦት፡ ለምርጫው ሂደት የሚያስፈልጉ ቁሳቁሶች በሙሉ በተገቢው መልኩ ተሟልተው ቀርበዋል።

🚶‍♂️ የረጃጅም ሰልፎች ጉዳይ፡ በምርጫው ዕለት የታዩትን ረጃጅም ሰልፎች በተመለከተ ኮሚሽኑ ለምርጫ ቦርድ ጥቆማ ማድረጉንና ቦርዱም ፈጣን የማስተካከያ እርምጃዎችን መውሰዱን ገልጿል።

➡️ በቀጣይ ምን ይጠበቃል?

ኮሚሽኑ በድህረ-ምርጫ ሂደቶች ላይም ተከታታይ ክትትል ማድረጉን እንደሚቀጥልና የሚያገኛቸውን ማናቸውንም ግኝቶች ለሕዝብ ይፋ እንደሚያደርግ አስታውቋል።

👉 ዝርዝር መረጃዎችን ለማግኘት ገጻችንን ይከታተሉ!

#ኢዜአ #ኢሰመኮ

የሲቪል ማኅበራት የምርጫ ትዝብትየኢትዮጵያ የሲቪል ማኅበራት ድርጅቶች ኅብረት ያወጣው የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የእኩለ ቀን የትዝብት ሪፖርት ይፋ አድርጓል።ኅብረቱ ከ3,100 በላይ ፕሮፌሽናል አ...
01/06/2026

የሲቪል ማኅበራት የምርጫ ትዝብት

የኢትዮጵያ የሲቪል ማኅበራት ድርጅቶች ኅብረት ያወጣው የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የእኩለ ቀን የትዝብት ሪፖርት ይፋ አድርጓል።

ኅብረቱ ከ3,100 በላይ ፕሮፌሽናል አገር በቀል ታዛቢዎችን በመላ አገሪቱ በጥናት ላይ በተመሠረተ ተመጣጣኝ ስልት በማሰማራት፣ በዜጎች ተሳትፎ ላይ የተመሠረተ የምርጫ ትዝብት ማከናወን ችሏል።

📊 ዋና ዋና የሪፖርቱ ግኝቶች በቁጥር፡

🔓 99% በሚሆኑት ጣቢያዎች ላይ ታዛቢዎች ያለምንም ገደብና እንቅፋት ገብተው ሂደቱን በነፃነት ታዝበዋል።

⏰ 97% የሚሆኑት ጣቢያዎች ከንጋቱ 12፡00 ሰዓት በፊት ተከፍተዋል፤ 95% በሚሆኑት ላይ ከ3 በላይ አስፈጻሚዎች በሥራ ገበታቸው ተገኝተዋል።

👩‍💼 አካታችነት፡ 61% ጣቢያዎች ከአንድ በላይ ሴት አስፈጻሚዎች የነበሯቸው ሲሆን፣ 26% የሚሆኑትን ጣቢያዎች በበላይነት የመሩት ሴቶች ናቸው። 13% በሚሆኑት ላይ ደግሞ አካል ጉዳተኞች በአስፈጻሚነትና በኃላፊነት ተመድበዋል።

⚖️ ገለልተኝነት፡ 97% ጣቢያዎች በሕግ በተፈቀዱ ገለልተኛ ሥፍራዎች የተቋቋሙ ሲሆን፣ 96% በሚሆኑት ጣቢያዎች ክልል ውስጥ ምንም ዓይነት የፖለቲካ ፓርቲ ቅስቀሳ አልተደረገም።

♿ ልዩ ድጋፍ፡ 96% ጣቢያዎች ለሴቶችና አረጋውያን፣ እንዲሁም 93% ጣቢያዎች አካል ጉዳተኞች ያለ ረዳት ገብተው ድምፅ እንዲሰጡ ተደርገው ተዘጋጅተዋል።

🔍 ለተጨማሪ ወቅታዊ መረጃዎች ገጻችንን Like እና Follow ያድርጉ!

#ምርጫ2018 #ምርጫቦርድ #ኢትዮጵያ

ተራዝሟል!እስከ ምሽት 6:00 ድረስ ድምጽ የመስጠት ሒደቱ ይቀጥላል- የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ
01/06/2026

ተራዝሟል!
እስከ ምሽት 6:00 ድረስ ድምጽ የመስጠት ሒደቱ ይቀጥላል

- የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

ሜድ ስታር የውስጥ ደዌ ስፔሻሊቲ ክሊኒክ በአዲስ መልክ ስራ መጀመሩን አስታወቀሜድ ስታር የውስጥ ደዌ ስፔሻሊቲ ክሊኒክ የተመሰረተበትን 6ኛ ዓመት እና በአዲስ መልኩ ወደ ስራ መግባቱን አስመል...
31/05/2026

ሜድ ስታር የውስጥ ደዌ ስፔሻሊቲ ክሊኒክ በአዲስ መልክ ስራ መጀመሩን አስታወቀ

ሜድ ስታር የውስጥ ደዌ ስፔሻሊቲ ክሊኒክ የተመሰረተበትን 6ኛ ዓመት እና በአዲስ መልኩ ወደ ስራ መግባቱን አስመልክቶ ቅዳሜ ግንቦት 22 ቀን 2018 ዓ.ም የምረቃ መርሃ-ግብር አካሂዷል።

ክሊኒኩ በአዲስ መልክ ስራ መጀመሩን ተከትሎ ለታካሚዎቹ ጥራትና ደረጃውን የጠበቀ የህክምና አገልግሎት ማቅረብ መጀመሩን የገለጸ ሲሆን፣ በዚህም ለ56 ዜጎች አዲስ የስራ እድል መፍጠር መቻሉን አስታውቋል።

የሜድ ስታር የውስጥ ደዌ ስፔሻሊቲ ክሊኒክ መስራች ዶክተር ዳዊት አማረ በምረቃው ስነ-ስርዓት ላይ እንደተናገሩት፤ ክሊኒኩ ላለፉት 6 ዓመታት በውስጥ ደዌ ህክምና ዘርፍ ስኬታማ አገልግሎት ሲሰጥ የቆየ አንጋፋ የህክምና ማዕከል ነው። አሁን ላይ ደግሞ የህሙማንን እርካታ ይበልጥ ለማሳደግና ደረጃውን የጠበቀ ህክምና ለመስጠት የሚያስችለውን ዝግጅት አጠናቆ በተሻለ መልኩ ስራ መጀመሩን ገልጸዋል።

"በምግባር ህሙማንን ማከም፣ በተግባር ህክምናን ማከል ዋና ዓላማችን ነው" ያሉት ዶክተር ዳዊት፣ ለታካሚዎች ደስታና እርካታን በሚያስገኝ መልኩ በከፍተኛ ትኩረት እየተሰራ መሆኑን አብራርተዋል።

ማዕከሉ ባለፉት ስድስት ዓመታት በተለያዩ የውስጥ ደዌ ስፔሻሊቲ ዘርፎች የህክምና አገልግሎት ሲሰጥ የቆየ ሲሆን፣ ከዚህ ጎን ለጎንም ማህበራዊ ኃላፊነቱን በቅልጥፍና እየተወጣ እንደሚገኝ ተነግሯል።

31/05/2026

አርሴናሎች ለ22 አመታት የጠበቁትን የፕሪሚየር ሊጉን ዋንጫ በደማቅ አቀባበል ተቀብለውታል

"እንደገና ጠንክረን እንመለሳለን! በዚህ እርግጠኛ ሁኑ!"                                                      -ራይስ
31/05/2026

"እንደገና ጠንክረን እንመለሳለን! በዚህ እርግጠኛ ሁኑ!"
-ራይስ

አስገራሚው የአርቴታ መግለጫ!" በእርግጥ ፒኤስጂ የአውሮፓ ሻምፒዮን ነው። እኛም እዚህ የተገኘነው ያንን ክብር ልንወስድባቸው ነው"- የአርሴናሉ አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ ከቻምፒየንስ ሊግ ፍጻሜ...
29/05/2026

አስገራሚው የአርቴታ መግለጫ!
" በእርግጥ ፒኤስጂ የአውሮፓ ሻምፒዮን ነው። እኛም እዚህ የተገኘነው ያንን ክብር ልንወስድባቸው ነው"

- የአርሴናሉ አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ ከቻምፒየንስ ሊግ ፍጻሜ ጨዋታ በፊት በሰጠው መግለጫ የተናገረው ነው።

Address

Africa Avenue
Addis Ababa

Telephone

+251-115-540404

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Tirita Media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Tirita Media:

Share