Tirita Media

Tirita Media News provider. Providing latest News and Information.

አርሰናል ለቪኒሺየስ ዝውውር...አርሴናል ለቪኒሺየስ ጁኒየር በክለቡ ታሪክ ከፍተኛ የተባለ ስምምነት ማቅረቡ ታውቋል።መድፈኞቹ ለብራዚላዊው ተጫዋች ሳምንታዊ ደሞዝ ከ400ሺ ፓውንድ በላይ ለመክ...
26/07/2026

አርሰናል ለቪኒሺየስ ዝውውር...

አርሴናል ለቪኒሺየስ ጁኒየር በክለቡ ታሪክ ከፍተኛ የተባለ ስምምነት ማቅረቡ ታውቋል።

መድፈኞቹ ለብራዚላዊው ተጫዋች ሳምንታዊ ደሞዝ ከ400ሺ ፓውንድ በላይ ለመክፈል መዘጋጀታቸውን ቴሌግራፍ ዘግቧል።

የባንዲራን ጉዳይ በተመለከተበአስር ሰዎች ደረጃ ተከፋፍሎ በተደረገው የንዑስ ቡድን ምክክር ላይ የኢትዮጵያ ሰንደቅ አለማ ፣ አርማ፣ መዝሙር እንዲሁም የክልሎች መዝሙር ፣ሰንደቅ አላማ እና አር...
26/07/2026

የባንዲራን ጉዳይ በተመለከተ

በአስር ሰዎች ደረጃ ተከፋፍሎ በተደረገው የንዑስ ቡድን ምክክር ላይ የኢትዮጵያ ሰንደቅ አለማ ፣ አርማ፣ መዝሙር እንዲሁም የክልሎች መዝሙር ፣ሰንደቅ አላማ እና አርማ ምን ይሁን በሚሉ ነጥቦች ላይ ተመካካሪዎች አማራጭ ሃሳብ አስቀምጠዋል።

ባለፉት ቀናት ፤10 ሰዎች ባሉት ንዑሳን ቡድን ተከፋፍለው ውይይት አድርገው 50 አባላት ላሉት ተመካካሪ ቡድን ቀርበው በቃለ ጉባዔ ፀድቆ ሰኞ ይጀመራል ወደ ተባለው 250 አባላት ወዳሉት ቡድን ከተላላፉ አጀንዳዎች ውስጥ በሀገር ግንባታ ስር የሚገኘው ፣ ሀገራዊ ምልክቶች እና መገለጫዎች ላይ ስምምነት ላይ መድረስ የሚለው ንዑስ አጀንዳ አንዱ ነው።

ሀገር ግንባታ በሚለው ዋና አጀንዳ ስር ከተዘረዘሩት 7 ንዑሳን አጀንዳዎች ውስጥ የሀገር ባለቤትነት ጉዳይ ፣ታሪክ እና ማንነት ፣የቋንቋ ጉዳዮች ፣ የሀገር ግንባታ እና ብዝሃነት አስተዳደር ፣ሀገራዊ ምልክቶች እና መገለጫዎች እና ሎሎችም ንዑሳን አጀንዳዎች ተዘርዝረዋል ።

ለንዑሳን አጀንዳዎቹ ደግሞ ለእያንዳንዳቸው ከሶስት እስከ ሰባት የሚደርሱ የውይይት መሪ ጥያቄዎች ቀርበዋል።

ለምሳሌ ሀገራዊ ምልክቶች እና መገለጫዎች ላይ ስምምነት ላይ መድረስ በሚለው ንዑስ አጀንዳ ስር ሶስት የውይይት መሪ ጥያቄዎች ተነስተዋል ።

የኢትዮጵያ ሰንደቅ አላማ ማለትም ቀለማቱ እና አርማው፣ብሔራዊ በዓላት እና መዝሙር የሁሉም ማህበረሰቦች ወካይ እንዲሆኑ ምን መለወጥ ያስፈልጋል የሚለው ጥያቄ አንደኛው ነው።

የክልል መዝሙር እና የክልል ሰንደቅ አለማ አስፈላጊ ነው ወይ? የሚሉ ተጨማሪ ሁለት የውይይት መነሻ መሪ ጥያቄዎችም ቀርበዋል።

በዚህ ንዑስ አጀንዳ ስር በቀረቡ መሪ ጥያቄዎች ላይ 50 አባላት ባሉት ቡድን ደረጃ ተወያይተው ቃለ ጉባዔ ይዘው ማጠናቀቃቸውን የተናገሩት የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤትን ወክለው በምክክሩ ላይ መሳተፋቸውን የተናገሩት አቶ ፈይሰል አብዱላዚዝ፤ የሀገሪቱ ሰንደቅ አለማ አርማ ምን ይሁን? የክልሎች ባንዲራ እና መዝሙርስ ምን መሳይ ይሁን? ለሚለው ሀሳብ በርካታ አማራጭ ሃሳቦች እንደቀረቡ ነግረውናል ።

የሀገሪቱን ሰንደቅ አለማ በተመለከተ አረንጓዴ ፣ቢጫ፣ቀይ ቀለም ያለው የአሁኑ ሰንደቅ አላማ አንዳይነካ ነገር ግን አርማው ይቀየር የሚሉ ሀሳቦች መነሳታቸውን ተናግረዋል ።

የቀረቡ አማራጭ ሀሳቦች ደግሞ አሁን ያለው የኮከብ አርማ አንዲቀር እና አሁን ባለው ሰንደቅ አላማ ላይ ለምሳሌ ልክ አንደ "አሜሪካ ባንዲራ" የሁሉም ብሔረሰብ አርማ ይቀመጥ የሚለው እንደ አንድ ሀሳብ መቅረብ አለበት የሚል መኖሩን አስረድተዋል ።

ከፊሉ ተወያይ ደግሞ የብሔረሰብ አርማ ሳይሆን የሰላም ምልክት የሆነችው "እርግብ" አርማ ትሁን የሚል ሃሳብ አቅርቧል ብለዋል አቶ ፈይሰል።

እርሳቸው በተሳተፉበት ቡድን በዋናነት እንዲሆን የተስማሙት ግን አሁን ያለው ሰንደቅ አላማ ሳይነካ በሀገሪቱ ያሉትን ሁሉንም ክልሎች ሊወክል የሚችል አርማ ይደረግ የሚለው ላይ አንደሆነ ተሳታፊው ዘርዝረዋል ።

የክልል ሰንደቅ አላማን በተመለከተ በአገሪቱ "ከአንድ ሰንደቅ አላማ ውጪ መኖር የለበትም " እና የሁሉም ክልሎች ሰንደቅ አላማ አሁን ያለው አረንጓዴ ፣ቢጫ፣ ቀይ ቀለም ያለው ሆኖ ነገር ግን አርማ የሚወክላቸውን እንዲጠቀሙ በሚለው ላይ ተነጋግረናል ብለዋል።

መዝሙርን በተመለከተ ደግሞ የአሁኑ ይቀጥል የሚለው ላይ ብዙዎች እሳቸው ባሉበት በቡደን ደረጃ መስማማታቸውን ጠቅሰው ክልሎች መዝሙር እንዲኖራቸው ነገር ግን የመዝሙሩ ይዘት ጠብ አጫሪ አንዳይሆን የሚለው ላይ ወይይት አድርገናል ሲሉ ነግረውናል።

25/07/2026

በኤአይ ስታርታፕ የመጀመሪያዎቹ ሰልጣኞች ተመረቁ

የኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት በኤአይ ስታርታፕ ያሰለጠናቸውን ወጣቶች አስመረቀ።

ዛሬ የተመረቁት ሰልጣኞች በስታርት አፕ በጤና ፣ በግብርና በሌሎች ወሳኝ ዘርፎች ላይ የፈጠራ ስራዎችን አቅርበዋል።

ቦስፈረስ ሜዲካል ሶልሽን አርቲስት ኢንጂነር ነብዩ እንድርያስን እና የማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪውን አብርሃም ዘራይን (1 ብር)  የብራንድ አምባሳደር አድርጎ ሾመ! ***ቦስፈረስ ሜዲካል ...
25/07/2026

ቦስፈረስ ሜዲካል ሶልሽን አርቲስት ኢንጂነር ነብዩ እንድርያስን እና የማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪውን አብርሃም ዘራይን (1 ብር) የብራንድ አምባሳደር አድርጎ ሾመ!
***
ቦስፈረስ ሜዲካል ሶልሽን ኃ.የተ.የግ.ማህበር ከታዋቂው አርቲስት ኢንጂነር ነብዩ እንድርያስ እና አብርሃም ዘራይ ጋር ለአንድ ዓመት የሚቆይ የብራንድ አምባሳደርነት የሥራ ውል ስምምነት በዛሬው ዕለት ተፈራርሟል።

በፊርማ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ እንደተገለጸው፣ አምባሳደሮቹ ከድርጅቱ ጋር በመሆን በቴሌቪዥን፣ በሶሻል ሚዲያዎች እና በተለያዩ መድረኮች በሚያስተላልፉ ማስታወቂያዎችና ፕሮሞሽኖች ላይ የሚሠራ ይሆናል።

🤝 የስምምነቱ ዓላማ እና የአምባሳአመራረጥ

ድርጅቱ ይህንን ስምምነት ያደረገበት ዋና ዋና ምክንያቶች፦
የሕዝብ ተደራሽነትን ማሳደግ፡ ከሕዝቡ ጋር ያለውን ግንኙነት በተሻለ መልኩ ለማጎልበት፣
ማኅበራዊ ኃላፊነትን መወጣት፡ ሕብረተሰቡ ስለ ቆዳ ጤና እና ውበት አጠባበቅ ያለውን ግንዛቤ ለማሳደግ በጋራ ለመሥራት ነው።

አምባሳደሮቹ ለዚህ ኃላፊነት የተመረጡበት ዋና ምክንያት ማኅበራዊ ግዴታዎቹን በተገቢው የሚወጣ እና በሥራቸው ላይ ብቻ የሚያተኩሩ ባለሙያ በመሆናቸው ነው።

🏥 ስለ ቦስፈረስ ሜዲካል ሶልሽን ኃ.የተ.የግ.ማህበር

የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ዮሐንስ መንግሥቱ አበበ እንደገለጹት፤ ቦስፈረስ ሜዲካል ሶልሽን ከተመሠረተ ከ2 ዓመት በላይ ያስቆጠረ ሲሆን፣ በኢትዮጵያ በጤና እና በውበት አጠባበቅ ዘርፍ በስፋት የሚሠራ ተቋም ነው። ድርጅቱ በዋናነት በሚከተሉት ሁለት ዓበይት ዘርፎች ላይ ያተኩራል፦

የትምህርትና ማሰልጠኛ ዘርፍ (Cosmetology & Skin Care Training): በኮስሞቶሎጂ እና በቆዳ እንክብካቤ ዘርፍ ይሰማሩ ለሚፈልጉ ሰልጣኞች የቲዎሪ እና የተግባር (Practical) ስልጠናዎችን በመስጠት በዘርፉ የሰለጠነ የሰው ኃይል ያፈራል፤ የሥራ ዕድልም ይፈጥራል።

የሕክምና እና የውበት ማዕከል (Skin & Aesthetic Center): ለተለያዩ የቆዳ ችግሮች የሕክምና አገልግሎት ከመስጠቱም በላይ፣ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም ለፊት እና ለሰውነት ውበት አጠባበቅ የሚያስፈልጉ ልዩ ልዩ የስነ-ውበት (Aesthetics) አገልግሎቶችን ያቀርባል።

"በቀጣዮቹ ሳምንታት 250 አባላት የያዙ ቡድኖች ውይይት ይጀምራሉ" ኮሚሽኑየኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን በቀጣዮቹ ሳምንታት 250 አባላት ያሏቸው ቡድኖች ውይይት እንደሚጀምሩ ገለጸ።ኮሚ...
25/07/2026

"በቀጣዮቹ ሳምንታት 250 አባላት የያዙ ቡድኖች ውይይት ይጀምራሉ" ኮሚሽኑ

የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን በቀጣዮቹ ሳምንታት 250 አባላት ያሏቸው ቡድኖች ውይይት እንደሚጀምሩ ገለጸ።

ኮሚሽኑ ዛሬ በሰጠው መግለጫ ጉባኤው በተቀመጡት ስምንት አጀንዳዎች ላይ በተለያዩ ቡድኖች የሚደረገውን ውይይት በማጠናከር ወደ ቀጣዩ የውይይት ምዕራፍ መሸጋገሩን ገልጿል።

የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መሥፍን አርዓያ ጉባኤው እስካሁን የተጓዘበትን ሂደት አስረድተዋል። እንደ ዋና ኮሚሽነሩ ገለጻ በ10 አባላት ንዑስ ቡድኖች ውስጥ ሲካሄድ የቆየው ውይይት ተጠናክሮ የቀጠለ ሲሆን ፤ የተሰበሰቡት ሃሳቦች በሰብሳቢዎችና በጸሐፊዎች አማካኝነት ለ50 አባላት ቡድኖች መቅረብ መጀመራቸውን ገልጸዋል።

በቀጣዮቹ ሳምንታት ውስጥም ሃሳቦቹ ተጨማሪ ውይይት ከተደረገባቸው በኋላ ለ250 አባላት ላሏቸው ቡድኖች እንደሚቀርቡ ኮሚሽነሩ አመላክተዋል።

ስፔን ቻምፒዮንስ!
19/07/2026

ስፔን ቻምፒዮንስ!

ባማኮን ሪል እስቴት ቦሌ አካባቢ ዘመናዊ ህንጻን አስመረቀባማኮን ሪል እስቴት በቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ አካባቢ የገነባውን ዘመናዊ የመኖሪያ አፓርታማ ህንፃ በይፋ አስመረቀ።ኩባንያው ግንባታው ...
16/07/2026

ባማኮን ሪል እስቴት ቦሌ አካባቢ ዘመናዊ ህንጻን አስመረቀ

ባማኮን ሪል እስቴት በቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ አካባቢ የገነባውን ዘመናዊ የመኖሪያ አፓርታማ ህንፃ በይፋ አስመረቀ።

ኩባንያው ግንባታው ሙሉ በሙሉ የተጠናቀቀውን ይህን ህንፃ፣ በዛሬው ዕለት ለደንበኞቹ አስረክቧል። በምረቃው ሥነ-ሥርዓት ላይ እንደተገለጸው፣ በሀገሪቱ የታየውን የዋጋ ንረትና የኢኮኖሚ ጫና ተቋቁሞ፣ በደንበኞች ላይ ምንም ዓይነት ተጨማሪ ክፍያ ሳይጠይቅ ፕሮጀክቱን ማጠናቀቅ መቻሉ ታውቋል።

የባማኮን ሪል እስቴት የሽያጭና ማርኬቲንግ ዋና ኦፊሰር አቶ ፍሬው በየነ፣ ህንፃው 22 ሰፋፊ መኖሪያ ቤቶችና አንድ ፔንት ሃውስን ያካተተ መሆኑን ገልጸዋል። በየወለሉ ሁለት አፓርታማዎች ብቻ የሚገኙበት ይህ ህንፃ፣ ለነዋሪዎች ምቹነትና ግላዊነት (Privacy) ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት የተገነባ መሆኑ ተጠቅሷል።

አፓርታማዎቹ የ206 እና 208 ካሬ ሜትር ስፋት ያላቸው ሲሆን፣ ለዘመናዊና ለባህላዊ የምግብ ዝግጅት የሚሆኑ ሁለት ኩሽናዎችን የያዙ ናቸው። ይህም የጭስና የምግብ ሽታ ወደ ሳሎን እንዳይሰራጭ ታስቦ የተሰራ ነው።

ባማኮን ሪል እስቴት፣ ህንፃው ወደ ገበያ ከመውጣቱ በፊት ከ80 እስከ 85 በመቶ ግንባታው ተጠናቆ እንደነበር የገለጸ ሲሆን፣ ይህም ለደንበኞች የዋጋ ጭማሪ እንዳይደረግ ትልቅ ድርሻ እንደነበረው አስታውቋል።

ባማኮን ሪል እስቴት ከተቋቋመ ሰባት ዓመታትን ያስቆጠረ ሲሆን፣ ያስረከበው ህንፃ አራተኛው ፕሮጀክቱ ነው። እናት ኩባንያው የሆነው ባማኮን ኢንጂነሪንግ ደግሞ በአዲስ አበባ የባንክ ዲስትሪክት አካባቢ ግዙፍ ህንፃዎችን በመገንባት ከ23 ዓመታት በላይ ልምድ እንዳለው ይታወቃል።

እንግሊዝ አስደንጋጭ ሽንፈት ደረሰባት!አርጀንቲና 2ለ1 በማሸነፍ ለአለም ዋንጫ ፍጻሜ አልፋለች!
15/07/2026

እንግሊዝ አስደንጋጭ ሽንፈት ደረሰባት!
አርጀንቲና 2ለ1 በማሸነፍ ለአለም ዋንጫ ፍጻሜ አልፋለች!

ስፔን ለፍጻሜ አለፈችስፔን በግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ፈረንሳይን 2ለ0 በመርታት ለፍጻሜው አልፋለች። በፍጻሜው ጨዋታም ከእንግሊዝና አርጀንቲና ጨዋታ አሸናፊ ጋር ትጫወታለች።
14/07/2026

ስፔን ለፍጻሜ አለፈች

ስፔን በግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ፈረንሳይን 2ለ0 በመርታት ለፍጻሜው አልፋለች። በፍጻሜው ጨዋታም ከእንግሊዝና አርጀንቲና ጨዋታ አሸናፊ ጋር ትጫወታለች።

እንግሊዝ ኖርዌይን 2ለ1 በማሸነፍ ግማሽ ፍጻሜ ማለፍ ችላለች።
11/07/2026

እንግሊዝ ኖርዌይን 2ለ1 በማሸነፍ ግማሽ ፍጻሜ ማለፍ ችላለች።

Address

Africa Avenue
Addis Ababa

Telephone

+251-115-540404

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Tirita Media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Tirita Media:

Shortcuts

Share