
02/08/2025
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከዲሲ ዩናይትድ ጋር ጨዋታውን ያደርጋል
ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_ሐምሌ 26/2017 ዓ.ም
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አሜሪካ ላይ ከዲሲ ዩናይትድ ጋር የሚያደርገውን ጨዋታ ዛሬ ለሊት ከ6:00 ጀምሮ ያደርጋል።
በኦዲ ፊልድ ስታድየም በሚደረገው ጨዋታው ከ13 ሺህ በላይ ተመልካቾች እንደሚገኙ ይጠበቃል።
ይህ ጨዋታ ለተጫዋቾች ዕድል መፍጠር እና የድያስፖራው ማህበረሰብ ብሔራዊ ቡድኑን በቅርበት የመመልከት አጋጣሚን ለመፍጠር ያለመ ነው።
በተጨማሪም ገቢ ከማግኘት እና የተለያዩ የማርኬቲንግ ስራዎችን ከመስራት አንፃርም ፌዴሬሽኑ ባለው ስምምነት መሰረት ጨዋታው የሚደረግ ይሆናል።
ለጨዋታው አሰልጣኝ መሳይ ተፈሪ 20 ተጫዋቾችን በመያዝ ወደ ስፍራው ማቅናታቸው የሚታወቅ ሲሆን ሁለት ልምምዶችንም አሜሪካ ላይ አድርገዋል።
ብሔራዊ ቡድኑ ጨዋታውን በማድረጉ ብቻ ፌዴሬሽኑ 25 ሺህ ዶላር የሚያገኝ ሲሆን በጨዋታው አሸናፊ ከሆነ ደግሞ ተጨማሪ 50 ሺህ ዶላር ያገኛል።
30 ክለቦችን በሚያሳትፈው የአሜሪካ ሜጀር ሊግ ሶከር የሚወዳደረው ዲሲ ዩናይትድ በ25 ጨዋታዎች 19 ነጥቦችን በመሰብሰብ በደረጃ ሰንጠረዡ 27ኛ ላይ ይገኛል።
ሀብታሙ ምትኩ
Social Media Links
Youtube➡️: https://www.youtube.com/c/PrimeMediaPM
FB AfaanOromoo ➡️ https://www.facebook.com/PrimeMediaPM/
FB Primesport ➡️ https://web.facebook.com/primesportet/
FB English ➡️ https://www.facebook.com/profile.php?id=61576239091981
Telegram Afaan Oromoo➡️: http://t.me/PrimeMedia
Tiktok➡️ https://www.tiktok.com/.tv