Prime Sport ET

Prime Sport ET Prime Media is an East African regional media organization that aims to educate, entertain, &inspire

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከዲሲ ዩናይትድ ጋር ጨዋታውን ያደርጋል ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_ሐምሌ 26/2017 ዓ.ም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አሜሪካ ላይ ከዲሲ ዩናይትድ ጋር የሚያደርገውን...
02/08/2025

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከዲሲ ዩናይትድ ጋር ጨዋታውን ያደርጋል

ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_ሐምሌ 26/2017 ዓ.ም

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አሜሪካ ላይ ከዲሲ ዩናይትድ ጋር የሚያደርገውን ጨዋታ ዛሬ ለሊት ከ6:00 ጀምሮ ያደርጋል።

በኦዲ ፊልድ ስታድየም በሚደረገው ጨዋታው ከ13 ሺህ በላይ ተመልካቾች እንደሚገኙ ይጠበቃል።

ይህ ጨዋታ ለተጫዋቾች ዕድል መፍጠር እና የድያስፖራው ማህበረሰብ ብሔራዊ ቡድኑን በቅርበት የመመልከት አጋጣሚን ለመፍጠር ያለመ ነው።

በተጨማሪም ገቢ ከማግኘት እና የተለያዩ የማርኬቲንግ ስራዎችን ከመስራት አንፃርም ፌዴሬሽኑ ባለው ስምምነት መሰረት ጨዋታው የሚደረግ ይሆናል።

ለጨዋታው አሰልጣኝ መሳይ ተፈሪ 20 ተጫዋቾችን በመያዝ ወደ ስፍራው ማቅናታቸው የሚታወቅ ሲሆን ሁለት ልምምዶችንም አሜሪካ ላይ አድርገዋል።

ብሔራዊ ቡድኑ ጨዋታውን በማድረጉ ብቻ ፌዴሬሽኑ 25 ሺህ ዶላር የሚያገኝ ሲሆን በጨዋታው አሸናፊ ከሆነ ደግሞ ተጨማሪ 50 ሺህ ዶላር ያገኛል።

30 ክለቦችን በሚያሳትፈው የአሜሪካ ሜጀር ሊግ ሶከር የሚወዳደረው ዲሲ ዩናይትድ በ25 ጨዋታዎች 19 ነጥቦችን በመሰብሰብ በደረጃ ሰንጠረዡ 27ኛ ላይ ይገኛል።

ሀብታሙ ምትኩ

Social Media Links

Youtube➡️: https://www.youtube.com/c/PrimeMediaPM

FB AfaanOromoo ➡️ https://www.facebook.com/PrimeMediaPM/

FB Primesport ➡️ https://web.facebook.com/primesportet/

FB English ➡️ https://www.facebook.com/profile.php?id=61576239091981

Telegram Afaan Oromoo➡️: http://t.me/PrimeMedia

Tiktok➡️ https://www.tiktok.com/.tv

8ኛው የቻን ውድድር ከዛሬ ጀምሮ ይደረጋል ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_ሐምሌ 26/2017 ዓ.ም በሀገር ውስጥ ሊግ የሚጫወቱ ተጫዋቾችን ብቻ የሚያሳትፈው የቻን ውድድር ለስምንተኛ ጊዜ ከዛሬ ...
02/08/2025

8ኛው የቻን ውድድር ከዛሬ ጀምሮ ይደረጋል

ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_ሐምሌ 26/2017 ዓ.ም

በሀገር ውስጥ ሊግ የሚጫወቱ ተጫዋቾችን ብቻ የሚያሳትፈው የቻን ውድድር ለስምንተኛ ጊዜ ከዛሬ ጀምሮ ይካሄዳል።

የዘንድሮው ውድድር የ2027 የአፍሪካ ዋንጫ አዘጋጅ በሆኑት በኬንያ ፣ ዩጋንዳ እና ታንዛኒያ አስተናጋጅነት የሚደረግ ነው።

አምስት ስታድየሞች የተዘጋጁ ሲሆን በታንዛኒያ ሁለት ፣ በኬንያ ሁለት እንዲሁም በዩጋንዳ አንድ ስታድየም ላይ ውድድሩ ይካሄዳል።

19 ሀገራት በአራት ምድቦች ተከፍለው የሚሳተፉ ሲሆን ሶስቱ ምድቦች እያንዳንዳቸው አምስት ብሔራዊ ቡድኖች ቀሪ አንዱ ምድብ ደግሞ አራት ብሔራዊ ቡድኖችን ይዟል።

የመክፈቻው ጨዋታ ዛሬ ከምሽት 2:00 ጀምሮ በዳሬ ሰላም ቤንጃሚን ምካፓ ስታድየም ላይ በታንዛኒያ እና ቡርኪናፋሶ መካከል ይደረጋል።

ኢንተርናሽናል ዋና ዳኛ ባምላክ ተሰማ እንዲሁም ኢንተርናሽናል ረዳት ዳኛ ፋሲካ የኋላሸት በዳኝነት በውድድሩ ይሳተፋሉ።

ሀብታሙ ምትኩ

Social Media Links

Youtube➡️: https://www.youtube.com/c/PrimeMediaPM

FB AfaanOromoo ➡️ https://www.facebook.com/PrimeMediaPM/

FB Primesport ➡️ https://web.facebook.com/primesportet/

FB English ➡️ https://www.facebook.com/profile.php?id=61576239091981

Telegram Afaan Oromoo➡️: http://t.me/PrimeMedia

Tiktok➡️ https://www.tiktok.com/.tv

ማንችስተር ሲቲ ከክለቡ ወሳኝ ሰው ጋር በይፋ ተለያየ ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_ሐምሌ 24/2017 ዓ.ም ማንችስተር ሲቲን ላለፉት 13 ዓመታት በስፖርቲንግ ዳይሬክተርነት ያገለገሉት ቲኬ ቤ...
31/07/2025

ማንችስተር ሲቲ ከክለቡ ወሳኝ ሰው ጋር በይፋ ተለያየ

ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_ሐምሌ 24/2017 ዓ.ም

ማንችስተር ሲቲን ላለፉት 13 ዓመታት በስፖርቲንግ ዳይሬክተርነት ያገለገሉት ቲኬ ቤግሪስቴይን ከክለቡ ጋር መለያየታቸው እርግጥ ሆኗል።

ቤግሪስቴይን ከወራት በፊት ከሲቲ ጋር እንደሚለያዩ መገለፁ የሚታወስ ሲሆን ክለቡም ከደቂቃዎች በፊት ይፋ አድርጎታል።

የ60 ዓመቱ ግለሰብ በማንችስተር ሲቲ የታላቅነት ጉዞ ላይ ትልቁን ሚና የተጫወቱ ሲሆን ፔፕ ጋርድዮላን ወደ ክለቡ ማምጣትን ጨምሮ ወሳኝ ተጫዋቾችን ወደ ኢትሀድ እንዲመጡ አድርገዋል።

በቲኪ ቤግሪስቴይን ዘመን ማንችስተር ሲቲ 6 የፕሪሚየር ሊግ ፤ አንድ የቻምፒየንስ ሊግ እና 2 የኤፍ ኤ ዋንጫን ጨምሮ 21 ዋንጫዎችን አሳክቷል።

ክለቡ ይፋ ባደረገው መረጃ መስከረም ላይ በሚደረገው የማንችስተር ደርቢ ጨዋታ ላይ ደማቅ አሸኛኘት ይደረግላቸዋል።

በምትካቸውም የቀድሞው የስፖርቲንግ ሊዝበን ስፖርቲንግ ዳይሬክተር ሁጎ ቭያና ኃላፊነቱን የሚረከቡ ይሆናል።

ሀብታሙ ምትኩ

Social Media Links

Youtube➡️: https://www.youtube.com/c/PrimeMediaPM

FB AfaanOromoo ➡️ https://www.facebook.com/PrimeMediaPM/

FB Primesport ➡️ https://web.facebook.com/primesportet/

FB English ➡️ https://www.facebook.com/profile.php?id=61576239091981

Telegram Afaan Oromoo➡️: http://t.me/PrimeMedia

Tiktok➡️ https://www.tiktok.com/.tv

በአቋም መለኪያ ጨዋታ አርሰናል ተሸነፈ ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_ሐምሌ 24/2017 ዓ.ም በቅድመ ውድድር ዘመን ዝግጅት ሶስተኛ የአቋም መለኪያ ጨዋታውን ያደረገው አርሰናል በቶተንሀም ሆት...
31/07/2025

በአቋም መለኪያ ጨዋታ አርሰናል ተሸነፈ

ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_ሐምሌ 24/2017 ዓ.ም

በቅድመ ውድድር ዘመን ዝግጅት ሶስተኛ የአቋም መለኪያ ጨዋታውን ያደረገው አርሰናል በቶተንሀም ሆትስፐርስ 1 ለ 0 ተሸንፏል።

በሆንግ ኮንግ በተደረገው ጨዋታ ፓፔ ማታር ሳር በ45ኛው ደቂቃ ላይ የቶተንሀም ሆትስፐርስን ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ አስቆጥሯል።

ቪክተር ዮኬሬሽ እና ክርስቲያን ሞስኬራ በአርሰናል ማልያ የመጀመሪያ ጨዋታቸውን አድርገዋል።

አርሰናል በቀጣይ ከቪያርያል ሲጫወት ቶተንሀም ሆትስፐርስ ደግሞ ከኒውካስትል ዩናይትድ ይጫወታል።

ሀብታሙ ምትኩ

Social Media Links

Youtube➡️: https://www.youtube.com/c/PrimeMediaPM

FB AfaanOromoo ➡️ https://www.facebook.com/PrimeMediaPM/

FB Primesport ➡️ https://web.facebook.com/primesportet/

FB English ➡️ https://www.facebook.com/profile.php?id=61576239091981

Telegram Afaan Oromoo➡️: http://t.me/PrimeMedia

Tiktok➡️ https://www.tiktok.com/.tv

ማንችስተር ዩናይትድ በርንማውዝን 4 ለ 1 አሸነፈ ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_ሐምሌ 24/2017 ዓ.ም በአሜሪካ በመካሄድ ላይ ባለው የፕሪሚየር ሊግ ሰመር ሲርየስ ውድድር ሁለተኛ ጨዋታ ማን...
31/07/2025

ማንችስተር ዩናይትድ በርንማውዝን 4 ለ 1 አሸነፈ

ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_ሐምሌ 24/2017 ዓ.ም

በአሜሪካ በመካሄድ ላይ ባለው የፕሪሚየር ሊግ ሰመር ሲርየስ ውድድር ሁለተኛ ጨዋታ ማንችስተር ዩናይትድ በርንማውዝን 4 ለ 1 አሸንፏል።

በጨዋታው ራስመስ ሆይሉንድ ፣ ፓትሪክ ዶርጉ ፣ አማድ ድያሎ እና ኢታን ዊልያምስ የማንችስተር ዩናይትድን ግቦች ያስቆጠሩ ተጫዋቾች ናቸው።

የበርንማውዝን ብቸኛ ግብ ማትየስ ዲ ላይት በ88ኛው ደቂቃ ላይ በራሱ መረብ ላይ አሳርፏል።

በሌላኛው የውድድሩ ጨዋታ ዌስትሀም ዩናይትድ ኤቨርተንን 2 ለ 1 ረቷል።

ሉካስ ፓኩዌታ እና ኒክላስ ፈልክረግ ለዌስትሀም ዩናይትድ እድሪሳ ጋና ጉዬ ደግሞ ለኤቨርተን ኳስ እና መረብን አገናኝተዋል።

የሰመር ሲርየስ ውድድሩ የፊታችን ቅዳሜ ለሊት ፍፃሜውን ሲያገኝ ማንችስተር ዩናይትድ ከኤቨርተን እንዲሁም ዌስትሀም ዩናይትድ ከበርንማውዝ ይጫወታሉ።

ሀብታሙ ምትኩ

Social Media Links

Youtube➡️: https://www.youtube.com/c/PrimeMediaPM

FB AfaanOromoo ➡️ https://www.facebook.com/PrimeMediaPM/

FB Primesport ➡️ https://web.facebook.com/primesportet/

FB English ➡️ https://www.facebook.com/profile.php?id=61576239091981

Telegram Afaan Oromoo➡️: http://t.me/PrimeMedia

Tiktok➡️ https://www.tiktok.com/.tv

Kilabni Madiin Itiyoophiyaa galii birrii miiliyoona 40 ol argate.Prime media(Finfinnee)_Adooleessa 23,2017Hoggantoonni P...
30/07/2025

Kilabni Madiin Itiyoophiyaa galii birrii miiliyoona 40 ol argate.

Prime media(Finfinnee)_Adooleessa 23,2017

Hoggantoonni Piriimiyeerliigii Itiyoophiyaa qoodiinsa maallaqa kilabootaa kan waggaa bara dorgommii 2017 ifa godhan.

Kana hordofuun shaampiyoonii bara kanaa kan ta'e Madiin birrii miil.40,295987.24 argachuun isaa ibsameera.

Bunni Itiyoophiyaa ammoo miiliyoona 37.70 ,Baahirdaar miiliyoona 33.02 argatanii jiru.

Sadarkaa xumuraan kan xumure Bunni Sidaamaa ammoo qarshii miiliyoona 19.47 argachuu danda'eera.

Kilaboota Tigiraayiin alatti kilaboonni 15 maallaqa hanga miiliyoona 409 ol addaan qooddataniiru.

Amaanu'eel Margaa

Social Media Links

Youtube➡️: https://www.youtube.com/c/PrimeMediaPM

FB AfaanOromoo ➡️ https://www.facebook.com/PrimeMediaPM/

FB Amharic➡️ https://web.facebook.com/PrimeMediaAm/

FBPrimesport ➡️ https://web.facebook.com/primesportet/

FB English ➡️ https://www.facebook.com/profile.php?id=61576239091981

Telegram Afaan Oromoo➡️: http://t.me/PrimeMediapm

Telegram Amharic➡️ https://t.me/primediaAm

Telegram Prime Sport➡️ https://t.me/primediasport

Tiktok➡️ https://www.tiktok.com/.tv

ኢትዮጵያ መድን ከ40 ሚልዮን ብር በላይ ገቢ አገኘ ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_ሐምሌ 23/2017 ዓ.ም የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ክለቦች የ2017 የውድድር ዘመን ዓመታዊ የገንዘብ ክፍፍልን...
30/07/2025

ኢትዮጵያ መድን ከ40 ሚልዮን ብር በላይ ገቢ አገኘ

ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_ሐምሌ 23/2017 ዓ.ም

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ክለቦች የ2017 የውድድር ዘመን ዓመታዊ የገንዘብ ክፍፍልን የፕሪሚየር ሊጉ አስተዳደር ይፋ አድርጓል።

በዚህም የሊጉ ሻምፒዮን ኢትዮጵያ መድን 40,295,987.24 ብር ገቢ ማግኘቱ ተገልጿል።

ተከታዩ ኢትዮጵያ ቡና 37.70 ሚልዮን ብር ፣ ባህርዳር ከተማ 35.28 ሚልዮን ብር ፣ አርባምንጭ ከተማ 33.02 ሚልዮን ብር ገቢ አግኝተዋል።

የመጨረሻውን ደረጃ የያዘው ሲዳማ ቡና 19.47 ሚልዮን ብር ገቢ አግኘቷል።

ከትግራይ ክለቦች ውጪ ያሉ 15 የፕሪሚየር ሊጉ ተሳታፊ ክለቦች የተከፋፈሉት አጠቃላይ የገንዘብ መጠን ከ409 ሚልዮን ብር በላይ ሆኗል።

ሀብታሙ ምትኩ

Social Media Links

Youtube➡️: https://www.youtube.com/c/PrimeMediaPM

FB AfaanOromoo ➡️ https://www.facebook.com/PrimeMediaPM/

FB Primesport ➡️ https://web.facebook.com/primesportet/

FB English ➡️ https://www.facebook.com/profile.php?id=61576239091981

Telegram Afaan Oromoo➡️: http://t.me/PrimeMedia

Tiktok➡️ https://www.tiktok.com/.tv

Liivarpuul Tapha Yookoohaamaa waliin taasise injifate.Prime media (Finfinnee)_Adoolessa 23,2017Liivarpuul tapha michooma...
30/07/2025

Liivarpuul Tapha Yookoohaamaa waliin taasise injifate.

Prime media (Finfinnee)_Adoolessa 23,2017

Liivarpuul tapha michoomaa garee Yookoohaamaa waliin taasise galchii 3fi 1'n injifachuuf danda'e.

Galchii injifannoo Liivarpuul kan lakkoofsisan ammoo ganna kana jijjiirraadhan gara kilaba kanaatti kan dhufa Wiirz galchii tokko yoo lakkoofsisu,Tireey Niinyoon fi Riyoon galchii tokko tokko lakkofsisaniiru.

Galchii moo’amuu jalaa isaan hin baraarre Yookoohaamaaf kan lakkoofsise immoo Yuuneekaatu dha.

Amaanu'eel Margaa.
Social Media Links
Youtube➡️: https://www.youtube.com/c/PrimeMediaPM
Fb Amharic➡️ https://web.facebook.com/PrimeMediaAm/ FB Primesport ➡️ https://web.facebook.com/primesportet/
Telegram Amharic➡️ https://t.me/primediaAm
Telegram Prime Sport➡️ https://t.me/primediasport
Tiktok➡️ https://www.tiktok.com/.tv

ፎሎሪያን ዊርዝ ግብ ባስቆጠረበት ጨዋታ ሊቨርፑል አሸንፏል ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_ሐምሌ 23/2017 ዓ.ም ሊቨርፑል የቅደመ ውድድር ዘመን ዝግጅት ሶስት የአቋም መለኪያ ጨዋታውን አድርጎ...
30/07/2025

ፎሎሪያን ዊርዝ ግብ ባስቆጠረበት ጨዋታ ሊቨርፑል አሸንፏል

ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_ሐምሌ 23/2017 ዓ.ም

ሊቨርፑል የቅደመ ውድድር ዘመን ዝግጅት ሶስት የአቋም መለኪያ ጨዋታውን አድርጎ 3 ለ 1 አሸንፏል።

የጃፓኑን ዮኮሀማ ገጥሞ ላሸነፈው ሊቨርፑል ፍሎሪያን ዊርዝ ፣ ትሬይ ንዮኒ እና ርዮ ጉሞሀ ግቦቹን አስቆጥረዋል።

ለጃፓኑ ክለቡ አሳሂ ዩኤናካ ብቸኛውን ግብ ከመረብ አሳርፏል።

ሊቨርፑል ቀጣይ የአቋም መለኪያ ጨዋታውን ከአትሌቲኮ ቢልባኦ ጋር በመጪው ሰኞ ያደርጋል።

ሀብታሙ ምትኩ

Social Media Links

Youtube➡️: https://www.youtube.com/c/PrimeMediaPM

FB AfaanOromoo ➡️ https://www.facebook.com/PrimeMediaPM/

FB Primesport ➡️ https://web.facebook.com/primesportet/

FB English ➡️ https://www.facebook.com/profile.php?id=61576239091981

Telegram Afaan Oromoo➡️: http://t.me/PrimeMedia

Tiktok➡️ https://www.tiktok.com/.tv

ግራኒት ዣካ ሰንደርላንድን መቀላቀሉ ይፋ ሆነ ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_ሐምሌ 23/2017 ዓ.ም ከዓመታት በኋላ ወደ ፕሪሚየር ሊጉ የተመለሰው ሰንደርላንድ ግራኒት ዣካን ከባየር ሊቨርኩሰን...
30/07/2025

ግራኒት ዣካ ሰንደርላንድን መቀላቀሉ ይፋ ሆነ

ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_ሐምሌ 23/2017 ዓ.ም

ከዓመታት በኋላ ወደ ፕሪሚየር ሊጉ የተመለሰው ሰንደርላንድ ግራኒት ዣካን ከባየር ሊቨርኩሰን ማስፈረሙን አሳውቋል።

ሰንደርላንድ ስዊዘርላንዳዊውን ተጫዋች በመነሻ 13 ሚልዮን ፓውንድ እና እስከ 17 ሚልዮን ፓውንድ በሚደርስ ውል የግሉ አድርጎታል።

የ32 ዓመቱ ተጫዋች በስታድየም ኦፍ ላይት ለቀጣይ ሶስት አመታት ለመቆየት የሚያስችለውን ውልም ፈርሟል።

ግራኒት ዣካ በክረምቱ የሰንደርላንድ ሰባተኛ ፈራሚ ሲሆን ክለቡ በዝውውር መስኮቱ እስካሁን 114 ሚልዮን ፓውንድ ወጪ አድርጓል።

ሀብታሙ ምትኩ

Social Media Links

Youtube➡️: https://www.youtube.com/c/PrimeMediaPM

FB AfaanOromoo ➡️ https://www.facebook.com/PrimeMediaPM/

FB Primesport ➡️ https://web.facebook.com/primesportet/

FB English ➡️ https://www.facebook.com/profile.php?id=61576239091981

Telegram Afaan Oromoo➡️: http://t.me/PrimeMedia

Tiktok➡️ https://www.tiktok.com/.tv

ባየር ሙኒክ ሉይስ ድያዝን ማስፈረሙን ይፋ አደረገ ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_ሐምሌ 23/2017 ዓ.ም ባየር ሙኒክ ሉይስ ድያዝን ከሊቨርፑል ማስፈረሙን ይፋ አድርጓል። የጀርመኑ ክለብ ለኮሎ...
30/07/2025

ባየር ሙኒክ ሉይስ ድያዝን ማስፈረሙን ይፋ አደረገ

ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_ሐምሌ 23/2017 ዓ.ም

ባየር ሙኒክ ሉይስ ድያዝን ከሊቨርፑል ማስፈረሙን ይፋ አድርጓል።

የጀርመኑ ክለብ ለኮሎምቢያዊው ተጫዋች ዝውውር እስከ 65 ሚልዮን ፓውንድ ይከፍላል ተብሎ ይጠበቃል።

የ28 ዓመቱ ተጫዋች በአልያንዝ አሬና ለአራት ዓመታት የሚያቆየውን ውልም በይፋ ፈርሟል።

ሉይስ ድያዝ በሊቨርፑል የሶስት አመት ተኩል ቆይታው 143 ጨዋታዎች አድርጎ 41 ግቦችን አስቆጥሯል።

ሀብታሙ ምትኩ

Social Media Links

Youtube➡️: https://www.youtube.com/c/PrimeMediaPM

FB AfaanOromoo ➡️ https://www.facebook.com/PrimeMediaPM/

FB Primesport ➡️ https://web.facebook.com/primesportet/

FB English ➡️ https://www.facebook.com/profile.php?id=61576239091981

Telegram Afaan Oromoo➡️: http://t.me/PrimeMedia

Tiktok➡️ https://www.tiktok.com/.tv

ጆአ ፌሊክስ አል ናስርን ተቀላቀለ ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_ሐምሌ 22/2017 ዓ.ም ፖርቹጋላዊው ጆአ ፌሊክስ የሳዑዲ አረቢያው አል ናስርን መቀላቀሉ ይፋ ሆኗል። ለተጫዋቹ ዝውውር አል ና...
29/07/2025

ጆአ ፌሊክስ አል ናስርን ተቀላቀለ

ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_ሐምሌ 22/2017 ዓ.ም

ፖርቹጋላዊው ጆአ ፌሊክስ የሳዑዲ አረቢያው አል ናስርን መቀላቀሉ ይፋ ሆኗል።

ለተጫዋቹ ዝውውር አል ናስር እስከ 43.7 ሚልዮን ፓውንድ የሚደርስ ገንዝብ ይከፍላል።

26.2 ሚልዮን ፓውንዱ በቀጥታ የሚከፈል ሲሆን 17.5 ሚልዮን ፓውንዱ ደግሞ እንደ ተጫዋቹ ብቃት ታይቶ የሚከፈል ነው።

ጆአ ፌሊክስ ባለፈው የውድድር ዘመን በሁሉም ውድድሮች 20 ጨዋታዎች አድርጎ ሰባት ግቦችን አስቆጥሯል።

ሀብታሙ ምትኩ

Social Media Links

Youtube➡️: https://www.youtube.com/c/PrimeMediaPM

FB AfaanOromoo ➡️ https://www.facebook.com/PrimeMediaPM/

FB Primesport ➡️ https://web.facebook.com/primesportet/

FB English ➡️ https://www.facebook.com/profile.php?id=61576239091981

Telegram Afaan Oromoo➡️: http://t.me/PrimeMedia

Tiktok➡️ https://www.tiktok.com/.tv

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Prime Sport ET posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share