26/10/2025
አርሰናል ድል ሲቀናው ማንችስተር ሲቲ ተሸንፏል
ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_ጥቅምት 16/2018 ዓ.ም
የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የዘጠነኛ ሳምንት አራት ጨዋታዎች ከ11:00 ጀምሮ ተደርገው ተጠናቀዋል።
ኢምሬትስ ላይ ክሪስታል ፓላስን ያስተናገደው አርሰናል 1 ለ 0 አሸንፏል።
ጎሉን የቀድሞው የክሪስታል ፓላስ ተጫዋች ኤቤሬቺ ኤዜ በ39ኛው ደቂቃ ላይ አስቆጥሯል።
ቪላ ፓርክ ላይ በተደረገው ጨዋታ ደግሞ አስቶንቪላ ማንችስተር ሲቲን 1 ለ 0 ረቷል።
ማቲ ካሽ በ19ኛው ደቂቃ ላይ የአስቶንቪላን ግብ ያስቆጠረው ተጫዋች ነው።
በሌሎች ጨዋታዎች በርንማውዝ ኖቲንግሃም ፎረስትን 2 ለ 0 ሲረታ በርንሌይ ወልቭስን 3 ለ 2 አሸንፏል።
ሀብታሙ ምትኩ