Prime Sport ET

Prime Sport ET Prime Media is an East African regional media organization that aims to educate, entertain, &inspire

አሰልጣኝ መሳይ ተፈሪ ለ20 ተጫዋቾች ጥሪ አደረጉ ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_መስከረም 16/2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ መሳይ ተፈሪ ለ2026 የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ...
26/09/2025

አሰልጣኝ መሳይ ተፈሪ ለ20 ተጫዋቾች ጥሪ አደረጉ

ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_መስከረም 16/2018 ዓ.ም

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ መሳይ ተፈሪ ለ2026 የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ የመጨረሻ ሁለት ጨዋታዎች ለተጫዋቾች ጥሪ አድርገዋል።

አሰልጣኙ ለ20 ተጫዋቾች ጥሪ ያደረጉ ሲሆም በመጪው ዕሁድ መስከረም 18 ወደ ሆቴል እንዲገቡ ጥሪ ተደርጎላቸዋል።

በግብ ጠባቂነት አቡበከር ኑራ እና ቢንያም ገነቱ ፤ በተከላካይ ቦታ ያሬድ ካሳዬ ፣ አህመድ ረሺድ ፣ ዋንጫ ቱት ፣ ኬኔዲ ከበደ ፣ ራምኬል ጀምስ ፣ ንጋቱ ገብረስላሴ እና በረከት ካሌብ ተካተዋል።

በአማካይ ቦታ ሀብታሙ ተከስተ ፣ በረከት ወልዴ፣ ሀይደር ሸረፋ ፣ ወገኔ ገዛኸኝ ፣ ቢንያም አይተን እና ይታገሱ ታሪኩ ተመርጠዋል።

በአጥቂ ስፍራ ቸርነት ጉግሳ ፣ በረከት ደስታ ፣ ኪቲካ ጀማ ፣ አህመድ ረሺድ እና መሐመድ አበራ ጥሪ የተደረገላቸው ተጫዋቾች ናቸው።

ብሔራዊ ቡድኑ ሁለቱን ጨዋታዎች ከጊኒ ቢሳው እና ከቡርኪናፋሶ አቻዎቹ ጋር ያደርጋል።

ሀብታሙ ምትኩ

Social Media Links

Youtube➡️: https://www.youtube.com/c/PrimeMediaPM

FB AfaanOromoo ➡️ https://www.facebook.com/PrimeMediaPM/

FB Primesport ➡️ https://web.facebook.com/primesportet/

FB English ➡️ https://www.facebook.com/profile.php?id=61576239091981

Telegram Afaan Oromoo➡️: http://t.me/PrimeMedia

Tiktok➡️ https://www.tiktok.com/.tv

ትልቁ ደርቢ በሊጉ የመጀመሪያ ሳምንት ይደረጋል ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_መስከረም 15/2018 ዓ.ም የ2018 ዓመተ ምህረት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐግብር ይፋ ሆኗል። በ20 ክለቦች...
25/09/2025

ትልቁ ደርቢ በሊጉ የመጀመሪያ ሳምንት ይደረጋል

ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_መስከረም 15/2018 ዓ.ም

የ2018 ዓመተ ምህረት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐግብር ይፋ ሆኗል።

በ20 ክለቦች መካከል ለሚደረገው ሊጉ የዕጣ ማውጣት ስነ ስርዓት በዛሬው ዕለት ተካሂዷል።

ሊጉ በአራት ከተሞች ላይ የሚደረግ ሲሆን እነሱም አዲስ አበባ ፣ አዳማ ፣ ሀዋሳ እና ድሬዳዋ ናቸው።

ሀያዎቹ ክለቦች በሁለት ምድብ የተከፈሉ ሲሆን በተለያዩ ሁለት ከተሞች ላይ በየምድባቸው ጨዋታዎችን ያደርጋሉ።

የሊጉ የመጀመሪያ ሳምንት መርሐግብር

ምድብ አንድ
ወልዋሎ አዲግራት ከ ሲዳማ ቡና
ፋሲል ከነማ ከ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
ስሁል ሽረ ከ መቀሌ 70 እንደርታ
መቻል ከ ወላይታ ድቻ
ድሬዳዋ ከተማ ከ ሀዋሳ ከተማ

ምድብ ሁለት
ኢትዮጵያ ቡና ከ ቅዱስ ጊዮርጊስ
ነገሌ አርሲ ከ አርባምንጭ ከተማ
ባህርዳር ከተማ ከ ሀድያ ሆሳዕና
ኢትዮ ኤሌክትሪክ ከ ሸገር ከተማ
አዳማ ከተማ ከ ኢትዮጵያ መድን

የ2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጥቅምት 08/2018 ዓ.ም እንደሚጀምር ይታወቃል።

ሀብታሙ ምትኩ

Social Media Links

Youtube➡️: https://www.youtube.com/c/PrimeMediaPM

FB AfaanOromoo ➡️ https://www.facebook.com/PrimeMediaPM/

FB Primesport ➡️ https://web.facebook.com/primesportet/

FB English ➡️ https://www.facebook.com/profile.php?id=61576239091981

Telegram Afaan Oromoo➡️: http://t.me/PrimeMedia

Tiktok➡️ https://www.tiktok.com/.tv

በካራባኦ ዋንጫ አርሰናል እና ማንችስተር ሲቲ ወደ አራተኛ ዙር አልፈዋል ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_መስከረም 15/2018 ዓ.ም በካራባኦ ዋንጫ የሶስተኛ ዙር ጨዋታዎች አርሰናል እና ማንችስ...
25/09/2025

በካራባኦ ዋንጫ አርሰናል እና ማንችስተር ሲቲ ወደ አራተኛ ዙር አልፈዋል

ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_መስከረም 15/2018 ዓ.ም

በካራባኦ ዋንጫ የሶስተኛ ዙር ጨዋታዎች አርሰናል እና ማንችስተር ሲቲ ተጋጣሚዎቻቸውን በተመሳሳይ ውጤት ረተዋል።

ፖርት ቬልን የገጠመው አርሰናል 2 ለ 0 ሲያሸንፍ ኤቤሬቺ ኤዜ እና ሊያንድሮ ትሮሳርድ ግቦቹን ከመረብ አሳርፈዋል።

ኸደርስፊልድን የገጠመው ማንችስተር ሲቲም በተመሳሳይ ውጤት ሲያሸንፍ ፊል ፎደን እና ሳቪንሆ ግቦቹን አስቆጥረዋል።

በተያዘው የአራተኛ ዙር ድልድሎች ይፋ ሲሆኑ አርሰናል ከብራይተን ፤ ማንችስተር ሲቲ ከስዋንሲ ሲቲ ፤ ኒውካስትል ዩናይትድ ከቶተንሀም ሆትስፐርስ ፤ ሊቨርፑል ከክሪስታል ፓላስ እንዲ ቼልሲ ከወልቭስ ተመድበዋል።

ሀብታሙ ምትኩ

Social Media Links

Youtube➡️: https://www.youtube.com/c/PrimeMediaPM

FB AfaanOromoo ➡️ https://www.facebook.com/PrimeMediaPM/

FB Primesport ➡️ https://web.facebook.com/primesportet/

FB English ➡️ https://www.facebook.com/profile.php?id=61576239091981

Telegram Afaan Oromoo➡️: http://t.me/PrimeMedia

Tiktok➡️ https://www.tiktok.com/.tv

24/09/2025

ዛሬ ከአመሻሽ 12:00 ጀምሮ ይጠብቁን | Prime Sport

ሪያል ማድሪድ የ100% የማሸነፍ ጉዞውን አስቀጥሏል ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_መስከረም 14/2018 ዓ.ም የስፔን ላሊጋ የስድስተኛ ሳምንት ጨዋታዎች ትናንት ምሽት ላይ መደረግ ጀምረዋል። ...
24/09/2025

ሪያል ማድሪድ የ100% የማሸነፍ ጉዞውን አስቀጥሏል

ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_መስከረም 14/2018 ዓ.ም

የስፔን ላሊጋ የስድስተኛ ሳምንት ጨዋታዎች ትናንት ምሽት ላይ መደረግ ጀምረዋል።

ወደ ሲዩቲት ዴ ቫሌንስያ ስታድየም አቅንቶ ሌቫንቴን የገጠመው ሪያል ማድሪድ 4 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፏል።

ኪልያን ምባፔ ሁለቱን ግቦች ሲያስቆጥር ማስታንቱኦኖ እና ቪኒሲየስ ጁንየር ቀሪዎቹን ግቦች ከመረብ አሳርፈዋል።

ኢታ ኢዮንግ የሌቫንቴን ብቸኛ ግብ ያስቆጠረው ተጫዋች ነው።

በሌሎች ጨዋታዎች ቪያርያል ሲቪያን 2 ለ 1 ሲረታ ፣ አትሌቲኮ ቢልባኦ ከጂሮና 1 ለ 1 እንዲሁም እስፓኞል ከቫሌንሽያ 2 ለ 2 ተለያይተዋል።

የሳምንቱ ጨዋታዎች ዛሬ ምሸትም ቀጥለው ሲደረጉ አትሌቲኮ ማድሪድ ከራዮ ቫዬካኖ ፣ ሄታፌ ከአላቬስ እንዲሁም ሪያል ሶሴዳድ ከማዮርካ ይጫወታሉ።

ሪያል ማድሪድ የደረጃ ሰንጠረዡን በ18 ነጥቦች ሲመራ ቀሪ ጨዋታ ያለው ባርሴሎና በ13 ነጥቦች የሁለተኛ ደረጃን ይዟል።

ሀብታሙ ምትኩ

Social Media Links

Youtube➡️: https://www.youtube.com/c/PrimeMediaPM

FB AfaanOromoo ➡️ https://www.facebook.com/PrimeMediaPM/

FB Primesport ➡️ https://web.facebook.com/primesportet/

FB English ➡️ https://www.facebook.com/profile.php?id=61576239091981

Telegram Afaan Oromoo➡️: http://t.me/PrimeMedia

Tiktok➡️ https://www.tiktok.com/.tv

በካራባኦ ዋንጫ ሊቨርፑል እና ቼልሲ ወደ ቀጣዩ ዙር አለፉ ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_መስከረም 14/2018 ዓ.ም የካራባኦ ዋንጫ ሶስተኛ ዙር ሁለት ጨዋታዎች ትናንት ምሽት ላይ ተካሂደዋል።...
24/09/2025

በካራባኦ ዋንጫ ሊቨርፑል እና ቼልሲ ወደ ቀጣዩ ዙር አለፉ

ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_መስከረም 14/2018 ዓ.ም

የካራባኦ ዋንጫ ሶስተኛ ዙር ሁለት ጨዋታዎች ትናንት ምሽት ላይ ተካሂደዋል።

አንፊልድ ላይ ሳውዝሀምፕሀንን ያስተናገደው ሊቨርፑል በአሌክሳንደር አይዛክ እና ሁጎ ኤኪቲኬ ግቦች 2 ለ 1 አሸንፏል።

የሳውዝሀምፕተንን ብቸኛ ግብ ሼ ቻርለስ አስቆጥሯል።

ከሜዳው ውጪ ሊንኮንን የገጠመው ቼልሲ በበኩሉ በተመሳሳይ 2 ለ 1 ረቷል።

ፋኩንዶ ቦናናቴ እና ቲሪክ ጆርጅ የቼልሲን ሮበርት ስትሪት ደግሞ የሊንኮልን ግቦች ያስቆጠሩ ተጫዋቾች ናቸው።

ጨዋታዎቹ ዛሬ ምሽትም ቀጥለው ሲደረጉ ኸድረስፊልድ ከማንችስተር ሲቲ እንዲሁም ፖርት ቬል ከአርሰናል ይጫወታሉ።

ሀብታሙ ምትኩ

Social Media Links

Youtube➡️: https://www.youtube.com/c/PrimeMediaPM

FB AfaanOromoo ➡️ https://www.facebook.com/PrimeMediaPM/

FB Primesport ➡️ https://web.facebook.com/primesportet/

FB English ➡️ https://www.facebook.com/profile.php?id=61576239091981

Telegram Afaan Oromoo➡️: http://t.me/PrimeMedia

Tiktok➡️ https://www.tiktok.com/.tv

ኦስማን ዴምበሌ - የ2025 የባሎን ዶር አሸናፊ ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_መስከረም 13/2018 ዓ.ም የፒኤስጂው ተጫዋች ኦስማን ዴምበሌ የ2025 የባሎን ዶር አሸናፊ ሆኗል። በ2024/2...
23/09/2025

ኦስማን ዴምበሌ - የ2025 የባሎን ዶር አሸናፊ

ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_መስከረም 13/2018 ዓ.ም

የፒኤስጂው ተጫዋች ኦስማን ዴምበሌ የ2025 የባሎን ዶር አሸናፊ ሆኗል።

በ2024/25 የውድድር ዘመን ከክለቡ ፒኤስጂ ጋር ስኬታማ ጊዜን ያሳለፈው ተጫዋቹ አስቀድሞም በብዙዎች የአሸናፊነት ቅድመ ግምትን አግኝቶ ነበር።

ዴምበሌ በውድድር ዘመኑ በሁሉም ውድድሮች 35 ግቦችን ሲያስቆጥር 14 ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን አመቻችቶ አቀብሏል።

ከክለቡ ፒኤስጂ ጋር የቻምፒየንስ ሊግን ጨምሮ የሀገር ውስጥ ውድድሮችን አሸናፊ መሆኑ ይታወሳል።

ተጫዋቹ ባሎን ዶርን ያሸነፈ ስድስተኛው ፈረንሳያዊ መሆንም ችሏል።

በተጨማሪም ላሚን ያማል 2ኛ ፣ ቪቲንሀ 3ኛ ፣ መሐመድ ሳላህ 4ኛ እንዲሁም ራፊንሀ የ5ኛ ደረጃን ይዘዋል።

ሀብታሙ ምትኩ

Social Media Links

Youtube➡️: https://www.youtube.com/c/PrimeMediaPM

FB AfaanOromoo ➡️ https://www.facebook.com/PrimeMediaPM/

FB Primesport ➡️ https://web.facebook.com/primesportet/

FB English ➡️ https://www.facebook.com/profile.php?id=61576239091981

Telegram Afaan Oromoo➡️: http://t.me/PrimeMedia

Tiktok➡️ https://www.tiktok.com/.tv

አርሰናል በተጨማሪ ደቂቃ ግብ ነጥብ ተጋርቷል ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_መስከረም 11/2018 ዓ.ም በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የአምስተኛ ሳምንት ተጠባቂ መርሐግብር አርሰናል እና ማንችስተር...
21/09/2025

አርሰናል በተጨማሪ ደቂቃ ግብ ነጥብ ተጋርቷል

ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_መስከረም 11/2018 ዓ.ም

በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የአምስተኛ ሳምንት ተጠባቂ መርሐግብር አርሰናል እና ማንችስተር ሲቲ 1 ለ 1 ተለያይተዋል።

በጨዋታው ኤርሊንግ ሀላንድ በዘጠነኛው ደቂቃ ላይ ያስቆጠረው ግብ ማንችስተር ሲቲን እስከ 92ኛ ደቂቃ ድረስ መሪ አድርጎ ነበር።

ነገር ግን በ90+3 ደቂቃ ላይ ተቀይሮ የገባው ማርቲኔሉ ያስቆጠረው ግብ መድፈኞቹ ከጨዋታው አንድ ነጥብ ይዘው እንዲወጡ አስችሏል።

ሀብታሙ ምትኩ

Social Media Links

Youtube➡️: https://www.youtube.com/c/PrimeMediaPM

FB AfaanOromoo ➡️ https://www.facebook.com/PrimeMediaPM/

FB Primesport ➡️ https://web.facebook.com/primesportet/

FB English ➡️ https://www.facebook.com/profile.php?id=61576239091981

Telegram Afaan Oromoo➡️: http://t.me/PrimeMedia

Tiktok➡️ https://www.tiktok.com/.tv

የሴቶች ከ20 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን አቻ ተለያየ ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_መስከረም 11/2018 ዓ.ም በፖላንድ ለሚደረገው የሴቶች ከ20 ዓመት በታች የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ቀዳሚ ጨዋ...
21/09/2025

የሴቶች ከ20 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን አቻ ተለያየ

ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_መስከረም 11/2018 ዓ.ም

በፖላንድ ለሚደረገው የሴቶች ከ20 ዓመት በታች የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ቀዳሚ ጨዋታውን ያደረገው የኢትዮጵያ ሴቶች ከ20 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን አቻ ተለያይቷል።

በአበበ ቢቂላ ስታድየም ላይ የኬንያ አቻው የገጠመው ቡድኑ ጨዋታውን 1 ለ 1 አጠናቋል።

ጨዋታው ገና አንድ ደቂቃ ሳይሞላው ኬንያዎች ቀዳሚ መሆን ቢችሉም የእሙሽ ዳንኤል የ66ኛ ደቂቃ ግብ ኢትዮጵያን አቻ አድርጓል።

የመልሱ ጨዋታ በኬንያ ናይሮቢ ላይ የፊታችን መስከረም 18 ይደረጋል።

ሀብታሙ ምትኩ

Social Media Links

Youtube➡️: https://www.youtube.com/c/PrimeMediaPM

FB AfaanOromoo ➡️ https://www.facebook.com/PrimeMediaPM/

FB Primesport ➡️ https://web.facebook.com/primesportet/

FB English ➡️ https://www.facebook.com/profile.php?id=61576239091981

Telegram Afaan Oromoo➡️: http://t.me/PrimeMedia

Tiktok➡️ https://www.tiktok.com/.tv

ኢትዮጵያ ከ32 ዓመታት በኋላ የዓለም ሻምፒዮናን ያለ ወርቅ ሜዳልያ አጠናቀቀች ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_መስከረም 11/2018 ዓ.ም በ20ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያ የምትሳ...
21/09/2025

ኢትዮጵያ ከ32 ዓመታት በኋላ የዓለም ሻምፒዮናን ያለ ወርቅ ሜዳልያ አጠናቀቀች

ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_መስከረም 11/2018 ዓ.ም

በ20ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያ የምትሳተፍበት የመጨረሻው የወንዶች 5 ሺህ ሜትር ውድድር ተካሂዷል።

በውድድሩ አትሌት ቢንያም መሐሪ የአምስተኛ አትሌት ሐጎስ ገብረሕይወት ደግሞ የ13ኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቀዋል።

በዚህም ኢትዮጵያ በቶክዮ በተደረገው 20ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና አንድም የወርቅ ሜዳልያ ሳታስመዘግብ አጠናቃለች።

ይህም በጀርመን ስቱትጋርት ከተደረገው አራተኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በኋላ ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ አንድም የወርቅ ሜዳልያ ሳታስመዘግብ ሻምፒዮናውን ፈፅማለች።

በሻምፒዮናው ኢትዮጵያ ሁለት የብር እና ሁለት የነሐስ በድምር አራት ሜዳልያዎችን በመያዝ አጠናቃለች።

ሀብታሙ ምትኩ

Social Media Links

Youtube➡️: https://www.youtube.com/c/PrimeMediaPM

FB AfaanOromoo ➡️ https://www.facebook.com/PrimeMediaPM/

FB Primesport ➡️ https://web.facebook.com/primesportet/

FB English ➡️ https://www.facebook.com/profile.php?id=61576239091981

Telegram Afaan Oromoo➡️: http://t.me/PrimeMedia

Tiktok➡️ https://www.tiktok.com/.tv

በሻምፒዮናው የፍፃሜ ዕለት ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች በወንዶች 5 ሺህ ሜትር ይሳተፋሉ ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_መስከረም 11/2018 ዓ.ም 20ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በዛሬው ዕለት...
21/09/2025

በሻምፒዮናው የፍፃሜ ዕለት ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች በወንዶች 5 ሺህ ሜትር ይሳተፋሉ

ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_መስከረም 11/2018 ዓ.ም

20ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በዛሬው ዕለት ፍፃሜውን የሚያገኝ ሲሆን 11 የፍፃሜ ውድድሮች ከ5:35 ጀምሮ ይካሄዳሉ።

ከውድድሮቹ መካከልም የወንዶች 5 ሺህ ሜትር ከቀን 7:47 ጀምሮ ሲደረግ አትሌት ሀጎስ ገብረሕይወት እና አትሌት ቢንያም መሐሪ ኢትዮጵያን ወክለው ይወዳደራሉ።

አትሌት ሀጎስ ገብረሕይወት በ2013 እና በ2015 የዓለም ሻምፒዮናዎች ላይ የብር እና የነሐስ ሜዳልያዎችን አሳክቷል።

በውድድሩ የ10 ሺህ ሜትር አሸናፊዋ ጂሚ ግሬሰር ፣ ግራንት ፊሸር እና ጃኮብ ኢንገብሪስቴይን ብርቱ ተፎካካሪዎች ይሆናሉ ተብሎ ይጠበቃል።

በዓለም ሻምፒዮና ታሪክ ኢትዮጵያ ሶስት የወርቅ ሜዳልያዎችን ከዚህ ቀደም ያሳካች ሲሆን ሁለቱ በአትሌት ሙክታር ዕድሪስ እንዲሁም አንዱ በአትሌት ቀነኒሳ በቀለ የተገኘ ነው።

ሀብታሙ ምትኩ

Social Media Links

Youtube➡️: https://www.youtube.com/c/PrimeMediaPM

FB AfaanOromoo ➡️ https://www.facebook.com/PrimeMediaPM/

FB Primesport ➡️ https://web.facebook.com/primesportet/

FB English ➡️ https://www.facebook.com/profile.php?id=61576239091981

Telegram Afaan Oromoo➡️: http://t.me/PrimeMedia

Tiktok➡️ https://www.tiktok.com/.tv

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Prime Sport ET posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share