Prime Sport ET

Prime Sport ET Prime Media is an East African regional media organization that aims to educate, entertain, &inspire

የ15ኛው "ፋንታ ሚዲያ ካፕ" ውድድር የምድብ ድልድል ይፋ ሆነፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_ጥር 08/2018 ዓ.ምበዮ ስፖርት አዘጋጅነት በየዓመቱ የሚደረገው እና ዘንድሮ ለ15ኛ ጊዜ የሚካሄደ...
16/01/2026

የ15ኛው "ፋንታ ሚዲያ ካፕ" ውድድር የምድብ ድልድል ይፋ ሆነ

ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_ጥር 08/2018 ዓ.ም

በዮ ስፖርት አዘጋጅነት በየዓመቱ የሚደረገው እና ዘንድሮ ለ15ኛ ጊዜ የሚካሄደው የአዝናኙ ሲዝናና የሚዲያ ካፕ ውድድር የምድብ ድልድል ይፋ ተደርጓል።

"ፋንታ ሚዲያ ካፕ" የሚል ስያሜን ይዞ በሚደረገው ውድድር ላይ በአጠቃላይ 29 ቡድኖች በሰባት ምድቦች ይሳተፋሉ።

የውድድሩ ዋና አዘጋጅ አቶ አንዱአለም አስፋው ውድድሩ የሚዲያ ባለሙያዎች እንዲዝናኑ ከማድረግ ባለፈ በአንድ ቦታ ተገናኝተው የሚተዋወቁበት እና የስራ ልምድ የሚለዋወጡበት ስለመሆኑ ገልጿል።

በመድረኩ የክብር እንግዳ የነበሩት የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት አቶ ባህሩ ጥላሁን ውድድርን በተከታታይ ለ15 ዓመታት በወጥነት ማዘጋጀት ከባድ መሆኑን በመጥቀስ አዘጋጁን አመስግነዋል።

በምድብ ድልድሉም ሚዲያችን ፕራይም ሚዲያ በምድብ 2 ከሪፖርተር ጋዜጣ ፣ ከኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን እና ከሆፕ ቴሌቪዥን ጋር ተደልድሏል።

በምድብ 1 ፌዴራል ፖሊስ ሚዲያ ፣ላይፍ ኢዝ ጉድ ፣ ዳጉ ስፖርት እና 4-3-3 ስፖርት ፤ በምድብ 3 ፋና ቲቪ ፣ ዲጄዎች ማህበር ፣ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እና ኢሳት ተደልድለዋል።

በምድብ 4 አርትስ ቲቪ ፣ ኢዜአ ፣ አሃዱ ሬድዮ እና መናኸሪያ ሬድዮ እንዲሁም በምድብ 5 ኢቢሲ ፣ ቲክቶከሮች ፣ ሽርጉድ ኢንተርቴይመንት እና ቻናል ዋን ተመድበዋል።

በምድብ 6 አዲስ ሚዲያ ኔትወርክ ፣ አባይ ቲቪ ፣ ሞዛይክ ስፖርት ፣ ሀገሬ ቲቪ ፣ ንስር ስፖርት በምድብ 7 ደግሞ ኢቢኤስ ፣ ብስራት ኤፍ ኤም ፣ ሳይበርኛ እና አራዳ ኤፍ ኤም ተካተዋል።

ውድድሩ ከጥር 13 ጀምሮ እስከ የካቲት 08 ድረስ 22 አካባቢ በሚገኘው የፉትሳል ሜዳ ላይ የሚካሄድ ይሆናል።

ሻምፒዮን የሚሆነው ቡድን የ200 ሺህ ብር እና ዋንጫ ተሸላሚ ሲሆን 2ኛ 100 ሺህ ብር 3ኛ ደግሞ 50 ሺህ ብር ይሸለማሉ።

በአጠቃላይ ለውድድሩ ከ600 ሺህ ብር በላይ ለሽልማት መዘጋጀቱም በመድረኩ ተገልጿል።

ሀብታሙ ምትኩ

ሀዋሳ ከተማ ቅዱስ ጊዮርጊስን 1 ለ 0 አሸነፈፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_ጥር 01/2018 ዓ.ምበሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ14ኛ ሳምንት የሁለተኛ ዕለት ሶስት ጨዋታዎች አዲስ አበባ ...
09/01/2026

ሀዋሳ ከተማ ቅዱስ ጊዮርጊስን 1 ለ 0 አሸነፈ

ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_ጥር 01/2018 ዓ.ም

በሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ14ኛ ሳምንት የሁለተኛ ዕለት ሶስት ጨዋታዎች አዲስ አበባ እና አዳማ ላይ ተደርገዋል።

በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ ስታድየም ላይ ከቀን 09:00 ጀምሮ በተደረገው ጨዋታ ሀዋሳ ከተማ ቅዱስ ጊዮርጊስን 1 ለ 0 ረቷል።

የሀዋሳ ከተማን ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ ሽመልስ በቀለ በ46ኛው ደቂቃ ላይ አስቆጥሯል።

በተመሳሳይ ሰዓት አዲስ አበባ ስታድየም ላይ የተደረገው የድሬዳዋ ከተማ እና ኢትዮ ኤሌክትሪክ ጨዋታ ያለ ግብ አቻ ተጠናቋል።

ከአመሻሽ 12:00 ጀምር አዳማ ላይ የተደረገው የመቀሌ 70 እንደርታ እና ሸገር ከተማ ጨዋታ በተመሳሳይ ውጤት 0 ለ 0 ተጠናቋል።

ሀብታሙ ምትኩ

https://t.me/primediasport
https://t.me/primediasport
https://t.me/primediasport

አርሰናል የወሳኝ ተጫዋቹን ውል ለማራዘም ተስማማፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_ጥር 01/2018 ዓ.ምአርሰናል የቡካዮ ሳካን ውል በአዲስ መልክ ለማራዘም ከተጫዋቹ ጋር ከስምምነት ደርሷል።እስከ ...
09/01/2026

አርሰናል የወሳኝ ተጫዋቹን ውል ለማራዘም ተስማማ

ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_ጥር 01/2018 ዓ.ም

አርሰናል የቡካዮ ሳካን ውል በአዲስ መልክ ለማራዘም ከተጫዋቹ ጋር ከስምምነት ደርሷል።

እስከ 2027 በአርሰናል የሚያቆየው ውል ያለው ሳካ አዲሱ ውሉ እስከ 2031 ድረስ በኢምሬትስ የሚያቆየው መሆኑ ተዘግቧል።

ከሰባት ዓመቱ ጀምሮ በአርሰናል ቤት ያለው የ24 ዓመቱ ተጫዋች ፈላጊ ክለቦች ቢኖሩትም የእርሱ ተቀዳሚ ፍላጎት ግን በለንደኑ ክለብ መቆየት ሆኗል።

በውድድር ዘመኑ 27 ጨዋታዎችን ለክለቡ ያደረገው ሳካ 7 ግቦችንም ከመረብ አሳርፏል።

ሀብታሙ ምትኩ

https://t.me/primediasport
https://t.me/primediasport
https://t.me/primediasport

ማንችስተር ሲቲ አንቷን ሴሜንዮን በይፋ አስፈረመፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_ጥር 01/2018 ዓ.ምማንችስተር ሲቲ አንቷን ሴሜንዮን እስከ 65 ሚልዮን ፓውንድ በሚደርስ የዝውውር ዋጋ ከበርንማ...
09/01/2026

ማንችስተር ሲቲ አንቷን ሴሜንዮን በይፋ አስፈረመ

ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_ጥር 01/2018 ዓ.ም

ማንችስተር ሲቲ አንቷን ሴሜንዮን እስከ 65 ሚልዮን ፓውንድ በሚደርስ የዝውውር ዋጋ ከበርንማውዝ በይፋ አስፈርሟል።

ተጫዋቹ እስከ 2031 በኢትሀድ የሚያቆየውን ውል የፈረመ ሲሆን 42 ቁጥር ማልያን እንደሚለብስም ተረጋግጧል።

በርንማውዝ ተጫዋቹን የሸጠበት ዋጋ የክለቡ ከፍተኛ ሽያጭም ሆኖ ተመዝግቧል።

ማንችስተር ሲቲን በመቀላቀሌ ኩራት ተሰምቶኛል ያለው ጋናዊው ተጫዋች የብቃቱ ጣሪያ ላይ ገና እንዳልደረሰም ተናግሯል።

የ26 ዓመቱ ተጫዋች በወድድር ዓመቱ ለበርንማውዝ ባደረጋቸው 20 የሊግ ጨዋታዎች 10 አስቆጥሮ 3 ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን አመቻችቶ አቀብሏል።

ከሶስት ዓመታት በፊት ከብሪስቶል ሲቲ በ10 ሚልዮን ፓውንድ የዝውውር ዋጋ በርንማውዝን የተቀላቀለው ሴሜንዮ 110 ጨዋታዎች አድርጎ 32 ግቦችን አስቆጥሮ 31 ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን አመቻችቶ አቀብሏል።

ሀብታሙ ምትኩ

https://t.me/primediasport
https://t.me/primediasport
https://t.me/primediasport

አርሰናል እና ሊቨርፑል ነጥብ ተጋርተዋልፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_ታኅሳስ 30/2018 ዓ.ምበ21ኛው ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የመጨረሻ ጨዋታ አርሰናል እና ሊቨርፑል ኢምሬትስ ላይ ...
08/01/2026

አርሰናል እና ሊቨርፑል ነጥብ ተጋርተዋል

ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_ታኅሳስ 30/2018 ዓ.ም

በ21ኛው ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የመጨረሻ ጨዋታ አርሰናል እና ሊቨርፑል ኢምሬትስ ላይ ያደረጉት ጨዋታ ያለ ግብ ተጠናቋል።

መድፈኞቹ በጨዋታው ካደረጓቸው 8 የግብ ሙከራዎች መካከል 4 ኢላማቸውን የጠበቁ ቢሆኑም ኳስ እና መረብ የተገናኙባቸው ግን አልነበሩም።

በጨዋታው ሊቨርፑል የ52.4% የኳስ ቁጥጥር የበላይነት የነበረው ሲሆን በሙከራ ረገድ ግን አንድም ኢላማውን የጠበቀ ሙከራ አላደረጉም።

ውጤቱን ተከትሎ አርሰናል ነጥቡን 49 በማድረስ ከተከታዩ ማንችስተር ሲቲ ያለውን ልዩነት ወደ 6 አስፍቷል።

ሊቨርፑል በበኩሉ ነጥቡን 35 አድርሶ በነበረበት የ4ኛ ደረጃ ቀጥሏል።

ሀብታሙ ምትኩ

ሪያል ማድሪድ ለስፔን ሱፐር ካፕ የፍፃሜ ጨዋታ አለፈፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_ታኅሳስ 30/2018 ዓ.ምበስፔን ሱፐር ካፕ ሁለተኛ የግማሽ ፍፃሜ ጨዋታ ሪያል ማድሪድን ከአትሌቲኮ ማድሪድ አ...
08/01/2026

ሪያል ማድሪድ ለስፔን ሱፐር ካፕ የፍፃሜ ጨዋታ አለፈ

ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_ታኅሳስ 30/2018 ዓ.ም

በስፔን ሱፐር ካፕ ሁለተኛ የግማሽ ፍፃሜ ጨዋታ ሪያል ማድሪድን ከአትሌቲኮ ማድሪድ አገናኝቶ በነጮቹ የ2 ለ 1 አሸናፊነት ተጠናቋል።

በጨዋታው ሮድሪጎ እና ፌዴ ቫልቨርዴ የሪያል ማድሪድን ግቦች ሲያስቆጥሩ አሌክሳንደር ሶርሎዝ የአትሌቲኮ ማድሪድን ግብ አስቆጥሯል።

በመጪው ዕሁድ የሚደረገው የፍፃሜ ጨዋታ ሪያል ማድሪድ እና ባርሴሎናን በንጉስ አብደላህ ስፖርት ሲቲ ስታድየም ያገናኛል።

ሀብታሙ ምትኩ

መሪው ሲዳማ ቡና ነጥብ ሲጥል አዳማ ከተማ ሰባተኛ የአቻ ውጤትን አስመዝግቧልፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_ታኅሳስ 30/2018 ዓ.ምበሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ14ኛ ሳምንት ሁለተኛ እና...
08/01/2026

መሪው ሲዳማ ቡና ነጥብ ሲጥል አዳማ ከተማ ሰባተኛ የአቻ ውጤትን አስመዝግቧል

ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_ታኅሳስ 30/2018 ዓ.ም

በሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ14ኛ ሳምንት ሁለተኛ እና ሶስተኛ ጨዋታዎች ከ10:00 ጀምሮ አዳማ እና አዲስ አበባ ላይ ተደርገዋል።

በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ ስታድየም በተካሄደው ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና ከአርባምንጭ ከተማ 0 ለ 0 ተለያይቷል።

ውጤቱን ተከትሎ ሲዳማ ቡና ነጥቡን 26 ሲያደርስ አርባምንጭ ከተማ በበኩሉ ነጥቡን 8 አድርሷል።

በ15ኛው ሳምንት ሲዳማ ቡና ከአዳማ ከተማ እንዲሁም አርባምንጭ ከተማ ደግሞ ከመቻል ጋር ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።

በተመሳሳይ ሰዓት አዲስ አበባ ስታድየም ላይ በተደረገው ጨዋታ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ እና አዳማ ከተማ 1 ለ 1 ጨዋታቸውን አጠናቀዋል።

ኪሩቤል ወንድሙ ለወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ እንዲሁም ቢንያም አይተን ለአዳማ ከተማ ግቦቹን አስቆጥረዋል።

ውጤቱን ተከትሎ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ ነጥቡን 11 ሲያደርስ አዳማ ከተማ በበኩሉ 22 ነጥብ ላይ ደርሷል።

በቀጣይ ሳምንት በሚደረጉ ጨዋታዎች ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ ከኢትዮጵያ መድን እንዲሁም አዳማ ከተማ ከሲዳማ ቡና ይጫወታሉ።

ሀብታሙ ምትኩ

ነገሌ አርሲ ምድረ ገነት ሽረን አሸነፈፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_ታኅሳስ 30/2018 ዓ.ምበሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ14ኛ ሳምንት ቀዳሚ ጨዋታ ነገሌ አርሲ ምድረ ገነት ሽረን 1 ለ...
08/01/2026

ነገሌ አርሲ ምድረ ገነት ሽረን አሸነፈ

ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_ታኅሳስ 30/2018 ዓ.ም

በሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ14ኛ ሳምንት ቀዳሚ ጨዋታ ነገሌ አርሲ ምድረ ገነት ሽረን 1 ለ 0 አሸንፏል።

በአዲስ አበባ ስታድየም በተደረገው ጨዋታ ከቤ ብዙነህ በ12ኛው ደቂቃ ላይ የነገሌ አርሲን የማሸነፊያ ግብ አስቆጥሯል።

ነገሌ አርሲ ማሸነፉን ተከትሎ ነጥቡን 25 በማድረስ በጊዜያዊነት ደረጃውን ወደ 2ኛ ከፍ አድርጓል።

በ15ኛው ሳምንት ነገሌ አርሲ ከወላይታ ድቻ እንዲሁም ምድረ ገነት ሽረን ሀድያ ሆሳዕናን ይገጥማሉ።

ሀብታሙ ምትኩ

ኢንተር ሚላን መሪነቱን ሲያጠናክር ናፖሊ ነጥብ ጥሏልፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_ታኅሳስ 30/2018 ዓ.ምበጣልያን ሴሪ ኤ የ18ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ምሽቱን ቀጥለው ሲደረጉ ኢንተር ሚላን አሸ...
08/01/2026

ኢንተር ሚላን መሪነቱን ሲያጠናክር ናፖሊ ነጥብ ጥሏል

ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_ታኅሳስ 30/2018 ዓ.ም

በጣልያን ሴሪ ኤ የ18ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ምሽቱን ቀጥለው ሲደረጉ ኢንተር ሚላን አሸንፎ ናፖሊ ነጥብ ተጋርቷል።

ከሜዳው ውጪ ፓርማን የገጠመው ኢንተር ሚላን በፌዴሪኮ ዲማርኮ እና ማርከስ ቱራም ግቦች 2 ለ 0 አሸንፏል።

ውጤቱንም ተከትሎ ነጥቡን 41 በማድረስ ጨዋታውን ዛሬ ምሽት ከሚያደርገው ኤሲ ሚላን ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ 4 አስፍቷል።

ሄላስ ቬርናን ያስተናገደው ናፖሊ ሁለት አቻ ሲለያይ ማክቶሚናይ እና ዲ ሎሬንዞ ለናፖሊ እንዲሁም ማርቲን ፍሬስ እና ጊፍት ኦርባን ለቬሮና ግበቹን አስቆጥረዋል።

በሌሎች ጨዋታዎች አታላንታ ቦሎኛን 2 ለ 0 እንዲሁም ዩዲንዜ ቶሪኖን 2 ለ 1 ሲረቱ ላዝዮ እና ፍዮረንቲና 2 ለ 2 ተለያይተዋል።

ሀብታሙ ምትኩ

ባርሴሎና ለስፔን ሱፐር ካፕ የፍፃሜ ጨዋታ አለፈፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_ታኅሳስ 30/2018 ዓ.ምበስፔን ሱፐር ካፕ ቀዳሚ የግማሽ ፍፃሜ ጨዋታ የሀንስ ፍሊኩ ባርሴሎና ለፍፃሜው ፍልሚያ ማ...
08/01/2026

ባርሴሎና ለስፔን ሱፐር ካፕ የፍፃሜ ጨዋታ አለፈ

ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_ታኅሳስ 30/2018 ዓ.ም

በስፔን ሱፐር ካፕ ቀዳሚ የግማሽ ፍፃሜ ጨዋታ የሀንስ ፍሊኩ ባርሴሎና ለፍፃሜው ፍልሚያ ማለፉን አረጋግጧል።

በሳዑዲ አረቢያ ጅዳ ላይ በተደረገው ጨዋታ አትሌቲኮ ቢልባኦን የገጠመው ባርሴሎና 5 ለ 0 አሸንፏል።

በጨዋታው ራፊንሀ ሁለት ግቦች ሲያስቆጥር ሩኒ ባርግጂ ፣ ፌራን ቶሬዝ እና ፈርሚን ሎፔዝ ደግሞ አንድ አንድ ግቦችን አስቆጥረዋል።

ሁለተኛው የግማሽ ፍፃሜ ጨዋታ ዛሬ ምሽት በሁለቱ የማድሪድ ክለቦች መካከል ይደረጋል።

ሀብታሙ ምትኩ

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Prime Sport ET posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share