
26/09/2025
አሰልጣኝ መሳይ ተፈሪ ለ20 ተጫዋቾች ጥሪ አደረጉ
ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_መስከረም 16/2018 ዓ.ም
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ መሳይ ተፈሪ ለ2026 የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ የመጨረሻ ሁለት ጨዋታዎች ለተጫዋቾች ጥሪ አድርገዋል።
አሰልጣኙ ለ20 ተጫዋቾች ጥሪ ያደረጉ ሲሆም በመጪው ዕሁድ መስከረም 18 ወደ ሆቴል እንዲገቡ ጥሪ ተደርጎላቸዋል።
በግብ ጠባቂነት አቡበከር ኑራ እና ቢንያም ገነቱ ፤ በተከላካይ ቦታ ያሬድ ካሳዬ ፣ አህመድ ረሺድ ፣ ዋንጫ ቱት ፣ ኬኔዲ ከበደ ፣ ራምኬል ጀምስ ፣ ንጋቱ ገብረስላሴ እና በረከት ካሌብ ተካተዋል።
በአማካይ ቦታ ሀብታሙ ተከስተ ፣ በረከት ወልዴ፣ ሀይደር ሸረፋ ፣ ወገኔ ገዛኸኝ ፣ ቢንያም አይተን እና ይታገሱ ታሪኩ ተመርጠዋል።
በአጥቂ ስፍራ ቸርነት ጉግሳ ፣ በረከት ደስታ ፣ ኪቲካ ጀማ ፣ አህመድ ረሺድ እና መሐመድ አበራ ጥሪ የተደረገላቸው ተጫዋቾች ናቸው።
ብሔራዊ ቡድኑ ሁለቱን ጨዋታዎች ከጊኒ ቢሳው እና ከቡርኪናፋሶ አቻዎቹ ጋር ያደርጋል።
ሀብታሙ ምትኩ
Social Media Links
Youtube➡️: https://www.youtube.com/c/PrimeMediaPM
FB AfaanOromoo ➡️ https://www.facebook.com/PrimeMediaPM/
FB Primesport ➡️ https://web.facebook.com/primesportet/
FB English ➡️ https://www.facebook.com/profile.php?id=61576239091981
Telegram Afaan Oromoo➡️: http://t.me/PrimeMedia
Tiktok➡️ https://www.tiktok.com/.tv