Prime Sport ET

Prime Sport ET Prime Media is an East African regional media organization that aims to educate, entertain, &inspire

አርሰናል ድል ሲቀናው ማንችስተር ሲቲ ተሸንፏልፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_ጥቅምት 16/2018 ዓ.ምየእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የዘጠነኛ ሳምንት አራት ጨዋታዎች ከ11:00 ጀምሮ ተደርገው ተጠና...
26/10/2025

አርሰናል ድል ሲቀናው ማንችስተር ሲቲ ተሸንፏል

ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_ጥቅምት 16/2018 ዓ.ም

የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የዘጠነኛ ሳምንት አራት ጨዋታዎች ከ11:00 ጀምሮ ተደርገው ተጠናቀዋል።

ኢምሬትስ ላይ ክሪስታል ፓላስን ያስተናገደው አርሰናል 1 ለ 0 አሸንፏል።

ጎሉን የቀድሞው የክሪስታል ፓላስ ተጫዋች ኤቤሬቺ ኤዜ በ39ኛው ደቂቃ ላይ አስቆጥሯል።

ቪላ ፓርክ ላይ በተደረገው ጨዋታ ደግሞ አስቶንቪላ ማንችስተር ሲቲን 1 ለ 0 ረቷል።

ማቲ ካሽ በ19ኛው ደቂቃ ላይ የአስቶንቪላን ግብ ያስቆጠረው ተጫዋች ነው።

በሌሎች ጨዋታዎች በርንማውዝ ኖቲንግሃም ፎረስትን 2 ለ 0 ሲረታ በርንሌይ ወልቭስን 3 ለ 2 አሸንፏል።

ሀብታሙ ምትኩ

አርሰናል ሲመራ ማንችስተር ሲቲ እየተመራ ነውፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_ጥቅምት 16/2018 ዓ.ምየእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የዘጠነኛ ሳምንት አራት ጨዋታዎች ከ11:00 ጀምሮ በመደረግ ላይ ሲ...
26/10/2025

አርሰናል ሲመራ ማንችስተር ሲቲ እየተመራ ነው

ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_ጥቅምት 16/2018 ዓ.ም

የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የዘጠነኛ ሳምንት አራት ጨዋታዎች ከ11:00 ጀምሮ በመደረግ ላይ ሲገኙ የሁሉም ጨዋታዎች የመጀመሪያ አጋማሽ ተጠናቀዋል።

ኢምሬትስ ላይ ክሪስታል ፓላስን በማስተናገድ ላይ ያለው አርሰናል 1 ለ 0 እየመራ አጋማሹን አጠናቋል።

ጎሉን የቀድሞው የክሪስታል ፓላስ ተጫዋች ኤቤሬቺ ኤዜ በ39ኛው ደቂቃ ላይ አስቆጥሯል።

ቪላ ፓርክ ላይ እየተደረገ ባለው ጨዋታ ደግሞ አስቶንቪላ ማንችስተር ሲቲን 1 ለ 0 በመምራት ላይ ይገኛል።

ማቲ ካሽ በ19ኛው ደቂቃ ላይ የአስቶንቪላን ግብ ያስቆጠረው ተጫዋች ነው።

በሌሎች ጨዋታዎች በርንማውዝ ኖቲንግሃም ፎረስትን 2 ለ 0 በርንሌይ ሲመራ በርንሌይ እና ወልቭስ በሁለት አቻ ውጤት ወደ መልበሻ ክፍል አምርተዋል።

ሀብታሙ ምትኩ

ማንችስተር ዩናይትድ ተከታታይ ሶስተኛ ድሉን አስመዘገበፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_ጥቅምት 15/2018 ዓ.ምበእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የዘጠነኛ ሳምንት አራተኛ ጨዋታ ብራይተን ሆቭ አልብዮንን ...
25/10/2025

ማንችስተር ዩናይትድ ተከታታይ ሶስተኛ ድሉን አስመዘገበ

ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_ጥቅምት 15/2018 ዓ.ም

በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የዘጠነኛ ሳምንት አራተኛ ጨዋታ ብራይተን ሆቭ አልብዮንን ያስተናገደው ማንችስተር ዩናይትድ 4 ለ 2 አሸንፏል።

ብራዚላውያኑ ማትያሰ ኩንሀ እና ካዜሚሮ አንድ አንድ እንዲሁም ካሜሩናዊው ብርያን ኤምቡኤሞ ደግሞ ሁለቱን የቀያይ ሰይጣኖቹን ግቦች አስቆጥረዋል።

የብራይተንን ግቦች የቀድሞው የማንችስተር ዩናይትድ ተጫዋች ዳኒ ዌልቤክ እና ቻራላምፖስ ኮስቱላስ አስቆጥረዋል።

ማንችስተር ዩናይትድ ድሉን ተከትሎ ነጥቡን 16 በማድረስ በጊዜያዊነት የ4ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።

ሀብታሙ ምትኩ

TELEGRAM - https://t.me/primediasport

በተጠባቂው የሴሪ ኤ ጨዋታ ናፖሊ ኢንተር ሚላንን አሸነፈፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_ጥቅምት 15/2018 ዓ.ምበስምንተኛው ሳምንት የጣልያን ሴሪ ኤ ተጠባቂ ጨዋታ ኢንተር ሚላንን ያስተናገደው ...
25/10/2025

በተጠባቂው የሴሪ ኤ ጨዋታ ናፖሊ ኢንተር ሚላንን አሸነፈ

ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_ጥቅምት 15/2018 ዓ.ም

በስምንተኛው ሳምንት የጣልያን ሴሪ ኤ ተጠባቂ ጨዋታ ኢንተር ሚላንን ያስተናገደው ናፖሊ 3 ለ 1 አሸንፏል።

ኬቨን ዴ ብሩይን ፣ ስኮት ማክቶሚናይ እኔ ፍራንክ አንጉይሳ የናፖሊን ግቦች ያስቆጠሩ ተጫዋቾች ናቸው።

የኢንተር ሚላንን ብቸኛ ግብ ሀካን ቻልሀኖግሉ አስቆጥሯል።

ናፖሊ ማሸነፉን ተከትሎ ነጥቡን 18 በማድረስ የደረጃ ሰንጠረዡ መሪ ሆኗል።

በተጨማሪም በዕለቱ በተደረጉ ሌሎች ጨዋታዎች ፓርማ ከኮሞ አቻ ሲለያዩ ዩዲንዜ ሊቼን 3 ለ 2 አሸንፏል።

ሀብታሙ ምትኩ

ማንችስተር ዩናይትድ ብራይተን ሆቭ አልብዮንን 2 ለ 0 እየመራ ነውፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_ጥቅምት 15/2018 ዓ.ምበእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የዘጠነኛ ሳምንት አራተኛ ጨዋታ ብራይተን ሆቭ...
25/10/2025

ማንችስተር ዩናይትድ ብራይተን ሆቭ አልብዮንን 2 ለ 0 እየመራ ነው

ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_ጥቅምት 15/2018 ዓ.ም

በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የዘጠነኛ ሳምንት አራተኛ ጨዋታ ብራይተን ሆቭ አልብዮንን ያስተናገደው ማንችስተር ዩናይትድ 2 ለ 0 እየመራ ነው።

የጨዋታው የመጀመሪያ አጋማሽ የተጠናቀቀ ሲሆን ብራዚላውያኑ ማትያሰ ኩንሀ እና ካዜሚሮ የቀያይ ሰይጣኖቹን ግቦች ያስቆጠሩ ተጫዋቾች ናቸው።

የሩበን አሞሪሙ ቡድን ውጤቱን አስጠብቆ መውጣት ከቻለ ተከታታይ አራተኛ ድል ኦልድትራፎርድ ላይ የሚያስመዘግብ ይሆናል።

ሀብታሙ ምትኩ

ቼልሲ ስታምፎርድ ብሪጅ ላይ በሰንደርላንድ ተሸነፈፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_ጥቅምት 15/2018 ዓ.ምበእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የዘጠነኛ ሳምንት ሁለት ጨዋታዎች ከ11:00 ጀምሮ ተደርገው ሲ...
25/10/2025

ቼልሲ ስታምፎርድ ብሪጅ ላይ በሰንደርላንድ ተሸነፈ

ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_ጥቅምት 15/2018 ዓ.ም

በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የዘጠነኛ ሳምንት ሁለት ጨዋታዎች ከ11:00 ጀምሮ ተደርገው ሲጠናቀቁ ሰንደርላንድን ያስተናገደው ቼልሲ 2 ለ 1 ተሸንፏል።

ሰማያዊዎቹ አሌሀንድር ጋርናቾ በአራተኛው ደቂቃ ባስቆጠረው ግብ መሪ መሆን ቢችሉም ቸምስዲኔ ታይቢ በ22 ደቂቃ ሰንደርላንድን አቻ አድርጓል።

በ90+3ኛ ደቂቃ ላይ ግን ዊልሰን ኢሲዶር ግብ አስቆጥሮ ጥቋቁር ድመቶቹን አሸናፊ አድርጓል።

ውጤቱንም ተከትሎ ሰንደርላንድ ነጥቡን 17 በማድረስ በጊዜያዊነት የሁለተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።

በተመሳሳይ ሰዓት ሴንት ጀምስ ፓርክ ላይ በተደረገው ጨዋታ ኒውካስትል ዩናይትድ ፉልሀምን 2 ለ 1 ረቷል።

ጃኮብ መርፊ እና ብሩኖ ጉማሬሽ የኒውካስትል ዩናይትድን የማሸነፊያ ግቦች ሲያስቆጥሩ ሳሳ ሉኪች የፉልሀምን ብቸኛ ግብ አስቆጥሯል።

የኤዲ ሆው ቡድን ማሸነፉን ተከትሎ ነጥቡን 12 ያደረሰ ሲሆን በደረጃ ሰንጠረዡም ወደ 11ኛ ከፍ ብሏል።

ሀብታሙ ምትኩ

በሮዱዋ ደርቢ ሲዳማ ቡና አሸነፈፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_ጥቅምት 15/2018 ዓ.ምበሲበኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የሁለተኛ ሳምንት የመጨረሻ መርሐግብር ሲዳማ ቡና ሀዋሳ ከተማን 1 ለ 0...
25/10/2025

በሮዱዋ ደርቢ ሲዳማ ቡና አሸነፈ

ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_ጥቅምት 15/2018 ዓ.ም

በሲበኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የሁለተኛ ሳምንት የመጨረሻ መርሐግብር ሲዳማ ቡና ሀዋሳ ከተማን 1 ለ 0 አሸንፏል።

የሲዳማ ቡናን ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ ያሬድ ባየህ በ52ኛው ደቂቃ ላይ በፍፁም ቅጣት ምት አስቆጥሯል።

ውጤቱንም ተከትሎ ሲዳማ ቡና ስድስት ነጥቦች ላይ የደረሰ ቀዳሚው ክለብ ሆኗል።

የሊጉ የሶስተኛ ሳምንት ጨዋታዎች ከመጪው ማክሰኞ ጀምሮ ይካሄዳሉ።

ሀብታሙ ምትኩ

ማንችስተር ዩናይትድ ተከታታይ ሶስተኛ ድል ያስመዘግብ ይሆን ? ሊቨርፑልስ ወደ ድል ይመለሳል ?ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_ጥቅምት 15/2018 ዓ.ምየዘጠነኛው ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊ...
25/10/2025

ማንችስተር ዩናይትድ ተከታታይ ሶስተኛ ድል ያስመዘግብ ይሆን ? ሊቨርፑልስ ወደ ድል ይመለሳል ?

ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_ጥቅምት 15/2018 ዓ.ም

የዘጠነኛው ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ አራት ጨዋታዎች ዛሬ ከ11:00 ጀምሮ ይደረጋሉ።

በዕለቱ ከሚደረጉት ጨዋታዎች መካከል ኦልድትራፎርድ ላይ ማንችስተር ዩናይትድ ብራይተን ሆቭ አልብዮንን የሚያስተናግድበት ጨዋታ ይጠበቃል።

ጨዋታው ከምሽት 1:30 ጀምሮ የሚደረግ ሲሆን የሩበን አሞሪሙ ማንችስተር ዩናይትድ ተከታታይ ሶስተኛ የሊግ ድል ለማስመዝገብ ይጫወታል።

ቡድኑ ሰንደርላንድ እና ሊቨርፑልን በተከታታይ ማሸነፉ የሚታወስ ሲሆን ኦልድትራፎርድ ላይ ደግሞ በርንሌይ ፣ ቼልሲ እና ሰንደርላንድን በተከታታይ ረቷል።

ብራይተን ሆቭ አልብዮንን ከገጠመባቸው ያለፉት አስር የሊጉ ጨዋታዎች በስድስት የተሸነፈው ማንችስተር ዩናይትድ ካለፉት ሰባት የእርስ በርስ ግንኙነቶች በአንዱ ብቻ አሸንፏል።

ኦልድትራፎርድ ላይ የተደረጉት ያለፉት ሶስት የሁለቱ ክለቦች የሊግ ጨዋታዎች በብራይተን አሸናፊነት የተጠናቀቁ ናቸው።

ማንችስተር ዩናይትድ በ13 ነጥቦች በደረጃ ሰንጠረዡ 9ኛ ላይ የተቀመጠ ሲሆን ብራይተን በበኩሉ በ12 ነጥቦች 10ኛ ላይ ይገኛል።

ምሽት 4:00 ጀምሮ በሚደረገው ጨዋታ ደግሞ ጂ ቴክ ኮሙኒቲ ስታድየም ላይ ብሬንትፎርድ ሊቨርፑልን ያስተናግዳል።

የአርን ስሎቱ ቡድን ባለፉት ሶስት ተከታታይ የፕሪሚየር ሊጉ ጨዋታዎች ላይ መሸነፉ የሚታወስ ነው።

በመጀመሪያ አምሰት የሊጉ ጨዋታዎች ላይ 15 ነጥቦችን የሰበሰበው ሊቨርፑል በደረጃ ሰንጠረዡ ሶስተኛ ላይ የሚገኝ ሲሆን ብሬንትፎርድ በበኩሉ በ10 ነጥቦች 14ኛ ላይ ተቀምጧል።

በተጨማሪም ሊቨርፑል ወደ ለንደን ተጉዞ ባደረጋቸው ያለፉት አራት የሊጉ ጨዋታዎች በሙሉ ተሸንፏል።

በአንፃሩ ያለፉት አምስት የሁለቱ ክለቦች የሊግ የእርስ በርስ ጨዋታዎች በሊቨርፑል አሸናፊነት የተጠናቀቁ ናቸው።

ከሁለቱ ጨዋታዎች መካሄድ አስቀድሞ ከ11:00 ጀምሮ ሁለት ጨዋታዎች ሲደረጉ ስታምፎርድ ብሪጅ ላይ ቼልሲ ሰንደርላንድን ያስተናግዳል።

ሁለቱም ክለቦች ተመሳሳይ 14 ነጥቦችን የሰበሰቡ ሲሆን በግብ ክፍያ ተበላልጠው ቼልሲ 5ኛ ሰንደርላንድ ደግሞ 6ኛ ላይ ተቀምጠዋል።

ሰንደርላንድ በሊጉ ከለንደን ክለቦች ጋር ከሜዳው ውጪ ባደረጋቸው ያለፉት 13 ጨዋታዎች በአንዱም ሽንፈት ያላስተናገደ ሲሆን በአራቱ አሸንፎ በዘጠኝ አቻ ተለያይቷል።

በተመሳሳይ ሰዓት ሴንት ጀምስ ፓርክ ላይ በሚደረገው ጨዋታ ኒውካስትል ዩናይትድ ከፉልሀም ይጫወታሉ።

ኒውካስትል ዩናይትድ በ9 ነጥቦች 15ኛ ደረጃ ላይ ሲገኝ ፉልሀም በበኩሉ በ8 ነጥቦች የ16ኛ ደረጃን ይዟል።

ሀብታሙ ምትኩ

31ኛው የሮዱዋ ደርቢ ዛሬ ይካሄዳል ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_ጥቅምት 15/2018 ዓ.ምበሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የሁለተኛ ሳምንት የመጨረሻ ጨዋታ ሲዳማ ቡና ከሀዋሳ ከተማ ዛሬ ይጫ...
25/10/2025

31ኛው የሮዱዋ ደርቢ ዛሬ ይካሄዳል

ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_ጥቅምት 15/2018 ዓ.ም

በሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የሁለተኛ ሳምንት የመጨረሻ ጨዋታ ሲዳማ ቡና ከሀዋሳ ከተማ ዛሬ ይጫወታሉ።

ጨዋታው በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ ስታድየም የሚደረግ ሲሆን ከቀን 10:00 ጀምሮ ይደረጋል።

የሮዱዋ ደርቢ የሚል ስያሜ ያለው ጨዋታው ለ31ኛ ጊዜ የሚደረግ ሲሆን ከዚህ ቀደም በተደረጉት 30 ጨዋታዎች በተመሳሳይ 10 ጊዜ ተሸናንፈዋል።

ባለፉት አራት የሁለቱ ክለቦች የእርስ በርስ ጨዋታዎች ሀዋሳ ከተማ በሁለት አሸንፎ በሁለቱ አቻ ተለያይተዋል።

ሀብታሙ ምትኩ

ኢትዮ ኤሌክትሪክ ከሀድያ ሆሳዕና ነጥብ ተጋርተዋልፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_ጥቅምት 14/2018 ዓ.ምበሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሰባተኛ ጨዋታ ኢትዮ ኤሌክትሪክ እና ሀድያ ሆሳዕና ያለ...
24/10/2025

ኢትዮ ኤሌክትሪክ ከሀድያ ሆሳዕና ነጥብ ተጋርተዋል

ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_ጥቅምት 14/2018 ዓ.ም

በሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሰባተኛ ጨዋታ ኢትዮ ኤሌክትሪክ እና ሀድያ ሆሳዕና ያለ ግብ አቻ ተለያይተዋል።

በመጀመሪያ ሳምንት ጨዋታዎች ኢትዮ ኤሌክትሪክ ሸገር ከተማን ማሸነፉ የሚታወስ ሲሆን ሀድያ ሆሳዕና በበኩሉ በባህርዳር ከተማ ተረቷል።

ሀብታሙ ምትኩ

መቻል እና መቀሌ 70 እንደርታ አቻ ተለያዩፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_ጥቅምት 14/2018 ዓ.ምበሲበኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የሁለተኛ ሳምንት ስድስተኛ ጨዋታ መቻል እና መቀሌ 70 እንደ...
24/10/2025

መቻል እና መቀሌ 70 እንደርታ አቻ ተለያዩ

ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_ጥቅምት 14/2018 ዓ.ም

በሲበኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የሁለተኛ ሳምንት ስድስተኛ ጨዋታ መቻል እና መቀሌ 70 እንደርታ 2 ለ 2 ተለያይተዋል።

በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ ስታድየም በተደረገው ጨዋታ ኪቲካ ጀማ እና ፍፁም አለሙ የመቀሌ 70 እንደርታን ግቦች አስቆጥረዋል።

አብዱልከሪም ወርቁ እና ቸርነት ጉግሳ ደግሞ የመቻልን ግቦች ያስቆጠሩ ተጫዋቾች ናቸው።

ሀብታሙ ምትኩ

ባህርዳር ከተማ በግርማ ዲሳሳ የተጨማሪ ደቂቃ ግብ ነጥብ ተጋርቷልፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_ጥቅምት 14/2018 ዓ.ምበሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የሁለተኛ ሳምንት የዕለቱ ቀዳሚ ጨዋታ ...
24/10/2025

ባህርዳር ከተማ በግርማ ዲሳሳ የተጨማሪ ደቂቃ ግብ ነጥብ ተጋርቷል

ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)_ጥቅምት 14/2018 ዓ.ም

በሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የሁለተኛ ሳምንት የዕለቱ ቀዳሚ ጨዋታ አርባምንጭ ከተማ እና ባህርዳር ከተማን 1 ለ 1 ተለያይተዋል።

በጨዋታው ታምራት ኢያሱ በ75ኛው ደቂቃ ላይ አዞዎቹን ቀዳሚ ያደረገ ግብ ያስቆጠረው ተጫዋች ነው።

ታምራት ኢያሱ በቀዳሚው ጨዋታም ነገሌ አርሲ ላይ ግብ ማስቆጠሩን ተከትሎ በሊጉ ያስቆጠራቸውን ግቦች ሁለት አድርሷል።

መደበኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ተጠናቆ በተጨማሪ ደቂቃ(90+1) ላይ ግን ግርማ ዲሳሳ ከማዕዘን የተነሳ ኳስ አስቆጥሯል።

አስቀድሞ የቢጫ ካርድ ግርማ ዲሳሳ ግቡን ካስቆጠረ በኋላ ማልያውን ማውለቁን ተከትሎ በሁለተኛ የቢጫ ካርድ ከሜዳ ተሰናብቷል።

ውጤቱንም ተከትሎ ባህርዳር ነጥቡን 4 ሲያደርስ አርባምንጭ ከተማ በበኩሉ 2 ነጥብ ላይ ደርሷል።

ሀብታሙ ምትኩ

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Prime Sport ET posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share