Sales Agent

Sales Agent ቅንነት
መልካምነት
ሀቀኝነት
እምነት
ተስፍ
አስፈላጊ ናቸው።
(1)

12/11/2024
21/08/2024

ደፋሪዋ በነፃ ተለቆ በነፃነት እየኖረ ነው‼️
ይህንንም ጉድ ስሙና ፍረዱ‼️

ይህች የ11ዓመት ህፃን ትባላለች!የምትኖረው ከአባቷና ከእንጀራ እናቷ ጋር ጋሞ ዞን ቁጫ ወረዳ ሰላምበር የሚባል አካባቢ ነው!

ሀሙስ ሰኔ6/2016ዓ.ም አባት የታመሙ እናቱን ጠይቆ ባለቤቱም ስራ ጨርሳ ማታ 4ሰዓት አካባቢ ወደ ቤት ተመልሰው በር ሲያንኳኩ የሚሰማቸው ሰው አጡ! ሌላ ቀን ሮጣ የምትከፍታቸው ሀሴት ድምጿን ሲያጡ አባት ተደናግጦ በሩን ሰብሮ ሲገባ ህፃኗ ተደፍራ ራሷን ስታ ወድቃለች!አባትም እንዳያት "ወይኔ ልጄ" ብሎ ወደቀ!!ምን ማድረግ እንዳለባቸው ግራ ገብቷቸው ወደ ሆስፒታል ሲወስዷት"ስፔሻሊስቱ ዶ/ር
ስለሌለ ጠዋት ኑ"ብለው ቢመልሷቸው ከቀናት በኋላ በተደረገላት ምርመራ የ5ተኛ ክፍል ተማሪዋ ሀሴት ተገዳ መደፈሯ ተረጋገጠ! ?

ሰኔ6ማታ ዝናብ እየዘነበ ካስትሮ የሚባል የ2ልጆች አባት የቤተሰቡ የቅርብ ጎረቤት ሁሌም ከስራ ሲመለሱ አብሯቸው ወደ ሰፈር የሚመጣ ሰው እንደተለመደው የእንጀራ እናት ጋር ይደውልና "መሸ ወደ ቤት እንሄድም ወይ?"ሲላት "አይ ትንሽ እቆያለሁ ባለቤቴንም እጠብቀዋለሁ፣አንተ ሂድ "ትለዋለች!!

ይህ ሰው ወደ ቤቱ ከመግባት ይልቅ ብቻዋን እንደሚያገኛት እርግጠኛ ወደ ሆነው ሀሴት(ውሹ)ጋር ደርሶ በር ያንኳኳል፣"እኔ ካስትሮ ነኝ አባትሽ መልዕክት ልኮኝ ነው"በሚል በሩን አስከፍቷት ከቆለፈው በኋላ ታግሏት አንገቷን አንቆ፣አፏን ዘግቶ ምላሷን ጎርሳ ራሷን እስክትስት ድረስ አስጨንቆ ከደፈራት በኋላ በሌላ በር ወጥቶ ሄዷል!!

አባት አቶ አድማሱ እንደነገረን"ጉዳዩን አቃቢ ህግ ይዞት ክስ ተመስርቶ ለጋሞ ዞን አርባምንጭ ቁጫ ወረዳ ሰላምበር ከተማ አስተዳደር ፍርድ ቤት ቢቀርብም በቂ ምስክር የለም ህፃኗም በስርዓት አላስረዳችም በሚል ሰበብ በጭካኔ የደፈራት ያ የምታውቀው ጎረቤቷ በነፃ ተለቋል!!አቃቢ ህግም ለምን እንዲህ ይሆኗል?እንዴት ደፍሮ በነፃ ይለቀቃል ሲል፣እኔንና ፍርድቤቱን ተዳፍረሀል በሚል ደኛው 2000ብር ቀጥቶት ፋይሉን ዘግቷል😭ይግባኝ ለዞኑ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ጠይቀዋል!!

አባት በመጨረሻ ምን አለኝ መሰላችሁ" የሚገርምህ ሞታለች ብሎ ነው የሄደው፣ፍትህ እኮ የለም፣ልጄን የደፈረው ሰው አሁን ተፈቶ በመንገዴ ሳገኘው ደሜ እየፈላ ውስጤ የሆነ ነገር አድርገውና ለመንግስት እጅህን ስጥ"ይለኛል!አለኝ‼️
እያመመኝም እያናደደኝም ቢሆን እንዲህ አልኩት" እሱ ምን አልባት ተስፋ የቆረጠ ሰው ይሆናል፣አንተ ለልጅህ ታስፈልጋታለህ እስከመጨረሻው በህጉ ታሸንፈዋለህ አይዞህ ታገል"ብዬ ስልኩን ዘጋሁት!! #ያማል!!
እንደ ህፃን ሀሴትም ፍትህ የተነፈጉ ነፍሶች ብዙ ናቸው‼️

😭 ለሐሴትም ፍትህ ይሰጥልን!! ‼️
Via: ሄኖክ ፍቃዱ
#ሼር ሼር በማድረግ ትኩረት እንዲሰጣት እናድርግ 🙏

17/08/2024

እስኪረፋፍድም አይጠብቅም ፡ በቃ በጠዋት ከመኝታው እንደተነሳ ፡ ቁርሱን እንኳን በደንብ ሳይበላ ይወጣና አዘውትሮ አልኮል ወደሚጠጣበት ባር በመሄድ

ቀኑን ሙሉ ሲጠጣ ውሎ ፡ መጠጥ በቅቶት ሳይሆን ፡ ብርጭቆ የማንሳት አቅም ሲያጣ ፡ እንደምንም እየተንገዳገደ ወደቤቱ ይመለሳል ።

ይህ ከላይ ያለው ኑሮ ፡ የዝነኛው የእግር ኳስ ኮከብ ፡ የክርስቲያኖ ሮናልዶ ታላቅ ወንድም የሆነው የ hugo dos santos aveiro ለአመታት የኖረበት ህይወት ነው ።

የሮናልዶ እናት እና ራሱ ሮናልዶ ጭምር ሁጎን ከዚህ ከመጠጥ ሱሱ ለማዳን ለአመታት ሞክረዋል ።

በተለይ ሮናልዶ ፡ የመጠጥ ሱስ ማለት ምን ማለት እንደሆነ ፡ በአባቱ ያውቀው ነበርና ፡ ወንድሙን በዚህ ምክንያት እንዳያጣ ይሰጋል ።

እና አንድ ቀን ወንድሙን እንደሚፈልገው ነግሮት አንድ ሬስቶራንት ይዞት ሄደ ፡ ምሳ እየበሉ ሊመክረው ፡ ከዚህ የመጠጥ ሱስ እንዲያቆም እንደሁልጊዜው ሊማፀነው ነው ያሰበው ።

እና አስተናጋጇ መጣች ፡ ምን ይምጣላችሁ ስትል ጠየቀች ፡ ቀልደኛው የሮናልዶ ወንድም ለኔ የሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫ ሲል ቀለደ ። በዚህ ከተሳሳቁ በኋላ የሚበላ አዘው ማውራት ጀመሩ ፡ እና ሮናልዶ ፡ ቀንደኛ የማድሪድ ደጋፊ ለሆነው ወንድሙ ይሄን ያህል ዋንጫ ርቦሀል እንዴ ሲል ጠየቀው ።

" አዎ በጣም ፡ በተለይ የሻምፒየንስ ሊግ " ሲል መለሰለት
በቃ አይዞን በዚህ አመትማ እንበላዋለን ፡ ግን ቃል ግባ
" ምን ብዬ " አለ ሁጎ
በዚህ አመት ማድሪድ የሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫን ካነሳ መጠጥ ታቆማለህ ?
" አዎ "
ፕሮሚስ ?
" ፕሮሚስ !!! " ባንዳፍ ! እንግዲህ ቃል ገብተሀል እንዳትረሳ ። ተባብለው ተለያዩ ።

ከወራት በኋላ ሮናልዶ ያሰበው ተሳካ , እናም ትልቅ ሪከርድ ሊባል በሚችል በአንድ የሻምፒየንስ ሊግ 2013-2014 ሲዝን በድምሩ 17 ግቦችን በማስቆጠር ማድሪድና ፡ ወንድሙ የፈለጉትን ድል ማሳካት ቻለ ።

እና ልክ የዋንጫው ጫዋታ እለት ማድሪድ አሸንፎ ዋንጫውን ሲያነሱ ፡ የማድሪድ ደጋፊ ወንድሙ ሲሮጥ ወደ ሜዳ መጣ ፡ ከሮናልዶ ጋር ተቃቀፉ ፨
እና ሮናልዶ ያሸነፈበትን ማልያ ለወንድሙ ከሰጠው በኋላ በጆሮው ፡ እኔ ቃሌን ጠብቂያለሁ ፡ አሁን ደግሞ ተራው ያንተ ነው አለው ።

ለአመታት በመጠጥ ሱስ ተይዞ ቤተሰቡን ሲያሰቃይ የነበረው ሁጎም የማድሪድን ዋንጫ ማግኘት ተከትሎ ቃሉን ጠበቀ ፨
መጠጥ እርግፍ አድርጎ ተወ ።

ዛሬ ላይ ሁጎ ትልቅና የተከበረ ሰው ነው ። በፖርቹጋል የሚገኘውን የሮናልዶን ሙዚየምና ሌሎች ቢዝነሶቹንም የሚቆጣጠርለት እሱ ነው ።

በወንድሙ የአመታት ምክርና ጥረት ሁጎ አሁን የቤተሰቡ መኩሪያ ሆኗል ።
Wasihun Tesfaye

11/08/2024

እንኳን ደስ አለን
***

በፓሪስ 2024 ኦሎምፒክ ዛሬ ረፋድ ላይ በተካሄደው የሴቶች ማራቶን አትሌት ትዕግስት አሰፋ ሶስተኛውን የብር ሜዳሊያ ለሀገራችን ኢትዮጵያ በማምጣት አኩሪ ድል አስመዝግባለች።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ እንኳን ደስ አላችሁ ይላል።

04/08/2024
30/07/2024
22/07/2024

የአንዲት አፍሪካዊት እናት ተማጽኖ !!😢

ከስሯ የተንበረከከችውን ሴት ፡ ከምንም ባለመቁጠር ፡ በዚህ መልኩ እያናገረች ያለችው ኬንያ ውስጥ የአንድ ትንሽ ከተማ አስተዳዳሪ ናት ።

ነዋሪዎቹን ለማወያየት መጥታ ነው ። እና በመከራ የማይገኙትን ባለስልጣናት ድንገት ያገኘችው ይህች እናት አጋጣሚውን በመጠቀም ፡ ተንበርክካ እየለመነች ነው ።
" እባክዎ ልጄን ስራ ያስገቡልኝ " እያለች ።
ክብር ለልጆቻቸው ሲሉ የሰው ፊት የሚያዩ ፡ የባለስልጣናትን ደጅ ለሚጠኑ ወላጆች ይሁን ።😢😔

(ዋሲሁን ተስፋዬ)

21/07/2024

የ21ኛው ክፍለ ዘመን ምርጥ አፍሪካዊ ስፖርተኛ ተብሎ በመመረጡ ደስታችንን እየገለጠን...ዛሬም እንደ ትላንቱ ስለ እርሱ እንጠይቃለን...

◾️አገርን ወርቅ ላለበሰ
◾️በኦሊምፒክ ሶስት የወርቅ ሜዳሊያዎችን ላስገኘ ጀግና
◾️4 የዓለም አትሌቲክስ ላይ ተሳትፎ 5 ወርቅ ለሚያስገኝ
◾️ ለአገር ክብር በተደረጉ ውድድሮች ላይ ብቻ ከ20 በላይ ወርቆችን ለአገር ላበረከተ
◾️እልፍ ክብረወሰኖችን ላሻሻለ
◾️ለ21ኛው ክፍለ ዘመን ምርጥ አፍሪካዊ ስፖርተኛ
◾️አገርን በክብር ሲያስጠራ ለኖረ...
የሱስ ክብር ስንት ነው...ዋጋው ምኑ ጋ ነው...?

በስሙ የተሰየመ አንድ ተራ የብየዳ እና አሽከርካሪዎች ማሰልጠኛ ፖሊ ቴክኒክ...? አንድ ዘፈን..? በቃ..? ይሄው ነው...?

ቀነኒሳ በተደራራቢ ጉዳቶች ተፈትኖ ከውድድር በራቀ ጊዜ ብቅ ያለውን ትውልደ ሶማሊ ብሪትሽን አስታወሳችሁት...? አዎ ሞ ፋራን! ለውለታው በብሪታንያ የተሰጡትን ክብሮች እና ሽልማቶች አሁን መዘርዘር ቢጀምር ሳልጨርስ ይነጋብኛል። ስለ እሱ የተፃፉትን አንብቦ መጨረስ ያዳግታል። በብሪታንያ ምድር ከሁሉ በላይ የሆነው...የክብሮች ሁሉ ቁንጮ...የሽልማቶች ሁሉ ራስ የሆነ ክብርም ተሰጥቶታል...የ SIR! ማዕረግ ደፍተዋል።
ከ Sir ሌላ ምን አለ..? ከSIR በላይ ሰማይ እንጂ ሌላ የለም። እናም በብዙ ነገር የሚታሙት ብሪትሾች... ሶማሊ ነው ሳይሉ...ሙስሊም ነው ሳይሉ...ስደተኛ ነው ሳይሉ...ጥቁር ነው ሳይሉ...ለስፖርታዊ አበርክቶው SIR MOHAMMED MUKTAR JAMA FARAH ብሎ አከበሩት። በዛች ምድር ይህ የክብሮች ሁሉ ክብር ነው።

ሞ የአርሰናልን ጨዋታ ለማየት ስታዲየም ሲገባ ፊርማውን ለማግኘት የሚራኮት ነጭ ስፍር ቁጥር የለውም። ለእሱ ብቻ ሳይሆን ለህፃናት ልጆቹ እንኳን የሚያሳዩት አክብሮት ይገርማል። ገድሉ የብሪታንያ ትርክት አካል ሆኖዋል።

አይፀዱም...? አያስቀኑም...? ይህን እያሰብክ ቆሼ ቆምቦሬው ፖሊ ቴክኒክ ትዝ ስልህ አትበግንም...? አይዞሽ ገለቴ ስላቅ ቋቅ አይልህም...? እንደው ገድሉ ይቅር...ጀግንነቱም ይረሳ...ግን ቀነኒሳ ምን በድሎን ነው እንዲህ የጨከንበት አያሰኝም...?

ተፃፈ በጥላዬ ያሚ

17/07/2024
10/07/2024

ጥብቅ ማሳሰቢያ ለሴቶች‼️

ራስን የሚያስት መድኃኒት በመጠጣቸው ውስጥ እየተጨመረ የሚደፈሩ ሴቶች ቀን በቀን እየጨመሩ ነው።

(መልእክቱን ሼር ያድርጉ)

በግሌ ከማክማቸው ሴቶች መካከል የተወሰኑ ይሄንን መሰል ታሪኮች የነገሩኝ ሲሆን ከተለያዩ ሰዎችም ተመሳሳይ ገጠመኞችን በየቦታው እየሰማሁ ነው። በተለይም ይሄ በክለቦችና መዝናኛ ስፍራዎች በድራፍትና ውስኪ ውስጥ ተጨምሮ የሚሰጠው አደንዛዥ መድኃኒት ሽታና ቀለም ስለሌለው ለተጠቂዋ ሴት ምንም አይነት ፍንጭ የማይሰጥ መሆኑ ችግሩን አስጊ አድርጎታል።

እናም ይሄንን መድኃኒት ከመጠጧ ተጨምሮባት የጠጣች ሴት በአጭር ጊዜ ውስጥ ንቃተ-አእምሮዋ እጅግ ይወርድና ሰመመን ውስጥ ትገባለች። ብዙዎቹ የሚነቁት ከማያውቁት መኝታ ክፍል ውስጥ ሁሉ ነገር ተከናውኖ ካበቃ በኋላ ነው።

ስለዚህ በቅጡ ከማያውቁት ሰው ጋር በመዝናናት ሰበብ መገናኘት፣ በተለይም መጠጥ ቤቶች ውስጥ መጋበዝና መጠጥ መጎንጨት ትልቅ የአካላዊና ሥነልቦናዊ ጠባሳ ጥሎ ሊያልፍ እንደሚችል ማወቅ ያሻል። በተለይም በተለምዶ የቤት ልጅ የሚባሉ ሴቶችና ታዳጊዎች ላይ ይሄ ነገር እየተበራከተ ስለሆነ ቤተሰቦች ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ አለባችሁ።

አያድርገውና ሁኔታው ከተከሰተም ሴቶች ወዲያውኑ ለፖሊስ መጠቆም፣ የእርግዝናና በሽታ መከላከያ መድኃኒቶችን መውሰድ እንዲሁም የሥነአእምሮ ባለሙያ ማማከር አለባችሁ።

ምስጢራዊነቱ ስለሚሻል የመድኃኒቱን ስም ከመጥቀስ ተቆጥቢያለሁ።

(ዶ/ር ኤልያስ ገብሩ አእምሮ፣
የሥነ-አእምሮ ስፔሻሊስትና የሥነ-ልቦና አማካሪ)

Address

Addis Ababa

Telephone

+251903640313

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Sales Agent posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share