ሮሃ ሚዲያ / Roha Media

ሮሃ ሚዲያ / Roha Media #ፈጣን የመረጃ ምንጭ!
════════

የብልፅግና ፓርቲ ም/ቤት ን በቁርጠኝነት ለማከናወን ያስቀመጣቸው ሰባት ጉዳዮች፡-👉ግጭትን ሊያስቀሩ የሚችሉ ሰላማዊ አማራጮችን በሁሉም አቅጣጫ ለመሞከርና በሰላማዊ መንገድ ለመታገል ለሚወስኑ ...
08/08/2025

የብልፅግና ፓርቲ ም/ቤት ን በቁርጠኝነት ለማከናወን ያስቀመጣቸው ሰባት ጉዳዮች፡-

👉ግጭትን ሊያስቀሩ የሚችሉ ሰላማዊ አማራጮችን በሁሉም አቅጣጫ ለመሞከርና በሰላማዊ መንገድ ለመታገል ለሚወስኑ ታጣቂዎች አስፈላጊውን ሁሉ ለማድረግ፤

👉የሰላምን አማራጭ ባለመቀበል በሕዝብና በሀገር ንብረት ላይ ችግር ለመፍጠር በሚነሡ ኃይሎች ላይ በተጠናከረ መንገድ ሕግ ለማስከበር፤

👉በየደረጃው የሚነሡ የሕዝብ የመልካም አስተዳደር፣ የፍትሕና የኢኮኖሚ ጥያቄዎችን በኢትዮጵያ ዐቅም ልክ በየደረጃው ለመመለስ፤

👉ተገቢውንና እውነተኛውን መረጃ ለሕዝብ በየጊዜው ለመስጠትና ሐሰተኛ መረጃዎችን ለማጋለጥ፤

👉በየተቋማቱ ተመድበው የዲሲፕሊን ጉድለት፣ሙስናና የአስተዳደር በደል የሚያደርሱ የሥራ መሪዎችንና አገልጋዮችን ለመታገል፤

👉በግብርና፣ በአምራች ኢንዱስትሪ፣ በቱሪዝም፣ በማዕድን፣ እንደዚሁም በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ዘርፍ የጀመርናቸውን የልማት ሥራዎች የበለጠ ስኬታማ በማድረግ፤ የተጀመሩ ኢኒሼቲቮችን ለውጤት በማብቃት፤ የሕዝብን ተሳትፎ ባረጋገጠ መልኩ የከተማና የገጠር ትራንስፎርሜሽን ለማረጋገጥ፤

👉በዲፕሎማሲው መስክ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅሞች በሁሉም መንገድ ለማስከበር፤

ዶ/ር ግርማ አመንቲ ከግብርና ሚንስትርነት ተነሱበምትካቸውም አቶ አዲሱ አረጋ የግብርና ሚኒስትር ሆነው ተሾመዋል።ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከዛሬ ጀምሮ አቶ አዲሱ አረጋን የግብ...
01/08/2025

ዶ/ር ግርማ አመንቲ ከግብርና ሚንስትርነት ተነሱ

በምትካቸውም አቶ አዲሱ አረጋ የግብርና ሚኒስትር ሆነው ተሾመዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከዛሬ ጀምሮ አቶ አዲሱ አረጋን የግብርና ሚኒስትር አድርገው ሾመዋል፡፡

አቶ አዲሱ አረጋ የጠቅላይ ሚንስትሩ የደህንነት አማካሪ ሆነው ከመሾማቸው በፊት በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የኦሮሚያ ክልል ገጠር ክላስተር አስተባባሪ ሆነው ሲያገልግሉም ነበር፡፡

ከዛሬ ጀምሮ የግብርና ሚኒስትር ሆነው መሾማቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት አስታውቋል፡፡

ዶ/ር ግርማ አመንቲ ከስልጣን ለምን እንደለቀቁ በይፋ ባይገለጽም ወደ አንድ ዓለም አቀፍ ተቋም ማምራታቸው ከሰሞኑ ሲገለጽ ነበር።

ለበለጠ እና ትኩስ መረጃዎች ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

Facebook https://www.facebook.com/Rohamedia

ገዥው ብልጽግና ፓርቲ፣ የሥራ አስፈጻሚ እና የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላቱን በሙሉ "ወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች" ላይ ለመምከር ለአስቸኳይ ስብሰባ ወደ አዲስ አበባ መጥራቱ ታወቀ። ይህ አስቸኳይ ጥሪ፣...
01/08/2025

ገዥው ብልጽግና ፓርቲ፣ የሥራ አስፈጻሚ እና የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላቱን በሙሉ "ወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች" ላይ ለመምከር ለአስቸኳይ ስብሰባ ወደ አዲስ አበባ መጥራቱ ታወቀ። ይህ አስቸኳይ ጥሪ፣ ሀገሪቱ በበርካታ ከባድ ፈተናዎች ውስጥ በምትገኝበት ወቅት የመጣ ሲሆን፣ ከስብሰባው የሚወጡ ውሳኔዎች የሀገሪቱን ቀጣይ አቅጣጫ ሊጠቁሙ እንደሚችሉ ይጠበቃል ሲሉ የዘ-ሐበሻ የፓርቲው ምንጮች ገልጸዋል።

ምንጮች እንደገለጹት፣ ከነገ ቅዳሜ ሐምሌ 26, 2017 ዓ.ም. (August 2, 2025) ጀምሮ በ4 ኪሎ ቤተመንግስት በሚካሄደው በዚህ ስብሰባ ላይ ለመሳተፍ፣ የፓርቲው ከፍተኛ አመራሮች ከተለያዩ ክልሎች ወደ አዲስ አበባ በመግባት ላይ ናቸው።

የብልጽግና ፓርቲ አመራሮች ስብሰባቸውን የሚያካሂዱት፣ ኢትዮጵያ ውስብስብ በሆኑ የጸጥታ፣ የኢኮኖሚ እና የፖለቲካ ቀውሶች ውስጥ ባለችበት ወቅት ነው። ምንጮች ለዘ-ሐበሻ እንደገለጹት፣ ከስብሰባው አጀንዳዎች መካከል እንደሚሆኑ የሚገመቱት ዋነኛ ሀገራዊ ፈተናዎች የሚከተሉት ናቸው፦

1ኛ. እየተስፋፋ የመጣው የጸጥታ ቀውስ፦

በአማራ እና በኦሮሚያ ክልሎች ያለው ግጭት ተባብሶ በመቀጠሉ፣ ከፍተኛ ሰብዓዊ እና ኢኮኖሚያዊ ውድመትን እያስከተለ ነው።

በሰሜን ያለው አዲስ ውጥረት፦ በኢትዮጵያ እና በኤርትራ መካከል ያለው የቃላት ጦርነት ወደ ግጭት ሊያመራ ይችላል የሚለው ስጋት ጨምሯል። በትግራይ ክልል ውስጥም፣ በተለያዩ የውስጥ ኃይሎች መካከል የሚታየው አለመረጋጋት ለሰላም ስምምነቱ መተግበር ፈተና ሆኗል።

2ኛ. ከባድ የኢኮኖሚ ጫና፦

በሀገሪቱ ያለው የኑሮ ውድነት እና የዋጋ ግሽበት ህዝቡን ክፉኛ እየፈተነ ነው።

በህጋዊው የባንክ ስርዓት እና በጥቁር ገበያ መካከል ያለው የዶላር ምንዛሬ ልዩነት በከፍተኛ ሁኔታ መስፋቱ፣ በኢኮኖሚው ላይ ተጨማሪ ጫና ፈጥሯል።

3ኛ. የውስጥ አስተዳደራዊ እና ፖለቲካዊ ችግሮች፦

በቅርቡ በኦሮሚያ እና በሶማሌ ክልሎች አዋሳኝ ላይ በተደረገው የአስተዳደር ወሰን ማካለል ምክንያት የተቀሰቀሰው ህዝባዊ ተቃውሞና የፖለቲካ ውዝግብ፣ በክልሎች መካከል ያለውን ግንኙነት እየፈተነ ይገኛል።

4ኛ. የመጪው ምርጫ ተዓማኒነት ስጋት፦

በ2018 ዓ.ም. ለሚካሄደው 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ከአንድ ዓመት ያነሰ ጊዜ በቀረበት ወቅት፣ በርካታ የተቃዋሚ ፓርቲዎች በምርጫ ቦርድ ገለልተኝነት ላይ ያላቸውን እምነት ማጣታቸውን በይፋ ገልጸዋል። በሀገሪቱ ባለው የጸጥታ ሁኔታ ምክንያት ምርጫውን በሰላም ለማካሄድ ስለሚቻልበት ሁኔታም ከባድ ጥያቄዎች እየተነሱ ነው። ይህ ጉዳይ፣ ለገዥው ፓርቲ የፖለቲካ ህጋዊ ተቀባይነት (legitimacy) ሲባል በስብሰባው ላይ በሰፊው ይመከርበታል ተብሎ ይጠበቃል።

የብልጽግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች የሚያካሂዱት ይህ አስቸኳይ ስብሰባ፣ ከላይ የተጠቀሱትን ከባድ ሀገራዊ ፈተናዎች ለመፍታት የሚያስችሉ አቅጣጫዎችን ያስቀምጣል ተብሎ እንደሚጠበቅ የገለጹልን ምንጮች፣ "የስብሰባው ውሳኔዎች፣ የሀገሪቱን የሰላም፣ የመረጋጋት እና የኢኮኖሚ የወደፊት እጣ ፈንታ በመወሰን ረገድ ወሳኝ ሚና ይኖራቸዋል ወይ?" ሲሉም ይጠይቃሉ።

ኤርትራ ሠራዊቷን እያጠናከረች፣ ኢትዮጵያ እንዳትረጋጋ እያደረገች ነው - ሪፖርትቢቢሲ--አማርኛJuly 2, 2025ኤርትራ ተጥሎባት የነበረው የጦር መሳሪያ ማዕቀብ መነሳቱን ተከትሎ ሠራዊቷን መ...
03/07/2025

ኤርትራ ሠራዊቷን እያጠናከረች፣ ኢትዮጵያ እንዳትረጋጋ እያደረገች ነው - ሪፖርት

ቢቢሲ--አማርኛ
July 2, 2025

ኤርትራ ተጥሎባት የነበረው የጦር መሳሪያ ማዕቀብ መነሳቱን ተከትሎ ሠራዊቷን መልሳ በማጠናከር በአካባቢው በተለይም በኢትዮጵያ መረጋጋት እንዳይኖር እያደረገች ነው ሲል አንድ የአሜሪካ መንግሥታዊ ያልሆነ ድርጅት ሪፖርት አመለከተ።

ኤርትራ ግን የቀረበባት ክስ የፈጠራ እና ማሳበቢያ ነው በማለት በአካባቢው ለተፈጠረው ውጥረት ተጠያቂያዋ ኢትዮጵያ ናት ስትል ከስሳለች።

'ዘ ሴንትሪ' የተባለው የአሜሪካ የመብቶች ተከታታይ መንግሥታዊ ያልሆነው ድርጅት ሰኞ ዕለት ባወጣው ሪፖርት ኤርትራ ተጥሎባት የነበረው የጦር መሳሪያ ማዕቀብ ከሰባት ዓመት በፊት ከተነሳ በኋላ ሠራዊቷን መልሳ በመገንባት እና በማጠናከር "በጎረቤቶቿ በተለይም በኢትዮጵያ ውስጥ አለመረጋጋት እየፈጠረች ነው" ብሏል።

ከደም አፋሳሽ የድንበር ጦርነት በኋላ ከሁለት አስርት ዓመታት በላይ በፍጥጫ ውስጥ የቆዩት ኢትዮጵያ እና ኤርትራ በ2010 ዓ.ም. የሰላም ስምምነት መፈራረማቸውን ተከትሎ በተባባሩት መንግሥታት ተጥሎባት የነበረው የጦር መሳሪያ ማዕቀብ እንደተነሳላት ይታወሳል።

"የተጣለባት ማዕቀብ በተነሳበት በአሁኑ ወቅት ኤርትራ ጦር ሠራዊቷን መልሳ እያገነባች፣ የመከላከያ ኃይሏን እያጠናከረች እና ጎረቤቶቿ እንዳይረጋጉ ማድረጓን ቀጥላለች" ሲል የአሜሪካው መንግሥታዊ ያልሆነ ድርጅት 'ዘ ሴንትሪ' ያወጣው ሪፖርት ላይ አመልክቷል።

ሪፖርቱ አክሎም "ያለው ሁኔታ ሳይቀየር ባለበት የሚቀጥል ከሆነ [ኤርትራም] እያደረገች ባለው ትቀጥላለች ተብሎ ይጠበቃል" ሲል አስጠንቅቋል።

'ዘ ሴንትሪ' ባወጣው ሪፖርት በኤርትራ ላይ የቀረበውን ክስ በተመለከተ በፈረንሳይ ዜና ወኪል፣ ኤኤፍፒ የተጠየቁት የማስታወቂያ ሚኒስትሩ የማነ ገብረመስቀል "የፈጠራ ትርክት" በማለት ሪፖርቱ የሌሎችን ድርጊት በኤርትራ ላይ "የሚያላክክ" ነው በማለት አጣጥለውታል።

ሚኒስትሩ አክለውም "በቀጣናው ለተፈጠረው አዲስ ውጥረት ምክንያቱ ኢትዮጵያ ከሕግ ውጪ በይፋ ወደብ እና የባሕር ጠረፍ የማግኘት ፍላጎት እንዳላት ማሳወቋ" መሆኑን በመጥቀስ ኢትዮጵያን ተጠያቂ አድርገዋል።

ባለፈው በዚህ ዓመት አጋማሽ ላይ የኤርትራ መንግሥት የቀድሞ የሠራዊት አባላት ወደ የክፍሎቻቸው ለዳግም ሥልጠና እንዲመለሱ እና ሌሎች ዜጎቹ ከአገር ለመውጣት የሚጠበቅባቸውን መስፈርቶች ማጥበቁን ቢቢሲ መዘገቡ ይታወሳል።

በዚህም ከ60 ዓመት በታች የሆኑ በኤርትራ ሠራዊት ውስጥ ያገለገሉ ዜጎች ተመዝግብው ወደ ማሠልጠኛ እንዲገቡ፤ እንዲሁም ከ50 ዓመት በታች የሆኑ ሰዎች ደግሞ ተገቢውን ፈቃድ ከሚመለከተው የመንግሥት አካል ሳያገኙ ከአገር እንዳይወጡ ዕገዳ መጣሉን ነዋሪዎች ተናግረዋል።

በትግራይ ጦርነት አንድ ላይ ቆመው የትግራይ ኃይሎችን የወጉት የኤርትራ እና የኢትዮጵያ መንግሥታት ወዳጅነታቸው መቀዛቀዝ የጀመረው ጦርነቱን ያበቃው የፕሪቶሪያ ስምምነት ከተፈረመ በኋላ ነው።

በተጨማሪም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ኢትዮጵያ የባሕር በር የማግኘት ጉዳይ የኅልውና ጉዳይ መሆኑን በይፋ ካሳወቁ በኋላ የሁለቱ አገራት ግንኙነት ወደ ውዝግብ እና መካሰስ ተሸጋግሯል።

የኢትዮጵያ መንግሥት ባለሥልጣናት ኤርትራ በውስጥ ጉዳያቸው ጣልቃ እየገባች ታጣቂዎችን እየደገፈች ነው የሚል ተደጋጋሚ ክስ ሲያቀርቡ የቆዩ ሲሆን፣ በቅርቡም የኤርትራ ኃይሎች ከያዟቸው የኢትዮጵያ ግዛቶች እንዲወጡ ተጠይቋል።

ከሁለቱም አገራት ከፍተኛ ባለሥልጣናት እና መገናኛ ብዙኃን በተደጋጋሚ የሚሰማው ንግግር ዳግም ጦርነት ሊፈነዳ ይችላል የሚል ስጋትን ፈጥሯል።

ኤርትራ ወ

በትግራይ ክልል ወጀራት በተባለው ወረዳ በትግራይ ኃይሎች እና በሌሎች ታጣቂዎች መካከል ግጭት ተፈጠረግጭቱ የተከሰተው በትግራይ ክልል ደቡባዊ ዞን ሰንዓለ የዞኑ አካባቢ በሁለቱ የታጠቁ ኃይሎች...
03/07/2025

በትግራይ ክልል ወጀራት በተባለው ወረዳ በትግራይ ኃይሎች እና በሌሎች ታጣቂዎች መካከል ግጭት ተፈጠረ

ግጭቱ የተከሰተው በትግራይ ክልል ደቡባዊ ዞን ሰንዓለ የዞኑ አካባቢ በሁለቱ የታጠቁ ኃይሎች መካከል ማክሰኞ ሰኔ 24/2017 ዓ.ም. አመሻሽ ከ10 አስከ 11 ሰዓት ባለው ጊዜ ውስጥ መሆኑን ነዋሪዎች ተናግረዋል።

ግጭቱ በአካባቢው ነዋሪዎች ላይ ስጋት እና ፍራቻ የፈጠረ ሲሆን፣ የአካባቢው የአገር ሽማግሌዎች በሁለቱ ታጣቂዎች መካከል ገብተው ለማሸማገል መሞከራቸውን የቢቢሲ ምንጮች ገልጸዋል።

ከትግራይ ኃይሎች ጋር ግጭት ውስጥ የገቡት ታጣቂዎች እስካሁን ድረስ ይፋዊ ስም ባይኖራቸውም በተለምዶ 'የነጻ መሬት ተዋጊዎች' በመባል ይታወቃሉ።

በሁለቱ ታጣቂ ኃይሎች መካከል የተፈጠረውን ፍጥጫ እና ተኩስ በተመለከተ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር አስካሁን ያለው ነገር የለም።

ይህ ማክሰኞ ዕለት ያጋጠመውን ግጭት ታጣቂዎቹ ከትግራይ ክልል ጋር ከሚዋሰነው ከአፋር ክልል ወደ ወጀራት ወረዳ እንደገቡ ከሰዓት በኋላ መሆኑን ነዋሪዎች ይገልጻሉ።

ቢቢሲ ከአካባቢው ነዋሪዎች እንዳረጋገጠው ከእሁድ ምሽት አንስቶ አስከ ሰኞ ድረስ . . . ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው 'የነጻ መሬት' ታጣቂዎች ወደ ሰንዓለ አካባቢ ገብተዋል።

ታጣቂዎቹ ወደ አከባቢው መግባታቸውን ተከትሎ የተቆጡት የትግራይ ኃይሎች በአካባቢው ተኩስ እንደከፍቱባቸው ነዋሪዎች ለቢቢሲ ተናግረዋል።

በሰንዓለ ነዋሪ እና የአገር ሽማግሌ የሆኑት አቶ ግደይ አለመን ሐጎስ "ተፋላሚዎቹ ሁሉም የትግራይ ተወላጆች ናቸው። እነኚ የነጻ መሬት ታጣቂዎች እሁድ ምሽት ከመጋሌ [ከአፋር ክልል] ተጕዞው ሰኞ ከጥዋቱ 12:00 ሰዓት ሰንዓለ ታይተዋል" ብለዋል።
ነገር ግን በአካባቢው ያሉት የትግራይ ኃይሎች ታጣቂዎቹን 'ለምን መጡ?' በማለት መፋጠጣቸውን እና ሁለቱም ቦታ ይዘው "ለመፋለም ሞክረው ነበር" በማለት የአገር ሽማግሌው አስረድተዋል።

ይህንም ተከትሎ በሰንዓለ ለረጅም ጊዜ እንደቆዩ የሚነገርላቸው የትግራይ ኃይል አባላት በታታቂዎቹ ላይ ከሦስት እስከ አራት ጊዜ ዲሽቃ [ከባድ መትረየስ] ተኩሰዋል።

የአካባቢው ነዋሪዎች እንዳሉት ከማክሰኞ 10 ሰዓት ጀምሮ የትግራይ ኃይሎች ቀድመው ታጣቂዎቹ ላይ ተኩስ ከፍተው የጥይት ድምጽ መሰማቱን ተናግረዋል።

'የነጻ መሬት' ታጣቂዎች በድንገት ወደ አካባቢው ከገቡ በኋላ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ተጨማሪ የትግራይ ኃይል አባላት ወደ አካባቢው መሰማራታቸውን የአካባቢው ነዋሪዎች ለቢቢሲ አረጋግጠዋል።

ሁኔታው በሕዝቡ ላይ ስጋት መፍጠሩን የገለፁት ነዋሪዎቹ ጉዳዩን ለማረጋጋት የአካባቢው የአገር ሽማግሌዎች ጥረት አድርገዋል።
ሻለቃ ገብረ አብርሃ ግጭቱን ለማረጋጋት ሁለቱን የታጠቁ ኃይሎች እስከ ምሽቱ ቢቢሲ ያነጋገራቸው ስማቸው እንዲገለጽ ያልፈለጉ የነጻ መሬት ታጣቂ ኃይል አንድ የግንባር አመራር በወጀራት ወረዳ የተከሰተውን ግጭት አረጋግጠው፤ ከአካባቢው የአገር ሽማግሌዎች ጋር በመግባባት ከሰንዓለ ቢወጡም አሁንም ወጀራት ወረዳን ጨምሮ ታጣቂዎቻቸው በብዙ የትግራይ አካባቢዎች እንደሚገኙ ተናግረዋል።

ተቀናቃኙ ኃይል "በውስጥ እንወያይ እያሉ ነው። ነገር ግን ይህ ለመዘጋጀት ጊዜ መግዣ ስልት ነው፣ ወደ ትግራይ ይገባሉ ብለው አልጠበቁም ነበር፤ አሁን እንደገባን ግን መንጫጫት ጀመሩ፣ እንደራደር እያሉን ነው።

"እስካሁን ግን እንደራደር እያሉ ሠራዊት እያስገቡ ነው፤ እኛ አንደራደርም አንልም፤ ነገር ግን ሥራችንን እየሠራን ነው የምንደራደረው።

ምክንያቱም በታሪካቸው እንደራደራለን ብለው ስብሰባ ጠርተው ታጋዮች ገድለው ነው ያደሩት" ብሏል።

BBC

አቶ ዓምዶም ገብረስላሴ የመድረክ ሊቀመንበር ሆኑ📌ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና ምክትል ሊቀመንበርና የውጭ ጉዳይ ኃላፊ ሆነዋል።  | የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ (መድረክ) " ...
29/06/2025

አቶ ዓምዶም ገብረስላሴ የመድረክ ሊቀመንበር ሆኑ

📌ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና ምክትል ሊቀመንበርና የውጭ ጉዳይ ኃላፊ ሆነዋል።

| የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ (መድረክ) " ታሪካዊ " ሲል የጠራውን ጠቅላላ ጉባዔውን አካሂዶ አዲስ አመራር መምረጡን ይፋ አደረገ።

" በሀገሪቱ ብቸኛው ቀዳሚ የብሔር ብሔረሰቦች የፖለቲካ ጥምረት " እንደሆነ የገለጸው መድረክ 17ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔውን በተሳካ ሁኔታ በማካሄድ የውስጥ መነቃቃቱን የሚያበስር ወሳኝ እርምጃ እንደወሰደ ገልጿል።

በግንባሩ ጽ/ቤት የተካሄደው ጉባዔ፣ አዲስ አመራር በመምረጥና እውነተኛ ዴሞክራሲያዊትና ሰላማዊ #ኢትዮጵያን ለመገንባት የሚያስችል ስትራቴጂካዊ አቅጣጫ በማስቀመጥ መጠናቀቁን አሳውቋል።

አዲስ የተመረጠው አመራር፣ ወጣት አመራሮችን ከተመክሮና ልምድ ካካበቱ አንጋፋ ፖለቲከኞች ጋር በስትራቴጂካዊ ቅንጅት ያካተተ እንደሆነና ይህም መድረክ የኢትዮጵያን ውስብስብ ፖለቲካዊ ተግዳሮቶች በብቃት እንዲወጣ እንደሚያስችለው አመልክቷል።

አዲሱ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ሆነው እነማን ተመረጡ ?

1. አቶ ዓምዶም ገብረስላሴ ፦ የመድረክ ሊቀመንበር
2. አቶ ሱልጣን ቃሲም፦ ምክትል ሊቀመንበርና የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ
3. ወ/ሮ መርየም ሓሰን ፦ ምክትል ሊቀመንበርና የፋይናንስ ጉዳይ ኃላፊ
4. አቶ ሙላቱ ገመቹ፦ ተቀዳሚ ምክትል ሊቀመንበርና የህዝብ ድርጅት ጉዳይ ኃላፊ
5. ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና ፦ ምክትል ሊቀመንበርና የውጭ ጉዳይ ኃላፊ
6. አቶ ለገሰ ለንቃሞ፦ የመድረክ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ
7. አቶ ደስታ ዲንቃ፦ የመድረክ ምክትል ጽህፈት ቤት ኃላፊ ሆነው ተመርጠዋል።

መድረክ ፦
- ዓረና ትግራይ ለዲሞክራሲና ሉዓላዊነት (ዓረና)፣
- የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ (ኦፌኮ)፣
- የሲዳማ አርነት ንቅናቄ (ሲአን) እና የዓፋር ህዝብ ፍትህና ዲሞክራሲ ፓርቲን በአባልነት አቅፏል።

28/06/2025

ሰላም የሮሃ ሚዲያ ቤተሰቦቻችንን ወደ እናንተ እያደረሱ ካሉ ዜናዎችን እንድታበርታቱ እና ድጋፍ እንድታደርጉስንል በአክብሮት እንጠይቃቺዎልን።

#ሮሃሚዲያ

ህዝቡን በኑሮና በጦርነት ያሰከረው የብልፅግና  ባለሥልጣን በዉስኪ ሰክሮ በማሽከርከር አደጋ ደርሶበት ሆስፒታል ገብተዋል። ኮማ ውስጥ ያለው ካሳሁን ጎንፋ የብልፅግና ሚንስቴር ከመጠን ያለፈ ሰ...
28/06/2025

ህዝቡን በኑሮና በጦርነት ያሰከረው የብልፅግና ባለሥልጣን በዉስኪ ሰክሮ በማሽከርከር አደጋ ደርሶበት ሆስፒታል ገብተዋል። ኮማ ውስጥ ያለው ካሳሁን ጎንፋ የብልፅግና ሚንስቴር ከመጠን ያለፈ ሰክሮ መኪና ሲነዳ ከቆመ ኤክስካቬተር ጋር ተጋጭቶ መጎዳቱ ተሰምቷል:: ህዝቡ በኑሮ ውድነት በብልፅግና ባቡር ይነዳል እነሱ በዉስኪ !

“ለዛ ለአሮጌ ባቡር ሸከተፍ ሸከተፍ እያላችሁ  የዘፈናችሁት እነ ጋሽ አበራ ሞላ፤ እንዴት ለጣና ነሽ አንድ  ነጠላ ዜማ መልቀቅ  አቃታችሁ?! -ስለ ከዚራ የዛፍ  ጥላ የዘፈኑት እነ ማህሙድ ...
18/06/2025

“ለዛ ለአሮጌ ባቡር ሸከተፍ ሸከተፍ እያላችሁ የዘፈናችሁት እነ ጋሽ አበራ ሞላ፤ እንዴት ለጣና ነሽ አንድ ነጠላ ዜማ መልቀቅ አቃታችሁ?! -ስለ ከዚራ የዛፍ ጥላ የዘፈኑት እነ ማህሙድ አህመድ እና እነ ሀይማኖት ግርማ -እንዴት ጨበራ ጩርጩራን ሳያዩት ቀሩ!? “አየናት መርካቶ እያላችሁ በአሮጌ ሰፈር ሕዝብ ስታስጨፍሩ ከርማችሁ፤ ለእኛ ኮሪደር ልማት እንዴት አንድ ዘፈን አጣችሁልኝ?! በውን ዓለም ለማታውቋት ሞናሊዛ ደጋግማችሁ ስትዘፍኑ፤ስንት ትምህርት ቤትና ዳቦ ቤት ላሠራችላችሁ ለዝናሽ ያልዘፈናችሁት፦ ሞገስ ግጥም አልጽፍም ብሏችሁ ነው!? ወይስ ካሙዙ አላቀናብርም ብሏችሁ ነው!?ሌላው ቀርቶ ቀደም ባሉት ዓመታት ለቢጫ ወባ ዘፍናችሁ - በእኛ ጊዜ MPOX ሲከሰት -ሁላችሁም ምንም እንዳልተፈጠረ ዝም ብላችኋል! በጣም ያሳዝናል!!”

የአማራ ክልል መንግሥት የክልሉን 90 በመቶ እንደሚቆጣጠር የኮሚኒኬሽን ሚኒስትሩ ተናገሩሚኒስትሩ 'ኤንቢሲ' ከተባለ የአገር ውስጥ የቴሌቪዥን ጣቢያ ጋር ባደረጉት ዘለግ ያለ ቃለ ምልልስ ስለ ...
07/05/2025

የአማራ ክልል መንግሥት የክልሉን 90 በመቶ እንደሚቆጣጠር የኮሚኒኬሽን ሚኒስትሩ ተናገሩ

ሚኒስትሩ 'ኤንቢሲ' ከተባለ የአገር ውስጥ የቴሌቪዥን ጣቢያ ጋር ባደረጉት ዘለግ ያለ ቃለ ምልልስ ስለ አማራ ክልል የፀጥታ ሁኔታ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
ክልሉ "የኅልውና አደጋ" ውስጥ ገብቶ ነበር ያሉት የኮሚኒኬሽን ሚኒስትሩ፤ በአሁኑ ጊዜ 90 በመቶ የክልሉ አካባቢዎችን መንግሥት መቆጣጠሩን ተናግረዋል።

የፋኖ ኃይሎች በበኩላቸው ከ80 በመቶ በላይ የክልሉ አካባቢው በእጃቸው እንደሆነ በተለያዩ ጊዜያት ሲናገሩ ተደምጠዋል።

ባለፉት ሁለት ዓመታት በመንግሥት ኃይሎች እና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል የሚካሄደው ግጭት አሁንም ድረስ መቀጠሉን ከሁቱም ወገኖች የሚወጡ መረጃዎች ያመለክታሉ።
ነገር ግን በአሁኑ ወቅት "የክልሉ መንግሥት ተጠናክሯል፤ አደረጃጀቱን እስከ ቀበሌ አጠናክሯል። በአብዛኛው 90 በመቶ በሚሆነው አካባቢ ክልሉ በራሱ ታጣቂ፣ አስተዳደር፣ የፀጥታ ሁኔታውን የሚቆጣጠርበት ሁኔታ ተፈጥሯል" ሲሉ ሚኒስትሩ ተናግረዋል።
ከቁጥጥሩ ውጪ የሆኑትን አካባቢዎችን በተመለከተ ደግሞ፤ "የቀሩትን የክልሉ የፀጥታ ኃይል እና የፌደራል ኃይል በጋራ ሆነው ችግሩን የሚፈቱበት ሁኔታ እየተፈጠረ ነው" ብለዋል።

"በድርድር እና ሕግ በማስከበር እንቅስቃሴ በአብዛኛው የክልሉ አካባቢዎች ሰላማዊ ሁኔታ ተፈጥሯል" ቢሉም ሚኒስትሩ፤ የክልሉ ነዋሪዎች ግን ማኅበራዊ እንቅስቃሴዎችን ጨምሮ የእለት ከዕለት ሕይወታቸው በግጭቱ መስተጓጎሉን ይናገራሉ።

ሚኒስትሩ ከቴሌቪዥን ጣቢያው ጋር ባደረጉት ቆይታ አጠቃላይ የአገሪቱን የሰላም እና የፀጥታ ሁኔታ ያነሱ ሲሆን፤ "ኢትዮጵያ ወደ ተሟላ የሰላም ሁኔታ መጥታለች" ሲሉ ሁለት የተቃርኖ ሀሳቦች መኖራቸውን ገልፀዋል።
"መሬት ላይ ያለው እውነታ እና የሰዎች አረዳድ የተለያዩ ናቸው" ሲሉ እገታ፣ ዝርፊያ እና የንብረት ውድመት የመሰሉ ክስተቶችን በማንሳት ይህ ሁኔታ "በየትኛውም አገር ይኖራል" ሲሉ ዶ/ር ለገሰ ተናግረዋል።

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስ በቫቲካን በሚገኘው ካሳ ሳንታ ማርታ መኖሪያ ቤታቸው ዛሬ ሰኞ፣ የልደት በዓላቸው ላይ በ88 ዓመታቸው ከዚህ...
21/04/2025

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስ በቫቲካን በሚገኘው ካሳ ሳንታ ማርታ መኖሪያ ቤታቸው ዛሬ ሰኞ፣ የልደት በዓላቸው ላይ በ88 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።

ዜና ሹመት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሚያዝያ 3 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ አቶ ጌታቸው ረዳን የምስራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር አድርገው ሾመዋል።
11/04/2025

ዜና ሹመት

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሚያዝያ 3 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ አቶ ጌታቸው ረዳን የምስራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር አድርገው ሾመዋል።

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ሮሃ ሚዲያ / Roha Media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category