Prime Media - አማርኛ

Prime Media - አማርኛ Prime Media is an East African regional media organization that aims to educate, entertain, &inspire
Voice of Reason

07/07/2025
07/07/2025

የህገር መከልከያ ዜናዎች | Prime News | Prime Media

Subscribe to our YouTube channel shorturl.at/dklLO
Prime Media is an East African regional media organization that aims to educate, inspire, entertain & empower people & to strengthen the social, economic, political and democratic institutions in the region.

For More:
Watch Prime Media World on Ethiosat with 11165 Frequency |Watch Prime Media World
| | ​ | ​ | | |​ | | |

Youtube➡️: https://www.youtube.com/c/PrimeMediaPM
Fb AfaanOromoo ➡️ https://www.facebook.com/PrimeMediaPM/
Fb Amharic➡️ https://web.facebook.com/PrimeMediaAm/ FB Primesport ➡️ https://web.facebook.com/primesportet/
Telegram Afaan Oromoo➡️: http://t.me/PrimeMediapm
Telegram Amharic➡️ https://t.me/primediaAm
Telegram Prime Sport➡️ https://t.me/primediasport
Tiktok➡️ https://www.tiktok.com/.tv

07/07/2025

የዬዌሪ ሙሴቬኒ ቀጣይ የምርጫ ፍላጎት | Prime News | Prime Media

Subscribe to our YouTube channel shorturl.at/dklLO
Prime Media is an East African regional media organization that aims to educate, inspire, entertain & empower people & to strengthen the social, economic, political and democratic institutions in the region.

For More:
Watch Prime Media World on Ethiosat with 11165 Frequency |Watch Prime Media World
| | ​ | ​ | | |​ | | |

Youtube➡️: https://www.youtube.com/c/PrimeMediaPM
Fb AfaanOromoo ➡️ https://www.facebook.com/PrimeMediaPM/
Fb Amharic➡️ https://web.facebook.com/PrimeMediaAm/ FB Primesport ➡️ https://web.facebook.com/primesportet/
Telegram Afaan Oromoo➡️: http://t.me/PrimeMediapm
Telegram Amharic➡️ https://t.me/primediaAm
Telegram Prime Sport➡️ https://t.me/primediasport
Tiktok➡️ https://www.tiktok.com/.tv

07/07/2025

የሽገር የኢንቨስትመንት ኤክስፖ 2025 መጠናቀቅ | Prime News | Prime Media

Subscribe to our YouTube channel shorturl.at/dklLO
Prime Media is an East African regional media organization that aims to educate, inspire, entertain & empower people & to strengthen the social, economic, political and democratic institutions in the region.

For More:
Watch Prime Media World on Ethiosat with 11165 Frequency |Watch Prime Media World
| | ​ | ​ | | |​ | | |

Youtube➡️: https://www.youtube.com/c/PrimeMediaPM
Fb AfaanOromoo ➡️ https://www.facebook.com/PrimeMediaPM/
Fb Amharic➡️ https://web.facebook.com/PrimeMediaAm/ FB Primesport ➡️ https://web.facebook.com/primesportet/
Telegram Afaan Oromoo➡️: http://t.me/PrimeMediapm
Telegram Amharic➡️ https://t.me/primediaAm
Telegram Prime Sport➡️ https://t.me/primediasport
Tiktok➡️ https://www.tiktok.com/.tv

07/07/2025

የዜግነት አገልግሎት ተግባር | Prime News | Prime Media

Subscribe to our YouTube channel shorturl.at/dklLO
Prime Media is an East African regional media organization that aims to educate, inspire, entertain & empower people & to strengthen the social, economic, political and democratic institutions in the region.

For More:
Watch Prime Media World on Ethiosat with 11165 Frequency |Watch Prime Media World
| | ​ | ​ | | |​ | | |

Youtube➡️: https://www.youtube.com/c/PrimeMediaPM
Fb AfaanOromoo ➡️ https://www.facebook.com/PrimeMediaPM/
Fb Amharic➡️ https://web.facebook.com/PrimeMediaAm/ FB Primesport ➡️ https://web.facebook.com/primesportet/
Telegram Afaan Oromoo➡️: http://t.me/PrimeMediapm
Telegram Amharic➡️ https://t.me/primediaAm
Telegram Prime Sport➡️ https://t.me/primediasport
Tiktok➡️ https://www.tiktok.com/.tv

በበጀት ዓመቱ የኢትዮጵያን ነባራዊ ሁኔታ የሚያስረዱና ከሀገራት ጋር ያለውን ግንኙነት የሚያጠናክሩ የፓርላማ ዲፕሎማሲ ሥራዎች ተከናውነዋልፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)ሰኔ 30/2017 ዓ.ምበ20...
07/07/2025

በበጀት ዓመቱ የኢትዮጵያን ነባራዊ ሁኔታ የሚያስረዱና ከሀገራት ጋር ያለውን ግንኙነት የሚያጠናክሩ የፓርላማ ዲፕሎማሲ ሥራዎች ተከናውነዋል

ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)ሰኔ 30/2017 ዓ.ም

በ2017 በጀት ዓመት የኢትዮጵያን ነባራዊ ሁኔታ የሚያስረዱና ከሀገራት ጋር ያለውን ግንኙነት የበለጠ የሚያጠናክሩ የፓርላማ ዲፕሎማሲ ሥራዎች መከናወናቸውን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምክትል አፈ-ጉባኤ ሎሚ በዶ ገለጹ።

ምክትል አፈ ጉባኤዋ ይህን ያሉት ምክር ቤቱ ባካሄደው 3ኛ ልዩ ስብሰባ ላይ የበጀት ዓመቱን የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ሲያቀርቡ ነው።

በዚሁ ወቅት በምክር ቤቱ ባሉ 16 የወዳጅነት ቡድኖች የተለያዩ የፓርላሜንታዊ ዲፕሎማሲ ሥራዎች መሰራታቸውን ነው ያብራሩት።

ከዚህ ውስጥ የምክር ቤት ከፍተኛ አመራሮች በጄኔቫ በተደረገ የዓለም ፓርላማ ኅብረት(IPU) ላይ መሳተፋቸውንና ከደቡብ ሱዳንና ናሚቢያ ከመጡ የፓርላማ አባላት ጋር የልምድ ልውውጥ መደረጉን ገልጸዋል።

በኡጋንዳ በተካሄደ የምሥራቅ አፍሪካ ሀገራት የፓርላማ ትብብር ጉባኤ ላይ የተሳተፉ የቋሚ ኮሚቴ አባላት ኢትዮጵያ በግብርናና በምግብ ራስን ለመቻል እያደረገች ስላለው ስኬታማ ስራዎች ማስረዳታቸውን አንስተዋል።

በቋሚ ኮሚቴ ደረጃና በወዳጅነት ቡድኖች ከሀገራት ጋር ያለውን ግንኙነት ለማጠናከር ዘርፈ ብዙ ስራዎችን መሰራታቸውንም ተናግረዋል።

በዚህም በንግድና ኢንቨስትመንት፣ በቴክኖሎጂና ጤናን ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች የልምድ ልውውጦች መደረጋቸውን ነው ያነሱት።

በበጀት ዓመቱ የኢትዮ-ፈረንሳይ፣ ኢትዮ-እስራኤል፣ ኢትዮ-አዘርባጃን፣ ኢትዮ-ደቡብ ኮሪያ፣ ኢትዮ-ጀርመን፣ ኢትዮ-ሞንጎሊያ፣ ኢትዮ-ኢራን፣ ኢትዮ-ፊንላንድ፣ ኢትዮ-ቻይና፣ የኢትዮ-ፓኪስታን፣ ኢትዮ-ካዛኪስታንና የኢትዮ-ስዊድን የወዳጅነት ቡድኖች ጋር ፍሬያማ ውይይቶች ተደርገዋል ብለዋል።

ከኢትዮ-ግሪክ የወዳጅነት ቡድን አባላት ጋር በፓርላማ ዲፕሎማሲ፣ በቴክኖሎጂ፣ በባህር ትራንስፖርት፣ በቱሪዝምና ኮንስትራክሽን ዘርፍ አብሮ ለመሥራት ያለመ ውይይት መደረጉን አንስተዋል።

በበጀት ዓመቱ በምክር ቤት ደረጃ 3 እና በቋሚ ኮሚቴዎች 22 በድምሩ 25 የፓርላማ ልዑካን ቡድን፣ የወዳጅነት ቡድን እና ሀገራት ጋር የጠንካራ ዲፕሎማሲ ሥራዎች መከናወናቸውን እንዲሁ ተገልፁል።

Social Media Links

Youtube➡️: https://www.youtube.com/c/PrimeMediaPM

FB AfaanOromoo ➡️ https://www.facebook.com/PrimeMediaPM/

FB Primesport ➡️ https://web.facebook.com/primesportet/

FB English ➡️ https://www.facebook.com/profile.php?id=61576239091981

Telegram Afaan Oromoo➡️: http://t.me/PrimeMediapm

Telegram Prime Sport➡️ https://t.me/primediasport

Tiktok➡️ https://www.tiktok.com/.tv

ከሽገር የኢንቨስትመንት ኤክስፖ 2025 ያቀድነዉን አግኝተናል፡- ከንቲባ ተሾመ አዱኛ ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)ሰኔ 30/2017 ዓ.ምየሸገር ኢንቨስትመንት ኤክስፖ 2025 የማጠቃለያ መርህ ...
07/07/2025

ከሽገር የኢንቨስትመንት ኤክስፖ 2025 ያቀድነዉን አግኝተናል፡- ከንቲባ ተሾመ አዱኛ

ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)ሰኔ 30/2017 ዓ.ም

የሸገር ኢንቨስትመንት ኤክስፖ 2025 የማጠቃለያ መርህ ግብር ተከናውኗል ።

በመረሃ ግብሩ የመዝግያ ንግግር ያደረጉት የሸገር ከተማ ከንቲባ ተሾመ አዱኛ(ዶ/ር) ከሽገር የኢንቨስትመንት ኤክስፖ 2025 ያቀድነዉን አግኝተናል ብለዋል ።

ሽገር ከተማ ያላትን እምቅ የኢንቨስትመንት አቅም እንደምስራቅ አፍሪካ ማሳየት ችለናል ብለዋል።

በኤክስፖው ከአለማቀፍ ባለሃብቶችና አምራቾች ልምድ የተቀሰመበትና ከ190 በላይ አምራቾች ምርቶቻቸውን አስተዋውቀዋል ብለዋል።

ሸገር አርሶ አደሩን እቅፍ የተመስረተች የኢኮኖሚ ከተማ መሆንዋንም እስመስክራለች ብለዋል።

የኢንደስትሪ ሚንስትር አቶ መላኩ አለበል ኢትዮጵያ እራስዋን እንድትችል ኢትዮጵያ ታምርትን ጅምረናል ብለዋል ።

ይሄም ውጤት እያስመዘገበ መሆኑን በዚህ ኤክስፖ አይቻለሁ ብለዋል ።

በዚህ ኤክስፖ በኢንደስትሪው ዘርፍ ያላችሁ አምራቾች አርበኛ መሆናችሁን አረጋግጫለሁም ብለዋል ።

የኛዘመን አርበኝነት ማምረትና የስራ እድል መፍጠር መሆኑን ጠቁሟል።

ብልጽግናን የምናረጋግጠው በማምረት ነው ሲሉም አክለዋል ።

በማጠቃሉያ ፕሮግራም ላይ ለመረሃ ግብሩ መሳካት አስቱዋጽኦ ላበረከቱ አካላት የእውቅናና ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።

Social Media Links

Youtube➡️: https://www.youtube.com/c/PrimeMediaPM

FB AfaanOromoo ➡️ https://www.facebook.com/PrimeMediaPM/

FB Primesport ➡️ https://web.facebook.com/primesportet/

FB English ➡️ https://www.facebook.com/profile.php?id=61576239091981

Telegram Afaan Oromoo➡️: http://t.me/PrimeMediapm

Telegram Prime Sport➡️ https://t.me/primediasport

Tiktok➡️ https://www.tiktok.com/.tv

07/07/2025

17ኛው የብሪክስ ጉባዔ | Prime News | Prime Media Subscribe to our YouTube channel shorturl.at/dklLO
Prime Media is an East African regional media organization that aims to educate, inspire, entertain & empower people & to strengthen the social, economic, political and democratic institutions in the region.

For More:
Watch Prime Media World on Ethiosat with 11165 Frequency |Watch Prime Media World
| | ​ | ​ | | |​ | | |

Youtube➡️: https://www.youtube.com/c/PrimeMediaPM
Fb AfaanOromoo ➡️ https://www.facebook.com/PrimeMediaPM/
Fb Amharic➡️ https://web.facebook.com/PrimeMediaAm/ FB Primesport ➡️ https://web.facebook.com/primesportet/
Telegram Afaan Oromoo➡️: http://t.me/PrimeMediapm
Telegram Amharic➡️ https://t.me/primediaAm
Telegram Prime Sport➡️ https://t.me/primediasport
Tiktok➡️ https://www.tiktok.com/.tv

ሽገር ከተማ አርሶ አደሩን ይዞ ለማደግና ለማሻገር የተመሰረተና እየሰራ ያለ የወደፊቱ ከተማ ነው:- ከንቲባ ተሾመ አዱኛ ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)ሰኔ 30/2017 ዓ.ምሸገር ከተማ አስተዳደ...
07/07/2025

ሽገር ከተማ አርሶ አደሩን ይዞ ለማደግና ለማሻገር የተመሰረተና እየሰራ ያለ የወደፊቱ ከተማ ነው:- ከንቲባ ተሾመ አዱኛ

ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)ሰኔ 30/2017 ዓ.ም

ሸገር ከተማ አስተዳደር 2025የኢንቨስትመንት ኤክስፖ ላይ ወደ ኢንቨስትመንት ከተሸጋገሩት አርሶ አደሮች ጋር በአዲስ ኮንቬንሽን ሴንተር ተወያይቷል።

በመድረኩም ላይ አርሶ አደሮች የተለያዩ ጥያቄዎችን አንስተዋል።

አርሶ አደሮች ካነስዋቸዉ ጥየቄዎችም በኮሪደር ልማት ተተኪ ቦታዎች ቢሰጡ፣በሲንቄ ባንክ አስፈላጊው ብድር ቢመቻች፣የዉሃ የመብራትና የመንገድ መሰረተ ልማቶች ቢሟሉልን ብለዋል ።

በመድረኩ መልስ የሰጡት በምክትል ፕሬዚዳንት ማእረግ የሸገር ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ዶ/ር ተሾመ አዱኛ ሸገር ከተማ አርሶ አደሩን ይዞ ለማደግና ለማሻገር የተመሰረተና እየሰራ ያለ የወደፊቱ ከተማ ነው ብለዋል።

ነገር ግን በአርሶ አደሮች ስም የሸገርን መሬት በህገወጥ መንገድ የሚመዘብሩ እንዳሉ እናቃለን ያሉት ከንቲባዉ አስፈላጊውን እርምጃ እንወስዳለን እናንተም ከራሳችሁ ዉስጥ ለይታችሁ ማውጣት አለባችሁ ብለዋል።

በኮሪደር ልማት 8 ቢሊዮን ብር መድበን ወደስራ ገብተናል ያሉት ከንቲባው በኮሪደር ልማት ማንም ሰው እንዳይጎዳ ጥንቃቄ አድርገናል እና ህጋዊ መሰረት ላላቸዉ መኖርያ ቤትም ሰተናል ብለዋል ።

የአርሶ አደሩን ህይወት ለመቀየር 8000 ሼዶችን ፤ 260 የገበያ ማእከልን፤ 2600 የጎጆ ኢንደስትሪና በየክፍለ ከተማው
ፋርመር ቪሌጅ እንዲኖር ሰርተናል ብለዋል።

አርሶ አደሩን ይዘን በመስራታችን ባንካችን አድጓል ያሉት ደግሞ የሲንቄ ባንክ ም/ፕሬዚዳንት አቶ ጌታቸው ዴሬሳ ናቸዉ ።

ባንካችን "ዲታ"በሚል አሰራር ለአርሶ አደሩ የብድር አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል ብለዋል ።

የአርሶ አደሩን የኑሮ ደረጃ ለመቀየር ቢሮክራሲውን በማሳጠር አስፈላጊው ዶክመንት ከተሟላ በ 21ቀናት በዲታ ለአርሶ አደሩ ብድር እናቀርባለን ብለዋል።

በሸገር ከተማ 32 ቅርንጫፍ አለን በሁሉም ቅርንጫፎች ለአርሶ አደራችን ሙሉ አገልግሎት እንሰጣለን ብለዋል።

ባለፈው በጀት አመት 26 ቢሊዮን ብር ለአርሶ አደር ብድር አዘጋጅተን 25 ቢሊዮን ብር ሰተናል ፤ በዘንድሮ አመት ደግሞ 68.8 ቢሊዮን ብር አዘጋጅተናል አስፈላጊው ዶክመንት ካሟላችሁ ለናንተው ነው ብለዋል።

አርሶአደሩ መሬቱን፤ቤቱንም ሆነ ያለዉን ንብረት አሲዞ አስፈላጊውን ብድር ማግኘት ይችላልም ብለዋል ።

የአርሶ አደሩን አቅም በማቀናጀት ሰፊ ስራዎችን ሰርተናል ያሉት ደግሞ የሽገር ከተማ የብልጽግና ፓርቲ ጽቤት ሃላፊ አቶ አለማየሁ ቱሉ ናቸው።

ሽገርን ለማፍረስ የሚንቀሳቀሱ አካላት እንዳሉ ይታወቃል አሁን የመጣውይ ለውጥ ያመጣችሁት እናንተ ስለሆናችሁ ለዉጡን በመጠበቅ የሀገራችንን ብልጽግናን በጋራ እናረጋግጣለን ብለዋል ።

Social Media Links

Youtube➡️: https://www.youtube.com/c/PrimeMediaPM

FB AfaanOromoo ➡️ https://www.facebook.com/PrimeMediaPM/

FB Primesport ➡️ https://web.facebook.com/primesportet/

FB English ➡️ https://www.facebook.com/profile.php?id=61576239091981

Telegram Afaan Oromoo➡️: http://t.me/PrimeMediapm

Telegram Prime Sport➡️ https://t.me/primediasport

Tiktok➡️ https://www.tiktok.com/.tv

በክልሉ በዜግነት አገልግሉት ከ30ሺህ በላይ የመምህራን መኖሪያ ቤቶቸ ይገነባሉ :- ኦሮሚያ ትምህርት ቢሮፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)ሰኔ 30/2017 ዓ.ምበኦሮሚያ ክልል በ2018 በጀት ዓመት...
07/07/2025

በክልሉ በዜግነት አገልግሉት ከ30ሺህ በላይ የመምህራን መኖሪያ ቤቶቸ ይገነባሉ :- ኦሮሚያ ትምህርት ቢሮ

ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)ሰኔ 30/2017 ዓ.ም

በኦሮሚያ ክልል በ2018 በጀት ዓመት የክረምት የዜግነት አገልግሎት 30,444 የመምህራን መኖሪያ ቤት ለመገንባት እቅድ መያዙን የክልሉ ትምህርት ቢሮ አስታወቀ ።

በ2017 የተሰሩ እንዲሁም በ2018 በጀት ዓመት የሚሰሩ የዜግነት አገልግሎት ተግባራት ላይ ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ተሰጥቷል ።

በ2018 በጀት ዓመት 66.4 ቢልዮን ብር ወጪ ሚገመቱ የዜግነት አገልግሉት ስራዎች እንደሚሰሩ ተገልጿል ።

የኦሮሚያ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ቶላ በሪሶ (ዶ/ር) ፥ በ2017 በጀት ዓመት 9 ሺህ 552 የመምህራን መኖሪያ ቤት ለመገንባት ታቅዶ ፣ 10ሺህ 181 መኖሪያ ቤቶች መገንባታቸውን ጠቁመዋል ።

በ2018 በጀት ዓመት የዜግነት አገልግሎት 30,444 የመምህራን መኖሪያ ቤቶችን ለመገንባት መታቀዱን ገልፀዋል ።

በሌላ በኩል በክልሉ በ2017 በጀት ዓመት 4,420 የቡዕረ ቦሩ ትምህርት ቤቶች መገንባታቸውን ጠቁመው ፣በአዲሱ በጀት ዓመት ተጨማሪ 2,853 የቡዕረ ቦሩ ትምህርት ቤቶችን ለመገንባት እቅድ መያዙን ቶላ (ዶ/ር) ገልፀዋል ።

በተጨማሪ በዜግነት አገልግሎት 772 የ1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መገንባታቸውን ጠቁመው ፣ በበጀት ዓመቱ ተጨማሪ 170 ትምህርት ቤቶች ይገነባሉ ብለዋል ።

የትምህርት ዘርፉ የ2018 በጀት ዓመት የዜግነት አገልግሎት ላይ ህብረተረቡና ባለድርሻ አካላት እንዲሳተፉ ጥሪ ቀርቧል ።

እየሩሳሌም ሽመልስ

Social Media Links

Youtube➡️: https://www.youtube.com/c/PrimeMediaPM

FB AfaanOromoo ➡️ https://www.facebook.com/PrimeMediaPM/

FB Primesport ➡️ https://web.facebook.com/primesportet/

FB English ➡️ https://www.facebook.com/profile.php?id=61576239091981

Telegram Afaan Oromoo➡️: http://t.me/PrimeMediapm

Telegram Prime Sport➡️ https://t.me/primediasport

Tiktok➡️ https://www.tiktok.com/.tv

በአፍሪካ በሥራ ዕድል ፈጠራ ላይ የሚደረጉ ትብብሮች እንዲሳለጡ ኢትዮጵያ በቁርጠኝነት ትሰራለች - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚልፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)ሰኔ 30/2017 ዓ.ምበአፍሪካ በሥራ ዕድ...
07/07/2025

በአፍሪካ በሥራ ዕድል ፈጠራ ላይ የሚደረጉ ትብብሮች እንዲሳለጡ ኢትዮጵያ በቁርጠኝነት ትሰራለች - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል

ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)ሰኔ 30/2017 ዓ.ም

በአፍሪካ በሥራ ዕድል ፈጠራ ላይ የሚደረጉ ትብብሮች እንዲሳለጡ ኢትዮጵያ በቁርጠኝነት ትሰራለች ሲሉ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገለጹ።

3ኛው የአፍሪካ የሥራ ዕድል ፈጠራ ፎረም በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው።

በፎረሙ ላይ የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፣ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሀመድ አሊ የሱፍ፣ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል፣ የአፍሪካ ሀገራት ሚኒስትሮች፣ የፈጠራ ባለሙያዎች፣ ሥራ ፈጣሪዎችና የዘርፉ ምሁራን እንዲሁም ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

ፎረሙ አፍሪካ ያላትን እምቅ ሀብት ወደ ተጨባጭ አቅም ለመቀየር፣ ሥራ አጥነትን ትርጉም ባለው መልኩ ለመቀነስ፣ ፍትሃዊ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነትንና አህጉራዊ ትስስርን ማላቅ ዓላማ አድርጎ ላለፉት ሁለት ተከታታይ ዓመታት ሲካሄድ ቆይቷል፡፡

ዘንድሮም ለሦስተኛ ጊዜ በኢትዮጵያ አስተናጋጅነት ከዛሬ ጀምሮ በዓድዋ ድል መታሰቢያ በመካሄድ ላይ ሲሆን እስከ ሐምሌ 2 ቀን 2017 ዓ.ም ይቆያል።

የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ በኢትዮጵያ ለሥራ ዕድል ፈጠራ በተሰጠው ትኩረት በአማካኝ በየዓመቱ ለ3 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር ተችሏል።

ለሥራ ፈጠራው ምቹ ሥነ ምህዳር የመፍጠሩ ሥራ ተጠናክሮ መቀጠሉንም አንስተዋል።

ከግሉ ዘርፍ፣ ከሴክተር መስሪያ ቤቶችና ከቀጣናዊ የልማት አጋሮች ጋር የተፈጠረው የትብብር አውድ መልካም ውጤቶች እንዲገኙ ምቹ ሁኔታ እየፈጠሩ ነው ብለዋል።

ዛሬ መገናኘታችን በርካታ ፋይዳዎች አሉት ያሉት ሚኒስትሯ የጋራ እጣ ፈንታችንን በጋራ እና በህብረት ለመጻፍ መነሳት እንዳለብን የሚያመላክት ነው ሲሉ ተናግረዋል።

ወቅቱ የሚጠይቀው አርበኝነት ጠንካራ የሥራ ባህል መገንባት በመሆኑ በትብብር መሥራት ይገባል ነው ያሉት።

በሥራ ዕድል ፈጠራ በኩል በአፍሪካ የሚደረጉ ትብብሮች እንዲሳለጡ ኢትዮጵያ በቁርጠኝነት እንደምትሰራም ሚኒስትሯ አረጋግጠዋል።

በአፍሪካ በየዓመቱ 30 ሚሊዮን ወጣቶች የሥራ ገበያውን የሚቀላቀሉ መሆኑን ጠቅሰው፤ እንዲያም ሆኖ በርካታ ተመራቂ ወጣቶች አሁንም ሥራ ይፈልጋሉ ብለዋል።

ሚኒስትር ሙፈሪሃት ክህሎትና ሥራ ዕድል ፈጠራዎች አሁንም ያልተሻገርናቸው የቤት ሥራዎች ናቸው ሲሉም አንስተዋል።

ፎረሙ በይፋ ሲጀመር እንደ አህጉር በሚቀጥሉት 15 ዓመታት ከ80 እስከ 125 ሚሊዮን ለሚደርሱ ወጣቶች የሥራ ዕድል ለመፍጠር ግብ መያዙን አስታውሰው፤ ግቡ ብዙ ሥራ የሚጠይቅ ሆኖ በትብብርና በቁርጠኝነት ከተሰራ ሊሳካ የሚችል ነው ሲሉም አብራርተዋል።

በመድረኩ የግብርና እሴት ሰንሰለት፣ ዲጂታላይዜሽንና የፋይናንስ አካታችነትን በማረጋገጥ በተለይ ለሴቶችና ወጣቶች ምቹና አስተማማኝ የሥራ ዕድል ለመፍጠር የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትስስርን ማላቅ ላይ ያተኮረ ምክክር ይደረጋል።

Social Media Links

Youtube➡️: https://www.youtube.com/c/PrimeMediaPM

FB AfaanOromoo ➡️ https://www.facebook.com/PrimeMediaPM/

FB Primesport ➡️ https://web.facebook.com/primesportet/

FB English ➡️ https://www.facebook.com/profile.php?id=61576239091981

Telegram Afaan Oromoo➡️: http://t.me/PrimeMediapm

Telegram Prime Sport➡️ https://t.me/primediasport

Tiktok➡️ https://www.tiktok.com/.tv

"ምክር ቤቱ ውጤታማ የዲፕሎማሲ ሥራዎችን አከናውኗል " ወ/ሮ ሎሚ በዶፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)ሰኔ 30/2017 ዓ.ምየኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፤ ምክትል አፈ ጉባኤ የተከበሩ ወ/...
07/07/2025

"ምክር ቤቱ ውጤታማ የዲፕሎማሲ ሥራዎችን አከናውኗል " ወ/ሮ ሎሚ በዶ

ፕራይም ሚዲያ(አዲስ አበባ)ሰኔ 30/2017 ዓ.ም

የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፤ ምክትል አፈ ጉባኤ የተከበሩ ወ/ሮ ሎሚ በዶ ምክር ቤቱ ውጤታማ የዲፕሎማሲ ሥራዎችን አከናውኗል ሲሉ ገለፁ፡፡

የምክር ቤቱን የ2017 በጀት ዓመት የዕቅድ ክንውን ሪፖርትን በ3ኛ ልዩ ሰብሰባው አድምጧል፡፡

የምክር ቤቱ ምክትል አፈ ጉባኤ የተከበሩ ወ/ሮ ሎሚ በዶ ተቋሙ በሕገመንግስቱ እና በህዝብ ዘንድ የተሰጠው ኃላፊነት በአግባቡ ለመወጣት የዕቅድ ዓላማውን ለማሳካት በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ ጠቁመዋል፡፡

በፓርላማ ዲኘሎማሲ በወቅታዊና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ፣ የሀገራትን ግንኙነትን ለማጠናከር፣ የልምድ ልውውጥ በማድረግ፣ ንግድና ኢንቨስትመንትን ለመሣብና ለማሳለጥ፣ በዲሞክራሲ፣ በጤናውና ትምህርት ዘርፉ መደጋገፍን ማጠናከር መቻሉን በሪፖርቱ ተመላክቷል፡፡

በዲፕሎማሲው በተሰራው ሥራ ኢትዮጵያ በግብርናው ዘርፍ የምግብ ዋስትና ራስን ለመቻልና የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የተሠሩ ያሉ ሥራዎች በጥናት ተሰንዶ መረጃን ለምስራቅ አፍሪካ የግብርና ተቋማት ማቅረብ መቻሉን የተከበሩ ወ/ሮ ሎሚ በዶ ገልጸዋል፡፡

ዲፕሎማሲ ስራዎችን ለማጠናከር ያግዝ ዘንድ በኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎች ዘርፍ ለምክር ቤት አባላት የአቅም ግንባታ ስልጠና መሰጠቱን የተከበሩ ወ/ሮ ሎሚ በዶ ጠቁመዋል፡፡

ለሀገር ብሔራዊ መግባባት ለኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምና ብልፅግና ዲፕሎማሲ ስራዎች በቀጣይ ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው የምክር ቤት አባላት አሳስበዋል፡፡

ምክር ቤቱ በበጀት ዓመቱ ከተለያዩ ሀገራት ጋር በርካታ የዲፕሎማሲ ስራዎችን ማከናወን መቻሉ በሪፖርቱ ተመላክቷል፡፡

Social Media Links

Youtube➡️: https://www.youtube.com/c/PrimeMediaPM

FB AfaanOromoo ➡️ https://www.facebook.com/PrimeMediaPM/

FB Primesport ➡️ https://web.facebook.com/primesportet/

FB English ➡️ https://www.facebook.com/profile.php?id=61576239091981

Telegram Afaan Oromoo➡️: http://t.me/PrimeMediapm

Telegram Prime Sport➡️ https://t.me/primediasport

Tiktok➡️ https://www.tiktok.com/.tv

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Prime Media - አማርኛ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share