Qalbeessa Toleeraa

Qalbeessa Toleeraa Odeeffannoo wayitawaa waa'ee Oromoo ibsan isiniin geenya. We will inform you latest info about Oromo

በፕሪቶሪያ ከፌደራል መንግስቱ ጋር በተደረገው ድርድር፣ ህውሃትን በመወከል ግንባር ቀደም ሚና የተጫወቱት ተደራዳሪዎች አቶ ጌታቸው ረዳ እና ጄነራል ፃድቃን ገብረ ትንሳይ መሆናቸው ይታወሳል። ...
27/03/2025

በፕሪቶሪያ ከፌደራል መንግስቱ ጋር በተደረገው ድርድር፣ ህውሃትን በመወከል ግንባር ቀደም ሚና የተጫወቱት ተደራዳሪዎች አቶ ጌታቸው ረዳ እና ጄነራል ፃድቃን ገብረ ትንሳይ መሆናቸው ይታወሳል። እነዚህን ወኪሎቹን እና ተደራዳሪዎቹን የገፋው እና አይናቸው ላፈር ያለው የህወሃት ክንፍ፣ የድርድሩን ሂደት እና የድርድሩ ውጤት የሆነውን የፕሪቶሪያ ስምምነት ባግባቡ የመረዳት ችግር ይታይበታል። ቀድሞውንም የራሱን ተደራዳሪዎች የምፈልገውን አይነት ስምምነት አይደለም የተፈራረማችሁት በሚል በተደጋጋሚ ሲወቅስ እና ሲኮንን የከረመው የህውሃት ክንፍ፣ በገሃዱ አለም የተደረገውን፣ አለም ያወቀውን ስምምነት ሳይሆን፣ በምናቡ እና በምኞቱ ያለውን ስምምነት፣ የፕሪቶሪያ ስምምነት ብሎ በመጥቀስ ራሱም ተወናብዶ፣ ሌሎችንም የሚያወናብድ አካሄድ ይከተላል።
▪ በዚህ አካሄድ የሚከሰተውን ውዥንብር ለማጥራት የሚከተሉትን ነጥቦች እና እውነታዎች መገንዘብ ጠቃሚ ነው፤
o የፕሪቶሪያ ስምምነት፣ የፖለቲካ ስምምነት እና ቃል ኪዳን፣ በሁለት ተፋላሚ ወገኖች መካከል የተደረገ የዘላቂ ተኩስ ማቆም እና የሰላም ስምምነት ነው። ስምምነቱ፣ የአለም አቀፍ ስምምነት( treaty) አይደለም፣ ህግ አይደለም፣ የኢፌድሪ ሕገ መንግስትን እና የሃገሪቱን ህጎች የሚተካ አይደለም።
o ይልቁኑም ስምምነቱ፣ ባስቀመጣቸው ግቦች፣ መርሆዎች እና ግዴታዎች ህጋዊነት እና ሕገ መንግስታዊነትን ትልቅ ስፍራ ሰጥቶዋቸዋል። የስምምነቱ አንድ መርህ ሆኖ የተቀመጠው፣ “Legality and respect for constitutional norms and principles enshrined in the FDRE Constitution” ህጋዊነት፣ የኢፌድሪ ህገ መንግስት ውስጥ የተካተቱ ድንጋጌዎችን እና መርሆዎቹን ማክበር ነው።
o በተጨማሪም፣ በስምምነቱ አንቀጽ 7 ውስጥ የህወሃትን ግዴታዎች አስመልክቶ በግልጽ እንደተመላከተው፣ ህወሃት የሚከተሉት ግዴታዎች አሉበት፤
▪ Respect the constitutional authority of the Federal Government, all constitutional bodies and organs of the Federal Government [ የፌደራል መንግስቱን፣ የሁሉንም ሕገ መንግስታዊ አካላት እና የፌደራል መንግስቱን አካላት ሕገ መንግስታዊ ስልጣን ማክበር]
▪ Cease all attempts of bringing about an unconstitutional change of government [ ሁሉንም ኢ-ሕገ መንግስታዊ በሆነ መንገድ የሚደረግ የመንግስት ለውጥ ሙከራዎች ማቆም]
o ስለዚህ የፕሪቶሪያ ስምምነት፣ የሃገሪቱ ህጎች እና ሕገ መንግስታዊ ስርዓት ሊከበር እንደሚገባው አፅንኦት የሚሰጥ፣ ይህንንም በተመለከተ በተለይም ህወሃት ላይ ግልጽ የሆኑ ግዴታዎችን ያስቀመጠ ነው።
▪ ስለዚህ፣ የፕሪቶሪያ ስምምነት የጊዜያዊ አስተዳደር፣ በሁለቱ ወገኖች ምክክር ሊቋቋም ይገባል ሲል፣ የጊዜያዊ አስተዳደርን አስመልክቶ ባለው የሃገሪቱ የህግ ስርዓት እና አግባብ መሰረት መሆኑ ግልጽ ነው። ምክንያቱም፣ ከላይ እንደተመላክተው፣ የፕሪቶሪያ ስምምነት ህጋዊነትን መልሶ ለማስፈን የተደረገ እንጂ ህጋዊነትን ለመገርሰስ የተደረገ ስምምነት አይደለም። የፖለቲካ ስምምነት፣ ወደ ህጋዊ ቅርጽ ሳይለወጥ እና የህግ መሰረት እንዲይዝ ማድረግ ሳይቻል፣ የጊዚያዊ አስተዳደር ሊኖር አይችልም። የፌደራል መንግስት በጀት ሊመድብለት የሚችል፣ አብሮት ሊሰራ የሚችል ጊዚያዊ አስተዳደር የግድ ህጋዊ መሰረት ያለው ጊዜያዊ አስተዳደር ነው።
▪ በኢትዮጵያ ሕገ መንግስታዊ ስርዓት ውስጥ ደግሞ በክልል ደረጃ የሚኖር ጊዜያዊ አስተዳደርን በተመለከተ ብቸኛው እና አግባብነት ያለው የሕግ ማዕቀፍ በኢፌዲሪ ሕገ መንግስት አንቀጽ 62(9) ላይ ተተመረኮዘው በፕሪቶሪያ ስምምነትም ታሳቢ የተደረገው የፌደራል መንግስት በክልል ጣልቃ የሚገባበትን ሥርዓት ለመደንገግ የወጣው አዋጅ ቁጥር 359/1995 ነው።
▪ በነገራችን ላይ፣ ይህ አዋጅ የወጣው በ1995 አመተ ምሕረት ህወሃት በፌደራል መንግስቱ ቁልፍ እና ሁነኛ ተዋናይ በነበረበት ወቅት ነው። ይህ አዋጅ፣ ከሰሞኑ ወይም ከለውጡ በኋላ የወጣ ህግ አይደለም፡፡ ግልጽ የሆነ ሕገ መንግስታዊ መሰረት ያለው አዋጅ ነው። ጊዜያዊ አስተዳደርን የተመለከትው የሃገራችን የሕግ ማቀፍም ይህ አዋጅ ነው።
▪ ይህ አዋጅ ለፌደራል መንግስት እና ለመራሄ መንግስቱ የኢፌድሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ሰፊ ስልጣን እና ሃላፊነት የሰጠ ቢሆንም፣ ይህን ስልጣን ተግባራዊ በማድረግ ሂደት የፌደራል መንግስቱ ህወሃትን ጨምሮ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር የሚያደርገው ምክክር እና የሚሰበስበው ግብዓት ጠቃሚ እና እጅግ አስፈላጊ ነው። የፕሪቶሪያ ስምምነት የሚቋቋመው ጊዜያዊ አስተዳደር አካታች መሆን እንዳለበት ይገልፃል። ስለዚህ የፌደራል መንግስት የጊዜያዊ አስተዳደሩን አካታችነት እና ቅቡልና ለማሳደግ ከህዝብ አስተያየት እና ጥቆማ መሰብሰቡ ተገቢ ነው።

ፊንፊኔ የልህቀት ከተማ‼️
13/02/2025

ፊንፊኔ የልህቀት ከተማ‼️

ከተማችንን ውብ እና ለቱሪዝም ማራኪ ለማድረግ ሌት ተቀን እየሰራን ነው። የካቲት 5/06/2017 የሚካሄደው የአፍሪካ ህብረት ጉባኤ የአፍሪካን የወደፊት እጣ ፈንታ የሚወስንበት እና ለትውልድ ...
12/02/2025

ከተማችንን ውብ እና ለቱሪዝም ማራኪ ለማድረግ ሌት ተቀን እየሰራን ነው።
የካቲት 5/06/2017 የሚካሄደው የአፍሪካ ህብረት ጉባኤ የአፍሪካን የወደፊት እጣ ፈንታ የሚወስንበት እና ለትውልድ የሚተላለፍ ታሪክ የሚሰራበት ይሆናል። በጋራ በመሆን ለአፍሪካ እድገት እና ብልጽግና እንሰራለን።

ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባን ከመስከረም እስከ ጥር በወፍ በረር!💧ማህበራዊ አገልግሎቶች!➤የምግብ ዋስትና: በቀን አንድ ጊዜ እንኳን መመገብ ለማይችሉ ወገኖቻችን 21ኛው የተስፋ ብርሃን የምገባ ማዕከል ለአዲ...
08/02/2025

አዲስ አበባን ከመስከረም እስከ ጥር በወፍ በረር!

💧ማህበራዊ አገልግሎቶች!
➤የምግብ ዋስትና: በቀን አንድ ጊዜ እንኳን መመገብ ለማይችሉ ወገኖቻችን 21ኛው የተስፋ ብርሃን የምገባ ማዕከል ለአዲስ ዓመት ስጦታ ተበርክቷል። ይህም የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የሚደረገውን ጥረት ያሳያል።

➤የቤት ግንባታ: ደሳሳ የቀበሌ ቤቶችን በማፍረስ ለመኖር ምቹ እና ለሰው ልጅ የሚመጥኑ 75 የመኖሪያ ቤቶች ያላቸው ባለ አምስት ወለል (G+5) ሁለት ህንጻዎች በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ዊንጌት እና ገብስ-ተራ አካባቢ ተገንብተው ለነዋሪዎች ተላልፈዋል።

➤የልማት ተነሺዎች ድጋፍ: ከካዛንቺስ አካባቢ በኮሪደር ልማት መልሶ ማልማት የሚነሱ ወገኖች ጉብኝትና ክትትል የተደረገ ሲሆን፣ ለኮሪደር ልማት እና ለመልሶ ማልማት ተነሺ ነዋሪዎች የተገነቡ ምትክ ቤቶች በፍጥነት እንዲጠናቀቁ ክትትል ተደርጓል።

➤የበጎ አድራጎት ሥራዎች: የዘመሙ ጎጆዎችን በማቅናት የሚፈሱ እንባዎች ሲታበሱ ማየት የከንቲባዋ የዕለት ተዕለት ተግባር ሆኖ፣ በተለያዩ አካባቢዎች ድጋፍና እርዳታ ተደርጓል።

➤የሴቶች ተሃድሶ: በነገዋ የሴቶች ተሃድሶና ክህሎት ማበልጸጊያ ማዕከል ለሴተኛ አዳሪነት እና ለተለያዩ የማህበራዊ ችግሮች ተጋልጠው የነበሩ 400 እህቶቻችንን እና ሴት ልጆቻችንን ለሁለተኛ ዙር ስልጠና መስጠት ተጀምሯል።
የሠርግ ድጋፍ: ከህጻንነታቸዉ ጀምሮ በማሳደጊያ ማዕከል ያደጉ 7 ልጆች ለጋብቻ በቅተዋል፣ የሠርግ ስነ ስርዓታቸውም በክብርት ከንቲባዋ ተከናውኗል።

💧መሠረተ ልማት

➤የኮሪደር ልማት: 18 ኪ.ሜ የሚሸፍነው የኮሪደር ልማት ስራ ከሳርቤት አደባባይ-መካኒሳ-ፉሪ ሀና በመገንባት ላይ ይገኛል።

➤በቀን 30 ሚሊዮን ሊትር ፍሳሽ የማጣራት አቅም ያለው የቦሌ አራብሳ ዘመናዊ የፍሳሽ ማጣሪያ ጣቢያ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል።
የመንገድና የትራንስፖርት ልማት: የትራንስፖርት አገልግሎትን ለማሳለጥ በአራት ኪሎ፣ ፒያሳ ጊዮርጊስ አካባቢ፣ ቸርችል መንገድ ቴዎድሮስ አደባባይ፣ ባሻ ወልዴ አካባቢ፣ ደጎል አደባባይ አካባቢ፣ ቦሌ ድልድይ አካባቢ፣ ቦሌ መንገድ ደንበል አካባቢ፣ ሳር ቤት፣ ቀበና አካባቢ፣ መገናኛ እና ሲኤምሲ አካባቢ ከመሬት በታች ከ 2 እስከ 3 ወለል ከመሬት በታች እና ከመሬት በላይ የሆኑ የታክሲና የባስ ተርሚናሎች ግንባታ በመካሄድ ላይ ነው።

➤የዲጂታል ሲቪል ምዝገባ ስርዓት: የከተማዋን ነዋሪዎች እንግልት የሚቀንስ እና ብልሹ አሰራርን በዘመናዊና የተሟላ ዲጂታል የሲቪል ምዝገባ ስርዓት የሚተካ ሥራ ተከናውኗል።

➤የመኖሪያ ቤት ግንባታ: በኦቪድ ገላን ጉራ ሳይት 60 ሺሕ ቤቶች ግንባታ፣ በለገሀር ጊፍት ሪልስቴት የሚገነቡ 4,370 ቤቶች የግንባታ ሂደት እና በቦሌ ሩዋንዳ በግሉ ዘርፍ እየለሙ የሚገኙ ዘመናዊ የመኖሪያ ቤቶች ግንባታ በመካሄድ ላይ ናቸው።

💧ሌሎች ተግባራት

➤ትምህርት: በ2016 የትምህርት ዘመን በ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በሀገር አቀፍ ደረጃ 500 እና ከዚያ በላይ የሆነ ውጤት ያስመዘገቡ 484 የከተማችን ተማሪዎች ተበረታተዋል።

➤የከተማ ፖሊስ: የከተማችንን ቁመና የሚመጥን በሰው ኃይል፣ በቴክኖሎጂ እና በሎጀስቲክ የተደራጀ የፖሊስ ተቋም ለማደራጀት ሥራዎች ተከናውነዋል። 874 መደበኛ የፖሊስ አባላትም ወደ ስራ ገብተዋል።

➤የመንግስትና የግል አጋርነት: ከአያት አክሲዮን ማህበር ጋር በመተባበር የ13,752 ቤቶች ግንባታ ተጀምሯል።

➤የስራ እድል ፈጠራ: በምግብ ዋስትና ሴፍቲኔት ፕሮግራም የስራ እድል አግኝተው ሲሰሩ የነበሩ ከ 31ሺ በላይ የከተማችን ነዋሪዎች ተመርቀው ወደ አምራችነት ተሸጋግረዋል።

Waadaa hanga Aadeeffanaatti !Margii kanaan dura Magaaloota Shaggar irraa hawaasa Horsiisee Bulaa naannoo Gammoojjii jira...
30/01/2025

Waadaa hanga Aadeeffanaatti !

Margii kanaan dura Magaaloota Shaggar irraa hawaasa Horsiisee Bulaa naannoo Gammoojjii jiraniif guuramaa ture hafee achumatti oomishuun gogiinsa dandamachuun qabatamaan danda'aameera.
Seenaa gammoojjii Oromiyaa jijjiiraa jirraa yoo Biiroon missooma Jallisiif Horsiisee Bulaa Oromiyaa dubbatu qabatamaadhaan hojiiwwan lakka'aman akkanaa hojjeteetu.
Harra manni kuusaa naannoo Booranaa Margaan guutamee jira horsiisee bultonni nannichaas gabaan margaa akkaa mijatuuf gaafachaa jiru.
Kaleessi seenaa ta'eera.

አዲስ አበባ የሰላም እና የመቻቻል ምልክት ናት። አዲስ አበባ የተለያዩ ባህሎች፣ ቋንቋዎች እና ሃይማኖቶች ሰላም በሰላም የሚኖሩባት ህብረ ብሔራዊት ከተማ ነች።
22/01/2025

አዲስ አበባ የሰላም እና የመቻቻል ምልክት ናት። አዲስ አበባ የተለያዩ ባህሎች፣ ቋንቋዎች እና ሃይማኖቶች ሰላም በሰላም የሚኖሩባት ህብረ ብሔራዊት ከተማ ነች።

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Qalbeessa Toleeraa posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share