Etio-bilal Muslim Whatsapp Group

Etio-bilal Muslim Whatsapp Group የፔጅ አላማ ወቅታዊ የሙስሊሞች ጉዳዪችን ይመለከታል

ኢንሻአላህ ሰምተናል እንታዘዛለን...!
27/05/2023

ኢንሻአላህ ሰምተናል እንታዘዛለን...!

በወቅታዊ ጉዳይ ከአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት የተሰጠ መግለጫ! መብቱን በሰላማዊ መንገድ ለመጠየቅ በወጣ ህዝብ ሙስሊም ላይ የተወሰደው እርምጃ ፍፅም ተቀባይነት የሌለው ፣...
26/05/2023

በወቅታዊ ጉዳይ ከአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት የተሰጠ መግለጫ!

መብቱን በሰላማዊ መንገድ ለመጠየቅ በወጣ ህዝብ ሙስሊም ላይ የተወሰደው እርምጃ ፍፅም ተቀባይነት የሌለው ፣ ኢ-ፍትሃዊና ኢ-ዲሞክራሲያዊ በመሆኑ የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ያወግዛል።

በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት በሸገር ሲቲ የመስጅድ ፈረሳ እንዲቆምና የፈረሱትም በአስቸኳይ መተኪያ እንዲሰጣቸው እንዲሁም በጉዳዩ ዙሪያ የሚመለከታቸው አካላት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ በተደጋጋሚ በደብዳቤ ለሚመለከተው አካል ለማሳወቅ የተሞከረ ሲሆን የመስጅድ ፈረሳው ባለመቆሙ ህዝበ ሙስሊሙ ተቃውሞውን በዛሬው እለት በአደባባይ ድምፁን በሰላማዊ መንገድ አሰምቷል።

ይህንንም ሰላማዊ የመብት ጥያቄ ተከትሎ በታላቁ አንዋር መስጅድ የፀጥታ አካል በወሰዱት ኢ-ህገ መንግስታዊ እና ኢ ሰብአዊ እርምጃ የሰው ሂይወት አልፋል፣ብዙሃን ቆስለዋል።

በመሆኑም ይህንን አስከፊ ጥቃት የፈፀሙ እና ያስፈፀሙ የፅጥታ አካላት ላይ ህጋዊ እርምጃ እንዲወሰድ አጥብቀን እንጠይቃለን ።

በቀጣይም የሚመለከተው አካል በኦሮሚያ ክልል በሸገር ከተማ እየተከናወነ ያለውን ድርጊት እንዲያስቆምነና ወደ ውይይት በመምጣት ስር ነቀል የእርምትና እርምጃ ተጠናክሮ እንዲተገበር አጥብቀን እንጠይቃለን።

የሀይማኖት ጉዳይ እና የእምነት ተቋማት ጉዳይ ሁሌም ቢሆን በስክነት መታየት ሲገባው ከዚህ ቀደም የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በእምነት በተቋማቱ ጉዳይ ሲከተሉት የነበረውን አካያሄድ እንደ ተሞክሮ ከመውሰድ ይልቅ በዚህ አከያሄድ የተሰራው አስነዋሪ ተግባር የሀገራችንን ብሎም የከተማችንን ሰላምና ደህንነት አደጋ ላይ እየጣለ ይገኛል።

በሸገር ከተማ መስጅድን በተመለከተ እየተከናወነ ያለው ድርጊት፣ሀላፊነት የጎደለው፣የህዝበ ሙስሊሙን ክብር ያዋረደ፣ሀገራችን ያለችበትን ነባራዊ ሁኔታ ያላገናዘበ፣የመንግስት የለውጥ ሪፎርምን ወደ ሀላ የሚመልስ በመሆኑ ጉዳዩ እንደ ሀገር ሊታሰብበት ይገባል።

በዛሬውም እለት በመስጅድ ፈረሳ ሳቢያ በሰላማዊ መንገድ መብቱን ለመጠየቅ በወጣው ህዝበ ሙስሊም ላይ በተወሰደው ኢ-ህገ መንግስታዊ እርምጃ ሒይወታቸው ላለፉ አላህ (ሱ.ወ) ጀነትን እንዲወፍቃቸው፣ለመላው ህዝበ ሙስሊም መፅናናትን እንመኛለን።

የከተማችንም ህዝበ ሙስሊሙ በቀጣይ ጉዳዩን በሰከነ መንፈስ እንዲከታተል አደራ እንላለን።

ግንቦት 18/2015ወቅታዊ #ጉዳይ #ከአዲስ #አበባ #እስልምና #ጉዳዮች #ከፍተኛ #ምክር #ቤት #የተሰጠ #መግለጫ።

መብቱን በሰላማዊ መንገድ ለመጠየቅ በወጣ ህዝብ ሙስሊም ላይ የተወሰደው እርምጃ ፍፅም ተቀባይነት የሌለው ፣ ኢ-ፍትሃዊና ኢ-ዲሞክራሲያዊ በመሆኑ የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ያወግዛል።

በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት በሸገር ሲቲ የመስጅድ ፈረሳ እንዲቆምና የፈረሱትም በአስቸኳይ መተኪያ እንዲሰጣቸው እንዲሁም በጉዳዩ ዙሪያ የሚመለከታቸው አካላት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ በተደጋጋሚ በደብዳቤ ለሚመለከተው አካል ለማሳወቅ የተሞከረ ሲሆን የመስጅድ ፈረሳው ባለመቆሙ ህዝበ ሙስሊሙ ተቃውሞውን በዛሬው እለት በአደባባይ ድምፁን በሰላማዊ መንገድ አሰምቷል።

ይህንንም ሰላማዊ የመብት ጥያቄ ተከትሎ በታላቁ አንዋር መስጅድ የፀጥታ አካል በወሰዱት ኢ-ህገ መንግስታዊ እና ኢ ሰብአዊ እርምጃ የሰው ሂይወት አልፋል፣ብዙሃን ቆስለዋል።

በመሆኑም ይህንን አስከፊ ጥቃት የፈፀሙ እና ያስፈፀሙ የፅጥታ አካላት ላይ ህጋዊ እርምጃ እንዲወሰድ አጥብቀን እንጠይቃለን ።

በቀጣይም የሚመለከተው አካል በኦሮሚያ ክልል በሸገር ከተማ እየተከናወነ ያለውን ድርጊት እንዲያስቆምነና ወደ ውይይት በመምጣት ስር ነቀል የእርምትና እርምጃ ተጠናክሮ እንዲተገበር አጥብቀን እንጠይቃለን።

የሀይማኖት ጉዳይ እና የእምነት ተቋማት ጉዳይ ሁሌም ቢሆን በስክነት መታየት ሲገባው ከዚህ ቀደም የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በእምነት በተቋማቱ ጉዳይ ሲከተሉት የነበረውን አካያሄድ እንደ ተሞክሮ ከመውሰድ ይልቅ በዚህ አከያሄድ የተሰራው አስነዋሪ ተግባር የሀገራችንን ብሎም የከተማችንን ሰላምና ደህንነት አደጋ ላይ እየጣለ ይገኛል።

በሸገር ከተማ መስጅድን በተመለከተ እየተከናወነ ያለው ድርጊት፣ሀላፊነት የጎደለው፣የህዝበ ሙስሊሙን ክብር ያዋረደ፣ሀገራችን ያለችበትን ነባራዊ ሁኔታ ያላገናዘበ፣የመንግስት የለውጥ ሪፎርምን ወደ ሀላ የሚመልስ በመሆኑ ጉዳዩ እንደ ሀገር ሊታሰብበት ይገባል።

በዛሬውም እለት በመስጅድ ፈረሳ ሳቢያ በሰላማዊ መንገድ መብቱን ለመጠየቅ በወጣው ህዝበ ሙስሊም ላይ በተወሰደው ኢ-ህገ መንግስታዊ እርምጃ ሒይወታቸው ላለፉ አላህ (ሱ.ወ) ጀነትን እንዲወፍቃቸው፣ለመላው ህዝበ ሙስሊም መፅናናትን እንመኛለን።

የከተማችንም ህዝበ ሙስሊሙ በቀጣይ ጉዳዩን በሰከነ መንፈስ እንዲከታተል አደራ እንላለን።

ግንቦት 18/2015

 #መስጅዳችንንአትንኩብን"መስጅዳችንን በህገወጥ ስም በማፍረስ እና በማጥፋት ሙስሊሙን በመግፋት የሚመጣ ልማትም ሆነ አንድነት ሊኖር አይችልም"።
21/05/2023

#መስጅዳችንንአትንኩብን
"መስጅዳችንን በህገወጥ ስም በማፍረስ እና በማጥፋት ሙስሊሙን በመግፋት የሚመጣ ልማትም ሆነ አንድነት ሊኖር አይችልም"።

21/05/2023

Magaalaan Shaggar Masjiidotaa fi Muslimoota kan of keessaa qulqulleessu yoo ta’e Muslimootaaf "rakkina" malee madda boonsaa ta'uu gonkumaa hin danda’u!
🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴

Mootummaan biyyattii kan bulchu lammiiwwan bakka bu’ee, maqaa lammiitiin akka ta’e hundaafuu ifaadha. Osoo kun ta’uu baatee aangawoonni mootummaa hunduu akkuma keenya lammii idileeti; silaa mirga ykn aangoo nurraa adda ta’e hin qabaatan ture.

Biyyattiin kan waloo ta’uun yoo mormame malee qabeenyii fi carraan biyyattiin qabdu hunduu kan walooti. Osoo akkana ta’ee jiruu, magaalota biyya keenyaa hunda keessatti yeroo maastar pilaaniin qophaa’u, warra pilaanicha qopheessu qofa osoo hin taane, hoggantoonni siyaasaas hanga yoomiitti masjida qofa adda baasanii pilaanii keessaa dagatu laata?

Ummanni muslimaa akka lammiitti maastar pilaanii keessatti masjiidonni karoorfamee dagatamuudhaan gaaffileen Muslimootaa masjidaafi hijaaba qofa irratti daangeffamee akka hafu gochuudhaan gaaffilee ummata Muslimaa isaan kana qofa fakkeessanii sochiiwwan amantichaa gufuuleen kan guutaman taasisuun tooftaa dhaabbachuu qabuudha.


Gaaffiiwwan mirgaa bu'uura ta’an kunniin "maastar pilaanii irratti masjidni asitti argama" jechuudhaan osoo hin gaafatamin deebii argachuu qabu turan. Ykn yoo gaafataman gaaffiiwwan salphaatti deebii argachuu qaban turan. Haa ta’u malee, Muslimoonni biyyattii guutuu keessa jiran lafa masjidaa kadhachuun ykn maallaqa isaaniitiin lafa bitanii ibaadaaf itti fayyadamuun, ykn sanarra kutee qabsoofi dhiigaan [qabsoo qabiyyee masjidaa kabachiisuuf godhamu keessatti Muslimoonni humna nageenyaatiin ajjeefaman baay’eedha] masjida aragchuun yoo hin dhaabbanne mirgi Muslimootaa ni kabajama jechuun hin danda’amu.


Namoonni tokko tokko masjiidonni "seeraan ala" waan ta'aniif diigamaa jiru nuun jedhu. Nama ajaa'iba. Warra kanaafi fakkaattota isaanii kan nuti gaafannu masjiidonni "seera qabeessa" jedhaman kam akka ta'an nuuf himaa kan jedhuudha.

Finfinnee dabalatee masjiidonni waggoota kudhanii ol erga itti salaatamee booda carraaqqiifi roorroo meeqaan kaartaan akka kennamu eenyunuu ni beeka.

Masjiidota gurguddaa akka Anwaarii fi Masjida Nuur (Baniin Safar) dabalatee kanneen bara Haylesillaaseetii jalqabee Finfinnee keessa turanillee kaartaa kan argatan 1990moota keessa yeroo Obbo Arkabee Qubaayi kantiibaa turaniidha. Kanumaa wajjin, Masjidni Anwaar bara Xaaliyaanii kan ijaarame yoo ta’u, Masjidni Nuur immoo weerara Xaaliyaaniin dura kan tureedha. Masjiidonni kun qabsoo ummata Muslimaa adda hin cinneen ijaaramanii waggaa hedduuf achitti ibaadaa hojjataa kan turan ta'us waggoota kurnan hedduu booda kaartaa seera qabeessa argatan.

Magaalota baay’ee naannoo lammiileen jiraatan keessatti, bakka bulchiinsonni maqaa ummataatiin aangoo qabatan jiranitti, maastar pilaaniin itti yaadamee masjiidota irraanfachaa kan jiran yoo ta’u, ummanni Musliimaa naannoo sanaa gaaffiin lafa Masjidaa isaan dadhabsiifnaan qabeenya ofii baasanii lafaafi mana bituudhaan kanuma itti salaataa jiran “masjiidummaaf hin eeyyamamne” jechuudhaan diiguun irra deddeebiin mul’achaa ture. Qorannoofi yaadannoo baay’ee booda adeemsa seeraatiin lafa mana amantii biroo irra baay’ee xiqqoo taate kennuun, kana jechuun bifa loogiin guutameen adeemsi tokkoof kaareedhaan kaaniif immoo hektaaraan kennuu dhaabbachuu qaba.

Adeemsiifi hojimaanni loogiin guutaman kuniifi kanneen isaan fakkaatan hunduu qabsoo yeroo gabaabaa, giddu galaafi dheeraa majlisniifi Ummanni Muslimaa godhuun maletti jijjiiramuu hin danda’u.

Masjiidonni har'a "seeraan ala" isaan jedhan kunniin halkan tokkotti ijaaramanii bulan osoo hin taane, inumaayyuu, osoma ummanniifi fi mootummaan beekuu Hawaasni Muslimaa waggootaaf itti fayyadamaa turan.

Yoo xiqqaate ijaarsi magaalota haaraa "Magaalaa Shaggar" jedhamu bifa haaraa fi karoora haaraadhaan waan karoorfameef, akka karoora haaraa magaalichaatti bakki kun masjiidaaf osoo hin taane kaayyoo biraatiif qophaa'e waan ta’eef (innumtuu pilaanichi masjidaaf akka mijatu gochuudha malee akka tasaa ka’anii masjida diiguun sirrii miti), bulchiinsonni Magaalaa Shaggar "akka karoora haaraatti bakki masjiidaaf isinii qophaa'e kana" jedhanii bakka bu’aa dhiheessanii mariifi wal hubannaadhaan ijaarsa magaalichaa keessatti masjinni akka ijaaramu godhanii dubbii fixuu hin barbaanne. Wanti isaan qabatamaan hojjataa jiran amantichaafi Muslimootaaf kabaja xiqqoollee osoo hin agarsiisin masjiidota diiguutti seenan.

Gaafa haala kana hubattuufi yeroo qabatamaanis sochii nama gaddisuusu kan masjiidota hedduu Magaalaa Shaggar keessa jiran jumlaan diiguuf godhamu ilaalte, dhimmichi gaaffii seera qabeessummaa osoo hin taane, [namoonni manneen irraa diigamaa jiran irra caalaan Muslimoota ta’uus ilaalcha keessa galchuudhaan] dhimmichi shira Masjiidotaa fi Muslimoota magaalaa Shaggar keessaa qulqulleessuuf godhamaaru isaan jalaa fakkaateera.

Kana galmaan gahuun dachii Itoophiyaa keessatti gonkumaa waan hin yaadamneefi Magaalaan Shaggar Masjidaa fi Muslimoota of keessaa qulqulleessuuf murteeffatee yoo itti fufe, Magaalattiin Hawaasa Muslimaa walakkaa biyyattiitiif "rakkina" malee "madda boonsaa" ta’uu gonkuma hin dandeessu!

21/05/2023
21/05/2023

መስጂዶች ህልውናችን ናቸው!

በሀገራችን ኢትዮጵያዊ የተገነቡ መስጂዶችን ታሪክ ስናይ አብዛኛው ብዙ መስዋትነት ተከፍሎባቸው የተገኙ ናቸው::

ሙስሊሞች እና መስጂድ የማይነጣጠሉ የአንድ ሳንቲም ሁለት ገፅታዎች ናቸው:: አሳ ያለ ውሃ እንደማይኖረው ሁሉ ሙስሊሞችም ያለሰላት እና ያለመስጂድ መኖር አይቻላቸውም::

መስጂዶች ለሙስሊሙ ከአምላኩ ጋር የሚገናኝባቸው የአምልኮ ቤቶች ብቻ ሳይሆኑ ሀይማኖቱን እና ስ-ነምግባሩን የመማሪያ፣ የመወያያ፣ እና አንድነቱን የሚያጠናክርባቸው መድረኮች ናቸው::

ቀደምት አባቶቻችን በብዙ መስዋትነት ያስረከቡን ሆነ አሁን ላይ በገንዘቡ፣በላቡ እና በደሙ የመሰረታቸውን መስጂዶች ማፍረስ እና ማጥቃት የሙስሊሙን ህልውና የሚፈታተን ተግባር ነው::
በሸገር ሲቲ ተባብሶ የቀጠለው መስጂዶቻችንን የማፍረስ ተግባር በአስቸካይ ይቆም ዘንድ ጥሪዬን አቀርባለሁ፡፡

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት (መጅሊስ) እንደ ተቋም በአዋጅ ህጋዊ ሰውነት አግኝቶ የተቋም ግንባታውን የጠነከረ አለት ላይ ለማሳረፍ ሰፊ ስራዎችን እየሰራ ባለበት በዚህ ወቅት የህዝበ ሙስሊሙን ህልውና የሆኑ ተቋማት ላይ የሚፈፀሙ ጥቃቶችን በቸልታ የሚያልፋቸው አይደሉም::

አዲሱ የመጅሊሱ አመራር እንደ ግለሰብ ወደ ተቋሙ ከመምጣታቸውም በፊት ከማንም በፊት መስጂዶችን በማስገንባት፣ ለመስጂዶች እና በአጠቃላይ ለዲኑ መከበር ዘብ በመቆም ብዙ መስዋትነትን የከፈሉ አባቶች ናቸው::

ትላንት ተሰሚነት ያለው የሙስሊሙ ወኪል እንዲኖር ብዙ ሲለፋ የነበረ አመራር ዛሬ ላይ የሙስሊሙ ወኪል የሆነውን መጅሊስ በሃላፊነት እንዲመራ ሲደረግ የሙስሊሙን ቁስል እና ህልውናን አደጋ ላይ የሚጥል ድርጊት ሲፈፀም ችላ ሊል ይችላል ብሎ ማሰብ ተገቢ አይደለም::

በተቋም ደረጃ የሚሰሩ ስራዎች ተቋማዊ አሰራራቸውን በጠበቀ መልኩ እርከናቸውን እና ስርዓታቸውን ጠብቀው እየተሰሩ ይገኛሉ::

ለአፍታም ቢሆን የሙስሊሙን ህልውናን የሚፈታተኑ ተግባራትን በዝምታ እና በቸልታ የሚያልፍ አመራር አለመኖሩን አስረግጬ ለማሳሰብ እወዳለሁ::

ይህ ከመሆኑም ጋር የተቋም ግንባታ በአንድ ጀንበር የሚጠናቀቅ አይደለም:: ይህን ለማሳካት አመራሩ ብቻውን የሚወጣው አይደለም:: ህዝበ ሙስሊሙ ተቋሙን ከጎኑ በመሆን በሚፈልገው ቁመና እና ልክ ከፍ ብሎ እንዲወጣ ሁሉም ተቋሜ ብሎ ድጋፍ ማድረግ ይኖርበታል::

መጅሊሱ እንደ ተቋም የመስጂዶችን ህልውና ለመታደግ ብቻ ሳይሆን ህዝበ ሙስሊሙ በሚገባው ልክ የአምልኮ ቦታዎች እንዲሰጡት ማድረግ ግዴታው ነው:: የሙስሊሙን ህልውና የሚፈታተኑ ዘመናትን ያሳለፉ የአስተሳሰብ እና መዋቅራዊ ችግሮችን ለማስተካከል የራስን ተቋም በማጠናከር ስር ነቀል ለውጥ ለመምጣት በጋራ መልፋትም ያስፈልጋል ::

በሀገራችን የትኛውንም የፓለቲካ መስመር የሚከተል አመራር የሀገሪቱ ግማሽ የሆነውን ህዝበ ሙስሊም ባከበረ እና ታሳቢ ባደረገ መልኩ መንቀሳቀስ ካልቻለ አድሏዊ አሰራርን፣ ጭቆናን እና መገፋትን አሜን ብሎ የሚቀበል ትውልድ አለመኖሩን ማስታወስ ያስፈልጋል::

ህዝበ ሙስሊሙ እንደ ዜጋ በሀገሪቱ ላይ እኩል ባለድርሻ መሆኑን በማወቅ የሚወጡ ህጎችም፣ ፖሊሲዎችም ሆነ የልማት እቅዶች ይህን መርህ ታሳቢ ያደረጉ መሆን ይኖርባቸዋል::

መስጂዶችን በህገወጥነት ስም በማፍረስ እና በማጥፋት ሙስሊሙን በመግፋት የሚመጣ ልማትም ሆነ እድገት ሊኖር አይችልም:: ሁሉንም የሀገሪቱ ህዝቦች በእኩልነት እና በፍትህ ያማከሉ የልማት እቅዶች ውጤታቸውም ለሁሉም በእኩልነት እና በፍትሃዊነት ተጠቃሚ ማድረጉ አይቀርም::

ሙስሊሙ ማህበረሰብ የህልውናው መሰረቱ በሆኑት መስጂዶቹ ላይ የተቃጣውን ጥቃት ከመሪ ድርጅቱ እና ከኡለማዎቹ ጎን በመቆም እና መሪውን በማድመጥ የመስጂዶቹ ዘብ መሆን ይጠበቅበታል::

ጠንካራ ተቋም ሲኖር ተሰሚነትም ይጨምራል:: ይህን ተሰሚነት ለማሳደግም የተቋሙ ባለቤት የሆነው ህዝበ ሙስሊም ተቋሙን በማጠናከር፣ በመምከር እና በማገዝ ኃላፊነቱን ሊወጣ እንደሚገባ ለማሳሰብ እወዳለሁ::

አላህ ሱወ ይርዳን
አገራችንን ሠላም ያድርግልን

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Etio-bilal Muslim Whatsapp Group posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Etio-bilal Muslim Whatsapp Group:

Share