Bisrat Promotion

Bisrat Promotion በአካል ጉዳተኝነት እና ጉዳተኞች ላይ የሚሰራ…እያዝናናን እ? A Multimedia Initiative Focused on Raising Disability Awareness!

ፍቅር ኢትዮጵያ የአእምሮ እድገት ውስንነት ብሄራዊ ማህበር የተመሰረተበትን 30ኛ አመት በስካይ ላይት ሆቴል እያከበረ ይገኛል በፕሮግራሙ ላይ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ሚኒስትር ድኤታ...
14/11/2024

ፍቅር ኢትዮጵያ የአእምሮ እድገት ውስንነት ብሄራዊ ማህበር የተመሰረተበትን 30ኛ አመት በስካይ ላይት ሆቴል እያከበረ ይገኛል

በፕሮግራሙ ላይ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ሚኒስትር ድኤታ :የአካል ጉዳተኛ ማህበራት አመራሮች :የአእምሮ እድገት ውስንነት ያለባቸው ልጆች ወላጆች:የአእምሮ እድገት ውስንነት ያለባቸው ልጆች እንዲሁም በጎ ፈቃደኞች ተገኝተዋል ።

የፍቅር ኢትዮጵያ የአእምሮ እድገት ውስንነት ብሄራዊ ማህበር ፕሬዝዳንት የሆኑት ወ/ሮ ምህረት ንጉሴ እንዳሉት ስኬቶቻችንን ስናከብር ብዙ የሚቀሩ ስራዎች እንዳሉም እንገነዘባለን። በየቤቱ በሰንሰለት የታሰሩ የፀሀይ ብርሃን የሚናፍቁ ወገኖቻችንን በልባችን ይዘን፤ ይህ በዓል ጥረቶቻችንና ተልእኳችን እንደሚቀጥል ለማስታወስ ይሁን።

የአእምሮ እድገት ውስንነት ያለባቸው ዜጎችንና ቤተሰቦቻቸውን መብት፣ ብቃት፣ ሙሉ ተሳትፎ እና ተጠቃሚነት ለመደገፍ ቁርጠኞች ነን። በጋራ ጥንካሬያችን፣ ገደቦችንና እንቅፋቶችን መግፋታችንን እንቀጥላለን በዚህም ለሁሉም ብሩህ፣ እኩልና አካታች ዓለም ወደፊት እንፈጥራለn

በ17ኛው የፓራሊምፒክ ጨዋታዎች አትሌት ትዕግስት ገዛኸኝ በ1500 ሴቶች የጭላንጭል (T-13) ፍጻሜ ለኢትዮጵያ የመጀመሪያ የወርቅ ሜዳሊያ አስገኝታለች።80 ሺህ ተመልካች በሚያስተናግደው የስ...
31/08/2024

በ17ኛው የፓራሊምፒክ ጨዋታዎች አትሌት ትዕግስት ገዛኸኝ በ1500 ሴቶች የጭላንጭል (T-13) ፍጻሜ ለኢትዮጵያ የመጀመሪያ የወርቅ ሜዳሊያ አስገኝታለች።

80 ሺህ ተመልካች በሚያስተናግደው የስታድ ደ ፍራንስ ብሔራዊ ስታዲየም በተደረገው ውድድር አትሌት ትዕግስት 4 ደቂቃ ከ22 ሴኮንድ ከ39 ማይክሮ ሴኮንድ አሸንፋለች።

አትሌት ትዕግስት እ.አ.አ በ2021 በቶኪዮ በተካሄደው 16ኛው የፓራሊምፒክ ጨዋታዎች በተመሳሳይ ርቀት ተሳትፋ በውድድሩ ታሪክ ለኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የወርቅ ሜዳሊያ ማምጣቷ የሚታወስ ነው።

ሞሮኮዋዊቷ አትሌት ፋጡማ ኢዝሃራና አሜሪካዊቷ አትሌት ሊዛ ኮርሶ ሁለተኛና ሶስተኛ በመውጣት የብርና የነሐስ ሜዳሊያ አግኝተዋል።

በውድድሩ ላይ 11 አትሌቶች ተሳትፈዋል።

በተያያዘም ዛሬ ቀን ላይ በተካሄደ የወንዶች 1500 ሜትር የእጅ ጉዳት (T-46 ምድብ) የፍጻሜ አትሌት ገመቹ አመኑ ስምንተኛ ደረጃን ይዞ አጠናቋል።

ነፍስ ይማር🙏💔ፕሮፌሰር እንድርያስ እሸቴ አረፉ 😭😭የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቀድሞ ፕሬዝዳት ፕሮፌሰር እንድርያስ እሸቴ ባደረባቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው ዛሬ ነሐኔ 23 ቀን 2016 ...
29/08/2024

ነፍስ ይማር🙏💔

ፕሮፌሰር እንድርያስ እሸቴ አረፉ 😭😭

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቀድሞ ፕሬዝዳት ፕሮፌሰር እንድርያስ እሸቴ ባደረባቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው ዛሬ ነሐኔ 23 ቀን 2016 ዓ.ም ማረፋቸውን አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ከደቂቃዎች በፊት አስታውቋል።

ፕሮፈሰር እንድሪያስ እሸቴ አካል ጉዳተኛ ለሆኑ የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች በስራ ዘመናቸው ከፍተኛ አገልግሎት የሰጡ ግለሰብ ናቸው

አቢሲኒያ ሽልማት🏅👏👏"ትጉኋንን እንሸልማለን"  በሚለው መርሀ ግብርበኢንተር ሌግዠሪ ሆቴል የኢትዮጵያ አካል ጉዳተኛ ሴቶች ብሄራዊ ማህበር  ዛሬ 21/11/2016 ዓ.ም ተሸልማለች።እንኳን ደስ...
28/07/2024

አቢሲኒያ ሽልማት🏅
👏👏
"ትጉኋንን እንሸልማለን" በሚለው መርሀ ግብር
በኢንተር ሌግዠሪ ሆቴል
የኢትዮጵያ አካል ጉዳተኛ ሴቶች ብሄራዊ ማህበር ዛሬ 21/11/2016 ዓ.ም ተሸልማለች።
እንኳን ደስ አላችሁ 👏🤟🥇

በጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ በኬንቾ ሻቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰ ድንገተኛ የመሬት ናዳ ውድ ህይወታቸውን ባጡ ወገኖቻችን ምክኒያት ብሄራዊ ሀዘን ታውጇል ስለሆነም የጣፍጭ መዝናኛ ዝግጅት ክፍል ዛሬ...
27/07/2024

በጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ በኬንቾ ሻቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰ ድንገተኛ የመሬት ናዳ ውድ ህይወታቸውን ባጡ ወገኖቻችን ምክኒያት ብሄራዊ ሀዘን ታውጇል ስለሆነም የጣፍጭ መዝናኛ ዝግጅት ክፍል ዛሬ የሚተላለፈውን ፕሮግራም አጥፎል

ውድ ህይወታቸው ላጡ ወገኖቻችን ቤተሰቦች መፅናናትን እየተመኘን በሚቀጥለው ሳምንት መደበኛ ፕሮግራማችን የሚቀጥል መሆኑን እንገልፃለን ።

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጎፋ ዞን፣ ገዜ ጎፋ ወረዳ፣ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በተከሰተው የመሬት ናዳ ምክንያት የዜጎቻችን ህይወት በመቀጠፉ  የተሰማንን ጥልቅ ሀዘን እገልፃለሁ።በተከሰተው ድንገ...
24/07/2024

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጎፋ ዞን፣ ገዜ ጎፋ ወረዳ፣ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በተከሰተው የመሬት ናዳ ምክንያት የዜጎቻችን ህይወት በመቀጠፉ የተሰማንን ጥልቅ ሀዘን እገልፃለሁ።

በተከሰተው ድንገተኛ አደጋ ሳቢያ ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖችና ለተጎጂ ቤተሰቦች ወዳጅ ወመዶች ሁሉ መፅናናትን እንመኛለን ።

ለአካል ጉዳተኞች የሚሆኑ የተለያዩ እቃዎችን ከፈለጉ ከብስራት ፕሮሞሽን ያገኛሉበ +251115577357   ይደውሉከምንሸጣቸው እቃዎች መካከል በጥቂቱTalking watchHearing aidWhe...
21/06/2024

ለአካል ጉዳተኞች የሚሆኑ የተለያዩ እቃዎችን ከፈለጉ ከብስራት ፕሮሞሽን ያገኛሉ
በ +251115577357 ይደውሉ
ከምንሸጣቸው እቃዎች መካከል በጥቂቱ
Talking watch
Hearing aid
Wheelchair
braille watch
Crutch
Talking calculator and other

የአካል ጉዳተኞችን ለማገዝ ዊልቸር በነፃ የምትሰጠው ኢትዮጵያዊትገና በልጅነቷ ባጋጠማት የፖሊዮ ህመም ምክንያት የቀኝ እግሯን እንደፈለገች አታዘውም፡፡ ቆማ መሄድ ባለባት የልጅነት አድሜዋ ቆማ...
14/06/2024

የአካል ጉዳተኞችን ለማገዝ ዊልቸር በነፃ የምትሰጠው ኢትዮጵያዊት

ገና በልጅነቷ ባጋጠማት የፖሊዮ ህመም ምክንያት የቀኝ እግሯን እንደፈለገች አታዘውም፡፡ ቆማ መሄድ ባለባት የልጅነት አድሜዋ ቆማ እንድትሄድ አላስቻላትም ነበር፡፡ ነገር ግን ጠንካራ እና የተሻለ የኑሮ ደረጃ ያላቸው ቤተሰቦች ነበሯት፡፡ ስለሆነም ብዙ ወጥተውና ወርደው ብዙ ወጪም አውጥተው በ5 ዓመቷ መራመድ እንድትችል አደረጓት፡፡ ሳባ ተክለማርቆስን፡፡

ሳባ ተክለማርቆስ የአጋፔ ሞቢሊቲ ኢትዮጵያ መስራች ነች፡፡ አጋፔ ለአካል ጉዳተኞች በነጻ ዊልቸሮችን የሚሰጥ ድርጅት ነው፡፡ ሳባ በመላው ዓለም የሚገኙ በጎ አድራጊዎችን አሰባስባ ይህን መልካም ተግባር ታደርጋለች፡፡ ማንም አካል ጉዳተኛ መሬት መንፏቀቅ የለበትም ብላ በማመን የዛሬ አራት ዓመት ይህንን ጉዞ እንደጀመረች ከአዲስ ዋልታ ጋር ባደረገችው ቆይታ ገልጻለች፡፡

በ14 ዓመት እድሜዋ ወደ አሜሪካ ያቀናችው ሳባ ትምህርቷን የጨረሰችውም ሆነ ቤተሰብ የመሰረተችው በዛው በአሜሪካ ነው፡፡ ከ20 ዓመታት ቆይታ በኋላ ለእረፍት ወደ ትውልድ ሀገሯ ስትመለስ የተመለከተችው ነገር አንድ ውሳኔ እንድትወስን አስገደዳት፡፡

ከብዙ ዓመታት በኋላ ስትመለስ ብዙ ነገር ረስታ እንደነበርና ቤተክርስትያን አካባቢ መሬት ላይ እየተንፏቀቁ ምጽዋት የሚጠይቁ በርካታ አካል ጉዳተኞች ስትመለከት ደነገጠች፡፡ አንድ ነገር ማድረግ አለብኝ ብላም ወሰነች፡፡ ለዚህም ወደ አሜሪካ ተመልሳ አጋፔ ሞቢሊቲ ኢትዮጵያን ከአራት ዓመት በፊት አቋቋመች፡፡

በአጋፔ የሚሰሩ የበጎ አድራጎት ሰራተኞች ሳባ በአሜሪካ ከልጇቿና ቤተሰቦቿ ጋር ተመችቷት መኖር ስትችል በየክፍለሀገሩ እየዞረች በጣም ለተጎዱ አካል ጉዳተኞች እና ረጂ ለሌላቸው በነጻ ዊል ቸር ትሰጣለች ሲሉ ደግነቷን ይገልጻሉ፡፡

አጋፔ ሞቢሊቲ ኢትዮጵያ በሁሉም ክልል እየሄደ በየአካባቢው ያሉ አካል ጉዳተኞችን ይደግፋል፡፡ ከየአካባቢው ፎቶና የተለያዩ መረጃዎች ይላካሉ፡፡ ነገር ግን አንድ የዊል ቼር አይነት ለሁሉም የአካል ጉዳተኞች አይሆንም፡፡ ስለሆነም እንደየጉዳቱ የተለያየ ዊል ቼር ያስፈልጋል፡፡ እንደየአስፈላጊነቱና እንደጉዳታቸው አይነት ዊል ቼርም የሳባ ድርጅት በነጻ ይሰጣል፡፡

ሳባ በመጨረሻም ማንም አካል ጉዳተኛ መሬት ላይ በመንፏቀቅ ሲሄድ ማየት አልፈልግም ስትል ምኞቷን ገልጻለች፡፡

የኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞች ማህበራት ፌደሬሽን ከኢትዮ ቴሌ ኮም ጋር በመተባበር 500 ለሚሆኑ የተለያየ አካል ጉዳት ላለባቸው ተማሪዎች ድጋፍ አደረገ።ደጋፍ ለተደረገላቸው ተማሪዎች  በአካል ድ...
20/03/2024

የኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞች ማህበራት ፌደሬሽን ከኢትዮ ቴሌ ኮም ጋር በመተባበር 500 ለሚሆኑ የተለያየ አካል ጉዳት ላለባቸው ተማሪዎች ድጋፍ አደረገ።

ደጋፍ ለተደረገላቸው ተማሪዎች በአካል ድጋፍ እና የቴክኖሎጂ መርጃ ቁሳቁስ እጦት ምክንያት ትምህርታቸውን እንዳያቆርጡ የዊልቸር፣ የክራንች፣ የነጭ በትር እና የጆሮ ማዳመጫ ናቸው ።

ድጋፉ በአዲስ አበባ ለሚገኙ አካል ጉዳተኞች የተከናወነ ሲሆን በሌሎች ክልሎችም የሚቀጥል መሆኑን የኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞች ማህበራት ፌደሬሽን ዋና ዳይሬክተር አባይነህ ጉጆ ተናገረዋል።

የኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ኮሚንኬሽን ኦፊሰር መሳይ ወብሸት ኩባንያው ያደረገው ድጋፍ ማህበራዊ ሀላፊነቱን ለመወጣት ያደረገው መሆኑን ተናግረዋል።

ኤፍ ኤም አዲስ 97.1 ‹‹ለተሻለ ነገ እናንብብ ››የሁለተኛ ቀን መራጭ ደራሲ ዘነበ ወላ ነው፡፡ደራሲው የማንበብ ልምዱን እንዲህ አጋርቷል፡፡ ‹‹እኔ 24 ሰዓታት ስራዬ ብዬ የማነብበት ጊዜ ...
26/02/2024

ኤፍ ኤም አዲስ 97.1 ‹‹ለተሻለ ነገ እናንብብ ››የሁለተኛ ቀን መራጭ ደራሲ ዘነበ ወላ ነው፡፡ደራሲው የማንበብ ልምዱን እንዲህ አጋርቷል፡፡

‹‹እኔ 24 ሰዓታት ስራዬ ብዬ የማነብበት ጊዜ አለ፤ ጠዋት ከእንቅልፌ ከመነሳቴ በፊት አነባበለሁ፡፡ ስተኛም እንደዛው፤ በቦርሳዬ ውስጥ የማነበውን ነገር ይዤ ነው የምንቀሳቀሰው፡፡ 24 ሰዓታት ማንንም በስልክ ሳላናግር ልቆይ፤ ሁለት እና ሶስት ቀን አልፎም ሳምንት ከቤት ሳልወጣ ላነብ እችላለሁ፡፡ ››

ደራሲ ዘነበ ወላ ህዝቡ ቢያነባቸው ደስ የሚለኝ የምንግዜም ምርጥ መፅሃፍት ምርጫዎቼ በማለት የሚከተሉትን ዘርዝሯል፡፡
1 ፍቅር እስከ መቃብር፡- ሀዲስ አለማየሁ
2 ከአድማስ ባሻገር ፡- በዓሉ ግርማ
3 የታንጉት ምሥጢር፡- ብርሃኑ ዘርይሁን
እንደተወዳጁ ደራሲ ዘነበ የማንበብ ትልቁ ጥቅሙ አንብበህ የራስህን ሃሳብ ማሰብ እንድትችል ማድረጉ ነው፡፡ ስታነብ ደስታን ትገበያለህ፤ ቋንቋህ ያድጋል በሃሳብ ትመጥቃለህ፤ በአንድ ጉዳይ በአንድ አቅጣጫ ብቻ ከማሰብ ትወጣለህ፤ እውነትህን በእራስህ እምነት ልክ ብቻ ከማየት መላቀቅ የምትችለው ስታነብ ነው ይላል፡፡

እርስዎም የራስዎን ምርጥ 3 መፅህፋት መርጠው ያጋሩ

15ኛው አለም አቀፍ የምልክት ቋንቋ ጉባኤ  በ2017 ዓም በኢትዮጵያ እንደሚካሄድ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ።ሚኒስቴሩ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር በቀጣዩ አመት...
14/02/2024

15ኛው አለም አቀፍ የምልክት ቋንቋ ጉባኤ በ2017 ዓም በኢትዮጵያ እንደሚካሄድ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ።

ሚኒስቴሩ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር በቀጣዩ አመት ዓለም አቀፍ የምልክት ቋንቋ ጉባኤን ለመጀመሪያ ጊዜ በኢትዮጵያ ለማዘጋጀት የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል።

ጉባኤው ከጥር 6 እስከ 9 ቀን 2017 ዓ.ም የሚካሄድ መሆኑ በመድረኩ ተገልጿል።

ስምምነቱን የተፈራረሙት የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትሯ ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬና የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት ዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ ትብብሩ ጉባኤውን በተሳካ መልኩ ለማካሄድ የሚያስችል መሆኑን ጠቅሰዋል።

በዚሁ ወቅት የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትሯ ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬ የዓለም የምልክት ቋንቋ ጉባኤ በቀጣይ አመት ለመጀመሪያ ጊዜ በኢትዮጵያ እንደሚካሄድ ተናግረዋል።

ይህንን ተከትሎ ሚኒስቴሩ ጉባኤውን ከብሔራዊ መስማት ከተሳናቸው ማህበርና ከተለያዩ አጋር ድርጅቶች ጋር በመተባበር ለማካሄድ ዝግጅት መጀመሩን ገልጸዋል።

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት ዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ በበኩላቸው የኢትዮጵያን ስም ከፍ የሚያደርጉና የአገራትን ትስስር ለማጠናከር የሚያስችሉ ተግባራትን ዩኒቨርሲቲው እያከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።

በዚህ ረገድ ጉባኤው በኢትዮጵያ እንዲካሄድ የተለያዩ ጥረቶች ሲደረጉ መቆየታቸውን አስታውሰዋል።

የዩኒቨርሲቲው ምሁራን ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ጋር በመተባበር ጉባኤው የተሳካ እንዲሆን የሚጠበቅባቸውን ሚና ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።

10/02/2024

የኢቢሲ ጋዜጠኛ ኢያሱ ፈጠነ ከዚህ አለም በሞት ተለየ
**************

ለረጅም አመታት በኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ያገለገለው ጋዜጠኛ ኢያሱ ፈጠነ ከዚህ አለም በሞት ተለየ።

ጋዜጠኛ ኢያሱ ፈጠነ ከ1999 ዓ.ም ጀምሮ በኢቢሲ ከሪፖርተርነት እስከ ከፍተኛ ኤዲተርነት አገልግሏል።

በ1975 ዓ.ም ሰኔ 12 ቀን በወንጂ ሸዋ የተወለደው ኢያሱ በተወለደ በ41 አመቱ በድንገተኛ አደጋ ከዚህ አለም በሞት ተለይቷል።

ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በኢትዮጵያ ቋንቋዎችና ስነ ጽሑፍ በመጀመሪያ ድግሪ የተመረቀው ጋዜጠኛ ኢያሱ ህይወቱ እስካለፈችበት ቀን ድረስ ላለፉት 17 አመታት በሞያው ሀገሩን ሲያገለግል ቆይቷል።

ጋዜጠኛ ኢያሱ ፈጠነ ባለትዳርና የሁለት ልጆች አባትም ነበር።

የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን በጋዜጠኛ ኢያሱ ፈጠነ ህልፈተ ህይወት የተሰማውን ጥልቅ ሃዘን እየገለፀ፤ ለቤተሰቦቹ ለወዳጅ ዘመዶቹ እና ለስራ ባልደረቦቹ መፅናናትን ይመኛል፡፡

ትናንት በጣም አዝኜ ነው የዋልኩት። ምክንያቱ ደግሞ አምና ያስተማርኳት ጎበዟና ጸባየ ሠናይዋ ተማሪዬ ህሊና ጌታነህ በመኪና ተገጭታ መሞቷን መስማቴ ነው። በ2015 ዓም የከፍተኛ ትምህርት (ዩ...
31/01/2024

ትናንት በጣም አዝኜ ነው የዋልኩት። ምክንያቱ ደግሞ አምና ያስተማርኳት ጎበዟና ጸባየ ሠናይዋ ተማሪዬ ህሊና ጌታነህ በመኪና ተገጭታ መሞቷን መስማቴ ነው። በ2015 ዓም የከፍተኛ ትምህርት (ዩኒቨርሲቲ) መግቢያ ፈተናን ከፍተኛ ውጤት ካሰመዘገቡ ዓይነሥውራን ተማሪዎች መካከል ህሉ ቀዳሚዋ ነበረች። በዚህም ምክንያት በከንቲባ አዳነች አበቤ ከፍተኛ ሽልማት ተበርክቶላታል። በዘንድሮው 2016 ዓም አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በመግባት የፍሬሽ ማን ኮርስን በከፍተኛ ነጥብ በማጠናቀቅ ዩኒቨርሲቲው የህግ ትምህርት እንድትማር የመጀመሪያ ምርጫዋን ጠብቆላት በዝግጅት ላይ ነበረች። ከስድስት ኪሎ ዩኒቨርሲቲ (በአምስተኛ በር ወጥታ) ወደ ዓይነ ሥውራን ማህበር (የካቲት 12 ሆስፒታል) በመሻገር ላይ እያለች በከፍተኛ ሁኔታ በመኪና ተገጭታ ወዲያው ህይወቷ አልፏል።

ለተሻለ ትምህርት ቤተሰቦቿን ተለይታ ከደሴ የመጣችው ህሊናን የመኪና አደጋ ያጋጠማትና ሕይወቷን የተነጠቀችበት ቦታ በቅርብ የማውቃቸውን ጨሞሮ በርካታ ዓይነሥውራን ተማሪዎችን በአጭር ቀጭቷል። መፍትሔ ለምን እንደማይበጅለት አይገባኝም። አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲስ እንዴት የተማሪዎቹ ሕይወት መቀጠፍ አይገደውም!? የትራፊክ ጽ/ቤትም አንድ ቦታ ላይ ተደጋጋሚ አደጋ ሲደርስ በቸልታ አይቶ እንዳላየ ማለፉ አስገራሚ ነው።
በብዙ ስጠብቅሽ አንዱ ክልፍልፍ በአጭሩ አስቀርቶ ምድራዊ ስኬትሽን እንዳታዪ እንቅፋት ቢሆንሽም ቸሩ እግዚአብሔር ነፍስሽን በአጸደ ገነት ያሳርፍ ዘንድ ቅዱስ ፈቃዱ ይኹን!

(አምና አንድ ክፍል ሆነው እየተፎካከሩ ፣ እየተረዳዱ እስከ ዩኒቨርሲቲ አብራት የዘለቀችው ጓደኛዋ ተማሪዬ ልዕልትም አብረው ሲሻገሩ ነበርና አደጋው የደረሰባቸው እሷም ከባድ የአካል ጉዳት ገጥሟት በሆስፒታል ትገኛለች)

፳፪/፭/፲፮ ዓ.ም

የወይን ዘለላ እንደፃፈችዉ።

አንጋፋው ጋዜጠኛ አስፋው መሸሻ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።ጋዜጠኛ አስፋው በአሜሪካን አገር  ህክምናውን ሲከታተል መቆየቱ ይታወሳል።ለቤተሰቦቻቸው እና ወዳጅ ዘመዶቻቸው መጽናናትን  ይመኛል።
14/01/2024

አንጋፋው ጋዜጠኛ አስፋው መሸሻ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።

ጋዜጠኛ አስፋው በአሜሪካን አገር ህክምናውን ሲከታተል መቆየቱ ይታወሳል።

ለቤተሰቦቻቸው እና ወዳጅ ዘመዶቻቸው መጽናናትን ይመኛል።

ከዚህ ዓለም ድካም አርፋለች 😭* ለ25 ዓመታት በ Etv ሰርታለች  የኢቲቪዋ በልጆች ጊዜ ፕሮግራም የአባባ ተስፋዬ የሥራ አጋር ፣ ቅኝት ፣ በመዝናኛ ላይ  ድንቅ መሰናዶዎቿ የምትታወቀው  "...
24/12/2023

ከዚህ ዓለም ድካም አርፋለች 😭

* ለ25 ዓመታት በ Etv ሰርታለች

የኢቲቪዋ በልጆች ጊዜ ፕሮግራም የአባባ ተስፋዬ የሥራ አጋር ፣ ቅኝት ፣ በመዝናኛ ላይ ድንቅ መሰናዶዎቿ የምትታወቀው "አይኒ"- Aynalem Balcha ሥርዓተ ቀብር ነገ፣ በቤተል ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ከቀኑ 9:00 ሰአት ይፈፀማል።

አይናለም ባልቻ

ተወዳጅ ሚድያ እና ኮሚኒኬሽን መዝገበ-አእምሮ በሚል ርእስ የ180 የሚድያ ሰዎችን ታሪክ በመጽሐፍ የህይወት ታሪኮችን ሰንዶ ነበር። በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የልጆች ፕሮግራም ላይ ሰፊ አገልግሎት የሰጠች ጋዜጠኛ አይናለም ባልቻ አንዱ አንደነበር አስነብቦኗል።

አይናለም ባልቻ

አይናለም ባልቻ ሐምሌ 21 ቀን 1961ዓ.ም ነበር የተወለደችው፡፡

አይናለም ከቤተሰቦቿ ጋር የነበራትን ግንኙነት ስንመለከት አባቷን የማታውቅ እናቷ ደግሞ ገና ልጅነቷን ሳትጨርስ በሞት ያጣች ልጅ ናት፤ ይህ ባሳሰባቸው በጎረቤቶቻቸው አማካይት ከወንድሟ ጋር የታችኛው ቤተመንግስት ውስጥ በነበረ ፍልውሃ የህፃናት ማሳደጊያ እንዲመዘገቡ ተደርገው የልጅነታቸውን ጊዜ አሳልፈዋል፡፡

አይናለም የህፃናት ማሳደጊያ ተቋምን ከተቀላቀለች በኋላ በወቅቱ እድሜዋ ለትምህርት ደርሷልና በእድገት በኅብረት ዘመቻ በቀድሞ አጠራሩ በየነ መርዕድ የተሰኘ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ገባች፡፡

በትምህርቷ እሳት የላሰች ሆነችና በአንድ ዓመት ውስጥ በመጀመሪያው መንፈቀ- ዓመት 1ኛ ክፍልን ተሻግራ ወደ ሁለት ገባች፡፡ በዓመቱ መጨረሻም ወደ 3ኛ ክፍል ተዘዋወረች፡፡እስከ አራተኛ ክፍልም በዚሁ ትምህርት ቤት ትምህርቷን ተከታተለች፡፡

የአይናለም ባልቻ ሌላኛው የልጅነቷ ክፍል እና ያደገችው ደግሞ በህፃናት አምባ ነው፡፡ ወደ ተቋሙ የገባችበት ራሱ ሂደት ነበረው፡፡ ይህም ህፃናት አምባ ሲቋቋምም ዓለምፀሐይ ወዳጆ ሙዚቃ ልታዘጋጅ ልጆችን በየህጻናት ማሳደጊያው በመዞር ታሰባስብ ነበር፡፡ ከእነዚህም ህፃናት መካከል ደግሞ አይናለም ካለችበት ፍልውሃ የህፃናት ማሳደጊያ ከተመረጡት ህፃናት መካከል አንዷ ሆነች፡፡

ለዚህም ዝግጅት በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር እና በአምባሳደር ቴአትር ቤት በፕሮግራም ስልጠናውን ከሚወስዱት ጋር አንድ ላይ ትሰለጥን ነበር፡፡

ሕፃናት አምባ ከእነአይናለም ቀድመው መግባት የነበረባቸው ልጆች ገብተውበት ነበር፡፡ የሰለጠኑትን በዚያው በህፃናት አምባ የተለያዩ ያዘጋጇቸውን መዝሙሮች

እነ ጋሼ መንግስቱ አባታችን፣
አባባ የወደቀለት ብሩህ ዓላማ የመሳሰሉትን ከፍተኛ ባለስልጣናት በተገኙበት አቅርበው ተደነቁበት፡፡

በዚህ መነሻነት ትርዒቱ በቀረበበት አላጌ በሚገኘው ህፃናት አምባ ከወንድሟ ቴዎድሮስ ሙሉጌታ ጋር ሳይለያዩ እንዲኖሩ አመጧቸው፤ግን እሱ በሰብለ ከ1-7 ዓመት ድረስ ያሉ ህፃናት የሚኖሩበት መንደር እርሷ ደግሞ በዘረዓይ ድረስ ከ7-18 ዓመት የሆኑ ልጆች በሚኖሩበት መንደር መኖር ጀመሩ፡፡

አምስተኛ እና ስድስተኛ ክፍልን በዚያው ከተማረች እና ሚኒስትሪን ከወሰደች በኋላም ወደ ጀርመን በመሄድ ለ20 ቀናት በተዘጋጀ ፌስቲቫል ላይ የመሳተፍ እድል አግኝታለች፡፡

ከጀርመን ከተመለሰች በኋላም በህፃናት አምባ ቆይታዋ የተለያዩ የውጭ ሃገራት ዜጎችን ጨምሮ ማዕከሉን በእንግድነት በሚጎበኙበት ጊዜ አስጎብኚም ሆነ አስተርጓሚ ሆና ተመርጣ ነበር፡፡

በዚህም ተግባሯን ስትከውን እንደ አጋጣሚ የቡልጋሪያ አባት ሀገር ግንባር ማህበር ፕሬዚዳንት እና ሌሎች አባላቶቻቸው ግቢውን ሊጎበኙ መጡ፡፡ ይሄም አይናለምን ጨምሮ በማዕከሉ ላሉ ልጆች መልካም ዜናን ይዞ የመጣም ነበር፡፡ ምክንያቱም ከቡልጋሪያ የመጡት እንግዶች ግቢውን ጎብኝተው ሲያጠናቅቁ ጎበዝ ጎበዝ የሆኑ 2 ተማሪዎች በየዓመቱ ወደ ቡልጋሪያ ሄደው በማህበሩ አማካይነት የትምህርት እድል እንዲያገኙ የሚያደርግ ነበር፡፡

በግቢው በተዘጋጀ መስፈርት መሰረትም አይናለም እና የያኔው የትምህርት ቤት ጓዷ እንዲሁም የኋላ ባለቤቷ የነበረው አደም ተመራጭ ሆነው የፓርቲ ተማሪዎች ይሄዱበት በነበረው ቻርተር አውሮፕላን ወደ ቡልጋሪያ ከዋና መዲናዋ ሶፊያ 183 ኪ.ሜ ርቀት ካላት የቱሪስት መናኸሪያ ወደሆነችው ከተማ ወደ ቡርጋስ ለትምህርት አመሩ፡፡

በቡልጋሪያም ሞግዚት ሆና በተመደበችላቸው እናት ልብስ እና ጫማ ተገዝቶላቸው የትምህርት ወቅት ሲጀመርም 2 ከህንድ፣ 2 ከቬየትናም እና ከኮንጎ የመጡ ልጆችን ጨምረው 10 በመሆን የቋንቋ ትምህርታቸውን ጀመሩ፡፡

መምህራቸው ፈፅሞ ከሃገሪቱ ቋንቋ ውጪ መግባባትን አትፈቅድም፡፡ እና አይናለምም እንደምትለው በሚደነቀው የቋንቋ የማስተማር ዘዴያቸው በ3 ወራት ምንም የማያውቁትን ቋንቋ መግባባት የሚችሉበት ሆነ፡፡

በዚህ ወቅትም በተለይ በመንገድ የሚመለከቷት የጸጉር አሰራሯን ተመልክተው እንዴት እንደሰራችው ሲጠይቋት እና መሰል ንግግሮችን ከሌሎች ጋር ማድረጓ ደግሞ ሰዎችን ከመተዋወቋም ባሻገር ቋንቋውንም ለማሳደግ ረዳት፡፡

ወደ ቡልጋሪያ በወሰዳቸው የቡልጋሪያ አባት ሀገር ግንባር መሪ አማካይነት በሃገሪቱ ምርጥ በሚሰኘው ትምህርት ቤት እንዲማሩ ተብሎ በተሰጠው ትዕዛዝ መሰረት በታሪካዊው ጊዮርጊ ሳቫ ራኮቭስኪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማረች፡፡

የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቷን እየተከታተለች በነበረበት ወቅት በ1977አ.ም የ10ኛ ክፍል ተማሪ ሆና በሀገራችን ተከስቶ በነበረው ድርቅ የሀገሬን ሰዎች መርዳት አለብኝ በማለት ትኖርበት ከነበረው ቡልጋሪያ ድጋፍ የሚሆን ምግብ እና ልብስ የተለያዩ ት/ቤቶች በመዘዋወር በሀገራችን የተከሰተውን ሁነት በመንገር አስቸኳይ እርዳታም ማግኘት ችላ ነበር፡፡ በዚህም የተሰበሰበውን ዱቄት እና አልባሳት በመርከብ በማስጫን ለወገኗ በዛ እድሜዋ በምትችለው ሁሉ መድረስም ችላ ነበር፡፡

ከትምህርት ቤት ጓደኞቼ ጋርም ጥሩ እና መልካም ትዝታዎች አሉኝ የምትለው አይናለም ባልቻ ሁለተኛ ደረጃን ስታጠናቅቅ የዩኒቨርሲቲ ትምህርቷን በዛው ቀጠለች፤ አብዛኛውን የቡልጋሪያ አካባቢ እና ዘዬን ለይቼ አውቃለሁ የምትለው አይናለም በዩኒቨርሲቲ ቆይታዋም ጥቁር ነሽ ተብላ ተንቃ እና አድልዎ ደርሶባት ሳይሆን ተከብራ መማሯን ነው የምታስታውሰው፡፡

የሕክምና ትምህርትን መማር ምኞቷ የነበረ ቢሆንም 8ኛ ክፍል ተማሪ በነበረችበት ወቅት ላብራቶሪ ክፍል ውስጥ ከመምህሯ ጋር በተፈጠረ አለመግባባት እና በሀገሪቱ ያለው ትምህርት ከባድ በመሆኑ የሃሳቧ መቀየር መነሻ ሆኗት፡፡ በዙሪያዋ የነበሩ ሰዎች "ለምን ጋዜጠኝነትን አትማሪም" የሚል ውትወታቸውን ተቀብላ የጋዜጠኝነት ትምህርትን መማር መረጠች፡፡

በቡልጋሪያ ለ 5 ዓመት በተማረችው የጋዜጠኝነት ትምህርት ክፍል ከሙሉ የመማሪያ እና አጋዥ መጽሐፍት አንስቶ የመምህራኖቻቸው የትምህርት ደረጃን እና የትምህርት አሰጣጣቸው የተለየ መሆኑ ትምህርቱን ወድጄ እንድማር እና የበለጠ እንዳውቀውም ረድቶኛል ትላለች፡፡

በ1986 ዓ.ም የኢትዮጵያ ማስ ሚዲያ እና ኮሚዩኒኬሽን በሚል ወደ 59 ገጽ የሚጠጋ የመመረቂያ ጽሑፍንም ለመስራት ተባባሪ በማጣት እና በከባድ ፈተናም ቢሆን በጥሩ ውጤት የማስተርስ ዲግሪዋንም በቡልጋሪያ አግኝታለች፡፡

በዚያን ወቅት እርግጥ ነው ታላቅ ውለታ የዋሉላትን አቶ ተሾመ ብርሀኑ ከማልን ማመስገን ትሻለች፡፡

የሥራ ጅማሮ እና ጉዞ

አይናለም የዩኒቨርሲቲ ትምህርቷንም ካጠናቀቀች በኋላ እናት አባት ሳይኖረኝ ያሳደገኝም ሆነ ቤተሰብ የሆነኝ ኢትዮጵያዊ ሁሉ ነው በማለት የአምስት ዓመት ልጇን ይዛ ኑሮዋን በዚሁ ለማድረግ ወደ ሀገሯ ኢትዮጵያ ተመለሰች፡፡

ከተመለሰች በኋላም ወደ ኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ብታመለክትም ሳይጠሯት ቀረ፤ በሜጋ ኪነ -ጥበባት ማዕከልም ያሏትን ሃሳቦች አቅርባ በመጠባበቅ ላይ ነበረች፡፡ ያሉትን ፈተናዎች አልፋ ጽፈሽ ነይ የተባለችውን ሁሉ አሟልታ በ1988 ዓ.ም የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ስራዋን ጀመረች፡፡

በዜና ክፍልም መልካም ሰው በምትለው አለቃዋ በነበረው ፍስሃ ገብርኤል አማካይነት የስክሪፕት ሃሳብ እና አፃፃፍን በሚገባ ተምራ ሥራውን በሚገባ ተላመደችው፡፡
የተለያዩ ክፍሎች ውስጥ ዜና፣ መዝናኛ እና ህፃናት ክፍል ውስጥም የሰራች ሲሆን በርካታ ፕሮግራሞችንም ወደ ተመልካቹ ማድረስም ችላለች፡፡

የልጆች ፕሮግራም ላይ ደግሞ የምትሰራቸው ፕሮግራሞች እና ታደርጋቸው የነበሩ የማስተዋወቅ መንገዶች የተለዩ እና ተወዳጅም ነበሩ፡፡

በህፃናት ክፍል ቆይታዋም የአዋቂ ሙዚቃዎች እንደሚሰሩት ሁሉ የህፃናት ሙዚቃዎች እንዲሰሩ እና እንዲቀረፁ በማድረግ ቀዳሚ ናት፡፡ ድራማዎች እንዲሰሩም በማድረግ በክፍሉ አዳዲስ ሃሳቦችን ማምጣትም ችላለች፡፡

ከ25 ዓመት የጣቢያው የሥራ ቆይታዋ ውስጥም ረዥሙ የሆነውን የሥራ ክፍል ያሳለፈችበትን ማለትም 15 ዓመትን የሰራችበት የህፃናት ክፍልን ወደ መጨረሻ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የሥራ ቆይታዋም የክፍሉ ዳይሬክተር በመሆን አገልግላለች፡፡ ቅኝት የሚባል ፕሮግራም ትሰራ ነበር፡፡ ይህ ፕሮግራም ባህል እና ታሪክ ላይ የሚያተኩር ሲሆን ፕሮግራሙንም ለ 4 አመታት ሰርታዋለች።

የቤተሰብ ሁኔታ

አይናለም ባልቻ ከቀድሞ ባለቤቷ አንድ ልጅ ያፈራች ሲሆን ልጇንም ለብቻዋ አሳድጋ በኮምፒውተር ሳይንስ አስመርቃለች:: ልጇም አፍሪካ ኅብረት ውስጥ ለ2 ዓመት ካገለገለች በኋላ አሁን በተባበሩት መንግስታት ማህበራዊ ፈንድ (UNFPA) ውስጥ በመስራት ላይ ትገኛለች፡፡ ባለትዳር እና የሁለት ልጆም እናት በመሆን እናቷን አያት አድርጋታለች፡፡

አይንዬ ነፍስሽ በሰላም ትረፍ 😭😭

በአለም አቀፍ ለ32ኛ ግዜ እንዲሁም በሀገር እቀፍ ደረጃ ለ31ኛ ግዜ ህዳር 23 2016 የሚከበረውን አለም አቀፍ የአካል ጉዳተኞችን ቀን ምክንያት በማድረግ በሀይሌ ግራንድ ሆቴል ጋዜጣዊ መግ...
30/11/2023

በአለም አቀፍ ለ32ኛ ግዜ እንዲሁም በሀገር እቀፍ ደረጃ ለ31ኛ ግዜ ህዳር 23 2016 የሚከበረውን አለም አቀፍ የአካል ጉዳተኞችን ቀን ምክንያት በማድረግ በሀይሌ ግራንድ ሆቴል ጋዜጣዊ መግለጫ እየተሰጠ ነው:: በአሉ የፊታችን ህዳር 23 በአሶሳ ከተማ በደማቅ ሁኔታ ይከበራል

" ለአካል ጉዳተኞች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት እና ለዘላቂ የልማት ግቦች ስኬት -ትርጉም ያለው ትብብር!!

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከ3 ዓመት በፊት እንዲቋቋም አቅጣጫ ባስቅመጡት መሰረት አዲስ የተቋቋመውን የኢትዮጵያ አካል ድጋፍ አገልግሎት ማዕከል ዛሬ ረፋድ ላይ መርቀዋል። ማዕከሉ በተፈጥ...
05/11/2023

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከ3 ዓመት በፊት እንዲቋቋም አቅጣጫ ባስቅመጡት መሰረት አዲስ የተቋቋመውን የኢትዮጵያ አካል ድጋፍ አገልግሎት ማዕከል ዛሬ ረፋድ ላይ መርቀዋል። ማዕከሉ በተፈጥሮ እና በአደጋ ምክንያት የአካል ጉዳተኛ ለሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች በሀገር ውስጥ አጋዥ ቁሶችን ለማምረት እና ለማቅረብ የተቋቋመ ማዕከል ነው።

የኢትዮጵያ አካል ድጋፍ አገልግሎት ማዕከል አጋዥ ቴክኖሎጂዎችን ለማምረት፣ ለማደስ እና ለማቅረብ የተቋቋመ ሲሆን ተደራሽ፣ ጥራት ያለው እና ደንበኛ ተኮር የሰው ሰራሽ እና የአካል ድጋፎች አገልግሎቶችን ለህብረተሰቡ የሚሰጥ ይሆናል።

HAPPY IRREECHAA  HOLIDAY 2016
06/10/2023

HAPPY IRREECHAA HOLIDAY 2016

Address

Addis Ababa
27526

Telephone

+251913351180

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Bisrat Promotion posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Bisrat Promotion:

Share