Addis Maleda - አዲስ ማለዳ

Addis Maleda - አዲስ ማለዳ አዲስ ማለዳ በቻምፒየን ኮምንኬሽንስ ተዘጋጅታ በሃገራችን ማኅበራዊ ለውጥ ለማምጣት ከሚዲያ የሚጠበቀውን ሚዛን የጠበቀ እና የተረጋገጠ መረጃ ለዜጎች የማድረስ ሚና ለመወጣት የምትሰራ ሚዲያ ነች።

10/09/2025

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፣ የ2018 ዓ.ም የዘመን መለወጫ በዓልን መግባት አስመልክተው የእንኳን አደረሳችሁ ቃለ ምእዳንና ቡራኬ ሰጥተዋል። የቅዱስነታቸው ሙሉ መልእክት የሚከተለው ነው።

“በታላቁ ሕዳሴ ግድብ ምርቃት ዋዜማ ዕለት በደብረ ጽዮን ገብረ ሚካኤል የሚመራው የሕወሓት ቡድን ታጣቂዎች በአላማጣ ከተማ የሽብር ተግባር ሲፈጽሙ አድረዋል”- አቶ ኃይሉ አበራ፣ የአላማጣ ከተ...
10/09/2025

“በታላቁ ሕዳሴ ግድብ ምርቃት ዋዜማ ዕለት በደብረ ጽዮን ገብረ ሚካኤል የሚመራው የሕወሓት ቡድን ታጣቂዎች በአላማጣ ከተማ የሽብር ተግባር ሲፈጽሙ አድረዋል”
- አቶ ኃይሉ አበራ፣ የአላማጣ ከተማ ከንቲባ

ረቡእ ጳጉሜ 5 ቀን 2017 ዓ.ም ( #አዲስ ማለዳ)

በታላቁ ሕዳሴ ግድብ ምርቃት ዋዜማ ዕለት በደብረ ጽዮን ገብረ ሚካኤል የሚመራው የሕወሓት ቡድን ታጣቂዎች በአላማጣ ከተማ የተለያዩ አካባቢዎች ዝርፊያ፣ በገበያ ማዕከል ላይ ጥይት ተኩሰው ቃጠሎ በማስነሳት ንብረት በማውደምና ንጹሐንን በመግደል የሽብር ተግባር ሲፈጽሙ ማደራቸውን የአላማጣ ከንቲባ አቶ ኃይሉ አበራ ለአዲስ ማለዳ ገለጹ።

በደብረ ጽዮን ገብረ ሚካኤል የሚመራው የሕወሓት ቡድን ታጣቂዎች በአላማጣ ከተማ በተለያዩ ጊዜያት ጥቃት ሲፈጽሙ መቆየታቸውን ያስታወሱት ከንቲባው፤ ጳጉሜ 3 ቀን 2017 ዓ.ም በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ምርቃት ዋዜማ ዕለት ደግሞ ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ጀምሮ ሕዝቡ የግድቡን ምርቃት ወጥቶ እንዳያከብር በሚል አስተሳሰብ በአላማጣ ከተማ ሽብር ሲፈጽሙ ማደራቸውን ተናግረዋል።

በዚህም በዕለቱ ምሽት ሦስት ሰዓት ጀምሮ በከተማዋ የተለያዩ አካባቢዎች ዝርፊያ ፈጽመዋል። በተለይም ወደመሆኒ፣ ቆቦና ኮረም መሄጃ መስቀለኛ መንገድ አደባባይ ላይ ሆነው ተኩስ በመክፈት በአካባቢው በሚገኝ ባለአራት ወለል ሕንጻ የገበያ ማዕከል ላይ እሳት እንዲነሳ በማድረግ የገበያ ማዕከሉ ሙሉ በሙሉ አውድመዋል።

በገበያ ማዕከሉ በተነሳው እሳትም በውስጡ የሚገኙ ከአርባ በላይ ሱቆች ሙሉ በሙሉ ወድሟል። አንድ ሰው በከፍተኛ ደረጃ የቆሰለ ሲሆን የሦስት ሰዎች ሕይወትም አልፏል።
የሕወሓት ታጣቂዎች በከተማዋ አካባቢዎች ከፈጸሙት ዝርፊያ በአሻገር በገበያ ማዕከሉ በከፈቱት ተኩስ በውስጡ ያሉ ተቀጣጣይ ነገሮች የተነሳ በተፈጠረው ቃጠሎ የሞቱትን ጨምሮ በድምሩ በንጹሐን ላይ በፈጸሙት ጥቃት በአራት ሰዎች ላይ የሞትና በአምስት ሰዎች ላይ ደግሞ የመቁሰል አደጋ መፈጸሙን ከንቲባው ለአዲስ ማለዳ ገልጸዋል።

የጥቃቱን ዓላማ በተመለከተም “በተለያየ ጊዜ በሞከሩት ተመሳሳይ ጥቃት አልሳካ ያላቸውን ሕዝቡን ንብረቱን በመዝረፍ፣ መኖሪያና መስሪያ ቦታውን በማቃጠልና በመግደል ሕዝቡን በማሸበር በኃይል ማፈናቀልና ከከተማው በማስወጣት የራሳቸውን አስተዳደር መመሥረት ነው” በማለት አብራርተዋል።

በደብረ ጽዮን ገብረ ሚካኤል የሚመራው የሕወሓት ታጣቂ ቡድን ዋነኛ ዓላማው እንዲያስተዳድረው ወዳልተፈቀደለት አካባቢ በኃይል በመግባትና ሕዝብን በማሸበር የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት በማፍረስ በአካባቢው ግጭትና ጦርነት ለመቀስቀስ መሆኑንም ከንቲባው አመላክተዋል።

ይህን የተገነዘበው የከተማው ሕዝብና መንግሥትና በስፍራው የሚገኜው የመከላከያ ሠራዊት አባላትም የታጣቂ ቡድኑን ሕገ ወጥና አፍራሽ ድርጊት በትግስት እየተከታተሉት መሆናቸውንና እስከመጨረሻው ድረስ ጉዳዩን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት እየተጠባበቁ መሆናቸውን የገለጹት ከንቲባው፤ ጉዳዩን ለክልልና ለፌደራል መንግሥታት ማሳወቃቸውንም ገልጸዋል።

“የትግራይ ሕዝብም ጉዳዩን ተገንዝቦታል፤ የታጣቂ ቡድኑን ድርጊት እየተቃወመውም ነው፤ ዓለም አቀፉ ማሕበረሰብም ችግሩን የተገነዘበው ይመስላል፤ እኛ ለሁሉም በመረጃና በማስረጃ አሳውቀናል” ያሉት የአላማጣ ከንቲባ አቶ ኃይሉ አበራ፤ እስከመጨረሻው በትግስትና በሰላማዊ መንገድ ሄደን ታጣቂ ቡድኑ ከዚህ የሽብር ድርጊቱ የማይመለስ ከሆነ ግን ሕዝቡ በእጁ ያለውን አማራጭ ለመጠቀም የሚገደድ መሆኑን አስገንዝበዋል።

ተጨማሪ ትኩስ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኜት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA

የግብጽ ክስና በግድቡ ምርቃት ላይ የተገኙ አፍሪካውያን መሪዎች ምስክርነትረቡእ ጳጉሜ 5 ቀን 2017 ዓ.ም ( #አዲስ ማለዳ)በኢትዮጵያውያን ላብና ደም፣ ሙሉ በሙሉ በራሳቸው ወጭ የተገነባውን...
10/09/2025

የግብጽ ክስና በግድቡ ምርቃት ላይ የተገኙ አፍሪካውያን መሪዎች ምስክርነት

ረቡእ ጳጉሜ 5 ቀን 2017 ዓ.ም ( #አዲስ ማለዳ)

በኢትዮጵያውያን ላብና ደም፣ ሙሉ በሙሉ በራሳቸው ወጭ የተገነባውንና ከአስራ አራት ዓመት እልህ አስጨራሽ ጉዞ በኋላ በትናንትናው ዕለት ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ መመረቁን ተከትሎ ግብጽ ሁነቱን በመቃወም ለተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጸጥታው ምክር ቤት አቤቱታ አስገብታለች።

የግብጽ ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ባደር አብደላቲ በዚሁ ደብዳቤያቸው፣ “ኢትዮጵያ ግድቡን ሕጋዊነት ለማላበስ ብዙ ያልተሳኩ ሙከራዎች ብታደርግም፣ ግድቡ ግን ዓለማቀፍ ሕጎችንና ደንቦችን የጣሰ ነው” በማለት የተለመደ ክሳቸውን ማቅረባቸውን ኢጀብት ቱዴይ እና የአናዱሉ ዘገባዎች ያመላክታሉ።

“ግብጽ በዓባይ ወንዝ ላይ ያላትን የህልውና ጥቅም በቀላሉ ትተዋለች ማለት ከንቱ ምኞት ነው” ሲል የገለጸው የአብደላቲ ደብዳቤ፤ ኢትዮጵያ የጋራ በሆነው የውሃ ሃብት ላይ በብቸኝነት ቁጥጥር እንድታደርግ ግብጽ እንደማትፈቅድና ካይሮ የህልውና ጥቅሟን ለማስከበር እንዲሁም በአለም አቀፍ ህግ እና በተባበሩት መንግስታት ቻርተር ስር የተፈቀዱትን ማናቸውም እርምጃዎች ለመውሰድ እንደምትችል ማስፈራሪያ አዘል ክሱን አሰምቷል

ግብጽ በግድቡ ዙሪያ ለጸጥታው ምክር ቤት ክስና አቤቱታ ስታቀርብ ይህ የመጀመሪያዋ ሳይሆን ከአስር ጊዜ በላይ ደጋግማ ያደረገችው መሆኑ ይታወቃል።

ግብጽ ይህን ትበል እንጂ በግድቡ ምርቃት ላይ የተገኙ አፍሪካውያን መሪዎች ግን ግድቡ ከኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለመላ አፍሪካ የትብብርና የአንድነት ብሎም የይቻላል መንፈስን የሚያጎናጽፍ ትእምርታዊ ፕሮጀክት መሆኑን መስክረዋል።

በዚህም በግድቡ ምርቃት ላይ የተገኙት የኬንያው ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ፣ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ አፍሪካ እጣ ፈንታዋን ራሷ እንደምትወስን ዓይነተኛ ማረጋገጫ መሆኑን ተናግረዋል።

“ዛሬ የዓባይ ግድብ ምርቃት ለጋራ ራዕያችን ወንድማዊ ትብብርን ማጠናከር እንዳለብን ያመላከተ ነው” ያሉት ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ በመሆኑም ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ሀገራዊ ፕሮጀክት ብቻ ሳይሆን የፓን አፍሪካኒዛም መገለጫ መሆኑን አመላክተዋል።

በምርቃት ሥነ ስርዓቱ ላይ የተገኙት የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሃሰን ሼክ መሀመድ በበኩላቸው እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ ያስመረቀችው ታላቁ የሕዳሴ ግድብ በቀጠናው ላሉ ሕዝቦች ሁሉ ታሪካዊ መሆኑን ተናግረዋል።

ፕሬዚዳንት ሀሰን ሸክ መሀመድ “ስለሆነም ስለቀጠናው ዕድገት ስናስብ ፉክክር ሳይሆን ትብብር ነው ማሰብ ያለብን” ብለዋል። ለዚህም ሶማሊያ የጎረቤት ሀገራት ሰላምና እድገት ለሚያጠናክሩ ተግባራትን በትብብር ለመስራት ቁርጠኛ መሆኗን አረጋግጠዋል።

በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የቤርቤዶስ ጠቅላይ ሚንስትር ሚያ ሞትሊ በበኩላቸው ግድቡ የታላቁ የዓድዋ ድል ተምሳሌት በምህንድስና ጥበብ ዳግም ተገልጦ የታየበት ነው በማለት አድናቆታቸውን ገልጸዋል።

የጅቡቲው ፕሬዝዳንት እስማኤል ኦማር ጌሌና የደቡብ ሱዳኑ ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር ማርዲያትም በግድቡ ምረቃ ስነ ሥርዓት ላይ ተገኝተው በተመሳሳይ ገንቢ አስተያየታቸውን አቅርበዋል።

ተጨማሪ ትኩስ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኜት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA

ያቋረጡትን ጨምሮ ሕጸናትና ተማሪዎች ወደትምህርት ቤት እንዲመጡ የተጀመሩ ንቅናቄዎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው ተገለጸማክሰኞ ጳጉሜ 4 ቀን 2017 ዓ.ም ( #አዲስ ማለዳ)በ2018 የትም...
09/09/2025

ያቋረጡትን ጨምሮ ሕጸናትና ተማሪዎች ወደትምህርት ቤት እንዲመጡ የተጀመሩ ንቅናቄዎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው ተገለጸ

ማክሰኞ ጳጉሜ 4 ቀን 2017 ዓ.ም ( #አዲስ ማለዳ)

በ2018 የትምህርት ዘመን ባለፈው ዓመት ከትምህርት ገበታ ውጪ የሆኑ ተማሪዎችን ጨምሮ ሁሉም ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ሕጻናትና ተማሪዎች ወደ ትምህርት ቤት እንዲመጡ የተጀመሩ ንቅናቄዎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው ትምህርት ሚንስቴር ገለጸ።

የ2018 የትምህርት ዘመን የትምህርት ቤቶች አከፋፈትን አስመልክቶ ትምህርት ሚኒስቴር ከክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊዎች ጋር የበይነ-መረብ ምክክር አድርጓል። በዚህም የ2018 የትምህርት ዘመን የመማር ማስተማር ሥራ ሰኞ መስከረም 5 ቀን 2018 ዓ.ም በይፋ የሚጀመር መሆኑን በትምህርት ሚንስቴር የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ወይዘሮ አየለች እሸቴ ገልጸዋል።

በትምህርት ካሌንደሩ መሠረት ዓርብ መስከረም 2 ቀን 2018 ዓ.ም ትምህርት ቤቶች ክፍት ሆነው መምህራንና ተማሪዎች ውይይት የሚያደርጉበትና መስከረም 5 ቀን 2018 ዓ.ም ደግሞ ትምህርት ቤቶች በይፋ ለሚጀመረው የትምህርት ስራ ቅድመ ዝግጅት የሚያደርጉበት ቀን መሆኑን ሚንስቴር ዲኤታዋ ተናግረዋል።

በመሆኑም በ2018 የትምህርት ዘመን ባለፈው ዓመት ከትምህርት ገበታ ውጪ የሆኑ ተማሪዎችን ጨምሮ ሁሉም ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ሕጻናትና ተማሪዎች ወደ ትምህርት ቤት እንዲመጡ የተጀመሩ ንቅናቄዎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው አመላክተዋል

ለዚህም ወላጆች፣ መምህራንና የዘርፉ ባለድርሻዎች የጀመሩትን የንቅናቄ ተግባር አጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባና የትምህርት ቤት ምዝገባውም እስከመጨረሻው ቀን ድረስ አጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባም ሚንስቴር ዴኤታዋ በውይይቱ ወቅት አሳስበዋል።

የተማሪዎችን ሥነ ምግባር በተመለከተም ከ2018 የትምህርት ዘመን ጀምሮ በየትኛውም ክልልና የከተማ አስተዳደር የሚገኝ ተማሪ ተንቀሳቃሽ ስልክ፣ ታብሌትና በማንኛውም የትምህርት ሥራ ላይ ተጽእኖ የሚያሳድሩና አዋኪ የሆኑ የኤሌክትሮኒክስ ቁሳቁሶችን ይዞ መገኘት ክልክል መሆኑንም ሚኒስትር ዴኤታዋ አስታውቀዋል።

ተጨማሪ ትኩስ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኜት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA

“ኢትዮጵያ ከሕዳሴ ግድብ የሚተካከል ለሰላማዊ ዓላማ የሚውል የኒውክሌር ፕላንት ትጀምራለች“ “በሚቀጥሉት አምስትና ስድስት ዓመታት በትንሹ 1 ነጥብ 5 ሚሊዮን ቤቶች ይገነባሉ”          ...
09/09/2025

“ኢትዮጵያ ከሕዳሴ ግድብ የሚተካከል ለሰላማዊ ዓላማ የሚውል የኒውክሌር ፕላንት ትጀምራለች“
“በሚቀጥሉት አምስትና ስድስት ዓመታት በትንሹ 1 ነጥብ 5 ሚሊዮን ቤቶች ይገነባሉ”
- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

ማክሰኞ ጳጉሜ 4 ቀን 2017 ዓ.ም ( #አዲስ ማለዳ)

ኢትዮጵያ ከሕዳሴን ግድብ የሚተካከል ለሰላማዊ ዓላማ ብቻ የሚውል የኒውክሌር ፕላንት በቅርቡ እንደምትጀምር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ምርቃት ላይ ገለጹ።

በጥቂት ሳምንታት ውስጥ የመጀመሪያው የጋዝ ፋብሪካ እንደሚመረቅ፤ ሁለተኛው የጋዝ ፋብሪካ እንደሚጀመር፣ የማዳበሪያ ፋብሪካ ሥራና በአፍሪካ ግዙፍ የሆነው የአየር መንገድ ሥራ የሚጀምሩ መሆናቸውንም ጠቅላይ ሚንስትሩ ተናግረዋል።

ከዚህ በተጨማሪም በሚቀጥሉት አምስትና ስድስት ዓመታት በትንሹ 1 ነጥብ 5 ሚሊዮን ቤቶች ለኢትዮጵያውያን የሚገነቡ መሆኑንና በድምሩ 30 ቢሊዮን ዶላር በላይ ሀብት የሚፈስባቸው አፍሪካን ቀና የሚደርጉና የኢትዮጵያን ብልጽግና የሚያበስሩ ሜጋ ፕሮጀክቶች የሚሠሩ መሆኑን አስታውቀዋል።

ተጨማሪ ትኩስ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኜት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA

የደም፣ የላብ እና የውሃ ጠብታ ምልክት ሆኖ የተሰራው የጠብታ ሐውልት በይፋ ተመረቀማክሰኞ ጳጉሜ 4 ቀን 2017 ዓ.ም ( #አዲስ ማለዳ)በግንባታው የተሳተፉትን ኢትዮጵያውያን የኅብረተሰብ ክፍ...
09/09/2025

የደም፣ የላብ እና የውሃ ጠብታ ምልክት ሆኖ የተሰራው የጠብታ ሐውልት በይፋ ተመረቀ

ማክሰኞ ጳጉሜ 4 ቀን 2017 ዓ.ም ( #አዲስ ማለዳ)

በግንባታው የተሳተፉትን ኢትዮጵያውያን የኅብረተሰብ ክፍሎች በሚያሳይ መንገድ በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ መገኛ የቆመው የደም፣ የላብ እና የውሃ ጠብታ ምልክት ሐውልት በቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው እና በባርቤዶስ ጠቅላይ ሚኒስትር ሚያ ሞትሊ ዛሬ በይፋ ተመርቆ ለዕይታ ክፍት ሆኗል።

ተጨማሪ ትኩስ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኜት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA

አሁን ሪቫኑ ተቆርጧል፤ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ተመርቋል!ማክሰኞ ጳጉሜን 4 ቀን 2017 ( #አዲስ ማለዳ)ይህ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በዛሬው እለት በክቡር የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ...
09/09/2025

አሁን ሪቫኑ ተቆርጧል፤ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ተመርቋል!

ማክሰኞ ጳጉሜን 4 ቀን 2017 ( #አዲስ ማለዳ)

ይህ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በዛሬው እለት በክቡር የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተመረቀ።

ከ14 ዓመታት በኋላ በመላ ኢትዮጵያውያን የጋራ ጥረት ለስኬት የበቃው የታላቁ ህዳሴ ግድብ ምረቃ ስነስርዓት ጉባ ላይ እየተካሄደ ነው።

በምርቃት ስነስርዓቱ ላይ የኬንያው ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ ፣ የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ ሞሀሙድ፣ የጅቡቲው ፕሬዚዳንት ኢስማኤል ኦማር ጌሌህ፣ የደቡብ ሱዳኑ ፕሬዚዳንት ሳልቫኪርና ሌሎችም መሪዎች በተገኙበት በዛሬው ዕለት ተመርቋል።

የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ይፋዊ ምረቃ ሥነ ስርዓት በድሮን እና በርችት ትርዒት እንዲሁም በሌሎች የተለያዩ ሁነቶች በዋዜማው ከትናንትና ምሽት ጀምሮ ሌሌቱን ሲከበር አድሯል።

ይህን ተከትሎም የሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት መስጫ አውቶብሶች ያለምንም ክፍያ አገልግሎት እየሰጡ መሆኑን እንዲሁም ኢትዮ ቴሌኮም ዛሬ ከጠዋቱ 12 ሰዓት እስከ 4 ሰዓት የሚቆይ ኢንተርኔት ለሁሉም ሰው ነፃ አድርጓል።

ኢትዮጵያዊ አንድነት የወለደው አዲሱ የኢትዮጵያውያን የጋራ ድል፤ ልክ እንደ ታላቁ የኢትዮጵያውያን የአድዋ ድል ገና ከአሁኑ ለመላ አፍሪካውያን የጋራ ትዕምርት መሆን የጀመረው ታላቁ የኢትዮጵያ...
09/09/2025

ኢትዮጵያዊ አንድነት የወለደው አዲሱ የኢትዮጵያውያን የጋራ ድል፤ ልክ እንደ ታላቁ የኢትዮጵያውያን የአድዋ ድል ገና ከአሁኑ ለመላ አፍሪካውያን የጋራ ትዕምርት መሆን የጀመረው ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ አፍሪካውያን ወንድምና እህቶች በተገኙበት በጋራ በድምቀት እየተመረቀ ነው!

ማክሰኞ ጳጉሜ 4 ቀን 2017 ዓ.ም ( )

ኢትዮጵያ የአየር ኃይሏን ለማጠናከር የፓኪስታንን ተሞክሮ የመውሰድ ፍላጎት እንዳላት ተጠቆመሰኞ ጳጉሜ 3 ቀን 2017 ዓ.ም ( #አዲስ ማለዳ)ኢትዮጵያ የአየር ኃይሏን ለማጠናከር የፓኪስታንን ...
08/09/2025

ኢትዮጵያ የአየር ኃይሏን ለማጠናከር የፓኪስታንን ተሞክሮ የመውሰድ ፍላጎት እንዳላት ተጠቆመ

ሰኞ ጳጉሜ 3 ቀን 2017 ዓ.ም ( #አዲስ ማለዳ)

ኢትዮጵያ የአየር ኃይሏን ለማጠናከር የፓኪስታንን ተሞክሮ የመውሰድ ፍላጎት እንዳላት ለዚህም ከፓኪስታን ጋር ወታደራዊና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቷን እያጠናከረች መሆኗ ተጠቆመ።

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ኢትዮጵያ ወታደራዊ ቅሟን ለማጠናከር ከተለመደው መንገድ ወጣ ያሉ አዳዲስ ዲፕሎማሲያዊና ወታደራዊ ትብብሮችን እየመሰረተችና እየጠናከረች መሆኗን ያመላከተው የሆርን ሪቪው ዘገባ፤ “በተለይም ከፓኪስታን ጋር እያደረገችው ያለው አዲስ ሁለንተናዊ ትብበር የአየር ኃይሏን ለማጠናከር ያለመ ነው” ብሏል።

በአውሮፓውያኑ አቆጣጠር ጥር 2025 ሁለቱም ሀገራት ወታደራዊ ትብብራቸውን ለማጠናከር በውጭ ጉዳይ ሚንስትሮቻቸው ደረጃ መስማማታቸውን፣ በመጋቢት 2025 ደግሞ በፓኪስታን የኢትዮጵያ አምባሳደር ጀማል በክር(ዶ/ር) ከፓኪስታን መከላከያ ባለስልጣናት ጋር ትብበሩን ይበልጥ ለማስፋት በቀጥታ መነጋገራቸውን ድረ ገጹ አስነብቧ።

ባለፈው ወር ነሐሴ 2025 ደግሞ የኢትዮጵያው አየር ኃይል አዘዥ ሌፍተነናንት ጀነራል ይልማ መርዳሳ ወደእስላማባድ ተጉዘው ከፓኪስታኑ አቻቸው ማርሻል ዛሂር አህመድ ሲድሁ ጋር መምከራቸውን ያስታወሰው ዘገባው፤ ይህም ኢትዮጵያ ጦሯን ለማዘመን በተለይም የአየር ኃይሏን ለማጠናከር ከፓኪስታን ጋር ትርጉም ያለው ወታደራዊ ትብብር ማድረግ እንደምትፈልግ የሚያመላክት መሆኑን ገልጿል።

ፓኪስታን የአየር ኃይል የደህንነቴ ዋነኛ ምሰሶ ነው ብላ የምታምንና ለኃይሏ ልዩ ትኩረት በመስጠት የምትታወቅ ሀገር ናት። በመሆኑም “ዒላማን የመምታት የላቀ ብቃት፣ ጠላት ጥቃት መፈጸም እንዳያስብ የሚያደርግ አስፈሪ የማጥቃት ብቃት መገንባትና ቴክኖሎጂን አሻሽሎ የመጠቀም ጥበብ” በሚል መርሕ ላይ የተመሰረተ ጠንካራ የአየር ኃይል መገንባት የቻለች ሀገር መሆኗዓ ይነገርላታል።

ኢትዮጵያም ከሀገሪቱ ጋር ያላትን ሁለንተናዊ ግንኙነት ወደላቀ ደረጃ በማሸጋገር ይህንኑ የፓኪስታን አየር ኃይል መርህ በመከተልና ተሞክሮውን ወደራሷ በመውሰድ ብሎም የዕውቀትና የቴክኒክ ድጋፍ እንድታገኝ የሚያስችሉ ትብብሮችን በመፈረም የአየር ኃይሏን አቅም ለማሳደግና በዓለም ላይ ስም ካላቸው አየር ኃይሎች ተርታ የማሰለፍ ፍላጎት ያላት መሆኑን አዲስ ማለዳ ተመልክታለች።

ተጨማሪ ትኩስ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኜት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA

በጉባኤው አፍሪካ እየገጠሟት የሚገኙ አንገብጋቢ ፈተናዎችን በዘላቂነት መሻገር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ምክክር ይደረጋልሰኞ ጳጉሜ 3 ቀን 2017 ዓ.ም ( #አዲስ ማለዳ)ከጳጉሜ 3 እስከ ጳጉሜ ...
08/09/2025

በጉባኤው አፍሪካ እየገጠሟት የሚገኙ አንገብጋቢ ፈተናዎችን በዘላቂነት መሻገር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ምክክር ይደረጋል

ሰኞ ጳጉሜ 3 ቀን 2017 ዓ.ም ( #አዲስ ማለዳ)

ከጳጉሜ 3 እስከ ጳጉሜ 5 ቀን 2017 ዓ.ም ሊካሄድ ቀጠሮ የተያዘለት ሁለተኛው የአፍሪካ የአየር ንብረት ጉባኤ ዛሬ በአዲስ አበባ አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል በይፋ ተከፍቷል።

“ዓለም አቀፍ የአየር ንብረት መፍትሄዎችን ማሳለጥ፣ የአፍሪካን አረንጓዴ ልማት በፋይናንስ መደገፍ” በሚል መሪ ሀሳብ የሚካሄደው ሁለተኛው የአፍሪካ የአየር ንብረት ጉባኤ አፍሪካ እየገጠሟት የሚገኙ አንገብጋቢ ፈተናዎችን በዘላቂነት መሻገር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ምክክር እንደሚደረግበት ተገልጿል።

አፍሪካውያን ዓለም አቀፍ የአየር ንብረት መፍትሄዎችን የሚሞክሩበት የአፍሪካን አረንጓዴ ልማት የሚደገፍበትን አማራጭ የሚያጤኑበት እንደሚሆንም ይጠበቃል።

ጉባኤው በሁለት አጀንዳዎች ላይ መሰረት አድርጎ እንደሚካሄድ የተገለጸ ሲሆን፤ በቅድሚያ የአፍሪካን የአየር ንብረት ለውጥ ጉዳት መሰረት ያደረጉ አህጉራዊ መፍትሄዎች ዕውቅና ይሰጣቸዋል ተብሏል፡፡

ዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ፋይናንስም በጉባኤው ተከታዩ አጀንዳ እንደሚሆን የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር) በሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል፡፡በጉባኤው ኢትዮጵያም የአየር ንብረት ለውጥ ችግርን በጋራ መከላከል የተሻለ ውጤት ለማምጣት ያላትን አቋም እና ያከናወነቻቸውን ተግባራት በጉባኤው ታንፀባርቃለች ተብሎ ይጠበቃል።

የኢትዮጵያ መንግስት እና የአፍሪካ ህብረት በጋራ ባዘጋጁት በዚህ ጉባኤ ከ25 ሺሕ በላይ ተሳታፊዎች ይገኙበታል የተባለ ሲሆን፤ በጉባዔው መክፈቻ ላይም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ፣ የአንጎላው ፕሬዚዳንት እና የወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር ጆኣኦ ሎሬንቾ፣ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ማህሙድ አሊ ዩሱፍ እና ሌሎች የአፍሪካ መሪዎች፣ እንዲሁም ከተለያዩ የዓለም ክፍሎች የመጡ ተሳታፊዎች ተገኝተዋል።

ተጨማሪ ትኩስ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኜት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA

"በአየር ንብረት ለውጥ ወጣቶች የመሪነት ሚና እንዲኖራቸው የሚያግዝ የአዲስ አበባ የአፍሪካ ወጣቶች ዲክላሬሽን ይዘጋጃል"- ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ዓርብ፣ ነሐሴ 30 ቀን ...
05/09/2025

"በአየር ንብረት ለውጥ ወጣቶች የመሪነት ሚና እንዲኖራቸው የሚያግዝ የአዲስ አበባ የአፍሪካ ወጣቶች ዲክላሬሽን ይዘጋጃል"

- ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ

ዓርብ፣ ነሐሴ 30 ቀን 2017 ዓ.ም ( )

በአየር ንብረት ለውጥ ወጣቶች የመሪነት ሚና እንዲኖራቸው የሚያግዝ የአዲስ አበባ የአፍሪካ ወጣቶች ዲክላሬሽን እንደሚዘጋጅ የኢፌዲሪ ምክትል ጠቅላይ ሚንስትር ተመስገን ትሩነህ ገለጹ።

ምክትል ጠቅላይ ሚንስትሩ ይህንን ያሉት በአዲስ አበባ እየተካሄደ በሚገኜው ሁለተኛው የአፍሪካ የወጣቶች የአየር ንብረት ጉባኤ ላይ ነው።

አፍሪካ ወደ ከባቢ አየር የምትለቅቀው በካይ ጋዝ መጠን ከጠቅላላው ከአራት በመቶ ያነሰ መሆኑን የጠቆሙት ምክትል ጠቅላይ ሚንስትሩ፤ ይሁን እንጂ በድርቅ፣ ጎርፍ፣ በምግብ ዋስትና አለመረጋገጥ፣ ዝናብ እጦት የመሳሰሉ ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር የተያያዙ ችግሮች ለአሕጉሪቱ ወጣቶች ስደትና ሌሎችም ችግሮች ተጨማሪ መንስኤዎች እየሆኑ መምጣታቸውን ተናግረዋል።

በመሆኑም አፍሪካውያን ወጣቶች አህጉሪቱ ለአየር ንብረት ለውጥ ችግሮች መፍትሔ ለመስጠትና በዘርፉ ፍትሐዊነትን ለማስፈን በምታደርገው ጥረት ከፊት በመሰለፍ የመሪነቱን ሚና መውሰድ እንደሚገባቸው አሳስበዋል።

ይህንንም እውን ለማድረግ የአዲስ አበባ የአፍሪካ ወጣቶች ዲክላሬሽን እንደሚዘጋጅም ምክትል ጠቅላይ ሚንስትር ተመስገን ጥሩነህ አመላክተዋል።

በጉባኤው እየተሳተፉ ያሉ አፍሪካውያን ወጣቶችም በአየር ንብረት ለውጥ ዙሪያ “ፍትህ እንፈልጋለን” የሚሉ ድምጾችን በተደገጋሚ ሲያስተጋቡ ተደምጠዋል።

ተጨማሪ ትኩስ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኜት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦

YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA

ለመጪዎቹ ዓለም አቀፍ ጉባኤዎች የሆቴሎችና ጤና ተቋማት ብቃት ማረጋገጥ መጀመሩን ባለስልጣኑ አስታወቀዓርብ ነሐሴ 30 ቀን 2017 ( #አዲስ ማለዳ)ለመጪዎቹ ዓለም አቀፍ ጉባኤዎች የሆቴሎችና ...
05/09/2025

ለመጪዎቹ ዓለም አቀፍ ጉባኤዎች የሆቴሎችና ጤና ተቋማት ብቃት ማረጋገጥ መጀመሩን ባለስልጣኑ አስታወቀ

ዓርብ ነሐሴ 30 ቀን 2017 ( #አዲስ ማለዳ)

ለመጪዎቹ ዓለም አቀፍ ጉባኤዎች የሆቴሎችና ጤና ተቋማት ብቃት ማረጋገጥ መጀመሩን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን አስታወቀ።

አህጉራዊና ሀገራዊ የሆኑ ልዩ ልዩ ሁነቶች ማለትም አህጉር አቀፍ የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ፣ የአፍሪካና የካረቢያን ሀገሮች ጉባኤ እንዲሁም የታላቁ ህዳሴ ግድብ ምርቃት ላይ የሚሳተፉ ዓለም አቀፍና ሀገር አቀፍ ተሳታፊዎች የሚያርፉበትም ሆነ አገልግሎት የሚያገኙበት ሆቴሎች፣ ትልልቅ ባርና ሬስቶራንቶች፣ መዝናኛ ቦታዎች፣ የእንግዳ ማረፊያ ፔንሲዮኖች እንዲሁም ሆስፒታሎች ስታንዳርዳቸውንና ደረጃቸውን የጠበቁ ስለመሆናቸውና አገልግሎት አሰጣጣቸው ኢትዮጵያዊ ጨዋነት የተላበሰ ስለመሆኑ ቁጥጥር እያደረገ መሆኑንም ገልጿል፡፡

በዚህም እስካሁን ባለው የክትትል ሂደት የስምንት ሆስፒታሎችና አምስት የሕክምና ማዕከሎች ብቃት ተረጋግጦ ዝግጅት መደረጉ የተገለጸ ሲሆን በተጨማሪም፣ 160 ሆቴሎች እና 308 የምግብና መጠጥ አቅራቢ ተቋማት ብቃታቸው ተረጋግጦ ለአገልግሎት ዝግጁ መሆናቸው ታውቋል።

ባለስልጣን መሽሪያ ቤቱ በሆቴል ዘርፉ በተደረጉ የቁጥጥር ሥራዎች ጉድለት የታየባቸው 2 ሆቴሎች ላይ እርምጃ መወሰዱን እና እንግዶች የሚያርፉባቸው ሆቴሎች፣ ሬስቶራንቶች እና የመዝናኛ ስፍራዎች የንጽህና እና የደህንነት ደረጃዎችን ለማረጋገጥ ሥራው መቀጠሉንም አመላክቷል።

ከተለመደው ሥራው በተጨማሪ፣ ወቅታዊ ክስተቶች ሲኖሩ ልዩ የክትትል ሥራዎችን የማከናወን ኃላፊነቱን የሚቀጥል መሆኑንም ባለስልጣኑ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።

ተጨማሪ ትኩስ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኜት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA

Address

Tsehay Messay Bldg, 4th Floor Near Bambis Supermarket
Addis Ababa
63000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Addis Maleda - አዲስ ማለዳ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Addis Maleda - አዲስ ማለዳ:

Share