
25/02/2025
ብሔራዊ ባንክ በውጭ ምንዛሪ ጨረታ አንድ የአሜሪካ ዶላር በአማካይ 135 ብር ዋጋ መሸጡ ተገለጸ
ማክሰኞ የካቲት 18 ቀን 2017 ( )
የኢትዮጵያ የብሔራዊ ባንክ በልዩ የውጭ ምንዛሪ ሽያጭ ጨረታ አንድ የአሜሪካ ዶላር በአማካይ 135 ብር ዋጋ መሸጡ ተገልጿል፡፡
ብሔራዊ ባንክ በዛሬው ዕለት ያካሄደው የ60 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ልዩ የውጭ ምንዛሪ ሽያጭ ጨረታ መጠናቀቁን አስታውቋል፡፡
በዚህ ልዩ ጨረታ ውጤት መሰረትም የአንድ የአሜሪካ ዶላር አማካይ የምንዛሪ ዋጋ 135 ነጥብ 6185 ብር መሆኑን ይፋ አደርጓል።
ጨረታው ላይ 27 ባንኮች መሳተፋቸውን የገለጸው ብሄራዊ ባንኩ፤ የውጭ ምንዛሪ ጨረታው ከፍተኛ ቁጥር ያለው ተሳትፎ የታየበት ነበር ብሏል።
በቀጣይ አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝና ከዋጋና ከውጭ ምንዛሪ መረጋጋት ጋር በሚስማማ መልኩ ተጨማሪ ጨረታዎችን እንደሚያካሂድ ባንኩ አስታውቋል።