Addis Maleda - አዲስ ማለዳ

Addis Maleda - አዲስ ማለዳ አዲስ ማለዳ በቻምፒየን ኮምንኬሽንስ ተዘጋጅታ በሃገራችን ማኅበራዊ ለውጥ ለማምጣት ከሚዲያ የሚጠበቀውን ሚዛን የጠበቀ እና የተረጋገጠ መረጃ ለዜጎች የማድረስ ሚና ለመወጣት የምትሰራ ሚዲያ ነች።

ብሔራዊ ባንክ በውጭ ምንዛሪ ጨረታ አንድ የአሜሪካ ዶላር በአማካይ 135 ብር ዋጋ መሸጡ ተገለጸማክሰኞ የካቲት 18 ቀን 2017 ( )የኢትዮጵያ የብሔራዊ ባንክ በልዩ የውጭ ምንዛሪ ሽያጭ ጨረ...
25/02/2025

ብሔራዊ ባንክ በውጭ ምንዛሪ ጨረታ አንድ የአሜሪካ ዶላር በአማካይ 135 ብር ዋጋ መሸጡ ተገለጸ

ማክሰኞ የካቲት 18 ቀን 2017 ( )

የኢትዮጵያ የብሔራዊ ባንክ በልዩ የውጭ ምንዛሪ ሽያጭ ጨረታ አንድ የአሜሪካ ዶላር በአማካይ 135 ብር ዋጋ መሸጡ ተገልጿል፡፡

ብሔራዊ ባንክ በዛሬው ዕለት ያካሄደው የ60 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ልዩ የውጭ ምንዛሪ ሽያጭ ጨረታ መጠናቀቁን አስታውቋል፡፡

በዚህ ልዩ ጨረታ ውጤት መሰረትም የአንድ የአሜሪካ ዶላር አማካይ የምንዛሪ ዋጋ 135 ነጥብ 6185 ብር መሆኑን ይፋ አደርጓል።

ጨረታው ላይ 27 ባንኮች መሳተፋቸውን የገለጸው ብሄራዊ ባንኩ፤ የውጭ ምንዛሪ ጨረታው ከፍተኛ ቁጥር ያለው ተሳትፎ የታየበት ነበር ብሏል።

በቀጣይ አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝና ከዋጋና ከውጭ ምንዛሪ መረጋጋት ጋር በሚስማማ መልኩ ተጨማሪ ጨረታዎችን እንደሚያካሂድ ባንኩ አስታውቋል።

በኦሮሚያ ክልል ያለውን የፖለቲካ፣ የጸጥታ ችግሮችን እና ሰብዓዊ ቀውሶችን  ለመፍታት በሚል የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ኦነግ ፣የኦረሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ኦፌኮ እና በኦሮሚያ ክልል ከ16 በላይ...
25/02/2025

በኦሮሚያ ክልል ያለውን የፖለቲካ፣ የጸጥታ ችግሮችን እና ሰብዓዊ ቀውሶችን ለመፍታት በሚል የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ኦነግ ፣የኦረሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ኦፌኮ እና በኦሮሚያ ክልል ከ16 በላይ የማህበረሰብ ተወካዮች፣ የሃይማኖት አባቶች አባገዳዎች የአራት ቀናት ምክክር አድርገዋል፡፡

ይህንን ጉዳይ በሚመለከት በዚህ ምክክር ላይ የተሳተፉትን የኦፌኮ ሊቀመንበርና አንጋፋ ፖለቲከኛ ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና ጋር አዲስ ማለዳ ቆይታ አድርጋለች፡፡ ሙሉ ቃለመጠይቁን ከስር ባለው ማስፈንጠሪያ በመጫን ይከታተሉ

#ዜና #ኢትዮጵያ አዲስ ማለዳ ወቅታዊ የኢትዮጵያን ጉዳዮች በስፋትና በጥልቀት የምትተነትን፣ እንዲሁም የተረጋገጡና የትም ያልተሰሙ ዜናዎች የሚቀርቡባት የ....

በኢትዮጵያ እና ኬንያ ድንበር አካባቢ በተፈጸመ ጥቃት 13 ኢትዮጵያውያን ተገደሉሰኞ የካቲት 17 ቀን 2017 ( )በኢትዮጵያ እና በኬንያ አሳ አጥማጆች መካከል በተፈጠረ የድንበር ግጭት 13 ...
24/02/2025

በኢትዮጵያ እና ኬንያ ድንበር አካባቢ በተፈጸመ ጥቃት 13 ኢትዮጵያውያን ተገደሉ

ሰኞ የካቲት 17 ቀን 2017 ( )

በኢትዮጵያ እና በኬንያ አሳ አጥማጆች መካከል በተፈጠረ የድንበር ግጭት 13 ኢትዮጵውያን ሲገደሉ፣ ሶስቱ ቆሥለዋል፤ በተጨማሪም ሁለት ዜጎች የገቡበት አልታወቀም፣ በአንፃሩ 22 ኬንያውያን የገቡበት መጥፋቱን ሬውተርስ ዘግቧል፡፡ ዓለም አቀፍ የመገናኛ አውታሩ መረጃውን የሁለቱም ሀገራት ባለስልጣናት አረጋግጠውልኛል ብሏል።

ግጭቱ ቅዳሜ አመሻሽ ላይ በኦሞ ወንዝ አካባቢ በሁለቱ ሀገሮች ድንበር ላይ መከሰቱን የኬንያ ቱርካና ካውንቲ አስተዳዳሪ ኤርሚያስ ሎሞሩካይ በሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል።

በሌላ በኩል ስማቸውን እንዳንጠቅስ የጠየቁ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን ዳሰነች ወረዳ ስየስ ቀበሌ ነዋሪዎች ነገሩኝ ብሎ አዲስ ስታንዳርድ እንደዘገበው፣ የኬንያ ታጣቂዎች “ስድስት ጀልባዎችን ጨምሮ 130 የሚደረሱ የአሣ ማጥመጃ መረቦች፣ እስከ 500 ሺህ የሚደርሱ ደረቅ አሣዎች እና በርካታ ንብረቶችን” መወሰዳቸውን ጽፏል።

በደቡብ ኦሞ ዞን የዳሰነች ወረዳ ዋና የመንግሥት ተጠሪ የሆኑት መሳይ ሊበን፤ “የኬንያ መንግሥት የኢትዮጵያን ድንበር አልፈው ለሚመጡ ታጣቂዎቹ ከተሽከርካሪ አንስቶ እስከ ተተኳሽ የጦር መሣሪያዎች ድጋፍ ማድረጉን” ለአዲስ ስታንዳርድ ተናግረዋል።

የኬንያ የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትር ኪፕቹምባ ሙርኮመን እሁድ ዕለት በኤክስ ገፃቸው ላይ እንደፃፉት፣ መንግሥት በድንበሩ ላይ ተጨማሪ ጥበቃ ማሰማራቱን እና "በሁለቱ ማኅበረሰቦች መካከል ሰላም ለመፍጠር" ከአዲስ አበባ ጋር እየተገናኘ ነው ብለዋል። ይሁን እንጂ በጉዳዩ ላይ የኢትዮጵያ መንግሥት እስካሁን ያለው ነገር የለም፡፡

ኢትዮጵያ አንፃራዊ ሰላም ያለው የድንበር ግንኙነት ከኬንያ ጋር ያላት ቢሆንም፣ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በኬንያ በኩል የእርሻ እና ግጦሽ መሬትን በሃይል ለመንጠቅ እንደዚሁም ውሃ ፍለጋ የሚደረጉ መተናኮሶች በተደጋጋሚ እየተከሰቱ እንደሆነ ዘገባዎች ያመለክታሉ፡፡ እነዚህ ግጭቶቹ በአካባው ሽማግሌዎች፣ አለፍ ሲልም የአካባቢ የመንግሥት አስተዳደሮች እልባት ሲሰጡት መቆየቱ ይታወቃል፡፡

በተመሳሳይ በቅርቡ ከጅቡቲ የተነሳ ድሮን በኢትዮጵያ አፋር ክልል ጥቃት ማድረሱ በሃገር ውስጥ የተለያዩ አካላት ዘንድ ቁጣ የቀሰሰ ክስተት እንደነበር ይታወሳል፡፡ በደቡብ ሱዳን የሙርሌ ብሄር ጥቃት እና ተደጋጋሚ ትንኮሳም የቅርብ ጊዜ ትውስታ ሲሆን፣ አልፋሽጋን እንደምክንያት በመጥቀስ የሱዳን ታጣቂዎች በተደጋጋሚ ወደኢትዮጵያ ድንበር ዘልቀው እንደሚገቡ እና የፀጥታ ሥጋት እንደሚፈጥሩም ይታወቃል፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በነገው ዕለት 60 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ለጨረታ ሊያቀርብ መሆኑን አስታወቀሰኞ የካቲት 17 ቀን 2017 ( )የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ልዩ የውጭ ምንዛሪ ጨረታ ነ...
24/02/2025

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በነገው ዕለት 60 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ለጨረታ ሊያቀርብ መሆኑን አስታወቀ

ሰኞ የካቲት 17 ቀን 2017 ( )

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ልዩ የውጭ ምንዛሪ ጨረታ ነገ የካቲት 18 ቀን 2017 ዓ.ም እንደሚያካሂድ አስታውቋል፡፡

በዚህም ጨረታ የሚቀርበው የውጭ ምንዛሪ መጠን 60 ሚሊየን የአሜሪካን ዶላር ሲሆን ጨረታው ለሁሉም ባንኮች ክፍት እንደሚሆን ተገልጿል።

እንዲሁም ከቅርብ ወራት ወዲህ ወርቅን ወደ ውጭ የመላክ ብቸኛ ሥልጣን ላለው ብሔራዊ ባንክ የሚቀርበው የወርቅ መጠን በመጨመሩ ምክንያት የባንኩ ዓለም አቀፍ የውጭ ምንዛሪ መጠባበቂያ ክምችት እጅግ አበረታች መሆኑም ተመላክቷል፡፡

ይሁን እንጂ የብሔራዊ ባንኩ የውጭ ምንዛሪ ፍሰት መጨመር የሪፎርሙ ጥሩና አዎንታዊ ውጤት ቢሆንም የማዕከላዊ ባንኩን ጥብቅ የገንዘብ ዕድገት ፖሊሲና የዋጋ ንረት ግብ ስኬት በማያደናቅፍ መልኩ ሊተገበር እንደሚገ አሳስቧል፡፡

በመሆኑም ከባንኩ የወርቅ ግዥ ጋር በተያያዘ የሚከሰተውን የገንዘብ አቅርቦት ዕድገት ለማገናዘብና በማዕከላዊ ባንኩ እጅ ካለው ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ክምችት ከፊሉን ለግሉ ዘርፍ በመስጠት በገበያው ላይ የውጭ ምንዛሪ አቅርቦትን ለማሻሻል ባንኩ የተወሰነ የውጭ ምንዛሪ ለባንኮች በጨረታ ለመሸጥ መወሰኑን አስታውቋል፡፡

ባንኩ በቀጣይ ጊዜ የውጭ ምንዛሪ ገበያ ሁኔታን በቅርበት በመከታተል እንደ አስፈላጊነቱ ተጨማሪ የውጭ ምንዛሪ ሽያጮችን እንደሚያካሂድ ተጠቅሷል፡፡

በተጨማሪም የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም ፕሮግራምን ተከትሎ የኢትዮጵያ የውጭ ክፍያ ሚዛን በተለይም የወጪ ንግድ፣ ሐዋላና የካፒታል ፍሰት በከፍተኛ ደረጃ መሻሻል ማሳየቱን ባወጣው መግለጫ አመላክቷል፡፡

የእንቁላል ዋጋ ጭማሪ እጅግ እያሻቀበ በመሆኑ መንግስት ሊቆጣጠረው ይገባል - ነዋሪዎች ሰኞ የካቲት 17 ቀን 2017 ( ) በአዲስ አበባ በተለያዩ አካባቢዎች ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እየተስተዋለ ...
24/02/2025

የእንቁላል ዋጋ ጭማሪ እጅግ እያሻቀበ በመሆኑ መንግስት ሊቆጣጠረው ይገባል - ነዋሪዎች

ሰኞ የካቲት 17 ቀን 2017 ( )

በአዲስ አበባ በተለያዩ አካባቢዎች ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እየተስተዋለ የሚገኘው የእንቁላል ዋጋ ጭማሬ የተጋነነ መሆኑን ነዋሪዎች ገልጸዋል፡፡

ከወራት በፊት አስር ብር እና ከዛ በታች ስንገዛ የቆየነው እንቁላል አሁን አንድ እንቁላል ሀያ ብር እና ከዛ በላይ እየተሸጠ ነው፤ ይህን ያህል የዋጋ ልዩነት በወራት ውስጥ መምጣቱ ከባድ እና ከማህበረሰቡ የመግዛት አቅም በላይ ነው ሲሉ የከተማዋ ነዋሪዎች ገልጸዋል፡፡

አዲስ ማለዳ ባደረገችው ማጣራት የእንቁላል ዋጋ እንደየ አካባቢው እና ቦታ የሚለያይ ሲሆን በአጠቃላይ በአማካይ ዋጋ ከ16 ብር እስከ 20 ብር ድረስ እየተሸጠ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡

የዋጋው መወደድ እጅግ አሳሳቢ ነው ያሉት ነዋሪዎች፤ እንኳን የየእለት ምግባችን ላይ ልናካትተው በዓላትን ጠብቆ ለመግዛትም አስቸጋሪ እንደሆነ እና ነዋሪው ከሚያገኘው ገቢ ጋር ተመጣጣኝ ያልሆነ በመሆኑ የሚመለከተው አካል አስፈላጊውን ቁጥጥር እንዲያደርግበት አሳስበዋል፡፡

ይህን ተከትሎ የዋጋው መናር መንስኤ ምንድነው ስትል አዲስ ማለዳ ዶሮ እና የዶሮ ተዋጽኦ አቅራቢዎችን አነጋግራለች፡፡

በመሆኑም ከአቅራቢው እስከ ተጠቃሚው እጅ እስኪደርስ ብዙ ውጣውረዶች መኖራቸውን ገልጸው ነገር ግን የዶሮ መኖ የዋጋ ጭማሬ እንደ አንድ ምክንያት ሊታይ እንደሚችል ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ የእንስሳት እርባታ እና የዶሮ ተዋጽኦ አቅራቢ ገልጸዋል፡፡

አክለውም ከአቅራቢው ወይም ከዶሮ አርቢው ተረክቦ እስከሚያከፋፍሉት ከዛም ለተጠቃሚው እስከሚያደርሱት ድረስ የሚታይ የዋጋ ለውጥ መኖሩን፤ እንዲሁም የትራንስፖርት እና የነዳጅ ዋጋ ጭማሬ አንዱ በሌላው ላይ ጫና እያሳደረ መሆኑን አመላክተዋል፡፡

በተጨማሪም ነጋዴው ከአላስፈላጊ ትርፍ መሰብሰብ ቢቆጠብ እና ምርቶቹን በተገቢው ዋጋ ቢያቀርብ የራሱ የሆነ ለውጥ እንደሚኖረውም ጠቁመዋል፡፡

አዲስ ማለዳ በዚህ ጉዳይ ላይ የሚመለከተውን የመንግስት አካል ለማናገር ያደረገችው ተደጋጋሚ ሙከራ አልተሳካም፡፡

ለቀድሞ የኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት አመራሮች ሹመት ተሰጠ።ዓርብ የካቲት 14 ቀን 2017( ) የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የሰላም ጥሪ ለተቀበሉ የቀድሞ የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት አመራሮች ሹ...
21/02/2025

ለቀድሞ የኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት አመራሮች ሹመት ተሰጠ።

ዓርብ የካቲት 14 ቀን 2017( )

የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የሰላም ጥሪ ለተቀበሉ የቀድሞ የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት አመራሮች ሹመት ሰጥቷል፡፡

በዚህ መሰረት፡-

1. አቶ ያደሳ ነጋሳ
በቢሮ ኃላፊ ማዕረግ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር የሰላምና ደህንነት ጉዳዮች አማካሪ

2. አቶ ኦሮሚያ ረቡማ
የኦሮሚያ ክልል ዓቃቤ ሕግ ምክትል ኃላፊ፣

3. አቶ ቶሌራ ረጋሳ
የኦሮሚያ ክልል ጸጥታና አሥተዳደር ቢሮ ምክትል ኃላፊ ሆነው መሾማቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጽ/ቤት መረጃ ያመላክታል፡፡

በአዳማ ከተማ ቀደምት ቤቶች ሊፈርሱ ነው መባሉ ከእውነት የራቀ ነው ተባለ:: ዕረቡ የካቲት 12 ቀን 2017 ( )የአዳማ  ከተማ ስትቆረቆር ጀምሮ የነበሩ በርካታ የግል እና የቀበሌ ቤቶች ሊ...
19/02/2025

በአዳማ ከተማ ቀደምት ቤቶች ሊፈርሱ ነው መባሉ ከእውነት የራቀ ነው ተባለ::

ዕረቡ የካቲት 12 ቀን 2017 ( )የአዳማ ከተማ ስትቆረቆር ጀምሮ የነበሩ በርካታ የግል እና የቀበሌ ቤቶች ሊፈርሱ ነው በሚል እየተሰራጨ ያለው መረጃ ሀሰት መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ አስታውቋል፡፡

የአዳማ ከተማ የነበሩ ቀበሌ በ05 ፣06 ፣07 ፣15 ፣18 ፣19 ቀበሌ የሚገኙ ከ3 ሺህ በላይ የግልና የቀበሌ ቤቶች ሊፈርሱ እንደሆነ እና ነዋሪዎቹ በሶስት ቀን ውስጥ እንዲወጡ ታዘዋል በሚል የተለያዩ መረጃዎች በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ሲዟዟር ተስተውሏል፡፡

ይህ መረጃ ምን ያህል እውነት ነው ስትል አዲስ ማለዳ ያነጋገረቻቸው የአዳማ ከተማ አስተዳደር ኮሚኒኬሽን ሀላፊ አሚና አኩሼ ከቤት ፈረሳ ጋር ተያይዞ ሲናፈስ የቆየውና አሁንም እየተናፈሰ ያለው የሀሰት መረጃ እንደሆነ እና የየትኛውም ቀበሌ ነዋሪ እንዲነሱ እንዳልተጠየቁ አስታውቀዋል፡፡

በ3 ቀን ውስጥ እንዲለቁ ተነግሯቸዋል የተባሉት ከ3 ሺህ በላይ አባወራዎች "የስድስት ወር የቤት ኪራይ ይሰጣችኋል፤ለወደፊቱ ደግሞ ቤት ይሰራላችኋል" ከመባል ውጪ የሚያርፉበት ቅያሪ ቤት ወይም ቦታ እንኳ አልተሰጣቸውም ተብሎ ነበር፡፡

ሀላፊዋ ይህን አስተያየት አስተባብለው ለኮሊደር ልማትም ሆነ ለመንገድ ስፋት ግንባታ እንዲነሱ እንዳልተጠየቀ እና ነገር ግን የከተማ አስተዳደሩ ዘመናዊ የጋራ መኖሪያ ቤቶችን እየገነባ እንደሆነ እና ለነዋሪውም እንደሚያስረክብ ገልጸዋል፡፡

ይልቁንም የጋራ መኖሪያ ቤቶች ግንባታ ሲጠናቀቅ እንደሚረከቡ ለነዋሪዎቹ እንደተነገራቸው እስከዛም ግን ማንም አባወራ የሚኖርበትን ቤት እንዲለቅ እንዳልተነገረው ጠቁመዋል፡፡

የኮሚዩኒኬሽን ሃላፊዋ መረጃው ሃሰት ነው ቢሉም መኖሪያቸውን እንዲለቁ የተነገራቸው ነዋሪዎች አብዛኛዎቹ አቅመ ደካሞችና ሰርተው መብላት እንኳ የማይችሉ መሆናቸውን እና "በኑሮ ውድነትና በቀን አንዴ መብላት ከብዶን ሳለ ፣ምንም ሳንዘጋጅ በሦስት ቀን ውስጥ እንዴት ቤት ልቀቁ እንባላለን" የሚሉ የአካባቢው የነዋሪዎች ቅሬታ እንደሆነ ነው እየተነገረ ያለው፡፡

ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ አለመግባባታቸውን ለመፍታት የመጀመሪያ ዙር ውይይት ማድረጋቸው ተገለጸዕረቡ የካቲት 12 ቀን 2017 ( ) የኢትዮጵያ እና የሶማሊያ ከፍተኛ ዲፕሎማቶች በትናንትናው እለት...
19/02/2025

ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ አለመግባባታቸውን ለመፍታት የመጀመሪያ ዙር ውይይት ማድረጋቸው ተገለጸ

ዕረቡ የካቲት 12 ቀን 2017 ( ) የኢትዮጵያ እና የሶማሊያ ከፍተኛ ዲፕሎማቶች በትናንትናው እለት የመጀመሪያ ዙር ድርድር በቱርክ ማድረጋቸውን የቱርክ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡

የቱርክ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እንዳስታወቀው በኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጤሞቴዎስ እና በሶማሊያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አሊ መሀመድ ኦማር የተመራ ልዑካን ቡድን በቱርክ መዲና አንካራ የመጀመሪያ ዙር የቴክኒክ ድርድር ማካሄዱ ተገልጿል።

ሁለቱ ሀገራት በኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ዙሪያ በቱርኩ ፕሬዝዳንት ሬሲፕ ታይፕ ኤርዶዋን አሸማጋይነት በተፈራረሙት የአንካራው ሥምምነት መሰረት ነው፤ የመጀመሪያውን ዙር የቴክኒካል ውይይት ያደረጉት።

ሀገራቱን ወደ ስምምነት ለማምጣት ጥረት በማድረግ ላይ የምትገኘው ቱርክ በውጭ ጉዳይ ሚኒስትር መሥሪያ ቤቷ በኩል ባወጣችው መግለጫ፤ የቴክኒክ ድርድሩ የአንካራውን ስምምነት የተከተለ መሆኑን ገልጻለች።

ልዑካኑ የአገራቱ መሪዎች በአንካራ ስምምነት ላይ ያስቀመጡትን ራዕይ ወደ ተግባር ለመቀየር እንዲሁም ለጋራ የዘላቂ ልማት ተጠቃሚነት መሠረት ለመጣል ተጨባጭ ሥራ መጀመራቸውን አስታውቋል።

ስምምነቱን ለማስፈጸምም ከመጋቢት ወር 2017 በፊት የቴክኒክ ኮሚቴ ተቋቁሞ የማመቻቸት ሥራ ይሰራል ተብሎ የነበረ ሲሆን፤ በ4 ወራት ውስጥ ደግሞ ሂደቱ ተጠናቆ ስምምነት እንደሚፈረም ተጠቁሟል፡፡

የሰማዕታት ቀን በዛሬው እለት በደማቅ ስነስርዓት ታስቧል:: ዕረቡ የካቲት 12 ቀን 2017 ( ) በዛሬው እለት የሰማዕታት ቀን ስድስት ኪሎ በሚገኘው መታሰቢያ ሀውልት ተከብሯል፡፡የዛሬ 88 ...
19/02/2025

የሰማዕታት ቀን በዛሬው እለት በደማቅ ስነስርዓት ታስቧል::

ዕረቡ የካቲት 12 ቀን 2017 ( ) በዛሬው እለት የሰማዕታት ቀን ስድስት ኪሎ በሚገኘው መታሰቢያ ሀውልት ተከብሯል፡፡

የዛሬ 88 አመት ፋሽስት ኢጣሊያ ኢትዮጵያን በወረረበት ወቅት አብርሃ ደቦጭና ሞገስ አስገዶም በጦር አዛዡ ሩዶልፍ ግራዚያኒ ላይ ቦንብ ወርውረው ጉዳት ማድረሳቸውን ተከትሎ የጣሊያን ጦር የካቲት 12 ቀን 1929 ዓ.ም 30 ሺህ የአዲስ አበባ ነዋሪዎችን በግፍ መጨፍጨፉን ታሪክ ይነግረናል፡፡

በዚህ ቀን ወጣቶች፣ የጦር መኮንኖች፣ ካህናትና ሌሎችም ካሉበት እየተለቀሙ በግፍ ተጨፍጭፈዋል፡፡

በዚህም በዓሉ በየአመቱ የካቲት 12 የሚታሰብ ሲሆን በዛሬው እለትም በተለያዩ ስነስርአቶች በመከበር ላይ ያገኛል።

ምክር ቤቱ የሀገራዊ የምክክር ኮሚሽንን የስራ ዘመን ለአንድ ዓመት አራዘመ::ማክሰኞ የካቲት 11 ቀን 2017( )የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባደረገው አስቸኳይ ስብሰባ፤ የኢትዮጵያ ሀገራ...
18/02/2025

ምክር ቤቱ የሀገራዊ የምክክር ኮሚሽንን የስራ ዘመን ለአንድ ዓመት አራዘመ::

ማክሰኞ የካቲት 11 ቀን 2017( )

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባደረገው አስቸኳይ ስብሰባ፤ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽንን የስራ ዘመን ለአንድ አመት አራዝሟል።

የኮሚሽኑን የስራ ዘመን ለማራዘም የቀረበው የውሳኔ ሀሳብ፤ በሶስት የፓርላማ አባላት ተቃውሞ በአብላጫ ጽምጽ ጸድቋል።

መሰረታዊ በሆኑ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ለተፈጠሩ ልዩነቶች “ወሳኝ ምክንያቶችን የመለየት” እና ውይይቶች የሚካሄዱባቸውን ርዕሰ ጉዳዮች በመለየት “ምክክር እንዲደረግባቸው የማመቻቸት” ዓላማ ይዞ የተቋቋመው ኮሚሽኑ፤ በአዋጅ የተቀመጠለት የስራ ዘመን ሶስት ዓመት እንደነበር ይታወቃል።

ፓርላማው ኮሚሽኑ ለተጨማሪ አንድ ዓመት በስራ ላይ እንዲቆይ ውሳኔ ከማሳለፉ አስቀድሞ፤ የተቋሙን የሶስት ዓመታት የስራ አፈጻጸም ሪፖርት አዳምጧል።

ሪፖርቱን ለፓርላማ አባላት በንባብ ያቀረቡት የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርአያ፤ ኮሚሽኑ በዚህ ጊዜ ውስጥ የምክክር፣ የአጀንዳ መለየት እና ለሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የሚሳተፉ ተወካዮችን የማስመረጥ ስራዎችን በ10 ክልሎች እና በሁለት ከተማ አስተዳደሮች ማጠናቀቁን አስታውቀዋል።

አባላቱ ኮሚሽኑ በተሰጠው ተጨማሪ የስራ ዘመን ተጠባቂ ቀሪ ስራዎችን እንዲያጠናቅቅ ጠይቀዋል።

ብሔራዊ ባንክ የዋጋ ግሽበት ቀንሷል ቢልም ተቃራኒ ሪፖርት መውጣቱ ተገለጸማክሰኞ የካቲት 11 ቀን 2017 ( ) የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ የሀገሪቱ የዋጋ ግሽበት በከፍተኛ ደረጃ መቀነሱን ባወ...
18/02/2025

ብሔራዊ ባንክ የዋጋ ግሽበት ቀንሷል ቢልም ተቃራኒ ሪፖርት መውጣቱ ተገለጸ

ማክሰኞ የካቲት 11 ቀን 2017 ( )

የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ የሀገሪቱ የዋጋ ግሽበት በከፍተኛ ደረጃ መቀነሱን ባወጣው የእስታትስቲክስ ሪፖርት ማስታወቁ ይታወሳል፡፡

ይህም በባለፈው አመት ጥር ወር ከነበረበት 29.4 በመቶ ወደ 15.5 በመቶ ዝቅ ያለ ሲሆን ይህም 13.9 በመቶ ማሽቆልቆሉን የሚያመለክት መሆኑን ገልጾ ነበር፡፡

እንዲሁም የምግብ ግሽበት በ16.6 በመቶ እና በምግብ ነክ ያልሆኑ የዋጋ ግሽበት በ10.2 በመቶ ቅናሽ አሳይቷል ተብሏል።

ይሁን እንጂ ትሬዲን ኢኮኖሚክስ ተደረገ ባለው ጥናት ከብሄራዊ ባንክ ሪፖርት ጋር ተቃራኒ የሆነ ቁጥር መመዝገቡን ገልጿል።

በመሆኑም የኢትዮጵያ አመታዊ የዋጋ ግሽፈት 17 በመቶ እንደሆነ ያስታወቀ ሲሆን የብሄራዊ ባንክ ካወጣው ቁጥር ጭማሪ የሚያሳይ ነው፡፡

ሁለቱም ሪፖርቶች የቁጥር ልዩነት ቢኖራቸውም የዋጋ ግሽበት እንደ አጠቃላይ ከነበረበት መቀነሱን አመላክተዋል፡፡

ምክር ቤቱ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽንን  የስራ አፈፃፀምን እያዳመጠ መሆኑ ተገለጸ፡፡ ማክሰኞ የካቲት 11 ቀን 2017 (አዲስ ማለዳ) የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ4ኛ ዓመት የሥራ ...
18/02/2025

ምክር ቤቱ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽንን የስራ አፈፃፀምን እያዳመጠ መሆኑ ተገለጸ፡፡

ማክሰኞ የካቲት 11 ቀን 2017 (አዲስ ማለዳ) የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን ባካሄደው 1ኛ አስቸኳይ ጉባዔ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የሦስት ዓመት የስራ አፈፃፀምን አያዳመጠ ይገኛል።

የምክር ቤቱ አፈ-ጉባኤ አቶ ታገሰ ጫፎ የሀገራዊ የምክክክር ኮሚሽኑ ባለፉት ሶስት አመታት ያከናወናቸው ተግባራት እንደሚቀርቡ እና ቀጣይ አቅጣጫ እንደሚቀመጥ አስረድተዋል።

ሪፖርቱ በኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርአያ (ፕ/ር) እየቀረበ የሚገኝ ሲሆን ምክር ቤቱ በቀረበው ሪፖርት ላይ በስፋት ተወያይቶ ቀጣይ አቅጣጫ ያስቀምጣል ተብሎ ይጠበቃል።

ምክር ቤቱ የሀገራዊ የምክክር ኮሚሽኑን “የስራ ዘመን ያራዝማል” ተብሎ ይጠበቃል፡፡

በታህሳስ 2014 ዓ.ም የጸደቀው የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ማቋቋሚያ አዋጅ፤ የኮሚሽኑ የስራ ዘመን ሶስት ዓመት እንደሆነ ይደነግጋል።

የኮሚሽኑ የስራ ዘመን የሚቆጠረው፤ በአዋጁ መሰረት የሚመረጡ ኮሚሽነሮች በፓርላማ ከተሾሙበት ጊዜ ጀምሮ እንደሆነ በድንጋጌው ላይ ሰፍሯል።

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ በዕጩነት የቀረቡ 11 ኮሚሽነሮችን ሹመት ያጸደቀው የካቲት 14 ቀን 2014 ዓ.ም. ነበር።

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Addis Maleda - አዲስ ማለዳ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Addis Maleda - አዲስ ማለዳ:

Share