Addis Maleda - አዲስ ማለዳ

Addis Maleda - አዲስ ማለዳ አዲስ ማለዳ በቻምፒየን ኮምንኬሽንስ ተዘጋጅታ በሃገራችን ማኅበራዊ ለውጥ ለማምጣት ከሚዲያ የሚጠበቀውን ሚዛን የጠበቀ እና የተረጋገጠ መረጃ ለዜጎች የማድረስ ሚና ለመወጣት የምትሰራ ሚዲያ ነች።

የህዳር 5 ቀን 2018 ዓ.ም፤ ዕለታዊ ዜና
14/11/2025

የህዳር 5 ቀን 2018 ዓ.ም፤ ዕለታዊ ዜና

#ዜና #ኢትዮጵያ አዲስ ማለዳ ወቅታዊ የኢትዮጵያን ጉዳዮች በስፋትና በጥልቀት የምትተነትን፣ እንዲሁም የተረጋገጡና የትም ያልተሰሙ ዜናዎች የሚቀርቡባት የ....

አሜሪካ ከልክ ያለፈ ውፍረትን ጨምሮ ከማይተላለፉ በሽታዎች ጋር ተያያዥነት ያላቸው ሌሎች የጤና ችግሮች ያሉባቸውን ሰዎች ቪዛ ልትከለክል እንደምትችል ተገለጸ  ዓርብ፣ ሕዳር 5 ቀን 2018 ዓ...
14/11/2025

አሜሪካ ከልክ ያለፈ ውፍረትን ጨምሮ ከማይተላለፉ በሽታዎች ጋር ተያያዥነት ያላቸው ሌሎች የጤና ችግሮች ያሉባቸውን ሰዎች ቪዛ ልትከለክል እንደምትችል ተገለጸ

ዓርብ፣ ሕዳር 5 ቀን 2018 ዓ.ም ( )

አሜሪካ ከልክ ያለፈ ውፍረትን ጨምሮ ከማይተላለፉ በሽታዎች ጋር ተያያዥነት ያላቸው ሌሎች የጤና ችግሮች ያሉባቸውን ሰዎች ቪዛ ልትከለክል እንደምትችል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ማርኮ ሩቢዮ መናገራቸው ተሰምቷል።

የትራምፕ አስተዳደር የአሜሪካ የቪዛ ኦፊሰሮች ከልክ ያለፈ ውፍረትን ጨምሮ ከማይተላለፉ በሽታዎች ጋር ተያያዥነት ያላቸው እንደልብ በሽታ፣ ስኳርና ካንሰር የመሰሰሉ ሌሎች የጤና ችግሮች ላሉባቸው ሰዎች የሚሰጡትን ቪዛ በድጋሜ እንዲያጤኑት ማዘዙን የሚገልጹ መረጃዎች በመውጣት ላይ ይገኛሉ።

በጉዳዩ ላይ የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ ከትናንትና ወዲያ ረቡእ ዕለት በዓለም ላይ ለሚገኙ የአሜሪካ ኤምባሲዎችና ቆንስላዎች በኬብል መልእክት ማስተላለፋቸውን ዋሽንግተን ፖስት ከተላለፈው የኬብል መልእክት ቅጁን አግኝቶ ማረጋገጡን ዘግቧል።

ይህም በትራምፕ አስተዳደር ስር ወደአሜሪካ የሚገቡ ስደተኞችን ለማስቆም ጥረት እያደረገች በምትገኜው አሜሪካ ቪዛ ኦፊሰሮች ከተላላፊ በሽታዎች በአሻገር በማይተላለፉ በሽታዎች ላይም የሕክምና ምርመራዎችን የማድረግና የቪዛ አመልካቾችን ያለመቀበል አዲስ ስልጣን የሚሰጣቸው ይሆናል።

ከአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ተላለፈ የተባለውና ለመጀመሪያ ጊዜ “ኬ.ኤፍ.ኤፍ ሄልዝ ኒውስ” በተባለ የሚዲያ አውታር ይፋ የተደረገው ከልክ በላይ ውፍረት ያለባቸው ሰዎችን ወደአሜሪካ እንዳይገቡ ይከለክላል የተባለው ይህ አዲስ የቪዛ ሕግ ገና ከአሁኑ በከፍተኛ ደረጃ ትችትንም ሙገሳንም በማስተናገድ አነጋጋሪ ሆኗል።

በዚህም በሬስቶን፣ ቨርጂኒያ የስደተኞች ጠበቃ የሆኑት ቪክ ጎኤል፤ “ይህ አዲሱ የቪዛ ሕግ በምንም ዓይነት መንገድ በራሳቸው መመዘኛ ሊሆኑ የማይችሉ የተለመዱ የጤና ችግሮችን መሰረት በማድረግ ወደአሜሪካ የሚመጡ አዳዲስ ስደተኞችን ብቻ ሳይሆን ነባሮችንም ጭምር ቪዛ የማግኜት መብት የሚከለክል ነው” በማለት በአጽንኦት ተቃውመውታል።

የዋይት ሐውሷ ቃል አቀባይ አና ኬሊ በበኩላቸው ሕጉን አወድሰዋል። “ባለፉት መቶ ዓመታት የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት የቪዛ ፖሊሲ በአሜሪካውያን ዜጎች ታክስ ከፋዮች ላይ ተጨማሪ ጫና የሚፈጥሩና የአሜሪካ ዜጎችን የጤና አገልግሎት ሃብት የበለጠ ለብክነት የሚዳርጉ ከልክ በላይ ክብደት ያለባቸውና መሳሰሉ ከአሜሪካ የጤና ሥርዓት ነጻ ግልጋሎት የሚያስፈልጋቸው ዜጎችን ቪዛ ለመከልከል የሚያስችሉ አግባቦች ያሉት መሆኑ ይታወቃል” ያሉት ቃል አቀባይዋ፤ አሁን የፕሬዚዳንት ትራምፕ አስተዳደር ሕጉን ሙሉ በሙሉ ሥራ ላይ እንዲውል፤ ለአሜሪካውያንም ቅድሚያ ሰጥቷል” የመንግሥታቸውን ውሳኔ አወድሰዋል።

በዓለም ላይ ከአንድ ቢሊዮን በላይ ከልክ በላይ ውፍረት ያላቸው ሰዎች የሚኖሩ ሲሆን፤ በፕሬዚዳንት ትራምፕ አስተዳደር አማካኝነት ከልክ በላይ ውፍረት ያላቸው ሰዎች ወደሀገሯ እንዳይገቡ የሚከለክል ሥራ ላይ ለማዋል በዝግጅት ላይ ነኝ የምትለው ራሷ አሜሪካ ከአርባ በመቶ በላይ የሚሆኑት ዜጎቿ ከልክ በላይ ወፍራሞች መሆናቸውን የዓለም የጤና ደርጅት መረጃ ያመላክታል።

ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦

YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA

14/11/2025

የኢሳያስ ዶክትሪን፣ በጌዲዮን አንደበት
“ የኢትዮጵያ መበጥበጥ፣ የኤርትራ ሰላም . . . ”
ይመልከቱ!

የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ጉባኤ በአርሲ የተፈጸመውን ጥቃት አወገዘዓርብ፣ ሕዳር 5 ቀን 2018 ዓ.ም ( )የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ጉባኤ ዋና ጸሐፊ ቄስ ጄሪ ፒሊ ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ...
14/11/2025

የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ጉባኤ በአርሲ የተፈጸመውን ጥቃት አወገዘ

ዓርብ፣ ሕዳር 5 ቀን 2018 ዓ.ም ( )

የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ጉባኤ ዋና ጸሐፊ ቄስ ጄሪ ፒሊ ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በላኩት የማጽናኛ ደብዳቤ በአርሲ በኦርቶዶክሳውያን ላይ በደረሰው ግድያ ጉባኤው በጥልቅ ማዘኑን ገልጸው ጥቃቱን አውግዘዋል።

ዋና ጸሐፊው ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በላኩት የማጽናኛ ደብዳቤ፤ “ይህ በሰዎች ላይ በዘፈቀደ የሚፈፀም ግድያ የሚያመላክተው የሰላሙ ሁኔታ ያልተረጋጋ መሆኑን የሚያመላክት ነው። ይህም አስቸኳይ እርቅ ለመፈጸምና ለሁሉም የሕብረተሰብ ክፍሎች ሰብዓዊ ጥበቃ ማድረግ ግዴታ መሆኑን የሚያመላክት ነው” ብለዋል።

“በዚህ አስከፊ የሃዘን ወቅት ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንና ከመላው ኢትዮጵያውያን በጋራ አብረን የምንቆም መሆናችንን ለመግለጽ እንወዳለን፤ በዚህ ጥቃት ሕይወታቸውን ላጡት ነፍሳቸውን በሰላም እንዲያሳርፍልን በጥቃቱ ለተጎዱት ሁሉ መጽናናትንና ጥንካሬን እንዲሰጥልን እግዚአብሔር አምላካችን በጸሎት እንጠይቃለን” ብለዋል ዋና ጸሐፊው ለቤተ ክርስቲያኗ በላኩት የማጽናኛ ደብዳቤያቸው።

“የግጭቶችን መሠረታዊ መንስኤ በመለየትና ንግግሮችና ምክክሮች እንዲኖሩ በማድረግ የሰው ልጆች ሕይወትና ክብር ይጠበቅና ይረጋገጥ ዘንድ እግዚአብሔር አምላክ በሁሉም ደረጃ ለሚገኙ መሪዎች ጥበብንና ቁእጠኝነትን እንዲሰጥልን እንጸልያለን” ብሏል ጉባኤው።

የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ጉባኤ በሰው ልጆች ላይ የሚፈፀም እንዲህ ዓይነቱን ግድያ በጥብቅ የሚያወግዝ መሆኑን የገለጹት ዋና ጸሐፊው፣ ሰላምን፣ ፍትሕንና በሕዝቦች መካከል ተቻችሎ በሰላም ለመኖር ለሚደረገው ጥረት ደግሞ ጉባኤው የማያቋርጥ ድጋፍ ያለው መሆኑን ገልጿል።

በኦሮሚያ ክልል፣ አርሲ ዞን፣ በጉና፣ በመርቲ፣ በሸርካ እና ሆሎንቆ ዋቢ ወረዳዎች የኦርቶዶክስ ኃይማኖት ተከታዮች መገደላቸውን ቤተ ክርስቲያኒቱን ጨምሮ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የኃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ገልጸው የነበረ ቢሆንም የኃይማኖት ተቋማት ጉባኤ በኋላ አደረግሁት ባለው ማጣራት ጥቃቱ በአንድ ሃይማኖት እና ብሔር ላይ ያነጻጸረ አለመሆኑን መግለጹ ይታወሳል።

ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦

YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA

አስር የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲዎች ትናንት የጋራ መግለጫ አውጥተዋል። መግለጫውን ተከትሎ አዲስ ማለዳ የተወሰኑ ጥያቄዎችን አንስታለች።የህብር ኢትዮጵያ ሊቀመንበር ግርማ በቀለ ለጥያቄዎቹ ምላሽ ...
13/11/2025

አስር የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲዎች ትናንት የጋራ መግለጫ አውጥተዋል። መግለጫውን ተከትሎ አዲስ ማለዳ የተወሰኑ ጥያቄዎችን አንስታለች።

የህብር ኢትዮጵያ ሊቀመንበር ግርማ በቀለ ለጥያቄዎቹ ምላሽ ሰጥተዋል።

ያድምጡት፤ አስተያየትዎን ያስፍሩ!

#ዜና #ኢትዮጵያ አዲስ ማለዳ ወቅታዊ የኢትዮጵያን ጉዳዮች በስፋትና በጥልቀት የምትተነትን፣ እንዲሁም የተረጋገጡና የትም ያልተሰሙ ዜናዎች የሚቀርቡባት የ....

በደላንታ ወረዳ ከ20 ወራት በፊት “ ናዳ የተደረመሰባቸው ሰዎች አስክሬን መታየቱን ” ማህበሩ ለአዲስ ማለዳ ተናገረሐሙስ፣ ህዳር 4 ቀን 2018 ዓ.ም ( )በአማራ ክልል፣ ደቡብ ወሎ ዞን፣ ...
13/11/2025

በደላንታ ወረዳ ከ20 ወራት በፊት “ ናዳ የተደረመሰባቸው ሰዎች አስክሬን መታየቱን ” ማህበሩ ለአዲስ ማለዳ ተናገረ

ሐሙስ፣ ህዳር 4 ቀን 2018 ዓ.ም ( )

በአማራ ክልል፣ ደቡብ ወሎ ዞን፣ ደላንታ ወረዳ በየካቲት 1 ቀን 2016 ዓ.ም “ ናዳ የተደረመሰባቸው ሰዎች አስክሬን ከ20 ወራት በኋላ መታየቱን ” የወርቅ ዋሻ የማዕድን አምራቾች ማህበር ሊቀመንበር ተስፋዬ አጋዥ ለአዲስ ማለዳ ተናግረዋል፡፡

በደቡብ ወሎ ዞን፣ ደላንታ ወረዳ ቆቅ ውኃ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ በማዕድን ማውጣት ሥራ ላይ በነበሩ ሰዎች ናዳ እንደተደረመሰባቸው ይታወሳል፡፡

በወቅቱ የቦታው አቀማመጥ ለማሽን የተመቸ ባለመሆኑ በሰው ኃይል በቁፋሮ የነፍስ አድን ጥረት ቢደረግም በህይወት ማዳን ሳይቸል ቀርቷል፡፡

አስክሬናቸውንም ለማውጣት የአካባቢው ማህበረሰብ፤ የተጎጂ ቤተሰቦች እንዲሁም የአካበቢዉ የመንግስት አካላት ጥረት አድርገዉ የነበረ ቢሆንም ሁኔታዉ አመች ባለመሆኑና ይበልጡኑ ሌላ ተጨማሪ አደጋን ያስከትላል የሚል ስጋት በመፈጠሩ አስክሬናቸዉም ጭምር ላለፉት 20 ወራት ገደማ አስክሬናቸዉ ተቀብሮ ቆይቷል፡፡

በዛሬው ዕለት ታዲያ የወርቅ ዋሻ የማዕድን አምራቾች ማህበር ሊቀመንበር ተስፋዩ አጋዥ ማዕድን ለማግኘት በተደረገ ቁፋሮ የተቀበሩትን ሰዎች አስክሬን ማየት እንደተቻለ ተናግረዋል፡፡

“ በዋሻው ውስጥ ተቀብሮ የቀረ የ9 ወጣቶች አስክሬን መሆኑን ” የተናገሩት ተስፋዬ “ አደጋው በደረሰበት ወቅት ተደጋጋሚ ሙከራዎች ከተደረጉ በኃላ አስክሬን የማውጣት ሥራው ቆሞ እንደነበር ” አስታውሰዋል፡፡

ረቡዕ ሌሊት በአካባቢው የሚገኙ ሌሎች የማዕድን ፍለጋ ስራ ላይ የተሰማሩ ሰራተኞች ማዕድን ለማውጣት ባደረጉት ቁፋሮ አስክሬኑን ማየት መቻላቸውን ገልጸዋል፡፡

“ አስክሬኑን ያገኙት ሰራተኞች ፍርሃት ሰላደረባቸው ለማውጣት አልሞከሩም ” ያሉት ሊቀመንቡሩ እርሳቸውን ጨምሮ የተጎጂ ቤተሰቦችን፣ የአካባቢውን የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች በማነጋጋር ወደ ስፍራዉ ለማቅናትና አስክሬኑን ለማውጣት በዝግጅት ላይ መሆናቸውንም አክለዋል፡፡

አስክሬኑ በዚያን ጊዜ በደረሰው አደጋ የተቀበረ ስለመሆኑን እርግጠኛ ስለመሆናቸው በአዲስ ማለዳ ጥያቄ የቀረበላቸዉ ተስፋዬ በአካባቢው ከዚያ በፊትም ይሁን በኃላ የደረሰ መሰል አደጋ አለመኖሩን ተናግረዉ ሁኔታውን አረጋግጠዋል፡፡

አዲስ ማለዳ ጉዳዩን ለማጣራት የወረዳው አስተዳዳሪ አያሌው በሪሁንን ያነጋረቻቸው ሲሆን “ በትክክል አስክሬናቸው መታየቱን ” አረጋግጠዋል፡፡

አስክሬን የማጣት ሥራውንም የተጎጂ ቤተሰቦችን በማነጋገርና የጤና ለሙያዎችን በማሳትፍ ዛሬ ማታ አልያም በነገው እለት ወደ ስፍራዉ እንደሚያቀኑ ተናግረዋል፡፡

ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA

የቡድን 7 ሀገራት በዩክሬይን እና በሱዳን አስቸኳይ የተኩስ አቁም እንዲደረግ ጠየቁ ሐሙስ፣ ሕዳር 4 ቀን 2018 ዓ.ም ( )አሜሪካ፣ ፈረንሳይ፣ ብሪታኒያ፣ ጀርመን፣ ካናዳ፣ ጣሊያንና ጃፓንን...
13/11/2025

የቡድን 7 ሀገራት በዩክሬይን እና በሱዳን አስቸኳይ የተኩስ አቁም እንዲደረግ ጠየቁ

ሐሙስ፣ ሕዳር 4 ቀን 2018 ዓ.ም ( )

አሜሪካ፣ ፈረንሳይ፣ ብሪታኒያ፣ ጀርመን፣ ካናዳ፣ ጣሊያንና ጃፓንን ያሰባሰበው፤ የበለጸጉት ሀገራት ጥምረት የሆነው የቡድን 7 ሀገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች በካናዳ በዝነኛው ኒያግራ ፏፏቴ አጠገብ ባከናወኑት ጉባኤ በዩክሩይን አስቸኳይ የተኩስ አቁም እንዲደረግ፤ በሱዳን ደግሞ ግጭት እንዲበርድ ባወጡት የጋራ መግለጫ ጠይቀዋል።

“አስቸኳይ የተኩስ አቁም ስምምነት በአፋጣኝ ሊደረግ ይገባል” ያለው የቡድን 7 ሀገራት መግለጫ፤ ሀገራቱ ለዩክሬይን የግዛት አንድነት ያላቸውን ያልተቋረጠ ድጋፍም አረጋግጠዋል።

ሀገራቱ ዩክሬይን እነርሱ “ወረራ” ብለው የሚጠሩትን የሩስያ ጦርነት ለመቋቋም የሚያስችላትን የገንዘብ ድጋፍ ማጠናከር በሚቻልባቸው አማራጮች ዙሪያ ተወያይተወዋል፡፡

በጉበኤው ላይ የተጋበዙት የዩክሬይኑ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንድሪ ሲቢሃ በበኩላቸው፤ የቡድን 7 ሀገራት በሩስያው ፕሬዝደንት ቭላድሚር ፑቲን ላይ የሚያደርጉትን ጫና የበለጠ አጠናክረው እንዲቀጥሉበትና በአንጻሩ ለዩክሬይን ደግሞ የውጊያ አቅሟን ሊያጠናክሩ የሚችሉ ድጋፎችን እንዲያደርጉ ጠይቀዋል።

በሱዳን የተፈጠረውን ቀውስ በተመለከተም የቡድን 7 ሀገራት የጋራ መግለጫ በዓለም ላይ ትልቁን ሰብዓዊ ቀውስ እየፈጠረ መሆኑን የሚገለጸውንና የሱዳን ብሔራዊ ጦርና ራሱን የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል እያለ በሚጠራው ኢመደበኛ ጦር መካከል እየተደረገ ያለውን ጦርነት በጽኑ አውግዟል።

ጉባኤውን አጠናቅቀው ወደሀገራቸው በተመለሱበት ወቅት የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርክ ሩቢዮ በሱዳን ደም አፋሳሹ ጦርነት ዳግም እንዲባባስ እያደረገ ነው በማለት ፈጥኖ ደራሽ ኃይሉን ወንጅለዋል። ፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ ከውጭ የሚያገኘው የጦር መሳሪያ አቅርቦት እንዲቋረጥ ዓለም አቀፉ ማሕበረሰብ ጫና እንዲያደርግም አሳስበዋል።

የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል እስካሁን በተደረገው የእርስ በእርስ ጦርነት ጠንካራ ይዞታ የተባለለትን የዳርፉር ግዛት ዋና መቀመጫ የሆነችውን የአል ፋሽር ከተማ ከተቆጣጠረ ከሁለት ሳምንት በኋላ የተካሄደው የቡድን 7 ሀገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ጉባኤ ሁለቱም ተፋላሚ ወገኖች ግጭት እንዲያበርዱና ዘላቂ የተኩስ አቁም ስምምነት በአስቸኳይ እንዲፈጽሙ፤ ብሎም ያልተገደበ የሰብዓዊ እርዳታ መስመር እንዲከፍቱ በአጽንኦት ጠይቋል።

ፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ አል ፋሽርን ከተቆጣጠረ ወዲሕ በአካባቢው የጅምላ ግድያ መፈጸሙንና የዘር ማጥፋት ወንጀሎች ተፈጽሞ ሊሆን እንደሚችል የሚያመላክቱ መረጃዎች እየወጡ መሆናቸውን፣ ጦርነቱ በዓለም ላይ ትልቁን የሰብአዊ ቀውስ መፍጠሩን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ማስታወቁን፣ አሜሪካን ጨምሮ ዓለም አቀፉ ማሕበረሰብ ለጉዳዩ ትኩረት እንዲሰጥ በተደጋጋሚ ጥሪ እየቀረበ ነው፡፡

ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦

YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA

በኦሮሚያ ክልል በከፍተኛ ሁኔታ እየተባባሰ የመጣውን የሰብዓዊ መብት ጥሰት ለማስቆም የክልሉም ሆነ የፌደራል የመንግስት አካላት ኃላፊነታቸውን በአግባቡ እንዲወጡ ኢሰመጉ ጠየቀረቡእ፣ ሕዳር 3 ...
12/11/2025

በኦሮሚያ ክልል በከፍተኛ ሁኔታ እየተባባሰ የመጣውን የሰብዓዊ መብት ጥሰት ለማስቆም የክልሉም ሆነ የፌደራል የመንግስት አካላት ኃላፊነታቸውን በአግባቡ እንዲወጡ ኢሰመጉ ጠየቀ

ረቡእ፣ ሕዳር 3 ቀን 2018 ዓ.ም ( )

በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ አርሲ ዞን እና በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን ሰላማዊ በሆኑ ዜጎች ላይ ያነጣጠሩ እና ለሞት፣ ለአካል ጉዳትና ለእገታ የዳረጉ ጥቃቶች መፈጸማቸውን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባኤ (ኢሰመጉ) ማረጋገጡን ባወጣው ጋዜጣዊ መግለጫ አስታውቋል። በክልሉ በከፍተኛ ሁኔታ እየተባባሰ የመጣውን የሰብዓዊ መብት ጥሰት ለማስቆም የክልሉም ሆነ የፌደራል የመንግስት አካላት ኃላፊነታቸውን በአግባቡ እንዲወጡም ጠይቋል።

በምስራቅ አርሲ የተፈጸሙ የተለያዩ የመብት ጥሰቶችን መመርመሩን ያስታወሰው ኢሰመጉ፤ “በእነዚህ አካባቢዎች የሚፈጸሙ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች በቂ ትኩረት እንዲሰጣቸው እና ድርጊት ፈጻሚዎች በሕግ ተጠያቂ እንዲሆኑ መግለጫ ማውጣታችንና ጥሪ ማቅረባችን የሚታወስ ነው” ብሏል።

በዚህም ኢሰመጉ ባሰባሰበው መረጃ መሰረት በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን በጉና መርቲ ሸርካ እና በሆሎንቆ ዋቢ ወረዳዎች ጥቅምት 14 ለ 15 ቀን 2018 ዓ.ም እንዲሁም በ 18 ለ 19 ቀን 2018 ዓ.ም ብዛት ያላቸው የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች፣ የእስልምና እምነት እንዲሁም የተለያዩ የሌሎች እምነት ተከታዮች በታጠቁ አካላት የተገደሉ መሆኑን እና የተወሰኑትም ታግተው የተወሰዱ መሆኑን ገልጿል።

በተመሳሳይ ጥቅምት 25 ቀን 2018 ዓ.ም በአርሲ ዞን መርቲ ወረዳ ጎዶ በሚባል አካባቢ የጤፍ አጨዳ ላይ ቆይተው ምሳ ለመብላት በተቀመጡበት አምስት አርሶ አደሮች በታጠቁ አካላት የተገደሉ መሆኑን ኢሰመጉ ባደረኩት ምርመራ ተረድቻለሁ ብሏል።

ይሁን እንጂ የክልሉም ሆነ የፌደራል የመንግሥት አካላት ለሰብዓዊ መብት መጠበቅ ኃላፊነታቸውን በበቂ ሁኔታ ባለመወጣታቸው የመብት ጥሰቱ በከፍተኛ ሁኔታ እየተባባሰ መምጣቱን ኢሰመጉ በመግለጫው አመላክቷል።

በመሆኑም የፌደራል እና የኦሮሚያ ክልል መንግሥታት በክልሉ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሱ የመጡትን የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች በቂ ትኩረት በመስጠት የሕዝቡ ሰላም ተጠብቆለት የመኖር መብቱን እንዲያከብሩና እንዲያስከብሩ ጥሪውን አቅርቧል።

የፌደራል እና የኦሮሚያ ክልል መንግሥታት የዜጎችን በሕይወት የመኖር መብት የማስከበር ግዴታቸውን በአግባቡ እንዲወጡ፣ በተለይም ጥቃቶች በተደጋጋሚ በሚፈጸሙባቸው አካባቢዎች በቂ የጸጥታ ጥበቃ እንዲያደርጉ፣ በኦሮሚያ ክልል በተደጋጋሚ ጊዜ ለሚፈጸሙ ጥቃቶች የፌደራልና የኦሮምያ ክልል መንግስታት የጸጥታ አካላት ጥቃቶች ሳይደርሱ ቅድመ የመከላከል ስራን በመስራት፣ ተፈጽመው ሲገኙም አፋጣኝ ምላሽና ትኩረት በመስጠት ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ኢሰመጉ አሳስቧል።

በምስራቅ አርሲ ዞን በተፈጸሙት ግድያዎች እና አፈናዎች ላይ በሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ በኩል የተጀመረው የምርመራ ሂደት መኖሩን ኢሰመጉ የሚገነዘበው ቢሆንም፣ ሂደቱ ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ደረጃዎችን ያሟላ፣ ሙሉ በሙሉ
ገለልተኛ፣ ግልጽ እና ተአማኒነት ያለው እንዲሆን መንግስት እንዲያረጋግጥና፤ የምርመራው ግኝትም ለሕዝብ ይፋ ተደርጎ የጥፋት ፈጻሚዎችና ትዕዛዝ ሰጪዎች በሕግ እንዲጠየቁ እንዲያደርግም አሳስቧል።

የምስራቅ አርሲ ዞን ሽርካ ወረዳ የጸጥታ አካላት በተለያዩ ቀበሌዎች እየተፈጸሙ ያሉት የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች እንዲቆሙ ለጉዳዩ በቂ ትኩረት በመስጠት እና በመከታተል ጥፋት አድራጊዎችን ለሕግ በማቅረብ ተጠያቂ እንዲሆኑ የድርሻቸውን እንዲወጡም ኢሰመጉ ጠይቋል።

በተመሳሳይ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በጋሞ ዞን የዘይሴ ማሕበረሰብ ያቀረበውን የልዩ የወረዳነት አስተዳደራዊ መዋቅር ጥያቄ ጋር ተያይዞ ጥቅምት 10 ቀን 2018 ዓ.ም በተቀሰቀሰ ግጭት ንጹኃን ዜጎች ላይ የአካል ጉዳት መድረሱን እና በርካቶች ለእስር መዳረጋቸውንም ኢሰመጉ ከአካባቢው ካሰባሰበው መረጃ ለመረዳት መቻሉን ገልጿል።

ስለሆነም የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በክልሉ የሚነሱ የመዋቅር ጥያቄዎች የሀገሪቱን ሕግ በተከተለ እና ማሕበረሰቡን አሳታፊ በሆነ በሰላማዊ መንገድ በወቅቱ የሚፈታበትን ሁኔታ እንዲያመቻችና በሂደቱ የሚፈጠሩ ግጭቶችን እንዲከላከል ኢሰመጉ በጥብቅ ማሳሰቡን አዲስ ማለዳ ከመግለጫው ተመልክታለች።

ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦

YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA

ከአሥር የአፍጋናውያን የስደት ተመላሽ ቤተሰቦች ዘጠኙ ለረሃብ የሚጋለጡ መሆናቸውን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የልማት ፕሮግራም ገለጸረቡእ፣ ሕዳር 3 ቀን 2018 ዓ.ም ( )በአፍጋኒስታን ...
12/11/2025

ከአሥር የአፍጋናውያን የስደት ተመላሽ ቤተሰቦች ዘጠኙ ለረሃብ የሚጋለጡ መሆናቸውን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የልማት ፕሮግራም ገለጸ

ረቡእ፣ ሕዳር 3 ቀን 2018 ዓ.ም ( )

በአፍጋኒስታን ከጦርነት ጋር በተያያየ ተፈናቀለዉ የነበሩ አፍጋናውያን ቤተሰቦች ወደቀያቸው ሲመለሱ ከአስሩ ዘጠኙ ለረሃብ እንደሚጋለጡ አለያም ብድር ውስጥ እንደሚገቡ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የልማት ፕሮግራም ገለጸ።

በአፍጋኒስታን ከጦርነት ጋር በተያያየ ተፈናቀለዉ የነበሩ አፍጋናውያን ቤተሰቦች ወደቀያቸው ሲመለሱ ከአስሩ ዘጠኙ ለረሃብ እንደሚጋለጡ አለያም ብድር ውስጥ እንደሚገቡ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የልማት ፕሮግራም አስተውቋል።

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የልማት ፕሮግራም አዲስ ባወጣው ሪፖርት መሰረት በሚሊዮን የሚቆጠሩ አፍጋናውያን በድህነት ወደተጠቃው ምስራቅና ሰሜን የሀገሪቱ አካባቢዎች ሲመለሱ ከአስር የቤተሰብ አባላት ዘጠኙ ለረሃብ ይጋከለጣሉ አለያም ብድርነ እዳ ውስጥ ይገባሉ።

የእርዳታ መቋረጥ፣ ማእቀብና ባለፈው ነሐሴ ወር የተከሰተውንና በሬክተር ስኬል 4 ነጥብ 5 የተመዘገበዉን የመሬት መንቀጥቀጥ ጨምሮ በተደጋጋሚ የተፈጥሮ አደጋዎች እየተፈተነች የምትገኜው በታሊባን ቁጥጥር የምትተዳደረዉ አፍጋኒስታን ከአውሮፓውያኑ 2023 ጀመሮ 4 ነጥብ 5 ሚሊዮን የሚሆኑ ከስደት ተመላሾችን ለማስተናገድ ተቸግራለች።

በዚህ ዓመት ብቻ አንድ ነጥብ አምስት ሚሊዮን የሚጠጉ ስደተኞች ከፓኪስታንና ኢራን በግዳጅ እንዲመለሱ መደረጋቸዉን ተከትሎ የአፍጋኒስታን ስደተኞችን የመመለሱ ሂደት የበለጠ ፈተና ውስጥ ገብቷል።

በመሆኑም ወደ አፍጋኒስታን እየተመለሱ ያሉ የስደት ተመላሽ አፍጋናውያን የከፋ የኢኮኖሚ ቸግር ዉስጥ የሚገኙ መሆናቸውን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የልማት ፕሮግራም ባወጣው ሪፖርት ስታውቋል።

በዚህም ከግማሽ በላይ የሚሆኑት ተመላሾች ምግብ ለመግዛት የህክምና አገልግሎትን ለመዝለል የሚገደዱ ሲሆን ከዘጠና በመቶ በላይ የሚሆኑት ደግሞ የብድር እዳ ውስጥ ገብተዋል።

ከዚህ ጋር በተያያዘ አማካኝ ወርሀዊ ገቢያቸዉ መቶ ዶላር ቢሆንም ከ373 እስከ 900 ዶላር የሚደርስ የብድር እዳ ውስጥ መሆናቸውን ከ 48 ሽሕ ቤተሰቦች በተወሰደ ናሙና መገንዘቡን ሪፖርቱ ገልጿል።

ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦

YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA

መዝገበ ቃላቱ ለኢትዮጵያ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዕውቀት ፈጠራና ተደራሽነት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ተገለጸረቡእ፣ ሕዳር 3 ቀን 2018 ዓ.ም ( )በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ እና የኢኖ...
12/11/2025

መዝገበ ቃላቱ ለኢትዮጵያ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዕውቀት ፈጠራና ተደራሽነት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ተገለጸ

ረቡእ፣ ሕዳር 3 ቀን 2018 ዓ.ም ( )

በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ እና የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ትብብር የተመረቀው የሳይንስና ቴክኖሎጂ የጽንሰ ሐሳብ አቻ ስያሜዎችን ከብያኔዎቻቸው የያዘው “አዲስ የሳይንስና ቴክኖሎጂ” መዝገበ ቃላት ለኢትዮጵያ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዕውቀት ፈጠራና ሥርጭት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ተገለጸ።

የሳይንስና ቴክኖሎጂ እንግሊዝኛ - አማርኛ መዝገበ ቃላቱ የሳይንስ ዕውቀትን በማስፋፋትና ሳይንሳዊ ባህልን በማዳበር ተልእኮውን በመፈጸም ሂደት ዓይነተኛ ግብዓት ለማበርከት ያለመ መሆኑንና መዝገበ ቃላቱ ወደ ፊት በሌሎች ሀገርኛ ቋንቋዎችም ተተርጉሞ ሰፋ ላለ ኅብረተሰብ አገልግሎት እንደሚሰጥ የተደረገ መሆኑንም የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ አስታውቋል።

መዝገበ ቃላቱን ማዘጋጀት ያስፈለገበት ዋናው ምክንያትም የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዕውቀት በዓለም አቀፍ ደረጃ በፍጥነት እያደገ በመምጣቱ እና በሀገራችን የትምህርት፣ የቴክኖሎጂ ሽግግርና የምርምር ዘርፎች ጉልህ የሆኑ ለውጦች እየታዩ በመሆናቸው በቋንቋ ምክንያት የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሐሳቦችን የመግለጽ ዐቅም ማዳበር አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ መሆኑንም አካዳሚው አመላክቷል።

በዓለም አቀፍ ደረጃ ሳይንስ ለመላው የሰው ልጆች ዕድገት እያበረከተ ያለው አስተዋጽዖ እና ዓለምን ለጋራ ዓላማ የማስተባበር ኃይሉ በመላው ዓለም በሚዘከርበት የዓለም የሳይንስ ቀን የተመረቀው አዲስ የሳይንስና ቴክኖሎጂ እንግሊዝኛ-አማርኛ መዝገበ ቃላት በሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዕውቀት ፈጠራ እና ሥርጭት ረገድ በኢትዮጵያ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚኖረውም የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ፕሬዚዳንት ፕሮፌሰር በላይ ካሳ ተናግረዋል።

በመጽሐፉ ምረቃ ሥነ ሥርዓት ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር በለጠ ሞላ(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ አዲሱ የሳይንስና ቴክኖሎጂ እንግሊዘኛ-አማርኛ መዝገበ ቃላት መጽሐፍ ሕትመት ተከናውኖ ለምረቃ መብቃቱ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዘርፍን በመረዳት ወደ ተግባር ለመለወጥ ለሚደረገው ጥረት ጉልህ ሚና ያለው መሆኑን ገልጸዋል።

በቀጣይ መዝገበ ቃላቱ በብዙ የሀገራችን ቋንቋዎች እየተተረጎመ ተደራሽ እንዲሆን ለማስቻል ከኢትዮጵያ የሳይንስ አካዳሚ እና ሌሎች ተመሳሳይ ዓላማና ተልእኮ ካላቸው ተቋማት ጋር በትብብር መሠራት ያለበት መሆኑንም ሚኒስትሩ አስገንዝበዋል።

በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ድጋፍ በኢትዮጵያ የሳይንስ አካዳሚ የታተመው “አዲስ የሳይንስና ቴክኖሎጂ” እንግሊዝኛ-አማርኛ መዝገበ ቃላት ከ30 በላይ የሙያ ዘርፎች፣ ከ90 በላይ ከከፍተኛ ትምህርት፣ ከምርምር ተቋማት እና ከሳይንስ አካዳሚ የተመረጡ ዕውቅ ባለሙያዎች የተሳተፉበት ሲሆን ከ 11 ሺሕ 500 በላይ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ስያሜዎች የተበየኑበት መሆኑን አዲስ ማለዳ ከኢትዮጵያ ሳይንስ አካኣሚ ያገኜችው መረጃ ያመላክታል።

ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦

YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA

በከባድ መኪና ሾፌሮች ላይ የሚደርሰው ግድያ፣ እገታና የኮቴ ክፍያ የሚቆመው በመንግሥት ብቻ መሆኑን ማሕበሩ ገለጸረቡእ፣ ሕዳር 2 ቀን 2018 ዓ.ም ( )በከባድ መኪና አሽከርካሪዎች ላይ በየ...
12/11/2025

በከባድ መኪና ሾፌሮች ላይ የሚደርሰው ግድያ፣ እገታና የኮቴ ክፍያ የሚቆመው በመንግሥት ብቻ መሆኑን ማሕበሩ ገለጸ

ረቡእ፣ ሕዳር 2 ቀን 2018 ዓ.ም ( )

በከባድ መኪና አሽከርካሪዎች ላይ በየጊዜዉ እየደረሰ የሚገኘዉን ጥቃት ተከትሎ አዲስ ማለዳ የከባድ መኪና አሽከርካሪዎችን አነጋግራለች። አሽከርካሪዎችም “እኛ ብንናገርም አሁንም ችግሩ መፍትሄ አላገኘም፤ በተዳጋጋሚ ጥቃት እየተፈጸመብን ነው፤ በጉዳዩ ላይ ማዉራት ትርፉ ድካም ሆኖብናል፤ ችግሩ በሰው የሚፈታ አይደለም” ሲሉ በተስፋ መቁረጥና በምሬት ቅሬታቸውን ለአዲስ ማለዳ ገልጸዋል።

የከባድ መኪና አሽከርካሪዎችን ቅሬታና አስተያየት መነሻ በማድረግ አዲስ ማለዳ ያነጋገረቻቸው የኢትዮጵያ ከባድ መኪና አሽከርካሪዎች ማሕበር ሥራ አስኪያጅ ሰለሞን ዘዉዱ በእርግጥም በከባድ መኪና ሾፌሮች ላይ በየጊዜው የሚደርሰው ችግር አሁንም ያላቆመ መሆኑን አመላክተው፤ በከባድ መኪና ሾፌሮች ላይ የሚደርሰው ግድያ፣ እገታና የኮቴ ክፍያ የሚቆመው በመንግሥት ብቻ መሆኑን ገልጸዋል።

የከባድ መኪና አሽከርካሪዎች በሁሉም ዘርፎች ተግዳሮቶች የሚገጥሟቸው መሆኑን የገለጹት ሥራ ስኪያጁ፤ አሁን ላይ ግን ለአሽከርካሪዎቹ ቀዳሚ ችግር እየሆነባቸዉ የሚገኘው የመንገድ ላይ ዝርፊያ፣ እገታ እና ግድያ ብሎም ኬላ እና ኮቴ መሆኑን ተናግረዋል።

“በተለያዩ ጊዜያት በሹፌሮች ላይ የሚደርሰዉን ግድያ አስመልክቶ በተለያዩ ምክንያቶች ቁጥራዊ መረጃዎች ለመያዝ እቸገራለሁ” ያሉት ሥራ አስኪያጁ፤ ባለፉት 15 ቀናት ዉስጥ ሁለት አሽከርካራች አማራ ክልል ዉስጥ መገደላቸዉን ገልጸዋል።

ችግሩ እየተከሰተ የሚገኜው በሁሉም የኢትዮጵያ አካባቢዎች አለመሆኑን ያመላከቱት አቶ ሰለሞን፤ ግድያና ዝርፊያዎች አብዛኛዉን ጊዜ በአማራ ክልል እና አልፎ አልፎ ደግሞ በኦሮሚያ ክልል የሚከሰቱ መሆናቸውን ጠቁመዋል።

የመንገድ ላይ ኮቴና ኬላ ክፍያዎችን በተመለከተ ደግሞ በኦሮሚያ እና ሱማሌ ክልሎች በሚገኙ የተለያዩ አካባቢዎች በቋሚነትና በተለዋዋጭ ሁኔታዎች በስፋት የሚጠየቁ መሆናቸውን አመላክተዋል።

ከኮቴ እና ኬላ ክፍያ ጋር በተያያዘ አልከፍልም በሚሉ ሹፌሮች ላይ የሚደርሱ ጥቃቶች መኖራቸውንም አንስተዋል።

ማሕበሩ ጉዳዩን ይዞ በሚንቀሳቀስባቸዉ የፌደራልም ሆነ የክልል መሥሪያ ቤቶች ኃላፊዎች ዘንድ ተቀባይነት ያለው ቢሆንም ጉዳዩን ወደ መሬት የማውረድና የመፈጸም ችግር መኖሩን የጠቆሙት ሥራ አስኪያጁ፤ ማሕበሩ ትናንትና ሕዳር 2 ቀን 2018 ዓ.ም ከኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ትራንስፖርት ኤጀንሲ ጋር ውይይት ማድረጉን ጠቅሰዋል።

በዚህም ከክልሉ ትራንስፖርት ኤጀንሲ ጋር በተደረገው ውይይት የኮቴ ክፍያ እንዳይከፈል የሚል ውሳኔ መተላለፉን የገለጹት አቶ ሰለሞን፤ “መቼ ተግባራዊ ይደረጋል የሚለውን ግን አላወቅንም” ሲሉ ለአዲስ ማለዳ ተናግረዋል።

ይሁን እንጂ ችግሩ ያለው ከተሞቹ ላይ መሆኑንና ከተሞች ይህንን ክፍያ እንደ ገቢ ምንጭ እየተጠቀሙት በመሆኑ ለማስቆም ፍቃደኛ አለመሆናቸውንም ገልጸዋል።

ማኅበሩ ከዚህ ቀደም በተደጋጋሚ ይህንን መሰል ችግር ይከሰትበት በነበረዉ የአፋር ክልል ባደረገዉ ውይይት ዛሬ ላይ በአካባቢዉ በሹፌሮች ላይ የሚደርስ ጥቃት መቀነሱንም ሥራ አስኪያጁ አመላክተዋል።

በተለይም በአማራ ክልል የሚፈጸመዉ የግድያና የእገታ ጉዳይ በሹፌሮች ላይ ብቻ ያነጻጸረ አለመሆኑን የጠቆሙት ሥራ ስኪያጁ፤ “ከፀጥታው ሁኔታ ጋር በተያያዘ በሁሉም ዜጋ ላይ የሚደርስ ችግር በመሆኑ ችግሩ የሚፈታው በመንግሥት ብቻ ነው” ብለዋል።

ከሰዎች ከቦታ ቦታ የመዘዋወር ነጻነት አለመከበርና ከመንገድ ደህንነት አለመረጋገጥ ጋር በተያያዘ የሚፈጸሙ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሳቸውን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን የዛሬ ወር ጥቅምት 3 ቀን 2018 ዓ.ም መዘገቧ ይታወሳል።

በዚህ ዘገባ መንግሥት ሰዎች በሰላም እና ነጻነት ወጥተው መግባት እንዲችሉ በመንገዶች ላይ በታጠቁ ኃይሎች ለሚደርሱ ጥቃቶች፣ እገታዎች፣ የንብረት ዘረፋዎች እና ውድመቶች ተገቢውን ትኩረት በመስጠትና በአካባቢው ከሚገኙ ነዋሪዎች ጋር በቅርበት በመሥራት ችግሮች ሲከሰቱ በወንጀሉ የተሳተፉ ግለሰቦችን በሕግ ተጠያቂ እንዲሆኑ ማድረግና ተጠያቂነትን ለማረጋገጥ ተገቢ የሆኑ እርምጃዎችን እንዲወስድ ኮሚሽኑ ጥሪ አቅርቦ ነበር።

ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦

YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA

የቀድሞው የሊቢያ መሪ ፕሬዝደንት ሙአመር ጋዳፊ ልጅ፣ ሃኒባል ጋዳፊ በሊባኖስ ከእስር ተፈታማክሰኞ፣ ህዳር 2 ቀን 2018 ዓ.ም( )በሊባኖስ ለአስር ዓመታት ለሚጠጋ ጊዜ በእስር ላይ የነበረው...
11/11/2025

የቀድሞው የሊቢያ መሪ ፕሬዝደንት ሙአመር ጋዳፊ ልጅ፣ ሃኒባል ጋዳፊ በሊባኖስ ከእስር ተፈታ

ማክሰኞ፣ ህዳር 2 ቀን 2018 ዓ.ም( )

በሊባኖስ ለአስር ዓመታት ለሚጠጋ ጊዜ በእስር ላይ የነበረው የቀድሞው የሊቢያ መሪ ፕሬዝደንት ሙአመር ጋዳፊ ልጅ ሃኒባል ጋዳፊ ከእስር መፈታቱን ጠበቃው አስታውቀዋል። ሃኒባል ጋዳፊ ከእስር የተፈታው በ900 ሺሕ ዶላር የዋስትና ገንዘብ ክፍያ መሆኑም ታውቋል።

የ49 ዓመቱ ሃኒባል ጋዳፊ በሊባኖስ ለእስራት የተዳረገው በአሁኑ ሰዓት የሊባኖስ ሺዓ ቡድን-ሂዝቦላሕ አጋር የሆነው የአማል ንቅናቄ መስራች ሊባኖሳዊው የሺዓ ጸሐፊ ሙሳ ሳድር በአውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1978 በሊቢያ መሰወራቸውን ተከትሎ መረጃ ደብቃሃል በሚል በቀረበባቸው ክስ ሲሆን፤ ነገር ግን በእስራት ዘመናቸው ፍርድ ቤት እንዳልቀረቡ ቲአርቲ አፍሪካ ዘግቧል።

ይሁን እንጂ ሙሳ ሳድር በሊቢያ ሲጠፉ ሃኒባል ጋዳፊ ገና የሁለት ዓመት ሕጻን ነበረ።

ከአስር ዓመታት እስራት በኋላ ሃኒባል ጋዳፊ በ900 ሺሕ ዶላር የገንዘብ ዋስትና በትናንትናው ዕለት ከእስር የተፈታ ሲሆን፤ “ገንዘቡ ዛሬ ተከፍሏል፤ በመጨረሻም ሃኒባል ጋዳፊ ከእስር ተፈትቷል፤ ለአስር ዓመታት የዘለቀው አስፈሪው የሃኒባል የእስር ቤት ቆይታ ዛሬ መቋጫውን አግኝቷል” ብለዋል ጠበቃው ሎረን ባየን።

ባለፈው ጥቅምት ወር ጉዳዩን የያዙት ዳኛ ሃኒባል ጋዳፊንን ከእስር ለመልቀቅ 11 ሚሊዮን ዶላር የዋስትና ገንዘብ እንዲከፈል አዝዘው የነበረ ሲሆን ተከላካይ ጠበቆች ባቀረቡት ይግባኝ ገንዘቡ ወደ 900 ሺሕ ዶላር ዝቅ እንዲል መደረጉን የቲአርቲ አፍሪካ ዘገባ አመላክቷል።

የሊቢያን ፓስፖርት የያዘው ደንበኛቸው ሃኒባል ጋዳፊ ምስጢራዊ መዳረሻ እንዲኖረው ተደርጎ ከሊባኖስ እንዲወጣ መወሰኑን ጠበቃው ሎረን ባየር ገልጸዋል።

“ሃኒባል ጋዳፊ ባልተረጋገጠ ክስ በሊባኖስ ለአስር ዓመታት ታስሮ እንዲቆይ የተደረገው የፍትሕ ሥርዓቱ ገለልተኛ ባለመሆኑ ነበር” ያሉት የሃኒባል ጠበቃ፤ የደንበኛቸው ከእስር መለቀቅ በሊባኖስ ባለፈው ጥር ወር ላይ በተመሰረተው የለውጥ መንግስት ስር የፍትሕ ሥርዓቱ ገለልተኝነት እንደገና እያንሰራራ ለመምጣቱ ማሳያ መሆኑን ተናግረዋል።

ከሊባኖሳዊቷ ሞዴል አሊን ስካፍ ጋር በጋብቻ የተሳሰረው ሃኒባል ጋዳፊ በሊባኖስ ለእስር የተዳረገው በሀገሩ የተከሰተውንና ለ42 ዓመታት በስልጣን ላይ የቆዩትን አባቱን ፕሬዝደንት ሙዐመር ጋዳፊን በአሰቃቂ ግድያ ከስልጣን ያስወገደውን ሕዝባዊ አመጽ ሸሽቶ በሶሪያ በስደት ይኖር በነበረበት በአውሮፓውያኑ 2015 በታጣቂዎች ተይዞ ወደሊባኖስ ከተወሰደ በኋላ ነው፡፡

ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦

YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA

Address

Tsehay Messay Bldg, 4th Floor Near Bambis Supermarket
Addis Ababa
63000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Addis Maleda - አዲስ ማለዳ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Addis Maleda - አዲስ ማለዳ:

Share