Gurage limat

Gurage limat ነገም ሌላ ቀን ነው

21/02/2026

መልካም ቀዳሚት ሰንበት ይሁንላቹ ከምንሰማቸው የጦርነት ዜናዎች ይጠብቀን ለሀገራችን ሰላሙን ያድለን ያላሰብነው በረከት ያድለን አሜን።

28/12/2025

መልአኩም መልሶ፦ “እኔ በእግዚአብሔር ፊት የምቆመው ገብርኤል ነኝ፥ እንድናገርህም ይህችንም የምሥራች እንድሰብክልህ ተልኬ ነበር::
ሉቃስ 1:19

ታላቅ የቤተ ክርስቲያንልጅነት ዘመቻበቅዱስ ሚካኤል የንግሥ በዓል ላይ በየምናነግስበት ደብር ድምፃችንንለአርሲ ሰማዕታት ወገኖቻችን ድምፃችንን በፅሁፍ አናሰማባገኘነው ነገር የምንፅፋቸው ፅሁፎች...
20/11/2025

ታላቅ የቤተ ክርስቲያን
ልጅነት ዘመቻ
በቅዱስ ሚካኤል የንግሥ በዓል ላይ በየምናነግስበት ደብር ድምፃችንን
ለአርሲ ሰማዕታት ወገኖቻችን ድምፃችንን በፅሁፍ አናሰማ
ባገኘነው ነገር የምንፅፋቸው ፅሁፎች
1 ትኩረት ለአርሲ ኦርቶዶክሳውያን ወገኖቻችን
2 ፍትህ ከአርሲ ሰማዕታት ወገኖቻችን
3 ሞት ይብቃ!
4 አርሲ ትጣራለች
የመረጥነውን ፅፈን በማዘጋጀት ታቦት ሲዞር ሌላ ድምፅ ሳናሰማ በጨዋነት ድምፃችንን እናሰማ
አጀንዳችን አርሲ ናት

የእኛ የኦርቶዶክስ ጥያቄ አትግደሉን ነው ።እናንተ ገድላቹን ስታበቁ መግደላችንን አትናገሩብን ብላቹ መገደላችን መናገራችን እንደጥፋት እና እንደ ወንጀል እየቆጠራቹን ነው። ተው ፅዋው ሞልቶ የ...
09/11/2025

የእኛ የኦርቶዶክስ ጥያቄ አትግደሉን ነው ።እናንተ ገድላቹን ስታበቁ መግደላችንን አትናገሩብን ብላቹ መገደላችን መናገራችን እንደጥፋት እና እንደ ወንጀል እየቆጠራቹን ነው። ተው ፅዋው ሞልቶ የፈሰሰ ዕለት የሚመጣው ከባድ ነው ። እረፉ እረፉ አንዳንዶቻቹ ደግሞ በሞታችን የምትሳለቁ የአባቶቻቹ በደል ነው ያላቹ ይሄ ጭፍጨፋ በእኛ የሚቀር መስሏቹ ከሆነ ተሳስታችኋል ተራ እየጠበቃቹ እንደሆነም ተረዱ አንተ በመጠጥ የናወዝክ እና በዲኤስ ቲቪ ኳስ የናወዝክ ትውልድ ንቃ አንተ እየሰከርክ ሌላው ሚሰራውን እየሰራ ነው ንቃ ቤተክርስቲያንህን ጠብቅ ክርስቲያን አዲስ አበባ ያለውም አርሲ ያለውም ቅበት ያለውም ወረጋ ያለውም ....ክርስቲያን ነው በክርስቶስ ክርስቲያን የተባለ አንዱ ብልት ላይ ያለ እኛ እጃችን ሲቆረጥ እግራችን ካልቆረጡት እያልን ነውና አንድ ክርስቲያንን መጠበቅ እራስን መጠበቅ ነው ተላልፈን አንሰጣጥ መልክቴ ነው።

07/11/2025

13: መርዶክዮስም አክራትዮስን፦ “ሂድና ለአስቴር እንዲህ በላት፡” አለው፦ “አንቺ፦ በንጉሥ ቤት ስለ ሆንሁ ከአይሁድ ሁሉ ይልቅ እድናለሁ፡ ብለሽ በልብሽ አታስቢ።
14: በዚህ ጊዜ ቸል ብትዪ ዕረፍትና መዳን ለአይሁድ ከሌላ ስፍራ ይሆንላቸዋል፥ አንቺና የአባትሽ ቤት ግን ትጠፋላችሁ፤ ደግሞስ ወደ መንግሥት የመጣሽው እንደዚህ ላለው ጊዜ እንደ ሆነ ማን ያውቃል?”
መ /አስቴር 4:13_14

07/11/2025

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን
ከጥቅምት ፳፬ ቀን ዓ.ም ጀምሮ እየተደረገ ስለሚገኘው ዓለም አቀፍ የሚዲያ ዘመቻ ንቅናቄ ከአስተባባሪ ኮሚቴዎች የተሰጠ መግለጫ

እንደሚታወቀው ከጥቅምት 24 ጀምሮ ለተከታታይ ሦስት ቀናት ላለፉት ሰባት ዓመታት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንና በኦርቶዶክሳውያን ላይ በመንግሥት ድጋፍ፣ ኃይል ተመድቦ፣ ከለላ ተሰጥቶ፣ በዕቅድና በተልዕኮ እየተፈጸመ ያለውን Genocide ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ፣ ለሀገራት መሪዎች፣ ለዓለም አቀፍ የሚዲያ ተቋማትና ችግሩ ለሚመለከታቸው አካላት ለማድረስ የማኅበራዊ ሚዲያ ዘመቻ እያካሄድን እንደሆነ ይታወቃል፡፡ ይህ ዘመቻ ከተጀመረበት ቀን አንስቶ በመላው ዓለም የሚገኙ ኦርቶዶክሳዉያን የሀዘን ምልክት የሆኑ አልባሶቻችንን በመልበስ፣ Profile Picture በመቀየር እንዲሁም በተለያዩ የመገናኛ ዘዴዎች ላይ ንቅናቄ በማድረግ ለዓለም አቀፍ ማህበረሰብ የኦርቶዶክሳውያንን ሞት በማሳዎቅ ላይ ይገኛሉ። ይህንንም ተከትሎ የተለያዩ የውጭ ሀገር ዜጎች፣ የኦሬንታል ኦርቶዶክስ አባቶችና አገልጋዮች፣ በተለያዩ ሚዲያዎች ላይ የሚሰሩ ጋዜጠኞች ሀዘናቸውን በተለያየ መንገድ በመግለጥ ላይ ይገኛሉ።
ዘመቻው ከተጀመረ ወዲህ በትናንትናው እለት በአርሲ ዞን ወርቲ ወረዳ አቦምሳ ከተማ ጋዶ ቀበሌ በ24/02/2018 ስማቸው ይርጋ ሲሳይ፣ የሺጥላ ሲሳይ፣ ጥበቡ ዝቅአርጋቸው፣ አሞኜ ኃይልዬ፣ ንጉሴ ከበደ በአጠቃላይ 6 ሰዎች ተገድለዋል። 5ቱ ተቀብረዋል የ 1 ሬሳ እስካሁን ድረስ አልተገኘም በተጨማሪም 3 ሰዎች ታፍነው ተወስደዋል። እዛው አቦምሳ ከተማ ፈረቀሳ ቀበሌ ማታ ላይ ስሙ እንዳለ መኮነን የተባለ እድሜው 56-60 የሚገመት ኦርቶዶክሳዊ በማሳው ላይ ሳለ ተገድሏል። በ25/02/2018 ከታፈኑት 3ቱ ሰዎች 2ቱ ተገድለው ዛሬ በ26/02/20 አቦምሳ መድኃኔዓለም ቀብራቸው ተፈጽማል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ የአርሲ ዞን የመንግሥት መዋቅር ትላንት ባደረገው ስብሰባ ለጩኸታችን እልባት ከመስጠት ይልቅ ሀገረ ስብከቱ ፍጹም ሰላም እንደሆነና መዋያየት ያለብን በልማትና በዘላቂ ሰላም ጉዳዮች ነው በማለት ጭካኔ የተሞላበት ድምጽንና ሐዘንን የማፈን ዘመጃ፣ እንዲሁም ዘመቻውን ለመቀልበስ በተለያየ መንገድ የተለያዩ አጀንዳዎችን በማውጣት የኦርቶዶክሳውያንን ሞት ለመሸፈን ሲሯሯጥ እንደነበር አይተናል፡፡
ይህ ሁሉ ሲሆን ከ60 በላይ አህጉረ ስብከት፣ ከሰባት መቶ ያላነሱ ወረዳ ቤተ ክህነቶች፣ በርካታ አድባራትና ገዳማት፣ የሰንበት ትምህርት ቤት ኅብረቶች፣ በመቶዎች የሚቆጠሩ ማኅበራት፣ የቤተ ክርስቲያን ሚዲያዎች አንዳቸውም እንኳን ስለ አሰቃቂው የአሪሲ ኦርቶዶክሳውያን ሞትና ስደት ትንፍሺ ሊሉ አልፈቀዱም፡፡ ከሁሉም የሚያሳዝነው ደግሞ በጠቅላይ ቤተ ክህነት ሥር ያሉ መዋቅራት በጉዳዩ ላይ ትኩረት አድርገው ይሠሩበት ዘንድ በተደጋጋሚ ቢጠየቁም፣ የእለህ በሚመስል ሁኔታ ሁሉም ዝም በማለት ይባስ ብሎ አንዳንዶች ሀዘናችን ላይ በመሳለቅ ስለጉባኤ ስለመዝሙራት፣ ስለመጻሕፍት ሲናገሩ፣ ለዘምቻው ማስቀየሻ ይሆን ዘንድ ይበጀናል ያለውን ‘’ፍኖተ ጽድቅ’’ የሚባል የተሐድሶ ሚዲያን ሕጋዊ አስደርጌያለሁ በማለት ዜና ያስነግራል፡፡
አሁን ጥያቄው ይኸ ሁሉ ተቋማት ያሏት ቤተ ክርስቲያን ድምጽ የሚሆናት ጠፍቶ ልጆቿ በየሜዳው ወድቀው፣ በጅምላ እየተቀበሩ ይቀጥላሉ? ወይስ የሚለው ነው። ምንም እንኳን ችግራችንን የሚፈታልን መሪ ባይኖረንም የኦርቶዶክሳውያንን ሞት ማስቆምና ዘላቂነት ያለው መፍትሔ ማምጣት ለነገ የማይባል ጉዳይ በመሆኑ፣ እንደዚህ ቀደሙ ጀምረን የምንተወው ሳይሆን መፍትሔ እስክናገኝ

04/11/2025

የቲዊተር ዘመቻ ተጀምሯል።ይህንን እንፖስት
Innocent Ethiopian Orthodox Christians are facing persecution for their faith.
We call for global media attention, protection, and dignity for vulnerable believers. ✝️🕯️



ሁላችንም ሸር እናድርገው

11/09/2025

ትንሽዬ የሀገር ቤት ትውስታ አክራሚ
በልጅነት አእምሮዬ ከምወዳቸው በዓላት አንደኛው ምናልባትም ሁለተኛው በዓል ነው ። ዋዜማው ላይ ሆኜ የአዲስ አበባን ግርግር ተመለከቱኩት አስራ ስምንት ዓመት ወደኋላ መለሰኝ ወደምወዳትና ወደምናፍቃት የትውልድ ሀገሬ 120 እስከ 127 ኪሎ ሜትሮችን አስጓዘኝ ምን ልታደርግ አትሉኝም ለዋዜማው ለበዓል ለከብቶቼ የበዓል መዋያቸው ሳር ላጭድ ለቤቴ እንጨት ልለቅም ለሳሎኔ ቄጤማ ላጭድ የአዲስ አበባን ግርግር ስልችት አድርጎኝ ሀገር ቤት ወሰደኝ በሀሳቤም የተሰማኝ እረፍት የተስፋ ጭላንጭል ቀጣዩን ዓመት መናፈቅ ምን ልበላቹ ድቅን አሉብኝ ለቤታችን የሚያስፈልጉኝን ሁሉ ጨረስኩና ለጠዋት ገላዬ ስታጠብ እንዳይበርደኝ እሳት ማቀጣጥልበት ግንድ ፍለጋ ለቡ የምወዳት ወንዜ ወረድኩ እሷስ መች አሳፈረችኝ ለእንቁጣጣሽ ይጠቅምሃል ብላ ክረምቱን በጎርፍ ተሸክማ አዘጋጅታልኛለች እያመሰገንኳት ሰበሰብኩና እቤቴ ተመልሼ አባቴን ከአዲስ አበባ ይዟት ከሚመጣው በግ ጋር ለመጠበቅ ወደቤት አቤት ልጅነት አይኔ ሰው ባየ ቁጥር ክርትት አባቴን አግኝቼ ቤታችን ተሟልቶ አባቴም ዞር ዞር ብሎ ክረምቱ ምን እንዳጎደልን ምን እንዳለማን እንዲሁም ከብቶቹን ከጎበኘ በኋላ ለዛ ቀን ባልተኛው እያልኩ ዋዜማዬን ጨርሼ ሊነጋጋልኝ ወገግ ሲል በበሪ ልጆች ላለመቀደም ወደ ወንዛችን ኩራታቻን ትውስታችን ወደ ሆነችው ለቡ የበሪ ሰው እንዳለ ተሰብስቦ በለሊት ገላ መታጠብ ከታጠብን በኋላም ዋናችንን ዋኝተን የማርያም ፀበል የሚጠመቀው ተጠምቆ ከጨረሰ በኃላ ወደ እሳት መሞቃችን አምርተን ያለው ጨዋታ የሚነገረን ታሪክ የሚሳቀው ሳቅ እስከ ረፋድ 3 ሰዓት ይዘልቃል ። ሳልነግራቹ ወንዶች እና ሴት ወጣት ልጆች እንዲሁም እፃናት ነን ደግሞም ልዩ የሚያደርገው የበሪ ሰው ነው እንዲ የሚያደርገው የእናንተም ከፈለጋቹ አካፍሉን በቃ አታስቀናን ካላቹ ከወንዛችን ወደ በዓል ማክበራችን ወደ ቤት እንመለስ እናቶቻችን ግን እኛ እንደዛ ስንዝናና እና ስንሳሳቅምኮ እቤት ሆነው ቂንጬ እያቀነጩ ነው ክብር ለእናቶቻችን !!! ገብተን ቂንጬውን በጋራ ከጎረቤት ጋር ቡና ተፈልቶ እንበላና የአካባቢው ሰው መዞር ይጀምራል አቤት ምንበላት አይቤ በጎመን ሲጣፍጥ በጋችን ታርዶ ተሰርቶ በልተን በየ ቤቱ ዙረት አቤት ደስታ ቀሰቀሰኝ የሚለው የበዓል ዜማ ብልጭ አለብኝ እንዴ እናንተ የት ሄድኩኝ እረ መልሱኝ ነገሩ ተው እዛ ይሻለኛል ። ግንኮ የገባሁት እንኳን አደረሳችሁ ልላቹ ነበር እንኳን ለአዲሱ ዓመት ከጎደሉት ሳያጎድል ካሉት ሳያሳንስ በፍቅሩ ማርኮ በጠብቆቱ ጠብቆ እንደ አምላክነቱ መግቦ ይቺን ዓመት ለንስሐ ጨምሮ አደረሳችሁ ።!! መልካም አዲስ አመት ከትውስታዬ

16/06/2025

1ኛ ነገሥት19:-9
እዚያም ወዳለ ዋሻ መጣ፥ በዚያም አደረ፤ እነሆም፦ ኤልያስ ሆይ፥ በዚህ ምን ታደርጋለህ? የሚል የእግዚአብሔር ቃል ወደ እርሱ መጣ።
10: እርሱም፦ ለሠራዊት አምላክ ለእግዚአብሔር እጅግ ቀንቻለሁ፤ የእስራኤል ልጆች ቃል ኪዳንህን ትተዋልና፥ መሠዊያዎችህንም አፍርሰዋልና፥ ነቢያትህንም በሰይፍ ገድለዋልና፤ እኔም ብቻዬን ቀርቻለሁ፤ ነፍሴንም ሊወስዱአት ይሻሉ፡ አለ።

14/06/2025

በእናንተ ዘንድ ሁሉ በፍቅር ይሁን።
1ቆሮ 14

Address

Kolfe
Addis Ababa

Telephone

+251910999188

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gurage limat posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Gurage limat:

Share

Category