Gurage limat

Gurage limat ነገም ሌላ ቀን ነው

14/04/2025



1, #ስግደት :-
በሰሙነ ሕማማት 41 ጊዜ ኪርያላይሶን 12 ጊዜ አቡነ ዘበሰማያት እየተዜመ እጅግ አብዝቶ ይሰገዳል።

2, #ጸሎት :-
በሰሙነ ሕማማት ከ24 ሰዓት ውስጥ 10 የጸሎትና የንባብ ሰዓታት ይገኛሉ እነዚህም ከጠዋቱ 1 ሰዓት; 3ሰዓት; 6ሰዓት; 9ሰዓት; 11ሰዓት እንዲሁም ከምሽቱ 1 ሰዓት; 3ሰዓት; 6ሰዓት; 9ሰዓት; 11ሰዓት ናቸው።
በእነዚህም ሰዓታት የጌታን ስቃይ ለማዘከር መዝሙረ ዳዊትና ግብረ ሕማማት ድርሳነ ማኅያዊ አብዝተው ይጸለያሉ።

3, #ጾም :-
በሰሙነ ሕማማት ብዙ አዝማደ መባልዕት / አዘውትረን የምንመገባቸው ምግቦች አይበሉም። በዚህም ሳምንት እስከ ምሽቱ እንድንጾም; ይኸውም ቆሎ;ዳቦ;ወኃና ጨው ብቻ እንደታዘዙ በግብረ ሕማማት ላይ ተጽፎ ይገኛል።

4, #አለመሳሳም :-
አይሁድ ጌታችንን ለመስቀል እየተንሾካሾኩ ስለተመካከሩና ይሁዳ ጌታችንን በመሳም አሳልፎ ስለሰጠው መሳሳም አይፈቀድም። መስቀልም በዘመነ ኦሪት የወንጀለኛ መቅጫ የእርግማን ምልክት ስለ ነበር ጌታችን በክቡር ደሙ ቀድሶ የድል አርማ እስኪያደርግልን ድረስ አንሳለመውም ገላ.3:13 ማቴ.10:38 ማቴ. 26:29

5. #አክፍሎት :-
እመቤታችን; ያዕቆብና ዮሐንስ የጌታችን ትንሳኤ ሳናይ እህልና ውኃ አንቀምስም ብለው እስከ ትንሳኤው መቆየታቸውን በማሰብ የሚጾም ነው።

6, #ጉልባን :-
ከባቄላ ከስንዴ ከገብስ የሚዘጋጅ በጸሎተ ሐሙስ ዕለት የሚበላ ንፍሮ ሲሆን ትውፊቱም የስቅለቱ ሐዘን መግለጫ ነው።

7, #ጥብጠባ :-
ይህ ምዕመናን በሰሙነ ሕማማት የፈጸሟቸውን ኃጢአቶች ለካህን እየተናዘዙ በወይራ ቅጠል ቸብቸብ እየተደረጉ ስግደት የሚቀበሉበት ነው። ይህም የጌታ ምሳሌ ነው።

8, #ቄጠማ :-
ጌታችን ብርሃነ ትንሳኤዉን እንደገለጠልን የምናስብበት ሲሆን የእሾህ አክሊል በመድፋቱ ምሳሌም በራሳችን ላይ እናስረዋለን።
እንበለ ደዌ ወሕማም እንበለ ጻም ወድካም ያብጽሐነ ያብጽሕክሙ ለብርሃነ ትንሳኤሁ እግዚአብሔር በፍስሐ ወበሰላም።

14/04/2025

በሰሙነ ህማማት ወቅት የምንሰማቸው እንግዳ ቃላትና ትርጉማቸው

በግብረ ሕማማት ውስጥ በግዕዝም ሆነ በኋላ በአማርኛ ሳይተረጎሙ የተቀመጡ የእብራይስጥ፣ የቅብጥና የግሪክ ቃላት ይገኛሉ። የእነዚህ ቃላት ትርጉም የሚከተለው ነው፦

#ኪራላይሶን፦ ቃሉ የግሪክ ሲሆን አጠራሩ
< ኪርዬ ኤሌይሶን> ነው። #ኪሪያ ማለት እግዝእትነ / እመቤታችን" ማለት ሲሆን "ኪርዬ" ማለት ደግሞ "እግዚኦ / ጌታ ሆይ / አቤቱ" ማለት ነዉ፡፡ "ኤሌይሶን" ማለት ደግሞ "ማረን / ይቅር በለን" ማለት ነዉ ፡፡ ትርጉሙም "አቤቱ ማረን" ማለት ነዉ፡፡ "ኪራላይሶን" የምንለዉ በተለምዶ ነዉ፡፡ ይኸዉም "ኪርዬ" ከሚለዉ "ዬ" ኤሌይሶን" ከሚለዉ ደግሞ "ኤ" በመሳሳባቸዉ በአማርኛ "ያ"ን ፈጥረዉ ነዉ፡፡

#ናይናን፦ የቅብጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙ "መሐረነ፤ማረን" ማለት ነው።
#እብኖዲ ፦ የቅብጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙ "አምላክ" ማለት ነው። "እብኖዲ ናይናን" ሲልም " አምላክ ሆይ ማረን" ማለቱ ነው።
#ታኦስ ፦ የግሪክ ቃል ሲሆን ትርጉሙ "ጌታ፣አምላክ" ማለት ነው።
#ማስያስ ፦ የእብራይስጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙ "መሲህ" ማለት ነው።
#ትስቡጣ ፦ "ዴስፓታ" ከሚለው የግሪክ ቃል የመጣ ሲሆን ትርጉሙም "ደግ ገዥ" ማለት ነው።
፦ የቅብጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙ "ተዘከረነ እግዚኦ በውስተ መንግስትከ- አቤቱ በመንግስትህ አስበኝ" ማለት ነው።
፦ የቅብጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙ " ተዘከረነ ኦ ቅዱስ በውስተ መንግስትከ -ቅዱስ ሆይ በመንግስትህ አስበን" ማለት ነው።
፦ የቅብጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙ " ተዘከረነ እግዚአ ኩሉ በውስተ መንግስትከ -የሁሉ በላይ የሆንክ ሆይ በመንግስትህ አስበን " ማለት ነው።

ጮቢ በዓታ ለማርያም ገዳም ቦታውን መጎብኘት እና መርዳት ለምትፈልጉ ከዚ ስር ባለው መረጃ ይጠቀሙ
23/03/2025

ጮቢ በዓታ ለማርያም ገዳም ቦታውን መጎብኘት እና መርዳት ለምትፈልጉ ከዚ ስር ባለው መረጃ ይጠቀሙ

05/01/2025

- ማቴዎስ 14-16: በነቢዩም በኢሳይያስ፦
“የዛብሎን ምድርና የንፍታሌም ምድር፥ የባሕር መንገድ፥
በዮርዳኖስ ማዶ፥ የአሕዛብ ገሊላ፤
በጨለማ የተቀመጠው ሕዝብ ታላቅ ብርሃን አየ፥
በሞት አገርና ጥላ ለተቀመጡትም ብርሃን ወጣላቸው፡”
የተባለው ይፈጸም ዘንድ ይህ ሆነ።

10/09/2024

2017
አክራሚ የሺከተ ዬቀናልክምዪለቅቦ የኩን ለመንግስቲም ታው ዬበልን

09/09/2024

እንኳን ለአክራሚ አሰላንህም!!!

25/03/2024
መስቀል በጉራጌ
04/10/2023

መስቀል በጉራጌ

Viva ሳንጅዬዬዬ
10/07/2023

Viva ሳንጅዬዬዬ

10/07/2023

ለሃገረ መንግስቱ፣ ለኦሮሚያ ክልል፣ ለደቡብ ክልል፣ ለመላው ጉራጌና ሶዶ ክስታኔ ህዝብ ተወካዮች!

አርሶ-አደሩ...እርፍ ይጨብጥ መድፍ?
***
ሃገር የሰው ውጤት ነው። ቤተሰብ፤ ማህበረሰብ...እያለ ''ሃገር'' የሚባለውን ትልቅ ስዕል የሚሰጠን ሰው ነው።

ሰው ደግሞ ሁሉም እኩል ነው። በሌላ ነገር ቢበላለጥ እንኳ ''ነፍስ'' በምትባል ፍፁም ስስ ነገር እኩል ነው! ነገርዬው ይህ ሁሉ ማብራሪያ የሚፈልግ ባይሆንም ለመዘርዘር ግን እየተገደድን ነው።

''ኢትዮጵያ ውስጥ የሰው ሞት እጅግ እየተባባሰ ነው'' ሲባል መንግሥትም የሚያስተባብልበት ሞራል ላይ እንዳልሆነ እራሱ ያውቀዋል ባይ ነን። መንግሥት ግን አሁንም ''መገዳደል ምንም ጥቅም የለውም'' የሚል ምንም ጥያቄ የማያሻው ''የሞኝ ንግግር'' ላይ ነው። ገዳዩን እንዲያስቆሙለት፤ ሞቱን እንዲያስቀሩለት እንጂ የሚያውቀውን ነገር እንዲደግሙለት የሚፈልግ ማንም የለም።

በህዝብ የተመረጠ መንግሥት ሌላው ነገር ቢቀር ሰላም የማስፈን ግዴታ አለበት። ከማንም ጋር ተስማምቶም ይሁን ተጣልቶ! ታዲያ እዚህ ጋ ''መች?'' መባሉ አይቀርም። ''አሁን እና አሁን ብቻ'' ነው መልሱ!

አንድም ሰው አላማው በግልፅ ያልታወቀ የታጠቀ ቡድን ጥቃት ሰለባ ሳይሆን! ''ሰውም ነፍስም እኩል ነው'' ብለን የለ? አሁንስ? የብዙ ሰው ህይወት አልፏል። በርካቶች ተደብድበው ሀብት ንብረታቸውን ተቀምተዋል። የቀሩትም ስጋት በወለደው ቆፈን ላይ ናቸው! ይህ እጅግ አደገኛ እና ሃገርን የባሰ ዋጋ ሊያስከፍል የሚችል አደጋ ያዘለ በእንጭጩ ያልተቀጨ ችግር ነው።

ገዳዩን አካል ''ማንም አሉት ማን'' ዋናው ነገር ሞትና እንግልትን ማስቆሙ ላይ ነው። የመንግሥት መንግሥትነት ያለውም እዚህ ላይ ነው። ችግሩ በመላ ሃገሪቱ የተንሰራፋ ቢሆኖም ከቅርብ ወራት ወዲህ ግን በ #ጉራጌ በተለይም በ ህዝብ ላይ የተደቀነው አደጋ የህልውና ሆኗል! ችግሩ እንደተጠቀሰው የሃገር ቢሆንም ሞት ግን የሚጀምረው ከሃገር ሳይሆን ከግለሰብ፣ ከቤት፣ ከቤተሰብ፣ ከሰፈር-መንደርና አካባቢ እያለ ነው።

ስለሆነም ከጠቅላይ ሚኒስትሩ አንስቶ ባለባችሁ የበዛ ሃላፊነት ልክ መንቀሳቀስ ሲገባችሁ የበዛ ዝምታን የመረጣችሁ የህዝብ ተወካዮች #ህጋዊ እስከመምሰል የደረሰውን ግድያ አስቁሙልን! ምድራዊው ሀይል ያለው በናንተና እናንተ በምትመሩት ስርአት እጅ ነው። ህዝብ ምናልባት ለጊዜው መረጃ ሰጪ ቢሆን ነው። መረጃ ደግሞ የላችሁም አንልም።

አርሶ-አደሩ ለዛውም በዚህ ወርቃማ የአዝመራ ጊዜው ሲሞት፣ ሲገረፍና ሲዘረፍ ማየት እንደምን ዝምታን ያስመጣል? የሃገሬ ሰው ''ቀልደኛ ገበሬ በሰኔ ይሞታል'' ያለው ቢቻለው ተፈጥሯዊውን ሞት ጭምር መሞት የለበትም ለማለት ነው። ሲቀጥል ከእጅ ወደአፍ ህይወት የሚኖር አርሶ-አደር ስለምን ይገደላል? ስለምንስ ይዘረፋል? በሃገር ኢኮኖሚ ላይ የተቀጣጠለ እሳት አጥፊ እንጂ የፖለቲካ ብልሽት ማብረጃ ነው እንዴ አርሶ-አደር? በቀዬው እንዴት ይታፈናል? እንዴት በልጆቹ ፊት ይገረፋል? ከብቶቹን አሰማርቶ ወጥቶ የሚገባበት ታዛው ጦርሜዳ ነው እንዴ? እና አርሶ-አደሩን መሳሪያ በገፍ ከታጠቀ ገዳይ እና ከማንም የ የሚታደገው ማነው? በዚህ አስቸጋሪ ወቅትስ እንዴት ወጥቶ ይግባ? የሰአት እላፊ ገደቡ በርግጥስ አርሶ-አደሩን ተጠቃሚ አድርጓል ወይስ...? በጥቅሉ አርሶ-አደሩ እርፍ ይጨብጥ መድፍ?

እናም ተጠሪ እና ተወካዮቻችን ሆይ እባካችሁ አካባቢውን መልከት አድርጉት? የፌዴራል የፀጥታ ሀይላት ልዩ ትኩረት በሚያሻቸው የገጠር ቀበሌ ማዕከላትና አቅራቢያ ከተሞች እንዲሰፍሩ ቢደረጉ። ሌላው እዛው አርሶ-አደር ጉያ ተወሽቀው መረጃ በማቀባበልና በማቀሳሰር ከመቺው በላይ አስመቺ #ሆድ-አደሮችን እንኳ የዘረጉትን የሴራ ኔትወርክ በመበጠስ አርሶ-አደሩ ''አዎ መንግሥት አለ'' እንዲል ምክንያት ሁኑት። ታጣቂ ቡድኑን በተመሳሳይ የትጥቅ አፀፋም ሆነ በሌላ ሃገር በቀል የሰላም መንገድ በማነጋገር ሂደቱን መምራት ያለበትም እራሱ መንግስት ነው። ከነዚህ ሁለቱ መፍትሔዎች አንዱም ባለመደረጉ ግን በሚስኪን አርሶ-አደሮች ላይ የሚደርሰው ግፍ አሁንም ሞልቶ እየፈሰሰ ነው።

ከዞን እስከ ወረዳ እና ቀበሌ ባለው የመንግሥት መዋቅር እጃቸው በንፁሃን ገንዘብና ደም የቆሸሸ አመራር አሉ። እየሆነ ያለው ነገር ''መንግሥትም የጥቃቱ ደጋፊ ወይም አካል ነው'' የሚያስብል ነው። ጨለም ሲል በየአቅጣጫው የሚፈነዳው ግጭት አርሶ-አደሮች የሚቋቋሙት አይደለም። አንዳንዶቹ አካባቢዎች ላይ የአርሶ-አደሩን በግና ፍየል እያሳረዱ በግድ አብሮ እስከመኖር ደርሷል።

ሃገሪቱ በግልፅ ታውቀው የነበረው የሰላም ችግር የፌደራሉ መንግሥት ገብቶበት የነበረው ጦርነት ነው። እሱ ይሻላል። መንግሥትም ሆነ የህዝብ ተወካዮች አሁን በአርሶ-አደሩ ላይ ስለሚፈፀመው ኢ-መደበኛ ጥቃት ምንም ሲሉ እየተሰሙ አይደለም። እንደድሮው ልዩ ሀይል እንኳ በሌለበት ክልልና ዞን ይህንን የሚያክል አውዳሚ ሀይል በአካባቢ ፖሊስና በገበሬ ትከሻ መቋቋም የማይታሰብ ነው።

አርሶ-አደር እኮ ''ሰለጠንኩ'' ያለው የከተሜው ነዋሪ፣ አሻጥረኛ ነጋዴና ፖለቲከኞች የፈጠሩትን የኑሮ ውድነት ያለጥፋቱ እየተጋፈጠ የሚገኝ #አፈር-ገፊ ነው። ነገር ግን የአፈር ማዳበሪያ እንኳ በቅጡ እንዳይደርሰው ተደርጎ የሚያርስበትን በሬ ከቀንበሩ ፈትቶ፤ የሚታለብ ላሙን ከጥጃው ነጥሎ እስከመሸጥ በደረሰ ዘግናኝ ዋጋ ገበያ ወጥቶ ለመግዛት ሲገደድ ዝም ብሎ ማየት እንዴት ያለ ጭካኔ ነው? እሺ ይሁን፤ እሱን ገዝቶ ወደቀየው ሲገባ እንዴት ይገደላል? ቢያንስ በሰብአዊነት እንተዛዘን እንጂ!

Address

Kolfe
Addis Ababa

Telephone

+251910999188

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gurage limat posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Gurage limat:

Share

Category