Team Talk Sport ቲም ቶክ ስፖርት

Team Talk Sport ቲም ቶክ ስፖርት ሁሉንም ስፖርት በአንድ መነፅር, "THE IN & OUT" We feed all sport news and analysis from every corner. sport news source

 #አርሰናል የውድድር ዓመቱን የመጀመሪያ የቻምፒየንስ ሊግ ጨዋታ በድል ተወጥቷል።በኤስታዲዮ ሳንማሜስ አትሌቲክ ቢልባኦን የገጠመው አርሰናል 2ለ0 አሸንፏል።ኤቤሬቼ ኤዜን ቀይሮ የገባው ጋብርኤ...
16/09/2025

#አርሰናል የውድድር ዓመቱን የመጀመሪያ የቻምፒየንስ ሊግ ጨዋታ በድል ተወጥቷል።

በኤስታዲዮ ሳንማሜስ አትሌቲክ ቢልባኦን የገጠመው አርሰናል 2ለ0 አሸንፏል።

ኤቤሬቼ ኤዜን ቀይሮ የገባው ጋብርኤል ማርቲኔሊ እና በዮኬሬሽ ተቀይሮ የገባው ሊአንድሮ ትሮሳርድ የመድፈኞቹን ሁለት ግቦች ከመረብ አሳርፈዋል።

በሌላ ጨዋታ በሜዳው ኡኑዮን ሴንት ጂልዋስን የገጠመው ፒ ኤስ ቪ አይንዶቨን 3ለ1 ተሸንፏል።

ምሽት 4 ሰዓት ላይ አራት ጨዋታዎች ይከናወናሉ።

አርሰናል ዛሬ አትሌቲክን የሚያሸንፍ ከሆነ የስፔን ክለቦችን ለተከታታይ 6ኛ ጊዜ ያሸነፍ ክለብ ያሰኘዋል
16/09/2025

አርሰናል ዛሬ አትሌቲክን የሚያሸንፍ ከሆነ የስፔን ክለቦችን ለተከታታይ 6ኛ ጊዜ ያሸነፍ ክለብ ያሰኘዋል

✍️በወንዶች 800 ሜትር ማጣሪያ በምድብ 6 የተወዳደረው 🇪🇹አትሌት ዮሃንስ ተፈራ በ1:50.93 በሆነ ሰአት 8ኛ ደረጃን ይዞ በማጠናቀቁ ወደ ግማሽ ፍፃሜው ሳያልፍ ቀርቷል።* በ800 ሜትር ...
16/09/2025

✍️በወንዶች 800 ሜትር ማጣሪያ በምድብ 6 የተወዳደረው 🇪🇹አትሌት ዮሃንስ ተፈራ በ1:50.93 በሆነ ሰአት 8ኛ ደረጃን ይዞ በማጠናቀቁ ወደ ግማሽ ፍፃሜው ሳያልፍ ቀርቷል።

* በ800 ሜትር የመጀመሪያ ዙር ማጣሪያ ወደ ግማሽ ፍፃሜ የሚያልፉት ከየምድቡ ከ1-3ኛ ያጠናቀቁ እና ከሁሉም ምድቦች ፈጣን ሰአት ያላቸው 3 አትሌቶች ነበሩ።

  ትኬት ስታዲየም አይገባም፦ መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ።የደህንነት ካሜራ በአዲስ አበባ ስታዲየም ይገጠማል፣ የሚያጠፋ ይለቀማል። ለደጋፊዎች መታወቂያ ግድ ነው።
16/09/2025

ትኬት ስታዲየም አይገባም፦ መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ።

የደህንነት ካሜራ በአዲስ አበባ ስታዲየም ይገጠማል፣ የሚያጠፋ ይለቀማል። ለደጋፊዎች መታወቂያ ግድ ነው።

"ክቡር አቶ ይድነቃቸው ተሰማ በወቅቱ ከዘመኑ እርቀው እግር ኳሳችንን በብቃት የመሩ ታላቅ ፕሬዝዳንት ባሉበት ሀገር እንዴት መሪ እናጣለን" ኢንስትራክተር አብርሀም መብርሀቱየ2018 ዓ.ም የኢ...
16/09/2025

"ክቡር አቶ ይድነቃቸው ተሰማ በወቅቱ ከዘመኑ እርቀው እግር ኳሳችንን በብቃት የመሩ ታላቅ ፕሬዝዳንት ባሉበት ሀገር እንዴት መሪ እናጣለን" ኢንስትራክተር አብርሀም መብርሀቱ

የ2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎችን አዲስ አበባ ስታዲየም ላይ ለማስጀመር ክክለቦችና ከፌዴሬሽን አመራሮች ጋር በቅድመ ዝግጅቱ ዙሪያ ውይይት ተደርጏል::

በምክክሩ ላይ ሀሳብ ከሰጡ ባለሙያዎች መካከል አንዱ የሆኑት ኢንስትራክተር አብርሀም መብርሀቱ ሲሆኑ የፀጥታ ችግር ያለው በእግር ኳሱ አዲስ አበባ ብቻ አይደለም፣ክልሎችም ሊፈተሹ የገባል፣አዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረትን በብቃት የምታዘጋጅ ከተማ እንዴት እግር ኳሱን ማዘጋጀት አቃታት ሲሉ ተናግረዋለ::

ሌላው ኢንስትራክተሩ ያነሱት ሀሳብ ከዘመኑ ቀድመው የኢትዮጵያን እግር ኳስ በብቃት የመሩትን ክቡር አቶ ይድነቃቸው ያፈራች ሀገር እንዴት እሳቸውን የሚያህል ሀገር ወዳድ መሪ አጣን፣ሁላችንም መቆጨት አለብን ሲሉ ሀሳባቸውን ሰጥተዋል።

ይገደብ አባይ

አዲሱ የብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ!?የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዋልያዎቹ በቅርቡ ከግብፅና ከሴራሊዮን ጋር ያደረጉትን የዓለም ዋንጫ አስመልክቶ ትናንት መግለጫ ሰጥቷል። በመግለጫው ላይ "ለ1...
16/09/2025

አዲሱ የብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ!?

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዋልያዎቹ በቅርቡ ከግብፅና ከሴራሊዮን ጋር ያደረጉትን የዓለም ዋንጫ አስመልክቶ ትናንት መግለጫ ሰጥቷል።

በመግለጫው ላይ "ለ17 ዓመት በታች የወንዶች ቡድን ከአሜሪካ ኖርካል አካዳሚ መጥተው በRoad 2029 ስልጠና የሰጡትን ሚስተር ቤንጃሚን ዚመር ዋና አሰልጣኝ አድርገን ቀጥረናል፡፡በዚህ ሂደት ውጤታማ ስራ ይኖረናል ብለን እናስባለን፡፡በጥቅምት ወር የሚካሄድ የሴካፋ 17 ዓመት በታች ውድድር ይኖረናል፡፡አላማችን በዚህ ውድድር አልፎ ለአፍሪካ ዋንጫ መብቃት ነው፡፡……" ተብሏል።

የዋናውን ብሔራዊ ቡድን(ዋልያዎቹ) በተመለከተ በሦስት ዓመት ከስድስት ወር ውስጥ አራት አሰልጣኞች ተቀያይረዋል ውጤትም እየመጣ አይደለም። ይህን ተከትሎ በቀጣይ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በአሰልጣኝ መሳይ ተፈሪ ከቡድኑ ጋር ይቆያል ወይስ ፌዴሬሽኑ የውጭ ሀገር አሰልጣኝ ይቀጥራ? እንዲሁም አሰልጣኝ ካሳዬ አራጌ ብሔራዊ ቡድኑ ለምን አያሰለጥንም? በሚል ለተነሳው ጥያቄ ስራ አስፈፃሚው አቶ ባህሩ ጥላሁን ተከታዩን ምላሽ ሰጥተዋል:-

“በተጠቀሱት ዓመታቶች ውስጥ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የተለያዩ አሰልጣኞች በጊዜያዊነት እና በዋናነት መርተዋል ከዚህ ሂደት ውስጥ ፌዴሬሽኑ ያሰናበተው አሰልጣኝ የለም። ከአሰልጣኝ ውበቱ ጋር በስምምነት ከተለያየን በኋላ ሌሎቹ አራት አሰልጣኞች ኮንትራት ማብቃት ጋር ተያይዞ የለቀቁ ናቸው። ከውጤት አንፃር እግርኳሳችን ያለበት ሁኔታ የሚያስደስት አይደለም። በቀጣይ ስለሚሆነው አሰልጣኝ ስራ አስፈፃሚ የሚያደርገው ስብሰባ ይኖራል። አዳዲስ ነገሮችን የሚኖሩ ከሆነ የምናሳውቅ ይሆናል።”

“በተጫዋችነት ዘመኑ እጅግ የምናከብረው ክብር የምንሰጠው ነው። ወደ አሰልጣኝነትም ከመጣ በኋላ የራሱን ሀሳብ ለመተግበር እየሞከረ ያለ አሰልጣኝ ነው። ካሳዬን በተመለከት ጥያቄው ተነስቷል። ከአጨዋወቱ ሀሳብ በዚህ ዙርያ እኔ ቴክኒካል የሆነ ነገር ስለሆነ ሀሳብ አልሰጥም ብለዋል።”

የአውሮፓ ቻምፒየንስ ሊግ የ70 ዓመታት ጉዞ ቁጥራዊ መረጃ70ኛው የውድድር ዓመት የአውሮፓ ቻምፒየንስ ሊግ ዛሬ ይጀምራል፡፡ ፎርማቱን እቀየረ ፣ ፉክክሩን እያላቀ እዚህ የደረሰው የአውሮፓ ቻም...
16/09/2025

የአውሮፓ ቻምፒየንስ ሊግ የ70 ዓመታት ጉዞ ቁጥራዊ መረጃ

70ኛው የውድድር ዓመት የአውሮፓ ቻምፒየንስ ሊግ ዛሬ ይጀምራል፡፡ ፎርማቱን እቀየረ ፣ ፉክክሩን እያላቀ እዚህ የደረሰው የአውሮፓ ቻምፒየንስ ሊግ ዓለማችን ላይ በጉጉት ከሚጠበቁ የእግርኳስ ውድድሮች ቀዳሚው ሆኗል፡፡

ክለቦች እዚህ ውድድር ላይ ለመሳተፍ የማይከፍሉት መስዋትነት የለም፡፡ ጥራት ያላቸው ተጫዋቾች መፈረም የሚፈልጉት ቻምፒየንስ ሊግ ለሚሳተፍ ክለብ ነው፡፡

እ ኤ አ 1955/56 ዩሮፒያን ካፕ በሚል 16 ክለቦችን አሳትፎ የጀመረው የአሁኑ የአውሮፓ ቻምፒየንስ ሊጋ ተሳታፊ ክለቦቹ 36 ደርሰዋል፡፡

አጠቃላይ ከዚህ ቀደም በነበሩት 69 የውድድር ዓመታት የተመዘገቡ ቁጥሮች ምን ይነግሩናል? ዘ አትሌቲክ ድረ-ገፅ የተወሰኑትን ዘርዝሯቸዋል፡፡

በርካታ ክለቦችን ማሳለፍ የቻሉ ሀገራት

1.ጀርመን፡- 31 ክለቦች
2.ዴንማርክ፡- 17 ክለቦች
3.እንግሊዝ፡- 17 ክለቦች
4.ፈረናሳይ፡- 16 ክለቦች
5.ጣልያን፡- 15 ክለቦች
6.ስፔን፡- 14 ክለቦች

አጠቃላይ ከ44 ሀገራት 348 ክለቦች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡ ዘንድሮ አራት አዳዲስ ክለቦች ሲቀላቀሉ ቁጥሩ ወደ 352 ከፍ ይላል፡፡

በርካታ ዋንጫ ያነሱ ክለቦች

1.ሪያል ማድሪድ፡- 15
2.ኤ ሲ ሚላን፡- 7
3.ባየርን ሙኒክ፡- 6
4.ሊቨርፑል፡- 6
5.ባርሰሎና፡- 5

አጠቃላይ 24 ክለቦች ዋንጫ የማሸነፍ ዕድል አግኝተዋል፡፡

በውድድሩ በርካታ ጨዋታ ያደረጉ ክለቦች

1.ሪያል ማድሪድ ፡- 501 ጨዋታዎች
2.ባየርን ሙኒክ ፡- 402 ጨዋታዎች
3.ባርሰሎና ፡- 347 ጨዋታዎች
4.ጁቬንቱስ ፡- 307 ጨዋታዎች
5.ማንችስተር ዩናይትድ ፡- 285 ጨዋታዎች

በርካታ ጨዋታ ያከናወኑ ተጫዋቾች

1.ክርስቲያኖ ሮናልዶ፡- 183
2.ኢከር ካሲያስ፡- 177
3.ሊዮኔል ሜሲ፡- 163
4.ቶማስ ሙለር፡- 163
5.ካሪም ቤንዜማ ፡- 152

ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪዎች

1.ክርስቲያኖ ሮናልዶ ፡- 140 ግቦች
2.ሊዮኔል ሜሲ ፡- 129 ግቦች
3.ሮበርት ሌቫንዶቭስኪ ፡- 105 ግቦች
4.ካሪም ቤንዜማ ፡- 90 ግቦች
5.ራኡል ጎንዛሌዝ ፡- 71 ግቦች

በርካታ ዋንጫ ያሸነፉ ተጫዋቾች

ፍራንሲስኮ ጌንቶ ፣ ዳኒ ካርቫሃል እና ሉካ ሞድሪች ሁሉም ከሪያል ማድሪድ ጋር ስድስት ስድስት ጊዜ ዋንጫ አሸንፈዋል፡፡

አልፍሬዶ ዴስቲፋኖ ፣ ጆሴ ማሪያ ዛራጋ ፣ ካሪም ቤንዜማ እና ቶኒ ክሩስ በሪያል ማድሪድ ፤ ክርስቲያኖ ሮናልዶ (በማድሪድ እና ማንችስተር ዩናይትድ) እንዲሁም ፓውሎ ማልዲኒ ከኤ ሲ ሚላን አምስት አምስት ዋንጫዎችን ማንሳት የቻሉ ተጫዋቾች ናቸው፡፡

በርካታ ዋንጫ ማሸነፍ የቻሉ አሰልጣኞች

1. ካርሎ አንቸሎቲ፡- ከኤ ሲ ሚላን እና ሪያል ማድሪድ ጋር አምስት ዋንጫ አሸንፈዋል፡፡

2.ቦብ ቤስሊ፡- ከሊቨርፑል ጋር ሦስት ዋንጫዎች አንስተዋል፡፡

3.ዚነዲን ዚዳን፡- ከሪያል ማድሪድ ጋር ሦስት ዋንጫዎችን አሸንፏል፡፡

4.ፔፕ ጋርዲዮላ ፡- ከባርሰሎና እና ማንችስተር ሲቲ ጋር ሦስት

ዋንጫዎችን ያሸነፈ አሰልጣኝ ነው፡፡

በሸዋንግዛው ግርማ

✍️ የሴቶች 1500 ሜትር የፍፃሜ ውድድር ዛሬ ቀን 10:05 ጀምሮ ይካሄዳል🥇🥈🥉🇪🇹 ፍሬወይኒ ሃይሉ - PB 3:54.16- የ24 አመቷ አትሌት ፍሬወይኒ በ1500 ሜትር በአለም የቤት ውስጥ ...
16/09/2025

✍️ የሴቶች 1500 ሜትር የፍፃሜ ውድድር ዛሬ ቀን 10:05 ጀምሮ ይካሄዳል🥇🥈🥉

🇪🇹 ፍሬወይኒ ሃይሉ - PB 3:54.16

- የ24 አመቷ አትሌት ፍሬወይኒ በ1500 ሜትር በአለም የቤት ውስጥ ሻምፒዮና በ2024 ግላስጎው ላይ የወርቅ ሜዳሊያ ለሃገሯ ያስገኘችበት ትልቁ ስኬቷ ነው።

- 🇪🇹በአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ታሪክ በ1500 ሜትር በሁለቱም ፆታ ወርቅ ያሸነፈችው 1 ጊዜ ብቻ ነው (በሴቶች በአትሌት ገንዘቤ ዲባባ 2015 ቤጂንግ ላይ🥇)

- ለንደን፣ ዩጂን እና ቡዳፔስት ላይ የነገሰችው የርቀቱ የአለም የሪከርድ ባለቤት (3:48.68)ኬንያዊቷ ፌይዝ ኪፕዬጎን በሻምፒዮናው የማሸነፍ ከፍተኛ ግምት አግኝታለች።

- በርቀቱ የሻምፒዮናው ክብረወሰን በኔዘርላንዳዊቷ አትሌት ሲፋን ሃሰን በ2019 ዶሃ ላይ በ3:51.95 ተይዟል።

አብሬያት አልተኛም !ለአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ጃፓን የሚገኘው የኢትዮጵያ ስብስብ ጉድ አሁንም ቀጥሏል።ለማረፊያ በተያዘላቸው ሆቴል ድልድል አንድ አትሌት የሀገሯን ልጅ ከእሷ ጋር አንድ አል...
16/09/2025

አብሬያት አልተኛም !

ለአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ጃፓን የሚገኘው የኢትዮጵያ ስብስብ ጉድ አሁንም ቀጥሏል።

ለማረፊያ በተያዘላቸው ሆቴል ድልድል አንድ አትሌት የሀገሯን ልጅ ከእሷ ጋር አንድ አልጋ የምትጋራውን ሌላኛ አትሌት ጋር አብሬ መተኛት አልፈልግም በማለት ተጨማሪ ክፍያ ተከፍሎ ሌላ ክፍል እንድትይዝ መደረጉ ተሰምቷል።

ውጤት እና ሰላም በተመሳሳይ ጊዜ ለራቀው አትሌቲክሳችን ይህ በቀላሉ የሚታለፍ ነገር አይደለም።

 #የሚበርድ ጫማ ውስጥ ነው የምንቆመው:_አቶ ኢሳያስ ጂራ  #የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን ፕሬዚዳንት አቶ ኢሳያስ ጂራ በቀጣይ የኢትዮጵያ ፕረሰሜር ሊግ በአዲስ አበባ እንዲካሄድና የስፖርታ...
16/09/2025

#የሚበርድ ጫማ ውስጥ ነው የምንቆመው:_አቶ ኢሳያስ ጂራ

#የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን ፕሬዚዳንት አቶ ኢሳያስ ጂራ በቀጣይ የኢትዮጵያ ፕረሰሜር ሊግ በአዲስ አበባ እንዲካሄድና የስፖርታዊ ጨዋነትን ለማስፈን በተዘጋጀው መድረክ ጠንከር ያለ መልእክት አስተላልፈዋል።

#የፊፍ የስፖርታዊ ጨዋነት መርሆችን በሚያብራሩበት ወቅት ለተግባራዊነቱ ርብርብ ያስፈልጋል ብለዋል።

#በተለይ በዘንድሮ የውድድር ዘመን ውድድሩን በአዲስ አበባ እንዲካሄድ ስራዎች መጀመራቸው የሚታወስ ሲሆን ከተማ ውስጥ መካሄዱ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ እንዳለው አውስተዋል።

#ውድድሮች በስፖርታዊ ጨዋነት እንዲካሄዱ ከክለብ ደጋፊዎች፣ አመራሮች፣ እንዲሁ ሚዲያውም በርብርብ በመስራት ስጋቶችንን በማስወገድ ጥሩ የውድድር ጊዜ ማሳለፍ ይጠበቅብናል ብለዋል።

🇪🇹 የኢትዮጵያ ብስክሌት ፌዴሬሽን ለ2025 በሩዋንዳ 🇷🇼 ለሚካሄደው የአለም ብስክሌት ሻምፒዮና ውድድር ብሔራዊ ቡድኑን ወክለው የሚወዳደረውን ቡድን ይፋ አድርጓል።  #በሴቶችፅጌ ካህሳይ - ...
16/09/2025

🇪🇹 የኢትዮጵያ ብስክሌት ፌዴሬሽን ለ2025 በሩዋንዳ 🇷🇼 ለሚካሄደው የአለም ብስክሌት ሻምፒዮና ውድድር ብሔራዊ ቡድኑን ወክለው የሚወዳደረውን ቡድን ይፋ አድርጓል።

#በሴቶች

ፅጌ ካህሳይ - መስፍን
ራሄል ታመነ - መስፍን
አየሩ ሃፍቱ - መስፍን
ብርሃን ፍቃዱ - መቀሌ 70 እንደርታ
ሰርካለም ታዬ - መቀሌ 70 እንደርታ

አሰልጣኝ ተከስተ ጥላሁን - መስፍን

#በወንዶች

ተክሌ ጸጋይ - ትራንስ ኢትዮጵያ
ገ/መድህን ገ/ሄር - ትራንስ ኢትዮጵያ
ቡዙአየሁ ተስፉ - መስቦ ሲሚንቶ ፋብሪካ
ሰመር ወልደ - ጉና

አሰልጣኝ መሃሪ ዱሪ - ከትራንስ ኢትዮጵያ

መካኒክ ዳንኤል ገ/አምላክ - መስፍን

Ethio Cycling News

16/09/2025

🚨 Four huge moments for Liverpool in the premier League this season! 👏✨

▪️ 🇮🇹 Chiesa's Goal against Bournemouth
▪️ 🏴󠁧󠁢󠁥󠁮󠁧󠁿 Rio Ngumoha's Goal against Newcastle
▪️ 🇭🇺 Szoboszlai's Goal against Arsenal
▪️ 🇪🇬 Mo Salah's Goal against Burnley

You'll never walk alone! ❤️✨

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Team Talk Sport ቲም ቶክ ስፖርት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Team Talk Sport ቲም ቶክ ስፖርት:

Share