Capital

Capital Capital is the longest-established private English newspaper in Ethiopia Capital is the longest established private English newspaper in Ethiopia
(1)

12/12/2025

ራሚስ ባንክ የደንበኞቹን ቁጥር ወደ 352 ሺህ (93% ጭማሪ) ማድረሱንና 47 ቅርንጫፎችን መክፈቱን ሲገልጽ፣ በዲጂታል አገልግሎትም የዩኤስ-ኤስዲ ተጠቃሚዎችን በ1,802% በመጨመር እና የሞባይል ባንኪንግ አገልግሎቶችን በማስተዋወቅ ስራውን እያዘመነ እንደሚገኝ ታውቋል።

የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር፣ 13 የተመረጡ የገቢ ምርቶች ወደ ኢትዮጵያ ከመላካቸው በፊት በመነሻ ሀገር በቅድመ-ላኪነት ተስማሚነት ማረጋገጫ (PVoC) አሰራር አማካኝነት ጥራታቸው እን...
11/12/2025

የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር፣ 13 የተመረጡ የገቢ ምርቶች ወደ ኢትዮጵያ ከመላካቸው በፊት በመነሻ ሀገር በቅድመ-ላኪነት ተስማሚነት ማረጋገጫ (PVoC) አሰራር አማካኝነት ጥራታቸው እንዲረጋገጥ መወሰኑን አስታወቀ።

ሚኒስቴሩ በሕዳር 30 ቀን 2018 ዓ.ም ባወጣው እና ለብሔራዊ ባንክ በላከው ደብዳቤ ላይ በሀገር ውስጥ የላብራቶሪ ፍተሻ የማይችሉ 13 ምርቶች አስመጪዎች ምርቶቹ ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገቡ የግድ በውጪ የጥራት ተቆጣጣሪዎች የምስክር ወረቀት ማቅረብ እንዳለባቸው አረጋግጧል።

ይህ መመሪያ የሀገሪቱ የPVoC መርሃ ግብር ማብቃቱን ተከትሎ አዲስ የተደረገ የስምምነት ማደስ አካል መሆኑ ተጠቁሟል።

ይህ አሰራር ከሚተገበርባቸው ከ13 ምርቶች ዉስጥ የኤሌክትሪክ ዕቃዎች (ሰርክዩት ብሬከሮች፣ ጄኔሬተሮች፣ UPS)፣ የፀሐይ ኃይል ምርቶች፣ የእርሻ ትራክተሮች፣ የቤት ውስጥ ማቀዝቀዣዎች፣ ማጠቢያ ማሽኖች እና መጫወቻዎች ይገኙበታል።

ሚኒስቴሩ በውጭ ሀገር የጥራት ማረጋገጫ ለመስጠት እንዲቻል ከኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ጋር ስምምነት ካደረጉ አራት ዓለም አቀፍ እውቅና ካላቸው ተቆጣጣሪ አካላት ጋር መስራት ጀምሯል። እነዚህ ዓለም አቀፍ ተቆጣጣሪዎች ቢሮ ቬሪታስ ፣ ቲዩቪ ራይንላንድ ሚድል ኢስት ኤፍ.ዜድ.ኢ፣ ኮቴክና ኢን ስፔክሽን ኤስ.ኤ ፣ ዎርልድ ስታንዳርዳይዜሽን ሰርተፊኬሽን ኤንድ ቴስቲንግ ግሩፕ ይሰኛሉ።

ከ13 ምርቶች በተጨማሪ፣ ቀሪዎቹ 17 ምርቶች ወደ ኢትዮጵያ ከገቡ በኋላ በሀገር ውስጥ ባለው የጥራት መሰረተ ልማት ማለትም በኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት አማካኝነት አስፈላጊው የጥራት ማረጋገጫ ስራ እንዲከናወን ተወስኗል።

የዚህ ፖሊሲ ለውጥ ዋና ዓላማ ለተወሰኑ ምርቶች የሚደረገውን የጥራት ማረጋገጫ ከሀገር ውስጥ ላብራቶሪዎች ወደ አለም አቀፍ ተቆጣጣሪዎች ማዛወር ነው። ይህ እርምጃ የጉምሩክ አሰራርን ለማቅለል፣ እንዲሁም የኢትዮጵያ ሸማቾችን ከደረጃ በታች ከሆኑና አደገኛ ከሆኑ ምርቶች ለመጠበቅ ያለመ መሆኑን ለመረዳት ተችሏል።

11/12/2025

ህብረት ኢንሹራንስ የኢንሹራንስ አገልግሎት ወጪዎችን በመቀነስ ውጤቱን በ77.6% አሳድጓል። ኩባንያው በ2017 በጀት ዓመት ያስመዘገበው ከታክስ በፊት 1 ቢሊዮን ብር ትርፍ የኩባንያው ታሪክ ከፍተኛው ሆኗል።

የዓለም ጤና ድርጅት እንዳስታወቀው ፤ የዓለም ህዝብ ግማሽ ያህሉ አስፈላጊ የጤና አገልግሎት ማግኘት ያልቻለ በመሆኑ፣ ባህላዊ ሕክምና ለብዙ ሰዎች ቅርብ ወይም ብቸኛው የጤና አገልግሎት አማራጭ...
11/12/2025

የዓለም ጤና ድርጅት እንዳስታወቀው ፤ የዓለም ህዝብ ግማሽ ያህሉ አስፈላጊ የጤና አገልግሎት ማግኘት ያልቻለ በመሆኑ፣ ባህላዊ ሕክምና ለብዙ ሰዎች ቅርብ ወይም ብቸኛው የጤና አገልግሎት አማራጭ ሆኗል።

የድርጅቱ የዓለም አቀፍ የባህል ሕክምና ማዕከል ዳይሬክተር የሆኑት ሺያማ ኩሩቪላ ፣ በዚህ ወር በሚካሄደው የዓለም ጤና ድርጅት ዓለም አቀፍ የባህላዊ ሕክምና ጉባኤ ላይ አስመልክተው በሰጡት መግለጫ " የዓለም ጤና ድርጅት አባል አገራት በሰጡት መረጃ መሠረት፣ ከ 40 እስከ 90 በመቶ የሚሆነው ህዝባቸው ባህላዊ እና ተጓዳኝ ሕክምናን ለተለያዩ የጤና ችግሮች በስፋት እንደሚጠቀም ጠቁመዋል።

ባህላዊ ሕክምና በብዙዎች ዘንድ ተመራጭ የሆነበትን ምክንያት ሲያስረዱ ደግሞ፣ "በግል የተበጀ እና ሁሉን አቀፍ ስለሆነ እንዲሁም ከባህል ጋር የተጣጣመ በመሆኑ ነው፤ ይህም የተወሰኑ የበሽታ ምልክቶችን ብቻ ከማከም ይልቅ አጠቃላይ ደህንነትን ይደግፋል" ብለዋል።

ይሁን እንጂ፣ ይህ ሰፊ አጠቃቀም እና ተፈላጊነት ቢኖርም፣ በአሁኑ ወቅት ከ አንድ በመቶ በታች የሚሆነው ዓለም አቀፍ የጤና ምርምር በጀት ብቻ ለባህላዊ ሕክምና ድጋፍ እየተደረገለት መሆኑን ገልጸዋል።

የዓለም ባንክ ድጋፍ የተደረገለት አዲሱ ኢንስቲትዮት ወጣቶች ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ የአካውንቲንግ ማረጋገጫ በሀገራቸው እንዲያገኙ ያስችላል ተባለበዛሬዉ ዕለት በይፋ የተመረቀው የኢትዮጵ...
11/12/2025

የዓለም ባንክ ድጋፍ የተደረገለት አዲሱ ኢንስቲትዮት ወጣቶች ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ የአካውንቲንግ ማረጋገጫ በሀገራቸው እንዲያገኙ ያስችላል ተባለ

በዛሬዉ ዕለት በይፋ የተመረቀው የኢትዮጵያ የተመሰከረላቸው የሒሳብ ባለሞያዎች ኢንስቲትዩት (ETI-CPA) በዓለም ባንክ ስልታዊ ድጋፍ አማካኝነት ለኢትዮጵያ ወጣቶች አዲስ የሙያ መስኮችን እንደሚከፍት ተገለጸ።

ተቋሙ መመስረቱ የኢትዮጵያ የረዥም ጊዜ የኢኮኖሚ ዘመናዊነት እና ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት ጥረት ውስጥ ወሳኝ ምዕራፍ እንደሆነ የተገለጸ ሲሆን፣ በተለይም ወጣቶች ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ የአካውንቲንግ ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት በገዛ ሀገራቸው ውስጥ እንዲያገኙ ያስችላል ተብሏል።

የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ በተቋሙ ማስጀመሪያ ላይ እንደገለፁት ፣ ወጣት ባለሙያዎች ለመጀመሪያ ጊዜ በአገር ውስጥ፣ በተመጣጣኝ ወጪ እና ከአካባቢው ሀገራት ጋር ተወዳዳሪነት ባለው ሁኔታ ብቃታቸውን እንዲያሳድጉ ያስችላቸዋል።

"በዚህ ተቋም አማካኝነት ወጣቶቻችን ትርጉም ያለው ሥራ ለመገንባት፣ በአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና በሚመጡ ዕድሎች ለመሳተፍ እና ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚያዊ ሽግግር አስተዋፅኦ ለማድረግ የሚያስችሉ መሳሪያዎች ይኖራቸዋል" ሲሉ የገንዘብ ሚኒስትሩ ገልጿል።

የኢንስቲትዩቱ መመስረት ከተጀመረበት ጊዜ ጀምሮ የዓለም ባንክ ወሳኝ አጋር መሆኑ ተመስግኗል። ባንኩ "ከዚህ ተነሳሽነት ፅንሰ-ሀሳብ ጀምሮ ዲዛይን እና ተቋማዊ አደረጃጀት" ድረስ ስልታዊ ድጋፍ በማድረግ የቴክኒክና የፋይናንስ አስተዋፅኦው "እስከዚህ ታሪካዊ ወቅት ለመድረስ የማይተካ" እንደነበር ተገልጿል።

መንግስትም ለ ETI-CPA መቋቋም እና ዘላቂነት ያለውን ጠንካራ ቁርጠኝነት ገልጾ፣ ኢንስቲትዩቱ ሙሉ የሙያ ራስን በራስ ማስተዳደር ደረጃ እስኪደርስ ድረስ ለቀጣይ ሰባት ዓመታት አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጧል። ተቋሙ በአገሪቱ ውስጥ ከፍተኛ ስልጠና ያላቸውን ባለሙያዎች በማቅረብ በአለም አቀፍ ደረጃ የታመነ የፋይናንስ ስነ-ምህዳር ለመፍጠር እንደሚሰራ ተጠቁሟል።

https://www.youtube.com/watch?v=GA0uLWseU4w
11/12/2025

https://www.youtube.com/watch?v=GA0uLWseU4w

የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ግልጽነትን ለማረጋገጥ እና የገበያ ደንብን ለማሻሻል በሚያደርገው ጥረት፣ በውልና ኢንቨስትመንት እርሻ ሥር ለለሙ የወጪ ንግድ ሰብሎች የሚፈጸም ክፍ...

11/12/2025

የኢትዮ ጅቡቲ ምድር ባቡር ድርጅት በግንባታ መስክ ለሚያደርገው አዲስ የቢዝነስ ክንፍ የተለያዩ ልምድ እና ድጋፍ ለመጋራት ከግዙፉ የቻይና ኩባንያ CCECC ጋር ውል አሰረ።

ሁለቱ ኩባንያዎች በቀጣይ አምስት አመት በተለይ በጋራ አብረው ለመስራት ነው የወሰኑት። CCECC የኢትዮ ጅቡቲ የባቡር መስመርን በከፊን እንዲሁም የኢንደስትሪ ፓርኮችን ጨምሮ በርካታ ፕሮጀክቶችን የገነባ ነው።

ዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (አይኤምኤፍ) ከኢትዮጵያ ጋር በ3.4 ቢሊዮን ዶላር የተራዘመ የብድር ፋሲሊቲ መርሃግብር በአራተኛው ግምገማ ላይ በባለሞያዎች ደረጃ ስምምነት ላይ መድረሱን አስታው...
11/12/2025

ዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (አይኤምኤፍ) ከኢትዮጵያ ጋር በ3.4 ቢሊዮን ዶላር የተራዘመ የብድር ፋሲሊቲ መርሃግብር በአራተኛው ግምገማ ላይ በባለሞያዎች ደረጃ ስምምነት ላይ መድረሱን አስታውቋል።

ይህ ስምምነት የአይኤምኤፍ ሥራ አስፈፃሚ ቦርድ ሲያጸድቀው፣ ቀጣዩ የ261 ሚሊዮን ዶላር ክፍያ ለኢትዮጵያ እንዲለቀቅ መንገድ ይከፍታል። ይህ ክፍያ ሲፈጸም በአጠቃላይ በፕሮግራሙ ስር ለኢትዮጵያ የተሰጠው የገንዘብ ድጋፍ ወደ 2.13 ቢሊዮን ዶላር ከፍ ይላል።

የገንዘብ ተቋሙ ባወጣው መግለጫ፣ የኢትዮጵያ መንግሥት የጀመረውን የማክሮ ኢኮኖሚ ማረጋጋት እና የልማት ማሻሻያዎችን በመገምገም፣ “የተሃድሶውን ፍጥነት ማስቀጠል የማክሮ ኢኮኖሚ መረጋጋትን ለማጠናከር እና በመካከለኛ ጊዜ ዕድገትንና ድህነትን ለመቀነስ ቁልፍ ይሆናል” የሚል አስተያየት ሰጥቷል።

ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ በሐምሌ 2024 የድጋፍ ብድሩን ስትይዝ፣ ከባድ የውጭ ዕዳ መልሶ የማዋቀር ሥራ ላይ ትገኛለች። አይኤምኤፍ ባወጣው ሪፖርት፣ በG20 የጋራ ማዕቀፍ ስር የዕዳ ዘላቂነትን ለመመለስ የሚደረጉ ጥረቶች እየገፉ መሆናቸውን ጠቁሟል።

ተጨማሪ ያንብቡ (https://capitalethiopia.com/2025/12/11/imf/)

ከሁለት ዓመት በፊት በኢትዮጵያ ስደተኛ መጠለያዎች የእርዳታ ድጋፍ በመቀነሱ ምክንያት ወደ ሶማሊያ የተመለሱ በመቶዎች የሚቆጠሩ የሶማሊያ ቤተሰቦች በደቡባዊ ሶማሊያ በዶሎው/ጌዶ ክልል በሚገኘው...
11/12/2025

ከሁለት ዓመት በፊት በኢትዮጵያ ስደተኛ መጠለያዎች የእርዳታ ድጋፍ በመቀነሱ ምክንያት ወደ ሶማሊያ የተመለሱ በመቶዎች የሚቆጠሩ የሶማሊያ ቤተሰቦች በደቡባዊ ሶማሊያ በዶሎው/ጌዶ ክልል በሚገኘው በካባሶ ተፈናቃዮች መጠለያ ጣቢያ ውስጥ ከፍተኛ ችግር እየገጠማቸው መሆኑ ተዘግቧል።

ቀደም ሲል በኢትዮጵያ የእርዳታ ቅነሳን ሸሽተው የመጡት እነዚህ ቤተሰቦች፣ እዚህም በግንቦት ወር 2025 የገንዘብና የምግብ እርዳታዎች በመቋረጣቸው ምክንያት ያለ ምንም ድጋፍ መቅረታቸው ተገልጿል።

በሶማሊያ መንግስት እና በእርዳታ ድርጅቶች በኩል ይሰጥ የነበረው ድጋፍ እዚያም በመቆራረጡ፣ እነዚህ ቀደም ሲል በኢትዮጵያ የነበሩ ተመላሽ ቤተሰቦች ያለ ምንም እርዳታ ለረሃብና ለበሽታ መጋለጣቸውን አስረድተዋል።

እነዚህ ተፈናቃዮች በካባሶ መጠለያ ጣቢያ ከዚህ ቀደም ይተማመኑበት የነበረው የገንዘብና የምግብ እርዳታ በአጠቃላይ የገንዘብ እጥረት ምክንያት መቋረጡ፣ የኑሮ ሁኔታቸውን በእጅጉ አወሳስቦታል።

ራዲዮ ኤርጎ እንደዘገበው፤ ቤተሰቦች ለዕለት ምግብ በአካባቢው ነዋሪዎች ምፅዋት ላይ እንዲተማመኑ ተገድደዋል፤ ይህ ደግሞ በበርካታ ሕፃናት ላይ የተመጣጠነ ምግብ እጥረትን አስከትሏል።

ከባድ የረሃብና የውሃ እጦት ችግሮች አብረው የሚታዩ ሲሆን፣ የውሃ ዋጋ መክፈል ባለመቻላቸው አቅም የሌላቸው እናቶች ልጆቻቸውን ወደ ሩቅ ወንዝ በመላክ ለደህንነታቸው አሳሳቢ ሁኔታ ይፈጥራሉ።

በተጨማሪም፣ የትምህርት ክፍያ መክፈል ባለመቻላቸው በርካታ ሕፃናት ትምህርታቸውን አቋርጠዋል፣ እንዲሁም እርዳታ ላይ ተመስርቶ የነበረው ጥቂት የአነስተኛ ንግድ እንቅስቃሴም ገዢዎች ገንዘብ በማጣታቸው ፈርሷል ሲል ዘገባው አክሏል።

በሁለቱም ድንበሮች መካከል የሚገኙ እነዚህ የተፈናቃይ ቤተሰቦች፣ አፋጣኝ የምግብ፣ የውሃ እና የገንዘብ ድጋፍ ካልተደረገላቸው የወደፊት ሕይወታቸው አደጋ ላይ እንደወደቀ ተገልጿል።

ሳፋሪኮም ቴሌኮሙኒኬሽን ኢትዮጵያ በአፍሪካ ግዙፉ ባንክ ከሆነው ከስታንዳርድ ባንክ የ138 ሚሊዮን ዶላር (R2.4 ቢሊዮን) የገንዘብ ድጋፍ ማግኘቱ ተገለጸ። ይህ ፋይናንስ ኩባንያው በኢትዮጵያ...
10/12/2025

ሳፋሪኮም ቴሌኮሙኒኬሽን ኢትዮጵያ በአፍሪካ ግዙፉ ባንክ ከሆነው ከስታንዳርድ ባንክ የ138 ሚሊዮን ዶላር (R2.4 ቢሊዮን) የገንዘብ ድጋፍ ማግኘቱ ተገለጸ። ይህ ፋይናንስ ኩባንያው በኢትዮጵያ እያካሄደ ያለውን የዲጂታል መሠረተ ልማትና አገልግሎት ማስፋፊያ ሥራ ለማገዝ ያለመ መሆኑ ተጠቁሟል።

ስታንዳርድ ባንክ ለ ሳፋሪኮም የተሰጠው የብድር ፋሲሊቲ ብቸኛ አደራጅ፣ አበዳሪና ፋሲሊቲ ወኪል ሆኖ እንዲሁም የአማካሪነት ሚና መጫወቱን በሰጠው መግለጫ አሳውቋል።

ይህ ድጋፍ በኬንያ ትልቁ የቴሌኮሙኒኬሽን አቅራቢ የሆነው ሰፋሪኮም በኢትዮጵያ የቴሌኮም ገበያ ውስጥ ያለውን ተሳትፎ የበለጠ ለማጠናከር ያስችለዋል።

የቴሌኮሙኒኬሽን ኩባንያው በ2021 በኢትዮጵያ ውስጥ ለመሥራት ፈቃድ ያገኘ ሲሆን ስታንዳርድ ባንክ በአገሪቱ አገልግሎት ሲሰጥ እና አውታረ መረብ ሲዘረጋ አብረው ከሰሩት አማካሪዎችና ፋይናንስ አቅራቢዎች አንዱ እንደነበር መረጃዎች ያመለክታሉ።

የገንዘብ ሚኒስትር እና የአፍሪካ ልማት ባንክ የኢትዮጵያ–ጅቡቲ–ደቡብ ሱዳን ትራንስፖርት ኮሪዶር ፕሮጀክት – ምዕራፍ IIን ለመደገፍ የሚያስችል የ184 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር የዕርዳታ ስም...
10/12/2025

የገንዘብ ሚኒስትር እና የአፍሪካ ልማት ባንክ የኢትዮጵያ–ጅቡቲ–ደቡብ ሱዳን ትራንስፖርት ኮሪዶር ፕሮጀክት – ምዕራፍ IIን ለመደገፍ የሚያስችል የ184 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር የዕርዳታ ስምምነት ዛሬ መፈራረማቸው ተገልጿል።

ገንዘቡ በአዲስ አበባ–ጅቡቲ ኮሪዶር ላይ ወሳኝ የሆነውን የ67 ኪሎ ሜትር የፍጥነት መንገድ ከመልካ ጂሎ እስከ አዋሽ ድረስ ለመገንባት ያስችላል ተብሏል።

ይህ መስመር ከ90% በላይ የሚሆነውን የኢትዮጵያ የባህር ንግድ የሚይዝ በመሆኑ ለሀገሪቱ የሎጂስቲክስ ፍሰት፣ ለክልላዊ ትስስር እንዲሁም በአፍሪካ ቀንድ ያለውን የኢኮኖሚ ውህደት ለማጠናከር እጅግ አስፈላጊ መሆኑን ተመላክቷል።

ከሳምንታት በፊት የአፍሪካ ልማት ባንክ ቡድን በሦስቱ ሀገራት መካከል የንግድ ልውውጥን፣ ትስስርን እና ኢኮኖሚያዊ ዕድገትን እንደሚያሳድግ የሚጠበቀው የክልላዊ ውህደት መሪ ፕሮጀክት የሆነውን የደቡብ ሱዳን - ኢትዮጵያ - ጅቡቲ የትራንስፖርት ኮሪደር ፕሮጀክት ሁለተኛ ምዕራፍን ለማስጀመር 214.47 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር የገንዘብ ድጋፍ ማፅደቁ ይታወቃል።

የገንዘብ ድጋፉ ከአፍሪካ ልማት ባንክ በዝቅተኛ ወለድ መጠን የተገኘ ሲሆን ለኢትዮጵያ 181.5 ሚሊዮን ዶላር፣ ለጅቡቲ 29.71 ሚሊዮን ዶላር እና ለደቡብ ሱዳን 1.96 ሚሊዮን ዶላር የሚሆን የእርዳታ ድጎማዎችን እንደሚያካትት ካፒታል ዘግቦ ነበር።

ይህ ሁለተኛ ምዕራፍ ፕሮጀክት በኢትዮጵያ፣ የ67 ኪሎ ሜትር ፈጣን መንገድ ግንባታን እና የትራፊክ አስተዳደርን የሚያሻሽሉ ዘመናዊ የትራንስፖርት ስርዓቶች መዘርጋትን እንደሚደግፍ ተገልጿል። እንዲሁም ለገጠር ማህበረሰቦች ተደራሽነትን ለማሳደግ 50 ኪሎ ሜትር የሚረዝሙ የአካባቢ መንገዶችን ያሻሽላል ተብሏል።

ሁሉም ባንኮች አዲስ እና ነባር ሂሳቦችን ለማስተሳሰር ወደ VeriFayda 2 እንዲሸጋገሩ ተወሰነየኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እና የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም፣ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያን ከሁሉም...
10/12/2025

ሁሉም ባንኮች አዲስ እና ነባር ሂሳቦችን ለማስተሳሰር ወደ VeriFayda 2 እንዲሸጋገሩ ተወሰነ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እና የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም፣ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያን ከሁሉም ባንኮች የደንበኞች ሂሳብ ቁጥር ጋር የማጣመር ስራ በይፋ መጀመሩን አስታውቀዋል።

ይህ ውህደት የፋይናንስ ዘርፉን የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ጉዞ አንድ እርምጃ ወደፊት የሚያስኬድ ወሳኝ ምዕራፍ እንደሆነ ተመላክቷል።

የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ከሁሉም ባንኮች የደንበኞች ባንክ ሂሳብ ቁጥር ጋር የማጣመር (Harmonization) ስራ በይፋ መጀመሩን ተከትሎ፣ ባንኮች ቀደም ሲል ይጠቀሙበት የነበረውን VeriFayda 1 (old eKYC) ስርዓት ሙሉ በሙሉ ትተው ወደ ይበልጥ ዘመናዊ እና የተቀናጀው VeriFayda 2 እንዲሸጋገሩ ተወስኗል።

ተጨማሪ ያንብቡ https://capitalethiopia.com/2025/12/10/nbe/

Address

Bole Behind Rwanda Embassy
Addis Ababa
P.O.BOX95CODE1110

Telephone

+251116183253

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Capital posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Capital:

Share