Capital

Capital Capital is the longest-established private English newspaper in Ethiopia Capital is the longest established private English newspaper in Ethiopia
(1)

ኢትዮጵያ የ1 ቢሊዮን ዶላር የዩሮ ቦንድ ዕዳዋን ለማዋቀር በመርህ ደረጃ ስምምነት ላይ መድረሷ ተሰማየገንዘብ ሚኒስቴር፣ በፈረንጆቹ 2024 ሊከፈል የነበረውን 1 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር የዩሮ...
02/01/2026

ኢትዮጵያ የ1 ቢሊዮን ዶላር የዩሮ ቦንድ ዕዳዋን ለማዋቀር በመርህ ደረጃ ስምምነት ላይ መድረሷ ተሰማ

የገንዘብ ሚኒስቴር፣ በፈረንጆቹ 2024 ሊከፈል የነበረውን 1 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር የዩሮ ቦንድ ዕዳ መልሶ ለማዋቀር ከባለዕዳዎች ኮሚቴ ጋር በመርህ ደረጃ ስምምነት ላይ መድረሱን አስታወቀ።

ባለፉት አስር ቀናት ሲካሄድ የነበረው ዝግ ድርድር ፍሬያማ በሆነ መልኩ መጠናቀቁን ሚኒስቴሩ ገልጿል። በድርድሩ ላይ ከጠቅላላው የቦንድ ዕዳ ከ45 በመቶ በላይ የሚወክሉ ዓለም አቀፍ ተቋማዊ የቦንድ ባለቤቶች የተሳተፉ ሲሆን፣ በሁለቱም ወገኖች በኩል ሕጋዊና የፋይናንስ አማካሪዎች ተገኝተዋል።

ይህ በመርህ ደረጃ የተደረሰው ስምምነት በዋናነት በፋይናንስ ውሎች ላይ ያተኮረ መሆኑ ተገልጿል።

የስምምነቱ ዝርዝር ሁኔታዎች ለዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) እና ለይፋዊ አበዳሪዎች ኮሚቴ የተላከ ሲሆን፣ ይህም የኢትዮጵያ የረጅም ጊዜ የዕዳ ዘላቂነት እንዲረጋገጥና የአበዳሪዎች ይሁንታ እንዲገኝ ለማድረግ መሆኑ ተጠቁሟል።

መንግስት ከባለዕዳዎቹ ኮሚቴ ጋር በመተባበር የፋይናንስ ነክ ያልሆኑ ሌሎች ዝርዝር ጉዳዮች ላይ መስማማት እንደሚጠበቅባቸው አመልክቷል። ይህ ሂደት እንደተጠናቀቀ በፈረንጆቹ 2026 መጀመሪያ ላይ የዕዳ ሽግሽግ ሂደቱን ተግባራዊ ለማድረግ ቁርጠኝነት እንዳለው ገልጿል።

የኢትዮጵያ ግብርና ባለሥልጣን ከአሜሪካ በህይወት ያሉ ከብቶችን ፣ የአንድ ቀን ጫጩቶች እና የሚፈለፈሉ እንቁላሎችን ወደ አገር ውስጥ ለማስገባት የቀረበውን የገበያ ተደራሽነት ጥያቄ ማፅደቁን ...
02/01/2026

የኢትዮጵያ ግብርና ባለሥልጣን ከአሜሪካ በህይወት ያሉ ከብቶችን ፣ የአንድ ቀን ጫጩቶች እና የሚፈለፈሉ እንቁላሎችን ወደ አገር ውስጥ ለማስገባት የቀረበውን የገበያ ተደራሽነት ጥያቄ ማፅደቁን የአሜሪካ ግብርና መሥሪያ ቤት አስታወቀ።

ይህ ታሪካዊ የተባለለት የገበያ ፈቃድ የተረጋገጠው ታህሳስ 7 ቀን 2018 ዓ.ም ሲሆን፣ ይህም በሁለቱ አገራት መካከል ለዓመታት ሲካሄድ የቆየው የቴክኒክ ድርድር መጠናቀቁን የሚያመለክት መሆኑ ተጠቁሟል።

ባለፉት ጥቂት ዓመታት የአሜሪካ የእንስሳትና ዕፅዋት ጤና ምርመራ አገልግሎት ከኢትዮጵያ ግብርና ሚኒስቴር እና በቅርቡ ደግሞ ከኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን ጋር በቅርበት ሲሰራ መቆየቱ ተገልጿል።

የዚህ ትብብር ዋና ዓላማ ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ የእንስሳት ጤና የምስክር ወረቀቶችን ማዘጋጀት ሲሆን፣ አሁን ላይ ሰነዶቹ በመጽደቃቸው በህይወት ያሉ እንስሳትን ከአሜሪካ ወደ ኢትዮጵያ ለማጓጓዝ የሚያስችል ሙሉ ህጋዊ መሠረት ተጥሏል።

ቀደም ሲል አሜሪካ የበሬ ዘር እና ፅንስ ወደ ኢትዮጵያ ለመላክ ፈቃድ አግኝታ የነበረ ቢሆንም፣ አሁን የተገኘው ፈቃድ ግን በህይወት ያሉ እንስሳትን በቀጥታ ለማስገባት የሚያስችል በመሆኑ ለዘርፉ ትልቅ እመርታ ተደርጎ ተወስዷል።

ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት በ70 ሚሊዮን ከብቶች፣ 43 ሚሊዮን በጎች፣ 53 ሚሊዮን ፍየሎች እና በ57 ሚሊዮን የዶሮ ሀብት በአፍሪካ ቀዳሚዋ አገር ናት። ይሁን እንጂ ዘርፉ ለግብርናው አጠቃላይ ምርት (GDP) 45 በመቶ ድርሻ ቢኖረውም፣ በአገር በቀል ዝርያዎች ዝቅተኛ ምርታማነት፣ በመኖ እጥረት እና በደካማ የእንስሳት ጤና አገልግሎት ምክንያት አገሪቱ ከሀብቷ የሚጠበቀውን ያህል ተጠቃሚ መሆን አልቻለችም።

የኢትዮጵያ መንግስት በአሁኑ ወቅት "የሌማት ትሩፋት" በሚለው አገራዊ ንቅናቄ እና በብሔራዊ የወተትና የዶሮ ልማት ስልቶች (2022-2031) አማካኝነት የወተት ምርትን በአራት እጥፍ ለማሳደግ እና የዶሮ እርባታን ወደ ንግድ ስርአት ለመለወጥ እየሰራ ይገኛል።

ይህ ከሰሞኑ ከአሜሪካ ጋር የተደረገው አዲስ ስምምነትም የመንግስትን የልማት አቅጣጫ በቀጥታ የሚያግዝ መሆኑ ተገልጿል። ከፍተኛ ምርት የሚሰጡ የአሜሪካ ዝርያዎች ወደ አገር ውስጥ መግባታቸው፣ አርሶ አደሮችና ባለሀብቶች በትንሽ እንስሳት ቁጥር ከፍተኛ የወተትና የስጋ ምርት እንዲያገኙ ያስችላቸዋል።

በተለይም በዶሮ እርባታ ዘርፍ ጥራት ያላቸው የአንድ ቀን ጫጩቶች እና የሚፈለፈሉ እንቁላሎች እጥረት ለዘርፉ እድገት ትልቅ ማነቆ ሆኖ መቆየቱ ይታወቃል።

02/01/2026

በአዋጁ መሰረት በልማት ድርጅቶች ላይ የቦርድ ስብጥር ለማስተካከል ቋት/ፑል አዘጋጅተናል ፤
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ም/ዋና ስራ አስፈጻሚ ሀብታሙ ሃይለሚካኤል

For reliable and timely insights, grab Capital Newspaper now.Grab your copy today and make us a part of your Sunday ritu...
02/01/2026

For reliable and timely insights, grab Capital Newspaper now.
Grab your copy today and make us a part of your Sunday ritual.

For a full experience of on-time news update we invite you to follow us on our social media platforms:
Website: www.capitalethiopia.com
Tweeter: https://twitter.com/Capitaleth
Telegram: https://t.me/Capitalethiopia
Telegram English: https://t.me/capitalethiopiaenglish
Whatsup: https://whatsapp.com/channel/0029VbBgfwp77qVNTEpy5V0E
YouTube: https://www.youtube.com/channel/UCi82vwZxmMYK32a9pi0AgIQ
FB: https://www.facebook.com/capitalethiopia/
Instagram: https://www.instagram.com/capitalethiopia/
TikTok:https://www.tiktok.com/.newspaper

01/01/2026

የአዲስ አበባ ንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት የሪፎርም ስራዎችንና የፀረ-ሙስና ትግሉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገለጸ

የምክር ቤቱ ፕሬዚዳንት ወ/ሮ ዘሐራ መሐመድ እንደገለጹት፣ የንግዱ ማህበረሰብ በሙስና ምክንያት ተገቢውን ምላሽ አላገኘሁም በሚል ተስፋ የመቁረጥ ስሜት ውስጥ ቢቆይም፣ አሁን ላይ ተጠያቂነትን የማስፈን ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ።

የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ሙስናን ለመከላከል የሚያስችል “አደራ” የተሰኘ የዲጂታል የጥቆማ መድረክ ይፋ አደረገበአፍሪካ ግዙፍ ከሆኑ የሉዓላዊ ሀብት ፈንድ አንዱ የሆነው የኢትዮጵያ ...
01/01/2026

የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ሙስናን ለመከላከል የሚያስችል “አደራ” የተሰኘ የዲጂታል የጥቆማ መድረክ ይፋ አደረገ

በአፍሪካ ግዙፍ ከሆኑ የሉዓላዊ ሀብት ፈንድ አንዱ የሆነው የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ (ኢኢሆ)፣ በሚያስተዳድራቸው የመንግስት የልማት ድርጅቶች ውስጥ የሚስተዋሉ የሙስና እና ብልሹ አሰራሮችን ለመታገል ያለውን ቁርጠኝነት ገለጸ።

ሆልዲንግሱ ይህንን ተግባር በዘመናዊ መንገድ ለመፈጸም የሚያስችለውን “አደራ” (Adera) የተሰኘ የዲጂታል ጥቆማ መቀበያ ድረ-ገጽ እና መተግበሪያ በይፋ ስራ አስጀምሯል።

ይህ አዲስ መተግበሪያ በልማት ድርጅቶች ውስጥ ግልጽነትን እና ተጠያቂነትን ለማስፈን ያለመ መሆኑ ተጠቁሟል።

ተጨማሪ ያንብቡ (https://capitalethiopia.com/2026/01/01/eih/)

Stay informed with Capital Newspaper — your reliable source for Ethiopian business news, analysis, and weekly updates in...
01/01/2026

Stay informed with Capital Newspaper — your reliable source for Ethiopian business news, analysis, and weekly updates in print and online.

For a full experience of on-time news update we invite you to follow us on our social media platforms:
Website: www.capitalethiopia.com
Tweeter: https://twitter.com/Capitaleth
Telegram: https://t.me/Capitalethiopia
Telegram English: https://t.me/capitalethiopiaenglish
Whatsup: https://whatsapp.com/channel/0029VbBgfwp77qVNTEpy5V0E
YouTube: https://www.youtube.com/channel/UCi82vwZxmMYK32a9pi0AgIQ
FB: https://www.facebook.com/capitalethiopia/
Instagram: https://www.instagram.com/capitalethiopia/
TikTok:https://www.tiktok.com/.newspaper

https://www.youtube.com/watch?v=io9rbxTvh8s
31/12/2025

https://www.youtube.com/watch?v=io9rbxTvh8s

ፍሊፐር ትምህርት ቤት ውዝግብ፡ መምህራን አድማ ላይ፣ ቅርንጫፎች ይዘጋሉ? | የትምህርት ጥራት ስጋት"

30/12/2025

ህገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር በቴክኖሎጂ የታገዘና እጅግ ውስብስብ እየሆነ መምጣቱን ተከትሎ፣ ወጣቶች በማያውቁት መንገድ ለከፍተኛ አደጋ እየተጋለጡ ናቸዉ ተብሏል።

የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ሁሪያ አሊ እንዳሉት ፤ ወጣቶች በተለያዩ የዲጂታል አማራጮች እጅግ አሳማኝ በሚመስሉ የሥራ ቅጥር ማስታወቂያዎች አማካኝነት እንደሚታለሉ ተገልጿል።

https://youtu.be/y86pu1ahCr0
30/12/2025

https://youtu.be/y86pu1ahCr0

ዘምዘም ባንክ ውህደቱን ውድቅ አደረገ! | ​ከሒጅራ ጋር አንዋሃድም አለ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ለዘመናት ተግባራዊ ሲያደርግ የቆየውንና በሕግ ተወስኖ የነበረውን የ7 በመቶ ዝቅተኛ የቁጠባ ወለድ (Minimum Deposit Saving Rate) በማንሳት፣ ከዚህ በ...
30/12/2025

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ለዘመናት ተግባራዊ ሲያደርግ የቆየውንና በሕግ ተወስኖ የነበረውን የ7 በመቶ ዝቅተኛ የቁጠባ ወለድ (Minimum Deposit Saving Rate) በማንሳት፣ ከዚህ በኋላ የወለድ መጠን በገበያ ፍላጎትና አቅርቦት እንዲወሰን መወሰኑን አስታወቀ።

​ባንኩ ለመጀመሪያ ጊዜ ያስላለፈው ይህ ታሪካዊ ውሳኔ፣ ከሐምሌ 2016 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ እየተደረገ ያለውን በወለድ ላይ የተመሰረተ የገንዘብ ፖሊሲ ማዕቀፍ ይበልጥ ውጤታማ ለማድረግ ያለመ ነው።

እንደ ብሔራዊ ባንክ የገንዘብ ፓሊሲ ኮሚቴ መረጃ ከሆነ፤ ቀደም ሲል መንግስት ዝቅተኛውን የወለድ መጠን ወስኖ አስቀማጮች በከፍተኛው መጠን ላይ ብቻ እንዲደራደሩ የሚያደርገው አሰራር ተቀይሮ፣ አሁን ግን የወለድ ተመኑ በአስቀማጮች እና በባንኮች መካከል በሚደረግ ነፃ ድርድርና ስምምነት እንዲወሰን በባንኩ ቦርድ ጸድቋል።

​የዚህ ፖሊሲ ዋና ዓላማ በኢኮኖሚው ውስጥ የሚዘዋወረውን የገንዘብ መጠን በወለድ በኩል በመቆጣጠር የዋጋ ንረትን ለማረጋጋትና የባንኮችን የውድድር መንፈስ በማሳደግ ቁጠባን ለማበረታታት መሆኑ ተጠቁሟል።

ብሔራዊ ባንክ አክሎም፣ ጥብቅ የገንዘብ ፖሊሲው በዋጋ መረጋጋት ላይ ችግር እንደሚገጥመው በተረዳ ጊዜ ያሉትን የፖሊሲ መሣሪያዎች ሁሉ እንደሚጠቀም አስታውቋል።

የገንዘብ ፖሊሲው አሁን ላይ ከማላላት ይልቅ ይበልጥ ጥብቅ ያደረገዉ ኮሚቴዉ ባንኮች በብሔራዊ ባንክ ዘንድ እንዲያስቀምጡ የሚገደዱት ወርሃዊ አማካይ የመጠባበቂያ ክምችት ምጣኔ ከነበረበት በሁለት በመቶ በማደግ ወደ 10 በመቶ እንዲያድግ ተወስኗል። ዕለታዊ ዝቅተኛው የመጠባበቂያ ክምችት ግን በነበረበት 5 በመቶ እንዲቀጥል ተደርጓል።

Address

Bole Behind Rwanda Embassy
Addis Ababa
P.O.BOX95CODE1110

Telephone

+251116183253

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Capital posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Capital:

Share