Capital

Capital Capital is the longest-established private English newspaper in Ethiopia Capital is the longest established private English newspaper in Ethiopia

  ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ የሶስት አስርት ዓመታት ጉዞውን በአውደ ርዕይ ሊያሳይ ነውበኢትዮጵያ ኢኮኖሚ እና ማኅበራዊ ዘርፎች ውስጥ ለሦስት አስርት ዓመታት በኢትዮጵያ  ኢንዱስትሪዉ መዝለ...
16/08/2025

ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ የሶስት አስርት ዓመታት ጉዞውን በአውደ ርዕይ ሊያሳይ ነው

በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ እና ማኅበራዊ ዘርፎች ውስጥ ለሦስት አስርት ዓመታት በኢትዮጵያ ኢንዱስትሪዉ መዝለቅ የቻለዉ ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ፣ ስኬቶቹንና አሁን እየሰራቸውን ያሉ ሥራዎች የሚያሳ የአምስት ቀን አውደ ርዕይ ለማዘጋጀት በዝግጅት ላይ ነው።

ዝግጅቱ ከነሐሴ 26 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ የሚካሄድ ሲሆን፣ የድርጅቱን ሁለንተናዊ ተሳትፎ ለሕዝብ ለማስተዋወቅ ያለመ መሆኑን የድርጅቱ የኮርፖሬት ኮሙኒኬሽን ፕሮሞሽን ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ሁናቸው ታዬ በሰጡት መግለጫ አስታዉቀዋል።

ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ በሀገሪቱ ካሉ ታላላቅ የግል ተቋማት ውስጥ ግንባር ቀደሙ ነው። በግብርና፣ በማኑፋክቸሪንግ፣ በሆቴል፣ በአገልግሎትና በኮንስትራክሽን ዘርፎች ሰፊ ሥራዎችን በማከናወን ይታወቃል። እስካሁን ድረስ ከ74 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ኢትዮጵያውያን የሥራ ዕድል መፍጠር መቻሉ ተገልጿል።

መጪው 'ሚድሮክ ለሀገር!' በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀው ይህ የአውደ ርዕይ፣ የድርጅቱን ስኬቶች፣ ምርቶችና አገልግሎቶች ለሕዝቡ በቅርብ የሚያስተዋውቅ ሲሆን በተለይም ባለፉት አምስት ዓመታት እንደ አዲስ በመደራጀት የትርፍ ማስመዝገቡ አስታውቋል።

  | Respected Comrade Kim Jong Un Meets Speaker of State Duma of Russian FederationPyongyang, August 15 (KCNA) -- Kim Jo...
16/08/2025

| Respected Comrade Kim Jong Un Meets Speaker of State Duma of Russian Federation

Pyongyang, August 15 (KCNA) -- Kim Jong Un, general secretary of the Workers' Party of Korea and president of the State Affairs of the Democratic People’s Republic of Korea, met Byacheslav Volodin, speaker of the State Duma of the Russian Federation, who paid a congratulatory visit to the DPRK as the head of the delegation of the State Duma of the Russian Federation on the occasion of the 80th anniversary of Korea's liberation, in the afternoon of August 14.

The respected Comrade Kim Jong Un warmly greeted Byacheslav Volodin and had a friendly talk.

Volodin courteously conveyed the friendly greetings and congratulatory letter sent by Comrade Vladimir Vladimirovich Putin, president of the Russian Federation, to the respected Comrade Kim Jong Un on the occasion of the 80th anniversary of Korea's liberation.

Comrade Kim Jong Un expressed deep thanks to President Putin for sending warm congratulations.

Warmly welcoming the visit to Pyongyang by Volodin and the delegation of the State Duma of the Russian Federation, Kim Jong Un said that the visit would serve as an occasion for adding significance to the 80th anniversary of Korea's liberation, further promoting the development of the DPRK-Russia relations already on a new level and deepening the friendly and fraternal feelings between the peoples of the two countries.

He referred to the fact that two days ago he had a phone conversation with Comrade Putin and agreed to expand and develop the DPRK-Russia bilateral cooperation in an all-round way and keep closer contact and communication between the state leaderships.

Stressing the importance of the position and role of the two parliaments in strengthening the political and cooperative relations between the two countries and creating a political and legislative environment favourable for the development of bilateral relations, Kim Jong Un hoped that the parliaments in the two countries would make joint efforts to ensure that new interstate treaties and agreements are fully implemented in all fields.

Expressing heartfelt thanks to the DPRK for dispatching excellent soldiers to the Kursk liberation operations for driving out the Ukrainian aggressors and for taking many measures helpful to defending the sovereignty and territorial integrity of Russia, Byacheslav Volodin said that Russia would never forget the DPRK people and government who rendered decisive assistance at the most crucial time and the heroic feats performed by the service personnel of the Korean People's Army who fought at the cost of their lives in Russia.

Noting that the relations between the Russian Federation and the Democratic People's Republic of Korea made much progress and have been further consolidated thanks to the strategic leadership of the heads of state of the two countries, he expressed the will to make proactive efforts to activate exchange and cooperation between the parliaments of the two countries.

Conveying warm greetings of the DPRK government and people to the esteemed Russian President Vladimir Vladimirovich Putin and the Russian people, Kim Jong Un wished Byacheslav Volodin and all the deputies to the State Duma of Russia greater success in their legislative activities for ensuring the socio-political stability of the country and promoting the economic development and people's living.
The conversation proceeded in a warm and friendly atmosphere.

  የሲኖትራክ ተሽከርካሪዎች ወደ ኢትዮጵያ እንዳይገቡ ተከለከሉየትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ከሲኖትራክ ምርት ተሽከርካሪዎች ጋር ተያይዞ በታየው የጥራትና ቴክኒክ ጉድለት ምክንያት፣ ...
16/08/2025

የሲኖትራክ ተሽከርካሪዎች ወደ ኢትዮጵያ እንዳይገቡ ተከለከሉ

የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ከሲኖትራክ ምርት ተሽከርካሪዎች ጋር ተያይዞ በታየው የጥራትና ቴክኒክ ጉድለት ምክንያት፣ እነዚህ ተሽከርካሪዎች ወደ ኢትዮጵያ እንዳይገቡ እገዳ መጣሉን አሳውቋል።

ይህ ውሳኔ በሰዎች ህይወት ላይ በተደጋጋሚ አደጋ እየደረሰ በመሆኑ እንደተወሰነ ካፒታል ከሰርኩላር ደብዳቤ ላይ ተመልክቷል።

ሚኒስቴሩ በጉምሩክ ኮሚሽን በኩል ለጉምሩክ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቶች በሙሉ ባስተላለፈው መረጃ መሰረት፣ የሲኖትራክ ካምፓኒው የጥራት ጉድለቶቹን እስኪያስተካክል ድረስ ከግንቦት 27 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ምንም ዓይነት የሲኖትራክ ተሽከርካሪ ማስገቢያ ፍቃድ እንደማይሰጥ አስታውቋል።

ከዚህም ባሻገር፣ ሚኒስቴሩ ፊርማና ማህተም በማስመሰል የሲኖትራክ ማስገቢያ ፍቃድ በማዘጋጀት ተሽከርካሪዎችን ወደ አገር ውስጥ ለማስገባት የሚሞክሩ ሰዎች መኖራቸውን መረጃ እንዳገኘ ገልጿል።

ይህን ተከትሎ፣ ከግንቦት 27 ቀን 2017 ዓ.ም ወዲህ በሚኒስቴሩ የተሰጠ ምንም ዓይነት የሲኖትራክ ማስገቢያ ፍቃድ የሌለ መሆኑን በመግለጽ፣ እንዲህ ዓይነት ሰነድ ሲቀርብ አገልግሎት እንዳይሰጥና ጥቆማ እንዲደረግለት ለጉምሩክ ኮሚሽን ጥብቅ ማሳሰቢያ ሰጥቷል።

የጉምሩክ ኮሚሽንም ይህንኑ የሚኒስቴሩን ውሳኔ ለሁሉም የጉምሩክ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቶች በማስተላለፍ፣ የሲኖትራክ ተሽከርካሪዎች ወደ አገር ውስጥ እንዳይገቡ ጥብቅ ቁጥጥር እንዲደረግ አዟል።

በኢያሱ ዘካሪያስ

  ኢትዮጵያ የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጠናን ለመተግበር ለረዥም ጊዜ ሲጠበቅ የነበረዉን ደንብ አወጣችኢትዮጵያ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና (AfCFTA) ስምምነትን በይፋ ለመተግበር የ...
16/08/2025

ኢትዮጵያ የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጠናን ለመተግበር ለረዥም ጊዜ ሲጠበቅ የነበረዉን ደንብ አወጣች

ኢትዮጵያ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና (AfCFTA) ስምምነትን በይፋ ለመተግበር የሚያስችል ደንብ ማውጣቷን አስታውቃለች። በሚኒስትሮች ምክር ቤት የወጣው ደንብ ቁጥር 574/2017፣ ከአባል ሀገራት ወደ ኢትዮጵያ በሚገቡ ዕቃዎች ላይ የሚደረገውን የጉምሩክ ቀረጥ ቅነሳ በዝርዝር አስቀምጧል።

በነጋሪት ጋዜጣ በታተመዉ ደንብ መሰረት፣ ዕቃዎች በሶስት ምድቦች የተከፈሉ ሲሆን፣ ከ90% በላይ የሚሆኑት ዕቃዎች በ10 ዓመታት ውስጥ ቀስ በቀስ እየቀነሱ በመሄድ ሙሉ በሙሉ ከቀረጥ ነፃ ይሆናሉ። ሌላኛው የምድብ "ለ" ዕቃዎች ከ7% አይበልጡም፣ እነሱም ከ2026 ጀምሮ በ8 ዓመታት ውስጥ ከቀረጥ ነፃ ይሆናሉ።

የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጠና ታሪፍ ሰንጠረዥ ተፈጻሚ የሚሆንባቸውን አባል ሀገራት የሚገልጽ ሲሆን፣ የገንዘብ ሚኒስቴር ደግሞ የዕቃዎችን ምድብ የመለየት እና የማስተካከል ስልጣን ተሰጥቶታል። በተጨማሪም፣ የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን ለዕቃዎች የሥሪት ሀገር የምስክር ወረቀት ይሰጣል።

ይህ ደንብ ከነሐሴ 2017 ዓ.ም. ጀምሮ ተግባራዊ የተደረገ ሲሆን፣ የኢትዮጵያ ንግድ ከሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ጋር ይበልጥ እንዲቀላቀል እና አዲስ የንግድ እድሎችን እንዲፈጥር ይጠበቃል።

  የተጨማሪ እሴት ታክስ ምጣኔ ወደ 17 በመቶ እንዲያድግ ምክረ ሃሳብ ቀረበበኢትዮጵያ ዝቅተኛ የሆነውን የግብር ከጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት ጥምርታን ለማሻሻል በሚደረገው ጥረት፣ የሀገሪቱ ...
15/08/2025

የተጨማሪ እሴት ታክስ ምጣኔ ወደ 17 በመቶ እንዲያድግ ምክረ ሃሳብ ቀረበ

በኢትዮጵያ ዝቅተኛ የሆነውን የግብር ከጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት ጥምርታን ለማሻሻል በሚደረገው ጥረት፣ የሀገሪቱ የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ምጣኔን ከ15% ወደ 17.5% እንዲያድግ ምክረ ሃሳብ መቅረቡ ታወቀ።

ይህንን የግብር ምጣኔ ማሳደግ፣ የሀገሪቱን የግብር ገቢ በከፍተኛ ሁኔታ ሊያሳድግ እንደሚችል ተነግሯል።

የገንዘብ ሚኒስቴር እና የፊስካል ጥናት ተቋም (IFS) በጋራ ባዘጋጁት አዲስ ጥናት፣ የኢትዮጵያ የ15% የተጨማሪ እሴት ታክስ ምጣኔ ከብዙ የምስራቅ አፍሪካ እና የደቡብ ሰሃራ አፍሪካ ሀገራት ምጣኔዎች ጋር ሲነጻጸር ዝቅተኛ ነው።

ለምሳሌ፣ የኬንያ የ ተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ምጣኔ 16% ሲሆን፣ የሩዋንዳና የዩጋንዳ ደግሞ 18% ነው። የደቡብ ሰሃራ አፍሪካ ሀገራት አማካይ ምጣኔም 17.5% መሆኑን አመልክቷል።

ጥናቱ አክሎም፣ የ ተጨማሪ እሴት ታክስ ምጣኔን ወደ 17.5% ማሳደግ ብቻ ከጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት በተጨማሪ 0.4% ነጥቦችን ከ ተጨማሪ እሴት ታክስ ሊያስገኝ እንደሚችል ጠቁሟል።

ይህንንም ተግባራዊ ለማድረግ፣ ከዚህ በፊት ታክስ አልተሰበሰበባቸው የነበሩ እንደ ነዳጅ ያሉ ምርቶች ላይ ተጨማሪ እሴት ታክስ መሰብሰብ መጀመሩ ትልቅ አዎንታዊ እርምጃ ተደርጎ ተወስዷል።

"የኢትዮጵያ ታክስ-ለ-ጂ.ዲ.ፒ ምጣኔ፡ የማነፃፀሪያ ግምት እና የአፈጻጸም ትንተና" በሚል ርዕስ የተዘጋጀው ይህ ጥናት፣ የኢትዮጵያ የታክስ-ለ-ጂ.ዲ.ፒ ምጣኔ በ2022/23 በጀት ዓመት ወደ 7.5% ዝቅ ማለቱን ያሳያል።

ይህ ቁጥር በ2014/15 ከነበረው ከፍተኛው 12.4% ጋር ሲነፃፀር 4.9 በመቶ ነጥብ ቅናሽ አሳይቷል። ለዚህ ከፍተኛ የገቢ ቅናሽ ዋና ዋና ምክንያቶችም ዉስጥ ​መዋቅራዊ ለውጦች ፣​የፖሊሲ ልዩነቶች እና ​ዝቅተኛ የታክስ ተገዢነት መሆናቸውን በዝርዝር አስቀምጧል።

  Capital has been publishing public opinions for the last 25 years about popular culture and major events in Ethiopia. ...
15/08/2025

Capital has been publishing public opinions for the last 25 years about popular culture and major events in Ethiopia. This year we have selected 25 categories for our readers to answer questions ranging from your favorite actor in 2017 EC to who you think was the most capable politician of 2017 EC? Capital invites you to participate in this survey and help us create a unique profile of our country, the results of which shall be published in our forthcoming issue.

  Wegagen Bank secures $85 million international trade finance guarantee facilityWegagen Bank has secured an internation...
15/08/2025

Wegagen Bank secures $85 million international trade finance guarantee facility

Wegagen Bank has secured an international trade finance guarantee facility worth $85 million through agreements with the Eastern and Southern African Trade and Development Bank (TDB) and the African Export-Import Bank (Afreximbank).

This agreement strengthens Wegagen Bank’s strategic partnerships with global financial institutions and enhances its capacity to provide Letter of Credit (L/C) confirmations.

Read More (https://capitalethiopia.com/2025/08/10/wegagen-bank-secures-85-million-international-trade-finance-guarantee-facility/)

  Somali Forces Target Al-Shabaab Militants in Middle Shabelle OperationSomali government troops carried out a security ...
15/08/2025

Somali Forces Target Al-Shabaab Militants in Middle Shabelle Operation

Somali government troops carried out a security operation on Sunday near villages along the Shabelle River in the Middle Shabelle region, targeting al Shabaab militants accused of harassing local communities. The operation focused on the areas of Deegaanleey, Muryaale, and Ceelka Waranle, where militants had reportedly infiltrated and were engaged in extortion, looting, and intimidation of civilians.

Read More (https://capitalethiopia.com/2025/08/10/somali-forces-target-al-shabaab-militants-in-middle-shabelle-operation/)

  China’s Two Tales: Why 2025 Is a Year of Opportunity for InvestorsIn the investing world, China has long been a source...
15/08/2025

China’s Two Tales: Why 2025 Is a Year of Opportunity for Investors

In the investing world, China has long been a source of intense debate, often framed as a region of stark contrasts. On one side, Western headlines emphasize the challenges China faces: a softening property market, cautious consumers, and persistent geopolitical tensions. Yet on the ground, investors and industry insiders see a different reality—one of an economy reinventing itself through innovation, sustainability, and strategic growth sectors. As 2025 unfolds, the question for savvy investors is: which story holds more truth, and where does real opportunity lie?

Read More (https://capitalethiopia.com/2025/08/10/chinas-two-tales-why-2025-is-a-year-of-opportunity-for-investors-2/)

  ፕሪሚየር ስዊች ሶሉሽንስ እና ማስተርካርድ ደህንነቱ የተጠበቀ የኦንላይን ክፍያ አገልግሎት በኢትዮጵያ አስጀመሩፕሪሚየር ስዊች ሶሉሽንስ (PSS) እና ማስተርካርድ በኢትዮጵያ የመጀመሪያውን ...
14/08/2025

ፕሪሚየር ስዊች ሶሉሽንስ እና ማስተርካርድ ደህንነቱ የተጠበቀ የኦንላይን ክፍያ አገልግሎት በኢትዮጵያ አስጀመሩ

ፕሪሚየር ስዊች ሶሉሽንስ (PSS) እና ማስተርካርድ በኢትዮጵያ የመጀመሪያውን ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ የዲጂታል ክፍያ ማረጋገጫ ስርዓት ይፋ አደረጉ።

በEMV 3-D Secure (3DS) ቴክኖሎጂ ላይ የተመሠረተው ይህ አዲስ አገልግሎት፣ እየጨመረ የመጣውን የኦንላይን ክፍያ ማጭበርበር ስጋት ለመቀነስ እና የኢ-ኮሜርስ ንግድን ለማሳደግ ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑ ተገልጿል።

የPSS ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አምሃ ታደሰ፣ ይህ ስርዓት ለሀገሪቱ የዲጂታል ኢኮኖሚ ትልቅ ምዕራፍ መሆኑን ገልጸዋል። የማስተርካርድ ከፍተኛ ምክትል ፕሬዝዳንት ሸህሪያር አሊ በበኩላቸው፣ አገልግሎቱ የዲጂታል ሽግግርን ከማፋጠኑም በላይ፣ ደህንነቱ የተጠበቀ የፋይናንስ ሥነ-ምህዳር ለመፍጠር እንደሚረዳ ተናግረዋል።

አዲሱ ስርዓት ለነጋዴዎች፣ ለባንኮች፣ ለፊንቴክ ኩባንያዎች እና ለደንበኞች ከፍተኛ ጥቅም እንደሚሰጥም ተጠቅሷል።

Address

Bole Behind Rwanda Embassy
Addis Ababa
P.O.BOX95CODE1110

Telephone

+251116183253

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Capital posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Capital:

Share