ASER MEDIA

ASER MEDIA ASER MEDIA is a news and current affairs channel. follow us on Facebook, tiktok, and YouTube.

አሻም ስርጭቱን ሙሉ በሙሉ አቆመ---------የሚድያው መግለጫ እነሆ:-አሻም ሚዲያ ትሬዲንግ አክሲዮን ማህበር ከተመሰረተችበት ባለፉት 8 ዓመታት ጀምሮ በማህበራዊ ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ጉ...
10/12/2025

አሻም ስርጭቱን ሙሉ በሙሉ አቆመ
---------
የሚድያው መግለጫ እነሆ:-

አሻም ሚዲያ ትሬዲንግ አክሲዮን ማህበር ከተመሰረተችበት ባለፉት 8 ዓመታት ጀምሮ በማህበራዊ ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ጉዳዮች ዙሪያ በዜናና ወቅታዊ እንዲሁም በመዝናኛ ዝግጅቶች መረጃዎችን በቴሌቪዥን እና በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮቿ ስታደርስ ቆይታለች፡፡
ይሁን እንጂ አሻም ሚዲያ ትሬዲንግ አክሲዮን ማህበር ስራዋን ለመቀጠል አቅም ስለሌላት በቴሌቪዥንም ሆነ በየትኛውም የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮቿ ከዛሬ ታህሳስ 01 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ሙሉ በሙሉ በይፋ ስርጭት ማቆሟን ለማሳወቅ እንወዳለን፡፡

ስለሆነም ከተጠቀሰው ጊዜ ጀምሮ የአሻም ሚዲያ መታወቂያ በመያዝ ወይም የሚዲያዋን ሎጎ በመጠቀም በየትኛውም ሁነት (Event) ፣ በእቅድ ዜና ወይም ፕሮግራም ፣ በስልጠና መድረክ ፣ ቃለ-መጠይቅ እና በመሰል ጉዳዮች ላይ የሚገኙ (የሚሳተፉ) ባለሞያዎች የሚዲያ ተቋሙን እንደማይወክሉ ለሁሉም የግልና መንግስታዊ ተቋማት እንዲሁም ግለሰቦች ጭምር በትህትና ለማሳወቅ እንወዳለን፡፡

ባለፉት 8 ዓመታት ከአሻም ሚዲያ ትሬዲንግ አክሲዮን ማህበር ጋር አብራችሁ ለዘለቃችሁ ለውድ ተመልካቶቻችንና ተከታታዮቻችን ልባዊ ምስጋናችን ላቅ ያለ ነው፡፡

አሻም ለሁላችን!

ስምረት ሙሉ እውቅና አገኘ.....የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በአዋጅ በተሰጠው ሥልጣን መሠረት ለ“ዲሞክራሲያዊ ስምረት ትግራይ (ስምረት)" ሕጋዊ የክልላዊ ፖለቲካ ፓርቲነት ማረጋገጫ የምሥ...
09/12/2025

ስምረት ሙሉ እውቅና አገኘ.....
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በአዋጅ በተሰጠው ሥልጣን መሠረት ለ“ዲሞክራሲያዊ ስምረት ትግራይ (ስምረት)" ሕጋዊ የክልላዊ ፖለቲካ ፓርቲነት ማረጋገጫ የምሥክር ወረቀት ኅዳር 29 ቀን 2018 ዓ.ም. ሰጥቷል።

ሠራሕተኛታት መንግስቲ ትግራይ ደሞዝ ስለዘይተለቐቐ ናብ ቤት ዕዮ ከይኸዱ ተነጊሩዎም፡፡--------ሓጎስ ገብረህይወት ኣብ 1993 ዓ.ም “ኢዶእ” ኢሉ ዝደረፋ ደርፊ ሎሚ ክትስማዕ ዘለዋ ይመስ...
06/12/2025

ሠራሕተኛታት መንግስቲ ትግራይ ደሞዝ ስለዘይተለቐቐ ናብ ቤት ዕዮ ከይኸዱ ተነጊሩዎም፡፡
--------
ሓጎስ ገብረህይወት ኣብ 1993 ዓ.ም “ኢዶእ” ኢሉ ዝደረፋ ደርፊ ሎሚ ክትስማዕ ዘለዋ ይመስለኒ፡፡
“ተገረፍና ብክልተ ሓለንጊ” ኢሉ ነይሩ ሓጉሻ! ሎሚ ህዝቢ ትግራይ ብክልተ ሓለንጊ ይግረፍ ኣሎ ፤ ብህወሓትን በፌደራል መንግስትን፡፡ ዝበዝሓ ኣብያተ ዕዮ ትግራይ መሃያ ወርሒ ሕዳር ኣይከፈላን፡፡ ተኻርዮም ዝነብሩ ሰራሕተኛታት ኪራይ ገዛ ክኸፍሉ ኣይከኣሉን፡፡ ሓጎስ ገብረህይወት ኣብ ደርፉ ነቲ ሓቂ ከምዚ ክብል ገሊፅዎ ነይሩ!
“አለውታ ፅባሕ ዝሕተቱ
በዕፅምቲ ጀጋኑ ዝፃወቱ
ፍረ ቃልሲ ብርሃን ዘፀልመቱ
መን ክነብር ምስ ደመኛታቱ”
እዙይ ሎሚ ተዝሪኦም ደኣ እንታይ ምበለ ዘብል ኢዩ፡፡ ብዝኾነ ሓጉሻ ስራሕኻ ዝሰራሕኻ ብኣጋ ኢዩ ነይሩ ሰማዒ ኣይተረኸበን እምበር - ብሰላም ዕረፍ!

ሓዱሽ መንገዲ ቃልሲ መንግስቲ ፌደራል---------ትግራይ ኣብ ሕድሕዳዊ ምቁርቛስ ኣትያ ሒግ ክትብል ከላ: ባዕላ ንባዕላ ተዳኽመሉ ጥጡሕ ባይታ ኢዩ። እዙይ ውድቀት ትግራይ ንዝደሊ ዝኾነ ሓይ...
05/12/2025

ሓዱሽ መንገዲ ቃልሲ መንግስቲ ፌደራል
---------
ትግራይ ኣብ ሕድሕዳዊ ምቁርቛስ ኣትያ ሒግ ክትብል ከላ: ባዕላ ንባዕላ ተዳኽመሉ ጥጡሕ ባይታ ኢዩ። እዙይ ውድቀት ትግራይ ንዝደሊ ዝኾነ ሓይሊ ብናፃ (ብዘይመስዋእትን ወፃኢን) ዓብዪ ዓወት ምዕታር ኢዩ።
እቲ ካልኣይን ሓዱሽን ሜላ ነተን ውሑዳት ዝጥቀሙለን ብሽም ህዝቢ ትግራይ ዝተጣየሻ ትካላት ትእምት ሓኒቕካ ምሓዝ ኢዩ። ከም በዓል ሞንጆሪኖ ዝበላ ላዕለዎት ኣመራርሓ (ደቂ ኣነስትዮ) ዝመርሓኣ ኣደዳይ ማይክሮ ፋይናንስን: ኣብ ኢትዮጵያ ዳርጋ ፈላመይቲ ቅድሚ ትካል ልቃሕን ዕቋርን ዝኾነት ደደቢትን እውን ኣብ ዓይኒ መንግስቲ ኣትየን አለዋ።
ደደቢት ከም ትካላት ትእምት ኔትወርክ - ኣዊ መሓውር ዝሓላለኻ: ብድሕሪኣ ዝተጣየሻ ተመሳሰልቲ ትካላት:-
አማራ ብድርና ቁጠባ ተቋም (አብቁተ) ናብ ጸደይ ባንክ
አዲስ ብድርና ቁጠባ ናብ ስኬት ባንክ...
ካልኦት እውን ብተመሳሳሊ ናብ ባንክ እንትዓብያ ደደቢት ንገባር ንተስካርን መርዓን ከይተረፈ እናለቀሐት ከምኣ ኢላ ተሪፋ ኣላ።
ትካላት ትእምት ሒሳበን ምእጋዱ ኣብቶም ብረሃፆም ዝነብሩ ሰራሕተኛታት ዘሔድሮ ፅዕንቶ ቀሊል ከምዘይኮነ እኳ እንተተፈለጠ ብዙሕ ከደንግፅ ኣይከኣለን። ምኽንያቱ ድማ እተን ትካላት ውሑዳት ሰባት ጥራሕ ከምዝጥቀሙለን ስለዝፍለጥ ኢዩ።
ብዝኾነ ከልቢ ብዝኸፈቶ ፈጫው ዝብኢ ይኣቱ ኮይኑ መራሕቲ ትግራይ ንስልጣንን ወርቂን ክዋረሩ ዝኸፈትዎ ፈጫው መእተዊ ኣዜብእ ኮይኑ።

ኣብ ትግራይ ፀገም ኣሎ። ፀገም የለን እናበልካ ምሽፍፋን ''የትም ኣያደርስም''! ትግራዋይ ፀገም ኣሎ ትግራዋይ መፍትሒ ዘድሎዮ! ደጋዊ ፀገም ምግባር ኣይጠቅም ምሽፍፋን አይጠቅም!
05/12/2025

ኣብ ትግራይ ፀገም ኣሎ። ፀገም የለን እናበልካ ምሽፍፋን ''የትም ኣያደርስም''! ትግራዋይ ፀገም ኣሎ ትግራዋይ መፍትሒ ዘድሎዮ! ደጋዊ ፀገም ምግባር ኣይጠቅም ምሽፍፋን አይጠቅም!

የኤርትራ መንግሥት ያለፍርድ ለ18 ዓመታት አስሯቸው የነበሩ 13 ሰዎችን ለቀቀ______የኤርትራ መንግሥት በወታደራዊ እስር ቤት ያለ ፍርድ ለ18 ዓመታት ያህል አስሯቸው የነበሩ 13 ሰዎችን ...
05/12/2025

የኤርትራ መንግሥት ያለፍርድ ለ18 ዓመታት አስሯቸው የነበሩ 13 ሰዎችን ለቀቀ
______
የኤርትራ መንግሥት በወታደራዊ እስር ቤት ያለ ፍርድ ለ18 ዓመታት ያህል አስሯቸው የነበሩ 13 ሰዎችን መልቀቁን ቤተሰቦቻቸው ለቢቢሲ ትግርኛ ተናገሩ።

አስራ ሦስቱ ግለሰቦች ታስረው የነበረው በአስቸጋሪ አነወኗር ማይ ስርዋ ተብሎ በሚጠራ ጥብቅ ቁጥጥር በሚደረግበት ወታደራዊ እስር ቤት ነው።

ከእስር የተለቀቁት ሰዎች ነጋዴዎች፣ የፖሊስ አባላት እንዲሁም በተለያየ የሙያ ዘርፎች ላይ ተሰማርተው የነበሩ ባለሙያዎች ሲሆኑ፣ ያለ ምንም ማብራሪያ ሐሙስ ኅዳር 25/2018 ዓ.ም. ተለቀው ከቤተሰባቸው ጋር ተቀላቅለዋል።

በማይ ስርዋ ወታደራዊ እስር ቤት ታስረው የነበሩ እና ስማቸው እንዳይገለጽ የጠየቁ አንድ ግለሰብ ለቢቢሲ ትግርኛ እንደተናገሩት ጥቅምት 2000 ዓ.ም. ላይ በወቅቱ የአገር ውስጥ ደኅንነት ኃላፊ ከነበሩት ከኮሎኔል ስምኦን ገብረድንግል የግድያ ሙከራ ጋር ተያይዞ በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን ገልፀዋል።

አክለውም የተያዙት ከሁለት ነጋዴዎች ጋር በተያያዘ መሆኑን አብራርተዋል።

መጀመሪያ ላይ 30 የሚሆኑ ሰዎች በቁጥጥር ሥር ውለው የነበረ ሲሆን፣ የተወሰኑት ከዓመታት እስር በኋላ ተለቅቀው 20ዎቹ ብቻ በአስቸጋሪው እስር ቤት ውስጥ ቆይተዋል።

ከተለቀቁት መካከል የቀድሞው የኦሊምፒክ ብስክሌተኛ እና ነጋዴ ዘርአግብር ገብረሕይወት፣ በንግድ ሥራቸው ታዋቂ የሆኑት ተስፋለም መንግሥተአብ እና በኩረ መብርሃቱ እንዲሁም ኢንጂነር ዳዊት ኃብተማሪያም እና ማቲዮስ ኃብተማሪያም የተባሉ ሁለት ወንድማማቾች ይገኙበታል።
በተጨማሪም ስድስት ነባር የኤርትራ ፖሊስ አባላት ሁለት አስርት ዓመታት ለሚጠጋ ጊዜ ከቆየው እስር በኋላ ከተለቀቁት መካከል ናቸው።

አቶ ታዬ ደንደአ የሰባት ዓመት ከሁለት ወር እስር ተፈረደባቸው::___የቀድሞው የሠላም ሚኒስትር ዴኤታ እና የኦሮሚያ ምክር ቤት አባል አቶ ታዬ ደንደአ ጥፋተኛ በተባሉበት ክስ የሰባት ዓመት ...
05/12/2025

አቶ ታዬ ደንደአ የሰባት ዓመት ከሁለት ወር እስር ተፈረደባቸው::
___
የቀድሞው የሠላም ሚኒስትር ዴኤታ እና የኦሮሚያ ምክር ቤት አባል አቶ ታዬ ደንደአ ጥፋተኛ በተባሉበት ክስ የሰባት ዓመት ከሁለት ወር እስር ተፈረደባቸው።

አቶ ታዬ ዛሬ አርብ ኅዳር 26/2018 ዓ.ም. የቅጣት ውሳኔ የተላለፈባቸው በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ የሕገ መንግሥት እና በሕገ መንግሥት ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎች ችሎት ጥፋተኛ በተባሉበት ሕገወጥ የጦር መሣሪያ ይዞ በመገኘት ነው።

የመንግሥት ከፍተኛ ባለሥልጣን እና የክልል ምክር ቤት አባል የነበሩት አቶ ታዬ ሕገ ሕገ ወጥ የጦር መሣሪያ ይዞ በመገኘት እንዲሁም ፍቃድ ሳይኖራቸው በቤታቸው ውስጥ አንድ ታጣፊ ክላሽንኮቭ ጠመንጃ ከ60 ጥይቶች ጋር ተገኝቷል በሚል ክስ ቀርቦባቸው ነበር።

የአቶ ታዬ ጠበቃ "መስማት የነበረባቸው ሦስት የመከላከያ ምስክሮች ነበሩ፤ እነርሱ ሳይሰሙ ቀርተዋል። የፍርድ ቤቱን ውሳኔ እናከብራለን ነገር ግን ቅሬታዎች አሉን" ሲሉ ለቢቢሲ አፋን ኦሮሞ ተናግረዋል።

ዐቃቤ ሕግ እና ተከሳሹ አቶ ታዬ ደንደአ ከቤታቸው በተገኘ ሕገወጥ የጦር መሣሪያ ክስ ላይ ሲከራከሩ የቆዩ ሲሆን፣ በክርክሩ ወቅት ዐቃቤ ሕግ ሁለት ምስክሮች አቅርቦ አስመስክሯል።

አቶ ታዬ የፌደራል ፖሊስ ምክትል ኮሚሽነር መላኩ ፈንታን ጠባቂዎቻቸው መልቀቃቸውን በመጥቀስ 'የደኅንነት ስጋቶች' ስላለባቸው መሣሪያ እንዲሰጣቸው መጠየቃቸውን ለፍርድ ቤቱ ገልጸው ኮሚሽነሩ መሣሪያ ይሰጠኝ የሚለውን ለጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ደብዳቤ እንዲጽፉ እንደነገሯቸው ገልጸዋል።

ከዚያም በወቅቱ የሰላም ሚኒስቴር ሚኒስትር የነበሩት እና አሁን በአሜሪካ የኢትዮጵያ አምባሳደር የሆኑትን አቶ ቢናልፍ አንዷለምን ደብዳቤ እንዲጽፉላቸው መጠየቃቸውን ለችሎቱ አስረድተዋል።

ይሁን እንጂ ደብዳቤ ከመጻፍ ይልቅ በቃል ይሻላል ተብሎ የሚፈልጉትን ጦር መሣሪያ እንዲታጠቁ ከስምምነት ላይ መድረሳቸውን ተናግረዋል።

በማርበርግ ቫይረስ ምክንያት ከዛሬ ሕዳር 20 ጀምሮ የትራንስፖርት አገልግሎት ተቋርጧል፡፡------------------------------በጂንካ ተከስቶ ለሰዎች ሞት ምክንያት እየሆነ ያለዉን ...
29/11/2025

በማርበርግ ቫይረስ ምክንያት ከዛሬ ሕዳር 20 ጀምሮ የትራንስፖርት አገልግሎት ተቋርጧል፡፡
------------------------------
በጂንካ ተከስቶ ለሰዎች ሞት ምክንያት እየሆነ ያለዉን የማርበርግ ቫይረስ ስርጭትን ለመቆጣጠር ያስችል ዘንድ ወደ በሽታዉ መነሻ የአሪ ዞን የሚገባም ሆነ የሚወጣ የትራንስፖርት እንቅስቃሴ ለ1 ሣምንት ዝግ እንዲሆን በአሪ ዞን ዋና አስተዳዳሪ የሚመራ ግብር ሃይል መወሰኑን የዞኑ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን መምሪያ ኃላፊ አቶ ደምመላሽ አቦነህ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል። ‎የቫይረሱ ስርጭት ከዕለት እለት አስከፊ እየሆነ በመምጣቱ የበሽታውን ስርጭት ለመቆጣጠር በአሪ ዞን ዋና አስተዳዳሪ የሚመራ ግብረሀይል ተቋቁሞ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

ኃላፊዉ እስካሁን በነበረው ሂደት ትምህርት ቤቶች የተዘጉና ፣ ሕዝብ የሚሰበሰብባቸዉ ጉዳዮች ላይ እቀባ የተጣለ ቢሆንም ስርጭቱን በሚፈለገዉ ልክ መግታት ባለመቻሉ የትራንስፖርት ዘርፉን ለ1 ሳምንት መዝጋት አስፈላጊ በመሆኑ ከዛሬ ህዳር 20/2018ዓም ጀምሮ ለ1 ሳምንት ዝግ እንዲሆን ግብረሀይሉ መወሰኑን ተናግረዋል።‎ጂንካ ከተማን ጨምሮ ለሁሉም መዋቅር የትራፊክ ፍሰት እና የፀጥታ ዘርፍ አስተባባሪዎች ይህ መልዕክት መተላለፉንም አቶ ደምመላሽ አስታዉቀዋል። ‎በዚህ መሰረት ከክልል በወረደው አቅጣጫ መሰረት አገር አቋራጭ የህዝብ ትራንስፖርት ለ1 ሳምንት የታገደ ሲሆን በከተማ የሁለት እግር ተሽከርካሪዎችና የታክሲ አገልግሎት የሚሰጡ ተሽከርካሪዎች ብሎም በዞኑ ውስጥ የሚኖሩ የትራንስፖርት እንቅስቃሴዎች በቀጣይ ቀናት ውስጥ ውሳኔ እንደሚሰጥባቸው ገልፀዋል። ‎ኃላፊው አያይዘውም በአሁኑ ወቅት የማርበርግ በሽታ በአሪ ዞን ጂንካ ከተማ የተከሰተ ቢሆንም ጂንካ ለቅሶ መጥቶ የተመለሰ የሀዋሳ ከተማ ነዋሪ በበሽታዉ መሞቱን መስማታቸዉንና የስርጭት መጠኑን ለመቀነስ ብሎም ለመቆጣጠር ዉሳኔዉ መተላለፉን በመግለፅ በዞኑም ሆነ ከዞኑ ዉጪ ያለ ሕብረተሰብ ይህን ተግባራዊ እንዲያደርግ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል አሳስበዋል።

#ቲክቫህ ኢትዮጵያ

ኖርዌይ የኤርትራ መንግሥትን ለሚደግፉ ኤርትራውያን የሰጠችውን ዜግነት እንደምትነጥቅ አስታወቀች--------ኖርዌይ የኤርትራን መንግሥት የሚደግፉ ትውልደ ኤርትራውያንን ዜግነት እንደምትነጥቅ አ...
29/11/2025

ኖርዌይ የኤርትራ መንግሥትን ለሚደግፉ ኤርትራውያን የሰጠችውን ዜግነት እንደምትነጥቅ አስታወቀች
--------
ኖርዌይ የኤርትራን መንግሥት የሚደግፉ ትውልደ ኤርትራውያንን ዜግነት እንደምትነጥቅ አስታወቀች።
የኖርዌይ የስደተኞች አገልግሎት ተቋም እንዳለው፤ ለሁለት ዓመታት ምርመራ ካደረገ በኋላ የኤርትራን መንግሥት የሚደግፉ ኖርዌጅያን-ኤርትራውያንን ዜግነት ለመንጠቅ ወስኗል። የኖርዌይ ዜግነት የተሰጣቸው ኤርትራውያኑ ለኤርትራ መንግሥት ድጋፍ ይሰጣሉ ያለው አምስት አባላት ያሉት መርማሪ ኮሚቴ ነው። 135 ኤርትራውያን ላይ ምርመራ ያደረገ ሲሆን፤ ማኅበራዊ ሚዲያ ላይ የሚጽፉትን እንዲሁም ሌሎች ሰዎች ስለ እነሱ የሚናገሩትን ተከታትሏል። ምርመራ የተደረገባቸው 135 ሰዎች የኖርዌይ ዜግነት የተሰጣቸው ሲሆኑ፤ ላለፉት ስምንት ዓመታትም በአገሪቱ ኖረዋል። እስካሁን ድረስ 20 ሰዎች መኖሪያ ፈቃዳቸውን ሲነጠቁ፤ የሌሎች 30 ሰዎች ጉዳይ ደግሞ እየተመረመረ ነው። በአጠቃላይ ምን ያህል ሰዎች ዜግነታቸውን እንደሚነጠቁ ግልጽ አይደለም። በኖርዌይ ሕግ መሠረት፤ በአገሪቱ ጥገኝነት የጠየቁ ሰዎች የሚሰጣቸው የመኖሪያ ፈቃድ ወይም ዜግነት ሊነጠቅ ይችላል። የመኖሪያ ፈቃድ ወይም ዜግነት የተሰጣቸው ስደተኞች አንዳች ስህተት ከተገኘባቸው ውሳኔው ሊቀለበስ እንደሚችል ሕጉ ይደረግጋል። የኖርዌይ መንግሥት የትውልደ ኤርትራውያንን የመኖሪያ ፈቃድ ወይም ዜግነት ሲነጥቅ የአሁኑ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው። ኤርትራውያን በትውልድ አገራቸው ሳሉ ለግዳጅ ውትድርና፣ ለእስራት፣ ለብዝበዛ እና ለስቅይት እንደሚጋለጡ በመጥቀስ በኖርዌይ ጥገኝነት ከጠየቁ በኋላ ለኤርትራ መንግሥት ድጋፍ እንደሚሰጡ ተገልጿል። የኖርዌይ የስደተኞች አገልግሎት ተቋም እንዳለው፤ ኤርትራውያኑ ለኖርዌይ መንግሥት የገለጿቸው የግዳጅ ብሔራዊ ውትድርና፣ የሰብአዊ መብት ጥሰት እና እስራት ትክክለኛ አይደሉም። የኖርዌይ መንግሥት ምርመራ የከፈተው በኤርትራ መንግሥት ደጋፊዎች እና ተቃዋሚዎች መካከል ከሁለት ዓመታት በፊት በተነሳው ግጭት ምክንያት ነው። በዚህ ግጭት ውስጥ ተሳታፊ ከነበሩ ኤርትራውያን አንዱ እአአ በ2013 በኖርዌይ ጥገኝነት ያገኘ ግለሰብ ነው።
የኖርዌይ የስደተኞች አገልግሎት ተቋም እንዳለው፤ ትውልደ ኤርትራውያኑ ላይ የተካሄደው ምርመራ በዋነኛነት ያተኮረው ለመንግሥት ድጋፍ በሚሰጡት ላይ ነው። በኦስሎ እና በርገን ከተሞች በመዘዋወር ምርመራውን ያካሄደ ሲሆን፤ በርገን ከዚህ ቀደም በኤርትራ መንግሥት ደጋፊዎች እና ተቃዋሚዎች መካከል ግጭት የተከሰተባት ከተማ ናት። የኤርትራን መንግሥት የሚደግፉ ስደተኞች ላይ ምርመራ ከተከፈተ በኋላ ተቋርጦ የነበረ ሲሆን፤ በድጋሚ ምርመራው መጀመሩ ተገልጿል። ከአውሮፓውያኑ አዲስ ዓመት በኋላ የኤርትራውያኑ ይግባኝ እንደሚታይ የኖርዌይ የስደተኞች አገልግሎት ተቋም አስታውቋል።
በምርመራው ወቅት ስደተኞቹ ለምን የጥገኝት ጥያቄያቸው ተቀባይነት አገኘ? ለምን የሸሹትን መንግሥት ይደግፋሉ? የሚሉትም መፈተሻቸው ተገልጿል። መርማሪ ቡድኑ ከማኅበራዊ ሚዲያ ጽሑፎች በተጨማሪ ኖርዌይ ከሚኖሩ እና የኤርትራን መንግሥት ከሚቃወሙ ትውልደ ኤርትራውያን ጥቆማ ሰብስቧል።
ለጥገኝነት ጥያቄ የተሳሳተ መረጃ ያቀረቡ ስደተኞች የመኖሪያ ፈቃድ እና ዜግነትም ሊሰረዝ ይችላል።
ወደ እስራኤል በሕገ ወጥ መልኩ የገባ እና የኤርትራ መንግሥትን በመደገፍ ይታወቃል የተባለ ኤርትራዊ ባለፈው ወር ወደ አገሩ መባረሩን የእስራአል መገናኛ ብዙኃን መዘገባቸው ይታወሳል።
እስራኤል የኤርትራ ዜግነት ያለው እና የመንግሥት ደጋፊ የሆነን ግለሰብ ከአገሯ ስታባርር ለመጀመሪያ ጊዜ ነው። የአንድ ልጅ አባት የሆነው ኤርትራዊ ወደ እስራኤል የገባው በአውሮፓውያኑ 2011 ሲሆን፤ ላለፉት 14 ዓመታት ኑሮውን በዚያው አድርጎ ቆይቷል። እአአ በ2023 በእስራኤል መዲና ቴል አቪቭ በኤርትራውያን መካከል በተከሰተ ግጭት እስራኤላዊ ፖሊስን ጨምሮ 150 ሰዎች መጎዳታቸው ይታወሳል። የኤርትራ መንግሥት ደጋፊዎች እና ተቃዋሚዎች ጎራ ለይተው በተሳተፉበት ግጭት 11 ሰዎች በጥይት ተመትዋል። እአአ በ2024 በነተሳ ግጭት ደግሞ ሁለት ሰዎች ሲገደሉ ስምንት ሰዎች ክፉኛ መቁሰላቸው አይዘነጋም።

(ዘገባው የቢቢሲ አማርኛ ነው)

“ዘይሓወየን ኣብ ስቓይን  ዘሎ ህዝብና ዳግም ናብ ዘይደልዮ ኣዕናዋይ ኩናት ከይኣቱ ክንሰርሕን ኢና።”  ፕረዚደንት ለ/ ጀነራል  ታደሰ ወረ-------ፕረዚደንት ታደሰ ወረደ ናይ ሕሉፍ ርብዒ...
28/11/2025

“ዘይሓወየን ኣብ ስቓይን ዘሎ ህዝብና ዳግም ናብ ዘይደልዮ ኣዕናዋይ ኩናት ከይኣቱ ክንሰርሕን ኢና።”
ፕረዚደንት ለ/ ጀነራል ታደሰ ወረ
-------
ፕረዚደንት ታደሰ ወረደ ናይ ሕሉፍ ርብዒ ዓመት ኣፈፃፅማ፣ናይ ቀፃሊ ኣንፈታትን መደባትን ግዚያዊ ምምሕዳር ትግራይ ንምግምጋምን ንምዝታይን ኣብ ዝተዳለወ ናይ ላዕለዎት ሓለፍቲ ኣብያተ ዕዮ ክልል መድረኽ ተረኺቦም ኣብ ዝሃብዎ መብርህን ናይ ስራሕ መምርሕን እዩ፡፡

ፕረዚደንት ለ/ ጀነራል ታደሰ ወረደ ኣብቲ ንኽልተ መዓልቲ ዝወሰደ ከባቢያዊ፣ ሃገራዊን ክልላዊን ዝዳህሰሰ ገምጋም ተረኺቦም ኣብ ዝሃብዎ መብርህን ናይ ስራሕ መምርሕን፣ በብግዚኡ እናተለዋወጡ ኣብ ዝኸዱ ዘለዉ ፖለቲካዊ: ፀጥታን ደሕንነትን ምንቅስቓሳት ንትግራይ ዝፀልውሉ ግዳማዊ ኹነታት ብቀጥታ ይኹን ብተዘዋዋሪ ምህላዎም ብምሕባር፣ ነዚኦም ንምክልኻል እንተዘይሰሪሕና ናብ ውሽጥና ጉዳያት ልሒኾም ሓደጋ ዝኾንሉ ዕድል ሰፊሕ ምዃኑ ሓቢሮም።

ዝኾነ ሕብረተሰብ ዘጋጥሞ ሓደጋ ህልዉና ካብ ውሽጥን ግዳምን ዝብገስ ምዃኑ ዝገለፁ ፕረዚደንት ታደሰ፣ ኣብ ትግራይ እውን ክልቲኦም ምንጪታት ሓደጋ ህልውና ዝተኸሰተሉ ኣጋጣሚ ከምዘሎ ብምሕባር፣ በቲ ሓደ ገፅ ካብ ውሽጢ ልዑል ሓደጋ ተቓላዕነት፣ በቲ ካልእ ገፅ ድማ ካብ ግዳም ዝተበየነልና ፅንተትን ኮይኖም ንክልቲኦም ምንጪታት ሓደጋ ብሙሉእ ዓቕምና ምቅላስ ግድን ምዃኑ ኣብሪሆም።

ትግራይን ህዝባን ሕዚ’ውን ናይ ህልውና ሓደጋ ኣለዋ ዝበሉ ፕረዚደንት ታደሰ፤ ብምዃኑ ድማ ሕድ ሕድ ኣብያተ ዕዮ ዘለው ፀገማት ኣብ ምቕራፍ ዝነበሮ ግደ ብምግምጋም ንቐፃሊ እንታይ ክስራሕ ከም ዝግበኦ ከአንፍት ኣተሓሳስቦም። እቶም ፕረዚደንት ወሲኾም ሕድ ሕድ ኣብያተ ዕዮ፣ ኣብ ትግራይ ኣንፀላልዩ ዘሎ ናይ ህልውና ሓደጋ ኣብ ምቕልባስ እንታይ እጃም ከም ዝነበሮ ኣተሓሒዙ ኣፈፃፅማ ስርሑ ክግምግም ከም ዘለዎ ሓቢሮም፡፡

ሓለፍቲ ሕድሕድ ኣብያተ ዕዮ ጥቡቕ ኽትትል፣ ገምጋምን ድጋፍን ብምክያድ ኣብ ትሕቲኦም ዘለዉ ሰራሕተኛታትን መላእ ህዝብን ብምስታፍ፣ መደባት ግዝያዊ ምምሕዳር ትገራይ ተግባራዊ ክኾኑን ህዝቢ ዝደልዮ ኣገልግሎት ኣብ ግዚኡ ክረክብን ብልዑል ወነን መንፈስን ክረባረቡ ፕረዚደንት ጀነራል ታደሰ ወረደ ፀዊዖም። ሱር ዝሰደዱ ናይ ሰናይ ምምሕዳር ፀገማት፣ ካብ ግዘ ናብ ግዘ እናተጋደደ ዝኸድ ዘሎ ስራሕ ስእነትን ኢኮኖሚያዊ ቅልውላውን ቀጥታ ናይ ህልውና ሓደጋን ፈተናን እዮም ዝበሉ ፕረዚደንት ታደሰ፤ እዚኦም ብኣግባቡ እንተዘይፈትሺናዮም፣ ፍትሕን ርትዕን ኣስፊንና ጠንካራ ማእኸል ዘለዎ መንግስቲ እንተዘይፈጢርናን ናብ ዘይተደለየን ዘይንወፆን ፀገም ናይ ምእታውና ዕድል ሰፊሕ እዩ ኢሎም። ጠንካራን ማሕበራዊ ፍትሒ ዝዓሰላ ትግራይ ንምህናፅ ቅድሚ ኹሉ እቲ ዝተበላሸወ ስርዓት ካብ ምስትኽኻልን ጠንካራ ማእኸል ዘለዎ መንግስቲ ካብ ምፍጣርን ካሊእ ኣማራፂ ከም ዘየለ ድማ ገሊፆም።

ብወገን ትግራይ ውዕሊ ፕሪቶርያ ብኣግባቡ ንምፍፃም ልዑል ቁርፀኝነት ከምዘሎ ዝሓበሩ ፕረዚደንት ታደሰ፣ ዝተሰደደን ዝተመዛበለን ህዝብና ናብ መረበቱ ንምምላስን ላእላውነትና ንምውሓስን ናይ ቀዳምነት ቀዳምነት እንህቦ ጉዳይ እዩ ኢሎም። ብምዃኑ ድማ ዘይሓወየን ኣብ ስቓይን ዘሎ ህዝብና ናብ ዘይደልዮ ኣዕናዋይ ኩናት ከይኣቱን ደበና ኩናት ክንምቕንጣጥን ዝለዓለ ፃዕሪ ክንገብርን ሓላፍነት ወሲድና ክንሰርሕን ኢና ኢሎም። ይኹን እምበር ተወዓዓሊና ዝኾነ ፊደራል መንግስቲ እውን ተመሳሳሊ ፅኑዕ መርገፂ ክወስድን ዘይተመለሱ መሰረታዊ ጠለባትና ንምምላስ ክተግህን ፀዊዖም።

ብተወሳኺ ድማ ኣብ ውሽጥና ፖሎቲካዊ ኣፈላላያት ተፈጢሮም እዮም፣ ስለዚ እዞም ፀገማት ብምዕባጥን ዕሽሽ ብምባል ዘይኮነ፣ ከም ውህብ ብምውሳድ እቶም ፀገማት እንታይ ምዃኖም ኣለሊና መፍትሒ ብምሃብን እቲ ልሂቅ እውን ዘለውዎ ኣፈላላያት ብዝሰልጠነ መንገዲ ብልዝብ: ዘተን ምርድዳእን ክፈትሕ ዕድል ምፍጣርን ኣብ ጉዳይ ዓዱ ናብ ሓድነት ክመፅእ ምግባርን እዩ ክኾን ዘለዎ ኢሎም ፕረዚደንት ታደሰ ።

ኣብ መወዳእታ ንኽልተ መዓልታት ክካየድ ዝፀንሐ ናይ ሕሉፍ ርብዒ ዓመት ገምጋምን፣ ናይ ቀፃሊ ኣንፈታትን መደባትን ግዚያዊ ምምሕዳር ትግራይ በቢ ደረጅኡ ንታሕቲ ወሪዱ ምይይጥ ከም ዝግበረሉን ተገሊፁ፡፡

ቤት ፅሕፈት ፕረዝደንት
19 ሕዳር 2018 ዓ/ም

በመቐለ ከተማ የፈነዳው ቦምብ--------ትናንት ሀሙስ ህዳር 18/2018 ዓ.ም ከሌሊቱ 4:25 በመቐለ ዩኒቨርስቲ ዓዲ ሓቂ ግቢ አጥር ዙሪያ ከባድ የቦንብ ድምፅ ፍንዳታ ተሰምቶ ነበር። በቦ...
28/11/2025

በመቐለ ከተማ የፈነዳው ቦምብ
--------
ትናንት ሀሙስ ህዳር 18/2018 ዓ.ም ከሌሊቱ 4:25 በመቐለ ዩኒቨርስቲ ዓዲ ሓቂ ግቢ አጥር ዙሪያ ከባድ የቦንብ ድምፅ ፍንዳታ ተሰምቶ ነበር። በቦምብ ፍንዳታው በሰው ህይወት ያጋጠመ አደጋ የሌለ ሲሆን ፍንዳታው በነበረበት አቅራቢያ ያሉ ቤቶች መስተዋቶቻቸው መሰባበሩ ታውቋል:: ነዋሪዎች " ፍንዳታው በእጅ የተጣለ ቦምብ ሳይሆን ለረጅም ጊዜ ተቀብሮ የቆየ ፈንጅ ሊሆን ይችላል " የሚል አስተያየት አጋርተዋል። የመቐለ የሰላምና ፀጥታ ፅህፈት ቤት የትናንት ምሽት ፍንዳታው አስመልክቶ ለ104.4 ሬድዮ የመቐለ ኤፍ ኤም በሰጠው መረጃ ፍንዳታው ሆን ተብሎ ህዝብ ለማሸበር የተፈፀመ ነው ብሏል።

የድርጊቱን ፈፃሚዎች ማንነት እንደሚያጣራ የገለፀው ፅህፈት ቤቱ ፤ ህዝቡ ድርጊቱ እንዲያወግዘው አስገንዝቧል።

ፕረዚደንቱ ሃገር ጥለው ሸሹ-------በመፈንቅለ መንግስት ከስልጣን የወረዱት የጊኒ ቢሳው ፕሪዚዳንት ወደሴኔጋል መሸሻቸው ተገለጸ:: ሀገሪቱ በወታደራዊ መፈንቅለ መንግስት ስልጣን ላይ በወጡት...
28/11/2025

ፕረዚደንቱ ሃገር ጥለው ሸሹ
-------
በመፈንቅለ መንግስት ከስልጣን የወረዱት የጊኒ ቢሳው ፕሪዚዳንት ወደሴኔጋል መሸሻቸው ተገለጸ:: ሀገሪቱ በወታደራዊ መፈንቅለ መንግስት ስልጣን ላይ በወጡት ኃይሎች ታስረው የነበሩት ፕሬዚዳንት ኡማሮ ሲሴኮ ኢምባሎ ወደሴኔጋል መሸሻቸው የተገለጸው ፕሬዚዳንቱ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እነዲለቀቁ የአፍሪካ ሕብረት ጥሪ ካቀረበ ከሰዓታት በኋላ ነው።
እሁድ ዕለት በጊኒ ቢሳው ፕሬዚዳንታዊና ፓርላሜንታዊ ምርጫ ተካሄዶ ነበር። የምርጫው ውጤት ትናትንና ሐሙስ ሊገለጽ ቀጠሮ ተይዞለት የነበረ ሲሆን ሀገሪቱን ለሁለተኛ ዙር ለመምራት በመወዳደር ላይ የነበሩት ፕሬዚዳንት ኡማሮ ሲሴኮ ኢምባሎ እና ተቀናቃኛቸው ፈርናንዶ ዲያዝ ዳ ኮስታ ግን የምርጫው ውጤት ከመገለጹ በፊት ከማክሰኞ ጀምረው ሁለቱም በየፊናቸው ማሸነፋቸውን መግለጽ ጀመሩ።
በዚህ መካከል ነበር “ብጥብጥ እንዳይከሰትና ሁኔታውን ለማረጋጋት” በሚል በመሃል የገባው የሀገሪቱ ጦር ከአንድ ቀን በኋላ በተደራጁ ከፍተኛ የጦር መኮንኖች አማካኝነት ረቡዕ ዕለት መፈንቅለ መንግስት ማድረጉንና በኃይል ስልጣን መያዙን በሀገሪቱ ብሔራዊ የቴሌቪዥን ጣቢያ ቀርቦ የገለጸው። መፈንቅለ መንግስቱ የተመራው በራሳቸው በፕሬዚዳንት ኡማሮ ሲሴኮ ኢምባሎ የግል ጠባቂና የሃገሪቱ የፕሬዚዳንታዊ ዘብ ዋና አዛዥ በነበሩት ጀኔራል ዴኒስ ንካና ሲሆን ፕሬዚዳንት በመጨረሻም ፕሬዚዳንት ኢምባሎንም ተቀናቃኛቸው ፈርናንዶ ዲያዝንም በጥጥር ስር በማዋል ማሰሩንም አስታወቀ። መጨረሻም ከፍተኛ ወታደራዊ ቡድኑ በትናንትናው ዕለት ጀነራል ሆርታ ንታምን የሀገሪቱ መሪ አድርጎ መሾሙን የገለጸ ሲሆን እርሳቸውም በቀጣይ ለአንድ ዓመት የሀገሪቱ መሪ ሆነው ለማስተዳደር ቃለ መሃላ ፈጽመዋል። በዚህም በጊኒ ቢሳው በመፈንቅለ መንግስት በኃይል መንበረ ስልጣኑን በተቆጣጠሩት ወታደራዊ መኮንኖች ከረቡዕ ጀምሮ በእስር ላይ የቆዩት ፕሬዚዳንት ኡማሮ ሲሴኮ ኢምባሎ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲፈቱ የአፍሪካ ሕብረት ጥሪ ካቀረበ በኋላ በአሁኑ ሰዓት ተለቀው ወደሴኔጋል መሸሻቸው ታውቋል። የሀገሪቱ የቀድሞ ቅኝ ገዥ ፖርቱጋል፣ የምዕራብ አፍሪካ መንግሥታት ኢኮኖሚክ ኮሚሽን(በእንግሊዝኛ ምህጻሩ ኢኮዋስ)፣ የአፍሪካ ሕብረትና የተባበሩት መንግስታት በጊኒ ቢሳው የተካሄደው መፈንቅለ መንግስት የሀገሪቱን ሕገ መንግስት የሚጥስ መሆኑን በመግለጽ በሀገሪቱ ሕግና ስርዓት ወደነበረበት እንዲመለስና የሲቪል መንግስት እንዲቋቋም ሁሉም አካላት ወደንግግርና ውይይት እንዲገቡ በማሳሰብ ላይ ይገኛሉ። ከግማሽ በላይ የሚሆነው ሕዝቧ በአስከፊ ድህነት ውስጥ የሚኖርባት ትንሿ ምእራብ አፍሪካዊት ሀገር ጊኒ ቢሳው በአውሮፓውያን አቆጣጠር በ1974 ከፖርቹጋል ቅኝ ግዛት ነጻ ከወጣች ወዲህ ከዘጠኝ ጊዜ በላይ የተሳኩና ያልተሳኩ የመፈንቅለ መንግስት ሙከራዎች የተካሄዱባት ሀገር መሆኗንና ይህም ሀገሪቱን በማያቋርጥ የፖለቲካ ቀውስ ውስጥ እንድትሽከረከርና ከዓለማችን እጅግ ድሃ አገሮች መካከል አንዷ እንድትሆን ማድረጉን መረጃዎች ያመለክታሉ።

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ASER MEDIA posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to ASER MEDIA:

Share