13/05/2026
ነገ የጠናቀቃል - የመጨረሻ ቀን
---------
የባንክ ሂሳብን ከፋይዳ ቁጥር ጋር ለማስተሳሰር የተሰጠው የጊዜ ገደብ ነገ ይጠናቀቃል።
አዲስ አበባ ከተማን ጨምሮ በ27 ዋና ዋና ከተሞች ለሚገኙ የባንክ ደንበኞች፣ የባንክ ሂሳባቸውን ከፋይዳ (ብሔራዊ መታወቂያ) ቁጥራቸው ጋር የሚያስተሳስሩበት ጊዜ ገደብ ነገ ግንቦት 6 ቀን 2018 ዓ.ም ያበቃል።
ከተሞቹ ፦
- አዲስ አበባ
- ድሬዳዋ
- ሐረር
- ባህርዳር
- ጎንደር
- ደሴ
- ደብረብርሃን
- ኮምቦልቻ
- ሀዋሳ
- አርባ ምንጭ
- ወላይታ ሶዶ
- ሆሳዕና
- ወልቂጤ
- ሸገር
- ጅማ
- አዳማ
- ሻሸመኔ
- ቢሾፍቱ
- ባቱ
- አምቦ
- መቐለ
- አክሱም
- ዓዲግራት
- ጋምቤላ እና አሶሳ ናቸው።
ይህን ሊንክ id.et/connect በመጠቀም ካሉበት በመሆን ፋይዳ መታወቂያን ከባንክ ጋር ማስተሳሰር እንደሚቻል የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ገልጿል።
ብሔራዊ ባንክ እስከ ተሰጠው የጊዜ ገደብ ድረስ አካውንታቸውን ያላስተሳሰሩ ደንበኞች የባንክ ሂሳባቸው እንዲዘጋ ወይም እንዳይንቀሳቀስ (Dormant) የሚደረግ መሆኑን፣ ባንኮችም ይህንኑ ለደንበኞቻቸው እንዲያሳውቁ ትዕዛዝ ማስተላለፉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጾ ነበር።
ሂሳባቸው የተዘጋባቸው ደንበኞች ወደ ባንክ በመቅረብ የማስተሳሰር ሂደቱን በማከናወን ሂሳባቸውን መልሰው ማንቀሳቀስ ይችላሉ።
በሌሎች ከተሞች (ከተጠቀሱት ውጭ) ያሉ የባንክ ደንበኞች የባንክ ሒሳባቸውን እስከ ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ባለው የጊዜ ገደብ ማስተሳሰር ይጠበቅባቸዋል።
#ቲክቫህ ኢትዮጵያ
Welcome to the NID Home page