አዲስ ዓይን

አዲስ ዓይን አብረን በአዲስ አይን በአዲስ ፍቅር እንተያይ።

የኢነርጂ ፍላጎትን በዘላቂነት ለማሟላት የግል ዘርፉ ሚና ማጠናከር ይገባል-የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዴኤታ ሱልጣን ወሊ (ዶ/ር) የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በኢትዮጵያ ያለውን የኢነርጂ ፍላጎት ...
28/10/2025

የኢነርጂ ፍላጎትን በዘላቂነት ለማሟላት የግል ዘርፉ ሚና ማጠናከር ይገባል-የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዴኤታ ሱልጣን ወሊ (ዶ/ር)

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በኢትዮጵያ ያለውን የኢነርጂ ፍላጎት በዘላቂነት ለማሟላት የግል ዘርፉ ሚና የላቀ በመሆኑ ተሳትፎውን ማጠናከር እንደሚገባ ተገለጸ፡፡

ሁለተኛው የውሀና ኢነርጂ ሳምንት አውደ ርዕይ እና ፓናል ከትናንት ጀምሮ በሳይንስ ሙዚየም እየተካሄደ ይገኛል።
በዛሬው ዕለት በነበረ የፓናል ውይይት ላይ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዴኤታ ሱልጣን ወሊ (ዶ/ር) እንዳሉት፤ ለሀገር ኢኮኖሚ እድገት ኢነርጂ ወሣኝነት አለው።

ቀጣይነት ያለው የኢነርጂ አቅርቦት ሀገራችን ለያዘችው ብልፅግና የጀርባ አጥንት ነው ብለዋል።

በኢትዮጵያ አብዛኛው ህብረተሠብ የማገዶ ተጠቃሚ በመሆኑ የእፅዋቶች መጠን እንዲቀንስ፣ የአየር ንብረት ለውጥ ጫና እንዲጨምር እና የአፈር መሸርሸር እንዲባባስ ማድረጉን ገልጸዋል።

ይህም የግብርና ምርታማነት ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ በማስከተል የምግብ ዋስትና የማረጋገጥ ሂደትን ከማደናቀፍ ባለፈ በጭስ ምክንያት የበሽታ ተጋላጭነትን እንደሚጨምር ተናግረዋል።

ከለውጡ በኋላ የኢነርጂ አቅርቦት እየተሻሻለ መምጣቱን የገለጹት ሚኒስትር ዴኤታው፤ ፍላጎቱን ለማሟላት መስራት እንደሚያስፈልግ አመልክተዋል።

በመሆኑም የፖሊሲ ክለሳ በማድረግ የግል ዘርፉን ማሳተፍ ይገባል ማለታቸውን ከሚኒስቴሩ የተገኘው መረጃ ይጠቁማል፡፡ የኢነርጂ ፍላጎትን በዘላቂነት ለማሟላት የግል ዘርፉ ሚና ማጠናከር ይገባል-የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዴኤታ ሱልጣን ወሊ (ዶ/ር)

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በኢትዮጵያ ያለውን የኢነርጂ ፍላጎት በዘላቂነት ለማሟላት የግል ዘርፉ ሚና የላቀ በመሆኑ ተሳትፎውን ማጠናከር እንደሚገባ ተገለጸ፡፡

ሁለተኛው የውሀና ኢነርጂ ሳምንት አውደ ርዕይ እና ፓናል ከትናንት ጀምሮ በሳይንስ ሙዚየም እየተካሄደ ይገኛል።
በዛሬው ዕለት በነበረ የፓናል ውይይት ላይ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዴኤታ ሱልጣን ወሊ (ዶ/ር) እንዳሉት፤ ለሀገር ኢኮኖሚ እድገት ኢነርጂ ወሣኝነት አለው።

ቀጣይነት ያለው የኢነርጂ አቅርቦት ሀገራችን ለያዘችው ብልፅግና የጀርባ አጥንት ነው ብለዋል።

በኢትዮጵያ አብዛኛው ህብረተሠብ የማገዶ ተጠቃሚ በመሆኑ የእፅዋቶች መጠን እንዲቀንስ፣ የአየር ንብረት ለውጥ ጫና እንዲጨምር እና የአፈር መሸርሸር እንዲባባስ ማድረጉን ገልጸዋል።

ይህም የግብርና ምርታማነት ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ በማስከተል የምግብ ዋስትና የማረጋገጥ ሂደትን ከማደናቀፍ ባለፈ በጭስ ምክንያት የበሽታ ተጋላጭነትን እንደሚጨምር ተናግረዋል።

ከለውጡ በኋላ የኢነርጂ አቅርቦት እየተሻሻለ መምጣቱን የገለጹት ሚኒስትር ዴኤታው፤ ፍላጎቱን ለማሟላት መስራት እንደሚያስፈልግ አመልክተዋል።

በመሆኑም የፖሊሲ ክለሳ በማድረግ የግል ዘርፉን ማሳተፍ ይገባል ማለታቸውን ከሚኒስቴሩ የተገኘው መረጃ ይጠቁማል፡፡
Sheger Times Media

የሥነ ጽሑፍ ሳሎን አንደኛ ዓመት!ኦክቶበር 2024 በጋዜጠኛና ጸሐፊ ሶስና አሸናፊና ገዛኽኝ መኮንን ተመስርቶ ከመላው ዓለም የተገኙ አባላት እንዲሁም እንደ አዳም ረታ ፍቅረማርቆስ ደስታ ያሉ ...
26/10/2025

የሥነ ጽሑፍ ሳሎን አንደኛ ዓመት!

ኦክቶበር 2024 በጋዜጠኛና ጸሐፊ ሶስና አሸናፊና ገዛኽኝ መኮንን ተመስርቶ ከመላው ዓለም የተገኙ አባላት እንዲሁም እንደ አዳም ረታ ፍቅረማርቆስ ደስታ ያሉ ምርጥ ደራሲያን የሚገኙበት በሀገራችን ሥነ ጽሑፍ ታሪክ በአይነቱም ሆነ በይዘትና አቀራረቡ የተለየ አለምአቀፋዊ የሥነ ጽሑፍ ማኅበረሰብ መድረክ ነው።

መድረኩ የተመሰረተበት አንደኛ ዓመት የፊታችን እሁድ ማለትም November 2,2025 ቀን ከ 11:00am EST በዙም ይከበራል።

በክብር እንግድነት አንጋፋዋ አርቲስትና በዲያስፖራ ለኪነ ጥበብ እድገት ዋጋ የከፈለችው ዓለምፀሐይ ወዳጆና በሀገር ቤት ለንባብ መስፋፋት ትልቅ አስተዋጽኦ ያበረከተው የቀድሞ የወመዘክር ዳይሬክተር ይኩኖአምላክ መዝገቡ ይገኛሉ።

በዕለቱ ለአንደኛ አመቱ የተዘጋጀው የአባላት ሥራዎች የተካተቱበት መጽሐፍም ይመረቃል።

ታዋቂዋ ድምፃዊ ሜላት መንገሻ ከቶሮንቶ ድምፃዊ በላይ መልሴ ከለንደን ሙዚቃ ያቀርቡልናል።

መድረኩን ጋዜጠኛና ፀሐፊ ገዛኽኝ መኮንን ከቶሮንቶ ደራሲ ትዕግስት ሳሙኤል ከአምስተርዳም ይመሩታል!

ሁላችሁም ተጋብዛችኋል!

Sheger Times Media

ልቀት ኮሌጅ በመጀመሪያ ዲግሪ እና በደረጃ 4 ያስተማራቸውን ተማሪዎች በሐገር ፍቅር ቴአትር አስመርቋል። ከ2010 ዓ.ም ጀምሮ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ተማሪዎችን ሲያስተምር የቆየው ልቀት...
26/10/2025

ልቀት ኮሌጅ በመጀመሪያ ዲግሪ እና በደረጃ 4 ያስተማራቸውን ተማሪዎች በሐገር ፍቅር ቴአትር አስመርቋል።

ከ2010 ዓ.ም ጀምሮ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ተማሪዎችን ሲያስተምር የቆየው ልቀት ኮሌጅ ዘንድሮም በፊልም ጥበባት፣ በማኔጅመንት፣ በማርኬቲንግ፣ በአካውንቲንግና በሌሎች ዘርፎች ያስተማራቸውን የ2017 ዓ.ም ተመራቂ ተማሪዎችን አስመርቋል።

ጥቅምት 15 ቀን 2018 ዓ.ም በሐገር ፍቅር ቴአትር በተካሄደው የኮሌጁ የምርቃት ሥነ–ስርዓት ላይ የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ሚንስትር ዴኤታ ክቡር ረ/ፕ ነብዩ ባዩ፣ የአዲስ አበባ ባህል፣ ኪነ–ኪነጥበብና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ሒሩት ካሳው፣ ፕሮፌሰር ተከተል ዮሐንስ የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ዳይሬክተር እና ሌሎች የክብር እንግዶች ተገኝተው ተማሪዎችን መርቀዋል።

ልቀት ኮሌጅ ከዚህ በፊት ሲያደርግ እንደነበረው ዘንድሮም በኢትዮጵያ የኪነ–ጥበብ ኢንዱስትሪ የጎላ አበርክቶ ላደረጉ ሁለት ባለሙያዎች ዕውቅና እና የክብር ሽልማት አበርክቷል። በዚህም መሰረት ለረጅም ዓመታት በተለይ በትወና ብቃቱ የሚታወቀው ኪሮስ ኃ/ስላሴና ዕውቁ ሲኒማቶግራፈርና ዳይሬክተር ሰውመሆን ይስማው (ሶሚክ) በልቀት ኮሌጅ የ2017 ዓ.ም ተመራቂ ተማሪዎች የምረቃ ሥነ–ስርዓት ላይ ዕውቅና እና የኮሌጁን የክብር ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።

የዕለቱ የክብር እንግዶች ለተመራቂዎች መልዕክቶችን ያስተላለፉ ሲሆን የክብር ሽልማቱን የሰጡት የባህልና ሚኒስቴር ሚንስተር ዴኤታ ክቡር ረ/ፕ ነብዩ ባዬ ለተመራቂዎች ባስተላለፉት የመዝጊያ ንግግር ተመራቂዎች ከሚለብሱት ጋዋን ጋር በድህነት ያስተማሯቸውን እናት አባቶቻችውን እንዲያስቡ በሀቀኝነት ለመስራት ቃል እንዲገቡና ትምህርት መቼም እንዳያቆሙ ያሳሰቡ ሲሆን "ሃገራችውን የምትወዱበት፣ ለሃገር የምትሰሩበት ሙያ" ያድርግላችሁ ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

የፕሮግራም ቀንና ቦታ ለውጥ*************************" ወደ ማዶ " ኮሜዲ ትያትር ዛሬ ቅዳሜ በኬንያ - ናይሮቢ እንደሚታይ መገለፁ ይታወሳል።ይሁንና ናይሮቢና አካባቢው የሚገኙ ...
25/10/2025

የፕሮግራም ቀንና ቦታ ለውጥ
*************************
" ወደ ማዶ " ኮሜዲ ትያትር ዛሬ ቅዳሜ በኬንያ - ናይሮቢ እንደሚታይ መገለፁ ይታወሳል።

ይሁንና ናይሮቢና አካባቢው የሚገኙ በርካታ ኢትዮጵያውያን የቦታና የፕሮግራሙ ቀን እንዲጨመርላቸው በጠየቁት መሰረት ዛሬ ይታይ የነበረው ትያትር ለቀጣዩ ሳምንት ቅዳሜና እሁድ CISS Tsavo Hall Diamond Plaza one parkLandን በመጨመር ፦

ቅዳሜ:- Nov 1/25 በCISS Tsavo Hall

እሁድ:- Nov 2/25 Diamond Plaza one parkLand የፕሮግራም ለውጥ ተደርጎ የሚታይ መሆኑን በአክብሮት እንገልፃለን።

12 ቱ እንግዶች ዘውትር ቅዳሜ በ8፡00 ሰዓት በኢትዩጵያ ብሄራዊ ትያትር ቤት  የአንድ ሰው ህይወት ጠፍቷል የአንድ ሰው ህይወት በእጃችሁ ለይ ነዉ፡፡ በአሜሪካዊው ታዋቂ ፀሃፊ ሬግናልድ ሮዝ...
23/10/2025

12 ቱ እንግዶች ዘውትር ቅዳሜ በ8፡00 ሰዓት በኢትዩጵያ ብሄራዊ ትያትር ቤት

የአንድ ሰው ህይወት ጠፍቷል የአንድ ሰው ህይወት በእጃችሁ ለይ ነዉ፡፡
በአሜሪካዊው ታዋቂ ፀሃፊ ሬግናልድ ሮዝ ‘’12 angry Men’’ በሚል የተፃፈው እና ከ29 ሀገራት በላይ በሎካል ቋንቋዎች ተትርጉሞ ለመድረክ የበቃው የአሜሪካ ካላሲክ ፕለይ በአዲስ ተስፋ ተርጓሚነት በብሄራዊ ትያትር
ፕሮዲዩሰርነት ዘውትር ቅዳሜ በ8፡00 ሰዐት ይቀርባል፡፡

ቅዳሜያችሁን ከአስራ ሁለቱ እንግዶች ጋር በኢትዮጵያ ብሄራዊ ትያትር ቤት ያድርጉ ፡፡ ፍትህ ፣ጭፍን ጥላቻ ፣ምክንያታዊነት እና ቸለልተኝነት በአንድ ጠረጰዛ ዙሪያ ተቀምጠዋል፡፡

" ወደ ማዶ " - በኬንያ ናይሮቢ************************  KICC HALL የፊታችን ቅዳሜ (October 25/25 ) 5:00 PM    የእኛ እና የትያትር ወዳጆች በሙሉ   በ...
21/10/2025

" ወደ ማዶ " - በኬንያ ናይሮቢ
************************
KICC HALL የፊታችን ቅዳሜ (October 25/25 ) 5:00 PM

የእኛ እና የትያትር ወዳጆች በሙሉ በማድረግ ብታስተዋውቁልን ።

ልቀት ኮሌጅ ተማሪዎቹን ሊያስመርቅ ነው ።***********************************        በፊልም ትምህርት በዲግሪ ደረጃ የሚያስተምረው ብቸኛው የግል ኮሌጅ የሆነው ልቀት ...
15/10/2025

ልቀት ኮሌጅ ተማሪዎቹን ሊያስመርቅ ነው ።
***********************************
በፊልም ትምህርት በዲግሪ ደረጃ የሚያስተምረው ብቸኛው የግል ኮሌጅ የሆነው ልቀት ኮሌጅ በተለያዩ መርሐግብሮች ያሰተማራቸውን ወደ 400 የሚሆኑ ተማሪዎቹን ቅዳሜ ጥቅምት 15/18 በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር ያስመርቃል ። መምህራን ፣ ተማሪዎችና ቤተሰቦቻቸው እንኳን ደስ አላችሁ ።

እባካችሁ አግዙኝጓደኛዬ የስራ ባልደረባዬ ባያዬ ታሞብናል። እናግዘው።በሀይሉ ዘለቀ በትያትር መምህርነት ከ15 አመት በላይ ያገለገለ ተወዳጅ መምህር እና በተለያዩ ፊልሞችና ተከታታይ ድራማዎች ...
14/10/2025

እባካችሁ አግዙኝ

ጓደኛዬ የስራ ባልደረባዬ ባያዬ ታሞብናል። እናግዘው።

በሀይሉ ዘለቀ በትያትር መምህርነት ከ15 አመት በላይ ያገለገለ ተወዳጅ መምህር እና በተለያዩ ፊልሞችና ተከታታይ ድራማዎች ሲተውን የምናቀው አመለ ሸጋው ባለሞያ ነው። ለዚህ አብረውት የሰሩት የሞያ ባልደረቦቹ እና ተማሪዎቹ ምስክር ናቸው። በአሁኑ ሰአት የልብ ህመም ገጥሞት እየተሰቃየ ሲሆን ላለፉት ወራቶች በህክምና ላይ ይገኛል። ሆኖም የነበረውን ገንዘብ በህክምና የጨረሰ በመሆኑ የሁላችንም እገዛ ያስፈልገዋል። የቻልነውን እንርዳው።

ዳግማዊት ፋንታሁን
ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
1000542247731
Mahlet Solomon

  በቦታ ርቀት ለተገደባችሁ  #በቀጥታ ይተላለፋል! ነገ ሞቅ ያለ ልብስ ደርባችሁ በአካልና በኦንላይን ይታደሙ!   ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ሥላሴ የሥነ ጥበባት ማዕከል የግዕዝ ቋንቋ በትምህ...
10/10/2025

በቦታ ርቀት ለተገደባችሁ #በቀጥታ ይተላለፋል!
ነገ ሞቅ ያለ ልብስ ደርባችሁ በአካልና በኦንላይን ይታደሙ!



ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ሥላሴ የሥነ ጥበባት ማዕከል የግዕዝ ቋንቋ በትምህርት ሥርዓት ውስጥ በሚል ርዕስ በፕሮፌሰር ዘላለም ልየው አወያይነት በዶ/ር በድሉ ዋቅጅራ እና በይኩኖ አምላክ መዝገቡ መካከል ሙያዊ ውይይት ያካሄዳል፡፡
ዝግጅቱ ቅዳሜ ጥቅምት 1፣ 2018 ዓ.ም ከ8 ሰዓት ጀምሮ በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ቅጥር ግቢ ውስጥ ይቀርባል፡፡

(በብዙዎቻችሁ ጥያቄ መሰረት ውይይቱን በአካል እና በአማራጭ መከታተያ መንገድ እንድትታደሙ ጋብዘናል፤ ውይይቱ በቀጥታ ከZoom በተጨማሪ የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ የYouTube ቻናል እና የፌስቡክ ገጽ ላይ በቀጥታ ይተላለፋል፡፡)

በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ የብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ሥላሴ የሥነ ጥበባት ማዕከል በዝግጅቱ እንዲታደሙ ግበዣውን ያቀርባል፡፡

የዝግጅቱ ቦታ፡ በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ የብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ሥላሴ የሥነ ጥበባት ማዕከል ቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል አካባቢ (በንግድ ባንክ ጉለሌ ቅርንጫፍ በኩል ገባ ብሎ)፡፡

Topic: The EAS Public discussion on “The Geez language in educational system”
Date: October 11, 2025
Time: 2:00 P.M.-5:00 P.M.
Meeting ID: 845 8019 2226
Passcode: 570957
Link: https://us06web.zoom.us/j/84580192226?pwd=bfRsMfkSp1YsfMFccKHUcnCLAbbqK5.1https://us06web.zoom.us/j/84580192226?pwd=bfRsMfkSp1YsfMFccKHUcnCLAbbqK5.1

ጎግል ማፕ፡ https://maps.app.goo.gl/yb1LFT7PDTwLUP217

ወላጆች ተጠንቀቁ!
09/10/2025

ወላጆች ተጠንቀቁ!

አመኒም ሶሊዩሽንስ ዓለም አቀፍ የአርቲፊሻል ኢንተሊጀንስ (AI) ስልጠና ምዝገባ ጀመረ::ዋሽንግተን ዲሲ – Oct 06 2025 – አመኒም ሶሊዩሽንስ፣ በትውልደ ኢትዮጵያውያን በአሜሪካ የተቋቋ...
06/10/2025

አመኒም ሶሊዩሽንስ ዓለም አቀፍ የአርቲፊሻል ኢንተሊጀንስ (AI) ስልጠና ምዝገባ ጀመረ::

ዋሽንግተን ዲሲ – Oct 06 2025 – አመኒም ሶሊዩሽንስ፣ በትውልደ ኢትዮጵያውያን በአሜሪካ የተቋቋመ የስልጠና ተቋም ነው
ይህ ተቋም ለቴክኖሎጂ ዕውቀት ልቀት የሚታትር ሲሆን የቀደመ የቴክኖሎጂ መስክ ልምድ ለሌላቸው ሠልጣኞችም አጫጭር ስልጠናዎችን በማይክሮሶፍት 365፣ SharePoint እና Power Platform ለረጅም ጊዜ ስልጠና በመስጠት በርካቶችን ለቁም ነገር አብቅቷል። አሁንም ለ23ኛ ዙር ምዝገባ ጀምሯል::

ይህ የታመነ ተቋም 22 ዙሮችን በስኬት በማስተማር ታላቅ ልምድን ያገኘው አሜኒም ሶሊዩሽንስ ተማሪዎቹን በማስመረቅ በመንግስት፣ በኮርፖሬት፣ በትምህርትና በማህበረሰብ ድርጅቶች የሚሰሩ ሙያዊ ሰዎችን ማብቃት ችሏል።
ብዙዎቹም የክህሎታቸውን ደረጃ ከፍ በማድረግ የሥራ ዕድሎቻቸውን ማሳደግ ችለዋል ።

ተቋሙ የMicrosoft 365፣ SharePoint እና Power Platform ስልጠናዎቹ በተጨማሪም የመጀመሪያ ዙር ዓለም አቀፍ AI ስልጠና እየጀመረ መሆኑን አስታውቋል ።

አዲሱ የAI ስልጠናም የዘመኑን ዲጂታል ኢኮኖሚ የሚያስፈልጉ ክህሎቶችን ለመገንባት የተዘጋጀ ነው።

እነዚህ ዓለም ዓቀፍ ስልጠናዎች በየትኝውም ቦታ ሆነው online የስራ ባለቤት ያደርጎታል ምክንያቱም

• ማይክሮሶፍት 365 (የቀድሞው Office 365) አሁን በአለም ዙሪያ ከ3.7 ሚሊዮን በላይ ድርጅቶች ውስጥ ጥቅም ላይ ውሏል።

• ማይክሮሶፍት 365 - 345 ሚሊዮን Active ተጠቃሚዎች አሉት (የ2023 መረጃ)

• SharePoint ብቻ 200 ሚሊዮን+ ወርሃዊ Active ተጠቃሚዎች አሉት

• የማይክሮሶፍት ፓወር ፕላትፎርም በፍጥነት እያደገ ነው፡ በቅርብ ጊዜ ሪፖርቶች እንደተገለጸው ከ33 ሚሊዮን በላይ ወርሃዊ active ተጠቃሚዎች አሉት።

እነዚህ ቁጥሮች የትምህርቱን ሚዛኑን ያሳያሉ:: እነዚህ platforms ዘመናዊ ንግድን፣ መንግስትን፣ ትምህርትን፣ ጤናን እና ሌሎችን የሚያንቀሳቅሱ ናቸው።

በኢትዮጵያ ፣ በኬንያ፣ በአሮፖም ፣ በአሜሪካም ወይም ከየትኛውም ዓለም ክፍል እንደሆኑ በonline ተሳትፎ መማር ይችላሉ።

ያላቸው ቦታ ውስን ስለሆነ ፈጥነው ይመዝገቡ::

ለመመዝገብና ለበለጠ መረጃ፡

240 338 6273/ 301 640 0907
www.amenimsolutions.com

On Media:

https://amharic.voanews.com/a/7826544.html

https://www.facebook.com/share/1Cunhc8qeC/?mibextid=wwXIfr

መረጃው የ አብነት ተዋበ ነው

በግብፅ የቀረበው ውንጀላ መሰረተ ቢስ ነው - ኢትዮጵያ—ኢትዮጵያ በሱዳን የተከሰተውን ጎርፍ ከታላቁ የሕዳሴ ግድብ ጋር በማያያዝ ግብጽ ያቀረበችውን መሰረተ ቢስ ውንጀላ ውድቅ አደረገች፡፡ግብጽ...
04/10/2025

በግብፅ የቀረበው ውንጀላ መሰረተ ቢስ ነው - ኢትዮጵያ

ኢትዮጵያ በሱዳን የተከሰተውን ጎርፍ ከታላቁ የሕዳሴ ግድብ ጋር በማያያዝ ግብጽ ያቀረበችውን መሰረተ ቢስ ውንጀላ ውድቅ አደረገች፡፡

ግብጽ ከቀናት በፊት በውሃ እና መስኖ ሚኒስቴሯ በኩል ባወጣችው መግለጫ፥ ሰሞኑን በሱዳን የተከሰተው ጎርፍ በግድቡ የአስተዳደር ችግር የተፈጠረ ነው የሚል ውንጀላ አቅርባለች፡፡

የኢትዮጵያ ውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከግብጽ በኩል የቀረበው ውንጀላ መሰረተ ቢስና ከእውነታው ጋር የሚጣረስ መሆኑን ገልጾ፥ ግድቡ ጎርፍ ከማስከተል ይልቅ የጎርፍ አደጋን መቀነስ እንዳስቻለ አስገንዝቧል፡፡

ሚኒስቴሩ በመግለጫው ኢትዮጵያ የኃይል ማመንጫ ግድቦችን የመገንባትና የውሃ ፍሰታቸውን የማስተዳደር ልምድ እንዳላት ጠቅሶ፥ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ መገንባት በሱዳን እና ግብጽ ሊከሰት የሚችለውን ከፍተኛ ጎርፍ ማስቀረቱን አስረድቷል፡፡

በክረምት ወራት በኢትዮጵያ ከፍተኛ ቦታዎች የጣለው ዝናብ በሱዳንና ግብፅ በሰውና ንብረት ላይ ከፍተኛ ውድመት ሊያስከትል የሚችል ጎርፍ ይከሰት እንደነበር ገልጿል፡፡

የሱዳን የግብርና እና መስኖ ሚኒስቴር በሀገሪቱ ለተከሰተው ጎርፍ የመሰረተ ልማት ችግርን ጨምሮ ምክንያት ያላቸውን ጉዳዮች በግልጽ አስቀምጧል፡፡

ነገር ግን ግብጽ ከዚህ በተቃራኒ የጎርፍ አደጋውን ከታላቁ የሕዳሴ ግድብ ጋር በማገናኘት ዓለም አቀፉን ማህበረሰብ ለማሳሳት ሀሰተኛ ክስ ኢትዮጵያ ላይ ማቅረቧን የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር በመግለጫው አመልክቷል፡፡

ግብጽ ለጎረቤት ሀገራት ተቆርቋሪ በመምሰል ያወጣችውን የሀሰት ውንጀላና የስም ማጥፋት መግለጫ ሙሉ በሙሉ ውድቅ እንደሆነ ሚኒስቴሩ አረጋግጧል፡፡

https://www.youtube.com/c/ShegerTimesMedia
Sheger Times Media

Address

Adisayen@gmail. Com
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when አዲስ ዓይን posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share