አዲስ ዓይን

አዲስ ዓይን አብረን በአዲስ አይን በአዲስ ፍቅር እንተያይ።

 #እሁድ 8:00 ሰዓት በሀገር ፍቅር ቴአትር - " ደጋግ ሰይጣኖች "**************************************************( ኮሜዲ ቴአትር )ደራሲ - ውድነህ ክፍሌ...
07/06/2025

#እሁድ 8:00 ሰዓት በሀገር ፍቅር ቴአትር - " ደጋግ ሰይጣኖች "
**************************************************

( ኮሜዲ ቴአትር )
ደራሲ - ውድነህ ክፍሌ
አዘጋጅ - ተፈራ ወርቁ

 #ዛሬየ" ደጋግ ሰይጣኖች " ቀን ነው ፤ ሀገር ፍቅር ቴአትር!!!!********************************************( ኮሜዲ ቴአትር )ደራሲ - ውድነህ ክፍሌአዘጋጅ - ...
02/06/2025

#ዛሬ
የ" ደጋግ ሰይጣኖች " ቀን ነው ፤ ሀገር ፍቅር ቴአትር!!!!
********************************************
( ኮሜዲ ቴአትር )
ደራሲ - ውድነህ ክፍሌ
አዘጋጅ - ተፈራ ወርቁ

መግቢያ ካርድ የደረሳችሁ በሙሉ 11:00 ሰዓት እንገናኝ ።

#ኑ ።

ተስፋ የኪነጥበብ ኢንተርፕራይዝ

ሂወት ታደሰ Hiwot Tadesse    ባለፉት አምስት ዓመታት የልደት ቀኗን ምክንያት በማድረግ ብዙ የበጎ አድራዎችን ሰርታለች። በተለይም ደግሞ እግዚአብሔር አግዟት ሞታቸውን እየተጠባበቁ ያ...
02/06/2025

ሂወት ታደሰ Hiwot Tadesse ባለፉት አምስት ዓመታት የልደት ቀኗን ምክንያት በማድረግ ብዙ የበጎ አድራዎችን ሰርታለች። በተለይም ደግሞ እግዚአብሔር አግዟት ሞታቸውን እየተጠባበቁ ያሉ በርካታ ልብ ህሙማን ህፃናት ልባቸው ተጠግኖ ተስፋቸው እንዲለመልም ምክንያት ሆናለች። ሶሻል ሚዲያን በመጠቀም ለምታደርገው የበጎ አድራጎት ስራ እውን መሆን ባለቤቷ አንተነህ ከበደም ሊመሰገን ይገባል።
እንኳን ተወለድሽ ሂዊ ! እግዚያብሄር ብዙዎች ቤት ተስፋ፤ ደስታ፤ ሳቅ... እንዲሆን ምክንያት አድርጎሻል።

የዛሬ ሳምንት ግንቦት 23 2017፣208 ባለሙያዎችን በአንድ መድረክ ይገናኛሉየሕይወት ታሪካቸው በአንድ መፅሐፍ ላይ የተሰነደላቸው ባለሙያዎች በብሔራዊ ቴአትር በልዩ ሁኔታ ሊከበሩ ነው፡፡ ቅ...
30/05/2025

የዛሬ ሳምንት ግንቦት 23 2017፣208 ባለሙያዎችን በአንድ መድረክ ይገናኛሉ

የሕይወት ታሪካቸው በአንድ መፅሐፍ ላይ የተሰነደላቸው ባለሙያዎች በብሔራዊ ቴአትር በልዩ ሁኔታ ሊከበሩ ነው፡፡

ቅዳሜ ግንቦት 23 2017 ዓ.ም በሚኖረው መርሀ ግብር ታሪካቸው ዘመን ተሻጋሪ በሚሆን መልኩ የተከተበላቸው የጥበብ፣ የፅሁፍና የሚድያ ሰዎች ከነ ቤተሰቦቻቸው በዚህ ታላቅ ሥነ ሥርዐት ላይ እንደሚታደሙ ይጠበቃል።

በዕለቱ የመፅሀፍ ዳሰሳ ፣አዝናኝ ወግ፣ ዲስኩር ፣ትዝታ ቀስቃሽ ዶክመንተሪ፣ በቫዮሊንየሚቀርብ ሙዚቃም ይኖራል።

616 ገፅ የፈጀውን "መዝገበ አእምሮ" የተሰኘውን በኢንሳይክሎፒዲያ ቅርፅ የተሠናዳ መፅሀፍ ያዘጋጀውና ያሳተመው የተወዳጅ ሚድያና ኮምዩኒኬሽን መሥራች ዕዝራ እጅጉ ሲሆን ሥራውም ከ 3 ዐመት በላይ ወስዶበታል።

"መዝገበ አእምሮ" ፣በ 1970ዎቹና በ1980ዎቹ በ1990ዎቹ ላይ የነበሩ የጥበብና የሚድያ ሰዎችን የበለጠ ትኩረት ሰጥቶ ታሪካቸውን የሰነደ ሲሆን ሥራውን በባለሙያ ዕይታ እንዲቃኝ ለማድረግም 21አባላት ያሉት የመማክርት ቡድን ተዋቅሮ ሥራውን ማከናወን ተችሏል፡፡

"መዝገበ አእምሮ " ቅፅ 1ሐምሌ 30 2014 ዓ.ም በይፋ የምረቃ መርሀ- ግብር ተደርጎለት የተመረቀ መፅሐፍ ሲሆን 180 የሚድያ ሰዎችም የሕይወት ታሪካቸው ተካቶበታል፡፡

አሁን የሚመረቀው "መዝገበ አእምሮ" የመፅሀፉ የንድፍ ዝግጅት በፕሮፌሽናል ግራፊክ ዲዛይነር ዘሪሁን አሰፋ የተሰናዳ ሲሆን ንድፉን የሚያብራራ ርዕሰ- አንቀፅም መፅሀፉ ላይ ሰፍሯል።

መዝገበ አእምሮ ላይ 27 የሕይወት ታሪክ አዘጋጆች፣3አርታዒያን የተሳተፉ ሲሆን የይዘት አማካሪዋም ቤርሳቤህ ጌቴ ናት፡፡
ስለ ኪነ ጥበብ እና የሚድያ ሰዎች መረጃ ለማግኘት መዝገበ አእምሮ ሁነኛ አማራጭ መሆኑን በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጋዜጠኝነት ምሁራን የመሰከሩ ሲሆን ፕሮጀክቱንም ለማገዝ የሚመለከታቸው አካላት ከጎን መሆን እንዳለባቸው ተመልክቷል፡፡

"መዝገበ አእምሮ" ላይ ያሉት ታሪኮችን የበለጠ ተደራሽ ለማድረግ የስነዳ ሥራው በተወዳጅ ሚድያ የዲጂታል አማራጮች ማለትም tewedajewikipedia.com እና tewedajemedia የፌስ ቡክ ገፅ ላይ እንዲጫኑ ተደርጓል።

ቅዳሜ ግንቦት 23 2017ዓ.ም በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር ከጠዋቱ 3 ሰዐት በሚሰናዳው የባለሙያዎች የትውውቅ እና የምረቃ መርሀ -ግብር ላይ ታላላቅ እንግዶች ታድመው መፅሀፉን እንደሚመርቁ ይጠበቃል።

የመዝገበ አእምሮ ቅፅ 2 ሕትመትና ዝግጅት የተሳካ እንዲሆን የኢትዮጵያ አእምሯዊ ንብረት ባለሥልጣን፣ዳሸን ባንክ ፣ ታሜ ሶል ኮምዩኒኬሽን፣ቶቶት የባህል ምግብ ቤትና ዓለምፀሀይ ሹሩባ ድጋፍ አድርገዋል፡፡

እንዴት ያለ ነገር ነው! የሦስት ልጆች እናት ድንገት እንደዋዛ ከቤት እንደወጣች አልተመለሰችም። ...ዛሬ አራተኛ ቀኗ!"እባካችኹ ለየሚዲያው አድርሱልኝ!" ይሏችኋል በከባድ ኀዘን ላይ የሚገኙ...
30/05/2025

እንዴት ያለ ነገር ነው! የሦስት ልጆች እናት ድንገት እንደዋዛ ከቤት እንደወጣች አልተመለሰችም። ...ዛሬ አራተኛ ቀኗ!

"እባካችኹ ለየሚዲያው አድርሱልኝ!" ይሏችኋል በከባድ ኀዘን ላይ የሚገኙት ሦስት ልጆቿ እና እናቷ!

ብዙዎችን ሲያመሰግን ኖሮ አንዳችንም በልኩ ያላመሰገነው ሰው***************************************************          በኢትዮጵያ ትያትር ታሪክ ውስጥ ከብ...
30/05/2025

ብዙዎችን ሲያመሰግን ኖሮ አንዳችንም በልኩ ያላመሰገነው ሰው
***************************************************
በኢትዮጵያ ትያትር ታሪክ ውስጥ ከብዙ ትልልቅ ባለውለታ ዎቻችን ጎን በዚሀ ዘመን በበቂ ያልተነገረለት ሰው ተፈራ ወርቁ ነው ። እኛም እንደ ጓደኛ ብቻ እያየነው ሳንዘምርለት ቀረን ። ይሁንና ስራው እየዘመረለት አለ ።

ላለፉት 25 ዓመታት ከኢትዮጵያ ኪነጥበብ ( በተለይም ከሙዚቃና ትያትር ) ጎን አለ ። ብዙዎችን ከጥበብ ስራቸው ጋር ለአደባባይ አብቅቷቸዋል ። ለእኔም " ሩብ ጉዳይ " እና " ሰዓት እላፊ " የተባሉ ተውኔቶቼን ለሕዝብ አቅርቦልኛል ። በ " ሩብ ጉዳይ " ትያትርን ከተቀመጠበት አቧራውን አራግፎ ሁላችንንም እርካታ እንድናገኝበት ፣ ገንዘብ እንድንሰራበት ፣ በታሪክ እንድንደምቅበት ያደረገን ባለውለታችን ነው ተፈራ ወርቁ ። ቁጭታችንን የተወጣልን ሰው ነው ። ከትያትር ቤቶች ስንገፋ መሸሻችን ነው ።

ካሜራ ባልቀረጻቸውና ለአደባባይ ባልበቁ መልካምነቶቹ ስመጥር ነው ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር " በጀት አጠረኝ " ብሎ ያቆመውን " የቴዎድሮስ ራዕይ " ትያትር ተፈራ ወርቁ ባይሆን ማንም ለመድረክ አያበቃውም ። የፊታችን ሰኞ ግንቦት 25/17 በሀገር ፍቅር ቴአትር በልዩ ፕሮግራም ለሕዝብ የሚያደርሰው የውድነህ ክፍሌ ድርሰት የሆነው " ደጋግ ሰይጣኖች " ከትጋቶቹ አንዱ ነው ። የትያትሩ አዘጋጅና ፕሮዲዩሰር ነው ተፈራ ። ሁሌም ብርታቱን ፣ መልካምነቱንና አይታክቴነቱን በልባችን የምናመሰግነው ተፈራ ወርቁ በአደባባይ የሚመሰገንበት ቀን ይመጣል ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ ።

ሰኞ በ11:00 ሰዓት ሀገር ፍቅር ቴአትር እንገናኝ ።
Tewodros Teklearegay

ነገ ይመጣል እንጂ አይደርስም!በኢትዮጵያ የመጀመሪያው "ኢትዮ ዲጂታል ምስጋና ፌስት" ሊካሄድ ነው።እኔም የማመሰግነው ሰው አለኝ፤በግል ማንን ማመስገን ይፈልጋሉ?እንደ ማህበረሰብ ቢመሰገን የሚ...
30/05/2025

ነገ ይመጣል እንጂ አይደርስም!

በኢትዮጵያ የመጀመሪያው "ኢትዮ ዲጂታል ምስጋና ፌስት" ሊካሄድ ነው።

እኔም የማመሰግነው ሰው አለኝ፤

በግል ማንን ማመስገን ይፈልጋሉ?

እንደ ማህበረሰብ ቢመሰገን የሚሉትስ ማን አለ?

"ነገ ነገ" በማለት እስከዛሬ ሳላመሰግን አለፍኩኝ ብለው ይቆጫሉ?

ላለፉት አራት አመታት በተለያዩ ዘርፎች ሲያመሰግን የቆየው የ"ጣፋጭ ህይወት ምስጋና" አሁን ደግሞ ሁላችንም በጋራ የምናመሰግናቸውን ግለሰቦች ይበልጥ የምናሳትፍበት እድል ይዞ መጥቷል።

ለአምስት ሰዓታት፤ በልዩ የሶሻል ሚዲያ ቀጥታ ስርጭቶች (Live) ቆይታ ቤተሰብ፣ ማህበረሰብ፣ የስራ ባልደረባ፣ ሊመሰገን ይገባዋል/ይገባታል የምንላቸውን ሁሉ በልዩ የምስጋና ፌስቲቫል ከልብ እያመሰገንን እና እየተመሰጋገንን እንቆያለን ::

ግንቦት 24 ከቀኑ 10:00 ጀምሮ በሁሉም የማህበራዊ ሚዲያ ትስስር ገጾች ላይ በቀጥታ ስርጭት እንገናኝ።

እኔም የማመሰግነው ሰው አለኝ!

ኢላን መስክ ከትራምፕ አስተዳደር ራሱን ማግለሉን አስታውቋል።መስክ በሺዎች የሚቆጠሩ የፌዴራል መንግሥት ሠራተኞች የተባረሩበት የዶጅ ንቅናቄ ኃላፊ ነበር። ዶጅ እየተባለ የሚጠራው የአሜሪካ የብ...
29/05/2025

ኢላን መስክ ከትራምፕ አስተዳደር ራሱን ማግለሉን አስታውቋል።

መስክ በሺዎች የሚቆጠሩ የፌዴራል መንግሥት ሠራተኞች የተባረሩበት የዶጅ ንቅናቄ ኃላፊ ነበር።

ዶጅ እየተባለ የሚጠራው የአሜሪካ የብክንት ቅነሳ መሥሪያ ቤት ትራምፕ ሥልጣን ላይ ከወጡ ጀምሮ ሲያገለግል ቆይቷል።

መስክ በማኅበራዊ ሚድያው ኤክስ በኩል በለቀቀው መግለጫ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕን አመስግኗል።

ቢቢሲ እንደተረዳው ዋይት ሐውስ ካለፈው ረቡዕ ጀምሮ ኢላን መስክ የመንግሥት ልዩ መልዕክተኛ የተሰኘ መለያው እንዲነሳ አድርጓል።

የዓለማችን ቱጃሩ ሰው ዶጅን እየመራ እንደማይቆይ እና ኃላፊነቱ ጊዜያዊ እንደሆነ ሲያስታውቅ ቆይቷል።

"ፕሬዝደንት ትራምፕ ብክነትን እንድቀንስ ዕድሉን ስለሰጡኝ አመሰግናለሁ። ነገር ግን ዶጅ ተጠናክሮ ይቀጥላል" ብሏል።

ደቡብ አፍሪካ የተወለደው ጉምቱ የቴክኖሎጂ ሰው "ልዩ የመንግሥት ሠራተኛ" የሚል ኃላፊነት ተሰጥቶት በዓመት 130 ቀናት እንዲሠራ ተፈቅዶለት ነበር።

ትራምፕ ሥልጣን ላይ ከወጡ ጀምሮ ባለፈው ጊዜ ስሌት መሠረት በያዝነው የፈረንጆቹ ግንቦት ወር መገባደጃ 130 ቀናት ይሞሉታል።

ነገር ግን መስክ በትራምፕ የበጀት ረቂቅ አዋጅ "እንደተከፋ" ባስታወቀ ማግስት ኃላፊነቱን መልቀቁ አነጋጋሪ ሆኗል።

የትራምፕ አዲሱ ረቂቅ አዋጅ በትሪሊ የን ዶላሮች የሚቆጠር የግብር እፎይታ እና የመከላከያ በጀት እንዲጨምር የሚያበረታታ ነው።

መስክ የትራምፕ አስተዳደርን ሲቀላቀል 2 ትሪሊየን ዶላር ብክነት እቀንሳለሁ ብሎ ነበር የተነሳው። ነገር ግን ይህን ቁጥር ወደ 150 ቢሊዮን ዝቅ አድርጎታል።

በዶጅ ምክንያት ከ2.3 ሚሊዮን የፌዴራል ሠራተኞች መካከል 260 ሺህ የሚሆኑት ከሥራ ገበታቸው ተሰናብተዋል።

መስክ ባለፈው ሚያዚያ ከመንግሥት ኃላፊነት ገሸሽ ብሎ ትኩረቱን የግል ኩባንያዎቹ ላይ እንደሚያደርግ አስታውቆ ነበር።

ኢላን መስክ የዋይት ሐውስ ልዩ ሠራተኛ ሳለ የቴስላ መኪና ሽያጭ 13 በመቶ አሽቆልቁሏል። የቴስላ የአክሲዮን ገበያም 45 በመቶ ወርዶ እንደነበር ይታወሳል።

Via Ethio fm

ፖስፖርትና ሊብሬ ጠፋብኝ ።**********************ሰኞ በ18/09/17   ከ11:00 ስዓት በኋላ ቦሌ ሻላ ( አቢሲኒያ ባንክ ) አካባቢ ባላወቅሁት ሁኔታ ፖስፖርት ( ቪዛ የተመታ...
28/05/2025

ፖስፖርትና ሊብሬ ጠፋብኝ ።
**********************
ሰኞ በ18/09/17 ከ11:00 ስዓት በኋላ ቦሌ ሻላ ( አቢሲኒያ ባንክ ) አካባቢ ባላወቅሁት ሁኔታ ፖስፖርት ( ቪዛ የተመታበት ) እና የመኪና ሊብሬ ስለጠፋብኝ እባካችሁ ካገኛችሁልኝ ወረታውን እከፍላለሁ ።

ወንድማችሁ ሙሉጌታ ተገኘ
ብታገኙት # 0945966296አሳውቁኝ ።

በማድረግ መልዕክቱን አዳርሱልኝ ።

ትላንት ከምሽቱ 8:00 አካባቢ የሜትር ታክሲ ሹፌሮች ዲምቱ አደባባይ ለስራ በቆሙበት ጫት የጫነ አይሱዙ ከኋላ መጥቶ በመግጨቱ በአደጋው ኪሩቤል የተባለዉ እዛዉ ህይወቱ ሲያልፍ ሌሎቹ 2ቱ ደሞ...
28/05/2025

ትላንት ከምሽቱ 8:00 አካባቢ የሜትር ታክሲ ሹፌሮች ዲምቱ አደባባይ ለስራ በቆሙበት ጫት የጫነ አይሱዙ ከኋላ መጥቶ በመግጨቱ በአደጋው ኪሩቤል የተባለዉ እዛዉ ህይወቱ ሲያልፍ ሌሎቹ 2ቱ ደሞ ቤጂንግ ሆስፒታል ከገቡ በኋላ አርፈዋል። ቀብራቸዉ ነገ ይፈጸማል። ለቤተሰቦቻቸው መፅናናትን እንመኛለን ።

24/05/2025
በቅርብ ቀን!
23/05/2025

በቅርብ ቀን!

Address

Adisayen@gmail. Com
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when አዲስ ዓይን posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share